የተጠለፈው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አይሮፕላን

ዛሬ ጠዋት ጄኔቫ – ዚውዘርላንድ ላይ ለማረፍ የተገደደው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ጠላፊ ራሱ የአይሮፕላኑ ረዳት አብራሪው መሆኑ ተረጋግጧል። በርካታ መንገደኞችን አሳፍሮ ከአዲስ አበባ ወደ ሮም ይበር የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አይሮፕላን ጄኔቫ አየር ማረፊያ ሲራርፍ በመንገደኞቹ ላይ የደረሰ ጉዳት የለም።