የጎንደር ከተማ የታክሲ ሹፌሮች አዲሱን የትራፊክ የቅጣት ደንብ በመቃወም የስራ ማቆም አድማ መምታታቸውን የፍኖተ ነፃነት ምንጮች ጠቆሙ፡፡ የፍኖተ ነፃነት ምንጮች እንደጠቆሙት የተቃውሞው መነሻ ምክንያት ሶስት ተከታታ ቅታት የተጣለበት ሹፌር ለስድርት ወር እንዳያሽከረክር የሚከለክል ደንብ በመውጣቱ ነው፡፡ የታክሲ ባለንብረቶችም የታሪፍ ማስተካከያ አለመደረጉን በመቃወም የታክሲ ሹፌሮቹን ተቀላቅለዋል፡፡ የከተማው አስተዳደር ባለስልጣናት ሾፌሮቹና ባለንብረቶቹ ወኪል ልከው እንዲነጋገሩ ጠይቀዋል፤ ሆኖም […]

ዳኛ –የማረሚያ ቤቱ ፖሊስን ‹‹እዚሁ ልትለቃቸው ትችላለህ›› የማረሚያ ቤቱ ፖሊስ ‹‹አለቃቸውም›› አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የኢትዮጵያ ቴሌቭዥንና ሬዲዩ ድርጅት ባቀረበው “አኬልዳማ” በተሰነ ዶክመንተሪ ፊልም ስሜን አጥፍቷል በማለት ያቀረበው የፍትሀ ብሄር ክስ በአስር ቀናት ውስጥ ውሳኔ ማግኘት እንደሚገባው አዋጅ እንደሚደነግግ የተረዱት አቶ አስራት ጣሴ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት የፍትህ መጓተት ከፍርድ ቤቱ ፍትህ ማግኘት እንደማይቻል ማሳያ ነው […]

ማኅበረ ቅዱሳን ለሦስተኛ ጊዜ ያዘጋጀው የአብነት መምህራን ጉባኤ መታገዱን መግለጫዎችና ዜናዎች እያሳወቁን ነው፡፡ የአብነት መምህራን በቤተ ክህነቱ ‹ለአበል የተረሱ፣ ለሹመት የሚታወሱ› ሆነዋል፡፡ ስብሰባ፣ ዐውደ ጥናት፣ ሥልጠና፣ ጉዞ፣ ሲሆን እነርሱን የሚያስታውስ የለም፡፡ የጵጵስና ሹመት ሲመጣ ግን ‹ከእገሌ ይህንን ከእገሌም ያንን ተማርኩ› የሚለው ይበዛል፡፡ የቤተ ክርስቲያኒቱም ሆነ የሀገሪቱ ሀገራዊ ዕውቀት ማዕከል መሆናቸው ተረስቶ ይህንን ያህል ዘመን ሲኖሩ ‹ቤት ልሥራላቸው፣ ዘር ልዝራላቸው› ያለ ቤተ ክህነት አልገጠመንም፡፡ እንዲያውም እነ መምሬ በዕውቀቱን እነ አያ ብሩ እየቀደሟቸው ቦታ ቦታውን ይዘውታል፡፡
ማኅበረ ቅዱሳን ለውጥ አምጭ ሥራ ከሠራባቸው ዘርፎች አንዱ የአብነት ትምህርት ቤቶች መሆናቸውን እስላም ከክርስቲያኑ የሚመሰክረው ነው፡፡ ለአብነት መምህራን ደመወዝ ከመክፈል ቤት እስከ መሥራት፣ ትምህርት ቤቶቻቸውን ከመገንባት ለተማሪዎቹ ቁሳቁስ እስከ ማቅረብ፣ የጤና መርሐ ግብሮችን ከማከናወን እስከ ካሪኩለም ቀረጻ ሰፊ ሥራዎች ተሠርተዋል፡፡

ለአንድ ሊቅ ከቁሳዊ ነገር በላይ መንፈሳዊ ነገሩ ይበልጥበታል፡፡ ጽድቁ፣ ክብሩ፣ ስሙ፣ መዓርጉ፣ ታሪኩ ታላቅ ነገሮች ናቸው፡፡ ከቁሳዊው ድጋፍም ሞራላዊው ድጋፍ ታላቅ ነው፡፡ እነዚህ የአብነት መምህራን ቦታና ዐቅም ወስኗቸው፣ እድሜና አሠራር ገድቧቸው እንዳይቀሩ፤ እርስ በርስ ተገናኝተው እንዲመክሩ፤ አሠራራቸውን እንዲያዘምኑ፣ ዕውቀት እንዲከፋፈሉ፣ ልምድ እንዲለዋወጡ፣ ህልውናቸውን እንዲተዋወቁ፣ ወጥ አሠራር እንዲዘረጉ መደረጉ የሚያስመርቅ እንጂ የሚያስረግም አልነበረም፡፡

በርግጥ ይህንን መሰል ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸውን ሥራዎች ለመሥራት ተገቢ የሆኑ ቢሮክራሲያዊ መንገዶችን አሟጦ መጓዝ፤ ማወቅ ያለበት እንዲያውቅ፣ መስማት ያለበትም እንዲሰማ ማደረግ፣ ማሳመንና ማግባባት፣ በአሠራሩና በዓላማው ላይ ቀደም ብሎ ከሚመለከታቸው ጋር መወያየት ያስፈልጋል፡፡ አንድን ታላቅ መኪና የአንዲት ብሎን መላላትና መውለቅ እንደምታስቆመው ሁሉ የጥቂት ቤተ ክህነታዊ አሠራሮች አለመጠበቅ ታላቁን ዓላማ ሊያደናቅፈው እንደሚችል ማወቅ ተገቢ ነው፡፡ ትናንት እንዲህ ስለሠራን ነው ማለቱ ብዙም አያዋጣም፡፡ ሁልጊዜ ፋሲካ የለምና፡፡

በዚያም ሆነ በዚህ ግን የአብነት መምህራኑ መሰባሰብና በሞያቸውና አገልግሎታቸው ዙሪያ መምከር የሚጠቅመው ማንን እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ሲሆን ቤተ ክህነቱ ራሱ አስቦ መሥራት ነበረበት፤ ካልሆነም ደግሞ የሚሠሩትን ማትጋትና ማገዝ ይገባው ነበር፡፡ ሁለቱም ግን አልሆኑም፡፡ ማኅበሩ በቤተ ክህነቱ አሠራር ያላከናወናቸው ነገሮች አሉ ከተባለ እንዲያከናውን ማድረግ እንጂ አገር አቋርጠው ወንበር አጥፈው የመጡትን ሊቃውንት ማንገላታት የሚገባ አልነበረም፡፡ ጉባኤው ተስተካክሎ በመካሄዱ የምትጠቀመው ቤተ ክርስቲያን ናት ባለ መደረጉ ግን ከሰይጣን በቀር ተጠቃሚው ማነው

በሌላ በኩልም ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና የፓትርያርኩ ጽ/ቤት በጉዳዩ አፈታት ላይ የሄዱበት መንገድም አስገራሚ፣ አስተዛዛቢም ነው፡፡ የማኅበሩ ጽ/ቤት ከቤተ ክህነቱ በ50 ሜትር ርቀት ላይ መኖሩ እየታወቀ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁም ሆኑ ፓትርያርኩ ያንን ሁሉ የደብዳቤ ውርጅብኝ ማዝነብ ለምን አስፈለጋቸው? ደግሞስ ጉዳዩ የውስጥ ጉዳይ ነው፤ ለእነዚያ ሁሉ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች የመጻፉ ዓላማው ምንድን ነው? አስፈላጊ ከሆነ ልጆቹን ጠርቶ ‹ጉባኤውን አቁሙ› ማለት ይቻል የለም እንዴ? ደግሞስ መጀመሪያውኑ ሳያጣሩ መጻፍ፣ ከዚያ ደግሞ የመሻሪያ ደብዳቤ መጻፍ፣ አከታትሎ ደግሞ የመሻሪያ መሻሪያ መጻፍ የቤተ ክህነቱን ተቋማዊ ኪሣራ ከማሳየት በቀር ሌላ ምን ያሳያል?

የዛሬን አያድርገውና የፓትርያርክ ደብዳቤኮ የእምነት መግለጫ፣ የሚጠቀስ፣ በክብር የሚቀመጥ፣ በሃይማኖተ አበው መጽሐፍ ላይ የሚሠፍር ነበር፡፡ እንዲህ ጊዜ በሰጠ ቁጥር መዥለጥ እየተደረገ የሚጻፍ አልነበረም፡፡ ደግሞስ አንድ አባት ልጆቹን ጠርቶ መምከር እየቻለ ‹‹ልጆቼ እንዲህ ያሉ ናቸው›› ብሎ ለዓለም መንገር ከየት ያመጣነው ሥርዓት ነው? ዓለም ችግሯን ለቤተ ክርስቲያን ታቀርባለች እንጂ ቤተ ክርስቲያን ችግሯን እንዴት ለዓለም አቤት ትላለች?

የሊቃውንቱ መሰባሰብና መወያየት ለቤተ ክርስቲያኒቱ የወንጌል ሥምሪት ወሳኝ ነው፡፡ እንዲያውም ከሲኖዶሱ ጉባኤ በፊት ሊደረግ የሚገባው ነገር ቢኖር የሊቃውንቱ ጉባኤ ነበር፡፡ በቤተ ክርስቲያኒቱ የትምህርተ ሃይማኖት፣ የሥርዓትና የትውፊት ጉዳዮች ላይ መክረው የውሳኔ ሃሳቦችን ማቅረብ የነበረባቸው ሊቃውንቱ ናቸው፡፡ ይህ ባለመሆኑም ይመስላል የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ አጀንዳዎች ሃይማኖታዊ ከመሆን ይልቅ አስተዳደራዊና ቢሮክራሲያዊ የሆኑት፡፡ ስንትና ስንት የምእመናን ጥያቄዎች እያሉ የሹመትና የበጀት ጥያቄዎች ዋነኛ መነጋገሪያዎች የሚሆኑት፡፡

የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንኮ የራስዋን ጳጳሳት እንድትሾም የተሟገቱት ከመላዋ ሀገሪቱ የተሰባሰቡ ሊቃውንት ነበሩ፡፡ ምነው መሠረቱ ተዘነጋ፡፡

አሁንም ሊቃውንቱን ተዋቸው፣ ቤተ ክርስቲያን እንደነርሱ ላሉት ናትና፡፡ በጉባኤያቸው ተገኝቶ መወያየት፣ የጉባኤውን አጀንዳ አብሮ መቅረጽ፣ ጉባኤውን መምራት፣ አሠራሩን ማሳየት ይገባል፣ የአባትም ነው፡፡ የገዛ ሊቃውንቶቻችንን ግን አትሰብሰቡ፣ አትመካከሩ፣ አትወያዩ፣ ችግር አትፍቱ ብሎ ማገድ፣ እምቢ ካላችሁ  ‹ለመንግሥት እነግርባችኋለሁ›› ብሎ መንግሥትን ማስፈራሪያ ማድረግ ሃይማኖታዊ አይደለም፡፡ ምነው በጎንደሩ የጥምቀት ኤግዚቢሽ የመንግሥት አካላት ሊቃውንቱን ሲያከብሩ ባየን፤

አሁንም እጠይቃለሁ፤ የሊቃውንቱን ጉባኤ ማገድ ጥቅሙ ለማን ነው? ባሏን ጎዳሁ ብላ … እንደተባለው ካልሆነ በቀር፡፡ ሊቃውንቱንም አስተምረው ለወግ ለመዓርግ ባበቋቸው ልጆቻቸው ሲታገዱ ማየት የስምንተኛውን ሺ መግባት ከማሳየት በቀር ሌላ ምን ያሳያል፡፡

«ኢኬያ» በመባል የሚታወቀው የስዊድናውያኑ የመኖሪያ ቤት እቃዎች መሸጫ መደብር ከጥር 26፣ እስከ መጋቢት 20፣ 2006 ዓም ድረስ በዓለም አቀፍ ደረጃ እርዳታ የማሰባሰብ ተግባር በማካሄድ ላይ ይገኛል።

የማኅበሩ አመራር እግዱን አስመልክቶ ዛሬ ረፋድ ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣል ከ200 በላይ የጉባኤው ተሳታፊ የአብነት መምህራን አዲስ አበባ ገብተዋል ፓትርያርኩና አንዳንድ ሊቃነ ጳጳሳት በቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልናና በሕገ ወጥ ሰባክያን ላይ ያላቸው አቋም በከፍተኛ ደረጃ እየተሸረሸረ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤን ውሳኔ በቀጥታ እየተፃረሩ ነው 

በምሥራቅ አፍሪካ ሃገሮቹ የጋራ ልማት ባለሥልጣን – ኢጋድ አማካኝነት በሚካሄደው ድርድር ለመሳተፍ አዲስ አበባ የገቡት ሰባት ከእሥር የተፈቱ የቀድሞ የደቡብ ሱዳን ከፍተኛ ባለሥልጣናት የተቀሩት አራት እሥረኞችም እንዲፈቱ ጥሪ አቀረቡ።

በአዲስ አበባ የሚገኙ የዓረና ፓርቲ አባል ወጣቶች የአሰብ የባህር በርን በተመለከተ በየካቲት 2/2006 ዓ.ም ፓርቲው በከፈተው አዲስ ጽ/ቤት ጥልቀት ያለው ፖለቲካዊ ውይይት አድርጓል፡፡ በእለቱ ሰፊ ትንተና ያቀረበው ደራሲ እና ፖለቲከኛ ወጣት አስራት አብረሃም ሲሆን በውይይቱ ጊዜም ወጣቶቹ የጦፈ ክርክር አካሄደዋል፡፡ ወጣት ፖለቲከኛው ስለ አሰብ ጉዳይ ሲያብራራ ንጉስ ሐይለሥላሴ በአንድ ወቅት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተ.መ.ድ) ወይይት […]

የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት አቶ ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ የሥልጣን ዘመናቸውን ከጨረሱ በኋላ፣ የኢትዮጵያና የኤርትራ መንግሥታትን ማስታረቅ እንደሚፈልጉ የመንግሥት የቴሌቪዥን ጣቢያ በሆነው ኢቴቪ በይፋ ገልጸው መስመር የያዘላቸው መሆኑንም አሳውቀው ነበር፡፡ በቅርቡ ከኤርትራ ቴሌቪዥን ጋር ሰፊ ቃለ ምልልስ ያደረጉት ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ግን ምንም ዓይነት የዕርቅ ፍላጐት እንደሌላቸው የኢትዮጵያ መንግሥት በፕሮፓጋንዳ ብልጫ እየተጠቀመበት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ ኢትዮጵያን በተመለከተ […]

አቶ ወልደስላሴ በሕወሃት ተመድበው የጉምሩክ ምክትል ሃላፊ ነበሩ። ስራ ሲጀምሩ ደሞዛቸው 1600 ብር ነበር። በእድገት ደሞዛቸው ወደ 6000 ብር ይወጣል። እንዴት እንደሆነ በማይታወቅበት ሁኔታ ባለ 4 ፎቅ ህንጻ ባለቤት ሆነዋል። ወንድማቸው አቶ ዘርዓይ ወልደስላሴ፣ ደሞዛቸው 532 ብር ነበር። ነገር ግን በግል የባንክ አካዉንታቸው ከአምስት ሚሊዮን ብር በላይ ተገኝቷል። በአፋር ክልል ከ 1 ሚሊዮን አራት መቶ […]

የባለሞያ ቡድኑ ሰብሳቢ አቶ ታደሰ አሰፋ፡- ለባለሞያ ቡድኑ ይህ ታሪካዊ ዕድል ተሰጥቶን ችግር ፈቺ ጥናት እንድናጠና በመደረጋችን ምስጋናችን ከፍ ያለ ነው፡፡ የጥናት ሰነዱ የካህናት፣ የምእመናንና የሰንበት ት/ቤቶች ወጣቶች ሐሳብ የተካተተበት በመኾኑ ከአኹን በኋላ የመላው የቤተ ክርስቲያኒቱ አማኞች ሰነድ ነው ብለን እናምናለን፡፡ ለዝግጅቱ መሳካት አስተዋፅኦ ያደረጉ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ የሀ/ስብከቱ ሓላፊዎችና አገልጋዮች፣ የክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት …

የማዕከላዊት አፍሪቃ ሪፓብሊክ ሰሜናዊ ጎረቤት ፣ ቻድ፣ ከአካባቢው ሃገራት ፤ በጦር ኃይል ይበልጥ የደረጀች መሆኗ ይነገርላታል። በፕሬዚዳንት ኢድሪስ ደቢ የምትራው ቻድ፤ የማዕከላዊት አፍሪቃ ሪፓብሊክን ውዝግብ ለመፍታት ፤ ራሷ በምትፈለገው መልክ ውሳኔ

በየመን እስር ቤት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እስረኞች የፍትህ ያለህ እያሉ ነው። ከ 15 ዓመታት በላይ በየመን እስር ቤት ውስጥ እየተሰቃዩ እንደሚገኙ የገለጹት እነዚሁ ኢትዮጵያውያን እስረኞች ያለኣንዳች ማስረጃ ከ 25 ዓመት እስከ ይሙት በቃ ተፈርዶብናል ባይ ናቸው።

የአንድን ሀገር ወግ፤ ባህል፤ ታሪክ እና ሁለንተናዊ ጉዞን ለማወቅ፤ የህዝቦችዋን ባህላዊ የበዓል አከባበር፤ ስነ-ፅሁፎችዋን በተለይ ደግሞ ስነ- ግጥሞችዋን ተመልከት ሲሉ አንዳንድ ምሁራን ይገልፃሉ። በአሁኑ ወቅት በርካታ ገጣምያን በግጥም መድረኩ ሲሳተፉ ይታያል፤ በግጥም፤ እምቅ አድናቆትን በግጥም እምቅ ፍላጎትን፣

ካርቱሞች፥ የጠላቶቻቸዉን ቁርጥር መቀነስ፥ የደከመ ምጣኔ ሐብታቸዉን መጠገን ይሻሉ።አማፂያኑ፥ጁባዎች ዉጊያ ሲገጥሙ የዲፕሎማሲ፥ የገንዘብ፥ የመሳሪያ ምንጫቸዉ ካናቱ ተበጥብጧል።ሌፍ እንደሚሉት የደቡብ ሱዳን ጦርነት ለደቡብ ኮርዶፋን «ሳይደግስ አይጣላም» አይነት ነዉ-የሆነዉ።ቢያንስ ለጊዜዉ።

የካቲት ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሶማሊ ክልል በቀላፎ አካባቢ የሚኖሩ 19 የየረር ባሬ ጎሳ የአገር ሽማግሌዎች በክልሉ ውስጥ የተፈጸመውን ከፍተኛ እልቂት ለጠ/ሚንስትሩ አቤት ለማለት ወደ አዲስ አበባ በሄዱበት ወቅት  አካባቢውን በሚጠብቁ ልዩ ሃይሎች ተይዘው መታሰራቸውን ከስፍራው የደረሰን መረጃ አመልክቷል። ከእስር ያመለጡ አንዳንድ ሽማግሌዎች በትናንትናው እለት ወደ አዲስ አበባ በመሄድ ከዚህ ቀደም በልዩ …

የካቲት ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦሮሚያ ክልል በቡሌ ሆራ ወረዳ፣ በሀገረማርያም ከተማ ከአርሴማ ቤተክርስቲያን ጋር በተያያዘ የተነሳውን የውስጥ ችግር ተከትሎ ችግሩን ለመፍታት የተመረጡት የሰበካ ጉባኤ አባላት ታስረው የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ከተጠየቀባቸው በሁዋላ ህዝቡ ባሰማው ከፍተኛ ተቃውሞ የአገር ሽማግሌዎቹ በዛሬው እለት የተፈቱ ሲሆን፣ ህዝቡ በድል አድራጊነት ስሜት በሆታ አጅቦ ወደ ቤተክርስቲያን ወስዷቸዋል። …

የካቲት ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ አሸባሪ ካላቸው ግንቦት ሰባት እና ሌሎች ፖለቲካ ድርጅቶች ጋር ግንኙነት አላቸው ተብለው የተጠረጠሩ በርካታ የአዲስ አበባና አማራ ክልል ወጣቶች ወደ ማዕከላዊ እስር ቤት እየተጋዙ መሆኑን የአይን እማኞች ተናገሩ፡፡ ኢህአዴግ በጀመረው አዲስ አሰሳ በሀገሪቱ አንድንድ ቦታዎች ኢንተርኔትን ጨምሮ ስልክ እንዳይሰራ የተደረገ ሲሆን በአንዳንድ አካባቢዎችም የመከላከያ ሀይል ተበትኗል፡፡ …

የካቲት ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአዲስ አበባ መስተዳድር የካቲት 2፣ 2006 ዓም ከእድር ተጠሪዎች ጋር ባደረጉት ስብሰባ እያንዳንዱ እድር በነፍስ ወከፍ 8 ሺ ብር ለአባይ ግድብ ማሰሪያ እንዲከፍል ታዟል። ትእዛዙ የተጣለው የካቲት 2 ቀም 2006 ሲሆን፣ 650 እድሮች በነፍስ ወከፍ 8 ሺ ብር ይከፋላሉ። በዚሁ ከላይ በወረደው መመሪያ መንግስት ከእድሮች በአንድ ጊዜ …

የካቲት ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በቅርቡ በጋዜጠኛ መሳይ መኮንንና የኢሳት የኮምፒዩተር ባለሙያ በሆነው ተቀማጭነቱ ቤልጂየም በሆነው የኢሳት ባልደረባ ላይ የተገኙ ባእድ የመሰላያ ሶፍትዌሮች ከጣሊያኑ ሃኪንግ ቲም የተላኩ መሆናቸውን ሲትዝን ላብን በመጥቀስ ታዋቂው ጋዜጣ ዋሽንግተን ፖስት ዘግቧል። ጋዜጣው ባወጣው ሰፊ ዘገባ መረጃዎችን ከኮምፒዩተሮች ላይ ለመውሰድ የሚያስፈልገው ባእድ ሶፍትዌር የተላከው ከጣሊያን ኩባንያ ጋር ቢሆንም፣ …

(ለ1966ቱ አብዮት 40ኛ ዓመት ማስተዋሻ)
በአብዮቱ ዘመን አንድ ጓድ ከዚህ ቀጥሎ የተጠቀሰውን ቃለ መጠይቅ በመስጠቱ ለ17 ዓመታት ወኅኒ ተወርውሮ ነበር፡፡ በ1983 ዓም ከወኅኒ ሲወጣ ሰውዬው አርጅቷል፡፡ ከዘራውን ተደግፎ ቤቱ በረንዳ ላይ ይቀመጥና ቃለ መጠይቁ የታተመበትን ጋዜጣ እያየ ‹‹ይህን ቃለ መጠይቅ የሰጠሁት ዛሬ ቢሆን ኖሮስ?›› ብሎ ይጠይቃል፡፡ ለሰውዬው መልስ ለመስጠት ቃለ መጠይቁን አንብቡት፡፡

ጋዜጠኛ፡- ለእርስዎ ሀብት ክፍፍልን በተመለከተ በካፒታሊዝምና በሶሻሊዝም መካከል ያለው ልዩነት ምንድን ነው?

ጓድ፡- በካፒታሊዝም እኩል ያልሆነ የሀብት ክፍፍል ሲኖር፣ በሶሻሊዝም ደግሞ እኩል የሆነ የድኽነት ክፍፍል አለ

ጋዜጠኛ፡- ጭቆናን በተመለከተ በካፒታሊዝምና በሶሻሊዝም መካከል ልዩነቱ ምንድንነው?

ጓድ፡- በካፒታሊዝም ሰው ሰውን ይጨቁናል፣ በሶሻሊዝም ግን ፓርቲ ሰውን ይጨቁናል

ጋዜጠኛ፡- ለምሳሌ በሰሐራ በረሃ ውስጥ ሶሻሊስት ሪፐብሊክ ቢመሠረት ምን ለውጥ ሊያመጣ ይችላል ብለው ያስባሉ?

ጓድ፡- ከሦስት ዓመታት በኋላ ሀገሪቱ አሸዋ ከውጭ ማስመጣት ትጀምራለች

ጋዜጠኛ፡- በሶሻሊዝም አስተሳሰብ ደመወዝና ሠራተኛን እንዴት ይገልጧቸዋል?

ጓድ፡- በሶሻሊዝም ሠራተኛም በሚገባ የሠራ ለመምሰል ጥረት ያደርጋል፣ መንግሥትም ተገቢውን ደመወዝ የከፈለ ለመምሰል ጥረት ያደርጋል

ጋዜጠኛ፡- ገበያ የሚመራው በአቅርቦትና ፍላጎት ነው ይባላል፡፡ ይህንን ሃሳብ በሶሻሊዝም እንዴት ይገልጡታል?

ጓድ፡- በሶሻሊዝም የፈለግከውን ነገር መርጠህ አትገዛም፤ ነገር ግን የቀረበልህን ነገር ትገዛና፣ ከገዛህ በኋላ እንድትፈልገው ይደረጋል፡፡

ጋዜጠኛ፡- አንዳንድ ሰዎች የሶሻሊስት ፓርቲው ጋዜጣ በጣም ትልቅ ነው ይላሉ፤ ለምንድን ነው ትልቅ የሆነው?

ጓድ፡- ምክንያቱም ሰው እርሱን መያዝ ስለሚያፍር፣ የጋዜጣው ስፋት ስታነበው ፊትህን ለመሸፈን የሚበቃ መሆን አለበት

ጋዜጠኛ፡- በዓለም ላይ ሰባቱ አስደናቂ ነገሮች የሚባሉ አሉ፡፡ በሶሻሊዝም አስተሳሰብ ሰባቱ የዓለም አስደናቂ ነገሮች ምን ምን ናቸው ብለው ያስባሉ?

1.         ሁሉም ሰው ሥራ አግኝቷል

2.       ሁሉም ሰው ሥራ ቢያገኝም ቅሉ ማንም ሰው ግን ሥራ እየሠራ አይደለም(ስብሰባ፣ ግምገማ፣ የፓርቲ ሥራ፣ የአካባቢ ልማት ማኅበር ሥራ አለበት)

3.       ማንም ሰው ሥራ እየሠራ ባይሆንም እንኳን ሁሉም ሰው ግን ሀገሪቱ ያወጣችውን የዕድገት ዕቅድ ግቡን እንዲመታ አድርጓል

4.       ምንም እንኳን ሁሉም ሰው ዕቅዱን ተግባራዊ ቢያደርገው፣ ነገር ግን ምንም ዓይነት ውጤት አልተገኘም

5.       ምንም እንኳን ምንም ዓይነት ውጤት ባይገኝ፣ ነገር ግን ሁሉም ሰው የፈለገው ነገር ሁሉ እንዲኖረው ተደርጓል

6.       ምንም እንኳን ሁሉም ሰው የፈለገው ነገር ሁሉ ቢኖረው፣ ሁሉም ሰው ግን በሆነው ነገር ርካታ የለውም

7.       ምንም እንኳን ሁሉም ሰው በሆነው ነገር ሁሉ ርካታ ባይኖረው፣ ፓርቲው ግን የሕዝቡን 100%ድጋፍ አለው፡፡

እነዚህ ናቸው ሰባቱ አስደና ቂነገሮች፡፡

ጋዜጠኛ፡- ፓርቲው የሚመራባቸው ሦስቱ መሠረታውያን ሕግጋት ምንድን ናቸው?

ጓድ፡- ሶሻሊዝም ሩጫ ነው፤ በዚህ ሩጫ ውስጥ የፓርቲው መርሖዎች ሦስት ናቸው፡፡ የመጀመሪያው ሩጫው እንደተጀመረ ሯጮቹን ሁሉ ማሰናከልና የመሪነቱን ቦታ መያዝ ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ የሩጫውን ፍጥነት መቆጣጠር መቻል ነው፡፡ የመጨረሻውም በተቻለ መጠን ሩጫውን ሳያጠናቅቁ የመሮጫው ትራክ ላይ ረዥም ጊዜ ለመቆየት መቻልነው፡፡

ጋዜጠኛ፡- አንድ የእርስዎ ጓድ በአብዮታዊው ጦር ተይዘው በቀደም ወደ ወኅኒ ቤት ገብተዋል፡፡ ምን ጎድሎባቸው ነው ፀረ አብዮት የሆኑት፤ አብዮቱ ሁሉን ነገር አሟልቶላቸው ነበር?

ጓድ፡- ጓዱን የያዙት ሰዎችም ይህንን ነበር የጠየቁት፡፡ እርሱ ወደ አሜሪካ ለመሄድ በዝግጅት ላይ ነበር፡፡ ዝግጅቱን ሲያጠናቅቅ የመውጫ ቪዛ እንዲሰጠው አመለከተ፡፡ ይህንን የሰሙ ወታደሮች ከሌሊቱ በስምንት ሰዓት ወደ ቤቱ መጡ፡፡ በሩን ሰብረው ገቡና ‹‹አብዮቱ ቤት ሰጥቶሃል፣ መኪና ሰጥቶሃል፣ መሬት ሰጥቶሃል፣ የንግድ ድርጅት ሰጥቶሃል፣ሥልጣን ሰጥቶሃል፣ ከውጭ ዕቃ ያለ ቀረጥ እንድታስገባ ዕድል ሰጥቶሃል፤ ለምንድን ነው ወደ አሜሪካ መሄድ የፈለግከው›› ሲሉ ጠየቁት፡፡ እርሱም ተናድዶ ‹‹እንዲህ ከሌሊቱ በ8 ሰዓት እኔ ሳልፈቅድላችሁ በሬን ሰብራችሁ በመግባት እንዳትረብሹኝ ስለምፈልግ ነው አገር ጥዬ የምሄደው›› ብሎ መለሰላቸው፡፡ ለዚህ ነው ያሠሩት፡፡

ጋዜጠኛ፡- የእርስዎ ጓድ ብቻ ሳይሆኑ የጎረቤትዎ ልጅም መታሠሩን ሰምተናል፤ ልጁ በጣም ትንሽ ልጅ ነው፡፡ ደግሞም በጣም የታወቀ ዋናተኛ ነው፡፡ የታሠረውም ባለፈው ግዮን ሆቴል ዋና ተለማምዶ ሲመለስ ነው ይባላል፡፡ ምክንያቱን ሊነግሩን ይችላሉ?

ጓድ፡- እንደ ሰማሁት ከሆነ ልጁ የታወቀ ዋናተኛ ነው፡፡ አባቱ በሌለው ገንዘብ ከፍሎለት ግዮን ሆቴል ዋና ይለማመዳል፡፡ የፓርቲያችን ሊቀ መንበር በዚያ ቀን ዋና ለመዋኘት ግዮን ሄደው ነበር፡፡ በአጋጣሚ ዋና እየተለማመዱ ሳለ ወደ መካከል ሄደው ሊሰምጡ ደረሱ፡፡ አጃቢዎቻቸው ዋና የሚችሉ አልነበሩም፡፡ ልጆች ናቸው ተብለው በአካባቢው እንዲንቀሳቀሱ የተፈቀደላቸው የታሠረው ልጅና ሁለት ጓደኞቹ ብቻ ነበሩ፡፡ ሮጠው ገቡና ሊቀ መንበሩን ከመስመጥ አዳኗቸው፡፡ ጓድ ሊቀ መንበርም ለዚህ ውለታቸው አንዳች ሽልማት ሊሰጧቸው ፈለጉና ልጆቹን ጠየቋቸው፡፡ አንደኛው ልጅ ብስክሌት መረጠ፤ ሁለተኛው ልጅ ደግሞ የመጨዋቻ መኪና ጠየቀ፤ ይኼ የጎረቤቴ ልጅ ግን የአካል ጉዳተኞች መሄጃ ጋሪ መረጠ፡፡ ጓድ ሊቀ መንበርም በጣም ተገረሙና ‹‹ምን ያደርግልሃል፤ አንተ ሙሉ ጤነኛ ነህ›› አሉት፡፡ ልጁም ‹‹አባቴ እርስዎን ከሞት ማዳኔን ከሰማ እግሬን ይሰባብረዋል፤ ለዚያ ብዬ ነው›› አላቸው፡፡ በዚህ ተናደው ነው ያሳሠሩት፡፡

ጋዜጠኛ፡- ባለፈው ሰሞን ለሥራ ጉብኝት ወደ ቻይና ተጉዘው ነበር፡፡ በዚያ ጊዜ በአንድ ቻይናዊ፣ ኢትዮጵያዊና ዴንማርካዊ የፓርቲ ሰዎች መካከል የተፈጠረ ነገር እንደነበር ሰምተናል፡፡ ሊነግሩን ይችላሉ?

ጓድ፡- አዎ፤ አራታችን በአንድ ወንዝ ዳር ቆመን ስንዝናና አንድ ጋዜጠኛ መጣና ‹‹ሥጋ ለማግኘት ሲባል ሰልፍ ስለመያዝ ምን ታስባላችሁ?›› ሲል ጠየቀን፡፡ ዴንማርካዊው ‹‹ሰልፍ ማለት ምንድን ነው?›› ሲል መልሶ ጠየቀ፤ ቻይናዊውም ቀጠል አደረገና ‹‹ሥጋ ምንድን ነው?›› ሲል አከለበት፡፡ የኛው ፖለቲከኛ ደግሞ ‹‹ማሰብ ማለት ምንድን ነው?›› ብለው ጋዜጠኛውን መልሰው ጠየቁት፡፡ ይኼ ነው ታሪኩ፡፡

ጋዜጠኛ፡- በዚሁ አጋጣሚ አብዮታዊ መሪያችን በቻይና ለነበሩ ጋዜጠኞች የሃሳብ ነጻነትን አስመልክቶ አስደናቂ ነገር ተናግረዋል ይባላል፤  ምን ነበር?

ጓድ፡- ጋዜጠኛው የሃሳብ ነጻነት እያሉ ምዕራባውያን ሶሻሊስት ሀገሮችን ለመበጥበጥ ይሞክራሉ፤ እናንተ ይህንን ችግር እንዴት ፈታችሁት? ብሎ ጠየቃቸው፡፡ እርሳቸውም ‹እኛ መጀመሪያውኑ ሃሳቡ እንዳይኖር ስላደረግነው ነጻነት መስጠት አይጠበቅብንም› ብለው መልሰውለት በጣም ተደንቆ ነበር፡፡ ?

ጋዜጠኛ፡ – እኛ ራሳችን ስሕተታችንን ገምግመን ማሻሻል ባለመቻላችን ሌሎች ስሕተቶቻችንን ዐውቀው እየተጠቀሙበት ነው የሚል ትችት ሰንዝረው ነበር፡፡ አንድ ማሳያ እንኳን ሊነግሩንይችላሉ፡፡

መልስ፡- ይህንን ድክመት እንኳን ነጻ ሆኖ የሚከታተለን ሕዝብ ይቅርና ፀረ አብዮት ናቸው ብለን ያሠርናቸው እንኳን በሚገባ ዐውቀውታል፡፡ አንድ ቀላል አስቂኝ ነገር ልንገርሽ፡፡ አንድ ባልዋ ፀረ አብዮት ሆኖ የታሠረባት ሴትዮ አለች፡፡ ሴትዮዋ ድኽነቱ ሲመራት በቤቷ ጓሮ ድንች ተክላ መሸጥ ፈለገች፡፡ ግን ጉልበት ከየት ይምጣ፡፡ ሰው እንዳትቀጥር፣ ገንዘብ ከየት ይገኝ፡፡ በመጨረሻ ለባልዋ እንዲህ የሚል ደብዳቤ ጽፋ በወኅኒ ቤቱ በኩል ላከችለት ‹‹በጓሯችን ድንች ልተክል ነበር፡፡ ነገር ግን ማን ይቆፍርልኛል፤ አንተ እንዳታግዘኝም ገና ሁለት ዓመት ይቀርሃል›› ባልዋም ‹‹ጓሮውን ስትቆፍሪ ተጠንቀቂ፤ እጅግ ውድ የሆኑ ነገሮችን ደብቄበታለሁ›› ብሎ መልሶ ላከላት፡፡ ደብዳቤው በደረሳት ሌሊት ፖሊሶች መጥተው የተደበቀውን ነገር ፍለጋ የቤቷን ጓሮ ከጥግ እስከ ጥግ ቆፋፈሩት፡፡ እርሷም በድንጋጤ ከረመችና ‹‹ስድስት ፖሊሶች መጥተው የሆነ ነገር ፍለጋ ጓሮውን በቁፋሮ እንዳልነበረ አደረጉት፤ ያልቆፈሩት መሬት የለም፤ ምን ባደርግ ይሻለኛል?›› ስትል ጻፈችለት፡፡ ባሏም ‹‹አሁንማ ቆፍረውልሻል ድንችሽን ትከይ›› ብሎ መለሰላት፡፡

ጥያቄ፡- ይኼ የመጨረሻ ጥያቄያችን ነው፡፡ ባለፈው ጊዜ በአውሮፕላን ሲጓዙ አንድ ያልታወቀ ፍጡር አውሮፕላኑን እየተከተለ አስቸግሮ ነበር ይባላል፡፡ ፓይለቱና አስተናጋጆቹ ሊያባርሩት አልቻሉም፡፡ በአውሮፕላኑ የነበሩት የሃይማኖት አባቶችም ከዐቅማቸው በላይ ሆኖ ነበር፡፡ እርስዎ ግን የሆነ ነገር ሲያሳዩት እንደ ጢስ በኖ እንደ ጉም ተኖ ጠፋ ይባላል፡፡ ምን እንዳሳዩት ሊነግሩን ይችላሉ?

መልስ፡- እነርሱ ይህንን ያህል ገንዘብ እንሰጥሃለን አሉት፤ አልሄደም፤ የሃይማኖት አባቶችንም አልፈራም፡፡ ወደ እኔ ቀረብ ሲል ‹‹የወጣት ሊግ አባል ነው የማደርግህ›› ስለው በድንጋጤ ጥሎ ጠፋ፡፡

አመሰግናሉ፤ ስለ ቃለ መጠይቁ

አደራ ይኼ ቃለ መጠይቅ ከታተመ የሆነ ቦታ አንድ ቅጅ እንዲቀመጥ፡፡ ምናልባት ከሃያ ዓመት በኋላ እንዳገኘው

(መነሻ ሃሳብ Jokes of the Velvet Revolution)

ኳታር፣ ዶሃ

© ይህ ጽሑፍ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት የወጣ ነው

የአንድነት አባል በመሆኑ በሚያስተምርበት ትምህርት ቤት አስተዳደር የተለያዩ ዛቻዎችና ማስጠንቀቂያዎች እየደረሱበት እንደሆነ የሚናገረው መምህር አማኑኤል መንግስቱ “ከዚህ በፊትም ያለምንም ምክንያት ከማስተምርበት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አንስተው ወደ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አውርደውኛል፡፡” በማለት በመንግስት ኃላፊዎች የደረሰበትን በደል ለፍኖተ ነፃነት አስረድቷል፡፡ ተደጋጋሚ ዛቻ እየደረሰበት መሆኑንና በቅርቡም ከስራው ሊያፈናቅሉት እንዳቀዱ ጨምሮ አስረድቷል፡፡ መምህር አማኑኤል ላይ እየደረሰ ስላለው […]

ፖለቲካ ጥበብ ነው፤ አንዳንዶች ‘የማመቻመች ጥበብ’፣ አንዳንዶች ‘የማጭበርበር ጥበብ’፣ ሌሎች ‘art of possible’ ይሉታል። አንዳንዴ እውነተኛ የሕዝብ ተቆርቋሪዎች እያሉ አስመሳዮች ያሸንፋሉ፤ ሐሳብ አፍላቂዎቹ እያሉ ሰራቂዎቹ ይመሰገናሉ። ሌሎች ፖለቲካ ጫወታ (game) ነው ይሉታል። ለብዙዎች የጨቀየ ጫወታ ነው፤ ለጥቂቶች ግን ጥበብም ጫወታም ነው። ተጫዋቾቹ ደግሞ በጨዋታው ሕግ (rule of the game) መሠረት መጫወት አለባቸው።

በእኛ አገር ‘ፖለቲካ’ እና ‘ፖለቲከኝነት’ ዛሬም አፍላ ነው። እስከዛሬ ጉልቤው ገዢ ነው፣ ገዢው ወሳኝ ነው። ምንም ዓይነት ፖለቲካዊ ጥበብ የሚጠይቅ የፖለቲካ ፉክቻ የለም። በአገራችን የፖለቲካ ፓርቲዎች ዕድሜ 40 አይሞላም። በጠብ መንጃ ተነድቶ ሥልጣን ላይ የወጣ እንጂ በፖለቲካ ፉክክር ተንጓሎ የወጣ ፓርቲ የለም።

የፖለቲካ ፓርቲዎች ተቃዋሚ እና ገዢ ተብለው ፉክክር ውስጥ የገቡት በኢሕአዴግ ዘመን ነው። ሆኖም ከምርጫ 97 በኋላ ኢሕአዴግ በዴሞክራሲ ጉዳይ ላይ ስልታዊ ማፈግፈግ በማድረጉ ፓርቲዎች ትግሉን ከዜሮ እንዲጀምሩ አስገድዷቸዋል፤ ያውም በጠበበ ምኅዳር።

ከምርጫ 97 ወዲህ በተደረጉ የፖለቲካ ሽኩቻዎች ውስጥ ኢሕአዴግ በዝረራ ያሸነፈባቸው አጋጣሚዎች ብዙ ናቸው። ለዚህ መንስኤው ከኢሕአዴግ ዴሞክራሲያዊ ንፉግነት ባሻገር የተቃዋሚዎቹም ድክመት ተጠቃሽ ነው። ተቃዋሚዎች ፕሮግራሞቻቸውን በማስተዋወቅ እና ደጋፊ በማበርከት ረገድ ጉልህ ችግር አለባቸው። ሕዝቡ ተቃዋሚ መሆናቸውን አውቆ እንዲሁ እንዲመርጣቸው ይፈልጋሉ እንጂ የሚመርጥበትን ምክንያት ሊያስረዱት አይከጅሉም። ስለተቃዋሚዎች ድክመት ብዙ ተብሏል፤ እኔም አሁን አንዱን ነቅሼ ላወራ ነው – ሰው ፊት አቀራረብ (presentability)።

የተቃዋሚ አመራሮች ለፖለቲካ ክርክር፣ ለጋዜጣዊ መግለጫ ወይም ለቃለ ምልልስ ሕዝብ/ካሜራ ፊት ሲቀርቡ የሚኖራቸው አለባበስ፣ ንቃተ-ፊት እና አነጋገር ዝርክርክነት ሰዎች “ሲሪዬስሊ” እንዳይወስዷቸው ከሚያደርጉ  እንቅፋቶች አንዱ ነው። እዚህጋ ሁለት ትችቶች ሊነሱ ይችላሉ፤ አንደኛው ‘ፖለቲከኞች ማስመሰል አለባቸው ወይ?’ የሚለው ነው። የጫወታው ሕግ የሚጠይቅ ከሆነ አዎ! ሰዎች መጀመሪያ በሚያዩት ነገር ተማርከው ጆሮ ይሰጣሉ፣ አነጋገሩን አድምጠው ነገሩን ያጤናሉ። የመጀመሪያውን ፈተና ያላለፈ ቀጣዩን የመደመጥ ዕድል አያገኝም፣ ያንን ዕድል ያገኘ አነጋገሩን ካላሳመረ ነገሩን ገዢ አያገኝም። ሦስተኛው ደረጃ ላይ ያለው የመጨረሻው እና ወሳኙ ፈተና ነው።

‘የለም፤ ይህንን መጽሐፉን በሽፋኑ የሚዳኙትንም ጭምር መታገል አለብኝ’ የሚል ፖለቲከኛ፣ ፖለቲከኛ ሳይሆን አራማጅ (ለውጥ አማጭ) ነው መሆን የሚችለው።

ሮብ ያንግ የተባለ “Power Dressing” የተሰኘ መጽሐፍ ደራሲ ከፎርብስ ጋር ባደረገው ቃለ ምልልስ ፖለቲካን በሚያህል የአገር ዕጣ ፈንታ በሚወሰንበት ጉዳይ ስለአለባበስ ማውራት ብዙ ሰዎችን ያሳፍራቸዋል፣ ግን አማራጭ የለም ብሏል። “Politics wants to present itself as a serious institution about substantive issues, rather than a popularity contest based on what the contenders look like. But the fact is that fashion… can be mighty powerful political currency.”

አንዱና ትልቁ ችግር ፖለቲከኞች ራሳቸውንና ሕዝቡን ከአለባበሱ እና አቀራረቡ አልፈው ለመመልከት ቢሞክሩም ሕዝቡ የእነሱን አለባበስና አቀራረብ አስቀድሞ መገምገሙን አለማቆሙ ነው። ስለዚህ በጥቃቅን የአቀራረብ (presentability) ሳቢያ ትልቁ ቁምነገር ሰሚ ከሚያጣ፣ ትንሽ ዋጋ መክፈል ያዋጣል።

የፖለቲካ ፓርቲዎቻችን በተለይ ተቃዋሚዎች ይህንን ጉዳይ በቅጡ ያጤኑት አይመስልም። አቶ ይልቃል (ኢ/ር) ሰማያዊ ፓርቲን ወክለው የሰጧቸው ቃለምልልሶች ላይ የወጡ ፎቶዎቻቸው በሙሉ ጉስቁልቁል ያሉና ኮታቸው ተዛንፎ ወይም ከትከሻቸው የሰፋ መስሎ ነው። ዛሬ (የካቲት 6/2006) መግለጫ ሲሰጡ ያየኋቸው የሁለት ተቃዋሚ ፓርቲ አመራር አባላት፣ ጠረጴዛው ኋላ ሳያቸው ለአቀራረባቸው እንዳልተጨነቁ ያሳብቅባቸዋል። አለባበሳቸው የአዘቦት ዓይነት ነው፤ ‘ፎርማል’ በሚባል ሁኔታ እንኳን አልለበሱም። አንዱ ሲናገር ሌለኞቹ አንዱ አገጩን ተደግፎ፣ ሌላኛው በዚህንኛው ንግግር ያልተደሰት በሚመስል አኩርፎ፣ አንደኛውም ጉስቁል ባለ መልኩ ተቀምጠው ያደምጡታል። በኔ እምነት፣ አንዱ ሲናገር ሌላኛው በተቻለ መጠን የፊት ገጽታውን ሳያዘባርቅ፣ ቀጥ ብሎ ቢቀመጥ ሌላው ቢቀር የታዳሚዎችን ሐሳብ ከተናጋሪው አይሰርቅም።

ሌላው ጉዳይ የንግግር ዘዬ ጉዳይ ነው። በፖለቲካ አምባ፣ አንደበተ ርቱዕነት ወሳኝ ቁም ነገር ነው። እነ ልደቱ አያሌው፣ ብርሀኑ ነጋ፣ መለስ ዜናዊ፣ ሀብታሙ አያሌው የዚህ አንደበተ ርቱዕነት ማሳያ ናቸው። ይህ የሚያውቁትን አሳምሮ፣ የማያውቁትን አድበስብሶ የማሳለፊያ ጥበብ ለፖለቲከኞች ቁልፍ በመሆኑ ሌላው ዓለም ሥልጠና ሳይቀር ይወስዱበታል። የመጨባበጥ ሒደት፣ የእንግዶች /ካሜራ/ ፊት እንቅስቃሴ፣ የእጅ ውዝዋዜ ሳይቀሩ ይጠናሉ። ግለሰቦችን በአንቱታ እና ትክክለኛ ማዕረጋቸውን ሳያዛንፉ መጥራትም ራሱን የቻለ በልምምድ የሚገኝ ጥበብ ይጠይቃል፤ ትርፍም አለው።
የእኛ ፖለቲከኞች ለዚህ ቁብ አይሰጡትም። መወዳደሪያ እሴት ነው ብለው የሚያስቡም አይመስሉም። በመንግሥት በጀት ፕሮቶኮል የሚቀጠርላቸው ጠቅላይ ሚኒስትራችን ሳይቀሩ በኔልሰን ማንዴላ ቀብር ላይ ከሰው ሁሉ የተለየ አለባበስ ለብሰው የታዩት፣ እዚህ ግባ የማይባል ንግግር ያደረጉት በዚሁ ሳቢያ ነው። አነዚህ የአቀራረብ ቅንብሮች ተደማምረው ነው አንድን መሪ ሞገስ ያለው (charismatic) ነው፣ አይደለም የሚያስብሉት። ሰዎቹ፣ ብንወዳቸውም ብንጠላቸው አገራችንን ወክለው ሲቀርቡ ሞገስ ቢኖራቸው መልካም ነው።

በጥቅሉ ሲታይ ግን ተቃዋሚዎች ከገዢው አንፃር የመሪ-ሞገስ አልባ ናቸው ማለት ይቻላል። ገፅታ አይቶ በሚዳኝ ሕዝብ ውስጥ እየኖሮ ለአቀራረብ አለመንጠንቀቅ ዋጋ ያስከፍላል። ያንን ዋጋ ደግሞ ተቃዋሚዎች አይችሉትም።

መኢአድና አንድነት ፓርቲ በአንድነት ፓርቲ ጽ/ቤት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጡ፡፡
ከአንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) እና ከመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) የተሰጠ መግለጫ !!!!
ብአዴን ኢህአዴግ የአማራን ህዝብ የመምራት የሞራል ልዕልና የለውም፤ ህዝብ ያዋረዱ አመራሮቹም ለፍርድ ሊቀርቡ ይገባል፡፡

Image
የኢትዮጵያ ህዝብ እንደሚገነዘበው በዚህች ታሪካዊት እና የጥቁር ህዝብ ድል ማዕከል፤ የነፃነት ተምሳሌትና የአፍሪካ ህዝብ ኩራት በሆነች ሀገር የኋላ ዘመን ውጣ ውረድ ውስጥ ሰፊው የአማራ ህዝብ ከመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር በአንድ ተሰልፎ ለሀገር ግንባታ ተኪ የሌለው ሚና ተጫውቷል፡፡ በዚህም የተነሳ በአምባገነኖች ጡጫ ተደቁሷል፡፡ ዛሬም እንደ ትላንቱ በገዢዎቹ እየተረገጠ ያለ ህዝብ ነው፡፡
ይህ ህዝብ እንደትላንቱ ሁሉ ዛሬም በየጋራው እና በየሸንተረሩ ተበታትኖ የኔ እንዳይላት እንኳን በተነፈገው ኩርማን መሬት አፈር እየገፋ ለመኖር መዳረጉ ሳያንስ የኢህአዴግ ፖለቲካ ሌላ ሰቀቀን ጨምሮ ‹‹ጨቋኝ ገዥ መደብ የነበረ፤ ትምክህተኛ›› በሚል ጎራ መድቦ ያልዘራውን ግፍ እንዲያጭድ እያደረገው እንደሆነ ይስተዋላል፡፡
የአማራ ህዝብ እንደሌላው ጭቁን የኢትዮጵያ ህዝብ ሁሉ ዘመኑ ባነበራቸው የአገዛዝ ሥርዓቶች የጭቆና ቀንበር ተጭኖት፤ የግፍ ፅዋ የተጋተ መሆኑ ከመላው የኢትዮጵያ ህዝብ የተሰወረ አይደለም፡፡
ይሁን እንጂ ይህንን ህዝብ እወክላለሁ የሚለው የትላንቱ ኢህዴን የዛሬው ብአዴን ያፈራቸው አመራሮች ስልጣን በመቆናጠጥ የገዛ ህዝባቸውን ከመናቅና ከማዋረድ አልፈው ‹‹ትላንት ሽርጣም ያለህ ትምክህተኛ አንገቱን ይድፋ ዛሬ ተራው ያንተነው›› በማለት በግፍ እንዲገደል ማድረጋቸው ሰቆቃው ከህዝብ ህሊና ሳይወጣ አቶ መለስ ‹‹ጫካ መንጣሪ ሞፈር ዘመት›› ብለው እንደተሳለቁበት ሁሉ በሳቸው ራዕይ አስቀጣይ በዛሬዎቹ የብአዴን አመራሮችም ያው ዘመቻ ተጠናክሮ መቀጠሉ አገዛዙ የደረሰበትን አሳፋሪ ደረጃ በግልፅ ያሳያል፡፡
የክልሉ ምክትል ፕሬዘዳንት እና የብአዴን ጽህፈት ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ አለምነው መኮንን በቅርቡ አደረጉት ተብሎ የተደመጠው አስነዋሪ ንግግርም የክልሉን ህዝብ ብቻ ሳይሆን መላውን የኢትዮጵያ ህዝብ የናቁ እና ያዋረደ፤ የሀገሪቷን ህገ- መንግስት በግልፅ የጣሰ የወንጀል ተግባር ነው፡፡ በተጨማሪም የአማራን ህዝብ ከሌሎች ወንድሞቹ ለመነጠልና አንገቱን ደፍቶ እንዲኖር የተደረገ ዘመቻ ነው፡፡
የኢህአዴግ አገዛዝ በመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ከተጫነበት ጊዜ ጀምሮ በሁሉም ክልል ያለው ህዝብ በራሱ ቋንቋ ተናጋሪዎች በግፍ እየተገዛ፤ ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቱ ተገፍፎ በድህነት አረንቋ ውስጥ እየኖረ ቢሆንም የአማራን ህዝብ እንወክላለን እንደሚሉት ብአዴኖች የሚመራውን ህዝብ በአደባባይ በተደጋጋሚ የዘለፈ፤ ያዋረደ እና አንገት ያስደፋ ድርጅት አለ ለማለት ይቸግራል፡፡
የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) እና አንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የአማራን ህዝብ የመምራት የሞራል ልዕልና የሌለውን ብአዴን ኢህአዴግን ለመታገል መላውን አባላትና ደጋፊዎቻችንን ከጎናችን በማሰለፍ በፅናት እና በብቃት መታገል ያለብን ወሳኝ ጊዜ ላይ እንደሆንን እንገነዘባለን፡፡
መላውን ህዝብ ከዳር እስከ ዳር አንቀሳቅሰን ሰላማዊ ትግሉን ፍሬያማ በማድረግ አገዛዙ እንዲለወጥ እና የኢትዮጵያ ህዝብ ሉዓላዊ የስልጣን ባለቤት እንዲሆን ለማድረግ የጀመርነውን ሰላማዊ ትግል አጠናክረን የምንቀጥል መሆኑን እያረጋገጥን የካቲት 16 ቀን 2006 ዓ.ም በባህር ዳር ከተማ ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ በስርዓቱ ላይ ያለንን ተቃውሞ እናሰማለን፡፡ ይህ ትግል ህዝብ ያዋረዱ አመራሮች በተገቢው ፍጥነት ለፍርድ እስኪቀርቡ በሌሎች የሀገራችን ክፍሎችም ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡
የባህርዳር እና አካባቢው ነዋሪዎችም በነቂስ በመውጣት ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ተቃውሞውን እንዲገልፅ ሀገራዊ ጥሪ እናቀርባለን፡፡

ድል የህዝብ ነው !!!!
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር !!!
የካቲት 6 ቀን 2006 ዓ.ም
አዲስ አበባ

:evil:
ምንሊክ ሳልሳዊ :- ልብ ብለው ከሆነ በዚህ ሳምንት ሕወሓት/እሕኣዴግ በሁለት ጉዳዮች ላይ ተመርኩዞ የተለይዩ ተግባራትን ከውኖ ራሱን አጋልጦ አደባባይ ላይ አምባገነንነቱን አስመንጥሮ ተሽከርክሮ አሸባሪነትን እና አሸባሪዎችን እንዳቀፈ ጉዞውን እየተንገዳገደው ነው::

ሕወሓት በዚህ ሳምንት የራሱ የውስጥ ሽኩቻ እና የኢሕኣዴግ አባል ድርጅቶች የለውጥ እንቅስቃሴ አጣብቂኝ ውስጥ እንደከተቱት ለመውጣት በሚይደርገው መፍጨርጨር ሌላ አዳዲስ የሽብር ድርጊቶቹን ማንገውለል ይዟል:: ያው እንደተለመደው ድሮም እጆች ሁሉ ወደ ሕወሓት ቢያመለክቱም የአሁኑ ለየት ብሎ የራሱን ጣቶች ወደ ራሱ መቀሰሩ ነው::

ሕወሓት/ኢሕኣዴግ እና የሙስሊሙ ጥያቄዎች
ኢሕኣዸግ በህገመንግስቱ መሰረት በወንጀል መከሰስ አለበት::

ሓይማኖት እና ፖለቲካ እንደማይገናኙ መንግስት በሃይማኖት ጣልቃ እንደማይገባ በሕገመንግስቱ የተረጋገጠ ጉዳይ መሆኑ እየታወቀ በገዢው ፓርቲ በኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ላይ የተፈጸመው ወንጀል በሕገመንግስቱ መሰረት ወንጀለኛው ሕወሓት/ኢሕኣዴግ መሆኑ በይፋ ተረጋግቷል:: እስካሁን ድረስ መልስ ያልተገኘለት የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ጥያቄ በመንግስት ማነቆ እና በባለስልጣናቱ ሽብር የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ንጽሕናቸው እየታወቀ ወህኒ ቤት አስቀምጦ የራሱን ፖለቲካዊ መጅሊስ መገንብቱን በይፋ አምኗል:: በሽብር ስልት የገነባው መጅሊስ ላለው ስርኣት ትዛዥ የሚሆን እና የፖለቲካ ታማኞችን ያቀፈ መሆኑ በይፋ ማመኑ ሕወሓት ምን ያህል በሃይማኖቶች ውስጥ አብዮታዊ ዲሞክራሲን አስርጾ ለአገዛዙ በሚያመቸው መንገድ እንደቀረጸው አመነም አላመነም የታወቀውን ጉዳይ ግን በአቦይ ስብሃት በኩል ዘርግፎታል::ከቦሌ የተፈጠረው ሕገወጥ መጅሊስ በህያሉ እና አሸባሪው ሕወሓት እና መሪዎቹ ተጀምሮ እና ተስፋፍቶ እስከሽልምት ደርሶ መንግስት ሕገመንግስቱን እንደጣሰ እና በሃይማኖት ውስጥ ጣልቃ እንደገብ ሲያረጋግጥ የሙስሊሙን መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎችን ንጽሕና እንዳመነ እና ሴራው ለሽንፈት እንደዳረገው ተረጋግጥውል::

ሕወሓት ቅጥረኞቹ እና ተቃዋሚ ፓርቲዎች

እንደፈለጉ ቢናገሩ የማይታሰሩ ሰዎች አሉ አዎ አሉ ከተቃዋሚ ፓርቲ ከጋዜጠኞች እንዲሁም ከሌላው ዘርፍ…ስም መጠቃቀስ አስፈላጊ ባይሆንም ሕወሓት ይህን ሰሞን በየፓርቲው አስርጎ ባስገባቸው ቅጥረኞቹ አማካኝነት..የኣንድነት ኣባላትን
በፓርቲው ውስጥ ጥሩ እንቅስቃሴ የሚያደርጉትን እና ለገዢው ፈታኝ የሆኑ የፖለቲካ ሃሳቦችን የሚያመነጩትን ለይቶ …እንዲሁም የማይታሰሩ እንደፈለጉ የሚለፈልፉ እና የሚጽፉ ጋዜጠኞች እንደ እስክንድር ነጋ ያሉትን ጠንካሮችን አሳልፈው በ24 ሰዓት ያስያዙ ….. አሁንም ሌሎችን ከፕሬሱ እንዲወገዱ የሚሰሩ አስመሳዮች ወዘተ…..

የኣንድነት አመራሮች በሰበብ አስባብ የጻፉትን ጹሁፍ ተገን በማድረግ እና የፈጠራ ምርመራ ጀምሮ ለማዋከብ እና ለማወናበድ እንደገሃዳዊ ምክንያት ተያዘ እንጂ ዋናው የስርኣቱ አላማ ጠንካራ አመራር አባላትን በማሰር ከወዲሁ ፓርቲዉን ለማዳከም የታቀደ እና በውስጥ ቅጥረኞች እየተሰራ ያለው የብተና እና ፓርቲውን በቅጥረኞች ቁጥጥር ስር አውሎ ፓርቲውን ታማኝ ተቃዋሚ ለማድረግ የታቀዳ ሴራ ነው::

የሃይለማርያም መለሳዊ መግለጫ

ጠቅላይ ሚንስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ በወቅታዊ የሀገሪቱ ጉዳይ ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡ ሲሆን የህዳሴ ግድብ ግንባታና ከሱዳንና ግብጽ ጋር ያለውን ድርድር አስመልክቶ ድርድሩ እንዳላለቀ ፣ የኢትዮ ሱዳን የድንበር መካለልን በተመለከተ እየተናፈሰ ያለውን መሬት ለሱዳን ተሰጥቷል የሚለውን ወሬ አስመልክቶም ይህን መሰል ወሬዎች ምርጫ ሊደርስ አካባቢ መነዛታቸው አዲስ አይደለም ያሉ ቢሆንም የድንበሩን ጉዳይ በተመለከተ ካርቱም ሄደው የፈረሙት ፊርማ ሳይደርቅ እንደለመዱት ዘባርቀዋል::

እስከ 6 ወር ድረስ ህዝቡ ይዘናጋል በሚል እደምታ መግለጫቸውን የሰጥኡት የሕወሓቱ የሃሰት ስልጡን ሓይለማርያም የቴሌኮም ችግር በማስፋፊያው ስራ ሳቢያ የተፈጠረ ነው ከ6 ወራት በኋላ ለውጥ ይታያል ሲሉ ሰው ይታዘበኛል ያልፈጠረባቸው አቶ ሃይለማርያም አይን ቀቅለው ሳያበሏቸዋልቀሩም መሰል የአዲስ አበባ የውሃ ችግርንም በተመለከተ 24 ሰዓት ውሃ የሚያገኘው የከተማዋ ክፍል 75% ብቻ እንደሆነና የተቀረውንም ለማስተካከል መንግስት ይሰራል በማለት ከባድ የሆነ ውሸት ለጥፈው ዞር ብለዋል:: የውጭ ምንዛሪ እጥረትንና የባንኮች የብድር መስጠት ብቃት መመናመንን አስመልክቶ የተነሳውን ጥያቄ ጠቅላይ ሚንስትሩየእውቀት እጥረት ይሁን ሃቅን ማድበስበስ በቂ ማብራሪያ አልሰጡበትም፡፡ምንሊክ ሳልሳዊ

ከአንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) እና ከመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) የተሰጠ መግለጫ !!!! ብአዴን ኢህአዴግ የአማራን ህዝብ የመምራት የሞራል ልዕልና የለውም፤ ህዝብ ያዋረዱ አመራሮቹም ለፍርድ ሊቀርቡ ይገባል፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ እንደሚገነዘበው በዚህች ታሪካዊት እና የጥቁር ህዝብ ድል ማዕከል፤ የነፃነት ተምሳሌትና የአፍሪካ ህዝብ ኩራት በሆነች ሀገር የኋላ ዘመን ውጣ ውረድ ውስጥ ሰፊው የአማራ ህዝብ ከመላው […]

የካቲት 11 የተፈበረከው ሕወሃት ማለት እጅግ አሳፋሪ እና አሸባሪ የማፊያ ድርጅት ነው::

ሕወሓት ….. በምንሊክ ሳልሳዊ
= ህጻናትን በማደጎ እና በጉዲፈቻ ስም ይቸበችባል:: እንዲሁም በወሲብ ንግድ ውስጥ በመሰማራት
በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር የደላላ ኤጀንቶችን በማቋቋም ታዳጊ ወጣት ሴቶችን
ለሽያጭ ::ባለስልጣናቱ በብዙ መቶ ሺዎች ዶላሮች አፍሰዋል ::

= በስሩ ያደራጃቸውን ቡድኖች የዲፕሎማቲክ ካባ በማልበስ በአደንዛዥ እጽ ዝውውር ላይ እንዲሰማሩ እና ዲፕሎማቶች ከፍተሻ ነጻ ስለሆኑ በረቀቀ ስልት ካናቢስ ሃሺሽ እና መሰል ድራጎችን በማዘዋወር ስራ እና ንግድ ላይ ተሰማርቷል::

= ህገወጥ የሰው ዝውውር እና የአካላት ስርቆት ድርጊቶችን ይፈጽማል:: ወደ ተለያዩ የመካከለኛ ምስራቅ እና ደቡብ አፍሪካ የመሳሰሉ ሃገራት በህገወጥ መንገድ ሰዎችን በማዘዋወር ከባድ ወንጀል እየተሰራ ሲሆን ይህንን ስራ የሚሰሩ አካላትን ሰርቀው ሰውን በመግደል የሚከብሩ ደላሎች ከባለስልታናት ትእዛዝ የሚወርድላቸው እና ሕወሓት በአባልነት የመዘገባቸው ነው::

= በግብጽ እና በየመን በረሃዎች እንዲሁም በሱዳን ሊቢያ ድንበር ላይ ስደተኞችን በማፈን የተለያዩ የገንዘብ መጠኖችን በመጠየቅ ቤተሰብን በማስጨነቅ ሴቶችን በመድፈር አከላትን አውጥቶ በመሸጥ ስራ ላይ የተሰማሩት የሕወሓት አባላት የሆኑ ግለሰቦች ናቸው::

= የአገሪቷን መሬት ለውጭ ባለሃብቶች በመሸጥ ወገንን ለስራ ጥነት ለስደት ለመፈናቀል የሚዳርጉት በሕወሓት ሃይሎች የሚመሩት በአቋራጭ የከበሩ አባላቱ ናቸው::ከተላያዩ አከባቢዎች ለውጪ ኢንቨስተሮች በሚል ስም የተሸጡ መሬቶች የሽያጭ ገቢያቸው የት እንደሄደ እንደማይታወቅ እና ሸጡ የተባሉት ክልሎች እንኳን ለአከባቢው ነዋሪዎች ካሳ ያልከፈሉበት እና ያላቋቋሙበት ሁኔታዎች በገፍ ታይተዋል::

= በተለያዩ ጊዜያት በአዲስ አበባ እና በክልሎች ቦንቦችን በማፈንዳት ንጹሃን ዜጎችን በመግደል እና በማቁሰል የሽብር ስራ ላይ የተሰማራው ሕወሓት የተቃወሙትን ሁሉ የሚወነጅልበት አንዱ ብልሃቱ ቢሆንም ሞኝነቱ አዘንብሎ ተገኝቷል::አልቸባብን እና ሃማስን ከመሳሰሉ አሸባሪ ከሞባሉ ድርጅቶች ጋር የሁለትዮች ምስጢራዊ ስምምነት በመፍጠር ምስራቅ አፍሪካ እና መካከለጫው ምስራቅ ላይ ከፍተኛ ስጋት ለመፍጠር እና ዜጎቹን ለማስፈራራት እጅግ አሳፋሪ እና ዘግናኝ ድርጊቶችን ፈጽሟል: በመፈጸም ላይ ይገኛል:: ምንሊክ ሳልሳዊ

የሀ/ስብከቱ ጽ/ቤት ደግሞ በነገው ዕለት ለቋሚ ሲኖዶሱ ያስረክባል የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከትን የተቋማዊ ለውጥ አመራር ሲያጠና የቆየው የባለሞያ ቡድን በዛሬው ዕለት የአደረጃጀትና አሠራር ጥናት ሰነዱን ለሀ/ስብከቱ በይፋ ያስረክባል፡፡ ዛሬ፣ የካቲት ፮ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም ረፋድ ላይ በሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት በሚካሔደው የርክክብ እና ምስጋና መርሐ ግብር፣ 15 አባላት ያሉት የባለሞያ ቡድኑ ከአንድ ሺሕ በላይ አጠቃላይ ገጾች …

አሰግድ ኣረጋ (ኮለምበስ – ኦሃዮ)
ጤፍ Teff. Photo by Peter Bregg

ሰሞኑን ስለጤፍ ምርታችን የባዕዳኑ ብዙኀን መገናኛ አጀብ እያሉን ነው፤ ለዘመናት የተደበቀው የዘሩ ገመና መጋለጡን እየነገሩን ነው፤ ስለያዘው ንጥረ ነገር፣ ስለጤናማነቱ፣ በምዕራቡ ገበያ ስለመፈለጉ፣ ከሁለም በላይ ስለ ውጭ ምንዛሪ ምንጭነቱ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም Prof. Al-Mariamፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም – ነጻነት ለሀገሬ)

ፈረሰኛው ረሃብ ኢትዮጵያ ላይ አያነጣጠረ ነው!
ባለፈው ሳምንት ኤንቢሲ/NBC የተባለው የዜና ወኪል በኢትዮጵያ እየተንፏቀቀ በመጣው ረኃብ ላይ ያደረገውን ጥናታዊ ዘገባ ዋቢ በማድረግ በማርቲን ጌይስለር አማካይነት ከዚህ በታች የተመለከተውን ሀተታ ለአየር አብቅቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

እንደ መግቢያ ቅጥፈት የስብዕና መሽርሽር ምልክት ነው፡፡ የግለሰቦች ስብሰብ በሚፈጠረው ማህበረሰብ ውስጥ የስብዕና መሸርሸር ሲበራከት ማህረሰበባዊ አደጋ ሰላማዊ አኗኗሩን ማነዋወጥ ይጀምራል ፡፡ ማህበራዊ ቀውስ በሰፈነበት ደግሞ ከግለሰቦቹ ውድቀት የሚነሳው ገፊ ምክንያት እንደ ማህበረሰብ የተገነቡ የጋራ እሴቶችን ይንዳል፡፡ ባህል ፤ ሃይማኖት ፣ታሪክ ፣ወግ እና ልማዶች ሁሉ መሰረታዊ ይዘታቸውን የላቁና የሰው ልጅ እንደ እንስሳ በቀላሉ ከእንቱ ነገሮች […]

ታላላቆቹ መንግሥታት ፤ ዩናይትድ ስቴትስ፤ ሩሲያ፣ ቻይና ፣ ህንድና ሌሎችም ኅዋን በማሰስ ፤ ጨረቃንና ማርስን ዒላማ በማድረግ ፉክክራቸውን እንደቀጠሉ ናቸው። አዳዲስ የኅዋ ጣቢያዎችን የማቋቋም እቅድም አላቸው። የተጠቀሱት ሀገራት ብቻ ሳይሆኑ ፤

የካቲት ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአርሴማ ቤተክርስቲያን የተነሳውን የውስጥ ችግር ተከትሎ ችግሩን ለመፍታት የተመረጡት የሰበካ ጉባኤ አባላት ታስረዋል። በህዝቡ የተመረጡት 15ቱ ሽማግሌዎች ችግሩን ለመፍታት በሚንቀሳቀሱበት ጊዜ የቀጠናው ሃላፊ የሆኑት አቡነ ገብርኤል የሰበካ ጉባኤ አባላቱ እንዲበተኑና ችግሩን ለመፍታት እንደሚሞክሩ መግለጻቸው ህዝቡን አስቆጥቷል። ጳጳሱ  ለፌደራል ፖሊሶች በማመልከት የአገር ሽማግሌዎች እንዲታሰሩ ማድረጋቸውን የሚናገሩት የአካባቢው ነዋሪዎች፣ …

የካቲት ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአማራ ተወላጆች ላይ በጅምላ ፀያፍ ስድብ የሰነዘሩት የብአዴኑ አመራር እና የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የ አቶ ኣለምነው መኮነን መኖሪያ ቤት በድንጋይ መደብደቡን ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ የዘገበ ሲሆን፣ ዜናውን ተከትሎ ኢሳት ባደረገው ማጣራት የባለስልጣኑ መኖሪያ ቤት በ11 ፖሊሶች ሌትና ቀን እየተጠበቀ ነው። አቶ አለምነው የአማራው ህዝብ የትምክህት ለሃጩን …

የካቲት ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ  በጽ/ቤታቸው ለአገር ውስጥ ጋዜጠኞች በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ከፎርቹን ጋዜጣ ማኔጂንግ ኤዲተር አቶ ታምራት ገብረጊዮርጊስ በቀረበላቸው ጥያቄ በመቆጣት ዘለፋ ሰነዘሩ፡፡ አቶ ታምራት ለጠ/ሚኒስትሩ ያቀረቡት ጥያቄ በአሁን ሰዓት አገሪትዋን የሚመራት ማንነው ነው የሚል ይዘት ያለው ሲሆን ጠ/ሚኒስትሩም ብስጭታቸውን በምላሻቸው ወቅት አንጸባርቀዋል፡፡ ጠ/ሚኒስትሩ ለዚህ ጥያቄ ቀጥተኛ …

አሜሪካዊዉ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር እንደሚሉት የደቡብ ሱዳን፣ የማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ እና የኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክን ጦርነት፣ግጭትና ፖለቲካዊ ቀዉስን ለማስቆም ለማስቆም በሚደረገዉ ጥረት መንግሥታቸዉ ጉሉሕ አስተዋፅኦ እያደረገ ነዉ

የዓለም ኣገሮች እንደየ ገቢያቸው በዓለም ባንክ ትንቢያ መሰረት የበለፀጉ መካከለኛ ገቢ ያላቸው እና ደኃ ኣገሮች ተብለው በሶስት ይከፈላሉ። በዚሁ መሰረት ዓመታዊ የኣገር ውስጥ ጥቅል ገቢያቸው ለህዝብ ቁጥር ተካፍሎ የእያንዳንዱ ዜጋ የነብስ ወከፍ ገቢ በዓመት ከ 12 000 የአሜሪካን ዶላር በላይ ከሆነ ከፍተኛ

ለደቡብ ሱዳን ነፃነት በጋራ የታገሉት የሐገሪቱ ፖለቲከኞች ካለፈዉ ታሕሳስ ጀምሮ የለየለት ዉጊያ ገጥመዋል።ጦርነቱን ለማስቆም የሚደረገዉ ሁለተኛ ዙር ድርድር ከታቀደለት ቀን ተሸጋሽጎ ቢጀመርም ተፋላሚ ወገኖች መካሰሳቸዉ መቀጠሉ ነዉ የተሰማዉ።

የካቲት ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የክልሉ የፍትህ ቢሮ በክልሉ ውስጥ ለሚገኙ ፍርድ ቤቶች በጻፈው ደብዳቤ ማንኛውም ባለጉዳይ አቤቱታዎችን በኮምፒዩተር ካላስጻፈ ጉዳዩ እንዳይታይለት ወስኗል። በክልሉ የሚገኙ ዳኞች በበኩላቸው ውሳኔው የህዝቡን የኑሮ ሁኔታ እና የእድገት ደረጃ ግምት ውስጥ ያላስገባ ነው ይላል። ዳኞች እንደሚሉት አብዛኛው ህዝብ አቤቱታዎችን አስጽፎ የሚያቀርበው በወረቀትና በእስክር ቢቶ ሆኖ ሳለ፣ የድሆችን …

የካቲት ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የግብፅ የውኃና መስኖ ሚኒስትር መሐመድ አብዱል ሙታሊብ ከኢትዮጵያ አቻቸው ጋር የሁለትዮሽ ውይይት ለማድረግ በጠየቁት መሠረት ባለፈው ሰኞ አዲስ አበባ ቢገቡም፣ የዓባይ ግድብ ግንባታ እንዲቆም በመጠየቃቸው ውይይቱ በሰዓታት ውስጥ ተቋረጠ፡፡ ሪፖርተር እንደዘገበው  የግብፅ ሚኒስትር ከኢትዮጵያ አቻቸው አቶ አለማየሁ ተገኑና ከባልደረቦቻቸው፣ እንዲሁም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከተወከሉ ባለሙያዎች ጋር ባለፈው …

የካቲት ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአማራ ክልል ቋሪትና ጃቢጠህናን ወረዳዎች ይካሄድ የነበረው መረን የለቀቀ ህገወጥ የአራጣ ብድር ስርዓት በአስከተለው ቀውስ ከ250 በላይ ጠንካራ ነጋዴዎች ተሰደዋል ተባለ፡፡ ከፍተኛ ማታለል የነበረበት ይህ ህገወጥ የአራጣ ብድር ስርዓት ነጋዴዎችን ባዶ ያስቀረና ያሰደደ ከመሆኑ ባለፈ ብዙዎችን ለእብደትና ለቤት መፍረስ ዳርጓል ሲሉ ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉና ከ121 ሺህ ብር …