የ31 ዓመቱ ወጣት ረዳት አብራሪ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላንን ጠለፈ
”ጠላፊው ለአምስት ዓመታት በአየር መንገዱ አገልግሏል”መንግሥት
”በጠለፋው ሳይሆን ተሳፋሪዎቹን በማገቱ እስከ 20 ዓመት ሊያሳስር የሚችል ክስ ሊመሰረትበት ይችላል”የስዊስ አቃቤ ሕግ
Ethiopia Zare (ሰኞ የካቲት 10 ቀን 2006 ዓ.ም. Feb. 17, 2014)፦ ዛሬ ጠዋት ሮም ሊገባ የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ”ኢቲ 702” በ31 ዓመቱ ረዳት አብራሪ ኃይለመድህን አበራ ተገኝ ተጠልፎ በስዊዘርላንድ፤ ጄኔቭ ከተማ ከንጋቱ 12 ሰዓት ላይ አረፈ። በጣሊያንና ስዊዘርላንድ ድንበር አካባቢ ሲደርስ በሁለት ተዋጊ ጀቶች ታጅቦ የነበረ ሲሆን፣ ረዳት አብራሪው በስዊዘርላንድ ጥገኝነት ጠይቋል። ተሳፋሪዎቹ አውሮፕላኑ መጠለፉን አያውቁም ነበር።