የዚህ ታላቅ ሰው ድንገተኛ ዜና-ዕረፍት ህሊናዬን ዘልቆ አናውጦታል ፣ ለጥቂት አፍታዎች ተደነባብሬ ነበር፣ እስከ አሁንም ውስጤን በምናቤ ሳሰላስለው የሰቀቀን ስሜት እንደ ዋጠኝ አለሁ። ታላቅ ዋጋ የምትሰጡት ፣ ፋይዳ ያለው የአገር ፣ የህዝብ እና የታሪክ ስንከሳር የታጨቀበት ግዙፍ መርከብ በማእበል ተመቶ ባህር ውስጥ የመስመጥ አደጋ ደረሰበት የሚል ዜና የሰማሁ መሰለኝ። የዕውቀት ክምችት ፣ የዳበረ ልምድ ፣ […]

(አዲስ አድማስ፤ ቅጽ 16 ቁጥር 821፤ ቅዳሜ መስከረም 29 ቀን 2008 ዓ.ም.) የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ሰርቪስ(ኢቢኤስ)፤ በሳምንት አንድ ቀን በጣቢያው መንፈሳዊ ዝግጅት የሚያስተላልፉ ሃይማኖታዊ ፕሮግራሞች፣ የታደሰ የፈቃድ ማስረጃዎቻቸውን እንዲያስገቡ አስቸኳይ ትእዛዝ ሰጠ፡፡ የቴሌቪዥኑ ፕሮግራሚንግ ኮሚቴ መስከረም 21 ቀን 2008 ዓ.ም. ለአራት የሃይማኖታዊ ፕሮግራም ክፍሎች በጻፈው ደብዳቤ፤ ከጣቢያው ጋር በገቡት ውል መሠረት ለሚወክሉት የሃይማኖት ተቋም ወይም የሃይማኖት …

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ በሁለተኛው የትራንስፎርሜሽን ረቂቅ እቅድ ላይ ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር መወያየት ተገቢና አስፈላጊ መሆኑን አስታወቁ።

ኢሳት ዜና (ጥቅምት 27 ፣ 2008) በዋሺንግተን ዲሲ አቅራቢያ አርሊንግተን በተካሄደው በዚህ የቀብር  ስነ-ስርአትና በአሌክሳንድሪያ ከተማ በተከናወነው የጸሎት ፕሮግራም ከፍተኛ ቁጥር ያለው ህዝብ መገኘቱንም ለማየት ተችሏል ። ከአውሮፓ፣ ከካናዳና፣ ከተለያዩ የአሜሪካ ግዛት የመጡ እንዲሁም በዋሺንግተን ዲሲ ዙሪያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በተገኙበት የጸሎትና የቀበር  ስነ-ስርአት የአቶ ሙሉጌታ ወዳጆች ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል። የአንጋፋው ጋዜጠኛና ደራሲ እንዲሁም የፖለቲካ ተንታኝ የአቶ …

መስከረም 27, 2008 አንጋፋው ጋዜጠኛ፣ ሃያሲ፣ ደራሲና፣ የፖለቲካ ተንታኝ ሙሉጌታ ሉሌ በድንገት ከዚህ ዓለም በሞት በመለየታቸው የኢሳት ማኔጅመንት፣ ጋዜጠኞችና፣ መላው የኢሳት ቤተሰብ ከፍተኛ ሃዘን ተሰምቶታል። አቶ ሙሉጌታ ሉሌ በተባ ብዕራቸው ሃገራዊ ፍቅርን፣ አንድነትን፣ ነፃነትንና፣ ፍቅርን የሰብኩ፥ በአንደበታቸው ስለኢትዮጵያ የመሰከሩ፣ እስከመጨረሻ እስትንፋሳቸው ድረስ ኢትዮጵያን ያገለገሉና፣ ኢትዮጵያን ተቀምተው በስደት የቀሩ ሃገራዊ ሃብት ነበሩ። የሙያ አባታችን ሙሉጌታ ሉሌ …

መስከረም ፳፰ (ኅያ ስምት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦሮምያ ክልል በ በቆጂ ከተማ ከቤት ማፍረስ ጋር በተያያዘ በተነሳ ተቃውሞ ከ20 በላይ ወጣቶች በፖሊሶች ተደብድበው ሆስፒታል የገቡ ሲሆን፣ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ነዋሪዎች ደግሞ ተደብድበዋል። ግጭቱ የተከሰተው የወረዳው ባለስልጣናት ቤት አፍራሽ መኪኖችን በመላክ ህገወጥ ቤቶች ያሉዋቸውን ቤቶች ማፍረስ መጀመራቸውን ተከትሎ ሲሆን፣ ነዋሪዎች ድንጋይ በመወርወር ተቃውሞቸውን ገልጸዋል። …

መስከረም ፳፰ (ኅያ ስምት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከጸጥታ እና ከደህንነት ዋስትና ማጣት ጋር በተያያዘ፣ ስራ ያቋረጡት የመንግስት ሰራተኞች፣ ከወረዳው ባለስልጣናት ጋር ተናንት የተወያዩ ቢሆንም፣ መተማመን ላይ ባለመድረሳቸው አብዛኞቹ ዛሬም ስራ ሳይጀምሩ ቀርተዋል። አንዳንድ የመንግስት ሰራተኞች በግዴታ ስራ እንዲጀምሩ ቢደረግም፣ ብዙዎቹ በአድማው ቀጥለውበታል። የሀመር ወረዳ አርብቶአደሮች በየጊዜው በሚሰነዝሩት ጥቃት የፖሊስ፣ የመከላከያና የልዩ ሃይል አባላትን …

መስከረም ፳፰ (ኅያ ስምት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኢትዮጵያ የተከሰተውና ከ4 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ ሕዝብ ለምግብ እጥረት የዳረገው የድርቅ ችግር በቀጣይ ወራትም ሊስፋፋ እንደሚችል ከፍተኛ ስጋት ፈጥሯል። ከብሔራዊ ሚቲሮዎሎጂ ኤጀንሲ የወጡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ከኤልኒኖ ክስተት ጋር ተያይዞ ከቀጣይ ጥቅምት ወር ጀምሮ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች እንደሚያጋጥም ዓለም አቀፍ ትንበያ መኖሩን በመጥቀስ፣ …

መስከረም ፳፰ (ኅያ ስምት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በዳንግላ ዙሪያ ነዋሪ የሆነው አቶ ደግአረገ በአካባቢው ያሉ ወጣቶችን በትጥቅ ትግል ለሚታገሉ ሃይሎች እየመለመልክ ትልካለህ በሚል አሰቃቂ በሆነ ሁኔታ ተደብድቧል። ማንነታቸውን በውል ለይቶ የማያውቃቸው ሰዎች አይኑን በጨርቅ ሸፍነው ወደ ባህርዳር እንደወሰዱትና በመጨረሻም መረጃ ሲያጡ ፣ አይኑን ሸፍነው እንደለቀቁት ገልጿል።

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ዩሱፍ ያሲን (ኦስሎ)

የዴሞክራሲያዊ ምንቕስቓስ ህዝቢ ትግራይ ዴምህት ሊቀመንበር የነበሩት አቶ ሞላ አስገዶም / Mola Asgedom

ከሰሞኑ ጫጫታ ባሻገር

የሞላ አስገዶም ኩብለላ፣ ፍርጠጣ ክሕደት ወይም በመንግሥት ደጋፊዎች እንደተባለው ወሽመጥ በጣሽ የጀግንነት ሥራ በአሥመራ ተጓዞችና ደርሶ – ተመላሾች መሓል እየተቋጠረ መጥቷል ብለን ያሰብነው ንትርኩን እንደገና አደበላለቀው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

መስከረም ፳፯ (ኅያ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ክልል በሃመር ወረዳ በዲመካ ከተማ ማክሰኞ የተጀመረው የስራ ማቆም አድማ እስከ ዛሬ የቀጠለ ሲሆን፣ የዞኑ ባለስልጣናት ነዋሪውን ለማነጋገር ስብሰባ ጠርተዋል። የስራ ማቆም አድማው መንስኤ ካለፉት 6 ወራት ጀምሮ በአካባቢው በመካሄድ ላይ ያለው ግጭት ስራቸውን ለመስራት ስላላስቻላቸው ነው። የመንግስት ሰራተኞች እንደሚሉት ካለፈው ሰኔ ወር ጀምሮ በወረዳው …

መስከረም ፳፯ (ኅያ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከሁለት ሳምንት በፊት በሳዑዲ አረቢያ ሚና አካባቢ በሀጂ ስነ-ስርዓት ወቅት በተከሰት ግፊያና መጨናነቅ በደረሰ አደጋ ህይወታቸውን ያጡ ኢትዮጵያዊያን ቁጥራቸው ከ47 በላይ የበለጠ ቢሆንም ፣ የኢህአዴግ መንግስት ለዚህ ከባድ ሐዘን የሰጠው ትኩረት ማነስ እንዳሳዘናቸው ዘጋቢያችን ያነጋገራቸው በአዲስአበባ የሚኖሩ ሙስሊሞች አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የመጅሊሱን ወሬ በመያዝ …

መስከረም ፳፯ (ኅያ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በነሶልያ ሽመልስ የክስ መዝገብ በሽብረተኝነት በተከሰሱት ወጣት ጸሃፍት ላይ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ሲጠበቅ ዳኞች “አዳማ ስልጠና ላይ ናቸው” በሚል ለ38 ኛ ጊዜ እንዲራዘም ተደርጓል። ፍርድ ቤቱ ውሳኔ ለመስጠት ለ5ኛ ጊዜ ቀጠሮ አራዝሟል። በአንድ መዝገብ ከተከሰሱት መካከል የተወሰኑት መለቀቃቸው፣ ቀሪዎቹም ይለቀቃሉ የሚል ተስፋ አሳድሮ ነበር። ድንበር የለሽ …

መስከረም ፳፯ (ኅያ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሶማሊያ ሰላም አስከባሪ ሰራዊት አሚሶል ስር ያለውን ንብረነታቸው የኢትዮጵያ ጦር ሰራዊት የሆኑትን ሁለት ወታደራዊ ተሽከርካሪዎችን በደቡባዊ ምዕራብ ሶማሊያ በጌዶ ግዛት በደፈጣ ውጊያ ማውደሙን አልሸባብ አስታውቋል። ጥቃቱ የተፈፀመው በአሊላን መንደር ውስጥ በአልሸባብና በኢትዮጵያ ሰራዊት መሃከል ለሰዓታት የቆየ የተኩስ ልውውጥ ተደርጎ ነው። በአርፒጂ የጦር መሳሪያ ተሽከርካሪዎቹ መመታታቸውን የአካባቢው …

መስከረም ፳፯ (ኅያ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ላለፉት 4 ቀናት ያለማስጠንቀቂያ የተቋረጠው ኤሌክትሪክ፣ በንግድ ቤቶች እና በነዋሪዎች የእለት ተለት ህይወት ላይ ችግር ማስከተሉን ነዋሪዎች ገልጸዋል። የኤሌክትሪክ አገልግሎቱ የተቋረጠበት መንስኤ ለህዝቡ አለመገለጹንም ተናግረወዋል። ከዚህ በፊት በከተማው በተደጋጋሚ የ ኤሌክትሪክ መቋረጥ የሚከሰት ሲሆን ፣ ያሁኑ ደግሞ የተለየ ነው ሲሉ ነዋሪዎች በምሬት ይገልጻሉ። በከተማው በሳምንት አንድ …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ይቅርታ - የወያኔ ካርታ / yekerta ye tplf kartaይገረም አለሙ

1437ኛው የኢድ አል አድኻ (አረፋ) በዓል በአዲስ አበባ ስታዲየም ሲከበር ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት፤ በሽብር ወንጀል ተከሰው ከተፈረደባቸው የሙስሊሙ ማኅበረሰብ ችግሮች መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት መካከል ስድስቱ በቅርቡ የተለቀቁት በእነርሱ ጥያቄና ጥረት እንደሆነ፤ ጥያቄአቸው ምላሽ በማግኘቱና ጥረታቸው በመሳካቱ መደሰታቸውን ገልጸው፤ ለመንግሥት ምሥጋና ማቅረባቸውን የጀርመን ድምጽ ራዲዮ ዘጋቢ ከስፍራው ባስተላላፈው ዘገባ አሰምቶናል። ወያኔ ግዜና ወቅት እየጠበቀ የሚጠቀምባት የፖለቲካ ቁማር መጫወቻ የይቅርታ ካርድ በሌላ መንገድና መልክ ተመዘዘች ማለት ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

በዛሬው ዕለት በነሶልያና የክስ መዝገብ በዞን ዘጠኝ ጦማርያን ላይ ማለትም በሶልያና ሽመልስ በሌለችበት፣ አቤል ዋበላ፣ አጥናፍ ብርሃኔ፣ ናትናኤል ፈለቀ እና በፍቃዱ ኃይሉ ላይ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው ችሎት ዳኞች አዳማ ስልጠና ላይ ናቸው በሚል ባለመገኘታቸው ምክንያት ለጥቅምት 5/2008 ዓ/ም ቀጠሮ መሰጠቱን ለማወቅ ተችሏል፡፡


በእስር 531ኛ ቀናቸውን እያሳለፉ የሚገኙት ጦማርያኑ ይህ የፍርድ ቤት ቀጠሮአቸው ለ38ኛ ጊዜ የተሰጣቸው ነው ፣ ጥፋተኛ ናቸው ወይም አይደሉም የሚለውን ውሳኔ ለማሰማት ፍርድ ቤት የዛሬውን ጨምሮ ለ5ኛ ጊዜ የተሰጠ ቀጠሮ ነው፡፡


ስሜት የማይሰጡ ክሶች እና የተራዘሙ የፍርድ ሂደቶች ዜጎችን በአገራቸው የበለጠ ተስፋ እንዲቆርጡ የሚያደርጋቸው ከመሆኑም በላይ ያለዋስትና በፍርሃት እንዲኖሩ የሚያደርግ ነው፣ ይህ እንዲሆን ካልተፈለገ በቀር በቀጠሮዎች መራዘም ንጹሃንን ጥፋተኛ ማድረግ አይቻልም፡፡

ባልተፈጸመ ወንጀል፣ ባልቀረበ ማስረጃ ዜጎችን ማንገላታት ይቁም፡፡

Ethiopian Transitions: At Home and Abroad (by Kebede Haile) / የኢትዮጵያውያን ሽግግር - በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር (ከበደ ኃይሌ)አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ ዋለ

የመጽሐፉ ርዕስ፡- Ethiopian Transitions: At Home and Abroad (የኢትዮጵያውያን ሽግግር – በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር)

ፀሐፊ፡- ከበደ ኃይሌ

ቋንቋ፡- እንግሊዝኛ እና አማርኛ

ዋጋ፡- 32.99 የአሜሪካ ዶላር (ጠንካራ ሽፋን)

የገጽ ብዛት፡- 286

አሳታሚ፡- ኦልራይት ፐብሊሺንግ

ገበያ ላይ የዋለው፡- መስከረም 14 ቀን 2008 ዓ.ም. / ኦገስት 24 ቀን 2015 (እ.ኤ.አ.)

ደራሲና ፀሐፊ ከበደ ኃይሌ በቅርቡ እንግሊዝኛ እና በአማርኛ ቋንቋ የጻፉት “Ethiopian Transitions: At Home and Abroad” (የኢትዮጵያውያን ሽግግር – በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር) የተሰኘው መጽሐፍ በቅርቡ በገበያ ላይ መዋሉን ለኢትዮጵያ ዛሬ በላኩት ኢ-ሜይል ገለጡ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ዶ/ር አምባዬ ወልደ ሚካኤል የማሕጸንና ጽንስ ባለሞያ ናቸው፡፡ሥራ በጀመሩበት አዲስ አበባ ፌስቱላ ሆስፒታል ዐስራ አራት ዓመታት አገልግለዋል፡፡ በዚህ ቆይታቸው በሞያቸው ከሚያገለግሏቸው ሴቶች በተጫማሪ በሆስፒታሉ ውስጥ አንድ ቡድን በማዋቀር ከአዲስ አበባ ውጪ በሦስት ቦታዎች የፌስቱላ ሕክምና አገልግሎት መስጠት የሚችሉ ማዕከላትን አቋቁመዋል፡፡

ከደርግ መፈክሮች / Revolutionary monument extols the virtues of communism. Courtesy Paul Henze. ጌቱ ኃይሉ

አቶ ዠ 57 ዓመታቸው ነው። መተዳደሪያ አላቸው። እንዴት ያለ ሙያ!! ባሥራ ሰባት ዓመታቸው የጀመሩት። አርባ ዓመት ሙሉ ያለማቋረጥ እየሠሩ ያሉት። ሰዉ ከሥራው በመንግሥት ለውጥ፣ በሰበብ ባስባቡ ሲባረር እሳቸው ሥራ አላጡም። ሥራቸው መፈክር አድምቆ መጻፍ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Prof. Mesfin Woldemariam. ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም ይገረም አለሙ

ፈጣሪ ዕድሜ ከጥንካሬ ጋር ያደላቸው በሀገር ጉዳይ የማይታክቱት ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም ሰሞኑን በምድረ አሜሪካ ነዋሪ ከሆኑ ኢትዮጵያውያን ጋር ያደረጉትን ውይይት፤ ዘመነ ቴክኖሎጂ ምስጋን ይግባውና በያለንበት ሆነነን ተከታትለናል። ከውይይቱ ታዳሚዎች ከቀረቡ በርካታ ጥያቄዎች አንዱ፣ “በያ ትውልድ ላይ ጨከኑበት” የሚል ነበር። ፕ/ር መስፍን ሲመልሱም፤ አልጨከንኩበትም እውነቱን ነው የተናገርኩት፣ አንዳንዶቹ እንደውም ተማሪዎቼ ነበሩና አነጋሬአቸዋለሁ፣ ፍላጎታቸው ለሀገርና ለሕዝብ ሳይሆን ሥልጣን ነበር ብለዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

መስከረም ፳፮ (ኅያ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መስከረም 13 ቀን 2008 ዓም የሃጅ ጸሎት ለማድረስ ወደ አገሪቱ ከተጓዙት ኢትዮጵያውያን መካከል 47 ሙስሊሞች መሞታቸውን የእስልምና ጉዳዮች ጠ/ምክር ቤት አስታውቋል። 24 ጸሎት አድራሽዎች ቆስለው ከሆስፒታል ሲወጡ ፣ 2ቱ አሁንም ተኝተው በመታከም ላይ ናቸው። በእለቱ በደረሰው አደጋ የሳውዲ መንግስት 700 ሰዎች እንደሞቱ ቢናገረም፣ በእየለቱ የሚወጣው አሃዝ …

መስከረም ፳፮ (ኅያ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ቡድኑ ነገ ሃሙስ ክሳቸው ለ37ተኛ ጊዜ በፍርድ ቤት የሚታየውና በመፃፋቸው ብቻ በአሸባሪነት ክስ ተወንጅለው በእስር ላይ የሚገኙት አራቱ የዞን 9 ጦማሪያን ቡድን አባላት ካለምንም ቅድመ ሁኔታ ክሳቸው ተቋርጦ በነፃ እንዲለቀቁ ሲል አሳስቧል። ካለፈው ዓመት ጀምሮ በእስር ላይ ከሚገኙት ጋዜጠኞች አጥናፍ ብርሃነ፣ በፍቃዱ ኃይሉ፣አቤል ዋበላ እና ናትናኤል …

መስከረም ፳፮ (ኅያ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ድርጅቱ በማካሄድ ላይ ባለው 11ኛ ጉባኤ በተለያዩ ክልሎች ከ937 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳኑን ገልጿል። ከክልሎች ሁሉ ከፍተኛ ገንዘብ ከስርቆት የዳነው በአማራ ክልል ነው ሲል አክሎ ጠቅሷል። በዚህ ጊዜ እንደተገለጸው ግልጽነት በጎደለው የግዢ ሂደት ሊባክን የነበረ ከ937 ሚሊየን ብር በላይ የህዝብ ገንዘብ ለማዳን ተችሏል። ከሙስና ጋር በተያያዘ …

መስከረም ፳፮ (ኅያ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በህገወጥ መንገድ ድንበር አቋርጠው ኬንያ ሲገቡ መንገድ ላይ ያዝኳቸው ያለውን አስራ አራት ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች የኬንያ ፖሊስ ይዞ ማቻኮስ ፍርድ ቤት አቅርቧቸዋል።ስደተኞቹ የቀረበባቸውን ክስ ያልተቀበሉት ሲሆን የሃያ ሽህ ሽልንግ የገንዘብ ቅጣት ወይም የመቶሰላሳ ቀናቶች የእስር ቅጣት እንደሚበየንባቸውና ቅጣቱን ከከፈሉ በኋላ ወደ አገራቸው እንደሚላኩም ተገልጿል። ስደተኞቹ በናይሮቢ ሞንባሳ …

መስከረም ፳፮ (ኅያ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ነዋሪዎች እንደገለጹት በከተማው ቀበሌ 9 የድሃ ልጆች የሚማሩበትን መዋለ ህጻናት ትምህርት ቤት፣ ምርጫውን ሰበብ ተደርጎ ለፌደራል ፖሊስ በጊዜያዊነት ከተሰጠ በሁዋላ፣ ፖሊስ አለቅም በማለቱ ከነዋሪዎች ጋር ውዝግብ ተፈጥሯል። ፖሊስ በ15 ቀናት ቦታውን እንደሚለቅ ገልጾ፣ ትምህርት ቤቱን ቢረከብም፣ እስካሁን ድረስ ባለመልቀቁ ወላጆች ልጆቻቸውን ማስተማር አልቻሉም። ወላጆች አቤቱታ ለማቅርብ …

የሞ ኢብራሒም ፋውንዴሽን ሪፖርት ኢትዮጵያን በመልካም አስተዳደር አነስተኛ ደረጃ ሰጣት

በየዓመቱ የአፍሪካ አገሮችን የመልካም አስተዳደር ደረጃን ይፋ በማድረግ የሚታወቀው የሞ ኢብራሒም ፋውንዴሽን ባወጣው ሪፖርት ኢትዮጵያ  በመልካም አስተዳደር ረገድ ዝቅተኛ ደረጃ ላይ እንደምትገኝ ይፋ አደረገ፡፡

ባለፈው ሰኞ በለንደን ይፋ ባደረገው እ.ኤ.አ. የ2015 የአፍሪካ አገሮች መልካም አስተዳደር ደረጃ ከ54 የአፍሪካ አገሮች 21 የሚሆኑት በመልካም አስተዳደር ዝቅጠት እንዳሳዩ ጠቁሟል፡፡ 

ባለፉት አራት ዓመታት ከአንድ እስከ አሥር ከተቀመጡት መሪ አገሮች መካከል ግማሽ ያህሉ ብቻ መሻሻል እንዳሳዩ የሚገልጸው ሪፖርቱ፣ እ.ኤ.አ. ከ2011 በኋላ የአፍሪካ አገሮች በመልካም አስተዳደሩ ረገድ የተወሰነ መሻሻል በጥቅሉ በማስመዝገብ ባለፈው ዓመት 50.1 ዕድገት ማስመዝገባቸውን ሪፖርቱ ያሳያል፡፡

‹‹የአፍሪካ አገሮች ከ15 ዓመት በፊት ከነበረው ሁኔታ አንፃር ዛሬ ጤናማና ዴሞክራሲያዊ በሆነ ሁኔታ ውስጥ እየኖሩ ቢሆንም፣ የ2015ቱ ሪፖርት እንደሚያሳየው ወሳኝ በሆኑ መስኮች የታየው መሻሻል በተጠበቀው ደረጃ አልተመዘገበም ወይም በተቃራኒው ተፈጽሟል፡፡ ለዚህ ደግሞ ጥሩ የመሻሻል መስመር ላይ የነበሩት ጥቂት አገሮች ሳይቀር እየተንገዳገዱ መሆናቸው የማስጠንቀቂያ ደውል ሊሆነን ይገባል፤›› ሲሉ አስተያየታቸውን የገለጹት የሞ ኢብራሒም ፋውንዴሽን ሊቀመንበር ዶ/ር መሐመድ ኢብራሒም፣ ሁሉንም የአፍሪካ አገሮች ያማከለና ቀጣይነት ያለው መሻሻል በሁሉም መስክ ሲመዘገብ ብቻ የአፍሪካ የወደፊት ዕጣ ፈንታዋ ብሩህ እንደሚሆን ጠቁመዋል፡፡

ከአንድ እስከ 20 ደረጃን ይዘው ከሚገኙት መሪ አገሮች መካከል የመጀመሪያዎቹ አምስት አገሮች እ.ኤ.አ. በ2015 ሪፖርት ከፍተኛ ለውጥ ያመጡ መሆናቸው ሲጠቆም፣ ከእነዚህም መካከል ሴኔጋል ከነበረችበት የ9ኛ፣ ኬንያ ከነበረችበት የ14ኛ፣ ሞሮኮ ከነበረችበት የ16ኛ፣ ሩዋንዳ ከነበረችበት የ11ኛና ቱኒዝያ ከነበረችበት የ8ኛ ደረጃ ተነስተው ወደ መጀመሪያዎቹ አምስት አገሮች ተርታ መካተታቸው ተገልጿል፡፡

እ.ኤ.አ. ከ2011 ጀምሮ ኢትዮጵያ በጠቅላላው የመልካም አስተዳደር ግምገማ ከአሥሩ የመጀመሪያዎቹ አገሮች ተርታ ውስጥ የተካተተች ቢሆንም፣ በአዲሱ ሪፖርት አጠቃላይ ውጤቷ 48.6 በመቶ ነው፡፡ ይህም ከአፍሪካ አገሮች መካከል 31ኛ ደረጃን እንድትይዝ ሲያደርጋት ከቀጣናዋ ደግሞ 5ኛ አድርጓታል፡፡ ከአራቱ ዋና ዋና የመልካም አስተዳደር እመርታ ከሚታይባቸው ዘርፎች መካከል ሕዝባዊ ተሳትፎና ሰብዓዊ መብት፣ የሰው ሀብት ልማትና በተለይም ደኅንነትና የሕግ የበላይነት በቀዳሚነት ለምዘና የሚቀርቡ መሆናቸውን የሚገልጸው ሪፖርቱ፣ በደኅንነትና በሕግ የበላይነት ኢትዮጵያ በአኅጉሩ 26ኛ ደረጃ ሲኖራት በምሥራቅ አፍሪካ ደግሞ 5ኛ መሆኗን ያሳያል፡፡ በዚህ ዘርፍ 13.8 የመሻሻል ዕድገቷን እ.ኤ.አ. ከ2011 ጀምሮ ጠብቃ ብትገኝም፣ በአገር ውስጥ የእርስ በርስ ግጭቶችና በድንበር አካባቢ በሚታዩ ግጭቶች የመንግሥት ጣልቃ ገብነት ታክሎበት ለውጦች ቢመዘገቡም፣ በአገር ውስጥ በሚፈናቀሉ ዜጎችና በውጭ አገሮች የፖለቲካ ጥገኝነት በሚሹ ዜጎች ቁጥር ረገድ ሲታይ ግን፣ ደካማ አፈጻጸሞች መኖራቸውንም ሪፖርቱ ይፋ አድርጓል፡፡

በግለሰብ ደኅንነት ረገድ በአኅጉሩ 12ኛ ደረጃን እንደያዘች የሚያሳየው ሪፖርት፣ በዚህ ንዑስ ዘርፍ በተለይም በብጥብጥና ወንጀል እንዲሁም በሕገወጥ የሰዎች ዝውውር ከአኅጉሪቱ በቀዳሚነት እንድትቀመጥ የሚያደርጋትን ሥራዎች ባለፉት አራት ዓመታት ውስጥ መሥራቷን የሞ ፋውንዴሽን የ2015 ሪፖርት ያስረዳል፡፡ በአንፃሩ በሕዝባዊ ተሳትፎና በፆታ እኩልነት አገሪቱ ዝቅተኛውን ደረጃ መያዟ ብቻ ሳይሆን፣ ባለፉት አራት ዓመታት ከፍተኛ ዝቅጠት ማሳየቷም ተመልክቷል፡፡ በዚህም ዘርፍ በሕዝባዊ ተሳትፎ ከአኅጉሩ 39ኛ ደረጃን ስትይዝ ለዚህም በዋነኝነት እንደማሳያ የቀረበው ፍትሐዊና ነፃ የሆነ ምርጫን የማካሄድ አቅሟ በኔጋቲቭ (-11.1) የተመዘገበ መሆኑ ታይቷል፡፡ በሴቶች ላይ በሚደርስ አድልኦና ጥቃትም አገሪቱ ኔጋቲቭ (-25.00) ያስመዘገበች መሆኑ ተገልጿል፡፡

የሪፖርቱን ይፋ መሆን ተከትሎ በተለያዩ ዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙኃን ከተዘገቡት ጉዳዮች መካከል ኢትዮጵያን ያካተተው የቀዳሚዎቹ አሥር አገሮች ዝርዝር፣ በአፍሪካ መፃኢ ዕድል ከፍተኛ ሚና የሚኖራቸው አገሮች መኖራቸው ነው፡፡ ለዚህም ኢትዮጵያ በብሔራዊ ደኅንነት፣ በመረጃ ነፃነት፣ በማኅበራዊ አለመረጋጋትና መንግሥትን ያማከለ ግጭቶችን የመፍታት፣ የሥልጣን ሽግግርና የሙስና ወንጀልን ከመከላከሉ ጋር በተያያዘ እየታየ ያለው መሻሻል እንደሆነ ሜይል ኤንድ ጋርዲያን አፍሪካ የተሰኘ ድረ ገጽ አስፍሯል፡፡ ኢትዮጵያ ይፋ በሆነው አዲሱ ሪፖርት በአጠቃላይ ውጤት በ31ኛ ደረጃ ላይ መቀመጧ ብዙ የሚጠብቃት የቤት ሥራ እንዳለ የሚጠቁም መሆኑን፣ ከላይ በተጠቀሱት ዋና ዋና የመሻሻል ዕርምጃዎች ታግዛ ደረጃዋን ልታሻሽል እንደምትችልም ግምት መኖሩ ተጠቁሟል፡፡ እንደ አገር ምዕራብ አፍሪካዊቷ ኮትዲቯር እጅግ በጣም መሻሻልን ያሳየች አገር ሆና ስትገኝ፣ በአንፃሩ ወጣቷ ደቡብ ሱዳን በከፍተኛ ዝቅጠት የመጨረሻውን ደረጃ ይዛለች፡፡   

የሞ ኢብራሒም ፋውንዴሽን በሱዳናዊ ብሪታኒያዊ ቢሊየነር ዶ/ር ሞሐመድ ኢብራሒም የተመሠረተ ሲሆን፣ በአፍሪካ በመልካም አስተዳደርና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ምርምር የሚያደርግና የተለያዩ ስኬታማ የሥራ ውጤቶችን የሚደግፍ ድርጅት ነው፡፡ እ.ኤ.አ. ከ2006 ጀምሮ በዚህ ሥራ ላይ ሲገኝ መቀመጫውም ለንደን ነው፡፡ 

 

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

አንዱዓለም ተፈራ

መከወኛ ሃሳብ፤

ዛሬ ካለንበት የፖለቲካ ሀቅ ላይ ቆመን የነገዋን ኢትዮጵያ በሃሳብ ብንመለከት፤ ሶስት እውነታዎች ገጠው ይታያሉ። የመጀመሪያው፤ አሁን በሥልጣን ላይ ባለው የገዥ ቡድን አስተዳደር፤ ምንም ቢሆን ምንም፤ ኢትዮጵያ የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት ሊኖራት አለመቻሉ ነው። ሁለተኛው ደግሞ፤ ኢሕአዴግ፤ ውስጡ እየነቀዘ፤ ወደ አንድ ፓርቲነት ከማደግ ይልቅ፤ በየድርጅቶቹ መጎነታተል እየተወጣጠረ፤ ከውስጥ መርቅዞ ወደ መበታተኑ በመሄድ ላይ ያለ መሆኑ ነው። ሶስተኛው ደግሞ፤ አሁን በያዝነው ሂደት፤ ሀገራችን እጅግ ወደ ከፋና ልትወጣበት ወደማትችለው መቀመቅ ውስጥ እየዘቀጠች መሆኗ ነው። እኒህ ፈጠው ያደገደጉ የፖለቲካ ሀቆች፤ በዚህ ጽሑፍ ተተንትነው ቀርበዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

የላይ አርማጭሆ ገበሬዎች በህወሓት አገዛዝ ፌደራልና ልዩ ኃይል ፖሊሶች በገፍ እየታፈሱ ወደ እስር ቤት እየተጋዙ ነው፡፡ ዘረኛው እና ፋሽስቱ የህወሓት አገዛዝ ከፌደራል ፖሊስ፣ ከልዩ ኃይል እና ከመከላከያ ተመርጦ የተውጣጣ ሰራዊት በላይ አርማጭሆ በሚገኙ የገጠር ቀበሌዎች ማለትም በሙሴ ባንብ በጃኒካው፣ በገንበራ እና በሌሎች በርካታ አካባቢዎች ያሰራጨ ሲሆን ከሦስቱ ክፍሎች የተጣመረው ኃይል በየገበሬው መንደር ተሰግስጎ በማሸበር በመሳሪያ […]

ገዳሟን ለችግር የዳረጉት ጥበቃና ክብካቤ እየተደረገላቸው፣ ሰበካ ጉባኤው እንዳይሠራ ተደርጓል ለጠቅላላ ጉባኤው ሪፖርት ለማቅረብ ጽ/ቤቱ ቢጠየቅም ሌላ የሰበካ ጉባኤ ምርጫ ተካሒዷል የገዳሟ ሒሳብ በውጭ ኦዲተር እንዲጣራ በፓትርያርኩ የተሰጠው ትእዛዝ ተግባራዊ አልኾነም ፓትርያርኩ፣ ወደ ተግባራዊ የፀረ ሙስና እና የመልካም አስተዳደር ርምጃ እንዲገቡ ተጠይቋል *          *          * በ7 ወራት ሒሳብ የቅድመ ኦዲት ዳሰሳ ብቻ ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ …

አቶ ሬድዋን ሁሴን በሃሰት ሲምሉለት የነበረውን ወንበር አጥተዋል።… ☞ ሃይለማርያም ከኒውዮርክ መልስ ሁለት ቀን ከመኖሪያቸው እንዳይወጡ ከሰው እንዳይገናኙ ተደርገዋል።… ☞ ጥያቄ የሚያበዙት አቶ አለማየሁ ተገኑ እና አቶ ሶፊያን አህመድ ከአሽከርነት ቦታቸው ተነስተዋል።… ☞ ትግላችን ላይ በማተኮር ሕወሓትን ከነአሽከሮቹ ልናጠፋቸው ይገባል። . የሕወሓት አሻንጉሊት የሆነው ሃይለማርያም ደሳለኝ በትናንትናው እለት ባቀረበው የቸብ ቸብ ካቢኔ መሰረት ሕወሓት የጦር […]

የመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ፣ ትምህርት ሚኒስቴር አንድ ሺሕ ሞተር ብስክሌቶችን ለመግዛት ያወጣውን ጨረታ አገደ፡፡ ኤጀንሲው ጨረታውን ያገደው መስከረም 18 ቀን 2008 ዓ.ም.

ለትምህርት ሚኒስቴር በጻፈው ደብዳቤ ነው፡፡ ጨረታው የታገደው በጨረታው ተሳታፊ የሆነው አግታ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ያቀረበው አቤቱታ ተቀባይነት በማግኘቱ ነው፡፡

አግታ መስከረም 14 ቀን 2008 ዓ.ም. ለመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ቅሬታውን በደብዳቤ አቅርቧል፡፡ አግታ ባቀረበው አቤቱታ ትምህርት ሚኒስቴር የመንግሥትን የግዥ አዋጅ በተፃረረ መልኩ ከፍተኛ ዋጋ ላቀረበ ኩባንያ ሥራው መሰጠቱን ተቃውሟል፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር ከሰባት ወራት በፊት አንድ ሺሕ ሞተር ብስክሌቶች ግዥ ለመፈጸም ጨረታ አውጥቶ ነበር፡፡ በጨረታው አራት ኩባንያዎች ቢሳተፉም፣ አንዱ ኩባንያ በቴክኒክ ምክንያት ወዲያውኑ ከጨረታ ውጪ ተደርጓል፡፡ የተቀሩት አግታ፣ ሐግቤስና በላይ አብ ሞተር ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ 

አንድ ሺሕ ሞተር ብስክሌቶች ለማቅረብ አግታ 37 ሚሊዮን ብር ሲያቀርብ፣ ሐግቤስ ኩባንያ ደግሞ ከ49 ሚሊዮን ብር በላይ አቅርቧል፡፡ የአግታ ኩባንያ ቅሬታ ከዚህ የመነጨ ሲሆን፣ ተመሳሳይ ሞተር ብስክሌቶች ለማቅረብ 13 ሚሊዮን ብር ብልጫ ያለው መወዳደርያ ገንዘብ ያቀረበ ኩባንያ አሸናፊ መደረጉ አግባብ አይደለም፣ የመንግሥትን የግዥ ሥርዓት ይፃረራል በማለት የአግታ ዋና ዳይሬክተር አቶ ግርማይ  ወልደአረጋይ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ 

“መንግሥትና ሕዝብን ሊከሳራና ለሕገወጥ ወጪ የሚዳርግና ፍትሐዊ የንግድ ውድድር እንዳይኖር ያደርጋል፤” በማለት የትምህርት ሚኒስቴር የግዥ ሒደት ሕገወጥ መሆኑን አቶ ግርማይ ተናግረዋል፡፡ 

የመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ የአግታን አቤቱታ በመቀበል ለትምህርት ሚኒስቴር ጨረታውን እንዲያቆም ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡ የፌዴራል መንግሥት የግዥና የንብረት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 649/2001 አንቀጽ 75 ንዑስ አንቀጽ 1 የግዥ አፈጻጸምና ንብረት አወጋገድ አቤቱታ አጣሪና ውሳኔ ሰጪ ቦርድ፣ አቤቱታ ሲቀርብለት፣ ወዲያውኑ አግባብ ላለው የመንግሥት መሥሪያ ቤት ማስታወቂያ ይልካል፡፡ ቦርዱ በጉዳዩ ላይ ውሳኔ እስከሚሰጥ ድረስም ማናቸውም ቀጣይ እንቅስቃሴ ወዲያውኑ መቆም እንዳለበት ይደነግጋል፡፡ 

በዚህ መሠረት የጨረታ ሒደቱ የታገደ ሲሆን፣ በአዲሱ አጠራር በገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ አለማየሁ ጉጆ የሚመራው የግዥ አፈጻጸምና ንብረት አወጋገድ አቤቱታ አጣሪና ውሳኔ ሰጪ ቦርድ፣ የመጨረሻ ምላሽ እስኪሰጥ ድረስ ጨረታው በእግድ ይቆያል፡፡

ኤጀንሲው ለትምህርት ሚኒስቴር በጻፈው ደብዳቤ ዕገዳ ከማስተላለፍ በተጨማሪ፣ የጨረታ ሒደቱ ሙሉ መረጃና ቃለ ጉባዔ እንዲላክለት ማሳሰቢያ ሰጥቷል፡፡ 

የትምህርት ሚኒስቴር የግዥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ገብረየሱስ ገብረ ሚካኤል በዚህ ጉዳይ ላይ አስተያየት መስጠት እንደማይፈልጉ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ 

 

የሱዳን ፕሬዚደንት ኦማር ሃሳን አልባሽር ደቡብ አፍሪቃን በጎበኙበት ወቅት ዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት እንዳዘዘዉ ቁጥጥር ስር ያለማዋልዋን የአገሪቱ ዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር አጥብቀዉ እየተከላከሉ ነዉ።

መስከረም ፳፭ (ኅያ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ጠ/ሚኒስትሩ ካላካተቱዋቸው የቀድሞ ሚኒስትሮች መካከል የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትሩ ሶፍያን አህመድ፣ የንግድ ሚኒስትሩ ከበደ ጫኔ፣ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ አለማየሁ ተገኑ፣ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሩ አሚን አብዱልቃድር፣ የፕላን ኮምሽን ሚኒስትሩ አቶ መኮንን ማንያዘዋል ይገኙበታል፡፡ በተጨማሪም አቶ ሬድዋን ሁሴንን ከኮምኒኬሽን ሚኒስትርነት አንስተው የወጣቶችና ስፖርት ሚኒስትር ያደረጉዋቸው ሲሆን፣ የህዝበ ሙስሊሙን …

መስከረም ፳፭ (ኅያ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከአመት በላይ ለሆነ ጊዜ በውጥረት ውስጥ የምትገኘዋ የጋምቤላና የደቡብ አዋሳኝ ከተማ ቴፒ፣ ባለፈው አንድ ሳምንት ውስጥ ብቻ ሶስት ዜጎች ተገድለውባታል። ከሳምንት በፊት የፌደራል ፖሊስ አባላት አንድ ሰው ከገደሉ በሁዋላ፣ ማንነታቸው በውል የማይታወቁ ሰዎች በወሰዱት የአጸፋ እርምጃ ደግሞ ከቴፒ 7 ኪሜትር እርቀት ላይ በምትገኝ ቀበሌ ውስጥ የሚኖሩ …

መስከረም ፳፭ (ኅያ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በ2008 ዓ.ም በ መንግስት ያዘጋጀውን የፖለቲካ ስልጠና ለመሳተፍ ፈቃደኛ ያልሆኑ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ደሞዛቸው እንዳይከፈል በመታገዱ የምንበላውና የቤት ኪራይ የምንከፍለው አጥተናል ሲሉ ገልጸዋል።በስብሰባው ላይ የተገኙ መምህራን ደሞዝ ሲከፈላቸው በተለያዩ ምክንያቶች ያልተሰበሰቡት መምህራን ደግሞ ደሞዝ እንደማይከፈላቸው ተነግሯቸዋል። በአዋሳ ዩኒቨርስቲ መምህራን ወደ ውጭ እንዳይወጡ ታግደው ስልጠናውን በግድ …

መስከረም ፳፭ (ኅያ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በመስተዳድሩ 10 ክፍለ ከተሞችና 116 ወረዳዎች የሚገኙ የኢህአዴግ ካድሬዎች የሹም ሽር እና የሹመት ቦታ ለውጥ መረጃዎች የታወቁ ሲሆን፣ የማዕከል መ/ቤት ቢሮዎችና ሹም ሽር ድልደላ በዚህ ሳምንት የሚጠናቀቅ ሆኖ፣ በወረዳዎችና ክፍለ ከተሞች አጠቃላይ ቁጥራቸው ከ800 የማያንሱ አመራሮች በሙስና፣ከድርጅቱ ጋር ባላቸው ተቃርኖ፣ በአመራር ብቃት ማነስ እንዲሁም በትምህርት ደረጃ …

መስከረም ፳፭ (ኅያ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአማራ ክልል መንገድ ስራ መስሪያ ቤት ውስጥ የሚታዩ በርካታ የአሰራር ችግሮች ለከፍተኛ ሙስና ሊያጋልጡ እንደሚችሉ በመናገር በየጊዜው እንዲስተካከሉ ሰራተኛው ቢጠየቅም፣ ከዓመት ዓመት አለመቀረፋቸው በስርዓቱና አመራሮች እምነት እንዲያጡ እንዳደደረጋቸው የኦዲት ባለሙያዎች በዓመታዊው የሰራተኞች ስብሰባ ላይ ገልጸዋል፡፡ በባለስልጣኑ መስሪያ ቤት ስር በሚገኙ ልዩ ልዩ ፕሮጀክቶች በተደረገ አጠቃላይ ምርመራ …

መስከረም ፳፭ (ኅያ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የዩኒቨርሳል ቲቪ ጋዜጠኞች የታሰሩት፣ ሁለት የፓርላማ አባላትን ጋብዘው የኢትዮጵያ ጦር በአገሪቱ ውስጥ መቆየት አለበት የለበትም የሚል ክርክር በማድረጋቸው መሆኑን የጣቢያው የዜና ክፍል ሃላፊ የሆነው ጋዜጠኛ አብዱላዚዝ ኢብራሂም ሙሃመድ ተናግሯል። በርካታ የሶማሊያ ዜጎች የኢትዮጵያ ጦር በሶማሊያ መቆየቱን መቃወም ጀምረዋል። ሟቹ ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ አልሸባብን በ2 ሳምንታት ውስጥ …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

የኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ያቀረቡትን የአዲሱ ካቢኔ አባላትን ሹመት አፀደቀ። ዛሬ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስቴር አቶ ሐይለማርያም ደሳለኝ ካቢኔያቸውን ሲያሳውቁ አብዛኞቹ የመንግስት ባለስልጣናት በነበሩበት ሲቀጥሉ ጥቂት ለውጦች ደግሞ በሹመኞቹ ዘንድ ታይተዋል።

መስከረም ፳፬ (ኅያ አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራንና ሰራተኞች ላይ ከኢሕአዴግ መንግስት የሚሰነዘረው የፖለቲካ ጠልቃ ገብነትና አፈና ከመቼውም ጊዜ የከፋ ደረጃ ላይ መድረሱን የአዋሳ ዩኒቨርሲቲ መምህራን በምሬት ተናግረዋል። የኢሕአዴግ መንግስት “ስልጠና’ በሚል ስም በአገር-አቀፍ ደረጃ ካዘጋጃቸው ስብሰባዎች አንዱ በሆነው ሰብሰባ ጠቅላላውን የአዋሳ ዩኒቨርሲቲ መምህራንና ሰራተኞች ከሰኞ መስከረም 10 እስከ …