በናይጀሪያ ጥቃት ያስፋፋው የቦኮ ሀራም ቡድን
ባለፈው ሳምንት በናይጀሪያ መዲና አቡዣ በአንድ የፖሊስ ጽህፈት ቤት ላይ በተጣለው የቦምብ ጥቃት ከሰላሳ የሚበልጥ ሰው ሲገደል ብዙዎችም ቆስለዋል፤ በንብረትም ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶዋል።
ባለፈው ሳምንት በናይጀሪያ መዲና አቡዣ በአንድ የፖሊስ ጽህፈት ቤት ላይ በተጣለው የቦምብ ጥቃት ከሰላሳ የሚበልጥ ሰው ሲገደል ብዙዎችም ቆስለዋል፤ በንብረትም ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶዋል።
የዩናይትድ ስቴትስ ዉጪ ጉዳይ ሚኒስቴር በዘንድሮዉ ሎተሪ እጣ የወጣላቸዉን የሃያ-ሁለት ሺሕ ሰዎች ዉጤት ሠርዟል።
ጋዜጠኞች ከባሕር ዳር ከተማ ወጣ ብለዉ የተሰሩትን ጢስ አባይ አንድና ሁለት የተሰኙትን ግድቦች ተዘዋዉረዉ ጎብኝተዋል
አንድ ወጣት ነዉ አሉ! በገጠር ፍየሎቹን ይዞ በጠዋት ለግጦሽ ሳር ፍለጋ ሲወጣ አንዲት ልጃገረድ የዉሃ እንስራዋን ይዛ ዉሃ ልትቀዳ ወደ ወንዝ ስትወርድ ያገኛታል። ታድያ ዉበትዋን አይቶ ድንግጥ ያለዉ ወጣት እረኛ እንዲ ገጥመላት አሉ!
በሐዋሳ የሚንቀሳቀሱ ትኩረታቸዉን በኤች አይቪ ቫይረስ ላይ አድርገዉ የሚሠሩ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጥምረት ፈጥረዉ መንቀሳቀስ መጀመራቸዉን አመለከቱ።
የአሜሪካኑ ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ እስከሚቀጥለዉ የአዉሮጳዉያን 2012ዓ,ም ድረስ ሰላሳ ሶስት ሺህ የአሜሪካን ወታደሮች ከአፍጋኒስታን እንደሚወጡ አስታወቁ።
ፓን ትልቁን አለም አቀፍ ድርጅት የመምራት ብቃትና ቅልጥፍናቸዉ ብዙ እያስተቻቸዉ ነዉ።በተለይ ለአፍሪቃ መሥራት የሚገባቸዉን ያሕል አልሰሩም የሚል ወቀሳ ይሰነዘርባቸዋል።ያም ሆኖ በድጋሚ ለመመረጥ ከሐያላኑ መንግሥታት ሙሉ ድጋፍ ነበር ያገኙት።
ካለፉት በርካታ ዓመታት አንስቶ በኢትዮጵያ በምግባረ ሠናይ ተግባር ተሰማርቶ የሚገኘዉ ሰዎች ለሰዎች ወይም በጀርመንኛዉ Menschen für Menschen የተሰኘዉ ድርጅት መሥራችና የበላይ ጠባቂ ካርል ሃይንዝ በም አዲስ አበባ ላይ በስማቸዉ ጎዳናና አደባባይ ተሰየመላቸዉ።
(DW) — የፍትህ ጋዜጣ አምደኛ ርዕዮት ዓለሙ በጸጥታ ኃይሎች ታሰረች። ዓርብ ዓርብ የሚወጣው ሳምንታዊ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ አቶ ተመስገን ደሳለኝ ዛሬ ለዶይቸ ቬለ እንዳረጋገጡት፡ ትናንት የመታሰር ዕጣ የገጠማት አምደኛ ወይዘሪት ርዕዩት ዛሬ ከቀትር በኋላ ፍርድ ቤት ቀርባ ነበር። የአውራ አምባ …
የዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት ሲ ፒ ጄይ ኢትዮጵያ በርካታ ጋዜጠኞች ለስደት ከሚዳረጉባቸው አምስት የዓለም ሀገሮች ውስጥ አንዷ መሆንዋን አስታወቀ።
„ a Tunisian Girl“ «ቱኒዚያዊቷ ልጃገረድ» የተሰኘ አምደ መረብ መስራች ሊና ቤን ሜህኒ ዛሬ በዶቸ ቬለ የአለም አቀፍ የመገናኛ ብዙኸን መድረክ ላይ ተሸላሚ ሆናለች።
የሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሞሐመድ አብዱላሂ አህመድ ሥልጣናቸውን መልቀቃቸውን ትናንት አስታውቀዋል ።
የጀርመን መንግስት ለመጀመሪያ ጊዜ ጠቅላላ የአፍሪቃን አህጉር የሚያጠቃልል የአፍሪቃ ጽንሰ-ሀሳብ የተባለ አዲስ መርሃግብር አወጣ።
የኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባለፈው ማክሰኞ በአሸባሪነት ከወነጀላቸው የፖለቲካ ድርጆች ሶስቱ ውንጀላውን ነቀፉ ።
በብሪታንያ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን በሚቀጥለዉ ሳምንት መጨረሻ ታላቅ የስፖርትና ባህላዊ ዝግጅቶችን በማቀናበር ከተለያዩ የአዉሮጳ አገሮች የሚመጡ ኢትዮጵያዉያንን ለማስተናገድ በዝግጅት ላይ ይገኛሉ።
በቅርቡ በህጋዊ መንገድ ተዋውለው ለሥራ ወደ ሳውዲ አረቢያ የሄዱ ኢትዮጵያውያን ሪያድ እስር ቤት ውስጥ በመሰቃየት ላይ መሆናቸውን አስታወቁ ።
ኢትዮጵያን ጨምሮ በአፍሪቃ የተስፋፋው ሰፋፊ መሬትን በተለያየ መንገድ ለውጭ ባለሃብቶች መስጠት ለሃገራቱ ምጣኔ ሃብት እድገት አንዳችም ፋይዳ እንደሌለው ተገለፀ ።
ባለፉት ጥቂት ቀናት ፣ በዓለም ዙሪያ በተለያዩ አካባቢዎች የምድር ነውጥና እሳተ ገሞራ መከሠታቸውን ልብ ብለን ይሆናል። በአፍሪቃው ቀንድም እንዲሁ! ምድራችን፤ የብሱና ውቅያኖሱ ቀዝቀዝ ይበል እንጂ፤ ውስጥ አካልዋ ግን ገና ያልበረደ የእሳት ሉል መሆኑ የታወቀ ነው።
እ.ጎ.አ ከ2002 ዓም አንስቶ ቱርክን የሚመሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ታይፕ ኤርዶሀን በሃገሪቱ አብይ የሚባሉ በርካታ ለውጦችን ማስመዝገባቸው ደጋግመው ለመመረጣቸው ዋነኛው ምክንያት ነው ።
የኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ አምስት የፖለቲካ ድርጅቶችን በአሸባሪነት ስም ፈርጆ ውሳኔ አሳልፎዋል።
የሊቢያ አማፅያን ብሔራዊ የሽግግር ምክርቤት ለሊቢያ ቀውስ ፖለቲካዊ መፍትሄ ለመሻት ከሚጥሩ ወገኖች ጋር እየተደራደረ መሆኑን አስታወቀ ።
በሊቢያ፡ በየመን እና በሶርያ የቀጠለው ውዝግብ እና የህዝብ ዓመጽ በሰሜን አፍሪቃዊቱ ሀገር ሞሮኮ የሚካሄደውን የተቃውሞ ንቅናቄ ከዓለም መገናኛ ብዙኃን ትኩረት እንዲርቅ አድርጓል።
የፊታችን ዕሁድ የሚካሄደው የቱርክ ምርጫ ለሀገሪቱ ቀጣይ ጉዞ ወሳኝ እንደሆነ እየተነገረ ነው። ይህም ከሆነ ፓርቲው ህገመንግስቱ ላይ ለውጥ የማድረግ አቅም ይኖረዋል ማለት ነው።
ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ወይዘሮ ሒላሪ ክልተን ሰላሳኛዉን አመት ምክንያት በማድረግ ባሥተላለፉት መልዕክት የበሽታዉን ሰለቦችና ቤተ-ሠቦቻቸዉን ለመርዳት የሚመደበዉ ገንዘብ መጨመር እንዳለበት አሳስበዋል።
የሰሜን አትላንቲክ የጋራ መከላከያ ኪዳን፥ ኔቶ የሊቢያ መሪ ሙአመር ጋዳፊን መንግስት ለማስወገድ በሀገሪቱ የጀመረውን ያየር ጥቃት እንደሚቀጥል አስታወቀ። የኔቶ ዋና ጸሀፊ አንደርስ ፎኽ ራስሙሰን ጋዳፊ እንዳበቃላቸውም ገልጸዋል።
በእጅ ቦምብ ፍንዳታ የተጎዱት የየመን ፕሬዚደንት አብዱላ ሳሌህ ለህክምና ከጥቂት ቀናት ወዲህ ሳውዲ ዐረቢያ ይገኛሉ፤
የፌደራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ዛሬ ለምክር ቤት ባቀረበዉ የ2002 በጀት አፈፃፀም ዘገባ፤ የሂሳብ ምርመራ ካደረገባቸዉ 143 መስሪያ ቤቶች፤ በአብዛኞቹ ከፍተኛ የገንዘብ ብክነት መገኘቱን አመለከተ።
በምድራችን የአየር ንብረት ላይና በሌላውም ተጽእኖ ሊኖራቸው ስለሚችል በኅዋ ስለሚከሠቱ አንዳንድ ነገሮች ፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ የበለጠ መረጃ ለማግኘት ሳይንስና ሥነ-ቴክኒክ መበጀቱ የሚያራጥር አይደለም።
ኢትዮጵያን ጨምሮ በእድገት ወደኃላ የቀሩ አገራት ዘላቂ የምጣኔ ሀብት መዋቅር እንዲዘረጉ ተጠየቁ ።
ሟቾች መንግሥትን የሚቃወመዉ የአል-አሕመር ጎሳ አባላት፥ ገዳዮች የመንግሥት ነጥሎ ገዳዮች ይሆኑ-ይሆን?ወይስ በተቃራኒዉ።የሕመር ታጣቂዎች የመንግሥትን ደጋፊዎች ገድለዉ ጥለዋቸዉ-ይሆን? ሌላም ብዙ ጥያቄ ይዥጎደጎዳል።እስካሁን የሚታወቀዉ ግን አንዱም አለመታወቁ ነዉ።
አብዛኛዉ ዓለም ደንቡ የዜግነትና የፖለቲካዊ መብቶችን የሚያስከብር መሆኑን የመገንዘቡን ያክል ለምጣኔ ሐብታዊ፥ ለማሕበራዊና ለባሕላዊ መብቶች መከበር የሚሰጠዉን ዋስትና ብዙም አላጤነዉም።
በጀርመን እስከአሁን በይፋ የ22 ሰዎችን ህይወት እንደቀጠፈ እየተነገረ ነዉ፤ ጥሬ አትክልት በመመገብ እንደሚከሰት የተነገረለት በጀርመንኛዉ ኤሄክ፤ የተሰኘዉ ተህዋሲ።
እስከ ዛሬ 10 ዓመት ድረስ የጀርመን የአቶም ኃይል ማመንጫዎች ሙሉ በሙሉ ሥራቸውን እንዲያቆሙ የወሰነው የጀርመን መንግሥት በዚህ ሳምንት ዝርዝር አተገባበሩን ይፋ አድርጓል ።
የሊቢያ መሪ ሙአመር ኧል ጋዳፊ ጦር ኃይላት ከዓማጽያኑ ጋ ውጊያ በቀጠሉበት እና የሰሜን አትላንቲክ የጋራ መከላከያ ኪዳን ኔቶም በጋዳፊ ኃይላት አንጻር ጥቃቱን ባጠናከረበት ባሁኑ ጊዜ በኔቶ ጽህፈት ቤት ውስጥ የኪዳኑ አባል ሀገራትን ተሳትፎ በተመለከተ ውይይቱ ቀጥሎዋል።
ኮሎኔል ተስፋይ ወልደስላሴ በኢትዮጵያ በቀድሞው ወታደራዊ ሶሻሊስታዊ መንግስት ዘመን የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚንስትር ሆነው አገልግለዋል።
የጀርመን መራሂተ መንግስት አንጌላ ሜርክል በዩኤስ አሜሪካ ልዩ ጉብኝት በማድረግ ላይ ይገኛሉ።
በየመን ዛሬ በቤተመንስቱ ላይ በተፈጸመ የሮኬት ጥቃት ፕሬዝዳንት አብደላ ሳሌህን ጨምሮ የተወሰኑ ባለስልጣናት ቆስለዋል።
ግጭቱ ዛሬ ጋብ ብሎ ነዉ የዋለዉ።ተማሪዎቹ ለግጭቱ መቀስቀስ መንስኤ ያሏቸዉ ወገኖች እንዲጠየቁና የታሰሩ ባልንጀሮቻቸዉ እንዲፈቱ ጠይቀዋል።የድሬዳዋዉ ወኪላችን ዩሐንስ ገብረ እግዚአብሔር የዩኒቨርስቲዉን ሐላፊዎች በስልክ ለማነጋገር ሞክሮ ነበር
በመጀመሪያ መምህር ነበረ፤ በኋላ የረጅም ዘመን የራዲዮ ጋዜጠኛ! ድሮ በብሥራተ ወንጌል ራዲዮ ጣቢያ ዓለምን እንይ! የሚል ተወዳጅ ዝግጅት ነበረው።
የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ አውጭ ግንባር በምህፃሩ ኦብነግ ከሁለት ሳምንት በፊት ኦጋዴን ውስጥ መታገታቸው የተነገረውን ሁለት የዓለም ምግብ ድርጅት ሰራተኞች ማግኘቱን አስታወቀ ።
ዴን ኻግ ውስጥ ሲጠበቁ ብዙ ጊዜ አልፎዋል፡ የቀድሞው የቦዝንያ ሰርቢያውያን ዋና ጦር አዛዥ፡ ራትኮ ምላዲች።
የኢትዮጽያ ህዝባዊ አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባር – ኢህአዴግ በኢትዮጵያ ህዝብ ድጋፍ በኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም ይመራ የነበረውን ወታደራዊ ሶሻሊስታዊ የደርግ ስርአት አስወግዶ ስልጣን ከያዘ ዛሬ ልክ ሀያ ዓመቱን ደፈነ።
መንግሥት ፤ ነጋዴዎች በተጨማሪ ለእሴት ታክስ አሰባሰብ እንዲመዘገቡ ካዘዘ ወዲህ የተመዘገቡትም፤ ያልተመዘገቡትም እሴት ታክሱን ጨምረው በማስከፈላቸው የድሬዳዋ ከተማ ፣
ይሕ ልሳን ተዘጋ።አማኑኤል በረከት ነገ-አይጠብቀንም፥ ትናንት እንጂ ዛሬም የለም።ከአርባ ዓመታት በላይ በተለያዩ ጣቢያዎች በራዲዮ ጋዜጠኝነት ያገለገለዉ በጣሙን በስፖርት ጋዜጠኝነኝ እዉቅናን ያተረፈዉ አማኑኤል በረከት በቃ።አረፈ።ስልሳ ዘጠኝ አመቱ ነበር።ማንተጋፍቶት ስለሺ አጭር ዘገባ አለዉ።
ፕሬዚዳንት አሊ አብደላ ሳሌህ፣ ከሥልጣን መንበር ከወረዱ ፤ የመን በእርስ-በርስ ጦርነት እንደምትማቅቅና የአል ቓኢዳ መፈንጫ እንደምትሆን ከመለፈፍ ካለመቦዘናቸውም፤
ደቡብ ሱዳን ከሰሜን ሱዳን ክፍል በመገንጠል ነጻነትዋን በይፋ ልታዉጅ ጥቂት ሳምንታት ሲቀራት፣ በነዳጅ ዘይት ሃብት በታደለችዉ የአብዪይ አካባቢ የባለቤትነት ጉዳይ ሌላ አዲስ ጦርነት እንዳይቀሰቅስ አስግቶአል።
ትናንት በየመኑ ፕሬዝደንት እና በተቃዋሚዎቻቸዉ መካከል ይፈረማል ተብሎ የተጠበቀዉ የስልጣን ሽግግር ስምምነት ከሽፏል።
ግዙፍን የአለም ገንዘብ ድርጅት ላለፉት ሰወስት አመታት ከላይ ለመዘወር ያበቃቸዉ የእድገት፥ዉጤት-ስኬት፥ ቀና መንገድ አጉዞ አጉዞ ፕሬዝዳትነትን አጎናፅፎ ከኤሊሴ ቤተ-መንግሥት ዶላቸዋል ነበር የብዙዎች-ግምት-ተስፋ። የሳቸዉ ጥረትም።ቁል ቁል ተሽቀንጥረዉ ዘብጥያ አረፉ
ኢትዮጵያ ከስምንት ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ በህገወጥ መንገድ ማጣቷን አንድ ጥናት አመለከተ።
ባለፈው ሳምንት አርብ በፀሀይ ሀይል ብቻ የምትንቀሳቀሰው አይሮፕላን በአውሮፓ የሙከራ በረራዋን በሚገባ ተወጥታለች።