በጀርመን ፍርድ ቤት ብይን ያገኙት ሩዋንዳዊ
ከ 20 ዓመት በፊት ሩዋንዳ ውስጥ ሙቩምባ በተባለች ሰሜን ምሥራቃዊ ከተማ ከንቲባ የነበሩት ኦንስፎር ሩዋቡኮምብ የተባሉት የ 54 ዓመት ጎልማሳ ፣ ያኔ በአንድ ቤተ-ክርስቲያን የተጠለሉ ሩዋንዳውያን እንዲጨፈጨፉ በማድረጋቸው ፣ ፍራንክፈርት ጀርመን ውስጥ
ከ 20 ዓመት በፊት ሩዋንዳ ውስጥ ሙቩምባ በተባለች ሰሜን ምሥራቃዊ ከተማ ከንቲባ የነበሩት ኦንስፎር ሩዋቡኮምብ የተባሉት የ 54 ዓመት ጎልማሳ ፣ ያኔ በአንድ ቤተ-ክርስቲያን የተጠለሉ ሩዋንዳውያን እንዲጨፈጨፉ በማድረጋቸው ፣ ፍራንክፈርት ጀርመን ውስጥ
ኢትዮጵያ እጅግ ደሀ ከሚባሉት ጥቂት የዓለማችን ኣገሮች መካከል ብትመደብም በሌላ ጎኗ ደግሞ በተፈጥሮ ኃብት የበለጸጉ ከሚባሉት አካባቢዎች መካከልም ያንኑ ያህል ትጠቀሳለች። ለዓብነት ያህልም ለግብርና ምቹ በሆነ ሰፊ መሬት የታደለችው ኢትዮጵያ በቡና ምርትም ቀዳሚ ከሚባሉት መካከል ስትሆን በእንስሳት ሀብቷም እንዲሁ ከዓለም 10ኛ ናት።
ኢትዮጵያ ዉስጥ የመሬትና ዉሃ ቅርምት ማኅበረሰቡን እየጎዳ እንደሚገኝ ዓለም ዓቀፉ የመብት ተሟጋች ሂዉማን ራይትስ ዎች አመለከተ። ድርጅቱ ይህን አመልክቶ ባወጣዉ ዘገባ በዚህ ምክንያትም ኢትዮጵያና ኬንያ ዉስጥ 500,000 አርብቶ አደሮች ለችግር መጋለጣቸዉን ገልጿል።
የዚህ ዕትም እንግዳችን ታዋቂው አርቲስትና አክቲቪስት ታማኝ በየነ ነው። ረዥም ጊዜያት በኪነ-ጥበብ ሙያ ላይ የቆየው ታማኝ፣ የደርግ መውደቅን ተከትሎ ኢሕአዴግ የአራት ኪሎውን ቤተ-መንግስት ከተቆጣጠረበት ዕለት (ግንቦት 20/1983 ዓ.ም) ጀምሮ በድፍረት የስርዓቱን አምባገነንነት፣ ከፋፋይነት፣ በብሔራዊ ጥቅም ላይ ያለውን ቸልተኝነት… ጠቅሶ ተችቷል። ይህንንም ተከትሎ በደረሰበት ከባድ ጫና፣ እስርና ግርፋት ሀገሩን ለቆ ለመውጣት ተገድዷል። በስደት በሚኖርባት አሜሪካም ያለውን የተከፋፈለ የተቃውሞ ፖለቲካ አስተባብሮ ከመምራቱም በላይ በየጊዜው የህሊና እስረኞች እንዲፈቱ የሚጠይቁና መሰል ሀገራዊ ጉዳዮችን በተመለከተ የሚዘጋጁ የተቃውሞ ሰልፎችን አስተባብሮ መርቷል። በዚህም በመላው ዓለም በሚገኙ በርካታ ኢትዮጵያውያን ከበሬታን አትርፏል። አክትቪስት ታማኝ በየነ፣ ከተመስገን ደሳለኝ ጋር ያደረገው ቃለ-መጠይቅ እንደሚከተለው ተዘጋጅቷል።
iframe

የደህንነት ስጋት ፤የአስተዳደር ብልሹነት እና የዘረኝነት መድልዎን የሚቃወም የአይሮፕላን ጠለፋ
ታዋቂነታችን በድርቅ በድህነት ብሎም በጭፍጨፋ ደሞ በሰብኣዊ መብት ጥሰት
ምንሊክ ሳልሳዊ :- በሃገሪቱ የተንሰራፋውን የደህንነት ስጋት በመልካም አስተዳደር እና በዘረኝነት ላይ የተመሰረተ አድልዎ ተከትሎ የተደረገው የአይሮፕላን ጠለፋ ህዝቦች በገዛ አገራቸው በደህንነት ላይ ምን ያህል ስጋት እንዳጠላበት እና በመኖር ህልውናቸው ላይ ኢትዮጵያውያን የስርአቱ ፖሊሲዎች እያሸማቀቋቸው እንደሚገኙ አለም ካለፈው ጊዘ በተሻለ እውነታውን ፍንትው አድርጎ እየመሰከረ ነው።
የሕወሓት መራሹ ጁንታ ወደ ስልጣን በጠበንጃ ሃይል ከመጣ ጀምሮ በአለም አቀፍ ደረጃ የተደነገጉ የሰብኣዊ መብት ህጎችን ካለምንም ማርቅርቅ እና ድካም ከሌሎች በመገልበጥ በወረቀት ላይ ከማስፈሩም በተጨማሪ ጥናቶች እንደሚጠቁሙት በአለም ላይ የሰው አገር ህግን እና አለማቀፍ ድንጋጌን ከሃገራችን ሁኔታ ጋር ሳይገናዘቡ በስፋት በደመነፍስ ለፍጆታ የተጻፈበት ሃገር ኢትዮጵያ ብቻ ሲሆን በየትኛውም አለም ሃገራት ያልተከሰተ የአለም አቀፍ ህጎችን ግልባጭ በከፊል በህገመንግስት እንዲሁም የገዢ ፓርቲን የፖለቲካ ፕሮግራም በከፊል ደባልቆ በጋር እንደ አውራ ህግ የወጣባት ሃገር ብትኖር ኢትዮጵያ ብቻ ናት::ኢትዮጵያ በታሪኳ ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ የመብቶች ሕጋዊነት በተጨበጨበለት ሁኔታ እና ይህ በማይባል ደረጃ የተደነገጉባት አገር ነች፡፡ እንግዲህ ይህ ሆኖ እያለ ነው በአገሪቱ የመብቶች ጥሰት ጉዳይ ከአገሪቱ ብሔራዊ አነታራኪ ፖለቲካዊ አጀንዳነት አልፎ ዓለም አቀፍ አጀንዳ ሆኖ ተገኝቷል፡፡
ጥላቻ በፈጠረው ፍርሃት ብቻ የሃገሪቱን ህጎች ዜጎች ለመጥለፍ እያዋሉት ነው::
የቀድሞ መንግስትን ሽንፈት ተከትሎ በኢትዮጵያ የሰብኣዊ መብት ጥሰቶች የፍፃሜ ምዕራፍ ይሆናል ተብሎ ተስፋ ተደርጎ ነበር፡፡ ነገር ግን ጭራሽ ብሶበት ቁጭ አለ፡፡ የሕወሓት ወንበሩን መቆጣጠር ተንተርሶ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያሉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በተለይም ሒዩማን ራይት ዎችና አምነስቲ ኢንተርናሽናል የወያኔን ጁንታ በሰብዓዊ መብት ጥሰት በማብጠልጠል ነበር የተቀበሉት፡፡ ባለፉት ሃያ ሁለት ዓመታት የሰብኣዊ መብት ጥያቄዎች አቤቱታ ማሰማታቸውን አላቆሙም፡፡ ጋዜጠኞችን የሃሳብ ነጻነት ከሚገድብ ጥቃት በመከላከል ላይ የተሰማሩ የመብት አስከባሪ ድርጅቶችም ወያኔ በሚፈጥረው ከባድ የሰብኣዊ መብት ጥሰት በየጊዜው መክሰስ ሥራቸው ሆኗል::የአሜሪካው ስቴት ዲፓርትመንት በየጊዜው በሚያወጣው ዓመታዊ መግለጫው ወያኔን በሰብዓዊ መብት ጥሰትና የፖለቲካ መብቶችን ማፈን ይከሰዋል፡፡ ባሁን ወቅትየእነኚህን አካላት መግለጫዎች የታወቁ ዓለም አቀፍ መገናኛ ድርጅቶች በመቀባበል ኢትዮጵያ የዜጎቿን መብቶች በመጣስና በማፈን ወደር የሌላት አገር እንደሆነች ዓለም እንዲረዳው እያደረጉ ናቸው፡፡
ኢትዮጵያ በአስከፊ ድርቅና ረሃብ ለመታወቅ እንደበቃችው ሁሉ ወያኔ የዜጎችን መብቶች በመጣስና በማፈን እንዲሁም በሰብዓዊነት ላይ በሚፈጽመው ወንጀል በዓለም ላይ ታዋቂነትን እያተረፈ ነው፡፡ ይህ ብቻ አይደለም;ወያኔ የፖለቲካ ተቀናቃኞችን መብቶች ለመጣስ ስለሚጠቀምባቸው ዘደዎች የሚቀርቡ ማስረጃዎች እና ማብራሪዎች እጅግ ዘግናኝ ናቸው፡፡የወያኔ መሪዎች የፖለቲካ ተቀናቃኖችን ለማዳከም ሲሉ ንፁኃንን ወንጀለኛ የሚያደርግ ዘዴዎችን ሥራ ላይ እንደሚያውሉ በተለያዩ ይፋዊ ሪፖርቶች ላይ ሁሉ ከነማስረጃው እየተነገረ ይገኛል::
የህ የሰብኣዊ መብጥ ጥሰት እየተባባሰ የሚሄድበት ምክንያት ወይኔ በአብዛኛው ካድሬዎች ዘንድ በስፋት ሰርጾ እንዲገባ ያደረገው የተቃዋሚዎች ጥላቻ እና እንዲሁም የተቃዋሚው ቡድን የትግል አቅጣጫው በተመሳሳይ መልኩ በጥላቻ ላይ የተመረኮዘ መሆኑ ነው::ተቃዋሚዎች የታጠቁ ሃይላት ባለመሆናቸው የመርሃቸው እንቅስቃሴ የተገደበ እና ለፖለቲካ እና ለሚዲያ ፍጆታ የዋለ ተዳፍኖ የሚገኝ ሲሆን የወያኔው ግን በታጠቁ የጸጥታ ሃይሎች እና በፖለቲካ ማጭበርበሮች ላይ ስለተመረኮዘ ካድሬዎቹ በተሰጣቸው የጥላቻ ተግዳሮት እና ወያኔያዊ ስልቶች የፈጠሩትን ጥቅማጥቅሞች ጠብቀው ለማቆየት ሲባል ጥላቻ በፈጠረው ፍርሃት ብቻ የሃገሪቱን ህጎች ዜጎች ለመጥለፍ እያዋሉት ነው::
ይህ ፍርሃት እና ጥላቻ በወያኔ ከትልቅ እስከ ትንሽ ካድሬዎች አናት ውስጥ ስር ለስር በመስደድ የፈጠረው ነገር ቢኖር ማንኛውም ዜጋ ተቃውሞ ካሰማ በወንጀለኛነት በመፈረጅ በማሳደድ በማጥፋት እረፍት ለማግኘት እና ጥቅማቸውን ለማስጠበቅ ሲራወጡ የህዝብን የበላይነት አፈር ከተውታል::ማእከላዊ የወያኔ ጁንታ በዲሞክራሲ ባለመወቀጣቸው የህጎችን የበላይነት ማረጋገጥ ካለመቻሉም በተጨማሪ በህዝብ እና በዲሞክራሲ ላይ በደሎችን የሚያደርሱ ባለስልጣናት የሚጠየቁት በሃገሪቱ የበላይ ህጎች ሳይሆን በወያኔያዊ የፓርቲ መመሪያዎች በመሆኑ በጥቅም መተሳሰር በፈጠርው ዝግ መንገድ የሰብኣዊ መብት ጥሰቶች እየተብራከቱም ከመሆኑ አልፎ የእለት ተእለት ተግባራት አካል ሆነዋል:: የአይሮፕላን ጠለፋዉም ከላይ ከገለጽኩት ጉዳዮች ጋር ቁርኝት ያለውና በሃገሪቱ እየተተገበረ ያለውን የቡድን አምባገነንነት በማጋለጥ ረገድ ትልቁን ሚና ተጫውቷል።
የፓትርያርኩ ልዩ ጽ/ቤት በጓሮ በር ለሚገቡ ሙሰኞችና ጎጠኞች ሽፋን መስጠቱን ቀጥሎበታል፡፡ ልዩ ጽ/ቤቱ እንደቀድሞው ጊዜ ኹሉ ዛሬም በማይመለከተው ጉዳይ ጣልቃ እየገባ የሕገ ቤተ ክርስቲያን ጥሰት እየፈጸመ ይገኛል፡፡ ሙሰኞችና ጎጠኞች የበላይነት ይዘው በተቆጣጠሩት ጽ/ቤት የቅ/ሲኖዶሱን ውሳኔ እየተላለፈ በሚፈጽመው ኢ-ፍትሐዊ ተግባር የመንበረ ፓትርያርኩን ተቀባይነትና አገልጋዩና ምእመኑ በመልካም አስተዳደር መስፈን ላይ ያለው እምነት እንዲሸረሸር መንሥኤ እየኾነ ይገኛል፡፡ ከላይ …![]()
ESAT Radio Daily Broadcast to Ethiopia. Frequency Details: 7 days a week Short Wave (SW) from 8:00 pm to 9:00 pm (Local Ethiopian Time) 19 Meter Band 15355 kHz, 15360 kHz, 15365 kHz, 15370 kHz, 15380 kHz, 15385 kHz and 15390 kHz Download/Listen
ESAT Radio Daily Broadcast to Ethiopia. Frequency Details: 7 days a week Short Wave (SW) from 8:00 pm to 9:00 pm (Local Ethiopian Time) 19 Meter Band 15355 kHz, 15360 kHz, 15365 kHz, 15370 kHz, 15380 kHz, 15385 kHz and 15390 kHz Download/Listen
የካቲት 16 በሚደረገዉ የባህር ዳር ሰልፍ፣ መኢአድ እና አንድነት በጋራ የጠሩት ነዉ። ድርጅቶች እንዲህ ሲተባበሩ ያስደስታል። የተናጥል የብቻ ጉዞ የትም አይደርስምና። ይህ ሰልፍ ምንም እንኳን የብሃአዴን አንድ አመራር አባል ለፍርድ እንዲቀርቡ የሚጠይቅ ቢሆንም፣ ጉዳዩ ከአንድ ግለሰብ ያለፈ መሆኑን መረዳት አለብን። ባለስልጣኑ ጸያፍና ነውረኛ አስተያየት ሰጡ የሚል ክስ ሲቀርበባቸው ፣ ገዚው ፓርቲ ፣ ግድ የለም፣ አሁኑኑ […]
News, Ask the Doctor, Agriculture and Business
እየጠረቃ ከመጣዉ የአፍሪቃ ምጣኔ ሐብት ከብዙዎቹ ቀድማ የገባች ብዙ የተጠቀመችና የምትጠቀም አዲት ሐገር አለች። ቻይና።እንደ ጎሮጎሮሳዉያኑ አቆጣጠር በሁለት ሺሕ አስራ-ሁለት ቻይና ከአፍሪቃ ጋር ያደረገችዉ የንግድ ልዉዉጥ ሁለት መቶ ቢሊዮን ዶላር ነዉ።
የካቲት ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ ቁጥር 702 የሆነውን አውሮፕላን በመጥለፍ ጄኔቫ ስዊዘርላንድ ያሳረፈው ረዳት ፓይለት ሃይለመድህን አበራ እስካሁን ድረስ የጠለፋውን መንስኤና ምክንያት በግልጽ የመናገር እድል ባለማግኘቱ የአለም የመገናኛ ብዙሃን የተለያዩ አስተያየቶችን እየሰጡ ነው። አንዳንዶች በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው አስከፊ ጭቆናና ፓይለቱ አውሮፕላኑን እንዲጠልፍ እንዳነሳሳው ሲገልጹ ሌሎች ወገኖች ደግሞ …
የካቲት ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ጋዜጠኛ ዮሃንስ ገ/እግዚያብሄር ማንነታቸው ያልታወቁ ግለሰቦች በመኪና እንደገጩትና “ገና እንገድልሃለን” የሚል ዛቻ እንደሰነዘሩበት ለፍኖተ ነፃነት መናገሩን ጋዜጣው ዘግቧል። “ጋዜጠኛው ከአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሃብታሙ አያሌው ጋር በፓርቲው ጽ/ቤት ቃለምልልስ አድርጎ ወደ መገናኛ አካባቢ ሲደርስ ኮድ 1 የታርጋ ቁጥር18345 የሆነ ሚኒባስ ታክሲ ሆነ ብሎ አደጋ …
የካቲት ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኦህዴድ ሊቀመንበርና የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አለማየሁ አቶምሳ የስልጣን መልቀቂያ ጥያቄ ማቅረባቸውን ተከትሎ፣ ምከር ቤቱ እንዳሰናበታቸው የመንግስት የመገናኛ ብዙሀን ዘግበዋል። አቶ አለማየሁ መታመማቸው ከተዘገበ የቆየ ቢሆንም እስካሁን ከስልጣን ሳይወርዱ ቆይተው አሁን ለምን ለማንሳት እንደተፈለገ ግልጽ አይደለም። በአፋር በቅርቡ በሚካሄደው የምክር ቤት ስበሰባ ላይ ፕ/ት አሊ ሴሮ …
የዓለም ዜና
የካቲት ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአዲስ አበባ የትራንስፖርት ችግርን ለመቅረፍ ይረዳሉ በሚል በብረታብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ተገጣጥመው ወደስራ ከተሰማሩ አውቶቡሶች የቴክኒክ አቁዋማቸው ብቃት መጉዋደልና የመለዋወጫ እጦት ጋር በተያያዘ በየቦታው በብልሽት በመቆማቸው ምክንያት የአዲስአበባ ከተማ የትራንስፖርት እጥረት እንዲባባስ አስተዋጽኦ ማድረጋቸው ተሰምቷል። ከአዲስአበባ መንገድ ትራንስፖርት ቢሮ የተገኘ መረጃ እንዳመለከተው በአሁኑ ወቅት በኮርፖሬሽኑ ከተገጣጠሙ 500 …
የካቲት ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፌብሩዋሪ 18//2014 በኤድመንድ ኮሚዩኒቲ ማእከል አዳራሽ በተዘጋጀው የእራት ግብዣ ላይ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን የቫንኮቨር ነዋሪዎች በመገኘት የገንዘብና የቁሳቁስ እርዳታ አበርክተዋል። የእርዳታ አሰባሳቢው ኮሚቴ የህዝብ ግንኙነት አቶ ደበበ ጉሉ ያቀናበሩት፤ በአረብ አገሮች የተከሰተውን የኢትዮጵያውያን ሰቆቃ የሚያሳዩ የቪዲዮ ቅጂዎች በዝግጅቱ ላይ ለእይታ በመቅረባቸው የወገኖቻቸውን ስቃይ በፊልሙ የተመለከቱ ታዳሚዎች …
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ተወልደ ገብረማርያም የአፍሪቃ የበረራ እህት ድርጅቶች በአህጉሩ ባለው የበረራ ገበያ ላይ ያላቸውን ድርሻ ከፍ ለማድረግ ተጠናክረውሊሰሩ እንደሚገባ አስታወቁ።
በናይጄሪያ የክርስትና እና የእስልምና ዕምነት ተከታዮች ዘንድ ብዙም ሰላም አይስተዋልም። ከሳምንቱ መጨረሻ ጀምሮ ዳግም በሰሜን ምስራቃዊ ናይጄሪያ ከ100 የሚበልጡ ሰዎች ተገድለዋል። ለዚህም የሚጠረጠረው የናይጄሪያው አክራሪ ቡድን ቦኩ ሀራም ነው።
ባለፈዉ መጋቢት ወር የሴሌካ አማፅያን ርዕሰ ከተማ ቦንጊን ከተቆጣጠሩወዲህ የማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፑብሊክ የፀጥታ ይዞታ ከዕለት ወደዕለት እየከፋ ነዉ። ክርስቲያንና ሙስሊሞች አንዳቸዉ በሌላቸዉ ላይ ተነስተዋል። ሰዎች ጎዳና ላይ ጥቃት ይደርስባቸዋል፣ በቆንጨራ ወይ በጥይት ተመተዉ ይገደላሉ፤ አካላቸዉ ይጎድላል።
ሴቶች ልጆችን መግረዝ እንዲቆም በተለያዩ ሃገራት ኅብረተሰቡን የሚያስተምሩና ጉዳቱን የሚያስረዱ እንቅስቃሴዎች መካሄድ ከጀመሩ ቆይተዋል።

ኢህአዴግ ራሱ ባወጣው አፋኝ ሕግ ታፈነ:: ለተፈጥሮ ሃብት የጠየቀው ዓለምዓቀፋዊ እውቅና ውድቅ ሆነ::
ምንጭ = ጎልጉል
ኢህአዴግ የተፈጥሮ ሃብትን በትክክለኛ መንገድ ለሕዝብ ጥቅም መዋሉን በመከታተል ለአገራት እውቅና የሚሰጠው The Extractive Industries Transparency Initiative (EITI) ለተሰኘ ዓለም ዓቀፋዊ ተቋም ያቀረበው የእውቅና ጥያቄ ማመልከቻ ከተገመገመ በኋላ መመዘኛዎቹን ማሟላት ባለመቻሉ መውደቁ ተሰማ። ኢህአዴግ የእውቅና ማመልከቻ በድጋሚ ማስገባቱን አስቀድሞ ያወቀው ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብት ጥበቃ ድርጅት (Human Rights Watch) ጉዳዩን ከሚከታተሉ ጋር ባገኘው መረጃ ኢህአዴግ የEITI መስፈርት የማያሟላና በሰብአዊ መብት ጥሰት የተወነጀለ ድርጅት መሆኑንን ማስረጃ አስደግፎ በመጥቀስ መሟገቻ ደብዳቤ ለድርጅቱ አስገብቶ ነበር።
EITI የዛሬ 11ዓመት አካባቢ የተቋቋመ በተፈጥሮ ሃብት ዙሪያ ዕውቅና የሚሰጥ ድርጅት ነው፡፡ ድርጅቱ የተፈጥሮ ሃብት የህዝብ መሆኑን የሚያምን ሲሆን ማንኛውም የተፈጥሮ ሃብት – ማዕድን፣ ዘይት፣ ብረታብረትና ጋዝ – ከመሬት በሚወጣበት ጊዜ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ የሚኖረውን ያህል ግልጽነትና ተጠያቂነት በሌለባቸው አገራት ድርጊቱ ለሙስና እና ግጭት በር እንደሚከፍት ይናገራል፡፡ በመሆኑንም ድርጅቱ አገራት ለሚያቀርቡት የዕውቅና ጥያቄ ማሟላት ያለባቸውን መስፈርት በዝርዝር አስቀምጧል፡፡ ልማትና እድገት በሚል ሰበብ የሕዝብ ሃብት የሆነውን የተፈጥሮ ሃብት በማውጣት የህዝባቸውን መብት ለሚረግጡ አገራት የሚያቀርቡትን የዕውቅና ማመልከቻ ውድቅ ያደርጋል፡፡
የጎልጉል የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ምንጭ እንደጠቆሙት ኢህአዴግ ያቀረበው የእውቅና ጥያቄ ውድቅ መደረጉ እውነት ነው። ምንጩ እንዳሉት ኢህአዴግ በውሳኔው በመበሳጨት ይግባኝ ለመጠየቅ በዝግጅት ላይ ነው። ድርጅቱ (EITI) አንድ አገር ለሚያቀርበው የእውቅና ማመልከቻ በመስፈርቱ መሰረት ግምገማ ካካሄደ በኋላ እውቅና እንዲሰጥ ሲያምን በራሱ ድረገጽ ላይ የዚያን አገር ስም በመመዝገብ ተጠቃሹ አገር ከተፈጥሮ ሃብት ጋር በተያያዙ ኢንቨስትመንቶች የሚገኘው ትርፍ ለህዝብ ጥቅም እንዲውል ያደርጋል የሚል እውቅና በመስጠት ምስክርነቱን ያሰፍራል፡፡
ኢህአዴግ የመጀመሪያው የማመልከቻ ጥያቄ ያቀረበው በአውሮጳውያኑ አቆጣጠር በ2009 አካባቢ ነበር፡፡ ከEITI አምስት መስፈርቶች መካከል አንዱ፤ ማመልከቻ የሚያቀርቡ አገራት ከመያዶች (መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች) ጋር ለመስራት ያላቸው ፍላጎት ተጠቃሽ ነው፡፡ በወቅቱ ኢህአዴግ በመያዶች ላይ አፋኝ ሕግ አውጥቶ የነበረ በመሆኑ እውቅና ሰጪው ድርጅት – EITI – የኢህአዴግን ማመልከቻ ውድቅ አድርጎታል፡፡ የEITI ቦርድ ይህን ዓይነት ውሳኔ ሲያስተላልፍ ያሰፈረው ነገር ኢትዮጵያ በእጩ አባልነት ለመመዝገብ በመጀመሪያ በመያዶች ላይ ያወጣችውን ሕግ ማስወገድ አለባት የሚል እንደነበር የሰብዓዊ መብት ጥበቃ ድርጅት በድረገጹ ላይ አስቀምጦታል፡፡ በወቅቱ የተሰጠው ይህ ብያኔ በEITI እውቅና አሰጣጥ ታሪክ ውስጥ የመጀመሪያ እንደሆነ ተጠቁሞም ነበር፡፡
የEITI ዕውቅናን ለማግኘት ቋምጦ የነበረው ኢህአዴግ በድርጅቱ ውሳኔ ባለመደሰት ጥቂት ዓመታትን ቆጥሮ ከአቶ መለስ ሞት በኋላ በአቶ ሃይለማርያም በመመራት በድጋሚ ዕውቅና የማግኘት ዘመቻውን ማጠናከር ጀመረ፤ በይፋም እንቅስቃሴውን ቀጠለ፡፡ የማዕድን ሚ/ር መ/ቤትም ዕውቅና ማግኘቱ በጣም የሚያስፈልግ እንደሆነ በይፋ በመናገር ዘመቻውን አጧጡፎ ነበር፡፡ ከዚህም አልፎ ለዓመታት ሲጠቀምበት የነበረውን አሠራር በዓለምአቀፉ ድርጅት ላይ ተግባራዊ በማድረግ ኢህአዴግ Ethiopia Revenue Transparency Initiative (ERTI) የሚባል “ተለጣፊ” ተቋም በመመሥረት እንቅስቃሴ ሲያደርግ እንደቆየ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቱ ለEITI በጻፈው ደብዳቤ ላይ ገልጾዋል፡፡
ጉዳዩን በቅርብ ይከታተሉ የነበሩ የዲፕሎማቲክ ምንጮች ኢህአዴግ በአውሮጳውያኑ አቆጣጠር 2013ዓም በድጋሚ ማመልከቻ የማቅረብ ዓላማ እንዳለው ለዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብት ድርጅት አሳወቁ፡፡ በወቅቱ ኢህአዴግ ማሻሻያ እያደረጉ ነኝ የሚል ማስመሰያ ለማቅረብ የሞከረ ቢሆንም የመያዶችና የጸረ አሻባሪነት አፋኝ ሕጎቹ በተጨማሪ በቴሌኮሙኒኬሽን በኩል በስልክና ኢንተርኔት የሚያደርውን ህዝብን የመሰለል ተግባር አጠናክሮ የቀጠለበት እንደሆነ በመጥቀስ ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ ክፍሎች EITI ዕውቅና እንዳይሰጥ መወትወታቸውን ተያያዙ፡፡
እነዚሁ ወገኖች በተደጋጋሚ ያደረጉት “የወረቀትና የፔቲሽን ትግል” እየተባለ የሚቃለለው ትግል ውጤት በማምጣት ኢህአዴግ በደጋሚ ያስገባው የአባልነት ማመልከቻ ሰሞኑን ውድቅ መደረጉ ተሰምቷል፡፡ እንደ መረጃው ከሆነ EITI ማመልከቻ በሚመዝንበት በሁሉም መስፈርቶች ኢህአዴግ ወድቋል፡፡
አነስተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙና ኢህአዴግ “ልማታዊ” የሚላቸው ኢንቨስተሮች ሳይሆኑ በከፍተኛ ደረጃ የሚመደብ መዋዕለ ንዋይ የሚያፈሱ ባለሃብቶች ኢንቨስት የሚያደርጉበትን አገር ለመምረጥ የመጀመሪያው መለያቸው የEITI ድረገጽ የአባል አገራት ዝርዝር እንደሆነ ስለ አሰራሩ የሚያውቁ ይናገራሉ።
ኢህአዴግም አስፈላጊውን የምዝገባና የማመልከቻ መስፈርት በማሟላት የተቋሙን እውቅና የጠየቀው በድርጅቱ ድረገጽ ላይ ለመመዝገብ ነበር። የሁለት ጊዜ ሙከራው መክሸፉ ኢህአዴግ ራሱ ባወጣው አፋኝ ህግ መታፈኑ የሚያመላክት እንደሆነ የሚጠቅሱ ክፍሎች፤ ከኢህአዴግ ከፍተኛ ፍላጎት አኳያና ሰሞኑን በተለያየ አቅጣጫ እየተወጠረ ከመምጣቱ አንጻር ሁኔታው አጣዳፊና ፋታ የማይሰጥ በሽታ ምልክት እንደሆነ በምጸት ይናገራሉ፡፡
ስለEITI ውሳኔ ባጭሩ እንዲያብራሩልን የጠየቅናቸው ባለሙያ እንዳሉት “አንድ ዩኒቨርሲቲ ህንጻ በማስገንባቱና አስተማሪዎችን በመቅጠሩ ብቻ ዩኒቨርስቲ ተብሎ ሊጠራ አይችልም። ዩኒቨርስቲው ዓለም ዓቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ስለመሆኑ በዓለም አቀፍ መስፈርት መሰረት ተገምግሞ እውቅና የሚሰጠው መስፈርቶቹን በሙሉ አሟልቶ ስለመገኘቱ ምርመራ ተደርጎበት ፈተናውን ሲያልፍ ብቻ ነው። በዚሁ መሰረት አልፎ እውቅና ያላገኘ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ገብቶ መማር የተሳትፎ ያህል ነው። መስፈርቱን አሟልተው እውቅና ካገኙት ጋር መወዳደር ስለማይችል ተመራጭ አይሆንም። በተመሳሳይ Extractive Industries Transparency Initiative (EITI) የተባለው ድርጅትም ከየአገራቱ እውቅና እንዲሰጥ የሚቀርብለትን ጥያቄ /ማመልከቻ/ የሚመዝንበት መስፈርቶች አሉት። ኢህአዴግ የተፈተነው በዚሁ አቅልጦና አንጥሮ በሚያወጣው መመዘኛ ነው ብለዋል፡፡”
ስለጉዳዩ የተጠየቀው የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ /አኢጋን/ የህዝብ ግንኙነት ግብረ ኃይል ጉዳዩን በጥልቀት የሚያውቀውና ገና ከጅምሩ ሲከታተል የቆየው መሆኑን በመግለጽ በበርካታ ፈርጆች ከሚያካሂደው ትግል አንጻር በዕቅድ ሲያከናውነው የቆየ መሆኑን አመልክቷል። የህዝብ ግንኙነት ክፍሉ ለጎልጉል እንዳለው ከሆነ “የEITI ውሳኔ ኢትዮጵያን እንደ አገር የሚጎዳ መሆኑ ግልጽ ነው፤ ሆኖም ውሳኔው ኢህአዴግ በራሱ ግትረኝነትና እብሪት ያመጣው ጣጣ በመሆኑ የራሱን ተግባር ተከትሎ የተወሰነው ውሳኔ በአገሪቱ ላይ በማንኛውም መልኩ ለሚያደርሰው ኪሳራ ተጠያቂው ኢህአዴግና ህወሃት ናቸው” ብሏል። በማያያዝም የጋራ ንቅናቄው ይህንኑ ጉዳይ አስመልክቶ መግለጫ በማውጣት አስፈላጊ ናቸው ለሚላቸው ወገኖች እንደሚበትንና ተቋሙ በውሳኔው እንዲጸና የሚቻለውን ሁሉ በማድረግ ላይ ለተሰማሩ መልዕክት እንደሚያስተላልፍ አመልክቷል።
| ‹እኔ እንግዲህ የሚቻለኝን ደክሜያለሁ፤ ከዚህ በላይ ለማድረግ ዐቅሙም ዕውቀቱም የለኝም፡፡ ይህን ጉባኤ ቤት ደርቡሽ ፈተነው፣ መንግሥት ፈተነው፣ እሳት ፈተነው፣ ረሃብ ፈተነው፤ ይህንን ሁሉ ተቋቋመ፡፡ አሁን ግን እኔም አልፋለሁ፡፡ ትምህርት ቤቱም ይዘጋል፡፡ ሁላችንም ታሪክ ሆነን እንቀራለን›› |
ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
”ጠላፊው ለአምስት ዓመታት በአየር መንገዱ አገልግሏል”መንግሥት
”በጠለፋው ሳይሆን ተሳፋሪዎቹን በማገቱ እስከ 20 ዓመት ሊያሳስር የሚችል ክስ ሊመሰረትበት ይችላል”የስዊስ አቃቤ ሕግ
Ethiopia Zare (ሰኞ የካቲት 10 ቀን 2006 ዓ.ም. Feb. 17, 2014)፦ ዛሬ ጠዋት ሮም ሊገባ የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ”ኢቲ 702” በ31 ዓመቱ ረዳት አብራሪ ኃይለመድህን አበራ ተገኝ ተጠልፎ በስዊዘርላንድ፤ ጄኔቭ ከተማ ከንጋቱ 12 ሰዓት ላይ አረፈ። በጣሊያንና ስዊዘርላንድ ድንበር አካባቢ ሲደርስ በሁለት ተዋጊ ጀቶች ታጅቦ የነበረ ሲሆን፣ ረዳት አብራሪው በስዊዘርላንድ ጥገኝነት ጠይቋል። ተሳፋሪዎቹ አውሮፕላኑ መጠለፉን አያውቁም ነበር።
Ethiopia Zare (ሰኞ የካቲት 10 ቀን 2006 ዓ.ም. Feb. 17, 2014)፦ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ አለማየሁ አቶምሳ በገዛ ፈቃዳቸው ከኦሕዴድ ሊቀመንበርነታቸው ለቀቁ። በዛሬው ዕለት በተካሄደው የኦሮሞ ሕዝቦች ዲሞክራሲያዊ ድርጅት (ኦሕዴድ) ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ስብሰባ መልቀቂያቸውን ያስገቡት አቶ አለማየሁ አቶምሳ ጥያቄያቸው ተቀባይነት አግኝቶ ከሥልጣን መነሳታቸው ታውቋል።
በበረራ ቁጥር ET 702 የተመዘገበው የኢትዮጵያ ዓየር መንገድ አውሮፕላን በረዳት አብራሪው እንደተጠለፈ ታወቀ። ጠላፊው አሮፕላኑን ጄኔቫ ከተማ ሲያሳርፍ የስዊስ መንግሥትን የፖለቲካ ጥገኝነት መጠየቁም ተገልጧል።
የኢትዮጵያ መንግሥት ኰሚዩኒኬሽን ጽ/ቤት በበኩሉ ጠላፊው ሊያመልጥም ነበር ብሏል። ጠላፊው በስዊስ ፖሊሶች በቁጥጥር ስር ውሏል። ለዝርዝሩ ዘገባዎቹን ከዚህ ያድምጡ።
ግብጾች ሱዳን ኢትዮጵያ እና ግብጽ እያደረጉት ከነበረው የሶስትዮች ድርድር እራሷን ማግለሏ ይታወሳል። የግብጽ ሜዲያዎች በዚህ ጉድያ ጉዳይ ላይ በስፋት እየዘገቡ ሲሆን ጸረ-ኢትዮጵያ ዘመቻና ፖሮፖጋንዳዉን በስፋት ተያይዘዉታል። የቻይናዉ CCTV በዚህ ጉዳይ ያቀናበረዉን ለማየት እዚህ ይጫኑ።
(በፋክት መጽሔት ቅጽ 2 ቁጥር 33 የካቲት 2006 ታትሞ የወጣ) ሕፃን እዮሲያስ የጓደኛዬ ልጅ ነው። በሰባት ዓመቱ ሁለተኛ ክፍል ገብቷል። ፈጣንና መጠየቅ የሚወድ ታዳጊ ነው። ባገኘኝ ቁጥር በጥያቄ ልቤን ጥፍት ያደርገዋል። አብዛኛው ጥያቄዎቹ ትምሕርት ቤት ከጓደኞቹ ጋራ ከሚያደርጋቸው ጨዋታዎች የሚመነጩ ናቸው። ባለፈው ሰሞን እንዲህ ብሎ በእንቆቅልሽ መልክ ጠየቀኝ። ለእኔም አጠያየቁ ልጅነቴን ስላስታወሰኝ በትዝታ ፈገግታ ታጅቤ […]
ክፍል.1
በላይ ማናዬ

ስድስት ኪሎ አደባባይ የካቲት-12 ሰማዕታት ሐውልት ሥር ሆኜ ያን ዘመንና የወቅቱን አሰቃቂ ድርጊት ባሰብኩ ጊዜ ስቅጠት ተሰማኝ፡፡ የቆመው ሐውልት ማንን ለመዘከር እንደተጀነነ ባወኩ ጊዜ ደግሞ አንገቴን ቀና አድርጌ እኔም እንደ ሐውልቱ መጀነን ከጀለኝ፡፡ እናማ ሐውልቱ ሥር ሆኜ….ስሜቴ ዝብርቅርቅ ነው፤ ቋንቋዬ ብዙ ነው፤ መንፈሴ ጠንካራ ሐዘኔ መራራ ነው፤ ምናቤ የኋሊት ጎታች ምኞቴ ወደ ፊት ሸምጣጭ ነው፤ ሐውልቱ ለኔ የውስጠቱን ይገልጥልኛል፤ ታሪኩን ይነግረኛል….የተጋድሎ ታሪክ ይተርክልኛል፡፡
እንዲህ እያለ….
የካቲት 12 ከመባቱ በፊት የአዲስ አበባ ነዋሪዎችና ሌሎች መምጣት ያለባቸውና መገኘት የሚችሉ ሁሉ በዚህ በስድስት ኪሎ እንዲሰባሰቡ ጥሪ ቀረበ፡፡ እምቢልታ ተነፋ፤ ስማ በለው ተለፈፈ፤ ነጋሪት ተጎሰመ፤ ጥሩምባ ከወዲህም ከወዲያም አምባረቀ፡፡ ጥሪውን የሰማው ወገን ሁሉ በዕለቱ ለት ከተተ፡፡ የጥሪው መነሻ ፋሽስት ጣሊያን ሀገራችንን ከሞላ ጎደል ድል አድርጋ አዲስ አበባ ላይ ከከተመች ወዲህ መሪ ነኝ ባዩ ማርሻል ሮዶልፍ ግራዚያኒ «ሰርግና ምላሽ» የሚያደርግ መሆኑ ነበር፡፡ በዕለቱ የሮማ መንግስት ልዕልና እና የልጇ ልደት የሚዘከርበትም ጭምር ነበር፡፡
እናም ህዝብ አዳሜ ስድስት ኪሎን በዕለተ ሚካኤል አጥለቀለቀው፡፡ ህጻኑ፣ አዛውንቱ፣ ወጣቱ፣ ቆነጃጅቱ፣ ባንድ ቦታ ታደመ፡፡ ግራዚያኒ በጠባቂዎቹ ታጅቦ ግብር ለማብላት የንግስናው መንበር ላይ ተቀመጠ፤ ሰገነቱ ላይ ተንቆራጠጠ፡፡ ነጭና ሐበሻ ድምበር ለይቶም ቢሆን ተቀራርቦ የበረታው ቆሞ፣ የደከመው ተቀምጦ ሁኔታውን ያጤን ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ፈረሰኞችም አለፍ አለፍ ብለው ይታያሉ፤ ባንዳዎችም ሲያሸረግዱ የጉድ ነበር፡፡
ሰርግና ምላሹ ተጀምሮ ጥቂት ነገሮች በሰላም ከሄዱ በኋላ አካባቢው ተረበሸ፤ ከዚያ በሗላማ….
* * *
ሐውልቱ ሥር ሆኜ ታሪኩን አጣጣምኩት፤ ወደ ህይወት መለስኩት፤ ጊዜውን ጎትቼ አሁን ላይ አጫወትኩት፡፡ እናም እነዚያ ወጣቶች በሐገር ፍቅር ሲነዱ አየኋቸው፤ የወገን ጥቃት ሲያንገበግባቸው ተመለከትኩ፤ አውጥተው አውርደው መክረው ዘክረው ስለወሰኑት ውሳኔ አሰላሰልኩ፡፡ ውሳኔያቸውን የሚተገብሩበት ሰዓት ሲደርስ ተሰማኝ፤ ኢትዮጵያዊነት ወኔያቸው ወደ ፊት ሲገፋቸው፤ እምቢ ለሀገሬ ብለው ሲሸልሉ በውስጣቸው ሰመጥኩ፡፡
ባቀዱት መሰረት ወደ ተሰበሰበው ህዝብ ዘልቀው ገቡ፤ የያዙትን ነገር ደብቀው ወደ ግራዚያኒ እና ጠባቂዎቻቸው በቻሉት መጠን ተጠጉ፤ የወራሪዎች ትዕቢትና ንቀት ካሰቡት በላይ የሆነ መሰላቸው፡፡ የተሰበሰበው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ያለበትን ስሜት አጤኑ፤ ከፋቸው! አዎ፣ ሀበሻ የበላይነት ተወስዶበታል፤ ችግረኛ ተምበርካኪ ሆኖ ታያቸው፡፡ በዱር በገደሉ ከወራሪው ጋር የሚፋለሙትን አርበኞችም አሰቧቸው፤ ልባቸው ደነደነ፡፡ በገጠር የሚፋለሙትን አርበኞች ማገዝ፣ መተባበር አለባቸው፡፡ ስለዚህም ያቀዱትን ሁሉ ዛሬ የካቲት 12 ቀን በግራዚያኒ ላይ መፈጸም አለባቸው፡፡
ሰዓቷ ደረሰች፤ የያዙትን የእጅ ቦምብ ፈቱት….ወደ ኢላማቸውም ሰነዘሩት! ግ…ር!….ሽብ..ር…..ሽብርብር! ምስቅልቅል! የድርጊቱ ፈጻሚዎች ወዲያውኑ አካባቢውን ከግርግሩ መሐል ገብተው በመሹለክለክ ተሰናበቱ፡፡ ግራዚያኒ በጥቃቱ ቆስሎ ተንገዳገደ፤ ጠባቂዎች ተረባበሹ፣ ቆሰሉ፣ ሞቱ…የአለቃቸው መጎዳትም ጎዳቸው፡፡
ግራዚያኒ ትዕዛዝ አስተላለፈ፤ «ይሄን ሐበሻ በሉት፤ እረዱት!!»
ወዲያው የፋሽስት ሰይፍ ተመዘዘ፡፡ የሚካኤል ሰይፍ ግን ተጠቂዎችን ለማዳን ሰገባውን ሾልኮ አልወጣም ነበር፤ የካቲት 12…ዕለተ ምካኤል በአዲስ አበባ መርገምት ወረደ፡፡ ውጥንቅጡ የወጣ ነገር….. የህጻናት ዋይታ…የእናት እሪታ…..የባንዳ ሽለላ…..የፋሽስት ጥይት ጨኸት….የአዛውንቶች እግዚኦ…..የእግሬ አውጭኝ ሩጫ…..የታጣቂ ጡጫ….የፈረሶች ርግጫ….የቀሳውስት ከንቱ ምልጃ…..የቆነጃጅት መቅበዝበዝ…..የጎልማሶችና ጎበዛዝት መደንዘዝ…ኦህ! ያማል!
የደም ጎርፍ….የተቀላ አንገት….የተቦደሰ ታፋ…..የተጎለጎለ አንጀት….የተቆረጠ እጅ…..የታረደ ጉሮሮ….የተገመሰ ጭንቅላት…..የተቆራረጠ ጣት…..የሚያቃስቱ ነፍሳት…..የተጋደመ ሬሳ….የተነባበረ የሰው ልጅ ክምር…..የአልሞት ባይ ተጋዳይ ትንቅንቅ…..የውስጥ አርበኞች ሽምቅ…..በደም ስካር….በግዳይ ሽለላ….ተጨማሪ ነፍሳትን ለመንጠቅ መታተር….ሐበሻን የመጨረስ ሩጫ…..እድሜ፣ ዖታ፣ እቴ…አባቴ ሳይሉ በያዙት መሳሪያ ማንከት….መሰየፍ….መቀልጠም….መረሸን…..አቤት ጭካኔ!! አቤት የግራዚያኒ ጭካኔ! አቤት አረመኔነት!
የሺዎች ጩኸት፣ የሺዎች ዋይታ፣ የሺዎች መሰዋት፣ የሺዎች እልቂት….መች በዚህ አበቃ፡፡ ግራዚያኒ ህክምናውን ተከታተለ፤ ሐበሻ ግን ጥራሞቱ እየተደመጠ፣ ማቃሰቱ እየታዬ፣ እስትንፋሱ እየተፈተሸ እንዲጨረስ ተደረገ፡፡ ግራዚያኒ እልቂቱን ባዬ ጊዜ ደስ አለው፤ እርካታ ሊያገኝ ግን አልቻለም፡፡ ስለዚህም ጭፍጨፋው ለሶስት ቀናት እንዲቀጥል አዘዘ፤ ገዳማት እንዲወድሙ መመሪያ ሰጠ፡፡
አዲስ አበባ በደም ጨቀየች፡፡ ስድስት ኪሎ በደም ጎርፍ ተጥለቀለቀች፡፡ ኢትዮጵያ ወገቧን በገመድ አስራ አዘነች፤ እምምም ብላ ወደ ፈጣሪ ተመለከተች፤ አንገቷን ከመድፋት ይልቅ ቀና ብላ ፈጣሪ ያለበትን ሰማየ ሰማያት አየች፡፡ ፋሽስትም አንገት ከመድፋት ይልቅ ቀና ማለትን የሐበሻ ይትብሓል ባዬ ጊዜ ፍርሃት ናጠው፤ የሀበሾች ንግርት ‘ስታጠቃኝ ጠንክሬ እዋጋሃለሁ’ የሚል ሆነበት፡፡ አርበኞችን ባሰበ ጊዜ የእንሺርት ውሃው ፈሰሰ፡፡
እነዚያን ጥቃት ፈጻሚ ወጣቶች ክፉኛ ኮነናቸው፤ የሮማን ሃያልነት መቀበል አንሻም ብለው «ኢትዮጵያ!!» ያሉትን ጀግኖች በአዕምሮው አመላልሶ አያቸው፡፡ የምር ቆራጦች ናቸው! የምር አርበኞች ናቸው! የምር ኢትዮጵያዊያን ናቸው! የምር አድዋ ላይ የግራዚያኒን አባቶች ያንበረከኩት ልጆች ናቸው!
ግራዚያኒ ስለነዚህ ወጣቶች በቀል በአዲስ አበባ ያደረገውን ተዘዋውሮ ተመለከተ፤ በእብሪት የተሞላው ልቡ ቅንጣት ታህል ሀዘን አልተሰማውም፤ እንዲያውም «በግዳዩ» ላይ በንቀት ምራቁን ጢቅ አደረገ፡፡ በሰማዕታት በድን ላይ በመኮፈስ ተራመደ፡፡
ግራዚያኒ የመግደል ሙከራ የተደረገበትን ስድስት ኪሎ ተመለከተ፡፡ የሬሳ መዓት አንዱ በአንዱ ላይ ተነባብሯል፤ እናት ልጇን እንደያዘች ባፍጢሟ ተደፍታለች፤ ጎልማሶች እጆቻቸውን ለጡጫ እንደጨበጡ በአልሞት ባይ ተጋዳይነት ተጋድመዋል፡፡ ግራዚያኒ እነዚህን መሰል ሬሳዎች ሲያይ እንደገና ደም ደም ይሸተዋል፡፡ ትንሽ አለፍ ሲል ደግሞ ሽለላ ላይ የነበሩ አዛውንቶች አፋቸውን ከፍተው ወድቀዋል፤ «አድዋ!!» ሲሉ እንደነበር እያሰበ በንዴት ይተክናል፡፡
ግራዚያኒ የባንዳ ሬሳ ሲመለከት ብቻ ሳቁ ይመጣበታል፤ እንዴት እርስ በእርሳቸው እንዳገዳደላቸው እያሰበ ይረካል፤ ባንዳዎች ሀገራቸውንና ወገናቸውን ከድተው ለሱ በማደራቸው ይንቃቸዋል፤ ፍርፋሪ ለመለቃቀም ሲሉ ከጎኑ ስለሆኑ ከሰውነት ተራ ያስወጣቸዋል፤ ጀግንነታቸው የፈሪ ጀግንነት እንደሆነ አድርጎ ያስባቸዋል፤ በህይወት ባሉ ባንዳዎች ዘንድም ትዝብት ያሳድርባቸዋል፡፡
ዋ አረመኔው ግራዚያኒ!…..ስንቱን ጦስ ይዘህ መጥተህ ነበር! በሶስት ቀናት ብቻ በአዲስ አበባ ከተማ 30,000 ንጹሐን ተጨፈጨፉ፤ በታሪካዊው ደብረ ሊባኖስ ገዳም ያሉ መነኮሳት ተረሸኑ፤ ቤተ ክርስቲያናት ተቃጥለዋል፤ መኖሪያ ቤቶች ፈርሰዋል፡፡ ዋ አረመኔው ግራዚያኒ!
* * *
ሐውልቱ ስር ሆኜ ያስታወስኩት ይህን ብቻ አልነበረም፤ ስለ የካቲት 12 ቀን፣ ስለነዚያ ወጣቶች እና ስለ ሌሎች የታሪኩ ተዋናዮችም ሳውጠነጥን ነበር፡፡ እነዚያ ወጣቶች ያልኩህ አብርሃም ደቦጭና ሞገስ አስግዶምን ነው፡፡ በቀጣይ ስለነዚህ ወጣቶችና በዙሪያቸው ስለነበሩ የአርበኝነት ተጋድሎው አጋሮች እናወሳለን፡፡ ከዚያ በፊት ግን የሐውልቱን ምስክርነት የሰማዕታቱን ሞገስ ስድስት ኪሎ ተገኝተህ ጎብኝ፡፡ እነዚያ ወጣቶች ጋር በቀጣይ እንገናኝ፡፡
ESAT Radio Daily Broadcast to Ethiopia. Frequency Details: 7 days a week Short Wave (SW) from 8:00 pm to 9:00 pm (Local Ethiopian Time) 19 Meter Band 15355 kHz, 15360 kHz, 15365 kHz, 15370 kHz, 15380 kHz, 15385 kHz and 15390 kHz Download/Listen
«መንግስት የነዳጅ ዋጋን ማረጋጋት አለበት» (ዶ/ር ቆስጠንጢኖስ ብሩህ ተስፋ) «ባለፉት 8 ዓመታት የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ከአራት እጥፍ በላይ አድጓል» «የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ መንግስት ለዜጎቹ ግድ ማጣቱን አመላካች ነው፡፡» (የከተማዋ ነዋሪ) የስምንት ዓመት የዋጋ ንረት 1998 2006 ቤንዚን 6.57 20.47 ነጭ ጋዝ 3.45 15.75 ታክሲ (አጭር ርቀት) 0.60ሳ 1.50 ታክሲ (ረዥም ርቀት) 1.25 3.00 አንበሳ አውቶብስ […]
ልማታዊ ጋዜጠኛ፣ ልማታዊ ነጋዴ፣ ልማታዊ መመህር፣ ልማታዊ ሃኪም፣ ልማታዊ ቄስ፣ ልማታዊ ሼክ—- ልማታዊ የሚል መዳልያ ከኢህኣዴግ የሚገኝ ትልቅ የክብር ሽልማት ነው፡፡ ነገር ግን ይህ ኣይነት ሽልማት የሚሰጣቸው የተወሰኑ ሰዎች ናቸው፡፡ እነዚህም ኢህኣዴግ በህዝብ ላይ የፈለገውን አፈና ሲፈፅም ፣ የሃገር ኢኮኖሚ በሙስና ሲበዘብዝ ለምን ያማይሉ፣ ለሂሊናቸው ሶይሆን ለሆዳቸው ብቻ የሚኖሩና ለታሪክ ደንታ ቢስ የሆኑ ሁሉ በኢህኣዴግ […]
ጽዮን ግርማ
ሕፃን እዮሲያስ የጓደኛዬ ልጅ ነው። በሰባት ዓመቱ ሁለተኛ ክፍል ገብቷል። ፈጣንና መጠየቅ የሚወድ ታዳጊ ነው። ባገኘኝ ቁጥር በጥያቄ ልቤን ጥፍት ያደርገዋል። አብዛኛው ጥያቄዎቹ ትምሕርት ቤት ከጓደኞቹ ጋራ ከሚያደርጋቸው ጨዋታዎች የሚመነጩ ናቸው። ባለፈው ሰሞን እንዲህ ብሎ በእንቆቅልሽ መልክ ጠየቀኝ። ለእኔም አጠያየቁ ልጅነቴን ስላስታወሰኝ በትዝታ ፈገግታ ታጅቤ “ምናውቅልህ” አልኩት። ”እ … ቢሄዱ፣ ቢሄዱ የማይሰለቻቸው?” አለኝ። ጥያቄውን እኔ ከለመድኩት የልጅነት የእንቆቅልሽ መልስ ጋራ ለማዛመድ የዱር አልቀረኝ የቤት መንገድ አይሰለቻቸውም ስል ያሰብኳቸውን እንስሳት ማሰላሰል ቀጠልኩ። የመሰሉኝንም ስማቸውን ደረደርኩለት፤ አልተሳካልኝም።
Sochi olympic, sports, genzebie
አገሬን ለቅቄ ስደት የጀመርኩት በ1984 ነዉ። ኢሕአዴግ ስልጣን በጨበጠ በአንድ አመቱ። ከአስራ አራት አመታት በኋላ ለአንድ ወር ጉብኘት ቦሌን ረገጥኩ። እሑድ ቀን ፣ ግንብት ሰባት 1997 ነበር። ከዚያ በፊት ብዙም የፖለቲካን ነገር አልከታተለም ነበር። ምርጫ እንደሚደረግ፣ ቅንጅት ሕብረት እየተባለ የምርጫዉ ዘምቻ እንደተጧጧፈ ያወኩት ትኬት ከቆረጥኩ በኋላ፣ ከምርጫዉ 15 ቀናት በፊት ነበር። በአጭሩ አባባል፣ በአገሬ ዉስጥ […]
አንድነት በዚህ ጉዳይ ላይ ለየካቲት 16 ሰልፍ የጠራ ሲሆን፣ ኢትዮጵያውያን በኦንላይን ድምጻቸውን እንዲያሰሙ ፔተሽን ይፋ አደርጓል። ወደ ፔትሽኑ ለመሄድና ለመፈረም እዚህ ይጫኑ
የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ፣ በባህር ዳር ከተማ የካቲት 16 ቀን ፣ ከመኢአድ ጋር በመሆን በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ፣ የባህር ዳር እና የአካባቢዉ ሕዝብ፣ በነቂስ እንዲወጣ፣ ከፍተኛ የቅስቀሳ ዘመቻ እንደተጀመረ የሚገልጹ ዘገባዎች እየደረሱን ነዉ። «አንድነታችን ከልዩነቻትን በላይ ነው» ፣ «የአማራዉን ሕዝብ ያዋረዱ የብአዴን/ኢሕአዴግ ባለስልጣናት ለፍርድ ይቅረቡ» «ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ በባህር ዳር ከተማ የካቲት 16 ቀን 2006 ዓ.ም፣ […]
አትሌት ገንዘቤ ዲባባ በርሚንግሃም ላይ ከትናንት በስተያ በተካሄደው የቤት ውስጥ 2 ማይልስ ወይም ሦስት ሺ 200 ሜትር ሩጫ ውድድር 9 ደቂቃ ከ4.8 ሰከንድ በመግባት አዲስ የዓለም ክብረወሰን አስመዘገበች፡፡
ዛሬ በጠዋቱ ዜናው በሙሉ ከአዲስ አበባ ወደ ሮም ሲጓዝ የነበረን 202 ሰዎችን ያሳፈረ የኢትዮጵያ አውሮፕላን ‘መጠለፍ’ ጉዳይ ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ኮሙንኬሽን ጉዳዮች ሚኒስትር ‹ጠላፊው ካርቱም ላይ የተሳፈረ ሰው ይመስላል› ቢሉም በመጨረሻ አውሮፕላኑ ካርቱም ላይ ከነጭራሹ እንዳላረፈና ጠላፊውም ረዳት ፓይለቱ እንደሆነ ተረጋግጧል፡፡ ረዳት ፓይለቱ ለምን ይሄን ተግባር እንደፈፀመ ሲጠየቅም ኢትዮጵያ ውስጥ መኖር ስጋት ላይ እንደጣለው በመግለፅ፤ ሲዊዘርላንድ ጥገኝነት እንድትሰጠው ጠይቋል፡፡
ይህ ከሆነ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ የስዊዘርላንድ አቃቢ ሕግ መስሪያ ቤት እንደገለፀው ግን ጉዳዩ ጠለፋ (Hijacking) ሳይሁን እገታ ( Hostage Taking) ነው ብሏል፡፡ በሌላ በኩል ረዳት ፓይለቱ ወደ ኢትዮጵያ ተላልፎ እንዳይሰጥ ስዊዝን ተማፅኗል፡፡ ሁለት የህግ ጥያቄዎች አሉ፡
1. ጠለፋ ወይስ እገታ?
2. በረዳት ፓይለቱ ላይ የዳኝነት ስልጣን (Legal Jurisdiction) ያለው አካል ማነው? ኢትዮጵያ ወይስ ስዊዘርላንድ?
እነዚህን ጉዳዮች የሚፈቱልን ሁለት አለማቀፍ ሕጎች አሉ (ኢትዮጵያም ስዊዘርላንድም የሁለትም የሕጎቹ ፈራሚ ሀገራት ናቸው)፡፡
1. Convention for the Suppression of Unlawful Seizure of Aircraft – Hijacking Convention on Hijacking – 1970 &,
2. International Convention Against the Taking of Hostages – Convention on Hostage taking – 1983.
በነዚህ ሁለት ሕጎች መሰረትም የረዳት ፓይለቱን ሁኔታ (Situation ) እንይ፡፡
1ኛ. ጠለፋ ወይስ እገታ?
ከላይ በመጀመሪያ የጠቀስነው የHijacking Convention ‘ጠለፋ’ን በአንቀፅ አንድ ላይ እንዲህ ይፈታዋል:
Any person who on board an aircraft in flight:
unlawfully, by force or threat thereof, or by any other form of intimidation, seizes, or exercises control of, that aircraft, or attempts to perform any such act, or is an accomplice of a person who performs or attempts to perform any such act commits an offence [of Hijacking].
በሌላ በኩል ከላይ በሁለተኝነት የጠቀስነው የHostage taking convention ‘እገታ’ን በአንቀፅ አንድ ላይ እንዲህ ይተረጉመዋል፡
Any person who seizes or detains and threatens to kill, to injure or to continue to detain another person in order to compel a third party, namely, a State, an international intergovernmental organization, a natural or juridical person, or a group of persons, to do or abstain from doing any act as an explicit or implicit condition for the release of the hostage commits the offence of hostage-taking.
የኢትዮጵያዊው ረዳት ፓይለት ተግባርም ጥገኝነት ለማግኝት ያደረገው ማስገደጃ መሳሪያ በመሆኑ የስዊዘርላንድ አቃቢ ሕግ መስሪያ ቤት እንዳለው ተግባሩ ለእገታ የቀረበ ሲሆን፤ ተጠያቂነቱም ከእገታ ጋር በተያያዘ ይሆናል ማለት ነው፡፡
2ኛ. ኢትዮጵያ ወይስ ስዊዘርላንድ?
ጉዳዩ ‘እገታ’ ነው ካልን በጉዳዩ ላይ ተገቢ የሆነው ሕግ አለማቀፉ የፀረ እገታ ሰምምነት (Hostage taking convention) ነው ማለት ነው፡፡ በዚህም መሰረት በረዳት ፓይለቱ ላይ የዳኝነት ስልጣን ያለው የየትኛው ሀገር መንግስት ነው? የሚለው ቀጣዩ ጥያቄ ነው፡፡
ሕጉን ጠቅሰን ብናልፍ ይሻላል፡፡ ዓለማቀፉ የHostage taking convention በአንቀፅ አራት ላይ እንዲህ ይደነግጋል፡
State shall take such measures as may be necessary to establish its jurisdiction over the offence and any other act of violence against passengers or crew committed by the alleged offender in connection with the offence, in the following cases:
A. when the offence is committed on board an aircraft registered in that State (በዚህ መሰረት ኢትዮጵያ ስልጣን ይኖራታል);
B. when the aircraft on board which the offence is committed lands in its territory with the alleged offender still on board (በዚህ መሰረት ደግሞ ስዊዘርላንድ ስልጣን ይኖራታል ማለት ነው).
ስለዚህም በጉዳዩ ላይ የሁለት ሀገሮች የዳኝነት ስልጣን ያለ ሲሆን፤ ኢትዮጵያ የአውሮፕላኑ ባለቤት በመሆኗ፣ ስዊዘርላንድ ደግሞ አውሮፕላኑ በግዛቷ በማረፉ ስልጣን አላት ማለት ነው፡፡ በዚህ ጊዜ ማን ቀዳሚ ስልጣን ይኖረዋል? የሚለው የሚወሰነው ተጠርጣሪውን (በአሁኑ ጉዳይ ረዳት ፓይለቱ) በቁጥጥር ስር ቀድሞ በማዋል የሚወሰን ሲሆን በአሁኑ ጉዳይ ላይ የዳኝነት ስልጣኑ የስዊዘርላንድ ነው ማለት ነው፡፡
መውጫ፡
ኢትዮጵያ ተጠርጣሪው ተላልፎ እንዲሰጣት (Extradition) በፀረ እገታ ሰምምነቱ አንቀፅ 7ና 8 መሰረት መብት ቢኖራትም ኢትዮጵያና ስዊዘርላንድ የአሳልፎ የመስጠት ስምምነት (Extradition agreement) ስለሌላቸው (እኔ እስከማውቀው ድረስ) ተላልፎ የመሰጠት ጉዳዩ ብዙም አድል የለውም፡፡ የስዊዘርላንድ አቃቢ ሕግ መስሪያ ቤትም ከአሁኑ ክስ ለመመስረት ጉዳዩን እያጣራ እንደሆነ መልለጫ ሰጥቷል፡፡
በመጨረሻም:
ረዳት ፓይለቱ ጥፋተኛ ሆኖ ከተገኝ በስዊዘርላንድ የወንጀል ሕግ SR 311.0 አንቀፅ 185 መሰረት ከ3 ዓመት እስከ 20 ዓመት (እንደ ነገሩ ሁኔታ) የሚደርስ ቅጣት ይጠብቀዋል፡፡ በሌላ በኩል ‘ድንገት’ ተላልፎ ለኢትዮጵያ ቢሰጥ ደግሞ በኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ አንቀፅ 507/1 መሰረት ከ15 አስከ 20 ዓመታት እስር ይጠብቀዋል ማለት ነው፡፡
በበርሊኑ 64ኛ የፊልም ትርዒት፤ ባለፈው ሳምንት ከ 400 በላይ ፊልሞች ለተመልካቾች ቀርበው ታይተዋል። በዚያ ከቀረቡት የውጭ ፊልሞች መካከል፤ አንዱ በጠለፋና መደፈር ላይ ያተኮረው በአቶ ዘርእሰናይ ብርሃነ መሐሪ የተሰናዳው ኢትዮጵያዊ ፊልም ነው።
News, Sports, African Topics and Health
የመቀሌና ፤ በበልጂግ የሎይቨን ካቶሊካዊ ዩንቨርስቲ መካከል ባለፉት ዓመታት የተደረጉ የሥራ ትብብሮችና ውጤቶችን የገመገመ፤ የወደፊቱን አቅጣጫም ያመላከተ ስብሰባ ባለፈው ሰሞን በሎይቨን ዩንቨርስቲ ዋና ቤተ መጻሕፍት አዳራሽ መካኼዱን ገበያው ንጉሤ የላከልን
የካቲት ፲ (አስር) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አየር መንገዱ ከአዲስ አበባ ወደ ሮም ጣሊያን በማምራት ላይ በነበረበት ጊዜ ረዳት አብራሪው የጉዞውን አቅጣጫ በመቀየር ጄኔቭ አውሮፓላን ማረፊያ በማሳረፍ እጁን ለፖሊስ ሰጥቷል። የኢትዮጵያ መንግስት የኮሚኒኬሽን ባለስልጣን የሆኑት ሬድዋን ሁሴን አየር መንገዱ የተጠለፈው ሱዳን በቆመበት ጊዜ በተሳፈሩ ማንነታቸው ያልታወቁ ሰዎች ነው በማለት መጀመሪያ ላይ ለረዩተርስ መግለጫ ቢሰጡም፣ …
የካቲት ፲ (አስር) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከአርሴማ ቤተክርስቲያን የውስጥ ችግር ጋር በተያያዘ ከመንግስት ጋር በመሆን የድርጅት ስራ ሰርተዋል ተብለው የተወቀሱት አቡነ ገብርኤል፣ ትናንት ለአንድ ሰአት ያክል ታግተው ተለቀዋል። ህዝብ በመወከል ሲንቀሳቀሱ የነበሩት የአገር ሽማግሌዎች ታስረው በህዝብ ግፊት እንዲፈቱ ከተደረገ በሁዋላ፣ ለችግሩ መፍትሄ ያስገኛል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረ ቢሆንም፣ ችግሩ እልባት ሳያገኝ ቀርቷል። ጳጳሱ በህዝቡ …
ዛሬ ጠዋት ጄኔቫ – ዚውዘርላንድ ላይ ለማረፍ የተገደደው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ጠላፊ ራሱ የአይሮፕላኑ ረዳት አብራሪው መሆኑ ተረጋግጧል። በርካታ መንገደኞችን አሳፍሮ ከአዲስ አበባ ወደ ሮም ይበር የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አይሮፕላን ጄኔቫ አየር ማረፊያ ሲራርፍ በመንገደኞቹ ላይ የደረሰ ጉዳት የለም።