ይቅርታ – የወያኔ ካርታ
ይገረም አለሙ
1437ኛው የኢድ አል አድኻ (አረፋ) በዓል በአዲስ አበባ ስታዲየም ሲከበር ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት፤ በሽብር ወንጀል ተከሰው ከተፈረደባቸው የሙስሊሙ ማኅበረሰብ ችግሮች መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት መካከል ስድስቱ በቅርቡ የተለቀቁት በእነርሱ ጥያቄና ጥረት እንደሆነ፤ ጥያቄአቸው ምላሽ በማግኘቱና ጥረታቸው በመሳካቱ መደሰታቸውን ገልጸው፤ ለመንግሥት ምሥጋና ማቅረባቸውን የጀርመን ድምጽ ራዲዮ ዘጋቢ ከስፍራው ባስተላላፈው ዘገባ አሰምቶናል። ወያኔ ግዜና ወቅት እየጠበቀ የሚጠቀምባት የፖለቲካ ቁማር መጫወቻ የይቅርታ ካርድ በሌላ መንገድና መልክ ተመዘዘች ማለት ነው።