አንድ የጀርመን ፍርድ ቤት በእስር ላይ ሳለ በእሳት ቃጠሎ ሕይወቱን ባጣ የዉጭ ዜጋ ጉዳይ በፖሊስ ላይ ያሳለፈዉን ፍርድ አጸና። ካልስሬኸ ከተማ የሚገኘዉ የፌደራሉ መንግሥት ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሴራሊዮናዊዉ እስረኛ በንዝህላልነት ሕይወቱ ጠፍቷል በሚል ከዚህ ቀደም በፖሊስ ላይ የተጣለዉን የገንዘብ ቅጣት ዛሬም በድጋሚ አፅንቶታል።

ለኢትዮጵያ አስተዳደር አማራጭ የፖለቲካ መርሕ ከቀየሱት በሰላማዊ መንገድ ከሚንቀሳቀሱት የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል አንዱ ፣ አንድነት ለዴሞክራሲና ፍትሕ ፓርቲ ፤ በመጪው 2007 አዲስ ዓመት ፣ ሀገራዊ ኀላፊነትን መሸከም በሚያስችል መርኀ ግብር ለመሥራት

ናይጀሪያ ዉስጥ የሚንቀሳቀሰዉ እስላማዊ ፅንፈኛ ታጣቂ ቡድን የሚፈጽማቸዉን የኃይል ርምጃዎች እያጠናከረ በመሄድ ላይ ነዉ። በሰሜን የሀገሪቱ ክፍል በያዝነዉ ሳምንት መጀመሪያ አንዳንድ ከተሞችን መቆጣጠሩ የሚነገርለት ይኸዉ ቡድን ቀጥሎ የቦርኖ ግዛት ዋና ከተማ ማይዱጉሪን ሊይዝ ይችላል የሚል ስጋትም ይሰማል።

የአዲስ አበባ የትያትር ጥበባት ተማሪዎች «ልዑል አለማየሁ» በሚል ርዕስ አዲሱን 2007 ዓመት አስታከዉ በብሔራዊ ትያትር ሙዚቃዊ ተዉኔት ለማቅረብ ዝግጅት ላይ ይገኛሉ። ታሪካቸዉ እጅግም ብዙ እንዳልተፃፈበት እና ትያትርም ሆነ ሙዚቃ እንዳልተሰራለት ስለተነገረዉ ስለ አፄ ቴዎድሮስ ልጅ ስለ ልዑል አለማየሁ ቴዎድሮስ፤

ነሃሴ ፳፱(ሃያዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በ1997 ምርጫ ወቅት ለ200 ሰዎች ሞት እና በመቶዎች ለሚቀጠሩት ቁስለኞች ተጠያቂ በሆኑ 13 ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና ወታደራዊ  አዛዦች ላይ ለፖሊስ የክስ አቤቱታ አስገቡት በስዊድን ታዋቂ የሆኑት ጠበቃ ስቴላ ጋርደ ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ፣ በቅርቡ ለፖሊስ ከገባው አቤቱታ በተጨማሪ የኢትዮጵያ መንግስት በግፍ ለተገደሉት፣ ለቆሰሉት ፣ ለታሰሩት፣ ከስራ ለተፈናቀሉት አስፈላጊውን …

ነሃሴ ፳፱(ሃያዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአዲስ አበባ በተለያዩ ክፍለከተሞች በመካሄድ ላይ ባለው የኢህአዴግ አባላት ስብሰባ ፣ አባላቱ ዛሬም በርካታ ጥያቄዎችን ሲጠይቁ መዋላቸውን ከውስጥ ምንጮች የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ዛሬ ከሰዓት በኋላ በአባላቱ ከተነሱት ጥያቄዎች  መካከል፡- ” የኢትዮጵና የኤርትራ ህዝቦች የማይነጣጠሉ የአንድ ሃገር ዜጎች ሆነው ሳለ በመሪዎች አለመግባባትና ሽኩቻ በመለያየታቸው እስከዛሬ ድረስ እየተላቀሱ ይገኛሉ፤ ይህም የሆነው …

ነሃሴ ፳፱(ሃያዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ነገረ ኢትዮጵያ እንደዘገበው  ነሃሴ 29/2006 ዓ.ምበአራዳችሎትየቀረበው የአረና ፓርቲ የአመራር አባልና ታዋቂ ጸሃፊ መምህር አብርሃደስታ ፣ ፖሊስ ‹‹ተጨማሪሰነድለማሰባሰብናምስክሮችለማቅረብ” የጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው በመጠየቁ ፣ ፍርድ ቤቱ ለመስከረም 22 ቀጠሮ ሰጥቷል። የኢምባሲናሌሎችተወካዮችንጨምሮበርከትያለህዝብየተገኘሲሆንአብርሃደስታከማዕከላዊወደችሎቱበሚመጣበት ጊዜህዝቡደመቅባለ ጭበጭባእንደተቀበለው ነገረ ኢትዮጵያ ዘግቧል፡፡ህዝቡለአብርሃያደረገውንጭብጨባተከትሎምፖሊስህዝቡከግቢውእንዲወጣቢያስገድድምህዝቡ ሳይወጣ መቅረቱንም አክሎ ዘግባል። የአብርሃደስታጠበቃ  የሆኑት አቶ ተማምአባቡልጉከደንበኛቸውጋርበ28 ቀናትውስጥአንድቀንብቻ እንዳገኙት የነገረ ኢትዮጵያ ዘገባ ያመለክታል። ሀብታሙ አያሌው፣ …

የ «ጌታቸውን » የአቶ መለስን ራእይ፣ አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ በትጋት እየፈጸሙት እንደሆነ በስፋት እያየን ነው። የአቶ መለስ ራእይ ጭቆና፣ አምባገነንነት፣ ሰላማዊ ዜጎችን ማሰር፣ ሜዲያዉን መጨፍለቅ ነው። የአቶ መለስ ራእይ በእርቅና በፍቅር አገርን ማሳደግ ሳይሆን፣ ማክረር በዜጎችን ላይ መጨከን ነው። የፍቅርና የሰላም መጽሀፍን (መጽሐፍ ቅዱስን) በየቀኑ አነባለሁ በሚሉት በአቶ ኃይለማሪያም አገዛዝ ግን፣ ሕወሃት/ኢሕአዴግ በመለስ ጊዜ ከነበረው […]

ትላንት ከጠዋቱ 3፡00 በአራዳ ምድብ ችሎት ሐብታሙ አያሌው ዳንኤል ሺበሺና የሺዋስ አሰፋ እንደሚቀርቡ በመነገሩ የአንድነት፣ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና የየፓርቲዎቹ አባላትና ጋዜጠኞች ተገኝተው ነበር፡፡ ፖሊስ በፍርድ ቤቱ የተሰጠውን የቀጠሮ ሰዓት አክብሮ እስረኞቹን ማቅረብ አለመቅረባቸው ላይ ብዙዎች ስጋት የነበራቸው ፡፡ የታሳሪዎቹ ጠበቆች አቶ ተማም አባቡልጉና አቶ ገበየሁ ይርዳው በግምት 4፡30 ተጠርተው ዳኛ ስለሌለ ከሰዓት በኋላ በ8፡00 ሰዓት […]

እንደሰማሁት ከሆነ ጥቁር ሳምንት በሚል የተጀመረው ዘመቻ ጥሩ ዘመቻ ነው፡፡ በማህራዊ ሚዲያው ሲንቀሳቀሱ የነበሩትም ሆነ ጋዜጠኞች በመታሰራቸው እንቅስቃሴው አለመዳከሙ ያስደስታል፡፡ መጭው ዘመን የነጻነት ይሆን ዘንድ ኢትዮጵያውያን ይህን የመሰሉ እንቅስቃሴዎችን መደገፍ፣ ማበረታታትና መቀላቀል አለባቸው፡፡ በተለይ በአሁኑ ዘመን ማህበራዊ ሚዲያው ትልቅ ለውጥ እያመጣ ነው፡፡ በግብጽና ቱኒዚያ ማህበራዊ ሚዲያው ቀላል የማይባል ለውጥ አምጥቷል፡፡ ህወሓትና ሌሎችም ታጣቂ ኃይሎች ከቻይና […]

ነሃሴ ፳፰(ሃያስምንት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ በአዲስ አበባ የሚገኙ መላ አባላቱን ለስልጠና ምቹ የሆኑ አዳራሾች ባሉዋቸው ትምህርት ቤቶች እና የመንግስት ተቋማት ከትናንት ጀምሮ በፕላዝማ የታጀበ ስልጠና እየሰጠ ነው። ስልጠናው በመላው አገሪቱ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ያነሱዋቸው አፍራሽ የተባሉ ጥያቄዎች እና አመለካከቶች ወደ ህዝቡ ወርደው አደጋ ከመፍጠራቸው በፊት የኢህአዴግ አባላት እንዴት እንደሚከላከሉዋቸው ስልጠና ለመስጠት ያለመ ቢሆንም፣ የድርጅቱ …

ነሃሴ ፳፰(ሃያስምንት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፊታችን ቅዳሜ የሚከበረውን የአርባምንጭ የ50ኛ አመት የምስረታ በአልን የማጠቃለያ ዝግጅት ለመካፈል ጠ/ሚ ሃይለማርያም ደሳለኝ እና ሌሎች የመንግስት ባለስልጣናት የተገኙ ሲሆን፣ ይህን ተከትሎ በከተማዋ ረብሻ ሊያስነሱ ይችላሉ የተባሉ ወጣቶች እየታደኑ ነው። ዘጋቢያችን እንደገለጸው፣ ከ3 ቀናት በፊት እናቶች በየቀበሌው እየተጠሩ ልጆቻቸውን እንዲሰበስቡ ተነግሮአቸው ነበር። ማንኛውም ወጣት በምሽት ከተማ ውስጥ መዘዋወር፣ ሰብሰብ …

ነሃሴ ፳፰(ሃያስምንት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ድርጅቱ ለኢሳት በላከው መግለጫ ላይ  “ኮ/ል አለበል አማረ የድርጅቱ መስራችና ሊቀመንበር ሆነው ሲያገለግሉ መቆየታቸውን፣ ውጭ አገር ከሄዱም በሁዋላ ድርጀቱን በማጠናከር ከፍተኛ ሚና መጫወታቸውን” ካወሳ በሁዋላ፣ ድርጅቱ መስዋትነት እየከፈለበት ያለው የነጻነት ትግል በቶሎ ግቡን እንዲመታ መሬት ላይ ወርዶ መታገሉ የበለጠ ውጤታማ ያደርገዋል ተብሎ ስላሚታመን  በተደጋጋሚ እንዲመጡ ቢነገራቸው ሊመጡ ባለመቻላቸውና አሁን …

ነሃሴ ፳፰(ሃያስምንት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ጳጉሜ 1 ቀን 2006 ዓ.ም በሀገር አቀፍ ደረጃ ሊያካሂደው የነበረው የኪነጥበብ ሽልማት  አርቲስቶች ከፍተኛ ቅሬታ ከማቅረባቸው ጋር ተያይዞ እንዲሰረዝ መወሰኑ ተሰማ፡፡ ሚኒስቴሩ ኪነጥበብን ለማበረታታት በሚል በሥነጹሁፍ፣ በሥዕል፣በሙዚቃ እና በፊልም ዘርፎች ብቻ የየዘርፎቹ ማህበራት መርጠው የላኩዋቸውን 10፣ በድምሩ 40 ዕጩዎች በማወዳደር ከየዘርፉ የተሻለ ውጤት ያገኘውን ለመሸለም አቅዶ …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የአፍሪቃ ሕብረት አባል ሃገራት ጥቂት ርእሳነ ብሔርና የ 15 አገሮች ፤ የሕብረቱ የሰላምና ፀጥታ ም/ቤት ከፍተኛ ተወካዮች በኬንያ መዲና በናይሮቢ ፤ ትንናት የአንድ ቀን ጉባዔ በማካሄድ በክፍለ ዓለሙ፣አሳሳቢ ሆኖ ስለተገኘው አሸባሪነት መክረዋል።

ኢትዮጵያ ፤ በአፋር ምድርና በዋናው ስምጥ ሸለቆ በዛ ያሉ የከሰሙና በአሁኑም ጊዜ ቢሆን የሚንፈቀፈቁ ፣ እቶን እሳት የሚተፉ ፣ በዛ ያሉ እሳተ ገሞራዎች ያሏት ሀገር ናት። የዓለም ባንክ በቅርቡ ያወጣው እንዲሁ በነባቤ ቃል የተመረኮዘው ዘገባው

በብራዚል ፣ የዓለም የእግር ኳስ ዋንጫ ውድድር ከተደመደመ 2 ወር ሊሞላው ጥቂት ቀናት ናቸው የቀሩት። ሪዮ ዴ ጃኔሮ ውስጥ በዝነኛው ማራካና ስታዲየም ፤ በፍጻሜ ግጥሚያ ጀርመን ፣ አርጀንቲናን 1-0 አሸንፋ ለ 4ኛ ጊዜ የዓለም ዋንጫ ባለቤት መሆኗ

ቡድኑ ከሁለት ሳምንት በፊት ጄምስ ፎሌይ የተባለ ሌላ አሜሪካዊ ጋዜጠኛን በተመሳሳይ መንግድ ገድሎ ነበር። ግድያዉ ያስቆጣቸዉ የአሜሪካ ፖለቲከኞች የፕሬዝዳንት ባራካ ኦባማ መንግሥት በቡድኑ ላይ ጠንካራ ወታደራዊ እርምጃ እንዲወስድ እየጎተጎቱ ነዉ።


በሶፍት ኮፒ ተሰርቶ በኢንተርኔት የተሰራጨውን መጽሐፍ አሁን አንብቤ ጨረስኩት (ነሐሴ 27፡ ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ላይ ማለቴ ነው)፡፡ መጽሐፉ በስውር አልደረሰኝም፡፡ እዚሁ ፌስቡክ ላይ Book for All ከሚባለው ግሩፕ ነው ያገኘሁት፡፡ እርግጥ የደረሰኝ ኮፒ ለህትመት የተዘጋጀው ሳይሆን የመጽሐፉ የመጀመሪያ ረቂቅ ይመስለኛል፡፡

ያም ሆነ ይህ መፅሐፉን አነበብኩት፡፡ ሆኖም በመጽሐፉ ያነበብኩት ነገር ብዙም አላስደነቀኝም፡፡ የቀድሞው ም/ሚኒስትር ስናየው፣ ስንሰማውና በግሉ ፕሬስ ስናነበው የነበረውን ነው መልሰው የጻፉት፡፡ ያ ማለት ግን ዋሽተውናል ማለት አይደለም፡፡ አቶ ኤርሚያስ ለጊዜው ያልተናገሯቸው በርካታ ነገሮች ሊኖሩ እንደሚችሉ ብረዳም አሁን የጻፉት ነገር በኢህአዴግ አባላት ሲነገረን ከነበረው በምንም መልኩ የሚለይ አይደለም፡፡ አቶ መለስ ዜናዊን ጨምሮ ሌሎች አንጋፋ የኢህአዴግ መሪዎች በልዩ ልዩ የግምገማ መድረኮች ሲያወጧቸው የነበሩት ሪፖርቶች ከዚህ ቢብሱ እንጂ ከዚህ የሚያንሱ አይደሉም፡፡ ለአብነትም አቶ መለስ “ቦናፓርቲስታዊ የመበስበስ አደጋዎች” እና “ድርጅታችን ከእንጥሏና ከጭንቅላቷ መግማት ጀምራለች” በሚሉ ርዕሶች የጻፏቸውን ሪፖርቶች መጥቀስ ይቻላል፡፡

የአቶ ኤርሚያስ መጽሐፍ መልዕክቱ ለኢህአዴግ ተቃዋሚዎች አልመሰለኝም፡፡ ከዚህ ይልቅ አቶ ኤርሚያስ ለኢህአዴግና ለአባላቱ ማስጠንቀቂያ ያስተላለፉበት የተቆርቋሪነት ድርሳን ሆኖ ነው ያገኘሁት፡፡ አቶ ኤርሚያስ በጥቅሉ “ድርጅቱ የተመሰረተበትን ዓላማ እየሳተ በስህተት ላይ ስህተት እየጨመረ ሄዷል፤ ለወደፊቱ በዚሁ መንገድ ከቀጠለ የህልውናው ነገር አጠያያቂ ይሆናል፤ ሀገሪቷም አደጋ ላይ ተወድቃለች፤ ስለዚህ አመራሩና አባላቱ የድርጅቱን ህልውና ማስቀጠል ከፈለጉ ተገቢ የማስተካከያ እርምጃዎችን በጊዜ መውሰድ አለባቸው” የሚል መልዕክት ነው ያስተላለፉት፡፡

ይህ የአቶ ኤርሚያስ ስጋት በአቶ መለስ ዜናዊ በተለያዩ ጊዜያት ተንጸባርቋል፡፡ አቶ መለስ “የቆሰለው ጅብ ታሪክ”ን እያነሱ “ኢህአዴግ ራሱን እያረመና እያስተካከለ ካልሄደ እንደቆሰለው ጅብ ራሱን በልቶ ይጨርሳል” በማለት ጽፈዋል፡፡ በሌላ ጊዜም “የኢህአዴግ ዋነኛ ጠላቱ ተቃዋሚው ሳይሆን ኢህአዴግ ራሱ ነው፤ ኢህአዴግ ራሱን ካልጠበቀ ህልውናው ለአደጋ ይጋለጣል” በማለት በአደባባይ ተናግረዋል፡፡ ስለዚህ የኢህአዴግ አባላትና ደጋፊዎች ሰውየውንና መጽሐፉን ከማጥላላት ይልቅ የአቶ ኤርሚያስን ምክር በአዎንታዊነት ተመልክተው ለተግባራዊነቱ ሊንቀሳቀሱ ይገባል እላለሁ፡፡

—–

በአንጻሩ ግን አንድ ጥያቄ አለኝ፡፡ “እነኝህ በስልጣን ማማ ላይ ከቆዩ በኋላ ወደ ውጪ እየኮበለሉ የኢህአዴግን እኩይነት የሚያወጉን ባለስልጣናት ራሳቸው ምን ያህል ንጹህ ናቸው?” የሚል፡፡ እንዲህ የምለው ከኢህአዴግ አፈንግጠው ወደ ወጪ ከሚጠፉት ባለስልጣናት መካከል የብዙዎቹ ግለ-ታሪክ የተበላሸ መሆኑን ስለማውቅ ነው፡፡ ለምሳሌ የኦህዴድና የኢህአዴግ ፖሊት ቢሮ አባልና የኦሮሚያ ክልል የአስተዳደርና ጸጥታ ሃላፊ የነበሩት አቶ ዮናታን ዲቢሳን እንውሰድ፡፡ እኝህ ግለሰብ በየካቲት 1993 ከተሰደዱ በኋላ ኢህአዴግ የሰራቸው ወንጀሎች በማለት ብዙ ነገር ለፍልፈዋል፡፡ ነገር ግን በወቅቱ ስልጣን ላይ ከነበሩት የኦህዴድ (ኦፒዲኦ) መሪዎች መካከል የርሳቸውን ያህል በወንጀል የተነከረ ግለሰብ ያለ አይመስለኝም፡፡ በታችኛው እርከን (ዞን፣ ወረዳ፣ ቀበሌ) የነበሩት የኦሮሚያ ክልል አስተዳደር አካላት ተጠሪነታቸው ለርሳቸው ነበር፡፡ በመሆኑም በኦሮሚያ ክልል የሚካሄዱ እንቅስቃሴዎችን በቅርበት ይቆጣጠሩ ነበር፡፡ በዚህ ስልጣናቸው ተጠቅመው የከወኗቸው ብዙ ጉዶች አሉ፡፡

እኝህ ግለሰብ በሺህ የሚቆጠሩ የኦሮሞ ልጆች በኦነግ ደጋፊነት ተከስሰው እንዲታሰሩ፣ እንዲገደሉ፣ እንዲሰደዱና ደብዛቸው እንዲጠፋ የተደረገበትን ኦፕሬሽን ካቀናበሩትና ካስፈጸሙት አንዱ ናቸው፡፡ የኦሮሚያ መሬቶችን አላግባብ እየቆረሱ ለጎረቤት ክልሎች ሰጥተው ካበቁ በኋላ በሌሎች ክልሎች የተከለሉ ኦሮሞዎች “ወደ ኦሮሚያ ክልል መጠቃለል እንፈልጋለን” የሚል ጥያቄ ሲያነሱ አይቀጡ ቅጣት እንዲቀጡ አድርገዋል፡፡ በኦሮሚያ ክልል በሚኖሩ የአማራ ተወላጆች ላይ በተካሄዱ የመግደል፣ የማስደንበርና የማፈናቀል ዘመቻዎችም አውራ ተሳታፊ እንደነበሩ በሰፊው ይታወቃል (ወደ ውጪ ከኮበለሉ በኋላ በወለጋ ክፍለ ሀገር ከሆሮ ገድሩ አውራጃ ለተናፈቀሉ የአማራ ተወላጆች ተቆርቋሪ ሆነው የአዞ እምባ ማንባታቸው በጣም አስደምሞኛል)፡፡

አቶ ዮናታን በተለይም ለሃያ ዓመታት የግጭት ቀጣና በሆነው የአዋሽ-ቦርዶዴ-ሚኤሶ-አፍደም መስመር ላይ (የባቡር ሐዲድን ተክትሎ ባሉት ከተሞች) በኦሮሞና በሶማሌ ወንድማማች ህዝቦች መካከል በየሶስት ወሩ ለሚቀጣጠለው ግጭት ኢ-ፍትሐዊ ሽፋን በመስጠት ግጭቱ እንዳይረግብ ከሚያደርጉ ግለሰቦች ዋነኛው ነበሩ፡፡ ግጭቱን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የሚንቀሳቀሱ የዞንና የወረዳ ስራ አስፈጻሚዎችን አስረዋል፤ ከስራ አባረዋል፡፡ በግጭቱ የምንጊዜም ተጠቂ የሆኑት የአሰቦትና የሚኤሶ አርብቶ አደሮች ራሳቸውን የሚከላከሉባቸውን የጦር መሳሪያዎች በመንጠቅ ከሩቅ አካባቢ በሚመጡ ቆለኛ የከብት ዘራፊዎች በተደጋጋሚ እንዲገደሉና እንዲዘረፉ አድርገዋል፡፡ በዚህ ጥቃት የተንገበገቡት የሀረርጌ ሽማግሌዎች ለአቤቱታ ወደ ጨፌ ኦሮሚያና የፌዴራል መንግሥት ሲሄዱ ሰድበው በማዋረድ መልሰዋቸዋል፡፡
እኝህ ነውረኛና ወንጀለኛ ግለሰብ ናቸው እንግዲህ ወደ ውጭ ሄደው የኢህአዴግን አውሬነት የሚያረዱን፡፡ በልዩ ልዩ ሚዲያዎች ቀርቦ ሲጠየቅ “ለኦሮሞ ህዝብ ስለተቆረቆርኩና ኢሕአዴጎች በነጻነት ስላላሰሩኝ ሀገር ጥዬ ወጣሁ” ብሎናል፡፡ የሚገርመው ደግሞ ለኦሮሞ ህዝብ እታገላለሁ የሚለው ኦነግ “የኦነግ ደጋፊዎች ናችሁ” በሚል ስም የኦሮሞ ወጣቶችን ቁምስቅላቸውን ሲያሳይ የነበረውን ነውረኛ ግለሰብ በሁለት እጆቹ መቀበሉ!! አይ ፖለቲካ!! ውቢቷ እመቤት!!

አቶ ዮናታን ከሀገር የጠፉት በወቅቱ ኦሮሚያን በስውር ይመራ ከነበረው ሰለሞን ተስፋይ (ጢሞ) ጋር በመጣላታቸው ነው እንጂ ለኦሮሞ ህዝብ በመቆርቆራቸው አይደለም፡፡ ከሰለሞን ጋር በጥቅም ተጋጩ፤ ከርሱ የሚሰጣቸውንም ትእዛዝ አልቀበልም እያሉ ማስቸገር ጀመሩ፡፡ በመሆኑም “ቆይ! የሚል ዛቻ ደረሳቸው፡፡ በዚህም ቀን ከሌሊት እንቅልፍ አጡ፡፡ በመሀሉ እርሳቸውን የሚወዱ ሰዎች ለአጭር ጊዜ ስልጠና ወደ አውሮጳ ላኳቸው፡፡ ዮናታንም በዚያው ኮበለሉ፡፡ ታሪካቸው ይኸው ነው፡፡ (በነገራችን ላይ በመጋቢት 1993 ህወሐት ለሁለት ሲከፈል አቶ ሰለሞን ተስፋይ ከነ ስዬ አብረሃ ጋር ከድርጅቱ ተባረዋል፤ አቶ ዮናታን የሰለሞንን ዛቻ ችሎ ለአንድ ወር ቢቆይ ኖሮ ከሀገር ባልኮበለለም ነበር)፡፡

—–

የመጽሐፉ ፀሐፊ የሆኑት አቶ ኤርሚያስ ወንጀለኛ እንዳልሆኑ አምናለሁ፡፡ እኔም ወንጀለኛ ናቸው ከሚል አይደለም ይህንን የጻፍኩት፡፡ ነገር ግን ወደ ውጭ የኮበለሉት ባለስልጣናት ጠቅላላ ታሪካቸው መጠናት አለበት ባይ ነኝ፡፡ ሰውዬው እንደ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ከፖለቲካ ተሳትፎው ውጪ በግል የሰራው ወንጀል ከሌለ እሰየው! አሰላለፉን መቀየር ይችላል፡፡ ሰውየው እንደ ዮናታን ዲቢሳ በደም የጨቀየ ዶሴ በእጁ ላይ እያለ የኢህአዴግን እኩይነት የሚዘበዝብልን ከሆነ ግን በጭራሽ አንቀበለውም፡፡ ወንጀለኛ ምንጊዜም ቢሆን ወንጀለኛ ነው፡፡ የፖለቲካ አሰላለፍ ለውጥ ወንጀለኛነትን አይፍቀውም፡፡ አንድ ሺህ አንድ ነጥብ!!!

መላ አፍሪካ ውስጥ ሽብር ፈጠራንና ፅንኝነትን መዋጋት በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ለመምከር የአፍሪካ መሪዎች ነገ ኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ላይ ይሰበሰባሉ፡፡ ተቃዋሚዎችን በሽብር ፈጣሪነት መፈረጅና መወንጀል አደጋ አለው ሲሉ አንድ አፍሪካዊ ባለሙያ አስጠንቅቀዋል፡፡

 

 

 

በምዕራባዊያን መንግሥታት እርዳታና በኢትዮጵያ መንግሥት ድጋፍ በመንቀሳቀስ ላይ ያለው የሀገራዊ ተጠያቂነት ምርሃ ግብር በመንግሥት ለኅብረተሰቡ የሚሰጡ አገልግሎቶች እንዲሻሻሉ መርዳቱ ተገልጿል።

በአገልግሎት ሰጭዎችና ተቀባዮች መካከል የተሻለ መግባባት እንደፈጠረም ተገልጿል።

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

 

 

 

ሱዳን ዋና ከተማ ኻርቱም ላይ ሰሞኑን በተካሄደው የኢትዮጵያ፣ የሱዳንና የግብፅ የውኃና የመስኖ ሚኒስትሮች አራተኛ ዙር የምክክር ስብሰባ ላይ ግብፃዊያኑ የቀድሞ አቋማቸውን አስተካክለው በመምጣታቸው ስምምነት ላይ ለመድረስ ተችሏል ሲሉ አንድ የኢትዮጵያ የውኃ፣ የኢነርጂና የመስኖ ሚኒስቴር ባለሥልጣን ለቪኦኤ ገልፀዋል፡፡

የሚኒስቴሩ የወሰንና ወሰን ተሻጋሪ ወንዞች ዳይሬክቶሬት ዋና ዳይሬክተር አቶ ፈቅአሕመድ ነጋሽ ለቪኦኤ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

ሙሉውን ቃለምልልስ ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

ነሃሴ ፳፯(ሃያ ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአንድነት ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ሃብታሙ አያሌው፣ የድርጅቱ ም/ል የድርጅት ጉዳይ ሃለፊ ዳንኤል ሽበሺ፣ እንዲሁም የሰማያዊ ፓርቲ የምክር ቤት/ምክትል ሰብሳቢ የሺዋስ አሰፋ ከሰአት በሁዋላ ፍርድ ቤት ቀርበው የነበረ ቢሆንም፣ ፖሊስ ተጨማሪ መረጃ ለማሰባሰብ በሚል የጊዜ ቀጠሮ በመጠየቁ ፍርድ ቤቱ ተጨማሪ 28 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ፈቅዷል። የእስረኞችን ጉዳይ የሚከታተሉት …

ነሃሴ ፳፯(ሃያሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ለሁለት ሣምንታት ለዩኒቨርሲቲ አዲስና ነባር ተማሪዎች ሲሰጥ የነበረው የመጀመሪያ ዙር አስገዳጅ ሥልጠና የፊታችን ቅዳሜ የሚጠናቀቅ ሲሆን ሁለተኛው ዙር ሥልጠና ወዲያውኑ ለመቀጠል ትምህርት ሚኒስቴር መዘጋጀቱን መረጃዎች ጠቁመዋል። ተማሪዎችተገድደውበገቡበትበዚሁየሥልጠናቆይታቸውደስተኛያለመሆናቸውንበመናገርላይናቸው፡፡ በዋነኛነት የመንግሥት ፖሊሲዎችንና ስትራቴጂዎችን ለተማሪዎች ለማስተዋወቅ በሚል በመንግሥት ከፍተኛ በጀት ከ33 በላይ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች በሚሰጠው በዚሁ ሥልጠና ላይ የኢህአዴግ ዋና ዋና ካድሬዎች …

ነሃሴ ፳፯(ሃያሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መጪውን የትምህርት ዘመን ለመጀመር የሚያስችል ምዝገባ ለማካሄድ በትምህርት ቤቶች የተገኙ ተማሪዎች ለአባይ ግድብ ገንዘብ የማያዋጡ ከሆነ እንደማይመዘገቡ ተገልጸላቸዋል። ተማሪዎቹ በነፍስ ወከፍ 120 ብር የማይከፍሉ ከሆነ ምዝገባ እንደማያካሂዱ እንደተነገራቸው ለኢሳት እንደተነገራቸው ገልጸዋል። ሁለት እና ከዚያ በላይ  ልጆች ያላቸው ወላጆች በቤተሰብ ደረጃ ሳይሆን በእያንዳንዱ ልጅ ስም የመክፈል ግዴታ ተጥሎባቸዋል። አንዳንድ ተማሪዎች …

ነሃሴ ፳፯(ሃያሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአማራ ገጠር መንገዶች ባለስልጣን  ኪራይ ሰብሳቢዎች በባለሃብቱ እና በመስሪያ ቤቱ መካከል በመግባት ከፍተኛ ብዝበዛ እየፈጠሩ መሆኑን ይፋ አድርጓል፡፡ ሰኞ ነሃሴ 19/2006 ዓ.ም የመስሪያ ቤቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ስማቸው ንጋቱ በሰጡት መግለጫ የመስሪያቤቱ ወሳኝ ሰራተኞች ከደላሎች ጋር በፈጠሩት የረዢም ጊዜ ቁርኝት እያንዳንዱ ጨረታ ህጉን በተከተለ መንገድ ለመስራት አስቸግሮ እንደነበር ተናግረዋል፡፡ …

ነሃሴ ፳፯(ሃያሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቅርብ ተሰርተው ከተጠናቀቁት የኮንዶሚኒዮም ቤቶች መካከል ገሚሱን ለመከላከያየጦርመኮንኖችለመስጠትማቀዱንእናበቅርቡቤቶቹንእንደሚያስተላልፍከኢትዮጵያንግድባንክሰራተኞች የተገኘው  መረጃ አመልክቷል። የኮንዶሚኒየም ቤቶችን የሚያገኙ መኮንኖች በምን መስፈረት እንደተመረጡ ለጊዜው የታወቀ ነገር የለም። መንግስት ሰሞኑን በተለያዩ የአዲስ አበባ ክ/ከተሞች ለሚሰለጥኑ ፖሊሶች የኮንዶሚኒየም ቤቶችን እንደሚያድል ቃል መግባቱን መግለጻችን ይታወሳል።

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ኢትዮጵያ በ2005 ዓ.ም. የጀመረችውን የቡና ስያሜዎችና የንግድ ምልክቶች የማስመዝገብ ሂደት እንደገና አነቃቃች። የኢትዮጵያን አእምሯዊ ንብረት ጽሕፈት ቤት በበላይነት በሚመራውና ህገወጥ የቡና ንግድንና አላግባብ የሚጣል የቡና ዋጋ ተመንን ለመከላከል፣

የዩኤስ አሜሪካ ወታደራዊ አየር ኃይል በሰው አልባ አይሮፕላን በሶማልያ የሚገኙ የአሸባብ ሚሊሽያዎች ላይ የአየር ድብደባ አካሄደ። የአየር ጥቃቱ የተካሄደዉ ትናንት ሌሊት እንደሆን ተመልክቶአል።

ብሪታንያ ሀገሬ ላይ የአሸባሪዎች ጥቃት ሊደርስብኝ ይችላል በሚል ስጋት ካለፈው ሳምንት ወዲህ ቁጥጥሯን ማጥበቋ ተገለፀ። ከኢራቅ እና ከሶርያ የፅንፈኝነት አስተሳሰብ ይዘው የሚመለሱ የብሪታንያ ዜግነት ያላቸዉ ተጠርጣሪ ሙሥሊም አክራሪዎች

በያዝነዉ ዓመት የካቲት ወር በምዕራብ አፍሪቃ ጊኒ ከተከሰተ አንስቶ ወደተለያዩ የአካባቢዉ ሃገራት በመዛመት ከአንድ ሺህ አምስት መቶ በላይ ሰዎችን ህይወት መቅጠፉ የሚነገርለትን የኤቦላ ተኀዋሲ ለመከላከል የተለያዩ ሃገራት የየራሳቸዉን ጥረት እያደረጉ ነዉ።

ይህ መሠረታዊ ጥያቄ ነው። በተለይ በትግሉ ላይ የተሰማራነው ኢትዮጵያዊያን፤ ለዚህ ትክክለኛ መልስ መሥጠት አለብን። ለዚህ የምንሠጠው መልስ፤ ትብብሮችን ወይንም ውህደቶችን፣ ልዩነቶችን ወይንም መራራቆችን ያስከትላል። ከዚህ መሠረታዊ ጥያቄና ለዚህ ጥያቄ ከምንሠጠው መልስ፤ ማንነታችንን ብሎም የተሰባሰብንበትን ድርጅት ማንነት ማወቅ ይቻላል። እንግዲህ ሀገራችን ባለችበት ቀውጢ ሰዓት፣ የታጋዩ ክፍል ባለበት የተበታተነ ሀቅ፣ የተበታተነ ትግል በመከተል ትግሉ ማዕከል ባልያዘበት ሁኔታ፣ […]

በ1997 ዓ ም የቅንጅት በምርጫ ማሸነፍ ያሰጋቸው የወያኔ መሪዎች በሕዝብ ውስጥ መጠራጠርንና መከፋፈልን ለመፍጠር ፤ በ1994 ዓ ም በሩዋንዳ የተፈጠረውን የዘር ማጥፋት ተመስሌት ‘ኢትርሃሞይን’ ተቃዋሚዎች ሊፈጥሩ ነው ብለው ፕሮበጋንዳ ነዙ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለማያውቃችሁ ታጠኑ አላቸቸወ፤ በ1967 ዓ ም አማርኛ ተናገሪውን ለይተው ለማጥፋት በፕሮገራማቸው ነድፈው መቀሳቀሳቸውን በእነርሱ ቤት የኢትዮጵያ ሕዝብ አላየም፣ አልሰማም፣ አላነበበም፤ ኩኩ መለኮቴ መሰል […]

የማለዳ ወግ … የአረብ ሃገሩ ክፉ ስደት ! * እንደ እቃ እንጣላለን ፣ መደጋገፉ ጠፋ ! ገና ረፋዱ ላይ ጸሃዩ ናላን ያዞራል… የቢሮ የቤት ማቀዝቀዣዎች እንኳ ሙቀቱን ተቋቁመው የማብረድ ስራቸውን እንዳይከውኑ የሳውዲ ጅዳ በጋ ሃሩር ጸሃይ ፈተና ሆኖባቸዋል ! … በዚህ የቀለጠ የበርሃ ሃሩር ጤነኛ መቋቋም ያልቻለው ሙቀት በአንዲት ሰውነቷ የደቀቀ እህት ይወርድባታል … ቦታውም […]

ይህን የአንዱአለም አራጌን በራሱ አገላለጽ ከጠባቧ የቃሊቲ እስር ቤት የተጻፈ ግሩም መጽሐፍ ሳነብ የተሰማኝን ስሜት ባጭሩ ለመግለጽ እንጂ ሥነ ጽሑፋዊ ደንብ የተከተለ ሂስ ወይም የመጽሐፍ ግምገማ ለመስጠት አለመነሳቴን መግለጽ እፈልጋለሁ – መሆኑን እንዴት ከረማችሁ?

ከሁሉ በፊት ግን ከሰሞነኛ ጉዳዮች መካከል ቂላቂሉ ወያኔ በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ የሠራውን አስቂኝ ድራማ ስመለከት እያዘንኩ የታዘብኩትን በዓለም ወደር የማይገኝለት ምርጥ የምርመራ ውጤት በሚመለከት ትንሽ ልበል፡፡

የኢትዮጵያን ቴሌቪዥን በውነቱ አልመለከትም፤ አለመመልከቴ ስህተት መሆኑ ቢገባኝም ጤንነቴን አጥብቄ ስለምፈልገው ይሁነኝ ብዬና ቁም ነገር አገኝበታለሁ ብዬ ኢቲቪን አላየውም – ብዙዎች እኔን መሰሎች ስላሉ “የዐዋጁን በጆሮ” እንዳትሉኝ እንጂ፡፡ የሆኖ ሆኖ በቀደምለታ ከሰዎች ጋር የሆነ ቦታ ቁጭ ብዬ ቁርስ ቢጤ ስንቀምስ በፖሊስ ፕሮግራም የተከታተልኩት በዓይነቱም ሆነ በይዘቱ ድንቅ የሆነ የወያኔ የወንጀል ምርመራ ቴክኒክና ውጤት ያጫረብኝን ልዩ ስሜት በዚህ አጋጣሚ ሳላነሳው መቅረት አልፈለግሁም፡፡ ከእውነት ሰው መሆኔን ጠላሁ፡፡

“መርማሪው” ወያኔ አይታይም፤ ይህን የለመድነው ነው፡፡ ወያኔዎች ራሳቸውን እንደወንጀለኛ አድርገው ስለሚቆጥሩና ከአልቃኢዳ ጋር የሚያመሳስሏቸውን ድርጊቶች የሚፈጽሙ መሆናቸውን ሕዝቡ የተረዳው መሆኑን ስለለተገነዘቡ ይመስለኛል የመንግሥትን ሥልጣንና ኃይልም የጨበጡ “ምሁራኑ መርማሪዎች” በግልጽ በሚዲያ መታየትን የሚወዱ አይመስሉም ፤ እነዚህ ጭራቅ ገራፊዎችና ሀዘን አምላኪዎች (ሳዲስቶች) በራሳቸውም በመንግሥታቸውም የሚተማመኑ እንዳልሆኑና በሆዳቸውና በዘረኝነት ቁርኝታቸው ብቻ ተለክፈው በስሜት ፈረስ የዕውር ድምብር ግልቢያ ዜጎችን የሚያሰቃዩ ናቸው – ቀናቸው ሲደርስ ምን እንደሚውጣቸው ፈጣሪ ብቻ ነው የሚያውቀው፤ አሣር አለባቸው – የቁናው ሥፍር እየተንደረበበ ይጠብቃቸዋል – እዚህ ወይም እዚያ፡፡ ከሞራል ዕሤቶቻችንና ከምርመራ ህግ በወጣ ሁኔታ አቡበከር የሚባለውን የሙስሊም ተቃውሞ አመራር አባል እጆቹን በእጀሙቅ አስረው የሚያካሂዱትን “ምርመራ” በአደባባይ በቲቪ ለዓለም ሕዝብ ሲያሳዩም “መርማሪው ሊቅ” መታየትን አልወደደም – አስጠሊታ ሣቁ ግን ከአንጀቱ ጥርስ ሳይሆን ከማተብ የለሽ አንገቱ ይሰማ ነበር፡፡ ስለዚህ የአንዲ ልዩነት እጆቹ አለመታሰራቸው እንጂ ሂደቱ ልክ እንደአቡቦከር ነው፡፡ ይህ የምርመራ ሂደትና ውጤቱ የሀገራችን የለየለት ውርደትና የወያኔን ማንአለብኝነት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው፡፡ ወያኔዎች ከግዑዝ ድንጋይ የማይሻሉ የመጨረሻ ደደቦች መሆናቸውን ምናልባትም ለሚሊዮንኛ ጊዜ የገለጡበት ማፈሪያ ድርጊት ነው፡፡ የሚታዘነው በተመርማሪዎቹ ሳይሆን በመርማሪ ተብዬዎቹ ነው፡፡ ከመነሻው የዘረኝነት ልክፍት ያሽመደመደውና ከዘር ማዕቀፍ ውጭ የማያስብ ደንቆሮ ማይምና ሳዲስት እንዴት አንድን የተማረን ሰው ይመረምራል? እንዲያው ትንሽም ቢሆን የተማረ ዘረኛ ወያኔ ጠፍቶ ነው ወይ? ይህ ዓይነቱ የአደባባይ ግፍ ሄዶ ሄዶ የሚያስከትለውን መዘዝ እንዴት አጡት? ድንቁርና ይህን ያህል በጀብደኝት ያሳውራል?

ወደአስቂኙ ድራማ ልለፍ፡፡ አንዳርጋቸው በ“ነፃ ኅሊናው” የሰጠውና ለኢትዮጵያ ሕዝብ በደናቁር የወያኔ ወንበዴዎች እሳቤ ሊተላለፍ የተፈለገው መልእክት ይህን ይመስላል፤ “የግንቦት ሰባት ኅልውና ከእንግዲህ ግፋ ቢል ለሁለት ወራት ቢዘልቅ ነው፤ ወዲያም አለ ወዲህ ዕድሜው ከሁለት ወር አይበልጥም፡፡ የአውሮፓና አሜሪካ ምቾቱን ትቶ እንደኔ በረሃ ወርዶ የሚያታግል ቆራጥ ሰው አይኖረውም፡፡…” የግንቦት ሰባት ቀሪ ዕድሜ ሁለት ቀንም ይሁን ሁለት ወር እሱ ሌላ ጉዳይና ወደፊትም የሚታይ ሆኖ ይህን የተናገረው ግን አንዳርጋቸው ጽጌ መሆኑን ልብ ይሏል – አንዲን በሚዲያም ቢሆን ባላውቀው ኖሮ ከአሁን በፊት “የተናገረውን”ና ገና ወደፊት “እንደሚናገረው በጉጉት” የሚጠበቀውን ሁሉ በበኩሌ ሳላንገራግር በሙሉ ልቤ አምኜ በተቀበልኩና ከወያኔ የሸፈተውን ልቤን ወደወያኔ በመለስኩ ነበር – ይህ ሁሉ ድካማቸው ታያ የማንን ቀልብ ለመሳብ ? በመሠረቱ እስካሁን ወያኔ የነበረ በአንዳርጋቸው ንግግር ምክንያት የወያኔነት ደረጃው አይጨምርም – በተቃራኒውም እስካሁን ወያኔ ያልነበረ በዚሁ የአንዲ ንግግር ምክንያት ንዴቱና ቁጭቱ ይጨምርና ወደድርጊት ይገባ እንደሆነ እንጂ ከተቃዋሚነቱ የሚያፈገፍግ አይመስለኝም፤ እናም የወያኔዎች የጅልነት ምጥቀት ያሳዝነኛል ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያውያንንና ዓለምን በጠቅላላው እስከዚህን ያህል መናቃቸው ምን ያህል ወራዳዎች – እደግመዋለሁ ምዕመናን – ምን ያህል ወራዳዎች መሆናቸውን ከማሳየት በስተቀር የአንዲ ስቃይና የሙሌት ኑዛዜ የሚጨምርላቸው አንዳችም አወንታዊ ነገር የለም – ይህን ነባራዊ እውነት ለመናገር ደግሞ የክር ወይም የሃቂቃ ጉዳይ እንጂ የግንቦት ሰባት አባልም ሆነ ደጋፊ መሆንን አይጠይቅም፡፡ የወያኔዎችን ውስጠ ምሥጢርና የግፍ ታሪክ በየመድረኮች ሲዘከዘክ ሚሊዮኖችን በዕንባ ሲያራጭና በትካዜ ባህር ሲያሰምጥ የምናውቀው አንዳርጋቸው ጽጌ በምትሃታዊ ፍጥነት ወደማፊያው መንግሥት ተገልብጦ ተናገረው የተባለውን እንዲያ ሲናገር ይታያችሁ፡፡ የምናውቀው አንዳርጋቸው የምናውቅለትን ጽኑ ፀረ-ወያኔ አቋሙን በሻጥርና በብዙ ገንዘብ ክፍያ በየመኖች ተይዞ በወያኔዎች እጅ በገባ በሁለት ሣምንታት ጊዜ ውስጥ ሲለውጥ በዐይነ ኅሊናችሁ ይታያችሁ፡፡

ግሩም የምርመራ ውጤት! ዓለምን የሚያስደምም ሣይንሳዊ የወንጀል ምርመራ ግኝት! በዚህ በአንዳርጋቸው ቃልና የመከራ ኑዛዜ ማፈር ያለበት ቀደም ሲል ለመጠቆም እንደሞከርኩት ወያኔ ብቻ ነው፡፡ ከወያኔ ውጭ ማንንም ሊያሳፍር አይችልም፡፡ እንዲያውም እኔ ብሆን ኖሮ “ግንቦት ሰባት የሚባል ድርጅት ከነአካቴው በሕይወት አለ እንዴ? አሁን እናንተ ስትሉ ሰማሁ፡፡ ማን ተናገር እንዳለኝ አላውቅም ዝም ብዬ ነበር እኮ በኢሳት ያንን ሁሉ ንግግር የምዘባርቀው፡፡ ደግሞ ብርሃኑን ብሎ ግንቦት ሰባት! ከመነሻው ግንቦት ሰባት ብሎ ነገር ሲኖር አይደለም ወርቆቼ! …” ብዬ አስደስታቸው ነበር እንጂ የሌለን ምሥጢር ለመደበቅ በመሞከር ሰውነቴን ለስቃይ አልዳርግም – ሊያውም በዚያ ኑዛዜየም ስቃዩን ቢቀንሱልኝ አይደል? ግን አይቀንሱልኝም – ስለዚህ ብናገርም ባልናገርም ለውጥ የለውም፤ ጠባችን በደም የሚጠራ እንጂ በውሃ ታጥቦ የሚጸዳ አይደለምና፡፡

እንደውነቱ ታዲያ አንዳርጋቸው ሊሰጠው የሚችለው የማይታወቅ የተከደነ አዲስ ምሥጢር ሊኖር ይችላል? ሁሉም ነገር እኮ ግልጽ ነው፤ ወያኔ የሚባል ሀገር አጥፊና ፀረ-ሕዝብ የሆነ የማፊያዎች ቡድን አራት ኪሎ ቤተ መንግሥት ውስጥ መሽጎ አለ – እሱን ለማስወገድ ደግሞ ዜጎች በተበታተነ ሁኔታም ቢሆን በየፊናቸው ጥረታቸውን እያደረጉ ነው፤ ምሥጢር ከተባለ ይህ ነው ምሥጢሩ፡፡ አንዳርጋቸው የትግል መስመሩ ስላበሳጫቸውና እየሠራ ያለው ነገር ለኅልውናቸው አስጊ ሆኖ ክፉኛ የሚያሳስባቸው በመሆኑ እርግጥ ነው እሱን ከመድረክ ገለል እንዲል ማድረግ ቢፈልጉ ያንን መቀበል ይቻላል – ሰይጣናዊ ፍላጎታቸውን ለማርካት የሄዱበት ርቀት ብዙ የሕግና የሞራል ችግር ማስነሳቱ እንዳለ ሆኖ፡፡ ከዚያ ውጪ ምሥጢር አውጣ ብሎ የዓለማችን ቤት ባፈራው የማሰቃያ ዘዴ ሁሉ ሰውን ማሰቃየት፣ በዚያም ሂደት ራስን ለትዝብትና ለስላቅ የሚያጋልጥ ነውረኛ የምርመራ ሂደት ማካሄድና ተመርማሪዎች የማያምኑበትን ነገር እንዲናገሩ ማድረግ በእግረ መንገድም “በሰላም አንገዛም፣ አንገብርምም ያሉንንና ሕዝብን የሚያሳምጹብንን ቀንደኛ ጠላቶቻችንን ‹እንዲህ አሸናናቸው!›፣ የወንዶች ወንዶች መሆናችንን ብልታቸውን እየቆረጥን አሳየናቸው…” በማለት ስብዕናን ለማዋረድ መሞከር ወደራስ የሚዞር አሉታዊ ውጤትን መጋበዝ መሆኑን መረዳት ይገባቸው ነበር፡፡ ለነገሩ ወያኔ ልብሱም ጉርሱም ቅሌትና ውርደት በመሆኑ በዚህ ረገድ የሚሰማው አንድም የሀፍረትም ሆነ የይሉኝታ ስሜት የለም፡፡ ጃዝ ብለው የለቀቁት 13 እና 33 ቁጥሮችም እየሳቁበትና እየተዝናኑበትም ቢሆን ወያኔ ለሚሠራው ግፍና በደል ሁሉ ቡራኬያቸውን አይነፍጉትም፡፡ እነሱስ ቢሆን በጭፍሮቻቸው አማካይነት በጓንታናሞና ኢራቅ ውስጥ አስከሬኖች ላይ እስከመሽናት በሚዘልቅ ኢሰብአዊነት ስንትና ስንት ግፍ ይፈጸሙ የለም? ልጅ ከአባት ቢማርና የጭካኔ ደረጃውን አዘምኖ ምሥኪን ኢትዮጵያውያንን ምድራዊ ገሃነም ውስጥ ቢዘፍቃቸው ዋኖቹ ሀዘን አምላኪዎች ይደሰታሉ እንጂ ከከንፈር ሽንገላ ባለፈ ሕዝቡን ሊታደጉት አይፈልጉም – ይህንንም አሳምረን እናውቃለን፡፡ ጭምብሉን ፖለቲካዊ የተለሳለሰ የሚመስል አካሄድም አንዘነጋም – አገም ጠቀሙን፡፡

በነገራችን ላይ 13 እና 11 ወይም 33 ደግሞ ተመሳሳይነት አላቸው፡፡ ለሚያምንበት ሁሉም የትልቁ ቁጥር የአውሬው መገለጫ የ666 ቅንስናሾች ናቸው፡፡ አሥራ አንዶች በ110 የለበጣ ቀመር ቢያላግጡም እውነቱ ቀፎ የመለዋወጥ – የትሮይን ፈረስ ቅርጽ የማሻሻል ጉዳይ እንጂ ሲሙ ያው ነው – አሥራ አንድ፡፡ ለነገሩ ዝናር ባንገቴም ይሁን 11 ወይም ዜሮም ይሁን አንድ ሽንትር ዋናው ነገር ተግባር ነው፡፡ ሌላው ትርፍና ጨዋታን ለማሳመር ያህል በአጃቢነት የገባ ነው፡፡ እናም በሀገራችን ሁኔታ የሰውዬው ማንነት ምንም ይሁን ምን በስቃይና በግድያ የሚያምን ሁሉ እናት ክፍሉና ጥንተ አመጣጡ ከአውሬው መሆኑን ልብ ይሏል፡፡ ክፉና ደግ መንፈሶች ኅብረት የላቸውም፡፡ ሩህሩህ መሐሪና አረመኔ/ጨካኝ ገዳይ አንድነት የላቸውም፡፡ መጽሐፉም ጣፋጭ ፍሬ በዛፍ ላይ ሳለ ይታወቃል እንደሚል ማን የማን ወገን መሆኑ በተለይ በዘመናችን በግልጽ ይታወቃል፡፡ ማን ነው የበሽታ ሕዋሳትን በቤተ ሙከራ እየፈለሰፈና እያራባ ለዓለም በተለይም ለኋላቀር ሀገሮች እንደ ዕርዳታ ስንዴ የሚያከፋፍል? ማን ነው የዓለማችንን የአየር ንብረት እያዛባና ዕድሜዋን በብርሃን ፍጥነት እያሳጠረ የሚገኘው? የዓለምን ጠቅላይ ገዢነት በትረ መንግሥት በጉልበት የተቆጣጠረውና “ለኔ ካልሰገዳችሁ ሀብትና ሥልጣን አይኖራችሁም” ብሎ ሁሉን እያስደገደገ የሚገኘውና በትዕምርተ ኅቡኣታዊ ባለአንድ ዐይን ፒራሚዳዊ ቅርጽ ወይም በፔንታጋራማቲን የኮከብ ቅርጽ የሚታወቀው ምሥጢራዊ ኃይል ማን ነው? ማን ነው አሁንም ሆነ ከአሁን በፊት መካከለኛውን ምሥራቅ እያተራመሰ ያለው? መፍለቂያው የሆነችን የአንዲት ትንሽዬ ሀገር ኅልውናና የበላይነት ለማስጠበቅ ሲል ድምጽን በድምጽ የመሻር መብቱ የዓለምን የመንግሥታት ኅብረት እንደአሽከር ሰጥ ለምበጥ አድርጎ የሚገዛ ማን ነው? አይኤም ኤፍ፣ ዩኤን፣ ወርልድባንክ፣ ኔቶ፣ ሲአርኤፍ፣ … የማን አድቃቂ ክንዶች ናቸው? ለመሆኑ የዚህ ሞገደኛ የወቅቱ የዓለማችን ገዢ ዋና መሥሪያ ቤትና ቅርንጫፍ ቢሮዎቹ የት የት ናቸው? ጽዮንና ሀማስ የማን ልዑካን ናቸው? የግጭቶች መንስኤና የምክንያታዊነት ሚዛኑ ለማንም ያጋድል ዋናው የሁለቱም ተልእኮ ግና ለአውሬው ግብር የሚሆን ብዙ የደም ባህር ማቆር መሆኑን መዘንጋት የዓለም ነገር አያገባኝም ብሎ እንደመመነን ይቆጠራል፡፡ በየትኛውም የዓለም ክፍል – ማን ነው የጦር ኃይሎችን በሁለት ጎራ እየከፈለ በተፃራሪነት በማሰለፍ የሚሊዮኖችን ደም በከንቱ እያፋሰሰ ያለው? ኢራንና አሜሪካ በርግጥም ባላንጣዎች ይሆኑ እንዴ? በፍጹም፡፡ ጠላቶች መስለው ትያትር በመከወን ለአንድ ዓላማ ስኬት የሚተጉ የአንድ ገዢ አንድ አምሳል አንድ አካል ናቸው፡፡ ማን ነው በአራት ወራት ጊዜ ውስጥ ብቻ ከአፍ እስከገደፋቸው በንጹሃን ተሣፋሪዎች ጢም ብለው የሞሉ የሲቪል አውሮፕላኖችን(የማሌዥያን) ባልታወቀ ዕፀ መሠውርና በሚሳኤይል ድራሻቸውን ያጠፋው? ምን ዓይነት ወያኔያዊ ጨካኝ አንጀት ያለው ፍጡር ይሆን ይህን ያደረገ? ለምን ዓላማ? ቫቲካንንና መለስተኛ አውሮፕላን የምታህል የነጭ እርግብ ምስል ለማስመሰል ያህል በሰላም ምልክትነት በዋና የፓትርያርክ ጸ/ቤቱ በር ላይ ያቆመውን የኛኑ ኦርቶዶክስ ሳይቀር ከሞላ ጎደል ሁሉንም የሃይማኖት ተቋማት ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ተቆጣጥሮ ሁሉንም ሃይማኖት አለኝ ባይ በአውሬው ትዕዛዝ ሥር ያደረገው ማን ነው? ለመሆኑ በአሁኑ ሰዓት ቅዱስ ሊባል የሚችል ቦታና ሰው አለ ወይ? ፖፕ ጆን ፖል አንደኛ፣ ፖፕ ቤኔዲክት 16ኛ፣ ‹አቡነ› ጳውሎስ የኛ… ሌሎችም የማን ወኪል ነበሩ? ፍየሎች በበጎች ጋጣ ውስጥ መሽገዋል፡፡ በጎች እያለቁ ነው፡፡ አውሬው ሆሊውድና ቦሊውድን ብቻ ሳይን ገዳማትንና ካቴድራሎችንም ከተቆጣጠረ ምዕተ ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ ጭካኔን በሚያስተምሩ ፊልሞች፣ በልቅና ባልተገሩ ኢ-ሞራላዊም በሆኑ ፖርኖግራፊዎች በተለይ የዓለምን ወጣት ትውልድ ጡጦ ከመጣሉ በእንጭጩ ለማምከን ይህችን ዓለም ማንና ከየትስ ሆኖ እየገዛት እንዳለ መች አጣነው? የዚያ ‹ታላቅ› የጨለማ ንጉሥ የእጅ ሥራዎች የሆኑ ወያኔዎችም ባቅማቸው ቅድስቲቱን ሀገር ድራሽዋን ቢያጠፏት ከድጋፍ በስተቀር ማን ከልካይ አላቸው? በጎችስ ቢጮኹ አለጊዜው ማን ይደርስላቸዋል? ግን ግን አይዞን፤ የፍየሎችና የበጎች የመጨረሻ ዕድል ተለይቶ የሚታወቅበት የፍርድ ቀን በፍጥነት እየመጣ ነው፡፡ ብሎም ቢሆን ሥጋዊም ሆነ መንፈሳዊ ድል በምኞት ሊገኝ እንደማይችል ልብ ማለት ይገባናል፡፡ ብቻ ይህን መሰሉን ነገር በሆድ ይፍጀው ለሌላ ቀን በይደር ማቆየቱ ሳይሻል አይቀርም፡፡ ለነገሩ እኛን ምን አገባን? ሁሉም ከልኩ አይዘል፡፡

ከሰው ተውሼ እያነበብኩት ነበር – “ያልተሄደበት መንገድ”ን፡፡ በቅርብ ካነበብኳቸው በሀገር ችግር ዙሪያ ከሚያጠነጥኑ የቅርብ ጊዜ መጻሕፍት ውስጥ በኔ ዕይታና ለኔ ፍጆታ ይሄኛውን ወደር አላገኘሁለትም፡፡ አንዱአለም አራጌ ዋለ የተዋጣለት መጽሐፍ በመጻፉ – ሊያውም በዚህ አፍላ የጎልማሳነት ዕድሜውና በመከራ ውስጥ ሆኖ – ባለበት አድናቆቴ ይድረሰው፡፡ ወላድ በድባብ ትሂድ የሚባለው በዚህ ዓይነት አጋጣሚ ነው፡፡ ሚሊዮኖች ፈርተንና ለሥጋችን አድረን በየሽርንቁላው ተወትፈን በፍርሀት ቆፈን ስንርድ ሊያውም በእስር ቤት ውስጥ ሆኖ ይህን የመሰለ አብሪ መጽሐፍ ካለበቂ ማጣቀሻና ዋቢ መጻሕፍት በአዩኝ አላዩኝ ሰቀቀን ሌሊት ሌሊት እየተደበቁ መጻፍ ልዩ ጀግንነትና ተሰጥዖም ነው፡፡ አንዱአለምና መሰል የብዕርና የፖለቲካ ታጋዮች ለነፃይቱ ኢትዮጵያ በሕይወት እንዲደርሱ እግዚአብሔር ይታደገን፤ ይታደጋቸው፡፡ ቤተሰባቸውንም ይባርክ፡፡ ለእኛም ለባከንነውና ለራሳችን ጥቅምና ፍላጎት ስንል በ‹እስኪያልፍ ያለፋል› ተረት ራሳችንን እያታለልን የወያኔ ባርያ ሆነን ለጠፋነው ዜጎችም ፈጣሪ ረድኤቱንና ወኔውን ይስጠን፡፡ እንደዚህ ያሉ ዜጎች ባይኖሩን ኖሮ ሕይወት በጠቅላላው ለይቶላት ጨለማ በሆነች ነበር፡፡ ከዚህ አንጻር እግዜር የተመሰገነ ይሁን፡፡ እርሱን መሰል ሌሎች ጸሐፊዎችንና ታሳሪዎችንም ጭምር እግዜር ይባርክልን፡፡ ለቤታቸውም ያብቃልን፡፡ የሚሳነው ነገር የሌለው የኢትዮጵያ አምላክ የመከራ ደብዳቤያችንን የሚቀድድና ሃራ የሚያወጣን አንዳች ኃይል ይዘዝልን፡፡ አሜን፡፡

ይህ መጽሐፍ የዋቢ መጻሕፍትን ገጽ ጨምሮ በጠቅላላው 320 ገጾች አሉት፡፡ በአራት ዋና ዋና ክፍሎች ሥር የተካተቱ 18 ርዕሶችንም ይዟል፡፡ ጠቅጠቅ ብሎ የተጻፈ በመሆኑ እንደሌሎች በርካታ መሰል መጻሕፍት በቀላሉ አይገፋም፡፡ የሆኖ ሆኖ በተለይ እስከማገባደጃው ድረስ ስሜትን ቆንጥጦ በመያዝ መነበብ የሚያስችለው ሥነ ጽሑፋዊ ውበትና ይዘታዊ ግርማ ሞገስ አለው፡፡ እናም አንብቡት፡፡ በነገራችን ላይ ይህን መጽሐፍ እያነበብኩ ወደ ገጽ 100 አካባቢ ስደርስ የተዋስኩትን እንደምመልስ ገባኝና ወዲያውኑ ከተማ ወጥቼ ገዛሁት፡፡ ተውሼ ያነበብኩትን ወይም እያነበብኩት ያለሁትን መጽሐፍ ስገዛ ይህ የመጀመሪያ ጊዜየ ነው፡፡ አንጡራ ሀብቴና የመጻሕፍት መደርደሪያየ አንዱ ፈርጥ እንዲሆን ተመኘሁ፡፡ ተመኝቼም አልቀረሁ፡፡ ለልጆቼ ውርስ ይሆናል፡፡ እናንተም አሁኑኑ ግዙና ንብረታችሁ አድርጉት፡፡ መጽሐፉ “ኩሎ አመክሩ ወዘሰናየ አጸንዑ” እንዲል፡፡

አመስጋኝ አማሳኝ እንዳልባል በዚህ መጽሐፍ የታዘብኳቸውን አንዳንድ ግድፈቶችም በዚሁ አጋጣሚ ብጠቁም ደስ ይለኛል፡፡ ጥቂት የማይባሉ የአርትዖት ችግሮች አሉበት፡፡ አሉታዊ መሆን ያለበት በአወንታዊ ወይም የዚህ ተቃራኒ ሆኖ የሚጻፍበት አጋጣሚ አልፎ አልፎ ይስተዋላል፡፡ አማርኛ ላይ ብዙውን ጊዜ የምታስቸግር ነገር አለች – ለምሳሌ “እኔን እንደሚያገባኝ እንዴት ረሳኸው?” በሚለው ዐረፍተ ነገር ውስጥ “ሚ”ን “ማ” ብናደርጋት ትርጉሙ ሙሉ በሙሉ ይለወጣል፡፡ “ጽንፍ” ለማለት “ቅንፍ” ብንል አንዳንዶችን ግር ሊያሰኝ ይችላል፡፡ የአርትዖት ሥራ ሽንፍላ እንደማጠብ ነው፡፡ በተቻለ መጠን ብዙ ሰዎች በብዙ አዳዲስ ዐይኖች ሊተባበሩበት የሚገባው አስቸጋሪ ሥራ ነው፡፡ እንዲያም ሆኖ የማይጠራበት ጊዜ አለ፡፡ ከዚህ አኳያ ይህን ቆንጆና ለታሪክ የሚቀመጥ መጽሐፍ ዐዋቂ ሰው እንደገና “ኤዲት” ቢያደርገው የበለጠ ማለፊያ ይሆናል፡፡ የግሌ አስተያየት ነው፡፡ (አንድ ወዳጄ የነገረኝ አንድ አርትዖታዊ ስህተት በጭንቅላቴ ብልጭ እያለ ‹እዚህ ላይ ካልጻፍከኝ ሞቼ እገኛለሁ!› ብሎ አስቸገረኝ፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው፡፡ የመሥሪያ ቤቱ የብድር ኮሚቴ ስብሰባ ይጠራል፡፡ ለተሰብሳቢዎችም “ከብድር ኮሚቴ…. ለጠቅላላ አባላት” የሚል ጽሑፍ ተበትኗል፡፡ ሁሉን ያስፈገገው ግን ጸሐፊዋ “ከብድር ኮሚቴ” ከሚለው ሐረግ ውስጥ የአንዱን ቃል የመጨረሻ ፊደል ሳትጽፈው መቅረቷና እስከዚያን የስብሰባ ጊዜ ድረስ ማንም ጉዳዩ የሚመለከተው አካል ስህተቱን ልብ አለማለቱ ነበር፡፡ ያቺ “ነገረኛ” ጸሐፊ የትኛዋን ሆሄ እንደዘነጋቻት እኔም አሁን ዘነጋኋት፡፡ )

ከሆሄያት ግድፈትና ሞክሼ ፊደላትን በነባሩ ሰዋስዋዊ ልማድ ከመጠቀም አኳያ ከሚታዩ አንዳንድ ጥቃቅን “ስህተቶች” በተጓዳኝ ጥቂት የመረጃ መዛባትና የዘይቤና ፈሊጥ አጠቃቀም እጅግ አነስተኛ ችግር ሳይኖር እንደማይቀር እገምታለሁ፡፡ ለምሳሌ “ኢሕአፓ” የሚለው ምሕጻረ ቃል ሲፈታ እኔ የማውቀው “የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ ፓርቲ” በሚል ነው፡፡ በዚህ መጽሐፍ ግን “የኢትዮጵያ ሕዝብ አደራጅ ፓርቲ” በሚል ከአንዴም ሁለቴ ገደማ ቀርቧል፡፡ ፈሊጥን በተመለከተ “ለያዥ ለገራዥ” ለማለት “ለያዥ ለገናዥ” ተብሏል፡፡ በተጨማሪም የሃሳብ ድግግሞሽ በስፋት ይታይበታል፡፡ በዚያም ምክንያት አንድ አንባቢ በጀመረበት የስሜት ሞቅታ መጨረስ ባይችል ችግሩ ከዚህ የሃሳቦች መደጋገም የሚመነጭ ይመስለኛል፡፡ የሆኖ ሆኖ የመጽሐፉ አጻጻፍና ለኅትመት መብቃት በብዙ ችግር የታጠረ በመሆኑ የአሁኑ ይዘቱ ራሱ ከሚጠበቀው በላይና በአንጻራዊ ሁኔታ ከሌሎች በርካታ መሰል ጸሑፎች(እኔ ካነበብኳቸው) በጣም የተሻለ መሆኑን በበኩሌ ልገነዘብ ችያለሁ፡፡ በመሆኑም ይህ ጥረቱ ደራሲውን በእጅጉ ያስመሰግነዋል፡፡ እዬዬም ሲደላ ነው ጓዶች፡፡ እነኚህንና መሰል ሌሎች እንከኖችን አስተካክሎ በቀጣይ ኅትመት ለንባብ የሚያበቃው ወገን ከተገኘ መልካም ነው፡፡ ደግሞም የማይቻል አይመስለኝም፡፡

አንዱአለምን በዚህ መጽሐፉ ደርቤ እንዳነበብኩት የፕሮፌሰር መስፍን ደቀ መዝሙር ይመስለኛል፡፡ ይህን የምለው ፕሮፌሰሩ አንድ ወቅት እነብርሃኑ ነጋ “ሁለገብ ዘዴን በመጠቀም ወያኔን እንታገላለን” ባሉ ወቅት ክፉኛ ይተቿቸውና “እኛ ወደዚህ ‹የማይረባና ውዳቂ› የአስተሳሰብ ደረጃ አንወርድም” ማለታቸውን በማስታወስና አንዱአለምም በዚያው ቅኝት አሁንም ድረስ በዚህ በኢትዮጵያ ውስጥ ወንዝ ቀርቶ የደረቀ ምንጭ በማያሻግር የሰላማዊ ትግል ሥልት ወያኔን እንጥላለን ብሎ የሚያምን በመሆኑ ነው፡፡ እርግጥ ነው አንዱአለም አሁን ባለበት ሁኔታ በኃይል ወይም በጦር መሣሪያ ወያኔን እንታገል ብሎ ቢጽፍ የሚደርስበትን ተጨማሪ መከራና ፍዳ ስለምንገነዘብ ይህን አቋም ያርምድ ብለን በሰው ቁስል እንጨት አንሰድም፡፡ ይሁንና ቢያንስ ዝም ማለት ሲገባ ወያኔ የፈጠረው የኢትዮጵያ ውጥንቅጥ ችግር የሚፈታው ወያኔን በሰላማዊ መንገድ በመታገል ብቻ ነው የሚል እምነት በጭፍን ማራመዱን አልወደድኩለትም፡፡ (በነገራችን ላይ ኤርምያስ ለገሰ ቅድም በኢሳት አንድ ውይይት ላይ ሲናገር እንደሰማሁት የአንዳርጋቸውን በወያኔዎች መያዝ ኔልሰን ማንዴላ በኢዲያሚን ዳዳ እንደተያዘ ያህል እቆጥረዋለሁ ማለቱን እኔም በጣም እደግፋለሁ፡፡) ሰው ከሰው ጋር ቢታገል አሸናፊውና ተሸናፊው ይለያል፡፡ ከአውሬ ጋር ግን እንዴት መታገል ይቻላል? ውሾች በ“አስተሳሰብ” ከሚበልጡት ወያኔ ጋር እንዴት ስለሰላም መወያየት እንደሚቻል አንዱአለም ቢያስረዳኝ ደስ ባለኝ፤ ውሾ ሲሸናነፉ በሚያሳዩት ተፈጥሯዊ ምልክት ይግባቡና ጦርነቱን ያቆማሉ፤ ከዚያም በመካከላቸው ሰላም ይሰፍናል፡፡ ሁኔታዎችም ወደጥንቱ (statusquo ante) ይመለሱና ማኅበረከልባዊ ሕይወት ትቀጥላለች (“ከልብ” ውሻ ማለት ነው – “ል” ጠብቃ አትነበብም)፡፡ ወያኔ ግን ያሸነፈውን ሁሉ በሕይወት ያለውን ብቻም አይደለም የሞተውን ሳይቀር እስከ&#4