የሴራሊዮናዊዉ ሞትና የፍርድ ዉሳኔ

አንድ የጀርመን ፍርድ ቤት በእስር ላይ ሳለ በእሳት ቃጠሎ ሕይወቱን ባጣ የዉጭ ዜጋ ጉዳይ በፖሊስ ላይ ያሳለፈዉን ፍርድ አጸና። ካልስሬኸ ከተማ የሚገኘዉ የፌደራሉ መንግሥት ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሴራሊዮናዊዉ እስረኛ በንዝህላልነት ሕይወቱ ጠፍቷል በሚል ከዚህ ቀደም በፖሊስ ላይ የተጣለዉን የገንዘብ ቅጣት ዛሬም በድጋሚ አፅንቶታል።