መስከረም ፳፬ (ኅያ አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መንግስት እና አለማቀፍ የእርዳታ ድርጅቶች በኢትዮጵያ 4 ሚሊዮን 500 ሺ ህዝብ በረሃብ መጠቃታቸውን ይፋ ቢያደርጉም፣ በከተሞች የምግብ እጥረት ያጋጠማቸው ዜጎች ቁጥር ሲጨመር አጠቃላይ የተረጅዎችን ቁጥር ከ8 ሚሊዮን በላይ ሊያደርሰው እንደሚችል መረጃዎች አመልክተዋል። በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ሪፖርት ሲደረግ የቆየው በገጠሩ የሚታየው ችግር ብቻ ነው። ይሁን እንጅ የከተማና …

መስከረም ፳፬ (ኅያ አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የደቡብና የጋምቤላ አዋሳኝ በሆነቸው ቴፒ ከተማ በየጊዜው የሚታየው የጸጥታ ችግር ሰሞኑን እንደገና አገርሽቶበታል። የአካባቢው ነዋሪዎች እንደሚሉት ካለፈው አመት ጀምሮ ከፍ ዝቅ እያለ ሲካሄድ የነበረው ግጭት ተባብሶ የቀጠለ ሲሆን፣ በህዝብና በመንግስት መካከል ያለው ልዩነትም ሰፍቷል። መስከረም 20 ብርሃኑ የተባለ የዩኒቨርስቲ ጥበቃ የተገደለ ሲሆን፣ ለግድያው እስካሁን ሃላፊነቱን የወሰደ …

መስከረም ፳፬ (ኅያ አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦሮምያ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞን በጉንዶ መስቀል ከተማ በሶስት ቀበሌዎች የሚገኙ ከ1 200 በላይ ቤቶች እንዲፈርሱ መወሰኑን ተከትሎ በከተማው ውጥረት ነግሷል። የከተማው ባለስልጣናት ህዝቡን ሰብስበው ቤቶቻችሁን አፍርሱ ብለው ትእዛዝ ሲሰጡ፣ ነዋሪዎቹ ግን አጥብቀው ተቃውመዋል። መስከረም 13 ቀን በከተማው የተካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ በፌደራል ፖሊሶች ቢጨናገፍም፣ ውጥረቱ አሁንም …

መስከረም ፳፬ (ኅያ አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዛሬ ጠዋት በሳሸመኔ ተክለሃይማኖት ቤ/ክርስቲያን መቅደስ ውስጥ ካህናትና ዲያቆናት እርስ በርስ በመደባደባቸው ሰዎች ተገድተዋል። የግጭቱ መንስኤ የቆየ መሆኑን የሚናገሩት ምእመናኑ ዛሬ የተፈጠረው ድርጊት ግን ያልተጠበቀ ነው። ካህናቱ ጎራ ለይተው መደባደባቸውን ተከትሎ አካባቢው በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሎአል። ኢሳት ከገለልተኛ ወገን ለማጣራት ባይችልም፣ በሰአቱ የተኩስ ድምጽም ተሰምቷል። ጥይቱን …

መስከረም ፳፬ (ኅያ አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በውጭ የሚገኙ የኢትዮጵያ ነጻ-ፕሬስ ጋዜጠኞች “መልካም ስም ከመቃብር በላይ ዘላለማዊ ሆኖ ይኖራል” በሚል ርዕስ ባወጡት መግለጫ፣ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት እንዲረጋገጥ፤ ብሎም ለአዲሱ የፕሬስ ትውልድ ፈር ቀዳጅ የነበረው ጋዜጠኛ ሙሉጌታ ሉሌ ከዚህ አለም በሞት መለየቱ ለብዙዎች የኢትዮጵያ ነጻ-ፕሬስ ጋዜጠኞች እና ቤተሰቦች መሪር ሃዘን ነው ብለዋል። ጋዜጠኛ …

አንጋፋዉ ጋዜጠኛና ደራሲ ሙሉጌታ ሉሌ በ79ዓመቱ ትናንት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል። የቅርብ ጓደኞቹ የብዕር አርበኛ እያሉ የሚያወድሱት ጋዜጠኛ ሙሉጌታ በብዙዎች ዘንድ ፀጋዬ ገብረመድህን አርአያ በሚል የብዕር ስምም ይታወቃል።

ጤፍን ጨምሮ ነባር ዝርያዎች አደጋ እንደተጋረጠባቸው በጥናት ተረጋገጠ

ዝርያዎችን ለመታደግ አገር አቀፍ ፓኬጅ ተዘጋጅቷል

ጤፍን ጨምሮ በአርሶ አደሩ ዕጅ የሚገኙት የስንዴ፣ የገብስ፣ የዳጉሳና የሌሎች አዝርዕት ነባር ዝርያዎች አደጋ ተጋርጦባቸዋል ተባለ፡፡ ከተሻሻሉ ዝርያዎች አኳያ ያላቸውን የተሻለ ምርታማነት ከግምት ባለማስገባት በተሻሻሉና በድብልቅ

ዝርያዎች ለመተካት በሚደረገው ሙከራ ሳቢያ፣ የነባሮቹ ዝርያዎች ህልውና አደጋ ላይ መውደቁን በጥናት መረጋገጡን፣ የኢትዮጵያና የዓለም አቀፍ የብዝኃ ሕይወት ተቋማት ገልጸዋል፡፡

በተለይ በጤፍና በስንዴ ላይ በተደረጉ ጥናቶች በተፈጥሮ ይዞታቸው የሚታወቁት ነባር የአርሶ አደሩ ዝርያዎች፣ በሳይንሳዊ መንገድ ተዳቅለው ‹‹የተሻሻለ ዝርያ›› ተብለው የሚሰራጩት በምርታማነታቸውና በተስማሚነታቸው ውጤታማ መሆናቸውን የሁለቱ ተቋማት ኃላፊዎችና ተመራማሪዎች መስከረም 20 ቀን 2008 ዓ.ም. በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስረድተዋል፡፡

በኢሊሊ ኢንተርናሽናል ሆቴል በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ የኢትዮጵያ ብዝኃ ሕይወት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ገመዶ ዳቤ፣ ‹‹በተደጋጋሚ እንደሚነሳው የእኛ ያልሆኑ ዝርያዎች ምርታማ አይደሉም ሲባል ቆይቷል፡፡ ነገር ግን ከዓለም አቀፉ የብዝኃ ሕይወት ተቋም ጋር በጋራና በተናጠል ባደረግናቸው ጥናቶች ለአገር በቀል ዝርያዎች የተሰጠው ግምት የተሳሳተ እንደሆነ ከመረጋገጡም ባሻገር፣ በዘመናዊና በሳይንሳዊ መንገድ ተሻሽለው ተዘጋጁ ከሚባሉት የተሻለ ምርታማነት እንዳላቸው ተረጋግጧል፤›› ሲሉ ገልጸዋል፡፡

ዋና ዳይሬክተሩ አያይዘውም፣ ‹‹በእጃችን ያለውን እምቅ ኃይል ሳንጠቀም ከውጭ በመጡ ዝርያዎች ላይ ትኩረት ለማድረግ በመሞከራችን የራሳችንን አገር በቀል ዝርያዎች አደጋ ውስጥ እየጣልናቸው ነው፤›› በማለት ሥጋታቸውን ተናግረዋል፡፡

በተቋሙ ተባባሪ ተመራማሪ የሆኑት አቶ ፋንታሁን ባሳዝነው በበኩላቸው፣ ምንም እንኳ ኢትዮጵያ ጤፍን ለዓለም ያበረከተችና ጤፍም ከ4,000 ዓመታት በላይ ያስቆጠረ ታሪክ ቢኖረውም፣ በአገሪቱ ከስንዴና ከገብስ በፊት ምርምር ማድረግ ቢጀመርም፣ በአሁኑ ወቅት በተሻሻሉ ዝርያዎችና በሌሎችም ምክንያት ጤፍ አደጋ ተደቅኖበታል በማለት፣ ወደፊት ሊጠፋ ይችላል የሚለውን ሥጋት አጠናክረዋል፡፡

‹‹ይህ ዝርያ (ነባሩ ጤፍ) ከባህር ወለል በታች ከ3,000 እስከ 1,500 ሜትር ከፍ ሲልም እስከ 1,700 ሜትር፣ በአገራችን መመረት ይችላል፡፡ እንዲሁም በአገራችን አርሶ አደሮች ዕጅ ያለው የጤፍ ዝርያ በምርታማነቱ የበላይነት ከፍ ያለ ቢሆንም፣ አሁን አሁን ግን በተሻሻሉ ዝርያዎችና በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ ነባር ዝርያዎች ከፍተኛ አደጋ መጥቶባቸዋል፤›› በማለት ተባባሪ ተመራማሪው አስጠንቅቀዋል፡፡

በኢትዮጵያ ብዝኃ ሕይወት ኢንስቲትዩት ከ5,900 በላይ የጤፍ ዝርያ ናሙናዎች ተሰብስበው በኢትዮጵያ ዘረመል ባንክ ውስጥ እየተጠበቁ ሲሆን፣ በዚህ ሰብል ዝርያ ላይ የሚደረገው ናሙና የማሰባሰብና የባህርይ ትንተና ሥራ በግብርና ሳይንስ ምርምር ከ1950ዎቹ መጨረሻ አንስቶ ነበር የተጀመረው፡፡

እንደ ኃላፊዎቹ ከሆነ የባህርይ ትንተና አካል የሆነው ምርምር በ2006 እና በ2007 ዓ.ም. ተካሄዶ ነበር፡፡ ምርምሩም 12 የአርሶ አደር ዝርያዎችና ቁንጮ ተብሎ የሚታወቀውን ጤፍ ጨምሮ ሦስት አዳዲስ ዝርያዎችን (የተሻሻሉ ዝርያዎች) ያካተተ ሲሆን፣ በምንጃር ሸንኮራ ወረዳና በሌሎች አራት ወረዳዎች ውስጥ በሚገኙ የአርሶ አደር ማዕከላት ውስጥ የምርምር ሥራዎች መከናወናቸው ተነግሯል፡፡

በምርምር ሥራው የተገኙትን ውጤቶች ይፋ ያደረጉት አቶ ፋንታሁን፣ ‹‹ለማወዳደሪያነት በተረመጡት የተሻሻሉ ዝርያዎችና በአርሶ አደር ዝርያዎች መካከል መመዘኛ በተደረጉት ከመድረሻ ቀን፣ ከእህል ምርት፣ ከቁመት፣ ከዛላ እርዝመት አንፃር ሲታይ በስታትስቲክሳዊ ሥሌት መሠረት ልዩነት እንደሌላቸው ታይቷል፤›› ብለዋል፡፡

ምንም እንኳ የተለቀቁት የተሻሻሉ ዝርያዎች የተሻለ የምርት መጠን እንደሚኖራቸው በስፋት የሚታመን ቢሆንም፣ በተጠቀሱት የናሙና ውጤቶችና በስታትስቲክሳዊ ሥሌቶች መሠረት የአርሶ አደሩ ነባር ዝርያዎች የተሻለ ምርት እንደሚሰጡ መረጋገጡን ጠቁመዋል፡፡

ለአብነት ያህል ቁንጮ በሚባለው የተሻሻለ የጤፍ ዝርያና በነባሩ ዝርያ ላይ በአራት አካባቢዎች በተካሄደ ጥናት መሠረት፣ ነባሩ ዝርያ በሔክታር 22 ኩንታል ምርት ሲሰጥ ቁንጮ ግን 21 ኩንታል ብቻ መስጠቱን በአስረጅነት ጠቅሰዋል፡፡

እንደ ጤፍ ሁሉ በሌሎችም የአዝርዕት ዓይነቶች ላይ ተመሳሳይ ውጤት መታየቱን የሚገልጹት የተቋሙ ተመራማሪዎችና ኃላፊዎች፣ አገር በቀል ዝርያዎች ትኩረት እንደሚያስፈልጋቸውና የተለየ የአመራረት ፓኬጅም ተግባራዊ መደረግ እንደለበት አሳስበዋል፡፡

ዓለም አቀፉ የብዝኃ ሕይወት ተቋም በበኩሉ በአማራና በትግራይ ክልሎች ውስጥ በሚገኙ ሥፍራዎች በስንዴና በዳጉሳ ላይ ባካሄዳቸው የናሙና ጥናቶች፣ ከውጭ ከሚገቡትም ሆነ ከተዳቀሉት የተሻሻሉ ዝርያዎች አኳያ በሚሰጡት የምርት መጠንና በጥራት አገር በቀሎቹ ነባር ዝርያዎች የተሻሉ መሆናቸውን ማረጋገጡን ይፋ አድርጓል፡፡

በኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ ብዝኃ ሕይወት ተቋም ተጠሪ ካርሎ ፋዳ፣ ስኮላ ሳንታ አና ከተባለው የጣሊያን ዩኒቨርሲቲ ጋር በጥምር በተካሄደ ጥናት፣ በአርሶ አደሩ ዕጅ የሚገኙትና ለማካሮኒና ለፓስታ ማምረቻ የሚያገለግሉ ስንዴዎች (ዱረም) በተፈጥሮ ካላቸው የዝርያ ተያያዥነትም ሆነ ዘረመል አወቃቀር አንፃር፣ ለገበሬው ከተሰራጩ የተሻሻሉ ዝርያዎች (Mediterranean Group)  ከሚባሉት በእጅጉ የተሻለ ምርታማነት እንደሚታይባቸው አስረድተዋል፡፡ 

አደጋ ተደቅኖባቸዋል የተባሉ ዝርያዎችንና ሌሎች በይፋ ያልተለዩ አገር በቀል ዝርያዎችን በተሻለ መንገድ ለመጠቀምና ‹‹ከመዋጥ ሥጋት›› ለማዳን፣ የተለየ ፓኬጅ  በመዘጋጀቱ ተግባራዊ መደረግ እንዳለበት ዋና ዳይሬክተሩ ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡

ረዘም ላሉ ዓመታት ከአገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት ጋር በተያያዘ መንግሥት ለግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ ትኩረት መስጠቱን፣ ባለሙያዎች በተደጋጋሚ ሲገልጹ ተደምጠዋል፡፡ በተለይ ለምርትና ለምርታማነት ዕድገት ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ እያፈሰሰ መሆኑን የሚገልጸው መንግሥት፣ በግብርና ምርምር አቅምና በቴክኖሎጂ መስክ ዕድገት እየተመዘገበ መምጣቱን ደጋግሞ ሲናገር መቆየቱ ይታወሳል፡፡ የምርምር ማዕከላትን በመላ አገሪቱ እየተስፋፉ በመምጣታቸው በተሻሻሉ ዝርያዎች የተሻለ ውጤትና ተስፋ እየታየ እንደሆነ ይነገራል፡፡ የአሁኑ የጥናት ውጤት ግን ጥያቄን አጭሯል፡፡ በተለይ ባለፉት ዓመታት መንግሥት የግብርና ምርምር ተቋማት እንዲስፋፉና የነባሮችንም አቅም በማሳደግ በግብርና ምርት ዕድገት መታየቱን ይገልጻል፡፡ ነገር ግን በዘርፉ የተሰማሩ ተመራማሪዎች፣ የእስከዛሬው ጥረት አሁን ይፋ ከወጣው የጥናት ውጤት አኳያ ሲታይ የቀድሞዎቹ ኢንቨስትመንቶችና ጥረቶች ተገቢነት ላይ ትልቅ ጥርጣሬ ያሳደረ መሆኑን እየተናገሩ ነው፡፡

 

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ሙስና በአዲስ አበባ በኔትወርክ በመያያዙ ከኢሕአዴግ በስተቀር የሚፈታው እንደሌለ ተነገረ

ተመዘገበ የተባለው የባለሥልጣናት ሀብት ይፋ እንዲደረግ ተጠየቀ 

‹‹በየስብሰባው እየተወዳደሱና በጭብጨባ እየተደጋገፉ መለያየት ይቁም›› የፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን

ሙስና፣ ኪራይ ሰብሳቢነትና የመልካም አስተዳደር እጦት ከወረዳ እስከ ከተማ አስተዳደሩ ድረስ በኔትወርክ የተያያዙ በመሆናቸው ሊፈታቸውም ሆነ ሊያስቆማቸው የሚችለው ‹‹ድርጅቱ›› ኢሕአዴግ ብቻ መሆኑ ተጠቆመ፡፡ 

የፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን መስከረም 20 ቀን 2008 ዓ.ም. በግዮን ሆቴል ለግማሽ ቀን አዘጋጅቶት በነበረው የውይይት መድረክ ላይ ከተለያዩ የመንግሥትና የግል ተቋማት፣ የሁሉም ክፍላተ ከተሞች፣ ወረዳዎች ተወካዮችና ባለድርሻ አካላት ተገኝተው ነበር፡፡ ተሳታፊዎቹ እንደተናገሩት የመልካም አስተዳደር እጦት፣ ሙስናና ኪራይ ሰብሳቢነት በተለይ በአዲስ አበባ ከተማ በከፍተኛ ሁኔታ ተባብሶ ቀጥሏል፡፡ 

በመጠናቀቅ ላይ ካለው መስከረም ወር አጋማሽ ጀምሮ በሁሉም ክፍላተ ከተሞች ሊባል በሚችል ሁኔታ ከግንባታ፣ ከመሬትና ቤቶች ጋር በተገናኘ ነዋሪዎች እያለቀሱ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ የመድረኩ ተሳታፊዎች በተለይ በአዲሱ የሥራ ዘመን ከኃላፊነታቸው እንደሚነሱ ያወቁ፣ የጠረጠሩና ሹክሹክታ የሰሙ የክፍላተ ከተሞችና የወረዳዎች ተሿሚዎች ‹‹የሚፈርስ የማይፈርስ፣ መንገድ የሚወጣበት የማይወጣበት፣ ክርክር ያለበት የሌለበት፣ ግንባታ የተፈቀደለት ያልተፈቀደለት…›› በማለት በሥራ ሰዓትና ከሥራ ውጪ የነዋሪዎችን ግድግዳና የውጭ በር ቀለም ሲቀቡ እንደሚውሉ ጠቁመዋል፡፡ ያለምንም ማስጠንቀቂያ የሚያደርጉት እንቅስቃሴ ኅብረተሰቡን ሰላም እየነሳው በመሆኑ፣ የአስተዳደሩና የመንግሥት ከፍተኛ ኃላፊዎች ትኩረት ሰጥተው ሊያስቆሟቸው ወይም ዕርምጃ ሊወስዱባቸው እንደሚገባ ተሳታፊዎቹ አሳስበዋል፡፡ 

በመቐለ ከተማ በተደረገው የገዢው ፓርቲ ኢሕአዴግ አሥረኛ ጉባዔ በመጀመሪያው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን በተለያዩ የሥራ ዘርፎች ጥሩ ሥራ መሠራቱ የተገለጸ ቢሆንም፣ በመልካም አስተዳደር በኩል ግን ከፍተኛ ችግር እንደነበር መታመኑንና ፓርቲው ‹‹ተጠያቂ ነኝ ማለቱን››፣ የፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ዓሊ ሱሌይማን ለተሳታፊዎች አስታውሰዋል፡፡ በመቀጠልም ይህንን ምቹ ሁኔታ ሕዝቡ መጠቀም ስላለበት ከመንግሥት ጎን በመቆም ብልሹ አሠራርን፣ ሙስናንና ሌሎች ለሕዝቡም ሆነ ለአገር የማይጠቅሙ አሠራሮችንና ድርጊቶችን ማጋለጥ እንዳለበት ተናግረዋል፡፡ 

በየስብሰባው በመወዳደስና በጭብጨባ በመደጋገፍ መንቀሳቀስ መቆም እንዳለበትና ሕዝብ ያስቀመጠው ኃላፊ ለሕዝብ ማገልገል እንዳለበት መንገር ያለበት ኅብረተሰቡ መሆኑን የገለጹት ኮሚሽነሩ፣ በየስብሰባው የጉንጭ ጅምናስቲክ ሠርቶ መለያየትን ቆም አድርጎ ባለሥልጣኑ የሚጓዝበት ተሽከርካሪ፣ የሚኖርበትና የሚከፈለው ደመወዝ ሕዝቡ በሚከፍለው ታክስ መሆኑን በመግለጽ፣ በአግባቡ እንዲያገለግለው መናገር እንዳለበት አስታውቀዋል፡፡ 

የኮሚሽነሩን ማብራሪያ ተከትሎ የመድረኩ ተሳታፊዎች እንደገለጹት፣ ኮሚሽኑ የመንግሥት ተሿሚዎች የሕዝብ ሀብት በሙስናና በኪራይ ሰብሳቢነት እንዳይበዘብዙና መልካም አስተዳደር እንዲሰፍን በማለት የሕዝብ ተሿሚዎች ሀብታቸውን እንዲያስመዘግቡ ማድረጉ ትልቅ ነገር ነበር፡፡ ነገር ግን በብዙ ሺሕ የሚቆጠሩ የመንግሥት ተሿሚዎች መመዝገባቸው ከመገለጹ ውጪ ለሕዝቡ ይፋ አልተደረገም፡፡ ተመዝግቦ በድብቅ መያዙ ትርጉም ስለሌለው የትኛው ባለሥልጣን ምን ያህል ሀብት እንዳስመዘገበ ለሕዝብ ይፋ መደረግ እንዳለበት ተናግረዋል፡፡ ለሕዝብ ይፋ መደረጉ ሕዝቡ የሚያውቀውን ያህል ማስመዝገቡንና ያላስመዘገበም ከሆነ ተጨማሪ መረጃ በመስጠት እውነቱ ላይ እንዲደርስ እንደሚረዳ ተሳታፊዎች አውስተዋል፡፡ 

ሀብታቸውን ያስመዘገቡ ባለሀብቶች ይፋ እንዲደረጉ በተነሳው ጥያቄ ላይ ምላሽ የሰጡት ኮሚሽነር ዓሊ፣ መሥሪያ ቤታቸው ለማንም ክፍት መሆኑንና ማንም መጥቶ የሚፈልገውን ማስረጃ ማግኘት እንደሚችል ተናግረዋል፡፡ መረጃ የሚፈልግ ማንኛውም ዜጋ ደብዳቤ ጽፎ፣ ‹‹የእከሌን ባለሥልጣን ሀብት ማወቅ እፈልጋለሁ?›› ካለ ወዲያውኑ እንደሚገለጽለት ተናግረው፣ በመገናኛ ብዙኃን ግን ‹‹የእከሌ ባለሥልጣን ሀብት ይህንን ያህል ነው፤›› ብሎ ይፋ ማድረግ ከሕግ አንፃርም እንደሚያስኬድና ነውር መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡ በዓለም ደረጃም ከሲንጋፖር በስተቀር የሁሉንም ዜጎች ሀብት መዝግቦ ይፋ ያደረገ አገር አለመኖሩን አክለዋል፡፡ በቅርቡ በኮሚሽኑ ድረ ገጽ በኢሜይል መጠየቅና መረጃ ማግኘት እንደሚቻልም ጠቁመዋል፡፡ 

የመድረኩ ተሳታፊዎች በርካታ አስተያየቶችንና ጥያቄዎችን ያነሱ ሲሆን፣ በተለይ በሙስና ተጠርጥረው ስለሚታሰሩና ስለሚፈረድባቸው ተከሳሾች ተናግረዋል፡፡ አንድ በሙስና የተጠረጠረ ሰው በርካታ ገንዘብ በሙስና ካገኘ በኋላ ዘመዶቹ ዘንድ በታትኖ በማስቀመጥ፣ ሲፈተሽ የሚገኝበት ጥፋት በጣም ትንሽ ስለሚሆን የተወሰነ ዓመት ታስሮ እንደሚፈታ ገልጸዋል፡፡ 

ከእስር እንደተፈታ ለተወሰኑ ወራት ቀድሞ ከሚኖርበት አካባቢ በመልቀቅ ከቆየ በኋላ አስመጪና ላኪ ሆኖ እንደሚታይ የገለጹት ተሳታፊዎቹ፣ ይህንን የሚያዩ ተሿሚዎች የተወሰኑ ዓመታት ታስረው ለራሳቸውና ለቤተሰባቸው እንደሚተርፉ ራሳቸውን በማሳመን ከፍተኛ የሆነ የሕዝብ ሀብትን እየበዘበዙ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ይህንን ተግባር የሚመለከተው አካል ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ዕርምጃ ሊወስድበት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ 

ሙስናን የሚፀየፍ ትውልድ ለመፍጠር ትምህርቱ ከአምስት ዓመት ሕፃን እንዲጀምር በኮሚሽኑ የቀረበውን ሐሳብ የውይይቱ ተሳታፊዎች ድጋፍ ሰጥተውታል፡፡ 

በመቐለው ጉባዔ የተደረገው ስምምነት እንዳለ ሳይቀነስ ወደ ታች መውረድ እንዳለበት ያሳሰቡት የውይይቱ ተካፋዮች፣ በተለይ ከፍተኛ የመልካም አስተዳደር ዕጦት በሚታይባቸው ግብር አስከፋይና ንግድ ፈቃድ አዳሽ መሥሪያ ቤቶች የማይተገበር መመርያ እያወጡ የንግዱን ኅብረተሰብ ሳይወድ በግድ ወደ ሙስና እንዲገባ የሚያደርጉበት አሠራር ትኩረት እንዲሰጥበት ጠይቀዋል፡፡ የመልካም አስተዳደርና የፍትሕ ዕጦት ቢስተካከል ለውጥ ሊመጣ እንደሚችልም አክለዋል፡፡ 

‹‹ድርጅቱ ይታማል›› ያሉ አንድ አስተያየት ሰጪ፣ ተሿሚው እንክት አድርጎ ከበላ በኋላ እሮሮ ሲበዛበት ከነበረበት ቦታ ወይም ክፍለ ከተማ ተነስቶ ወደ ሌላ ክፍለ ከተማ ወይም ማዘጋጃ ቤት እንደሚሾም ገልጸው፣ ‹‹እርስዎ (አቶ ዓሊን) ለድርጅቱ ቅርብ ስለሆኑ ቢወያዩበትና መፍትሔ እንዲመጣ ቢያደርጉ የተሻለ ነው፤›› ማለታቸው የስብሰባውን ተሳታፊዎች አስፈግጓል፡፡ ከድርጅቱ ውጪ ማንም ሊፈታው እንደማይችልም አክለዋል፡፡ የብሔር ብሔረሰቦችን ችግር የሚፈታ መንግሥት እንዴት የሙስናን ችግር መፍታት እንዳቃተው እንዳልገባቸውም ተናግረዋል፡፡ 

ገዢው ፓርቲ ብቻውን የሚያደርገው ነገር እንደሌለ የገለጹት አቶ ዓሊ፣ የኅብረተሰቡ ተሳትፎ አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡ በእርግጥ አንዳንድ ድርጊቶችን ማስፈጸም እንዳልተቻለ የገለጹት አቶ ዓሊ፣ የማይገባ ድርጊት መፈጸሙ እየታወቀ ዞር ተደርጎ በከፍተኛ ደረጃ የሚሾም ተሿሚ መኖሩንም ጠቁመዋል፡፡ 

 

በአዲስ አበባ ለሁለተኛ ጊዜ በተሰናዳው የአፍሪካ ሆቴል ኢንቨስትመንት ፎረም ላይ የታደሙት የሒልተንና የሸራተን ኃላፊዎች፣ መንግሥት በቅርቡ መተግበር በጀመረው የሆቴሎች ደረጃ አሰጣጥ አለመደሰታቸውን ገለጹ፡፡ 

በሒልተን ዓለም አቀፍ የአውሮፓና የአፍሪካ ልማት ዘርፍ ከፍተኛ ምክትል ፕሬዚዳንት ፓትሪክ ፊትዝጊቦን ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ስለሚገኘው የሆቴሎች ደረጃ አሰጣጥ ተጠይቀዋል፡፡ ሒልተን አዲስ አበባ የአራት ኮከብ ደረጃ ማግኘቱን ተከትሎ ቅሬታቸውን ካቀረቡ 11 ባለኮከብ ሆቴሎች ውስጥ አንዱ እንደነበር ይታወሳል፡፡ ምክትል ፕሬዚዳንቱ ምንም እንኳ በደረጃ አሰጣጡ ሒደትና በሒልተን ውጤት ላይ አስተያየት ከመስጠት ቢጠነቀቁም፣ ደረጃ መዳቢዎች ከሚያወጡት የኮከብ ደረጃ ይልቅ የሒልተንን ማምነት የሚገልጸው ደንበኞች ከሒልተን የሚጠብቁት አገልግሎት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ የሒልተን ብራንድ ከሚሰጠው የኮከብ ደረጃ ይልቅ በደንበኞቹ ይታወቃል ያሉት ፊትዝጊቦን፣ በተዘዋዋሪ ከመናገር ውጪ በቀጥታ ቅሬታቸውን ከመግለጽ ተቆጥበዋል፡፡ 

በሌላ በኩል ሸራተን አዲስ ሆቴልን የሚያስተዳድረው ስታርውድ  ሆቴሎችና ሪዞርቶች ዓለም አቀፍ ኩባንያ ምክትል ፕሬዚዳንትና የአፍሪካና የህንድ ውቅያኖስ የቀጣናው የኦፕሬሽን ዘርፍ ዳይሬክተር ሐሳን አህዳብም ከሪፖርተር ስለደረጃ አሰጣጡ ተጠይቀው ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ እንደ አህዳብ አባባል በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ብቻም ሳይሆን በተለያዩ አገሮች ያሉ ደረጃ አውጪዎች ሊገነዘቡት የሚገባው የሆቴል ደረጃ አሰጣጥ ‹‹ጊዜው ያለፈበት›› ሥርዓት መሆኑን ነው፡፡ ሆቴሎች ባላቸው የብራንድና የቄንጠኝነት ደረጃ መመደብ አለባቸው የሚሉት አህዳብ፣ ከደረጃ አሰጣጥ ይልቅ በብራንድ ላይ መተኮር እንዳለበት አሳስበዋል፡፡ በየጊዜው እየተቀየረ ባለው የሰዎች አኗኗር ሳቢያ የኮከብ ደረጃ ሆቴሎችን ገላጭ ሆኖ እንዳላገኙት በመጥቀስ፣ ሸራተን ባለአምስት ኮከብ ከመባል ይልቅ ‹‹ለግዠሪ ኮሌክሽን›› በሚለው ደረጃው በደንበኞቹ ዘንድ እንደሚታወቅ፣ ይኸው ብራንድም መገለጫው እንደሆነ በመግለጽ የኮከብ ደረጃ አሰጣጥን አጣጥለውታል፡፡ 

የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር የሆቴሎች ደረጃ አሰጣጥን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ተቋማት ከሆኑት መካከል ከዓለም የቱሪዝም ድርጅት ባለሙያዎች ጋር በመሆን በኢትዮጵያ ባስተዋወቀው የደረጃ አሰጣጥ ሥርዓት መሠረት፣ እስካሁን መግለጫ የተሰጠባቸው 95 ባለኮከብ ሆቴሎች በአዲስ አበባ ተመዝነው ውጤት ቢነገራቸውም እነማን እንደሆኑ ለሕዝብ ይፋ ከማድረግ ግን ሚኒስቴሩ ተቆጥቦ ቆይቷል፡፡ የአዲስ አበባ ሆቴሎች ደረጃ አሰጣጥን ካጠናቀቀ በኋላ ለቀረቡለት ቅሬታዎች ምላሽ በመስጠት የደረጃ አሰጣጡ ያካተታቸው ሆቴሎችና ያገኙትን ደረጃ ይፋ እንደሚያደርግ ቢያስታውቅም እስካሁን ዝምታን መርጧል፡፡ ይሁንና ባለአምስት ኮከብ ደረጃ ያገኙት ሸራተን፣ ኢሊሊ ኢንተርናሽናል እንዲሁም ካፒታል ሆቴልና ስፓ ናቸው፡፡ ከእነዚህ ውጪ የተቀሩት ሆቴሎች ከአራት እስከ አንድ ኮከብ ባለው ደረጃ የተመደቡ ናቸው፡፡ 

ሒልተን ኢንተርናሽናል ሁለተኛውን ሆቴል በሐዋሳ ለማስተዳደር ከሰንሻይ ቢዝነስ ጋር በተዋዋለበት ሳምንት፣ ሸራተንን የሚያስተዳድረው ስታርውድ በበኩሉ በአፍሪካ 20 የሆቴል ፕሮጀክቶች ላይ እየሠራ መሆኑንና ከእነዚህ ውስጥ ሰባቱን በተለያዩ የአፍሪካ አገሮች ይፋ አድርጓል፡፡ ይሁንና በኢትዮጵያ ምንም ይፋ የሚያደርገው የሆቴል ፕሮጀክት እንደሌለ የስታርውድ የአፍሪካና የህንድ ውቅያኖሶች ቀጣና ልማት ከፍተኛ ምክትል ፕሬዚዳንት ኔል ጆርጅ አስታውቀዋል፡፡ 

አህዳብ በበኩላቸው ሸራተን አዲስን ከጥንስሱ ጀምሮ ሲያተዳድሩ ቆይተው በቅርቡ ያረፉት ዣን ፔዬር ማኒጎፍ በምክትላቸው ተተክተው ሆቴሉን የማስተዳደር ኃላፊነት እንደተረከቡና ሆቴሉ ይሰጣቸው የነበሩ አገልግሎቶችም ሳይስተጓጎሉ መቀጠላቸውን ከሪፖርተር ተጠይቀው አብራርተዋል፡፡ በሟቹ ማኒጎፍ አስተዳደር ጊዜ ከሠራተኞች ጋር የነበረውን ግጭት በሚመለከትም ተጠይቀዋል፡፡ ሟቹ በነበራቸው ሥራን በፍጥነት የመሥራት ፍላጎትና ችኮላ ይከሰቱ ከነበሩ ችግሮች ውጪ የጎላ ችግር እንዳልተፈጠረ ጠቅሰዋል፡፡ በአንፃሩ በተለያዩ ጊዜያት መብታቸውን በመጠየቃቸው ያለምንም ማስጠንቀቂያ ከሥራ ገበታቸው መሰናበታቸውን ሠራተኞች ሲገልጹና አስተዳደሩን ሲከሱ እንደነበር አይዘነጋም፡፡  

 

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

የአ/አበባ ጎልማሶችና ወጣቶች ማኅበራት ኅብረት ተቃውሞውን ያስተባብራል ለተቃውሞው፣ በሰባት ቀናት ከ100 ሺሕ በላይ የድጋፍ ፊርማዎች ተሰባሰቡ የጥቅምቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ እንዲወስንበት ለማድረግ ታቅዷል “በማስረጃ ተደግፎ የሚቀርብ ነገር ካለም እርምት እንወስዳለን” /የጣቢያው ሓላፊ/ (ምንጭ: አዲስ አድማስ፤ ቅጽ ፲፮ ቁጥር ፰፻፳፤ ቅዳሜ መስከረም ፳፪ ቀን ፳፻፰) በኢትዮጵያን ብሮድካስቲንግ ሰርቪስ (EBS) ቴሌቪዥን በሚተላለፉት “ታዖሎጐስ” እና “ቃለ ዐዋዲ” …


(ክፍል ሁለት)
1.   ተአምራት ማድረግ የምን ውጤት ነው? ተአምራት ማድረግ ከሁለት ነገሮች ሊመጣ ይችላል፡፡ ከመንፈሳዊ ብቃትና ከሰይጣን አሠራር፡፡ በክርስትና ሕይወቱ የበረታ ሰው መንፈሳዊ ብቃቱ በሕይወቱ በሚገለጡ ተአምራት ሊታወቅ ይችላል፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን የምናገኛቸው ቅዱሳን በገድል ተቀጥቅጠው፣ ሰማዕትነት ከፍለው፣ በመንፈሳዊ ሕይወታቸው በሚገባ ተጉዘው ዲያብሎስን ድል ሲነሡት በሕይወታቸው ውስጥ ተአምራት ይገለጣሉ፡፡ ይህም ማለት ተአምራት የመንፈሳዊ ብቃት መገለጫ ነው ማለት ነው፡፡ የተአምራት ስጦታ እንዲሁ በድንገት አይገለጥም፡፡ በዚያ ክርስቲያን ሕይወት ውስጥ እያደገ፣ እየተገለጠና እየተመሰከረለት በሚመጣ መንፈሳዊ ዕድገት ምክንያት እንጂ፡፡ ለዚህ ሁለት ምሳሌዎች እናንሣ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስና አቡነ ተክለ ሃይማኖት፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ በሐዋርያት ሥራ ውስጥ አራት ምዕራፍ ያለው መንፈሳዊ ዕድገቱ በየዘመናቱ ተገልጦልናል፡፡ በፍኖተ ደማስቆ መመለሱ(የሐዋ8)፤ በአንጾኪያ በሱባኤ መኖሩ(የሐዋ13)፣ ለአገልግሎት ተጠርቶ ከበርናባስ ጋር መውጣቱ እና ከአረማውያን፣ ከአይሁድና ከመናፍቃን ጋር ባደረገው ተጋድሎ የምናገኘው በትምህርትና በተአምራት የተገለጠ ሕይወቱ ናቸው፡፡ የቅዱስ ጳውሎስ ሕይወት ቀስ በቀስ እያደገ (ወየሐውር እም ኃይል ውስተ ኃይል እንዲል) የመጣ ነው፡፡

የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ሕይወት በመንፈሳዊ ትምህርት፣ በአካባቢያዊ ተጋድሎ፣ ገዳማትን በመሳለምና በመማር፣ ወንጌልን ለአረማውያን በማስተማር እየተገለጠ የመጣ የማያቋርጥ መንፈሳዊ ዕድገት የነበረው ነው፡፡ ክርስትና ደንገቴ ሊሆን አይችልም፡፡(ለ&

ካህናቱ እና ምእመናኑ ሀገረ ስብከቱን በሰልፍ ለመጠየቅ እየመከሩ ነው የአለቃው ጣልቃ ገብነት ሙዳየ ምጽዋቱ በወቅቱ እንዳይቆጠር አድርጓል “ሀገረ ስብከቱ ለቤተ ክርስቲያናችን ችግር ግድ እንደሌለው አሳይቶናል” /ምእመናኑ/ (ኢትዮ-ምኅዳር፤ ቅጽ 03 ቁጥር 121፤ ቅዳሜ መስከረም 22 ቀን 2008 ዓ.ም.) በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት፣ የደብረ ሲና እግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ አባላትና ምእመናን፤ ከአስተዳደርና ከአሠራር ጋር በተያያዙ …

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እና የግብጽ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በአፍሪካ አህጉር የሚገኙ ጥንታውያን እኅት አብያተ ክርስቲያናት ናቸው። የኹለቱ ግንኙነት ሃይማኖታዊ እና ተፈጥሯዊ ነው። ሃይማኖታዊ ትስስሩ ከኹለት ሺሕ ዓመት በላይ ዕድሜን ያስቆጠረ ነው። በተፈጥሮ ያለው ግንኙነት ደግሞ የዓባይ ወንዝ መፍሰስ ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ያለ ነው። ይኸው የሁለቱ እኅት አብያተ ክርስቲያናት ግንኙነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጎለበተ …

“መንግሥት ተቃዋሚዎችን አወያያለሁ
የሚለው ለፖለቲካ ፍጆታ ብቻ ነው”

አንድም ተቃዋሚ ፓርቲ ወይም የግል ተወካይ የማይኖርበት 5ኛው የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የፊታችን ሰኞ የሚመሰረት ሲሆን ም/ቤቱ አማራጭ የፖሊሲ ሃሳቦችና የሰሉ ትችቶች የማይደመጡበት እንደሚሆን ተቃዋሚዎች ገለፁ፡፡
በፓርላማው የተቃዋሚ ፓርቲ ድምፅ አለመኖር ህዝቡን ይጐዳል ያሉት የመድረክ ሊቀመንበር ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ፤ “ከዚህ ቀደም በፓርላማ በነበረን ጊዜ ያለመታከት የህዝብን ሰቆቃና እሮሮ ስናሰማ ነበር፤ አሁን ፓርላማው ከዚህ አይነቱ ጥያቄና አስተያየት ውጭ ነው” ብለዋል፡፡  በውጭም በሃገር ውስጥም ከማንኛውም መድረክ ይልቅ ተደማጭ የሚሆነው በፓርላማ የሚሰነዘር ሃሳብ ነው የሚሉት ፕ/ር በየነ፤ ይህ መድረክ አለመኖሩ ተቃዋሚው በሃገሩ ጉዳይ ያለውን ሃሳብ ህብረተሰቡ እንዳይረዳ እንቅፋት ይሆናል ብለዋል፡፡
ገዢው ፓርቲ እንደ ተምሳሌት ከሚከተለው የቻይና መንግሥት ጋር በዚህ ረገድ በሚገባ ተቀራርበዋል ያሉት ፕ/ሩ፤ ይህ ሁኔታ ግን ለኢትዮጵያ ህዝብ አደገኛ እንደሆነና የህዝብ እውነተኛ ድምፅ ሊታፈን እንደሚችል ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያውያን ዲሞክራቲክ ፓርቲ (ኢዴፓ) ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጫኔ ከበደ በበኩላቸው፤ “እስከዛሬ ከመንግሥት ጋር ተቀራርበን ለመስራት ያደረግነው ጥረት ውጤት አላስገኘም፣ ከዚህ በኋላ ትኩረት ሰጥተን የምንሰራው የስርዓት ለውጥ እንዴት መምጣት አለበት በሚለው ላይ ነው” ብለዋል፡፡  
የመድብለ ፓርቲ ስርአት ፍፁም የደበዘዘበትና ህዝቡ ተስፋ የቆረጠበት ሁኔታ ነው የሚታየው የሚሉት ፕሬዚዳንቱ፤ ፓርላማውም ቢሆን የአንድን ፓርቲ አስተሳሰብ በቻ የሚያንፀባርቅ በመሆኑ ለመጪዎቹ 5 አመታት ከፓርላማው ለኢትዮጵያ ህዝብ የሚጠቅም ነገር ይገኛል ብለን አናምንም ብለዋል፡፡
በፓርላማው የህግና የፖሊሲ ክርክር አድርጐ ለውጥ ለማምጣት ገዢው ፓርቲ ፍላጐት የለውም የሚሉት ዶ/ር ጫኔ፤ ምናልባት ይህ አካሄድ የተቃዋሚ ሃሳቦችን ከመድረኩ የማጥፋት ስትራቴጂ ውጤት ሊሆን ይችላል ይላሉ፡፡
የመላ ኢትዮጵያውያን አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ፕሬዚዳንት አቶ አበባው መሃሪ ደግሞ አዲስ የሚመሰረተው ፓርላማ  ለሃገሪቱም ሆነ ለመንግስት አይበጅም ባይ ናቸው፡፡  ምክንያታቸውን ሲጠቅሱም፤ ፓርላማው ሁሉን አቀፍ አሳታፊ ባለመሆኑ ነው ይላሉ፡፡ “አሳታፊ ያልሆነ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ደግሞ በምንም መልኩ ውጤታማ ይሆናል የሚል እምነት የለኝም” ብለዋል አቶ አበባው፡፡
የተቃዋሚዎች ድምፅ በፓርላማ አለመኖሩ እምብዛም እንደማያሳስበው የሚገልፀው መንግሥት በበኩሉ፣ በሌላ መንገድ ከተቃዋሚዎች ጋር የተለያዩ የውይይት መድረኮችን በመክፈት በሃገራዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት አደርጋለሁ ብሏል፡፡ በኢህአዴግ 10ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ መንግስታቸው ከተቃዋሚዎች ጋር በወሳኝ ሃገራዊ ጉዳዮች ላይ ለመምከር ዝግጁ እንደሆነ  ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ መግለፃቸው ይታወሳል፡፡
ተቃዋሚዎች ግን በጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር እምነት እንደሌላቸው ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡
መድረክ በተደጋጋሚ ከገዢው ፓርቲ ጋር ለመወያየት ያቀረባቸው ጥያቄዎች ምላሽ አለማግኘታቸውን የሚያስታውሱት ፕ/ር በየነ፤ “የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊም እንደ ወቅቱ  ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ሁሉ ተቃዋሚዎችን እናወያያለን ሲሉ የነበረ ቢሆንም አንድም ቀን አላወያዩንም፤ አሁንም እናወያያለን የሚለው ሃሳብ የለጋሾችን ቀልብ ለመግዛት ካልሆነ በስተቀር ተግባራዊ የሚሆን አይደለም ብለዋል፡፡ እንዲያም ሆኖ መድረክ አሁንም ከመንግሥት ጋር ለመወያየት ጥረት እንደሚያደርግ ፕሮፌሰር በየነ ገልፀዋል፡፡ ፡
የኢዴፓ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጫኔ ከበደ በበኩላቸው፤ በየጊዜው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተቃዋሚዎችን እናወያያለን የሚሉት  ፈፅሞ አምባገነናዊ ስርአት ነው ላለመባልና ዲሞክራሲያዊ ስርአት ያለ ለማስመሰል ነው ብለዋል፡፡ “አንድም ቀን መንግሥት ተቃዋሚ ፓርቲን  አቅርቦ አወያይቶ አያውቅም፣ በየጊዜው እናወያያለን ቢልም ወደ ተግባር ሲቀየር አላየንም” ብለዋል ዶ/ር ጫኔ፡፡ ነገሩ ከፖለቲካና ዲፕሎማሲያዊ ንግግር የዘለለ አይደለም ባይ ናቸው፡፡
የመኢአድ ፕሬዚዳንት አቶ አበባው መሃሪም የሁለቱን ፖለቲከኞች ሃሳብ ይጋራሉ፡፡  መንግሥት በተደጋጋሚ ተቃዋሚዎችን አወያያለሁ ቢልም እስከዛሬ ሲፈጽመው አልታየም፤ ለወደፊትም ያነጋግረናል የሚል ተስፋ የለኝም ይላሉ፡፡ “በትክክል ዲሞክራሲን ለማስፈን የሚደረግ ጥረት ያለ አይመስለኝም፤ ተቃዋሚዎች ‘አባሎቻችን ላይ ወከባና ድብደባ ደረሰብን’ ሲሉ ጆሮ ዳቦ ልበስ እየተባሉ፣ መንግሥት በምን ጉዳይ አወያያለሁ እንደሚል አይገባኝም” ብለዋል፡፡
የህዝብ ውይይት እየተካሄደበት እንደሆነ በሚነገርለት 2ኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ዙሪያ መንግሥት ተቃዋሚዎችን እንደሚያወያይ መግለፁ የሚታወቅ ሲሆን በቅርቡም ለሁሉም ፓርቲዎች በስልክ የውይይት ግብዣ ጥሪ መደረጉንና ተቃዋሚዎችም ጉዳዩ በደብዳቤ  ተጠቅሶ ጥሪ ይቅረብልን የሚል ምላሽ መስጠታቸው ታውቋል፡፡ ይህን ተከትሎም በደብዳቤ ጥሪ ይደረግላችኋል እንደተባሉና የውይይት ጊዜው እንደተቀየረም ተቃዋሚዎቹ ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡

የአቶ አቢሴሎም ይህደጐ የቀብር ስነስርአት ዛሬ ይፈፀማል

   የአትሌቲክስ ስፖርት ወዳጅ የነበሩት የቀስተ ደመና ስፖንጅ ፋብሪካ ባለቤት አቶ አቢሴሎም ይህደጐ፤ ከትላንት በስቲያ ከዚህ አለም በሞት የተለዩ ሲሆን የቀብር ስነስርአታቸው ዛሬ ከቀኑ 9 ሰአት በጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተክርስቲያን ይፈፀማል፡፡ ባደረባቸው ህመም ለአንድ አመት ያህል በውጭ ሀገርና በሃገር ውስጥ ህክምና ሲከታተሉ የቆዩት አቶ አቤሲሎም፤ በ72 አመታቸው ነው ያረፉት፡፡
ከወላጅ አባታቸው ብላታ ይህደጐ ለማ እና ከእናታቸው ወ/ሮ ምትክ ተስፋዬ፣ ኤርትራ አስመራ ውስጥ የተወለዱት ባለሃብቱ፤ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውንም የተከታተሉት በአስመራ ነው፡፡ በአዲስ አበባ በስዊድሽ ሚሽንና በተፈሪ መኮንን ት/ቤት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን መከታተላቸውንም ለማወቅ ተችሏል፡፡
ታዋቂው ባለሃብት አቶ አቤሴሎም የቀድሞ ሳምሶን ዳቦ ቤት ባለቤት እንደነበሩና በኋላም ቀስተደመና ስፖንጅ ፋብሪካን በማቋቋም ለበርካታ ወገኖች የስራ እድል እንደፈጠሩ  ከቤተሰቦቻቸው ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል፡፡
አቶ አቤሴሎም የ3 ልጆች አባት ነበሩ፡፡

በኢትዮጵያ የሚታየዉ የምግብ ርዳታ ፍላጎትና የተመጣጠነ የምግብ እጥረት በመጪዉ ዓመትም በእጥፍ እንደሚጨምር ግምት እንዳለ OCHA በመንስታቱ ድርጅት የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ትላንት ባወጣዉ ዘገባ ገለጸ።

መስከረም ፳፩ (ኅያ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-እንደ ነገረ ኢትዮጰያ ሪፖርተር ዘገባ ከአምስቱ እስረኞች መካከል አንዱ የሆነው የአንድነት ፓርቲው አቶ ዳንኤል ሽበሽ ጨለማ ቤት ታስሮ ይገኛል። የልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሀምሌ 14/2007 ዓ.ም ከተከሰሱበት የሽብር ወንጀል መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነፃ እንዲለቀቁ ወስኖላቸው የነበሩት አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ አቶ የሽዋስ አሰፋ፣ አቶ አብርሃ ደስታ፣ አቶ ዳንኤል …

መስከረም ፳፩ (ኅያ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሱዳን ትሪቢዪን እንደዘገበው ፕሬዚዳንት ኡመር ሀሰን አልበሽር ይህን ያረጋገጡት፤ ዛሬ ሀሙስ ከኤርትራው የፋይናንስ ሚኒስቴር ከአቶ ብርሀኔ ሀብተማርያም ጋር ካርቱም ውስጥ ባደረጉት ውይይት ነው። ሰሞኑን ካርቱም በኤርትራ የነበሩ የኢትዮጰያ አማጽያንን ወደ ኢትዮጵያ አሸጋግራለች የሚል መረጃ መውጣቱን ተከትሎ በኤርትራና በሱዳን መካከል ያለው ግንኙነት ሊሻክር እንደሚችል እየተነገረ ባለበት በአሁኑ …

መስከረም ፳፩ (ኅያ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ይህን ያሉት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊና የህዝብ ግንኙነት ዋና የስራ ሂደት መሪ አቶ ስዩም አድማሱ ናቸው። ሀላፊው በ2002 ዓ.ም በታቀደው የመጀመሪያው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ላይ በትምህርት ዘርፍ በርካታ ያልተሳኩ የአፈጻጸም ችግሮች መኖራቸውን ሰሞኑን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ባለፉት አምስት ዓመታት በትምህርት ዘርፉ …

መስከረም ፳፩ (ኅያ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-እድለኞቹ በአስተዳደሩ አታላይ ፕሮፖጋንዳ ማዘናቸውን ገልጰዋል። አስተዳደሩ ምርጫ 2007 ተከትሎ ከ32ሺ በላይ ቤቶች ላይ እጣ በመጋቢት ወር 2007 ያወጣ ሲሆን ቤቶቹንም በሳምንታት ጊዜ ውስጥ ከማስረከብ አልፎ ቀጣዩን እጣ በሰኔ ወር 2007 እንደሚያወጣ ቃል ቢገባም አንዱንም መፈጰም ሳይችል ቀርቶአል። አስተዳደሩ የካርታ ስራ እንዳዘገየው ቢናገርም እውነቱ ግን ቤቶቹ …

መስከረም ፳፩ (ኅያ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አንጋፋው ድምጸዊ አለማየሁ እሸቴ ደግሞ የህይወት ዘመን ሽልማት አሸናፊ ሆኗል። ከለ380 በላይ ሙዚቃዎችን የሰራው ድምፃዊ ኣለማየሁ አሸቴ ከ ዘመናዊ ሙዚቃ ፋናወጊው ከግርማ በየነ እጅ ሽልማቱን ከተረከበ በሁዋላ ባደረገው ንግግር ፦“ምናለ ጊዜን መመለስ ብችል እና ካለፉት ጓደኞቼ ጋር ይህን ቀን ባከብረው” በማለት ብዙዎችን ስሜት ውስጥ አስገብቷል። አርቲስት …

መስከረም ፳፩ (ኅያ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአገራችን አትሌቲክስ ስፖርት ሲነሳ ስማቸው አብሮ የሚነሳውና ለብዙ ሯጮች የችግራቸው ተጋሪ በመሆን አገራቸውንና ህዝባቸውን በቅንነት ሲያገለግሉ የነበሩት የቀስተደመና ስፖንጅ ፋብሪካ መስራች እና ባለቤት አቶ አቤሴሎም ይሕደጎ በተወለዱ በ79 ዓመታቸው ሀሙስ መስከረም 20 ቀን 2008 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። የአቶ አቤሴሎም የቀብር ስነስርዓት ቤተሰቦቻቸውና አድናቂዎቻቸው በተገኙበት …

በኢትዮጵያ የሚገኘው የኮንጎ ዲሞክራቲክ ሬፐንሊክ ኤምባሲ ለ 14 የቀድሞ ሠራተኞቹ ከ 25 ወራት በላይ ደሞዛቸውን ሳይከፍል መቅረቱን ፤ ክፍያ ያላገኙት ኢትዮጵያውያን ሠራተኞች ወቀሳ በማሰማት ላይ ይገኛሉ።

በአመታዊው የሐጅ የጸሎት ስነ-ስርዓት ላይ በደረሰው አደጋ ከሞቱት አብላጫውን ቁጥር የያዙት ኢራናውያን ናቸው። የኢራን መንግሥት464 ዜጎቹ መሞታቸውን አረጋግጧል።የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ደግሞ የሞቱት ኢትዮጵያውያን ቁጥር 13 መድረሱን አስታውቋል። የሟቾች ቁጥር ግን ከዚህም በላይ ነው እየተባለ ነው።

ታክሲ ውስጥ በብዛት ከሚፃፉት ጥቅሶችም በላይ አንዳንዴ ታክሲ ውስጥ ካሉት ሰዎች ጣል የሚደረጉት የምሬት አሊያም ሌሎች የፖለቲካ ወጎች የማህበረሰቡን አመለካከት በግልፅ ያሳያሉ፡፡ መጀመሪያ ከጎናቸው ያለውን ሰው የሚጠራጠሩት ተሳፋሪዎች ሁኔታውን አይተው ብሶታቸውን ያወራሉ፡፡ አንዳንዶቹ ወሬ የሚያስጀምር ሳያስፈልጋቸው በከተማው የሚታዘቡትን በግልፅ ይቃወማሉ፡፡ ስርዓቱን የሚደግፉ፣ የሚያስመስሉም እንደሚገኙበት ሁሉ፡፡ ዛሬ ያጋጠመኝ ግን ትንታኔ ነው፡፡ በቀልድም ቢሆን ደንበኛ የፖለቲካ ትንታኔ፡፡ […]

The post የታክሲዎች ፖለቲካ – (ጌታቸው ሺፈራው) appeared first on ሳተናው (Satenaw)-Latest Ethiopian News & Breaking News.

“አንድ የተፈረደበት የሕግ እስረኛ ከቦታ ወደ ቦታ መንቀሳቀስን ጨምሮ የሚታገዱበትና የሚከላከላቸው በርካታ መብቶች አሉ። የሕክምና አገልግሎት የማግኘት መብት ግን ከሚከለከሉት አንዱ አይደለም።” የሕግ ጠበቃው።

መስከረም ፳ (ኅያ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢሳት ገዢው ፓርቲ የሚያደርስበትን ተደጋጋሚ አፈና ተቋቁሙ ተጨማሪ የስርጭት መስመር የከፈተ ሲሆን ስርጭቱን አብዛኛው ኢትዮጵያዊ በሚከታተለው ናይል ሳት ላይ በቀላሉ ማግኘት እንደሚቻል አስተዳደሩ አስታውቋል። የአዲሱ ስርጭት ሙከራ እንደተሳካ ዝርዝር መረጃውን የምናቀርብ መሆኑን ለመግልጽ እንወዳለን።

መስከረም ፳ (ኅያ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሁለት ጎራ ተከፍለው ሲወዛገቡ የቆዩት የአፋር ክልል ባለስልጣናት ፣ የህወሃት ድጋፍ ያለው አቶ ስዩም አወልና የአቶ አሊ ሴሮ ቡድን በአሸናፊነት ከወጣ በሁዋላ፣ ላለፉት 20 አመታት የጸጥታ ዘርፍ ቢሮ ሃላፊ ሆነው የሰሩት አቶ ስዩም አወል አሁን ከያዘው ስልጣን በተጨማሪ የክልሉ ፓርቲ ሊቀመንበር ሆነው ተሹመዋል። በተቃራኒ ጎራ የተሰለፈውና የተማረውን …

መስከረም ፳ (ኅያ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦሮምያ ክልል የሚገኙ የአዲስ አበባ አጎራባች ቀበሌዎችን ወደ ዋናዋ ከተማ የሚጠቀልለው አዲሱ ማስተር ፕላን ወይም ፍኖተ ካርታ፣ አርሶደሮችን ከመሬታቸው በማፈናቀል ለጥቂት የዘመኑ ባለሃብቶች ለመስጠት ተብሎ የተዘጋጀ ነው በማለት ተቃውሞ ያሰሙ የኦሮሞ ወጣቶች መገደላቸውንና መታሰራቸውን ተከትሎ፣ ለአንድ አመት ያክል ከመጽደቅ እንዲዘገይ የተደረው እቅድ እንደገና ለማጸደቅ የተጀመረው እንቅስቃሴ፣ የኢህዴድ …

መስከረም ፳ (ኅያ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአፍሪካ ውስጥ በግድቦች አካባቢ የሚኖሩ ነዋሪዎች ለወባ በሽታ የተጋለጡ መሆናቸውን ጥናቶች አረጋገጡ በዓመት ውስጥ ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ከሰሃራ በታች በግድቦች አካባቢ የሚኖሩ አፍሪካዊያን በወባ በሽታ የሚጠቁ ሲሆን በአዲሱ ዓመት ብቻ ከሰባ ስምንት በላይ አዳዲስ ግድቦች በመሰራታቸው ተጨማሪ ሃምሳ ስድስት ሽህ የወባ ተጠቂዎች እንደሚኖሩ ጥናቱ ጠቁሟል። የውሃ …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ኢሳት ዜና (መስከረም 19 ፣ 2008) በአለማችን የደህንነት ስጋት ይታይባቸዋል ተብለው ከተፈረጁት ሃገራት መካከል ኢትዮጵያ በ 42ኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን በጉዳዩ ዙሪያ ጥናት ያካሄደ አንድ አለም አቀፍ ተቋም ገለጠ። የዘንድሮውን አመታዊ ረፖርት ይፋ ያደረገው ጋሉፕ አናሊቲክስ የተሰኘውና በአለም አቀፍ ህግና ስርኦቶች መከበር ዙሪያ የሚሰራው ተቋም በ 141 የአለማችን ሃገራት ላይ በተካሄደው ጥናት ኢትዮጵያ 42ኛ ደረጃ …

ኢሳት ዜና (መስከረም 19 ፣ 2008) የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ኮሚሽን በጄኔቭ ስዊዘርላንድ እየተካሄደ ካለው 30ኛ ጉባኤ ጋር ተያይዞ በተጠራ መድረክ ላይ የተጋበዙት የኢትዮጵያ መንግስት ልዑካን ስብሰባ ረግጠው ወጡ። ስኞ እለት የኢትዮጵያን ሰብዓዊ መብት በተመለከተ በተጠራው ስብሰባ ላይ የተገኙትና በኋላ በቀረበው ሪፖርት ሳይደሰቱ ስብሰባውን ረግጠው የወጡት የኢትዮጵያ መንግስት ልዑካን ወደ ስብሰባው አልተመለሱም። የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት …

መስከረም ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኢትዮጵያ ውስጥ የተከሰተውን ድርቅ ተከትሎ የተለያዩ አለማቀፍ ድርጅቶችና መንግስት በጋራ በፈረንጆች አቆጣጠር ሴፕቴምበር 24 ፣ 2015 ያደረጉት ስብሰባ ቃለ ጉባኤ እንደሚያስረዳው ፣ በአብዛኛው የአገሪቱ ክፍሎች እጅግ አሳሳቢ የሆነ የውሃና የምግብ እጥረት ተከስቷል። ችግሩም በሚቀጥሉት ሁለት ወራት እንደሚጨምር ለኢሳት የደረሰው ቃለ ጉባኤ ያስረዳል። በተለይ በሶማሊ ክልል ባለው …

መስከረም ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት እስካሁን 13 ሰዎች እንደሞቱ ቢገልጽም፣ የመጨረሻው መረጃ ይፋ ሲሆን ቁጥሩ ከዚህም በላይ ሊልቅ ይችላል። ከአስተባባሪዎች መካከል አንዱ የሆኑት ሼህ አህመድ ከሳውድ አረቢያ እንደገለጹት፣ 13 ቱ ሟቾች የተለዩት ዘመዶቻቸው ባረጋገጡት መሰረት ነው። የሳውዲ መንግስት የሟቾችን ቁጥር ሙሉ በሙሉ ለማሳወቅ እንዳልቻለ የገለጹት ሼህ …

መስከረም ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የዛንቢያ የስደተኞች ቢሮ በአገሪቱ ውስጥ በሕገወጥ መንገድ በመግባታቸው ክስ ከቀረበባቸውና የእስር ጊዜያቸውን ያጠናቀቁ ሃያ ስድስት የውጭ አገር ዜጎችን ወደየትውልድ አገራቸው መመለሱን አስታውቆ፣ ከእነዚህ መካከል 16ቱ ኢትዮጵያውያን ናቸው። ደቡብ አፍሪካ ለመግባት ሲሞክሩ ከኬንያ ጀምሮ ባሉት የመሸጋገሪያ አገራት ውስጥ አያሌ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች በእስርቤትና በታጋቾች በደልና ስቃይ እየደረሰባቸው ሲሆን …

መስከረም ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአማራ ገጠር መንገድ ስራ ባለስልጣን መስሪያ ቤት ባደረገው አመታዊ የሰራተኞች ስብሰባ ላይ ችግሩ አለመቀረፉን የገለጹት ባለሙያዎችና የድርጅቱ ሰራተኞች ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በተደጋጋሚ የሚያሳማው የጥራቱ ጉዳይ መሆኑን ተናገረዋል፡፡ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ሁልጊዜ ሊያሻሽለው አልቻለም በማለት ባለሙያዎች ያቀረቡት የጥራት ጉዳይ መንገዶች ጥገና ተደርጎላቸው ከተሰሩ በኋላም ተገቢውን ጊዜ አገልግሎት …

የዓለም አቀፉ የሆቴሎች ድርጅት ሒልተን በአዋሳ ከተማ በ42 ሚሊዮን ወይም ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ በአዋሳ ከተማ ላይ ሆቴል እንደሚገነባ ረቡእለት ይፋ አደረገ።

የሚገነባዉ ሆቴል ለሒልተን ዓለም አቀፍ አንድ ትልቅ ምእራፍ ነዉ ተብሏል። የግንባታዉን የስራ አመራር ከኢትዮጵያዉ የሰንሻይን የንግድ ኩባንያ ጋር ተፈራርመዋል።

 

ታካሚዎች የሰውነት መከላከያ እንክብል (ARV) የሚሰጣቸው የበሽታ መከላከያ ቁጥር ከተወሰነ ድረጃ በታች ሲወርድ ነው። በአዲሱ አሰራር በቫይረሱ መያዛቸው የታወቀ ሰዎች በፍጥነት የመከላከያ ህክምና ያስፈልጋቸዋል።

ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል በማፈራረስና ኦሮሚያ ክልልን የመገንጠል ፖለቲካዊ ዓላማ በመያዝ፣ ዓላማውን ለማስፈጸም ሲንቀሳቀሱ ተደርሶባቸዋል የተባሉ ሦስት ተጠርጣሪዎች ተከሰሱ፡፡

በመንግሥት ላይ ተፅዕኖ በማሳደር፣ ኅብረተሰቡን በማስፈራራትና የአገሪቱን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ተቋማትን ለማናጋት፣ ራሱን የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ብሎ ከሚጠራው ድርጅት ተልዕኮ ተቀብለው ሲንቀሳቀሱ ተደርሶባቸዋል የተባሉት ተከሳሾች ቶሎሳ በየነ፣ ቱሉ ሞኦ አቤቱና መገርሳ መሸሻ የሚባሉ መሆናቸውን የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ችሎት ያቀረበው ክስ ያብራራል፡፡ 

ተከሳሾቹ በኦነግ አማካይነት ‹‹የኦሮሞን ብሔር ከመንግሥት ጫና ለማላቀቅና ነፃ ለማውጣት መታገል አለብህ፤›› ተብሎ የቀረበላቸውን ጥያቄ በመቀበል አባል መሆናቸውን ክሱ ይጠቁማል፡፡

ተከሳሾቹ ከ2000 ዓ.ም. ጀምሮ በኦሮሚያ ክልል በምሥራቅ ወለጋ ዞን በነቀምት ከተማ በሚገኙ የተለያዩ የንግድ ቤቶች ከኦነግ አባላት ጋር በመገናኘት፣ ድርጅቱ የሚሰጠውን ወታደራዊና ፖለቲካዊ ሥልጠና ለመውሰድ ወደ ኤርትራ መጓዛቸውንም ክሱ ያክላል፡፡ ኤርትራ አገር ከደረሱ በኋላ ኢን ተብሎ በሚጠራው ማሠልጠኛ ካምፕ፣ ከሌሎቹ የድርጅቱ አባላት ጋር በመሆን ወታደራዊ የአካል ብቃት ሥልጠና መውሰዳቸውም በክሱ ተገልጿል፡፡ የጦር መሣሪያ አገጣጠም፣ ዒላማ ተኩስ፣ ቦምብ አፈታት፣ አገጣጠምና አወራወር ያካተተ ወታደራዊ ሥልጠና ለተከታታይ ሦስት ወራት መውሰዳቸውን ክሱ ይገልጻል፡፡ 

በቁጥጥር ሥር ካልዋሉት ግብረ አበሮቻቸው ጋር በመሆን ኢትዮጵያ ውስጥ የኤሌክትሪክና የውኃ መስመሮችን መቁረጥ፣ የመኪና መንገዶችን በድንጋይ መዝጋትና የኦሮሞ ገበሬዎች እህል ወደ ገበያ እንዳያወጡ ለማድረግ ተልዕኮ በመቀበል፣ በተለይ ቶሎሳ በየነ የተባለው ተከሳሽ ሲንቀሳቀስ እንደነበር ክሱ ያስረዳል፡፡ ተልዕኮ ማስፈጸሚያ ተብሎ 8,000 ብር ተቀብሎ ከኤርትራ በጂቡቲ በኩል ወደ ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት መስከረም ወር 2007 ዓ.ም. መግባቱንም ጠቁሟል፡፡

ተከሳሾቹ ቁጥሩን በማያሳይ ‹‹UN KNOWN›› በሚል ስልክ በመደዋወል የጦር መሣሪያ ይቀባበሉ እንደነበርና ጥይቶቹን በፍራሽ ጠቅልለው በትራንስፖርት ሲያሳልፉ እንደነበሩ የዓቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል፡፡

ቱሉ ሞኦ አቤቱ የተባለው ተከሳሽ ከኤርትራ ወደ ጂቡቲ ከዚያም በሚሌ አድርጐ ወደ ኮምቦልቻ ከሄደ በኋላ፣ ወደ አዲስ አበባ ከዚያም ወደ ነቀምት በመሄድ አንደኛ ተከሳሽ አባት ቤት ውስጥ ክላሽኒኮቭ ጠመንጃውን ከ60 ጥይቶች ጋር መደበቁን ክሱ ይገልጻል፡፡ ካልተያዙ ግብረ አበሮቹ ጋር ተቀብሎት የነበረው ተልዕኮ፣ ኦሮሚያ ውስጥ የሚኖሩ የአማራ ተወላጆችን ለመግደል እንደነበር የዓቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል፡፡ 

ተከሳሾቹ በአጠቃላይ የወንጀል ሕግ ቁጥር 32(1ሀን) እና የፀረ ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652 አንቀጽ 7(1)ን በመተላለፍ በፈጸሙት በሽብርተኛ ድርጅት ተግባር ውስጥ በመሳተፍ ወንጀል መከሰሳቸውን ዓቃቤ ሕግ በክሱ አስረድቷል፡፡ ተከሳሾቹ በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ትዕዛዝ ተሰጥቶ የቀረበባቸውን ክስ ለመስማት ለጥቅምት 2 ቀን 2008 ዓ.ም. ተረኛ ችሎቱ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡  

 

በሙስና ወንጀል ለተከሰሱት የልብ ሕክምና ስፔሻሊስት መንግሥት ትብብር እንዲያደርግላቸው ማኅበሩ ጠየቀ

በከባድ የሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ክስ በተመሠረተባቸው በእነ አቶ መላኩ ፈንታ የክስ መዝገብ የተካተቱትን የልብ ሕክምና ስፔሻሊስት ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ ወርዶፋን መንግሥት ትብብር እንዲያደርግላቸው፣ የግል ሆስፒታሎች ማኅበር ጠየቀ፡፡ 

በማኅበሩ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሲሳይ ማሩ ጆፋ ፊርማ በቀጥታ ክስ ለመሠረተው ለፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ተጽፎ በግልባጭ ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፣ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ለፍትሕ ሚኒስቴር፣ ለጤና ጥበቃ ሚኒስቴርና ለዳያስፖራ ዴስክ እንዲደርስ የተደረገው ደብዳቤ ማኅበሩ ለምን የመንግሥት ትብብር እንደተፈለገ ያብራራል፡፡ 

ደብዳቤው እንደሚገልጸው፣ በሙስና ወንጀል ክስ ተመሥርቶባቸው ጉዳያቸው በፍርድ ቤት በመታየት ላይ የሚገኙት ዶ/ር ፍቅሩ፣ በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን አዲስ የልብ ሕክምና ማዕከልን የከፈቱ ፈር ቀዳጅ የልብ ሕክምና ባለሙያ ናቸው፡፡ 

በሆስፒታሉ የተዘጉ የልብ የደም ሥሮች ማየት የሚችል ሕክምና፣ የልብ ምታቸው ለቀነሰ ሕሙማን የልብ ምት ማስተካከል፣ ድንገተኛ የልብ መቆም መከላከል ሕክምናና ሌሎችም በርካታ ከልብ ጋር የሚገናኙ ሕክምናዎች እንደሚሰጡ ማኅበሩ፣ በደብዳቤው ጠቁሟል፡፡ 

የነፍስ አድን መሣሪያዎች በሰውነታቸው የተገጠመላቸው ታካሚዎች በየሦስት ወራት እየተከታተሉ በሕይወት የመቆየት ተስፋ እንደነበረባቸው የሚገልጸው ማኅበሩ ዶ/ር ፍቅሩ በመታሰራቸው ይሰጥ የነበረው ሕክምና በመቋረጡ የልብ ታካሚዎቹ ለከፋ ችግር እየተጋለጡ መሆኑን አስረድቷል፡፡ 

ዶ/ር ፍቅሩ ኢትዮጵያውያን ሐኪሞችን ወደ ስዊድን በመላክ የልብ ሕክምና ስፔሻሊስት እንዲሆኑ ማድረጋቸውን ማኅበሩ በደብዳቤው ጠቁሞ፣ ከስዊድን ከሚመጡ ሐኪሞች ጋር በሚደረግ የሕክምና ሒደት ደግሞ የዕውቀት ሽግግርም ይካሄድ የነበረ ቢሆንም፣ እሳቸው በመታሰራቸው መቋረጡን አስረድቷል፡፡ 

በመሆኑም ዶ/ር ፍቅሩ በመታሰራቸው ምክንያት በእሳቸው ክትትል ይደረግላቸው የነበሩ ሕሙማን ለከፋ ችግር መጋለጣቸውን፣ በጤና አገልግሎቱም ክፍተት እየተፈጠረ መሆኑን፣ መንግሥት የእሳቸውን አስተዋጽኦ ከግምት ውስጥ በማስገባትና ኅብረተሰቡ የደረሰበትን የሕክምና ዕጦትና መንገላታት ታሳቢ በማድረግ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግላቸው ጠይቋል፡፡ 

ማኅበሩ ለሚመለከታቸው አካላት ደብዳቤ የጻፈው ጳጉሜን 2 ቀን 2007 ዓ.ም. ቢሆንም፣ እስከ መስከረም 18 ቀን 2008 ዓ.ም. ድረስ ከማናቸውም አካላት ምንም ዓይነት ምላሽ አለማግኘቱ ታውቋል፡፡ 

 

የግንቦት 7 ድርጅትን ተልዕኮ በመቀበል የሽብር ተግባር ለመፈጸም የፌዴራል ፖሊስ አባል በመሆን መረጃ ሲያስተላልፉ ተደርሶባቸዋል ተብለው የተጠረጠሩ ሁለት ፖሊሶች በቁጥጥር ሥር ውለው ክስ ተመሠረተባቸው፡፡ 

በፌደራል ፖሊስ ተቋም ውስጥ ተመድበው ሕገ መንግሥቱን ለመጠበቅ የተጣለባቸውን አደራ በመተው፣ የግንቦት 7 ጥምረት ነው የተባለውን የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች የሰጣቸውን ተልዕኮ በመቀበል ሲንቀሳቀሱ ነበር የተባሉት፣ ኮንስታብል ነገደ ሸዋ ቀናና ረዳት ሳጅን እንዳለ ዘየደ የሚባሉ መሆናቸውን፣ የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ችሎት መስከረም 10 ቀን 2008 ዓ.ም. ያቀረበው ክስ ይገልጻል፡፡

ኮንስታብል ነገደ የተባለው ተጠርጣሪ ኤርትራ ከሚኖርና የግንቦት 7 ድርጅት አባል ጋር በስልክ በመገናኘት፣ ለመንግሥት ጥሩ አመለካከት የሌላቸውን እየመለመለ አድራሻቸውን እንዲሰጠው መስማማታቸውን ክሱ ይገልጻል፡፡ በፌዴራል ፖሊስ ተመሳሳይ የሥራ ድርሻ የነበረው ተከሳሽ ረዳት ሳጅን እንዳለ ተመሳሳይ ድርጊት መፈጸሙን የሚገልጸው የዓቃቤ ሕግ ክስ፣ ሁለቱም ተከሳሾች በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በሽብርተኛ ድርጅት ውስጥ በማናቸውም መልኩ መሳተፍ ወንጀል ክስ መሥርቶባቸዋል፡፡ ክሱን ተቀብሎ ያየው ተረኛ ችሎትም ተከሳሾቹ በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ በማዘዝ፣ ክሱን ለመስማት ለጥቅምት 2 ቀን 2008 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

ሌላው የመከላከያ ሠራዊት አባል መሆኑ የተጠቀሰውና የኦነግ አባል በመሆን አባላትን በመመልመልና መረጃ በማስተላለፍ ተጠርጥሮ ክስ የተመሠረተበት ወታደር አማኑኤል ደስታ ጅማ ይባላል፡፡

ተከሳሹ ኅብረተሰቡን አደጋ ላይ ለመጣል፣ ሕይወት ለማጥፋትና ንብረት ለማውደምና በመንግሥት ላይ ተፅዕኖ ለመፍጠር፣ ከመስከረም ወር 2007 ዓ.ም. ጀምሮ በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን ሻኪሶ አካባቢ ከድርጅቱ አባላት ጋር ይገናኝ እንደነበር የዓቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል፡፡

ተከሳሹ የኦነግን ተልዕኮ ለማሳካት በጥር ወር 2007 ዓ.ም. በአገር መከላከያ ሠራዊት በመቀጠርና ለአራት ወራት ሁርሶ ወታደራዊ ሥልጠና በመውሰድ፣ ሠራዊቱን ተቀላቅሎ መመደቡን ክሱ ያብራራል፡፡ 

በሠራዊቱ ውስጥ ከተመደበ በኋላ አባላትን በመመልመልና በማደራጀት በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን፣ ሻኪሶ ወረዳ፣ ሻኪሶ ከተማ ከሚገኘውና የኦነግ አባል ከሆነው ደበበ ሚደቅሳ ከተባለው የድርጅቱ አባል ጋር ግንኙነት ሲያደርግ መቆየቱ በክሱ ተጠቅሷል፡፡ 

የመለመላቸውን ሻምበል ባሻ ስንታየሁና ሃምሳ አለቃ ሸለመ ሞቱማ የተባሉ የመከላከያ ሠራዊት አባላትንና ሌሎች ወታደሮችን አስከድቶ፣ ወደ ኤርትራ ሄደው ለመቀላቀል በዝግጅት ላይ እያሉ በቁጥጥር ሥር መዋሉን ክሱ ይገልጻል፡፡ ክሱን ለመስማት ፍርድ ቤቱ ለጥቅምት 22 ቀን 2008 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡    

 

መስከረም ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ መራሹ ገዥው ፓርቲ በመንግስት ቁጥጥር ስር የሚገኙ መገናኛ ብዙሃን የመልካም አስተዳደር፣ የሙስናና ኪራይ ሰብሳቢነት ችግሮችን አጋልጡ በሚል ከፍተኛ ግፊት ማድረጉን ተከትሎ ትርምስ መፈጠሩ ተሰማ፡፡ የመገናኛ ብዙሃኑን መሪዎች ጨምሮ አንዳንድ ጋዜጠኞች በሙስናና ብልሹ አሠራር የሚጠረጠሩ መሆናቸው ይበልጥ ነገሩን አወሳስቦታል፡፡ ኢህአዴግ በቅርቡ በመቀሌ ከተማ ባካሄደው ድርጅታዊ ጉባዔ …

መስከረም ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የህወሃት ነባር ታጋይና በሁዋላም የአፋር ብሄራዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ( አብዴፓን) መስርተው ክልሉን ላለፉት 24 ዓመታት ሲመሩት የቆዩት አቶ እስማኤል አሊ ሴሮ፣ ከስልጣን ተነስተው ወደ ፌደራል ሲዛወሩ እርሳቸውን ለመተካት በተፈጠረው የስልጣን ሽኩቻ፣ ህወሃት የደገፋቸው ቡድኖች አሸናፊዎች ሆነው መውጣታቸውን የደረሰን መረጃ ይጠቁማል። ቀድም ብለው ፓርቲውን እንዲመሩ የተመረጡት ወጣቱ …