]በአሉ ግርማና አስፋው ዳምጤ

[email protected]

ባለፉት ወራት የአገር ቤቶቹንም ሆነ ውጪ ያሉትን የሚዲያ አውታሮች በተለያየ መልክ ያነጋገረው የበአሉ ግርማ አሟሟት ላለፉት 30 አመታት ሲያነታርክ ቆይቶአል ። እስከደርግ መጨረሻ ድረስ በድብቅ ፤ ከዚያ በኋላ ደግሞ በግልፅ አነታርኳል ። ይህም የሆነው በሁለት ምክንያቶች ነው ። አንደኛው ምክንያት በአሉ ግርማ በኢትዮጵያ ዘመናዊ ስነ-ፅሁፍ አቻ የማይገኝለት ደራሲ በመሆኑና በብዙ አንባቢዎቹ ልብ ውስጥ ልዩ ቦታ ያለው መሆኑ ሲሆን ፣ ሁለተኛው ደግሞ ፍትህንና እውነትን ፈላጊ ተስፋ የማይቆርጥ ቤተሰብ ስላለው ነው ። በተለይ ደግሞ ባለቤቱ ወ/ሮ አልማዝ አበራ ። ለፍትህ እታገላለሁ የሚል ወገን ሁሉ ለበአሉ ግርማ ቤተሰብ ፍትህ ማግኘት የበኩሉን አስተዋፅኦ ሊያደርግ ይገባዋል የሚል እምነት አለኝ ። ይህን ያልኩበት ምክንያት በውጪም ሆነ በአገርቤት “በቃ በአሉ ግርማን ደርግ ገድሎታል ሁላችንም የምናውቀው ነውና እንተወው ፦ የሚሉ ወገኖች ስላሉ ፤ በተለይ የእያንዳንዱ ግለሰብ የግል ነጻነት ተከብሮ በሚኖርበት አውሮጳና አሜሪካ እየተኖረ ይህን የመሰለ ድፍን ያለ ድምዳሜ ላይ መድረስ በስደት ከየምንኖርበት አገር የፍትህ ስርአት የተማርነው እንደሌለና ሆዳችንን ከመሙላት በቀር ምንም ትርፍ እንዳላመጣን ማሳያ ይሆናልና ነው ።

ይህን ካልኩ በኋላ ለዛሬ አብይ ነው ብዬ ወደተነሳሁበት ጉዳይ ልምጣ ።

አቶ አስፋው ዳምጤ “በበአሉ ግርማ ጉዳይ ላይ ከህሊና እዳ ነፃ ነኝ” በሚል ርዕስ ስለ በአሉ ግርማ መሰወር ጉዳይ የሰጡትን ቃለ- መጠይቅ ፍቱን ከምትባል መፅሄት ላይ ተወስዶ በአንድ ዌብ ሳይት ላይ ተለጥፎ አግኝቼ አነበብኩትና ከቃለ መጠይቁ የተረዳሁትን ለአንባቢ ለማሳወቅ ፈልጌ ነው ።
አቶ አስፋው ፤ በመጀመሪያ በራስዎ ስም መልስ ለመስጠት በመሞከርዎ ላድንቅዎ እፈልጋለሁ ።የሰጡት መልስ አሳማኝም ይሁን አይሁን ዋናው ለቀረበብዎት ጥያቄ በቃለ-መጠይቅ መልክ መልስ ለመስጠት ሞክረዋል ። ያስመሰግንዎታል ። ከቃለ መጠይቅ ይልቅ በራስዎ ፅሁፍ የነበረውን ሁኔታ ቢገልፁልን ኖሮ ደግሞ ተመራጭ ይሆን ነበር ። አዲስ አበባ ተወልደው ስላደጉም ይሆናል በወዳጅ በዘመድ አፅፈው በጎን ለማለፍ አለመፈለግዎ ፤ ትልቅ ነገር ነው ።(በጋዜጠኛው አቀራረብ ላይ ጥያቄ ቢኖረኝም)።
ያነጋገርዎ ጋዜጠኛ እንደነገረን የመጀመሪያ ዲግሪዎን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሁለተኛውን ደግሞ ከካምብሪጅ አግኝተዋል ። ከዚያም ለረጂም ዘመናት በገንዘብ ሚኒስቴር ሰርተዋል ። ከዚህ በመነሳት ትምህርትዎ የጋዜጠኝነት ወይም የስነ-ፅሁፍ እንዳልሆነና economics ሊሆን እንደሚችል ጠርጥሬአለሁ ። ተሳስቼ እንደሆን ለመታረም ዝግጁ ነኝ ። ከዚያም በመፅሃፍ ድርጅትና በኩራዝ አሳታሚ ሰርተዋል ።
ይህን ካልኩ በኋላ በቀጥታ ወደርስዎ ቃለ-ምልልስ ልምጣ ።
የደራሲ በዓሉ ግርማ ባለቤት፣ ወ/ሮ አልማዝ አበራ፣
‹‹…የካቲት 24 ቀን 1976 ዓ.ም. ቀን ላይ አስፋው ዳምጤ እቤት ስልክ ደወለ :: በዓሉ ቤት አልነበረምና፣ ስልኩን አንሥቼ ያነጋገርኩት እኔ ነበርኩ :: የእግዜር ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ፣ ‹… በዓሉ እንደመጣ እዚያ እቀጠሯችን ቦታ ባስቸኳይ እንድትመጣ ብሎሃል በዪልኝ …› ብሎ ስልኩን ዘጋ ::››
አቶ አስፋው ፡ የዚህ አጭር መልሱ “ሃሰት” ነው ። ብለዋል ።
አበራ ለማ ከበአሉ ባለቤት ከወይዘሮ አልማዝ አገኘሁት ብሎ ካቀረበው ፅሁፍ ላይ ለእርስዎ ቃለ መጠይቅ መንደርደሪያ ሃሳብ ሆኖ የቀረበው ከፊሉ ብቻ ነው ። የአበራ ለማ ሙሉውን ምእራፍ ስናነብ ነው ፈታ ያለ ግንዛቤ የሚኖረን ። እንዲህ ይነበባል ፤ እጠቅሳለሁ፦
“….የካቲት 24 ቀን 1976 ዓ.ም. ቀን ላይ አስፋው ዳምጤ እቤት ስልክ ደወለ፡፡ በዓሉ ቤት አልነበረምና ስልኩን አነስቼ ያነጋገርኩት እኔ ነበርኩ፡፡ የእግዜር ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ ’… በዓሉ እንደመጣ እዚያ እቀጠሯችን ቦታ ባስቸኳይ እንድትመጣ ብሎሃል በዪልኝ…’ ብሎ ስልኩን ዘጋ፡፡ በዓሉ ወደ አሥራ አንድ ሰዓት ገደማ ወደ ቤት ሲመጣ መልእክቱን ነገርኩት፡፡ ወዲያው ሻወር ወስዶ ወጣና ለመሄድ ሲጣደፍ፣ ’እደጅ ውለህ መምጣትህ ነውና እባክህ ትንሽ እህል ብጤ ቀምሰህ ውጣ’ ብለው፤ ’አልችልም… ብርቱ ቀጠሮ አለንና ወደዚያው መፍጥን አለብኝ’ ብሎኝ ፈጥኖ ከቤት ወጣ::” የጥቅሱ መጨረሻ ።
መርምሮ ለሚያነብ ሰው የነገሩ ጭብጥ ያለው ወ/ሮ አልማዝ ከጠየቁትና አበራ ለማ ካቀረበው ከላይኛው ጥቅስ ጋር የተያያዘ ነው ። ወ/ሮ አልማዝ በስልክ መልእክት ከአቶ አስፋው ተቀብዬ ለባለቤቴ ነገርኩትና በመልእክቱ መሰረት ወደ ጓደኛው ወደ አቶ አስፋው ሄደ ነው የሚሉት ።
አቶ አስፋው የሚሉት ደግሞ የለም ስልክ አልደወልኩም ፤ ቀጠሮም አላደረኩም ፤ ሆኖም ግን ያለቀጠሮ በዚያች የመጨረሻዋ ምሽት በአሉን አግኝቼዋለሁ ነው ። እዚህ ላይ አንድ መሰረታዊ ጥያቄ ይነሳል ። ይኸውም ወይዘሮ አልማዝ ከአቶ አስፋው ጋር ጠብም ወዳጅነትም ቅርርብም የላቸውም አቶ አስፋው ዳምጤ እንደነገሩን ። ይህ ከሆነ ደግሞ ለምን ወይዘሮ አልማዝ እስካሁን ድረስ የምታውቀው ነገር አለና ንገረኝ ብለው አቶ አስፋውን ያስጨንቃሉ ፤ ለምን ሌሎቹን የበአሉ ጓደኞች አንደ አቶ አስፋው ሁሉ ጠይቀው አያውቁም ? ሌላው ደግሞ በመጨረሻዋ በአሉ በተሰወረባት ምሽት ፤ በአሉ ወደቤቱ ስላልተመለሰ ለወይዘሮ አልማዝ ከአስፋው ጋር አመሸሁ ብሎ አልነገራቸው ፤ ከእርስዎ ጋር ማምሸቱንስ ወ/ሮ አልማዝ እንዴት አወቁና ነው ወደቤትዎ የደወሉት ፤ ቀድመው ወደቤት ደውለው በወይዘሮ አልማዝ በኩል ለበአሉ ቀጠሮ ካልሰጡ ? አቶ አስፋው ወ/ሮ አልማዝ ወደቤቴ አልደወለችም ብለው ቢያስተባብሉም ጠዋት ላይ ወደስራዎ ደውለው እንደተነጋገሩ ደግሞ አልካዱም ። ወይዘሮ አልማዝ ባለቤቴ በአሉ ግርማ ማታ አልገባምና የምታውቀውን ንገረኝ ብለው ሲጠዩቅዎ “ አይቼዋለሁ ግን” ብየ የምለው ጠፋኝና ፤ የምለው ጠፋኝና ነው ያሉት ! ለምን የሚሉት ጠፋዎት ? አሁን የሚነግሩንን መገናኛችሁ አጠገብ ቆመን አንድ አንድ ብለን ተለያየን ብለው ለምን አልነገሯቸውም ለወ/ሮ አልማዝ ። ይህን ብለዋቸው እስቲ ደግሞ ከሌሎች ሰዎች ላጣራ ብለው ቢሆን ኖሮ የተናገሩት እውነት ይመስል ነበር ። አንድ ሰው የሚለው የሚጠፋው አንድ የሚያውቀው ነገር ሲኖርና ለዚያ መልስ ሳይዘጋጅ ድንገት ጥያቄ ሲቀርብበት ነው ። ወዲያው የሚያስገድደው ሁኔታ እስካልተፈጠረ ድረስ የመዘጋጃ ጊዜ ለመግዛት ዘዴ ይቀይሳል ። አቶ አስፋው ለርስዎ ጊዜ መግዣ አድርገው የተጠቀሙበት “ አሁን አንድ ትልቅ ባለስልጣን ዘንድ ስለምሄድ እሱን ጠይቄ እነግርሻለሁ ብለው ዛሬ በህይወት የሌሉትን ሰው ለማ ጉተማን ምስክርነት መጥራት ነው ። እስቲ ቆም ብለው ያስቡት ለራስዎም አልገረመዎትም ?
ሌላው ወ/ አልማዝ የተናገሩትን ለማስተባበል ማስረጃ አድርገው የተጠቀሙበት የሬይደልፍ ኬ ሞልቬርን Reidulf K. Molvaerን ብላክ ላዮንስ Black Lions የተባለው መፅሃፍ ላይ ደራሲው በአሉ ግርማ በጠፋባት በዚያች ምሽት ያቀረበውን ትንተና ነው ። በአጭሩ መፅሃፉ ላይ እርስዎ በአሉን መጥተው ከቤቱ ወሰዱት አይነት አቀራረብ ስለሆነ አንዴ ስልክ ደውሎ ቀጠሮ ሰጠው ፤ ሌላ ጊዜ ደግሞ ከቤቱ መጥቶ ወሰደው ተብሏልና አንዱን ይምረጡ ነው አባባልዎ ። መፅሃፉ ላይ እኮ ወ/ሮ አልማዝ እንደነገሩኝ ብሎ አልፃፈም ሞልቬር ፤ ስለዚህ ሞልቬር ይህን ነጥብ ከየትም ሊያገኘው ይችላል ። ሞልቤር ስህተት ፈፅሞ ከሆነ እንኳን ወ/ሮ አልማዝን ምርጪ አትምረጪ ሊያሰኛቸው አይችልም ። መፅሃፉ ላይ ለወጣው ፅሁፍ ተጠያቂ መሆን ያለበት ሞልቬር ብቻ ነው ። ታዲያ እኮ ሞልቬር እዚያው ገፅ ላይና እዛው ፓራግራፍ ላይ የጠቀሳቸው ነጥቦች ነበሩ ፤ እርስዎ ሳያዩአቸው አልፈዋል ወይም ሆን ብለው ዘለዋቸዋል ። ሞልቬር እንዲህ ይላል እዚያ ላይ ፤ እርስዎ አቶ አስፋው በአሉ ከተሰወረባት ከመጨረሻዋ ቀን አስራ አምስት ቀን በፊት ነው በአሉን ያየሁት ብለው ለሌሎች ሰዎች ተናግረዋል ብሏል ። ይህም ወ/ሮ አልማዝ ከተናገሩትና ከሚሉት ጋር ባለመግጠሙ ሰዎች ደንቆቸዋል ሲል ፅፏል ፤ ይህን ነጥብ ይያዙ ። ቀጥሎም እንዲህ ይላል ሞልቬር (ስም ባይጠቅስም) ምንልባትም ይህ ጓደኛው ፤ ላደረገው አብዮታዊ አስተዋፅኦ መንግስታዊ ለሆነው ኩራዝ አሳታሚ ድርጅት በዚያኑ ሰሞን ስልጣን ተሰጠው ፤ ብሏል ። ሞልቬር ብላክ ላዮንስ በሚለው መጽሃፉ ላይ ያስቀመጠው እንዲህ ይነበባል ገፅ 348 ፦ To other people he ( the friend ) said that he had not seen Be’alu for two weeks before he disappeared, and they were surprised to hear another story from Be’alu’s wife . Soon after the friend got ( perhaps as areward for his contribution to the revolutinary cause ) a high position with Kurraz , the government publishers.
እዚህ ላይ አንድ ነገር ትዝ አለኝ ። አበራ ለማ የሰዎች ስም አጠፋ የርስዎን የአቶ አስፋው ዳምጤን ጨምሮ እየተባለ ሲጠቀስ በየመጣጥፉ ላይ አንብቤ ነበር ። የእርስዎም ብሶት አበራ ለማ ስሜን አጥፍቷል ነው ። ከዛሬ 17 አመታት በፊት በ1997 እ.አ.ኤ ሞልቬር ይህንኑ ፅፎት የለም እንዴ ያውም ዘላለማዊ ሆኖ በሚቀር መፅሃፍ ላይ ! ምነው አበራ ለማ እንዚህን መረጃዎች ሰብስቦ ሲፅፍ ድንቅ ሆነ ?
አቶ አስፋው ሌላው ያሳዘነኝን ሳልገልፅልዎ ማለፍ አልፈልግም ። ጋዜጠኛው ከአበራ ለማ ጋር ቅራኔ ነበራችሁ ? ብሎ ይጠይቅዎታል ። መሆን የነበረበት ከቮልቴር ጋር ቅራኔ ነበራችሁ ? ነው ። እርስዎም ሲመልሱ “ እኔ ከእርሱ ጋር ቅራኔ ውስጥ ገብቻለሁ ብየ አስቤ አላውቅም ብለው ነበር ። ይህ የጨዋ መልስ በቂ ነበር ። በተረፈ ከዚያ አልፎ ከዛሬ 37 አመታት በፊት የተደረገን ስነፅሁፋዊ ክርክር ቂም በቀል አድርጎ ለማቅረብ መሞከርና በዚያ አስታኮ ስሙ ያልተጠቀሰ አስተማሪው እንዲህ ብሎ አለው ብሎ በማለት ሰውን በሾርኒ ለመስደብ መሞከር ትንሽነትን የሚያስይ ሆኖ አግኝቼዋለሁ ። በስነፅሁፍ ቅስሙ ቢሰበር ኖሮማ አበራ ለማ አሁን ይህን የመሰለ ኢንቬስቲጌቲቭ ስራ ባላቀረበልን ነበር ። በነገራችን ላይ አበራ ለማን ከፅሁፉ በስተቀር ጥቁር ይሁን ቀይ ሰልካካ ይሁን ኩርፋድ አላቀውም ። አስተያየቴ በሙሉ በአሉ ግርማን አስመልክቶ ከፃፈው ጋር የየያያዘ ነው ። በርግጥ ሌሎች የግጥም ስራዎቹንም አውቃለሁ ቅስሙ አልተሰበረም ህያው ነው ለማለት ነው ። እውነቱን ለመናገር እርስዎን ቃለ-መጠይቅ ካደረገልዎ ጋዜጠኛ ነው የድርሰት ስራዎች እንዳሉዎትም የሰማሁት ። ልጅ ሆኜ የአንደኛ ደረጃ ተማሪ እያለሁ ነው መፅሕፍትን የማንበብ ልምድ የተጥናወተኝ ። ካነበብኳቸው ውስጥ አንዱ ርዕሱ “ከልታማዋ እህቴ” ይላል አሁን የዚህን መፅሃፍ ደራሲ ማን እንደ ደራሲ ቆጥሮ ያስታውሰዋል !
ወደ ወ/ሮ አልማዝ አበራ ልመለስ ። እኔ እንደገባኝ ከሆነ የወ/ሮ አልማዝ ጥያቄ አቶ አስፋው ባለቤቴን በአሉን ገድለዋል ፤ ወይም በግድያው ላይ እጃቸው አለበት አይደለም ። በኦሮማይ ምክንያት ህይወቱ እንዳለፈም ያውቃሉ ። የሳቸው ጥያቄ ግን አንድና አንድ ብቻ ነው ። የሟች ባለቤቴን የሞት መንገድ ፍለጋ ላይ ነኝ መዳረሻውን ላለፉት 30 አመታት እየፈለኩ ነው ። የዚያች መንገድ መግቢያ ቁልፍ አቶ አስፋው እርስዎ እጅ ላይ ይገኛልና ለፍትህ ብሎም ለህሊናዎ ሲሉ ይጠቁሙኝ ነው ። አቶ አስፋው ወ/ ሮ አልማዝ ልብ ውስጥ እንደማንኛውም ሰው ሊመላለስ የሚችለውን ስሜት ሊረዱት ይገባል ። የውድ ባለቤታቸውን ደብዛ እየፈለጉ ያሉ ናቸውና ። ቀያፋ ላዘዛቸው ሮማውያን ወታደሮች ጲላጦስ እየሱስን በግላጭ ጉንጩን ስሞ አሳልፎ ሰጥቶታል ብለው ቢያስቡስ ወ/ሮ አልማዝ ላይ ይፈረዳል ?
አቶ አስፋው ሌላው ያሳዘነኝን ሳልገልፅልዎ ማለፍ አልፈልግም ። ወ/ሮ አልማዝ ላይ ለምን ጠየቀችኝ ከሚል ቅሬታ ተሰምቶዎታል ስለዚህም አቂመውባቸዋል ። ወ/ሮ አልማዝ ጋር በስራ ምክንያት የሚያገናኛችሁና በዚህ ተቀይማኛለች በማለት ሊያቀርቡት የሚችሉት ምክንያት ሊኖር አልቻለም ። እና የሞተውን ባላቸውን በአሉን ሌላ ውሽማ ነበረችው በማለት የሴትነት ብቃታቸውን ለማዋርድ ሞከሩ ። ባልሻረ ቁስላቸው ላይ ጨው ነሰነሱበት ። ምን አይነት ጭካኔ ነው ! አዝናለሁ እንዲህ በማለቴ ፤ እንዲያውም ወራዳነት ነው ። የገባበትና አፅሙ እንኳ የት እንደወደቀ ያልታወቀ ሙት ወዳጁን አጽም ፤ ሰው እንዴት ይግጣል ። ቤተሰቡን ለማስቀየምስ ለምን ይቸኩላል ። ከራስዎ ጥያቄና መልስ ልነሳና ይህን ራስዎ የፈጠሩት መሆኑን ደግሞ ላስረዳዎ አቶ አስፋው ።
ጠያቂው ጋዜጠኛ ቀድሞ የተዘጋጀበት በሚመስል መልኩ ከመሬት ተነስቶ አንድ ጥያቄ ያቀርብልዎታል ። በአሉ እርስዎጋ ከመድረሱ በፊት ይት ቆየ ብለው ነው የገመቱት ? ይልዎታል ። ከዚያ አስቀድመው እርስዎ ካላዘጋጁት በቀር የበአሉን መቆያ ቦታ ሐሳብ ከዬተ አመጣው ? የቃለ- መጠይቁን ቁራሽ እነሆ
ፍቱን ፦ በአሉ እርሶ ጋ ከመድረሱ በፊት የት ቆየ ብለው ነበር የገመቱት ?
አቶ አስፋው፦ጥቂት ቀደምብሎ እዚያው አካባቢ ወዳጅ እንደነበረው ተገንዝቤ ነበር ።
ፍቱን፦ የማን ቤት ነው?
አቶ አስፋው ፦ እሱን አልውቅም ።
ፍቱን፦ወንድ ሴት?
አቶ አስፋው ሴት ።
ፍቱን፦ በዚያች እለት ምሽት እዚያ ቆይቶ ከተመለሰ በኋላ ነበር ከእርሶ ጋር የተገናኛችሁት ?
አቶ አስፋው፦ እንደዚያ ነበር አመጣጡን ሳይ የገመትኩት ።
ወዳጅ እንደነበረው ተገንዝቤ ነበር ። ተገንዝቤ ነበር የሚለውን ቃል መጠቀም የሚቻለው ለትምርት ለእውቀት ሲሆን ነው ። ውሽማ ነበረችው ለማለት ግንዛቤ አያሻውም አውቅ ነበር ነው የሚባለው ፤ ፈጠራዎን ግዝፈት ለመስጠት ግዙፍ ቃል ተጠቀሙ ። ይህ የሚያሳየው ደግሞ ራስዎም የተናገሩትን እንዳላመኑበት ነው ። እዚያው ላይ ዝቅ እንበልና የማን ቤት ነው ? ሲል ይጠይቃል ጋዜጠኛው ። አቶ አስፋው እሱን አላውቅም ሲሉ ይመልሳሉ ። ወንድ ሴት ይልዎታል ጋዜጠኛው ። የእርስዎ መልስ ደግሞ ሴት ይላል ። የማን ቤት መሆኑን ከላይ ሲጠቅሱ አልውቅም ካሉ በኋላ ፤እንዴት የሴት ቤት መሆኑን አወቁ ? እርስዎ ጋር ከመገናኘቱ በፊት ደግሞ ውሽማውጋ ቆይቶ ነው የመጣው ? ሲልዎ ጋዜጠኛው ፣ እንደዚያ ነበር አመጣጡን ሳይ የገመትኩት ይላሉ እርስዎ ። ለካ ግምት ነው የተረጋገጠ ማስረጃ የለዎትም ! ታዲያ በስድስት አረፍተ ነገሮች ወስጥ ሶስት የተለያዩ የተምታቱ ነገሮችን ማቅረብ ወ/ሮ አልማዝን ለመስደብ የተፈጠረ ቅጥፈት መሆኑን አያሳይም ?
አንዳንድ ነጥቦችን ላንሳ ፤
1)በአሉ ግርማ ከወደአንዲት ሴት ቤት መምጣቱን ገመትኩ አሉ፡
2) ኮማንደር ለማ ጉተማን ምስክርነት ጠሩ ፤በህይወት የሌለ ሰው ፡
3)ስሙን ያልጠቀሱትን የአበራ ለማን መምህር ፤ እንዲህ ብሎ አለው አሉ ፡
4)ወ/ሮ አልማዝ መስሪያ ቤትዎ ደውለው ሲያነጋግሩዎ የሚሉት ጠፋብዎ ፡
5)አበራ ለማ በግጥሙ ምክንያት አደረገ ላሉት ክርክር ምስክር አድርገው አሁንም ያቀረቡት በህይወት የሌለውን ስብሃት ገ/እግዚአብሄርን ነው ።
ከተደረገልዎ ቃለ-መጠይቅ ላይ ከሰጧቸው መልሶች የቱን ተቀብለን የቱን እንተው ፤ የትኛው እውነት የትኛው ሃሰት እንደሆነስ በምን እናረጋግጥ ?
እስቲ እኔም እንደርስዎ ልገምት speculate ላድርግ በአሉ ግርማ ከሌላ ሴት ቤት መጣ ብየ ገመትኩ እንዳሉት ማለት ነው ። ከዚያ በፊት በደህናው ጊዜ በአሉ ከደሞዙ ሌላ በድርሰት ስራዎቹ የሚያገኘው ጠቀም ያለ ገንዘብ ነበረው ። እርስዎም ተቸግረው ከበአሉ ገንዘብ ተበድረው ነበር ። ያን ገንዘብ ሊከፍሉት አልቻሉም ወይም አልፈለጉም ። በመጨረሻዋ እለት ላለፉት 6 ወራት ስራ ስላልነበረው የተበደረውን ገንዘብ ሊከፍለኝ ነው ብሎ ይሆን እንዴ ለወይዘሮ አልማዝ በሰጧቸው ቀጠሮ አማካይነት ከቀጠሮው ስፍራ የደረሰው ። በቃለ- መጠይቅዎም ላይ እኔና እሱን ብቻ የምትመለከት የግል ጉዳይ ነበረችን ብለዋል ከገንዘብ ብድር ጋር የተያያዘች ትሆን ? በአሉን ሰዋራ ስፍራ ድረስ በመውሰድ ለደርግ ሰዎች ማስረከብ እርስዎን ከገንዘብ እዳ ነጻ ሲያደርግዎ ፤ ደርግ ተረጋጋሁ ባለበት በዚያ ዘመን በኦሮማይ እርቃኑን ያስቀረውን የቀድሞ ከፍተኛ ባለስልጣኑን በአሉን ያለግርግር እርስዎ ከወሰዱበት ስፍራ በቀላሉ ማፈን ችሏል ማለት ይሆን ?
አቶ አስፋው ፤ አንድ ነገር እንዲያስቡ እፈልጋለሁ ። ላለፉት 30 አመታት የውድ ባለቤቴን መውደቂያ እፈልጋለሁ ብላ ያለድካም የምትተጋ አንድ ወይዘሮ በቤቷ ውስጥ ምን ያህል ፍቅር እንዳለ ማሳያ ናት ። ለባለቤቷም ሆነ ለራሷ የፍቅር ተምሳሌት ናት ። እንዲህ አይነት ሴት ደግሞ ለማይነጥፍ የቤት ውስጥ ፍቅር ምንጭ ናት ። እንደማናቸውም ድንቅ ደራስያን ሁሉ በአሉ ግርማም ከቤቱ ያገኘው የነበረው ፍቅር ለድርሰት ስራዎቹ ሁሉ ፅኑ መሰረት ሆኖት ለኛም ለአንባቢዎቹና ለአድናቂዎቹ የድርሰቶቹ ትሩፋት ደርሰውናል ።
ለዛሬው በዚሁ ላብቃ ።

ከአንበሳው ይብራ !

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የኢትዮጵያ መንግሥት በመላይቱ ሀገር ከ350 ሺህ ለሚበልጡ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች 15 ቀን የዘለቀ ስልጠና ሰጥቶዋል።በዕረፍት ላይ ያሉት ተማሪዎች ስልጠናውን በሚገኙበት አካባቢ ባሉ የትምህርት ተቋማት ውስጥ እንዲከታተሉ መደረጉም ተሰምቶዋል። የስልጠናውን ይዘት እና ዓላማ የመወያያ ርዕስ አድርገነዋል።

ዩኤስ አሜሪካ ኢራቅ ሃዲታህ የተሰኘ ግድብ አካባቢ ራሱን እስላማዊ መንግሥት «IS» ብሎ በሚጠራዉ ቡድን ላይ የአየር ድብደባ ማካሄድዋን ገለፀች።በሌላ በኩል ሊባኖስ ዉስጥ IS በመባል የሚታወቀዉ አክራሪዉ እስላማዊ ቡድን አፍኖ የወሰደዉን ሊባኖሳዊ ወታደር አንገት መቀላቱን የሚያሳይ ቪዲዮ መሰራጨቱ ተዘገበ።

ዩኤስ አሜሪካ ኢራቅ ሃዲታህ የተሰኘ ግድብ አካባቢ ራሱን እስላማዊ መንግሥት «IS» ብሎ በሚጠራዉ ቡድን ላይ የአየር ድብደባ ማካሄድዋን ገለፀች።በሌላ በኩል ሊባኖስ ዉስጥ IS በመባል የሚታወቀዉ አክራሪዉ እስላማዊ ቡድን አፍኖ የወሰደዉን ሊባኖሳዊ ወታደር አንገት መቀላቱን የሚያሳይ ቪዲዮ መሰራጨቱ ተዘገበ።

በሰሜን አሜሪካው የኢትዮጵያዊያን ስፖርትና ባህል ፈዴሬሽን የቦርድ አባላት መካከል አለ የተባለውን አለመግባባት መነሻ በማድረግ ለመፍትሔ ፍለጋ ይረዳ ዘንድ በአሜሪካ ድምፅ የአማርኛው አገልግሎት፣ የራድዮ መፅሔት ዝግጅት፣ ቀጣዩን ተከታታይ ውይይት አዘጋጅቷል።

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በአፍሪቃ ሀገራት የመሠረት ልማት ፕሮዤ ለማነቃቃት በሚታሰብበት ጊዜ ሁሉም የሚያስበው ስለ ቻይና ነው። ቻይና እአአ በ1960 ኛዎቹ ዓመታት በሶሻሊስታዊው ፕሮዤ አማካኝነት ከዛምቢያ እስከ ታንዛንያ የሚዘልቅ የባቡር ሀዲድ ግንባታን በገንዘቧ መርዳቷ ይታወሳል።

ዘላለማችንን የፖለቲካ የበታችነት የተጠናወተን ጥገኞች ሆነናል:: በባህር ዳር ካለፈው ሳምንት ጀምሮ እየተካሄደ ያለው የብአዴን ካድሬዎች እና የለውጥ ሃዋርያ ብሎ ራሱን የሚጠራው የወጣት አባላት ቡድን በድርጅቱ ውስጥ ያገረሸውን የለውጥ ጥያቄ ተከትሎ በብኣዴን ውስጥ እየተነሳ ስላለው የፖለቲካ መብት ጥያቄ በሰፊው ውይይት የተደረገበት ሲሆን ብአዴን የኢሕኣዴግን መርሆ እንደጠበቀ ከሌሎች ድርጅቶች የበላይነት እና ጥገኝነት መላቀቅ አለበት በሚሉ እና ወደ […]

ብሔራዊ እርቅ (National Reconciliation) በተለይ በእርስ በእርስ ግጭት ደም የተቃባንና የከፋ አደጋ የተጋረጠበትን ኅብረተሰብ ወይም የመበታተን አደጋ የተጋረጠባትን ሀገር በይቅር ለእግዚአብሔር ይቅር አባብሎ ሰላም ለማውረድና የቂም በቀልን ዶሴ ዘግቶ በአዲስ መንፈስ ብሔራዊ መግባባትን (National Consensus) ፈጥሮ የአንዲት ሀገርን ሕዝብ በአንድነት አስተባብሮ ለማንቀሳቀስና ህልውናውን ከመረጋጋቱ ጋራ ለማስቀጠል ዓይነተኛ መንገድ ነው፡፡ በሕወሀት ኢሕአዴግ የአገዛዝ ዘመን የዚህ የብሔራዊ […]

ከክፍል አንድ የቀጠለ እሁድ (ሐምሌ 1 ቀን 2004 ዓ.ም) በአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ጽ/ቤት ውስጥ የ“አዲሱ ትውልድ ተልዕኮ” በሚል ርዕስ ወጣት ሀብታሙ አያሌውን ገብዘዉት ነበር፡፡ ሀብታሙን በአካል ያየሁት ያኔ ነበር፡፡ ከሀብታሙ ጋር በደንብ የተዋወቅነው ከዚህ ዘገባ በኀላ ነበር፡፡ ሀብታሙን ስሞኑን ሳስታውስው፣ ያኔ በስንደቅ ጋዜጣ ላይ የዘገብኩትን መለስ ብየ አየሁ። እስቲ በጋራ እናነብው ፡፡ ክፍል […]

እሁድ (ሐምሌ 1 ቀን 2004 ዓ.ም) በአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ጽ/ቤት ውስጥ የ“አዲሱ ትውልድ ተልዕኮ” በሚል ርዕስ ወጣት ሀብታሙ አያሌውን ገብዘዉት ነበር፡፡ ሀብታሙን በአካል ያየሁት ያኔ ነበር፡፡ ከሀብታሙ ጋር በደንብ የተዋወቅነው ከዚህ ዘገባ በኀላ ነበር፡፡ ሀብታሙን ስሞኑን ሳስታውስው፣ ያኔ በስንደቅ ጋዜጣ ላይ የዘገብኩትን መለስ ብየ አየሁ። እስቲ በጋራ እናነብው ፡፡ ክፍል 1 – የዛሬው […]

‹‹ከታሰርኩ ጀምሮ ከጠበቃዬ ጋር የተገናኘሁት አንድ ቀን ብቻ ነው›› አብርሃ ደስታ ‹‹ሕገ-ወጥ ሕጎች እየበዙ ነው፣ ማብቃት አለባቸው!›› ‹‹አንዱ በሀገርህ ላይ የመኖርህ መገለጫ ሳትሰጋህ መኖር ነው፤ ሌላ ሀገር ያለ ይመስል አልሰጋም›› ጠበቃ ተማም አባቡልጉ *****አብርሃ ደስታን በተመለከተ፣ ከጠበቃ ተማም አባቡልጉ ጋር ያደረኩት ቃለ-ምልልስ**** በዛሬው ዕለት አብርሃ ደስታ ጊዮርጊስ በሚገኘው የአራዳ ፍርድ ቤት ቀርቦ የ28 ቀናት የጊዜ […]

እንደሰማሁት ከሆነ ጥቁር ሳምንት በሚል የተጀመረው ዘመቻ ጥሩ ዘመቻ ነው፡፡ በማህራዊ ሚዲያው ሲንቀሳቀሱ የነበሩትም ሆነ ጋዜጠኞች በመታሰራቸው እንቅስቃሴው አለመዳከሙ ያስደስታል፡፡ መጭው ዘመን የነጻነት ይሆን ዘንድ ኢትዮጵያውያን ይህን የመሰሉ እንቅስቃሴዎችን መደገፍ፣ ማበረታታትና መቀላቀል አለባቸው፡፡ በተለይ በአሁኑ ዘመን ማህበራዊ ሚዲያው ትልቅ ለውጥ እያመጣ ነው፡፡ በግብጽና ቱኒዚያ ማህበራዊ ሚዲያው ቀላል የማይባል ለውጥ አምጥቷል፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

ጋዜጠኛ አንተነህ መርዕድ

ህወሃት በሻዕብያ ታዝሎ* ምኒልክ ቤተመንግስት ከገባና ኦነግንም ሆነ ሌሎቹን ጠፍጥፎ የሰራቸውን መናኛ ድርጅቶች እንኳ ሳያስቀርብ በብቻው የተያያዘው ዘረፋ፣ ሁሉን ለእኔ ብቻ ያለ ሂደቱ ያላስደነገጠው ኢትዮጵያዊ አልነበረም። ያለፉትን ስርዓቶች የተሻገሩ ሁለት አንጋፋ ጓደኛም ጋዜጠኞች ሲጨዋወቱ በቦታው ነበርሁ። አንደኛው ወያኔ ነፃ አወጣዋለሁ ከሚለው ከኩሩው ኢትዮጵያዊ ከትግራይ ህዝብ አብራክ የተገኘ ነበርና “ወንድሜ ይሉኝታ በትግርኛ ምንድን ነው የሚባለው?” ሲል ጠየቀው። “ይሉኝታ..ይሉኝታ…” እያለ ቃሉን ማፈላለግ ሲጀምርና ፈጥኖም ቃሉን ማግኘት ሲሳነው “ተወው ወንድሜ የሌለውን ነው የጠየቅሁህ ቃሉ ከሌለ ወያኔዎች ከየት ይማሩታል ብዬ ልጠብቅ” በማለት ሁላችንንም አሳቀን።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ

‹‹እኛታስረንም፣በኢትዮጵያጋዜጠኝነትእናጋዜጠኞችላይየሆነውነገርእጅግቅስምይሰብራል ( It’s really heart breaking!)››
ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ
‹‹እስርደግምነገርነው›› ጋዜጠኛ አስማማው ኃ/ጊዮርጊስ
‹‹የነጻነትትግልላይእንዳለሁያወኩትእስርቤትነው›› ጦማሪ ናትናኤል ፈለቀ
‹‹መጽሔቶችመታተምመቆማቸውያሳዝናል፡፡አማራጩምንይሆን?››
አህመዲን ጀበል (የሙስሊሞች ጉዳይ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባል) 

ከትናንት በስትያ፣ ሰኞ ነሐሴ 26 ቀን 2006 ዓ.ም በጣም የናፈቁኝን ታሳሪ ጋዜጠኞች እና ጦማሪያን ለመጠየቅ በማቀድ፣ ረፋድ ላይ ወደቂሊንጦ እስር ቤት አመራሁ። በቃሊቲ ወህኒ ቤት ዋና በር ጋር በታክሲ ሳልፍ፣ ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ እና ኤዶምን ካሳዬ፣ ጦማሪ ማህሌት ፋንታሁንን፣ አቶ አንዷለም አራጌን፣ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋንና ሌሎች የማውቃቸውን እስረኞች በሀሳቤ መጥተው ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ነሃሴ ፴(ሠላሳ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከመላው አውሮፓ የተሰባሰቡ ኢትዮጵያውያን የተገኙበት ይህ የተቃውሞ ሰልፍ እጅግ ደማቅ መሆኑን ወንድማገኝ ጋሹ በስልክ ገልጿል። የግንቦት7 ዋና ጸሃፊ  በየመን የጸጥታ ሃይሎች ተይዘው  ተላልፈው ከተሰጡበት ጊዜ ጀምሮ የኢትዮጵያ መንግስት ሰብአዊ መብታቸውን በመግፈፍ በኢትዮጵያውያን እንዳይጎበኙ ከልክሏል። አብዛኛውን ስራቸውን እንዳጠናቀቁ በተደጋጋሚ ሲናገሩ የነበሩት አቶ አንዳርጋቸው ወደተለያዩ ቦታዎች በሌሊት እየተዘዋወሩ ምርምራ እየተደረገባቸው መሆኑን …

ነሃሴ ፴(ሠላሳ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ በተለያዩ ሊጎች ወይም ፎረሞች ለሰበሰባቸው የአዲስ አበባ ነዋሪዎች የሚሰጠው የፖለቲካ ስልጠና ባልጠበቀው አቅጣጫ እየሄደበት መሆኑን ተከትሎ ሰዎችን ከመከፋፈል ጀምሮ እስከ ማባረር መድረሱን ምንጮች ገልጹ። በተለያዩ ክፍለ ከተሞች በሚገኙ የመሰብሰቢያ ቦታዎች በሚደረጉት ስልጠናዎች ላይ ለገዢው ፓርቲ ፈታኝ የሆኑ ጥያቄዎችን የሚያቀርቡ ወጣቶች እና የፖለቲካ ንቃት አላቸው የሚባሉ ነዋሪዎች ፣ ከቀሪ …

ነሃሴ ፴(ሠላሳ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ለገጣፎ ውስጥ በሶስት ጎጦች የሚኖሩ ዜጎች በ10 ቀን ውስጥ ቤታቸውን እንዲያፈርሱ መታዘዛቸውን ጋዜጣው የትእዛዝ ወረቀቱን በማያያዝ ያሰፈረው ዜና ያማለክታል፡፡ጎራጎጭ፣ዳሌናድሬበተባሉትሶስትጎጦችእስከ 23 ሺህህዝብእንደሚኖርባቸው ነዋሪዎቹ ለጋዜጣው ዘጋቢ ተናግረዋል። “የሰንዳፋወረዳሰራተኛናማህበራዊጉዳይጽ/ቤት ማህተም አስቀርጾ የመረዳጃ እድር ማቋቋሙን፣ ለመብራትኃይልአንድሚሊዮንያህልገንዘብከፍለውትራንስፎርመርለማስተከልእየተጠባበቁመሆናቸውንና፣የውሃናሌሎችተቋማት ህጋዊለሆነአካልየሚሰጡትንአገልግሎትከፍለውእያገኙእንደቆዩበመግለጽየሚኖሩበትአካባቢህገወጥአለመሆኑንበመግለጽ እየተከራከሩ ቆይተዋል። እንደጋዜጣው ዘገባ  ነሃሴ 26 ተጻፈየተባለናከፊንፊኔልዩዙሪያ  በረህወረዳ   የመሬትአስተዳደርጽ/ቤትእንደሆነ የሚገልጽፊርማየሌለውደብዳቤ  ማምነታቸው በውል ያልተለየ ሰዎች ነሃሴ 30 …

የኤቦላ ተሕዋሲ ሥርጭትን ለመግታትም ሆነ ለበሽታ የተጋለጡ ሠዎችን ለመርዳት መንግሥታት ተገቢዉን ጥረት አለማድረጋቸዉን ግብረ-ሠናይ ድርጅቶች አጋለጡ።ድንበር የለሽ ሐኪሞች፤ የአለም ጤና ድርጅትና ሌሎች ድርጅቶች በየፊናቸዉ እንዳሉት የኤቦላን «አደጋ» ለማስወገድ ከተገባዉ ቃል አብዛኛዉ ገቢር አልሆነም።

በልጅነት ወቅት ሳድግ ሀኪም፣ የአይሮፕላን አብራሪ፣ ጠበቃ፣ ሌላም ሌላም እሆናለሁ እያሉ የተለያዩ የሙያ መስኮችን መጥራት የተለመደ ነው። ታድያ የወጣትነት ጊዜ ሲደርስ ለዚህ መሰረት የሆነውን የትምህርት ዘርፍ ለመከታተል ወይም ጨርሶ በሌላ መስክ ለመሰማራት እንወስናለን።

የናኘዉን ፅንፈኛ ቡድንን የእሥልምና ሐይማኖት መሪዎች ሲቃወሙ፤ እርምጃዎቹን ሲያወግዙ የብሪታኒያ ሙስሊም መሪዎች የመጀመሪያዎቹ አይደሉም።የግብፁ ዓል-አዝሐር ዩኒቨኒርስቲ መሪዎች ISISን አዉግዘዉ ነበር።ከግብፆች በፊት የሳዑዲ አረቢያ የሐያማኖት አባቶችም ቡድኑን አዉግዘዉት ነበር።

ኢትዮጵያና ጀርመን የሁለትዮሽ ትብብር ዉል ተፈራረሙ። ትናንት የገንዘብ እና የኤኮኖሚ ልማት ሚኒስትር ዴታ አቶ አህመድ ሽዴ እና የፌደራል ሪፑብሊክ ጀርመን የኤኮኖሚና ልማት ምክትል ሚኒስትር ቶማስ ዚልበርሆርን ለሁለቱ ሃገራት የተፈራረሙት የትብብር ዉል ከጎርጎሪዮሳዊዉ 2015 እስከ 2018ዓ,ም የሚዘልቅ ነዉ።

ኢትዮጵያዊዉ የአፈር ሳይንስ ባለሙያና ተመራማሪ ፕሮፌሰር ተካልኝ ማሞ የኖርዌይን ዓለም ዓቀፍ ሽልማት ተቀበሉ። ሽልማት ሰጪዉ ተቋም በድረገፁ ላይ ባሰፈረዉ መረጃ መሠረት ተሸላሚዉ ፕሮፌሰር ተካልኝ የተማሩትን ትምህርት ከአካዳሚ ሚናዉ ባለፈ ለኅብረተሰብ ትልቅ ጥቅም ለሚያስገኝ ዉጤት ማዋሉ ተሳክቶላቸዋል።

ካለፈው ሰኞ አንስቶ በአልጀሪያ መዲና በአልጀርስ፤ በማሊ መንግሥትና በሰሜናዊው የአገሪቱ ክፍል በሚንቀሳቀሰው የቱዓሬጎች አማጺ ኃይል ለውዝግቡ መላ ለመሻት ሲካሄድ የሰነበተው ድርድር ሳንክ አጋጥሞታል። ድርድሩ 8 ሳምንታት እንደሚወስድ አስቀድሞ

አገር ውስጥ በሰላም የሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች አመራር አባላት ናቸው። አብርሃ ደስታ ከአረና፣ ዳንኤል ሺበሺና ሃብታሙ አያሌው ከአንድነት፣ የሺዋስ አሰፋ ከሰማያዊ። ሐምሌ 1 ቀን 2006 ሽብርተኞች ናችሁ ተብለው ተያዙ። ጠበቃዎቻቸው በሌሉበት በድብቅ ፍርድ ቤት ቀረቡ ተባለ። ፖሊስ ዜጎችን ከመያዙ በፊት በእጁ መረጃ ሊኖረው ሲገባ፣ መረጃ ለማሰባሰብ ጊዜ ያስፈልገኛል ብሎ ለ28 ቀናት ቀጠሮ ይጠይቃል። ፍርድ ቤቱ፣ ያለምንም ማቅማማት፣ […]

የመግቢያ ማስታወሻ

በጽሑፉ ውስጥ በግእዝ ቁጥሮች በቅንፍ ውስጥ የተጻፉት ሐሳቡን እንዲወክሉ ብቻ ነው፡፡ በኋላ (ቁጥር ፭ ተመልከት ቢል ያንን ሐሳብ መልሶ ለማየት እንዲረዳ ነው፡፡

የኢትዮጵያን የዘመን አቆጣጠር ለየት ከሚያደርጉት ነገሮች አንዱ ጳጉሜ የምትባል አሥራ ሦስተኛ ወር ስላለችን ነው፡፡ የቤት ኪራይና የወር ደመወዝ የማንከፍልባትና የማንቀበልባት፤ መብራትና ውኃ ግን ከነሐሴ ወር ጋር ጨምረው የሚያስከፍሉባት፤ ሲሻት አምስት፣ ሲያስፈልጋት ስድስት፣ ስትፈልግ ደግሞ ሰባት የምትሆን ወር ናት፡፡ እንዲያውም ከአሥራ ሁለቱ የኢትዮጵያ ወሮች ጳጉሜ በብዙ መንገድ የተለየች ናት፡፡

በአንድ በኩል በጣም ትንሿ ወር ናት፡፡ ሲቀጥልም ወርኃዊ በዓላት የማይውሉባት ወር ናት፡፡ እንዲያም ሲል ደግሞ ከሌሎች ወሮች በተለየ የቀኖቿ መጠን የሚቀያየሩ ብቸኛ ወር ናት፡፡ ከሌሎች የኢትዮጵያ ወሮች በተለየም ስሟ ኢትዮጵያዊ ያልሆነ ወር ናት፡፡ በሁለት ዘመናት መካከልም እንደ መሸጋገሪያ የምትታይ ወርም ናት፡፡  

ጳጉሜ ማለት በግሪክ ‹ጭማሪ› ማለት ሲሆን ዓመቱን በሠላሳ ቀናት ስንከፍለው የሚተርፉትን ዕለታት ሰብስበው የሰየሟት ተጨማሪ ወር ናት፡፡ ወይም በየዕለቱ በፀሐይና በጨረቃ አቆጣጠር መካከል የሚፈጠረውን ልዩነት ሰብስበው ያከማቹባት ወር ትባላለች፡፡ ዓመቱ በዐውደ ፀሐይ ሲለካ 365 ቀናት ከ15 ኬክሮስ 6 ካልዒት ሲሆን በጨረቃ ሲለካ ደግሞ 354 ቀናት ከ22 ኬክሮስ፣ 1 ካልዒት፣ 36 ሣልሲት፣ 52 ራብዒት፣ 48 ኀምሲት ነው፡፡ (60 ኬክሮስ አንድ ቀን ነው)በሁለቱ መካከል(በፀሐይና በጨረቃ) በዓመት ውስጥ ያለው ልዩነት 11 ቀናት ከ7 ኬክሮስ ይሆናል፡፡ [በነገራችን ላይ በዘመን አቆጣጠራችን ውስጥ ከዕለት በታች የምንቆጥርባቸው ስድስት መለኪያዎች አሉ፡፡ ኬክሮስ፣ ካልዒት፣ ሣልሲት፣ ራብዒት፣ ኀምሲትና ሳድሲት፡፡ 60 ሳድሲት አንድ ኀምሲት፣ 60 ኀምሲት አንድ ራብዒት፣ 60 ራብዒት አንድ ሣልሲት፣ 60 ሳልሲት አንድ ካልዒት፣ 60 ካልዒት ደግሞ 1 ኬክሮስ ይሆናል፡፡ 60 ኬክሮስ ደግሞ 1 ዕለት፡፡ 1 ኬክሮስ 24 ደቂቃ ነው]

ጳጉሜን ለማግኘት የሚጠቅመን የየዕለቱን ልዩነታቸውን መመልከቱ ነው፡፡ በየዕለቱ በጨረቃና በፀሐይ መካከል 1 ኬክሮስ 52 ካልዒት(60 ካልዒት አንድ ኬክሮስ ነው)፣ ከ 31 ሣልሲት(60 ሣልሲት አንድ ካልዒት ነው) ይሆናል፡፡[ይህም ማለት 5 ሰዓት ከ48 ደቂቃ ከ46 ካልዒት(ሴኮንድ?)] ይህ ልዩነት በአንድ ወር ምን እንደሚደርስ ለማወቅ በ30 እናባዛው፡፡ 30 ኬክሮስ፣ 1560 ካልዒት፣ ከ930 ሣልሲት ይሆናል፡፡ የዓመቱን ለማግኘት ደግሞ በ12 እናባዛው፡፡ 360 ኬክሮስ(፩)፣ 18720 ካልዒት(፪)፣ 11160 ሣልሲት(፫) ይመጣል፡፡

ቀደም ብለን 60 ኬክሮስ አንድ ዕለት ይሆናል ባልነው መሠረት 360 ኬክሮስ ለ60 ሲካፈል 6 ዕለታትን ይሰጠናል(፩)፡፡ 18720 ካልዒትን(፪) በስድሳ በማካፈል 312 ኬክሮስን እናገኛለን፡፡ ያም ማለት ትርፉን 12 ኬክሮስ ትተን 300ውን ኬክሮስ ለ60 በማካፈል 5 ዕለት እናገኛለን፡፡ ይኼም ማለት 5 ዕለት ከ12 ኬክሮስ(፬) ይሆናል፡፡ 11160 ሣልሲትን(፫)ለ60 ብናካፍለው 186 ካልዒት ወይም ደግሞ 3 ኬክሮስና 6 ካልዒት(፭) ይሆናል ማለት ነው፡፡

ከላይ ኬክሮስን በዓመቱ ቀናት አባዝተን ያገኘነው(፩) 6 ዕለት አለ፡፡ ይኼ ዕለት ሕጸጽ ይባላል፡፡ ፀሐይና ጨረቃን እኩል መስከረም አንድ ላይ ዓመቱን ብናስጀምራቸው ፀሐይ የወሯ መጠን ምንጊዜም ሠላሳ ሲሆን ጨረቃ ግን በአንደኛው ወር 29 በሌላኛው ወር ግን 30 ስለምትሆን ዓመቱ እኩል አያልቅም የጨረቃ ዓመት ነሐሴ 24 ቀን ያልቃል፡፡ ይህም ማለት ጨረቃ በሁለት ወር አንድ ጉድለት ታመጣለች፡፡ ያንን ነው ሊቃውንቱ ሕጸጽ(ጉድለት) ያሉት፡፡ በዚህም መሠረት ከላይ ኬክሮሱን(፩) በዓመቱ ቀናት አባዝተን ያገኘነውን 6 ዕለት ለጨረቃ ሕጸጽ ስንሰጠው የመስከረም/ ጥቅምት (1)፣ የጥቅምት/ ኅዳር(2)፣ የጥር/ የካቲት(3)፣ የመጋቢት/ ሚያዝያ(4)፣ የግንቦት/ ሰኔ (5)፣ የሐምሌ ነሐሴ (6) ሆነው ተካፍለው ያልቃሉ፡፡

በሌላም በኩል ደግሞ በጨረቃና በፀሐይ ዑደት መካከል በዓመት ያለው ልዩነት 11 ቀናት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልዒት) ይሆናል፡፡ ስድስቱን ዕለታት ጨረቃ ለምታጎልበት (ሕጸጽ) ብንሰጠው ቀሪ 5 ዕለት ይኖረናል፡፡ ጳጉሜ ማለት እነዚህ 5 ቀናት ናቸው፡፡ አሁን የአሥራ አንዱን ዕለታት ከፈጸምን ሽርፍራፊዎቹን (15 ኬክሮስና 6 ካልዒት) እንይ፡፡

ከላይ እንዳየነው በፀሐይና ጨረቃ ዓመታት መካከል የተፈጠሩትን 11 ቀናት ስድስቱ ለሕጸጽ ማሟያ ሲገቡ የቀሩት 5 ዕለታት ናቸው ጳጉሜ የምትባለውን ወር በመሠረታዊነት የፈጠሯት፡፡ በጎርጎርዮሳውያኑ አቆጣጠር እነዚህ 5 ተጨማሪ ዕለታት በጃንዋሪ፣ ማርች፣ ሜይ፣ ጁላይና ኦገስት ላይ ስለተጨመሩ እነዚህ ወራት 31 ለመሆን ተገድደዋል፡፡ (ይህንን የከፈለው በ46 ቅልክ የነበረው ዩልየስ ቄሣር ነው፡፡ ለአራቱ ወሮች 30 ቀን፣ ለአንዱ 28/29 (በየአራት ዓመቱ)፣ ለቀሩት ሰባት ወሮች ደግሞ 31 ሰጥቷቸዋል፤ ለአምስቱ ወሮች 31 ያደረጋቸው ከጳጉሜ ወስዶ ሲሆን ለሁለቱ ወሮች አንዳንድ ቀን የጨመረላቸው ከፌቡርዋሪ 2 ቀናት ወስዶና ወሩን 28 አድርጎ ነው)፡፡

ከእንግዲህ የሚቀሩን ከላይ የየዕለቱን ልዩነት ለዓመት ስናባዛ (ቁጥር ፪ና ፫ ተመልከት) የቀሩን 15 ኬክሮስና 6 ካልዒት ናቸው፡፡ ሁለቱን  ከላይ ያየናቸውን (፬ና፭) ስንደምራቸው (12 ኬክሮስ + 3 ኬክሮስ ከ6 ካልዒት) 15 ኬክሮስ ከ 6 ካልዒት ይመጣሉ፡፡

ቀደም ብለን አንድ ዕለት 60 ኬክሮስ ነው ብለናል፡፡ ስለዚህም አንድ ዕለት (60 ኬክሮስ) ለማግኘት ከላይ ያገኘነውን 15 ኬክሮስ በ 4 ማባዛት አለብን፡፡ በአራት ዓመት አንዴ ጳጉሜ 6 የምትሆነው እነዚህ በየዓመቱ የተጠራቀሙት 15 ኬክሮሶች አንድ ላይ መጥተው በአራት ዓመት አንድ ጊዜ አንድ ዕለት ስለሚሆኑ ነው፡፡ እርሷም ሠግር(leap year) ትባላለች፡፡ ጎርጎርዮሳውያኑ ይህቺን ሠግር በፌቡርዋሪ ወር ላይ ጨምረው ወሩን በየአራት ዓመቱ አንድ ጊዜ 29 ቀን ያደርጉታል፡፡

15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ተደምረው አንድ ዕለት መጡና በአራት ዓመት አንዴ ጳጉሜን ስድስት አደረጓት፡፡ የቀረችው 6 ካልዒትስ (ቁጥር ፭) የት ትግባ?

ካልዒት አንዲት ዕለት ትሆን ዘንድ 3600 ካልዒት ያስፈልጋሉ፡፡ ይህንን ያህል ካልዒት ለማግኘት 600 ዓመታት ያስፈልጉናል፡፡ ለዚህ ነው ጳጉሜ በየስድስት መቶ ዓመታት ሰባት የምትሆነው፡፡ እስካን የጠየቅኳቸው የባሕረ ሐሳብና የታሪክ ሊቃውንት በታሪካችን ውስጥ ጳጉሜን 7 የሆነችበትን ዘመን እንደማያውቁ ነግረውኛል፡፡ ሒሳቡ ሲሰላ በየ 600 ዓመቱ ሰባት ትሆናለች ቢባልም አስቦ በስድስት መቶኛው ዓመት ሰባት የሚያደርጋት እንደሌለ ይናገራሉ፡፡ በፈረንጆቹ ብሂል ‹ፌብሩዋሪ 30› ማለት የመሆን ዕድል ያለው ነገር ግን ሆኖሞ የማያውቅ ሊሆንም የማይችል(possible but never happen)› ተደርጎ እንደተወሰደው ሁሉ ምናልባት በኛም ጳጉሜን 7 ማለት እንደዚያው ይሆን ይሆናል፡፡

በነገራችን ላይ ጳጉሜን 5 ቀን በቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ዘንድ ‹ዕለተ ምሪያ› ወይም የተመረጠች ቀን ትባላለች፡፡ የጌታችን ልደት ለመጠበቅ ሊቃውንቱ ሲያሰሉባት የቆየችው ዕለት በመሆኗ ነው ይህንን ስያሜ ያገኘችው፡፡ የጌታችንን ልደት ቀን የምትወስነው ጳጉሜ 5 ቀን ናት፡፡ ልደት የሚውለው ጳጉሜ 5 በዋለበት ቀን ነው፡፡ ለምሳሌ ዘንድሮ ጳጉሜን 5 ቀን ረቡዕ ነው የምትውለው፤ ስለዚህም በ2007 ዓም ልደት የሚውለው ረቡዕ ነው፡፡ በየአራት ዓመቱ አንድ ጊዜ ጳጉሜን 6 ስትሆን ልደት በ28 የሚከበረው ዕለተ ምሪያን ስለማይለቅ ነው፡፡ ስድስተኛዋ ቀን ልደትን በአንድ ቀን ስታዘልለው እኛ በ28 እናከብረዋለን፡፡ ልደት ጳጉሜ 5 ቀንን(ዕለተ ምሪያን) ስለማይለቅ፡፡ ታድያ ምነው እነ ጥምቀትና ግዝረት አይለወጡም? ቢሉ፡፡ ሊቃውንቱ የሚሰጡት መልስ ‹ትውልድ ሱባኤ እየቆጠረ በተስፋ የጠበቃት ዕለተ ልደትን ስለሆነ ነው፤ ሌሎቹ የመጡት በልደቱ ምክንያት ነው›› የሚል ነው፡፡

በጎርጎርዮሳውያንም ቢሆን በአራት ዓመት አንዴ ልደት ዝቅ ትላለች፡፡ የእነርሱ የማይታወቀን ጭማሪዋ ፌብርዋሪ ላይ ስለሆነች ነው፡፡ ያ ደግሞ አዲሱን ዓመት ካከበሩ በኋላ ስለሚመጣ ነው፡፡ የእኛ ግን የምትወድቀው ጳጉሜን መጨረሻ ላይ በመሆኗ ከአዲስ ዓመት በፊት ስለምትጨመር ጎልቶ ይታወቃል፡፡

እንግዲህ ጳጉሜ የምትባለው አስገራሚ ትንሷ ወራችን እንዲህ በስሌት የተሞላች፣ አምስት ሆና ቆይታ በየአራት ዓመቱ አንዴ ስድስት፣ በየስድስት መቶ ዓመቱ ደግሞ ሰባት የምትሆን ናት፡፡ ታላላቆቹ ወሮች ምንም ሳይፈጥሩ የልደትን ቀን የምትወስን፣ የዓመቱን ሠግር የምታመጣ፣ ታሪከኛ ወር ናት፡፡ ትንሽ ትልቅ ማለት እንዲህ ነው፡፡

 

 

 

ከኅዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘ አዲስ አበባ የገቡት የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሜህ ሹክሪ ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ እና ከኢትዮጵያ አቻቸው ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ጋር ተገናኝተዋል፡፡

የሁለቱ ሃገሮች መሪዎች ከወራት በፊት ኢኳቶሪያል ጊኒ ዋና ከተማ ማላቦ ላይ ያደረጉት ውይይት ለተሻለ ግንኙነት አዲስ ምዕራፍ የከፈተ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በጋራ በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል፡፡

ለዝርዝሩ በመግለጫው ላይ የተገኘውን እስክንድር ፍሬውን ዘገባ ያዳምጡ፡፡

ለተጨማሪ መረጃና ማብራሪያዎች ከታች ያሉትን ማገናኛዎች እየተጫኑ…

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በኢትዮጵያ ፍትሕ ሚኒስቴር መከሰሳቸውን ተከትሎ ሀገር ጥለው የተሰደዱ የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች የደኅንነት ስጋት ገጥሞናል ይላሉ። የጋዜጠኞቹ የደኅንነት ስጋት ተዓማኒ ከሆነ ድጋፍ የሚያደርግ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ጉዳይ ድርጅት የኬንያ ፅ/ቤት ተናግሯል።