የደቡብ ሱዳን የቀድሞ ባለሥልጣናት ያዲሳባ መግለጫ

በምሥራቅ አፍሪካ ሃገሮቹ የጋራ ልማት ባለሥልጣን – ኢጋድ አማካኝነት በሚካሄደው ድርድር ለመሳተፍ አዲስ አበባ የገቡት ሰባት ከእሥር የተፈቱ የቀድሞ የደቡብ ሱዳን ከፍተኛ ባለሥልጣናት የተቀሩት አራት እሥረኞችም እንዲፈቱ ጥሪ አቀረቡ።