ዛሬ ጥቅምት 5 2007 በዋለው ችሎት አንድ አመት ከ5 ወር እስር ቤት የቆዪት አራት የዞን9 ጦማርያን ላይ ውሳኔ አስተላልፏል።
በውሳኔው መሰረት አንደኛ ተከሳሽ ሶልያና ሽመልስ መከላከል ሳያስፈልጋት ከክሱ ነፃ
ሶስተኛ ተከሳሽ ናትናኤል ፈለቀ መከላከል ሳያስፈልገው ከክሱ ነፃ
አምስተኛ ተከሳሽ አጥናፍ ብርሃኔ መከላከል ሳያስፈልገው ከክሱ ነፃ
ስድስተኛ ተከሳሽ አቤል ዋበላ መከላከል ሳያስፈልገው ከክስ ነፃ የተባሉ ሲሆን
ሁለተኛ ተከሳሽ ጦማሪ በፍቃዱ ሃይሉ ከሽብር ክስ ነፃ የተባለ ሲሆን መአከላዊ ምርመራ በሃይል እና በማሰቃየት የሰጠው ቃል ላይ አመፅ እንዳነሳሳ አምኗል በሚል በወንጀል ህጉ 257 መሰረት እንዲከላከል ግን ዋስትና መጠየቅ እንደሚችል ተገልፇል።
የጦማርያኑ ጠበቃ በፍቃዱ ይግባይ እንዲሰጠው የጠየቁ ሲሆን አቃቤ ህግ ተቃውሞ አሰምቶ ይግባኙ ላይ ለጥቅምት 10 ለማየት ቀጠሮ ሰጥቷል።
ባለፉት 1 አመት ከ5 ወራት በማንኛውም በቻላችሁት አቅም ሁሉ ከጎናችን ለቆማችሁ ከፍተኛ ምስጋና እያቀረብን በፍቃዱ ይፈታ የሚለው ጥያቄያችን እንደሚቀጥል ለማሳወቅ እንወዳለን።
የዞን 9 ጦማርያን ከማረሚያ ቤት ሲወጡም የምናሳውቅ ይሆናል።
‪#‎FreeBefekadu‬ ‪#‎Ethiopia‬
እልፍ ምስጋና ለዞን9 ነዋርያንና ወዳጆች
ስለሚያገባን እንጦምራለን!
ዞን9

እኔ እንዳዳመጥኩት Ené endadametkutጌቱ ኃይሉ

መቼም ሰው ይናገራል። እኔ ደግሞ ጆሮ ፈጥሮብኛልና እሰማለሁ። የምሰማውና የማዳምጠው ግን ይለያያል።

ባለፈው ሰሞን ቁጥር 00 ሰውዬ ሲናገሩ ሰማሁ፣ “የዛሬ አሥር ዓመት ከ80 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን ሥራ እናስይዛለን” ብለው ሲናገሩ ሰማሁ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ነፃነት ዘለቀ

Former TPDM fighters. የቀድሞ ዴምሕት አባላት

እንደምን ሰነበታችሁ። እንኳን ለአዲሱ ዓመት የ2008 ዓ.ም. ሁለተኛ ወር “ለጥቅምት አንድ አጥንት” በሠላም አደረሳቹ። ጥቅምት ብርዳምና ንፋሳም ነው። ዘንድሮም እንደዛው ነው። የአዲስ አበባ የሰሞኑ ብርድ ሚስት ያሳቅፋል። ግን ስንገናኝ ሠላምታ የማንለዋወጠው ለምንድነው? ብዙ መጣጥጥፍ ጸሐፊዎች ይህን ወግ ልማድ ረስተው በቀጥታ ሊያስተላልፉት ወደሚፈልገጉት ቁም ነገር ይገባሉ – ያበሳጩኛል። “እንዴት ሰነበታችሁ” ማለት ማንን ገደለ?

ሙሉውን አስነብበኝ …

እኔ እንዳዳመጥኩት Ené endadametkutጌቱ ኃይሉ

መቼም ሰው ይናገራል። እኔ ደግሞ ጆሮ ፈጥሮብኛልና እሰማለሁ። የምሰማውና የማዳምጠው ግን ይለያያል።

ባለፈው ሰሞን ቁጥር 00 ሰውዬ ሲናገሩ ሰማሁ፣ “የዛሬ አሥር ዓመት ከ80 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን ሥራ እናስይዛለን” ብለው ሲናገሩ ሰማሁ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ኢሳት ዜና (ጥቅምት 4 ፣ 2008) በኢትዮጵያ በተለያዩ ስራዎች ላይ ተሰማርተው የሚገኙ የቻይና ኩባንያዎች በኢትዮጵያዊያን ሰራተኞች ላይ የሚፈጽመው በደል ከአቅም በላይ እየሆነ መምጣቱን የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ፌደሬሽን ገለጠ። በኢትዮጵያዊያን ሊሰሩ የሚችሉ ቀላል ስራዎች በውጪ አገር ዜጎች እየተሰሩ እንደሚገኙ ያስታወቀው ፌደሬሽኑ 20 የሚሆኑ የቻይና ኩባንያዎች ሰራተኞቻቸው በማህበር እንዳይደራጁ ተጽዕኖ አሳድረው እንደሚገኙ አመልክቷል። በተለይ በኮንስትራክሽን ዘርፍ ላይ ተሰማርተው …

ጥቅምት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ካለፈው አመት ጀምሮ እንደ አዲስ በተጀመረው የሰራዊት ምልመላ የተፈለገውን የሰራዊት ቁጥር ማግኘት የተቸገረው መንግስት፣ ሰሞኑን ደግሞ በአንዳንድ ክልሎች የመከላከያ ሰራዊት አባላት በመኪና ላይ ሆነው ወጣቱ ለውትድርና እንደሚዘገብ በመቀስቀስ ላይ ናቸው። ከዚህ ቀደም ለእያንዳንዱ ቀበሌና ወረዳ የተሰጠው ኮታ ሊሟላ ባለመቻሉ፣ መንግስት በስራ ስልጠና ስም ወጣቶችን በመቀስቀስ ያለፍላጎታቸው እንዲዘምቱ …

ጥቅምት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሞተር ሳይክል ሰዎችን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ህይወታቸውን የሚመሩ 500 ያክል ወጣቶች ስራ እንዲያቆሙ በመታዘዛቸው ችግር ላይ መውደቃቸውን ተናግረዋል። ሰራተኞቹ በድንገት አቁሙ በመባላቸው፣ ቤተሰቦቻቸውን ለማስተዳደር ተቸግረዋል። መንግስት አማራጭ ስራ ሳይፈጥር በድንገት ስራ አቁሙ ማለቱ ተገቢ አይደለም በሚል ወጣቶቹ ያስነሱትን ተቃውሞ ተከትሎ የወረዳው ባለስልጣናት ተጨማሪ የማስጠንቀቂያ ጊዜ ሰጥተዋል። አንድ …

ጥቅምት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በተከዜ ወንዝ ጫፍ ላይ የምትኘውና የዋግና የበለሳ ነዋሪዎች መተላለፊያ የሆነችው አርባ ፀጓር ወረዳ ደርግን ለመጣል በተደረገው የትግል ወቅት የኢህአፓና የኢሕዲን መተላለፊያ መስመር የነበረች ሲሆን በወቅቱ የድሮው ኢሕዲን የአሁኑ ብአዴን ታጋዮች የነበሩት ለሕዝቡ የኑሮ ለውጥና ዴሞክራሲያ ስርዓት እንደሚገነቡ ቃል በመግባታቸው ነዋሪው ሸማቂዎቹን በማገዝ ከለላ ይሰጣቸው የነበረ ሲሆን ድል …

ጥቅምት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢትዮጵያ ስፖርት ፌዴሬሽን በሰሜን አሜሪካ፥ ESFNA በካናዳ የቶሮንቶን ከተማ የ2016 የስፖርት ክብረ በዓል ዓስተናጋጅ እንድትሆን መርጧል። ውሳኔው የተላለፈው፥ በኢትዮ-ስታር ቶሮንቶ የእግር ኳስ ክለብ ዓስተባባሪነት በቶሮንቶ ካናዳ በተዘጋጀው፥ የESFNA ዓመታዊ ጉባኤ የኢትዮጵያ ስፖርት ፌዴሬሽን በሰሜን አሜሪካ የክለብ ተዎካዮችና የቦርዱ ዓመራር ዓባላት በተገናኙበት፥ ባሳለፍነው ቅዳሜና እሁድ October 10 እና …

ጥቅምት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በስምጥ ሸለቆ ውስጥ የሚገኙት የቱርካና ሃይቅና የኦሞ ወንዝ ኢትዮጵያ በምትከተለው የኢንዱስትሪ ዘመቻ ምክንያት የመድረቅ እና የአየር ንብረት መዛባት አደጋን ማስከተሉንና በዚህም ለውጥ ሳቢያ የአካባቢው ነዋሪዎች ስጋት ውስጥ መሆናቸውን ሂውማንራይትስ ወች በጥናት ሪፖርቱ አመልቷል። በሰሜናዊ ምዕራብ ኬንያ በኢትዮጵያ ድንበር አካባቢ የሚገኘው የቱርካና ሃይቅ በዓለማችን በስምጥ ሸለቆ ውስጥ ከሚገኙት …

ሙሉጌታ ሉሌ / Mulugeta Luleበልጅግ ዓሊ

“ደግ ደጉን ስናጣ፣ ኀዘኑ መረረ

ሞት አምላኩ ከድቶት፣ ገሎት በነበረ።”

– የሠፈራችን ሙሾ አውራጅ

እነሆ ጋሼ ሙሉጌታ ዐረፈ። ከዚህ ምስቅልቅሉና ቅጥ አምባሩ ከወጣ ዓለም በአካል ተለየ። ጋሼ ሙሉጌታ ከእንግዲህ የሀገሩን አፈር በሞቱ እንኳ ላይቀምስ ነው። ዛሬ የሰው ሀገር አፈር ለብሶ በዝምታ ማሸለቡን መርጧል። ሀገሩን እንደናፈቀ የተለያት ቢሆንም ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚሸጋገር ትምህርት ሰጥቶን አልፏል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ጥቅምት ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በገጠሪቱ ኢትዮጵያ የሚገኙ 8 ሚሊዮን 200 ሺ ኢትዮጵያውያን አስቸኳይ የምግብ እርዳታ እንደሚሹ፣ በከተማ ውስጥ የሚኖሩ 4 ሚሊዮን ተረጅዎች እንዳሉ በመንግስት እና በአለማቀፍ ድርጅቶች ይፋ ከሆነ በሁዋላ፣ የአለማቀፍ ድርጅቶች መንግስት ለልማት በሚል የመደበውን ገንዘብ የዜጎቹን ነፍስ ለመታገድ እንዲያውለው ጠይቀዋል። እስከሚቀጥለው ታህሳስ ወር ድረስ ምግብ ገዝቶ ለማቅረብ የሚያስፈልገው 12 …

ጥቅምት ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ካለፈው እሁድ ጀምሮ በኢትዮጵያውያንና በሱዳን መንግስት ወታደሮች መካከል የተነሳው ጦርነት መቀጠሉን ከአካባቢው የደረሱን መረጃዎች ያመለካታሉ።ኢትዮጵያውያን ታጣቂዎች፣ ከዚህ ቀደም ማንነታቸው ያልታወቁ የሱዳን ታጣቂዎች 8 ኢትዮጵያውያንን ለሹፌርነት እንቀጥራችሁዋለን በማለት በአሰቃቂ ሁኔታ ከመኪና ላይ አውርደው መግደላቸውን ተከትሎ፣ ኢትዮጵያውያኑ በወሰዱት አጸፋ እርምጃ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ የሱዳን ወታደሮችን ገድለዋል። የሱዳን መንግስት ተጨማሪ …

ጥቅምት ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ክልል በሲዳማ ዞን በማልጋ ወረዳ ፣ ወታራና ጉጉማ በሚባሉ አካባቢዎች ከ2004 ዓም ጀምሮ በእየአመቱ የሚቀሰቀሰው ግጭት ሰሞኑን አገርሽቶ፣ እስካሁን 2 ሰዎች በከባድ ሁኔታ ተጎድተው አዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል ሲገቡ፣ መጠኑ ያልታወቀ ንብረትም ወድሟል። በቦንኬ ጎሳና በጉኑፋ ጎሳዎች መካከል የተነሳው ግጭት መንስኤ የአንዱ አካባቢ ተወላጅ ሌላውን ማስተዳደር አይችልም …

ጥቅምት ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመግባት ሲሞክሩ በማላ ዊ የድንበር ጠባቂዎች የተያዙ ከ317 በላይ ኢትጵያዊያን ስደተኞች በተለያዩ እስርቤቶች ውስጥ የሚገኙ ሲሆን በእስር ቤት ውስጥ ሰቆቃ እየተፈፀመባቸው መሆኑን አጃን ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል። የማላዊ ፍርድ ቤት በስደተኞች ላይ የእስር ቅጣትና ስድሳ አምስት የአሜሪካን ዶላር መቀጮ የጣለባቸው ሲሆን ፣ አብዛሃኞቹ ከስድስት ወራት …

ጥቅምት ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሽብር ወንጀል ተከሰው በ19ኛው ወንጀል ችሎት ነጻ የተባሉት የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ሃብታሙ አያሌው፣ የሰማያዊ ፓርቲ የምክር ቤት ም/ል ሰብሳቢ የነበረው የሽዋስ አሰፋ፣ የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ም/ል ስብሳቢና የደቡብ ተወካይ የነበረው ዳንኤል ሽበሺ እንዲሁም አብርሃም ሰለሞን ፣ ዛሬ ጠ/ፍርድ ቤት ቀርበው፣ በአቃቢ ህግ የተጠየቀባቸው ይግባኝ …

ጥቅምት ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦሮምያ ክልል በፍቼ ከተማ የትራንስፖርት አገልግሎት መስሪያ ቤትስራችንን በአግባቡ ሊያሰራን አልቻለም በሚል ምክንያት የባጃጅ አሽከርካሪዎች ከትናንት ጀምረው የስራማቆም አድማ አድርገዋል። የከተማው መንገድ ትራንስፖርት ባጃጅ ለመንዳት የታክሲ አንድ ፈቃድ መያዝ ያስፈልጋል የሚል መመሪያ ያወጣ ሲሆን፣ በሶስተኛ መንጃ ፈቃድ ሲያሽከረክር የተገኘ ሹፌር 2 ሺ 500 ብር ይቀጣል። የቅጣቱን መጠንና …

ባለፈው ቅዳሜ በተነሳው ግጭት ከፖሊስና ከመከላከያ አንዳንድ ወታደሮች ቆስለዋል። የግጭቱ መንስኤ ሁለት የመከላከያ ፖሊስ አባላት በፖሊሶች መደብደባቸው ነው። ከዚህ ቀደም አንድ ፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ ፍቼ አካባቢ ሰፍሮ የሚገኘውን የመከላከያ ሰራዊት አባል ከገደለው በሁዋላ፣ በመከላከያና በፖሊስ መካከል ለወራት የዘለቀ ቁርሾ እንዲፈጠር አድርጓል። ባለፈው ቅዳሜ ሁለት የመከላከያ ሰራዊት አባላት በከተማው እየተዝናኑ በነበረበት ወቅት፣ ፖሊሶቹ የደበደቡዋቸው ሲሆን፣ የመከላከያ […]

አስቸኳይ የምግብ ዕርዳታ ፈላጊዎች 8.2 ሚሊዮን መድረሳቸውን መንግሥት ይፋ አደረገ

–   ጠቅላላ የሚያስፈልገው የዕርዳታ መጠን 12 ቢሊዮን ብር ደርሷል

–    አራት ቢሊዮን ብር ከመንግሥት ካዝና ወጪ መደረጉ ተጠቁሟል

በድርቅ ምክንያት አስቸኳይ የዕለት ደራሽ የምግብ ዕርዳታ የሚፈልጉ ዜጎች ቁጥር 8.2 ሚሊዮን መድረሱን መንግሥት ይፋ አደረገ፡፡ ለጋሾች አስፈላጊውን ዕርዳታ እያቀረቡ

አለመሆኑን መንግሥት ሲያስታውቅ፣ በጠቅላላው አስከፊነቱ እየተባባሰ ለመጣው ድርቅ 12 ቢሊዮን ብር ወይም 600 ሚሊዮን ዶላር ገደማ እንደሚያስፈልግ፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ኤጀንሲዎች ይፋ አድርገዋል፡፡ 

ጥቅምት 1 ቀን 2008 ዓ.ም. ከለጋሽ አገሮች፣ ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ኤጀንሲዎችና መንግሥታዊ ካልሆኑ ለጋሾች ጋር በተደረገ የሁለትዮሽ ስብሰባ ላይ የብሔራዊ አደጋ መካከልና ዝግጁነት ኮሚቴ ጸሐፊ አቶ ምትኩ ካሳ እንዳስታወቁት፣ በኤልኒኖ ክስተት ምክንያት በበልግና በመኸር (ክረምት) የዝናብ ሥርጭት በመዛባቱ 8.2 ሚሊዮን ሰዎች አስቸኳይ የዕለት ደራሽ ዕርዳታ ያስፈልጋቸዋል፡፡ 

‹‹የበልግ ዝናብ መዛባት ከመኸር ዝናብ መስተጓጎል ጋር ተዳምረው የፈጠሩት ችግር ነው፡፡ ብዙ ጊዜ ግን በልግ በሚዛባበት ወቅት መኸር ጥሩ ይሆን ነበር፡፡ ለወትሮው በመኸር አምራች የሆኑ አካባቢዎች ለችግር ስለማይጋለጡ የተረጂዎች ቁጥር ዝቅ ያለ ነበር፡፡ አሁን ግን የሁለቱም መዛባት ችግሩን ፈጥሯል፡፡ ከዚህ ባሻገር ከጥር እስከ ሰኔ ወር በሚተገበረው ሴፍቲኔት ፕሮግራም ታቅፈው የነበሩ 4.4 ሚሊዮን ሰዎችም በ8.2 ሚሊዮን አኃዝ ውስጥ ይገኛሉ፤›› ያሉት አቶ ምትኩ፣ ከጥር ወር በኋላ በመደበኛው የሴፍቲኔት ፕሮግራም ተጠቃሚ የሆኑት ሰዎች ከዕለት ደራሽ ተረጂዎች ሲለዩ፣ አስቸኳይ የምግብ ዕርዳታ የሚቀርብላቸው ሰዎች ቁጥር እንደሚቀንስ አስረድተዋል፡፡ 

ባለፈው የበልግ ግምገማ ተካሂዶ ነሐሴ 12 ቀን 2007 ዓ.ም. ይፋ በተደረገው አኃዝ መሠረት የተረጂዎች ቁጥር 4.5 ሚሊዮን እንደነበር መገለጹን ያስታወሱት አቶ ምትኩ፣ ይህ አኃዝ ይፋ ከተደረገ በኋላ መንግሥት በአብዛኛው ምላሽ ሲሰጥ መቆየቱን፣ በተወሰነ ደረጃ የዓለም ምግብ ፕሮግራምና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አካል ያልሆኑ ድርጅቶች ማለትም በካቶሊክ ሪሊፍ ሶሳይቲ ሥር የሚንቀሳቀሱ ተቋማት ለድርቅ ጉዳተኞች ድጋፍ ሲያደርጉ መቆየታቸው ተገልጿል፡፡ የበልጉ ዝናብ በመዛባቱ የተከሰተው የምግብ እጥረት 4.5 ሚሊዮኖችን ጉዳት ላይ ጥሏል ቢባልም፣ የክረምቱ ዝናብም በኢልኒኖ ሳቢያ ዘግይቶ ከመግባት ባሻገር በመጠንና በሥርጭት ስለተዛባ የዕለት ደራሽ ዕርዳታ ፈላጊዎች ቁጥር ከ4.5 ሚሊዮን ወደ 7.4 ሚሊዮን፣ ቀጥሎም ወደ 7.7 ሚሊዮን ሊደርስ ችሏል፡፡ በአሁኑ ወቅት ግን የዕርዳታ ፈላጊዎች ቁጥር 8.2 ሚሊዮን መድረሱ ታይቷል ያሉት አቶ ምትኩ፣ ይህ ቁጥር ከዚህ ቀደም በሴፍቲኔት ፕሮግራም የታቀፉት 4.4 ሚሊዮን ሰዎች ያካተተ እንደሆነም አስታውቀዋል፡፡ 

አቶ ምትኩ በሪፖርተር ተጠይቀው እንዳብራሩት፣ መንግሥት ከራሱ መጠባበቂያ ፈንድና ከክልሎች በተዋጣ በጀት አራት ቢሊዮን ብር ወይም 192 ሚሊዮን ዶላር ለዕርዳታ ማዋሉንና እንደሚቀጥልበትም ገልጸዋል፡፡ መንግሥት ለአስቸኳይ ዕርዳታ እየዋለ ካለው ገንዘብ ውስጥ አብዛኛውን ከፌደራል መጠባባቂያ ፈንድ ቢያወጣም፣ ክልሎችም በራሳቸው ከያዟቸው የመጠባበቂያ ፈንድ በጀት ለድርቁ ሰለባዎች ማዋላቸው ተነግሯል፡፡ 

የኦሮሚያ ክልል 565 ሚሊዮን ብር በክልሉ ለተጎዱ ሰዎች ሲያውል፣ የአፋር ክልል በበኩሉ 100 ሚሊዮን ብር በመመደብ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል ተብሏል፡፡ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደርም ተመሳሳይ ዕርምጃ በመውሰድ ተጎጂዎችን እየታደገ መሆኑ ተገልጿል፡፡ በከፍተኛ መጠን የድርቅ ተጎጂዎች ካሉባቸው ክልሎች መካከል አፋር ትልቁን ቦታ ይይዛል፡፡ ሶማሌ ክልልም በተጎጂነት ከፍተኛውን ድርሻ ከሚይዙት ክልሎች ውስጥ ሲካተት የደቡብ፣ የአማራና የትግራይ ክልሎችም በድርቅ ምክንያት ተጎጂዎች የሚገኙባቸው ሆነዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ እስካሁን ለተረጂዎች የተገዛውን 450 ሺሕ ሜትሪክ ቶን ስንዴ ጨምሮ አንድ ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ስንዴ እንደሚገዛ ይፋ አድርገዋል፡፡ በጠቅላላው ከ620 ሺሕ ሜትሪክ ቶን በላይ ስንዴ ለመግዛት ዓለም አቀፍ ጨረታ መውጣቱን አቶ ምትኩ አስታውቀዋል፡፡ 

ይህም ቢባል ግን ከዚህ ቀደም በተመድ የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት ጥሪ ያቀረበበት አስቸኳይ የዕርዳታ መጠን 450 ሚሊዮን ዶላር (ከ9.4 ቢሊዮን ብር በላይ) ሊያስፈልግ እንደሚችል የሚጠቁም እንደነበር መዘገቡ ይታወሳል፡፡ እስካሁን ግን ይህ ነው የሚባል ድጋፍ አለመገኘቱን መንግሥት አስታውቋል፡፡ አቶ ምትኩ በጽሕፈት ቤታቸው ካነጋገሯቸው የውጭ ዕርዳታ ለጋሾች መካከል የእንግሊዝ ዓለም አቀፍ ልማት መሥሪያ ቤት (ዴፊድ) 45 ሚሊዮን ፓውንድ (ከ1.4 ቢሊዮን ብር በላይ)፣ የስዊዝ ትብብር ተቋም ሰባት ሚሊዮን የስዊዝ ፍራንክ (152.74 ሚሊዮን ብር) ለመለገስ ቃል ከመግባታቸው ውጪ፣ ሌሎቹ ተቋማት ዕርዳታ ለመስጠት ፍላጎት እንዳላቸው ከመግለጽ በቀር ቃል የገቡት የገንዘብ መጠን አልነበረም፡፡ 

መንግሥት ድርቅ ያስከተለው ከባድ አደጋ ከቁጥጥሩ ውጪ እንዳልሆነ ለለጋሽ አገሮች፣ ለተመድ ኤጀንሲዎች ተወካዮችና ለዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅቶች ያብራሩት አቶ ምትኩ፣ በአንፃሩ ከእነዚህ አካላት የተጠበቀውን ያህል ምላሽ አለመገኘቱን ጠቅሰዋል፡፡ የሰብዓዊ ዕርዳታ ከዓለም አቀፍ ለጋሾች ማግኘት አስቸጋሪ ከሆነባቸው ምክንያቶች መካከል፣ በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የተከሰቱ ቀውሶች የኢትዮጵያን የድርቅና የሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦት ቸል እንዲባል ሰበብ መሆናቸውን ሲገልጹ ተደምጠዋል፡፡ 

በዓለም የምግብ ፕሮግራም የቀጣናው አስተባባሪና በብሔራዊ አደጋ መከላከልና ዝግጁነት ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ጆን አይሊፍ የተመራው የለጋሾች ቡድን፣ በኢትዮጵያ የተከሰተው አስከፊ የድርቅ አደጋ አስቸኳይ ምላሽ እንደሚያስፈልገው ከስምምነት በመድረስ፣ በጥቅምት ወር ማብቂያና በኅዳር ወር መጀመሪያ አካባቢ ተጠቃሎ ይፋ እንደሚወጣ የሚጠበቀውን ሪፖርት በመንተራስ፣ የጉዳተኞች መጠንና የሚያስፈልገው የገንዘብ መጠን ምን ያህል እንደሚሆን በግልጽ እንደሚታወቅ ገልጸዋል፡፡

ይህም ሆኖ በጠቅላላው ለኢትዮጵያ የድርቅ ሰላባዎች ያስፈልጋል ከተባለው 12 ቢሊዮን ብር ውስጥ እስካሁን 258 ሚሊዮን ዶላር ወይም ከ5.1 ቢሊዮን ብር በላይ ከለጋሾች ቢገኝም ጥቅም ላይ በመዋሉ የምግብ፣ የተጨማሪ ምግብ አቅርቦት፣ የግብርና ዘርፍ ላይ ለህልውና የሚያስፈልጉ ምግብ ነክ አቅርቦቶች ከፍተኛ እጥረት መከሰቱን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሕፃናት ፈንድ (ዩኒሴፍ) ለሪፖርተር በላከው መግለጫ ይፋ አድርጓል፡፡ በዚህ መሠረት በመጪዎቹ ሦስት ወራት ውስጥ ለሰብዓዊ ድጋፎች በአስቸኳይ የሚያስፈልገው የገንዘብ መጠን 237 ሚሊዮን ዶላር ወይም ከ4.7 ቢሊዮን ብር በላይ እንደሆነ ዩኒሴፍ ይፋ አድርጓል፡፡ ከዚህ ባሻገር ለልማት ከተያዘው በጀት መንግሥት ወደ አስቸኳይ ዕርዳታ መዋል እንዳለበት ዩኒሴፍ አሳስቧል፡፡ የዴንማርክ ኤምባሲም የዩኒሴፍ ጥያቄን አስተጋብቷል፡፡ በዓለም ላይ በተከሰቱት ሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ አደጋዎች ሳቢያ የዕርዳታ ሽሚያ በማጋጠሙ፣ መንግሥት ለልማት ሥራዎች ከሚያውለው ፈንድ ውስጥ ለድርቁ ተጎጂዎች የሚውል ገንዘብ እንዲመድብ ጠይቋል፡፡

  ሴቭ ዘ ችልድረን ኢትዮጵያ ለለጋሾች ቡድን እንዳስታወቀው፣ በኢትዮጵያ የተከሰተው ድርቅ የከረረ  መሆኑን፣ መንግሥት ምላሽ የሰጠበት መንገድ ከወትሮው የተለየና ያልተለመደ ፍጥነት የታየበት እንደሆነ አስታውቋል፡፡ ሆኖም አስቸኳይ ዕርዳታ ካልተገኘ ግን አስከፊ የምግብ እጥረት ሊከሰት እንደሚችል ሥጋቱን ይፋ አድርጓል፡፡ የካናዳ ኤምባሲና የአሜሪካ ዓለም አቀፍ የልማት ኤጀንሲ (ዩኤስኤአይዲ) መንግሥት መረጃ በመስጠትና ድርቅ በከሰተባቸው አካባቢዎች ፈጣን ግምገማ በማካሄድ ያገኛቸውን ውጤቶች በማሠራጨት በኩል ጥሩ ሥራ መሥራቱን ገልጸዋል፡፡ አቶ ምትኩ በበኩላቸው ዘንድሮ በተከሰው ድርቅ መንግሥት ትልቁን ድርሻ በመያዝ የዕለት ደራሽ ዕርዳታ ከማቅረብ በተጨማሪ፣ ዕለታዊ መረጃዎችን ለለጋሾች በመስጠት ግልጽነት የተሞላበት ግንኙነት መመሥረቱን አስታውቀዋል፡፡ 

 

 

 

የመንግሥት ቤቶች ኤጀንሲ ለተሿሚዎች መኖሪያ ቤት ማቅረብ ተቸግሯል

የመንግሥት ቤቶች ኤጀንሲ በተለይ ሰሞኑን ለተሾሙ ሚኒስትሮችና የተወካዮች ምክር ቤት አባላትን ጨምሮ፣ ከምክትል ዋና ዳይሬክተር በላይ ሹመት በሚሰጣቸው የመንግሥት ተሿሚዎች የሚሰጠው በቂ ቤት እንደሌለው አስታወቀ፡፡

በሌላ በኩል ላለፉት 24 ዓመታት አዳዲስ መኖርያ ቤቶችን እንዳይገነባ የተደረገው የመንግሥት ቤቶች ኤጀንሲ፣ ለተሿሚዎች የሚያቀርበው መኖርያ ቤት በማጣቱ ነባር ነዋሪዎችን ለማስለቀቅ መዘጋጀቱን ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ የተቋሙ ከፍተኛ ባለሙያ ገለጹ፡፡ 

ከ600 በላይ የመንግሥት ተሿሚዎች የመኖርያ ቤት ጥያቄ አቅርበው ምላሽ እየተጠባበቁ ቢሆንም፣ ኤጀንሲው ለተሿሚዎች የሚያቀርበው መኖርያ ቤት በማጣቱ ሦስት አማራጭን ለከተማ ልማትና ቤቶች ሚኒስቴር አቅርቧል፡፡ 

የመጀመርያው አማራጭ ለዘመናት በኪራይ ቤት ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ግለሰቦችን ማፈናቀል ነው፡፡ ሁለተኛው አማራጭ በቤት ልማት ፕሮግራሞች እየተገነቡ ያሉ ኮንዶሚኒየሞችና ከግለሰቦች ደግሞ ሪል ስቴት ቤቶችን መግዛት ነው፡፡ ሦስተኛው አማራጭ በራሱ አቅምና በጀት መኖርያ ቤቶችን መገንባት የሚሉት መሆናቸው ታውቋል፡፡ 

ነገር ግን የተሿሚዎቹ የመኖርያ ቤት ፍላጎት አጣዳፊ በመሆኑና የመኖርያ ቤት ግዢም ሆነ ግንባታ አማራጮች ወቅታዊ ምላሽ ለመስጠት የማያስችሉ በመሆናቸው፣ ኤጀንሲው ትኩረቱን ተከራዮችን ማፈናቀል ላይ ማድረጉ እየተነገረ መሆኑን ጥቅምት 2 ቀን 2008 ዓ.ም. በግዮን ሆቴል በተደረገ ስብሰባ ላይ የተገኙ ተሳታፊዎች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

ኤጀንሲው ‹‹የተሻሻለው የቤቶች አስተዳደር በግል ርዕስ ባወጣው መመርያ ቁጥር 41/2007 አንቀጽ 3 ለመንግሥት ተሿሚዎች (ብቻ) ቤቶች እንደሚሰጥ አስቀምጧል፡፡ ከእነዚህ ውስጥም ለፌዴራል መንግሥት፣ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ ከኃላፊነት ለሚነሱ ባለሥልጣናት መኖርያ ቤት ይሰጣል ይላል፡፡ በመመርያው ለነዋሪዎች መኖርያ ቤት እንደሚሰጥ የሚገለጽ አንቀጽ አልተቀመጠም፡፡

በዚህ መሠረት ከመንግሥት ቤቶች ኤጀንሲ በግለሰብ ደረጃ ቤት መከራየት የሚታሰብ አለመሆኑን በርካታ ነዋሪዎች እየተናገሩ ነው፡፡ ከዚህ ባሻገርም የኤጀንሲው ነባር ተከራዮች የመፈናቀል አደጋ እያንጃበበብን ነው በማለት ሥጋታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ፡፡ 

በአሁኑ ወቅት ይህ አደጋ ሊያንዣብብ የቻለው ለመንግሥት ባለሥልጣናት አዲስ ሹመት ከመሰጠቱ በተጨማሪ፣ ለአምስት ዓመታት ያገለገሉ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የሥራ ጊዜያቸውን ጨርሰው በአዲስ መተካታቸው ነው፡፡ ይህ ሁኔታ አሳሳቢ ሊሆን የቻለው በርካታ አዳዲስ ተሿሚዎች የመኖርያ ቤት ጥያቄ እያቀረቡ ሲሆን፣ ከነባሮቹ የፓርላማ ነዋሪዎች መኖርያ ቤቶች ውስጥ 155 የሚሆኑት አገልግሎት ለመስጠት የማይችሉ በመሆናቸው ልዋጭ ያስፈልጋል በመባሉ ነው፡፡ 

ይህ ጉዳይ ገኖ ባይወጣም የመንግሥት ቤቶች ኤጀንሲ በ2008 የሥራ ዕቅድ ላይ ከተከራይ ደንበኞቹና ከባለድርሻ አካላት ጋር ጥቅምት 2 ቀን 2008 ዓ.ም. በግዮን ሆቴል ባደረገው ውይይት በተወሰነ ደረጃ ተነስቷል፡፡ 

ውይይቱን በንግግር የከፈቱት የመንግሥት ቤቶች ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ኃይለ ማርያም ዓለም ሰገድ፣ ‹‹የመንግሥት ቤቶች ኤጀንሲ ከዚህ በኋላ ቤት የሚያቀርበው ለመንግሥት ተሿሚዎች ብቻ ነው፤›› ካሉ በኋላ፣ ኤጀንሲው 17 ሺሕ ቤቶችን እንደሚያስተዳድር ገልጸዋል፡፡ ከእነዚህ ቤቶች ውስጥ የሲኤምሲ አፓርታማዎችን ጨምሮ የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የሚኖሩባቸው 141 አፓርትመንቶች ሲኖሩት፣ እነዚህ አፓርትመንቶች 5,294 ቤቶች አሏቸው፡፡ ኤጀንሲው እነዚህን አፓርትመንቶች ለማስተዳደር አዲስ መመርያ ማዘጋጀቱን አቶ ኃይለ ማርያም አስታውቀዋል፡፡ 

የአፓርትመንት አስተዳደር፣ አጠቃቀምና አጠባበቅ ረቂቅ መመርያ ላይ፣ በኤጀንሲው ደንበኞች በተቋቋሙ የአፓርታማ ነዋሪዎች ማኅበራት ተወክለው ከተገኙና ከተለያዩ አካላት ከተወከሉ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል፡፡ 

ተከራዮች የተከራዩትን ቤት እንዴት መያዝ እንዳለባቸው ማለትም የንፅህና አጠባበቅ፣ በየሕንፃዎቹ ላይ የተከራዩ ደንበኞች አንዱ የሌላውን መብት ሳይነካ የሕንፃውን ደኅንነት ጠብቀው መኖር እንዳለባቸውና ችግር የሚፈጥር ካለ ቤቱን እስከማስለቀቅ የሚደርስ ቅጣት እንደሚጣልበት በዝርዝር በረቂቅ መመርያው ተካተዋል፡፡ 

ኤጀንሲው፣ ‹‹የደንበኞቼን ደኅንነት ለመጠበቅ የቤቴን ደኅንነት መጠበቅ ግዴታ አለብኝ›› በማለት የሕንፃዎቹን ውበትና ንፅህና ለመጠበቅ ያዘጋጀውን ረቂቅ መመርያ ለተወያዩ ካስተዋወቀ በኋላ፣ መድረኩን ለተሳታፊዎች ክፍት አድርጓል፡፡ 

የውይይቱ ተሳታፊዎች የመመርያው መዘጋጀት ጥሩ መሆኑን በጥቅሉ ከተናገሩ በኋላ ትኩረት የሰጡት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ፣ ‹‹የመንግሥት ቤቶች ኤጀንሲ ከዚህ በኋላ የሚሠራው ለመንግሥት ተሿሚ ኃላፊዎች ብቻ ነው፤›› ለሚለው ጉዳይ ነው፡፡ ‹‹ቤት የምንሰጠው ለመንግሥት ባለሥልጣናት ብቻ ነው መባሉ ያሠጋናል፡፡ እናንተ ከቤታችን ልትወጡ ነው የሚል አባባል ይመስላል፤›› ያሉት ተሳታፊዎቹ ምን ማለት እንደሆነ ማብራሪያ እንዲሰጣቸው ጠይቀው፣ ኤጀንሲው ልብ ሊል የሚገባው የቤት ተከራዮች ታክስ እየከፈሉ አገልግሎት ማግኘት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡ 

ኤጀንሲው ተከራዮችን ሊያዳምጥና ያለባቸው ችግርም ሊመለከት እንደሚገባ ተናግረው፣ ፅዳትንና ዕድሳትን በሚመለከት በረቂቅ መመርያው ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ መቀመጡ ተገቢ በመሆኑ፣ ከኤጀንሲው ጋር ተባብረው ለመሥራት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ 

አንዳንዶቹ ሕንፃዎች ለተለያዩ አገልግሎቶች እየዋሉ በመሆናቸው፣ ኤጀንሲው በጥቃቅን ሥራዎች ላይ ማተኮሩን ተወት አድርጎ የትኛው ሕንፃ ለንግድ፣ የትኛው ለመኖሪያና ለቢሮ መዋል እንዳለበት በመለያየት ሥርዓት እንዲያሲዝላቸው ጠይቀዋል፡፡ ኤጀንሲው ከደንበኞቹ በሚቀርቡለት ጥያቄዎች ላይ ተገቢና አፋጣኝ ምላሽ እንደማይሰጥ የተናገሩት የውይይቱ ተካፋዮች፣ በምርኩዝ የሚሄዱ ጥበቃዎችን ቀጥሮ ሁሉም ነገር የተሟላለት ሕንፃ እንዳከራየ አድርጎ የሚናገረው ተገቢ እንዳልሆነ አስረድተዋል፡፡ 

በውይይቱ ተሳታፊዎች ለተነሱት ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽ የሰጡት የኤጀንሲው የተለያዩ ክፍሎች ኃላፊዎች እንደገለጹት፣ ቤቶች ለመንግሥት ተሿሚዎች ይሰጣሉ ማለት፣ ነባር ተከራዮች ይፈናቀላሉ ማለት አለመሆኑን ተናግረዋል፡፡ በአንድ አፓርትመንት ውስጥ ብዙ ተከራዮች ስላሉ፣ ወደ ሕንፃዎቹ ማን እንደሚገባ፣ ማን እንደሚወጣና ማን ነዋሪ እንደሆነ ለይቶ ለማወቅ፣ እንደሁም በዓለም ደረጃ ሥጋት እየፈጠሩ ያሉ አንዳንድ ችግሮች በዚህም እንዳይከሰቱ የደንበኞቹንም ደኅንነት ለመጠበቅ ጭምር መሆኑን፣ የኤጀንሲው ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ይገዙ አስረድተዋል፡፡ 

ኤጀንሲው ያስጨነቀው የደንበኞቹን ደኅንነት እንዴት መጠበቅ እንዳለበት መሆኑን የሚያሳየው ለ40 ዓመታት በነበረው የኪራይ ተመን አከራይቶ እንደሚገኝ ገልጸው፣ ደንበኞች የሕንፃዎችን ደኅነነት ጠብቀው እንዲኖሩና በአብዛኛው መታደስ ያለባቸው ሕንፃዎች ስላሉ ተባብሮ ለማደስ እንዲቻል ለማድረግ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ዝቅ ባለ የኪራይ ዋጋ የተከራየ ደንበኛ የቤቱን፣ የግቢውንና የአካባቢውን ንፅህና መጠበቅ እንዳለበትም አክለዋል፡፡ 

ለዜጎች ነፃነት ለመታገል ከመኖሪያ ቤታቸው ወደ ትግል ቦታ ወጥተው የነበሩ ታጋዮች በመንገድና በቱቦ ሥር እየኖሩ ባለበት ሁኔታ፣ በአራትና በስድስት ብር የተከራዩ የኤጀንሲው ደንበኞች የቤቱን ንፅህና አለመጠበቃቸው አሳዛኝ መሆኑን የገለጹት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ኃይለ ማርያም፣ ከኤጀንሲው ባከራዩት ቤት አሥር ሕንፃ የሚያስገነባ ሀብት ያገኙ ነጋዴዎች አንድ ጋሎን ቀለም መግዛት አቅቷቸው ሕንፃው ቆሽሾ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡ 

 

የአንጎል የደም ሥሮች ደም የማዘዋወር ሥራቸውን ሲያቋርጡ አለያም በአንጎል ውስጥ ደም ሲፈስ የሚከሰት ድንገተኛና አደገኛ የሕመም ሁኔታ ነው።

የሕመሙን ምልክቶች፤ ለድንገቱ አጋላጭ የሆኑትን ሌሎች የሕመም ዓይነቶች፥ የመከላከያ አማራጮችና እንዲሁም አጣዳፊ የሕክምና እርዳታና ሊገኙ የሚችሉ ውጤቶች የሚመረምር ተከታታይ ዝግጅት ነው።

በሕክምናው ዘይቤ “ስትሮክ” (Stroke) በሚለው መጠሪያው የሚታወቀውን የዚህን የጤና ሁከት ምንነት ጨምሮ ሌሎች ተዛማች ጥያቄዎች የሚመልሱት በዚህ በዩናይትድ ስቴትስ በአትላንታ ከተማ በነርቭና በአንጎል ሕክምና አማካሪ ሃኪምነት በማገልገል ላይ የሚገኙት ዶ/ር ዳንኤል ተስፋዬ ናቸው።

 

ኢሳት ዜና (ጥቅምት 2 ፣ 2015) የህዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ (ህወሐት ) ማእከላዊ ኮሚቴ ከአመታት በፊት በጡረታ የተገለሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ታጋዮች በድጋሚ እንዲደራጁ አዘዘ። ባለፈው እሁድ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በመቀሌ ከተማ ጉባኤ ያካሄደው የህወሀት ማእከላዊ ኮሚቴ፣ በትጥቅ ትግሉ ወቅት እንዲሁም በጡረታ ሰበብ የተሰናበቱ ታጋዮች ዳግም የማደራጀት ስራ እንዲካሄድ ወስኗል። ከአመታት በፊት በእድሜና በተለያዩ ምክኒያቶች …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ኢሳት ዜና (ጥቅምት 2 ፣ 2008 ዓም) በኢትዮጵያና ግብጽ መካከል በአባይ ግድብ ዙሪያ ሊካሄድ የነበረው ድርድር መዘግየትን ተከትሎ፣ የግብፁ ፕሬዚዳንት አብደል ፋታህ አልሲሲ ከሱዳን ጋር የሚመክር የልዑካን ቡድን ወደ ሃገሪቱ ላኩ። በሃገሪቱ የመስኖ ልማት ሚኒስትር ሆሳም ሞግሃዚ የተመራው ይኸው ልዩ የልዑካን ቡድን፣ ከፕሬዚዳን አልሲሲ የተላከን ልዩ መልዕክት በመያዝ ከሱዳን ባለስልጣናት ጋር ለመምከር ካርቱም መግባቱን አል-አህራም …

ኢሳት ዜና (ጥቅምት 2, 2008ዓም) በቅርቡ ወደሶማሊያ የተሰማራው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በደቡባዊ የሃገሪቱ ክፍል ለሁለተኛ ሳምንት ከባድ ውጊያ ኣያካሄደ ኣንደሚገኝ የሶማሊያ ወታደራዊ ባለስልጣናት ትናንት ገለጹ። ለሁለተኛ ሳምንት ቀጥሎ የሚገኘው ግጭት ልዩ ስሙ አልዩ ዲዮ በተባለ ደቡባዊ ምዕራብ የሶማሊያ አካባቢ እየተካሄደ እንደሚገኝ እነዚሁ ወታደራዊ ባለስልጣናት ለጋዜጠኞች አስታውቀዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስቴር በበኩሉ በአካባቢው እየተካሄደ ባለው ውጊያ፣ የኢትዮጵያ …

ጥቅምት ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መንግስትና አለማቀፍ ድርጅቶች በሰጡት መረጃ መሰረት የተረጂው ጠቅላላ ቁጥር 8 ነጥብ 2 ሚሊየን ደርሷል፡፡ መረጃዎች ግን ከዚህ በላይ መሆኑን ያመለክታሉ። የተጠቀሰው አሃዝ ቀደም ሲል በሴፍቲኔት ፕሮግራም ታቅፈው የሚረዱ ወደ 3 ነጥብ 8 ሚሊየን ኢትዮጵያዊን ወገኖችን ይጨምራል ተብሎአል። ይሁን እንጅ መንግስት ያዘጋጀው እና አለማቀፍ ለጋሽ ድርጅቶች የሚጠቅሱት ሰነድ …

ጥቅምት ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦሮምያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን አዳ በርጋ ወረዳ 30 ወጣቶች በኦሮምያ ልዩ ሃይሎች በሌሊት ታፍነው መወሰዳቸውን ሂውማን ራይትስ ሊግ ኦፍ ዘ ሆርን ኦፍ አፍሪካ ገለጸ። ድርጅቱ ለኢሳት በላከው መግለጫ አብዛኞቹ የታሰሩት ወጣቶች የናይጀሪያዊው ባለሀብት ንብረት የሆነው የዳንጎቴ ሲሚንቶ ፋብሪካ ሰራተኞች እና ለእረፍት ወደ ቤተሰቦቻቸው የሄዱ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች …

ጥቅምት ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሽብር ወንጀል ተከሶ በእስር ላይ የሚገኘው ታዋቂው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የእስር ቤት አስተዳዳሪዎች በሚያሳድሩበት ጫና ለተጨማሪ ስቃይ እየተዳረገ መሆኑን የሙያ አጋሮቹ ተናግረዋል። የቀለም ቀንድ ጋዜጣ ስራ አስኪያጅ አቶ አበበ ውቤ እንደገለጹት፣ እስክንድርን ከሁለት የቅርብ የቤተሰብ አባላት ውጭ ሌሎች ሰዎች እንዳይጥቁት ተከልክለዋል። በሃይማኖት አባቶችም ሆነ በጠበቃ እንደማይጎበኝ የገለጸው …

ጥቅምት ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኦህዴድ ላለፉት 2 አመታት ከተማዋን ሲመሩ የነበሩትን አቶ አብርሃም አዱላን ወደ ክልል ቢሮ በማዛወር የሻሸመኔ ከንቲባ የሆኑትን ለከተማዋ ከንቲባ አድርጎ ሾሟል። አዲሱ ከንቲባ በሻሸመኔ የሚገኙ ሙስሊም ኢትዮጵያውያንን በማሰቃት የሚወነጀሉ ሲሆን፣ ለአዳማ የተወሳሰበ ችግር መፍትሄ ያመጣሉ ተብሎ እንደማይታመን ምንጮች ይገልጻሉ። ነባሩ ከንቲባ፣ በደባል ሱሶች በመጠመድ ያለፉትን ሁለት አመታት …

እስከ 360 ሺሕ ብር ከፍተኛ ውዝፍ ያለባቸው ተከራዮች እንደሚገኙበት ታውቋል በቤተ ዘመድ የተሸፋፈነው የክፍያው አሰባሰብ የአስተዳደር ጉባኤ አባላቱን አወቃቅሷል በፍሳሽ እና በቃጠሎ አደጋ የተጎዳው ሕንጻ ከዕድሳት ዕጦት ደኅንነቱ ለአደጋ ተጋልጧል *          *          * ሓላፊው፣ በደንቡ መሠረት ለአስተዳደር ጉባኤው የሒሳብ ሪፖርት አቅርበው አያውቁም የበጀት ዓመቱ የኻያ በመቶ የፈሰስ …

ዜጎች በተራ ‹‹ወንጀል›› 14 ከዚህ አለፍ ሲል 28 ቀን እየተቀጠሩ በሚመላለሱበትና በሚጉላሉበት ሀገር፣ አባሪው እንኳ ባልተያዘበት ሁኔታ፣ ይህ ነው የሚባል ምርመራ ሳይደረግ የሳሙኤል አወቀ ገዳይ በ17 ቀን ውስጥ 19 አመት እስራት እንደተፈረደበት ተሰምቷል፡፡ ትናንት ችሎቱን የተከታተሉት ሰዎች በግምት ከምሽቱ ሶስት ሰዓት አካባቢ አዲስ አበባ ለሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች የነበረውን ድራማ በስልክ ሪፖርት ያደርጋሉ፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ […]

The post የሳሙኤልን ገዳይ መደበቅ ያልቻለው ድራማ – ጌታቸው ሺፈራው appeared first on ሳተናው .

የኢትዮጵያ መንግሥት በቀጣይ አምስት አመታት ተግባራዊ ሊያደርጋቸው ባቀዳቸው ነጥቦች ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ሐይለማርያም ደሳለኝ ከተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ጋር ዕርብ ዕለት ተወያይተዋል።

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ጥቅምት ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ለአመት የዘለቀው የቴፒ ግጭት በአካባቢው ለሰፈረው የፌደራል ፖሊስ እና ለፌደራል ባለስልጣናት እንቆቅልሽ ሆነ በቀጠለበት በዚህ ወቅት፣ ባለፈው ቅዳሜ ከሌሊቱ 6 ሰአት ከ45 ደቂቃ ላይ ሚሊኒየም ጎዳና ላይ ወይም ሚካኤል አካባቢ ካሳሁን የተባለ የከተማው ፖሊስ አባል ተገድሏል። ፖሊሱ በቅርቡ ለከተማው ተመድቦ የመጣ ነበር። እርምጃውን የወሰዱት ራሳቸውን የቴፒ ወጣቶች …

ጥቅምት ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባለፈው ቅዳሜ በተነሳው ግጭት ከፖሊስና ከመከላከያ አንዳንድ ወታደሮች ቆስለዋል። የግጭቱ መንስኤ ሁለት የመከላከያ ፖሊስ አባላት በፖሊሶች መደብደባቸው ነው። ከዚህ ቀደም አንድ ፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ ፍቼ አካባቢ ሰፍሮ የሚገኘውን የመከላከያ ሰራዊት አባል ከገደለው በሁዋላ፣ በመከላከያና በፖሊስ መካከል ለወራት የዘለቀ ቁርሾ እንዲፈጠር አድርጓል። ባለፈው ቅዳሜ ሁለት የመከላከያ ሰራዊት አባላት …

ጥቅምት ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሃገሪቱ ከሚገኙ አምራች አካባቢዎች አንዱ በሆነው በየዓመቱ ከሰኔ እስከ ህዳር ወር ድረስ ከፍተኛ የሰራተኛ ቁጥር የሚያስተናግደው የምዕራብ አርማጮኾ ወረዳ ውስጥ በሚገኙ ቀበሌዎች የሚገኙ የጤና ተቋማት ተገቢውን አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችላቸውን በጀት የክልሉ መንግስት ባለመመደቡ በየአመቱ ተገቢውን አገልግሎት መስጠት እንዳልቻሉ የወረዳው የጤና አመራሮችና ባለሙያዎች ተናገረዋል፡፡ በምዕራብ አርማጮኾ ወረዳ ያለው …

ኢትዮጵያ አምና ወደዚያው ከላከችው ስጋ 58.8 ሚ ዶላር አግኝታለች
     የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የኢትዮጵያ የስጋ ምርት ወደ ግዛቷ እንዳይገባ ከአንድ ሳምንት በፊት ጥላው የነበረችውን ማዕቀብ ማንሳቷን ተርኪሽ ዊክሊ ድረገጽ ትናንት ዘገበ፡፡
ከሳምንት በፊት ከኢትዮጵያ ሰባት ስጋ ላኪ ኩባንያዎች ወደ አገሪቱ ከገባው 36 ቶን የበግ ስጋ ጋር በተያያዘ የተፈጠረውን ችግር ተከትሎ አገሪቱ የኢትዮጵያ የስጋ ምርት ወደ ግዛቷ እንዳይገባ ገደብ ጥላ እንደነበር ያስታወሰው ዘገባው፣ ከሚመለከታቸው የኢትዮጵያ መንግስት አካላት ጋር በመነጋገር ችግሩን መፍታት መቻሉን ገልጧል፡፡
ይህን ተከትሎም የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የኢትዮጵያ የስጋ ምርት ወደ ግዛቷ እንዳይገባ የጣለችውን ማዕቀብ ማንሳቷንና አገሪቱ ያሳለፈችው ውሳኔ በዘርፉ የተሰማሩ ኢትዮጵያውያንን እንዳስደሰተ ዘገባው አስረድቷል፡፡
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የኢትዮጵያን የስጋ ምርት በስፋት በመግዛት ቀዳሚዋ አገር እንደሆነችና ኢትዮጵያ ወደ ተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ከምትልከው የምግብ ኤክስፖርት ምርት በአመት በአማካይ 30 ሚሊዮን ዶላር ገቢ እንደምታገኝም ገልጧል፡፡
ኢትዮጵያ ባለፈው አመት ወደ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ከላከችው 11.692 ቶን የስጋ ምርት 58.8 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቷንም ዘገባው አክሎ አስታውሷል፡፡

ጉዳዩን ለአለም የሚያሳውቅ ገለልተኛ አካል እንዲቋቋም ጠይቋል
                                
    ሠማያዊ ፓርቲ፤ በኢትዮጵያ የተከሰተው “ረሃብ”፤ ከገዥው ፓርቲ የፖሊሲ ውድቀት የመነጨ ነው በማለት ችግሩን ለአለም የሚያሳውቅ ገለልተኛ አካል እንዲቋቋምና አለማቀፉ ህብረተሰብ እርዳታውን እንዲለግስ ጠየቀ፡፡ ፓርቲው ከትናንት በስቲያ “ረሃቡ የገዥው ፓርቲ የፖሊሲ ውድቀት ነው!” በሚል ርዕስ በሠጠው መግለጫ፤ ችግሩ ከተፈጠረ በኋላ አለማቀፉ ማህበረሰብ ለዜጐች እርዳታ እንዳያቀርብ መንግስት ጉዳዩን ሲሸፋፍን ቆይቷል ሲል ተችቷል፡፡
“መንግስት የኋላ ኋላ ከአቅሙ በላይ ሲሆንበት ችግሩ እንደተከሰተ ቢገልጽም ዜጐች ተገቢውን እርዳታ በሚያገኙበት መልኩ እርምጃ እየተወሰደ አይደለም” ብሏል ፓርቲው በመግለጫው፡፡ የተከሰተው ችግር የፖሊሲ ውድቀትን ያመላክታል ያለው ሰማያዊ ፓርቲ፤ ገዥው ፓርቲ ቆሜለታለሁ የሚለውን አርሶ አደርና አርብቶ አደር ህይወት ለማሻሻል የረባ ስራ እንዳልሠራ ማረጋገጫ ነው ብሏል፡፡ “ግብርናው ኢኮኖሚውን ይመራል የሚለው በተግባር አልታየም፤ ምክንያቱም ሚሊዮኖች በየአመቱ ለ“ረሃብ” ችግር መጋለጣቸውን ቀጥለዋል” ሲል ገልጿል ፓርቲው፡፡
ለተከሰተው ሀገራዊ ችግር መንግስት አፋጣኝ እርምጃዎችን እንዲወስድ ያሳሰበው ሰማያዊ ፓርቲ፤ ስለ ችግሩ ለኢትዮጵያውያንና ለአለም አቀፍ ማህበረሰብ የሚያስረዳ ገለልተኛ አካል ተቋቁሞ፤ በችግሩ ለተጠቁ ዜጐች መፍትሔ እንዲፈለግ ጠይቋል፡፡
የምግብ እጥረቱ (ረሃቡ) ከተፈጠረባቸው አካባቢዎች መረጃ በማሰባሰብና በማጣራት ለህዝብ በየጊዜው እንደሚያሳውቅ የገለፀው ፓርቲው፤ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ኢትዮጵያውያንና የአለም ህብረተሰብ ከተጐጂዎች ጐን እንዲቆሙ ጥሪውን አስተላልፏል፡፡
መንግስት በበኩሉ፤ ችግሩ የተፈጠረው በአለማቀፍ ደረጃ ከተከሰተው የአየር ፀባይ ለውጥ (ኤሊኖ) ጋር ተያይዞ መሆኑን በመግለፅ፣ በአገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች ዝናብ ባለመዝነቡ የምግብ እጥረት ቢያጋጥምም “ረሃብ” አለመከሰቱን በተደጋጋሚ አስታውቋል፡፡

     በቅርቡ በሳዑዲ አረቢያ በሃጂ ስነስርአት ወቅት በተፈጠረ መጨናነቅ ህይወታቸውን ያጡ ኢትዮጵያውያን ቁጥር 47 መድረሱን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ገልጿል፡፡
ባለፈው መስከረም 13 ቀን 2008 በሳዑዲ አረቢያ ሚና አካባቢ በደረሰ አደጋ ከ1ሺህ በላይ የተለያዩ ሀገር የሃይማኖታዊ ስነ ስርአቱ ተሳታፊዎች ህይወታቸውን ባጡበት ወቅት ኢትዮጵያውያን ላይ አደጋ ስለመድረሱ ወዲያው ማወቅ ያልተቻለ ሲሆን ከቀናት በኋላ 2 ኢትዮጵያን ህይወታቸው ማለፉ ተዘግቦ እንደነበርና ኋላም የሟቾች ቁጥር ወደ 31 ማደጉ ይታወቃል፡፡ ከትናንት በስቲያ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ቁጥሩ 47 መድረሱንና ተጐድተው ሆስፒታል ገብተው ከነበሩት 26 ኢትዮጵያውያን 24 ተሽሏቸው ከሆስፒታል ሲወጡ፣ 2ቱ ተኝተው ህክምና እየተከታተሉ መሆኑ ታውቋል፡፡
ለሃጅ ስነስርአት ወደ ሳዑዲ አረቢያ ሄደው የነበሩ ከ1ሺህ 100 በላይ አማኞች መመለሳቸውንም ምክር ቤቱ አስታውቋል፡፡ በዘንድሮ የሃጂ ስነስርአት ላይ 10ሺ ኢትዮጵያውያን መሣተፋቸውም ታውቋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች ጋር ተወያዩ

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ላይ ከአገር አቀፍ ፓርቲዎች አመራሮች ጋር ውይይት አደረጉ፡፡

ባለፈው ዓርብና ቅዳሜ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክስ ኮሚሽን አዳራሽ በተካሄደ ስብሰባ ላይ ጥሪ የተደረገላቸው 22 የፖለቲካ ፓርቲዎች በውይይቱ ላይ ተሳትፈዋል፡፡ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) እና ሰማያዊ ፓርቲ ‘በዕድገትና በልማት አጀንዳዎች ላይ ከመወያየታችን በፊት፣ በሌሎች አጠቃላይ ፖለቲካዊና አገራዊ ጉዳዮች ላይ መወያየት መቅደም አለበት’ በማለት በስብሰባው እንደማይካፈሉ በማስታወቃቸው በአዳራሹ ሳይገኙ ቀርተዋል፡፡ ባለፈው ዓርብ  በመጀመሪያው የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ አፈጻጸም ላይ በሚኒስቴር ዴኤታ ማዕረግ የብሔራዊ የፕላን ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ጌታቸው አደም አማካይነት ማብራሪያ የቀረበ ሲሆን፣ በዕቅዱ አጠቃላይ አፈጻጸሞችና ጉድለቶች ላይ ከተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችና ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ምላሽ ሰጥተዋል፡፡    

 

  በአሥር ደረጃዎች ተከፋፍሎ ለገበያ ሲቀርብ የነበረው የኢትዮጵያ ቡና ምርት ወደ ስድስት ደረጃዎች ዝቅ ብሎ ለግብይት እንዲበቃ ተወሰነ፡፡

 ከኢትዮጵያ ምርት ገበያ የተገኘው መረጃ እንደሚያስረዳው፣ እስካሁን የአገሪቱ የቡና ምርት በአሥር ደረጃዎች ተከፋፍሎ እንደየደረጃው  ዋጋ እየተሰጠው ሲሸጥ ቆይቷል፡፡

ይህ የደረጃ አሰጣጥ ግን ለአሠራርም ሆነ የአገሪቱ የቡና ምርት ሊያገኝ የሚገባውን ዋጋ እንዳያገኝ በማድረጉ በአዲስ አሠራር እንዲለወጥ ተደርጓል፡፡ በቡና ደረጃዎች አሰጣጥ ላይ የተደረገ ጥናት አዋጭ የሚሆነው አሥር የነበሩትን የቡና ደረጃዎች ዝቅ ማድረግ እንደሚገባ ነው፡፡ 

በዚህ መሠረት የተደረገውን ጥናት የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ባለሥልጣንና ንግድ ሚኒስቴር በመቀበላቸው፣ የ2008 ዓ.ም. የቡና ምርት ከሚገባበት ከታኅሳስ ወር ጀምሮ የኢትዮጵያ ቡና በስድስት ደረጃዎች ተከፋፍሎ ለገበያ እንዲቀርብ መወሰኑን፣ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ኤርሚያስ እሸቱ አረጋግጠዋል፡፡

እንደ አቶ ኤርሚያስ ገለጻ፣ በዚህ ውሳኔ መሠረት ለምሳሌ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ተብሎ ደረጃ ይሰጣቸው የነበሩትን በአንድ ደረጃ ማጠቃለል ያስችላል፡፡ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ የሚሰጣቸው የቡና ዓይነቶች ዋጋ ልዩነት ተቀራራቢ በመሆኑ በአንድ ዋጋ እንዲሸጡ ያስችላል፡፡ የተሻለ ዋጋም ያስገኛል፡፡ በመጋዘን አሠራርም አሥር ቦታዎች ከፋፍሎ ከማስቀመጥ በስድስት ቦታዎች ማስቀመጥ ጊዜና ጉልበትን ይቆጥባል ብለዋል፡፡

በአዲሱ የምርት ዘመን ከታኅሳስ 2008 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆነው ይህ አሠራር፣ በቡና አቅራቢዎችም መደገፉን የምርት ገበያው መረጃ ያመለክታል፡፡

ከአንድ እስከ አምስት ደረጃ የተሰጣቸው ለኤክስፖርት የሚቀርቡ ሲሆን፣ ደረጃ ስድስት የተሰጠው ቡና ደግሞ ለአገር ውስጥ ገበያ የሚውል ነው፡፡

 

 ኤርትራ ዝቅተኛ የኢንተርኔት ተጠቃሚ በመሆን አለምን ትመራለች
   በኢትዮጵያ የኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚ የሆነው ከአጠቃላዩ ህዝብ 1.7 በመቶ የሚሆነው ብቻ ነው መባሉን የአሜሪካው የቢዝነስ መጽሄት ፎርቹን ዘገበ፡፡ኢንተርኔት ላይቭ ስታትስ የተባለው አለማቀፍ ተቋም ያወጣውን መረጃ ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣ እጅግ ዝቅተኛ የኢንተርኔት አገልግሎት አቅርቦት ካላቸው አስር የአለማችን አገራት መካከል ስምንቱ በአፍሪካ አህጉር እንደሚገኙና ኢትዮጵያም አንዷ እንደሆነች በጥናት ተረጋግጧል፡፡በኢንተርኔት አገልግሎት አቅርቦት ዝቅተኛነት ከአለማችን ቀዳሚውን ስፍራ የምትይዘው ኤርትራ መሆኗን የጠቆመው ዘገባው፣ ከአገሪቱ ህዝብ የአገልግሎት ተጠቃሚ የሆነው 0.91 በመቶ ብቻ መሆኑን ገልጧል፡፡ከአውስትራሊያ በስተሰሜን የምትገኘው ቲሞር ሌሴቴ ደሴት በ1 በመቶ፣ ማይንማር በ1.16 በመቶ፣ ብሩንዲ በ1.39 በመቶ እንዲሁም ሴራሊዮን በ1.49 በመቶ በኢንተርኔት አቅርቦት ዝቅተኛነት እስከ አምስተኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል ተብሏል፡፡  ሶማሊያ በ1.51 በመቶ፣ ኒጀር በ1.61 በመቶ፣ ኢትዮጵያና ጊኒ በ1.7 በመቶ እንዲሁም ኮንጎ በ1.92 በመቶ እንደሚከተሉም ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡

ግርማዊ እቴጌ መነን መጋቢት 25 ቀን 1883 ዓም በወሎ ጠ/ግዛት በአምባሰል አውራጃ ልዩ ስሙ ዕጎ ከተባለው ቀበሌ ከጃንጥራር አስፋውና ከወ/ሮ ስሀን ሚካኤል ተወለዱ። እቴጌ መነን በልጅነት ዘመናቸው በእናት በእባታው ቤት መምህር ተቀጥሮላቸው አማርኛ ማንበብና መፃፍ ጠንቅቀው አወቁ። በተጏዳኝ ልዩ ልዩ የቤት ባልትና ሙያዎችን ተምረው በማጠናቀቃቸው የቤት ራስ ለመባል በቅተዋል፡፡ በ1892 ማለትም በተወለዱ በአሥረኛ አመታቸው ለመጀመሪያ […]

The post ስለ እቴጌ መነን በጨረፍታ (ከስሜነህ ጌታነህ) appeared first on ሳተናው .

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

  መንግስት በጠራው ውይይት ላይ ዋናዎቹ ተቃዋሚዎች አልተሳተፉም
  •  ፓርቲዎቹ መቅደም ይገባቸዋል ሏቸውን ጉዳዮች አስቀምጠዋል

         መንግስት በነደፈው የ2ኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ውይይት ላይ ትናንትናና ዛሬ ተቃዋሚዎች እየመከሩ ሲሆን ዋናዎቹ ተቃዋሚዎች መድረክ፣ ሠማያዊ እና መኢአድ በውይይቱ ላይ አልተሳተፉም፡፡
መንግስት ለሁሉም ተቃዋሚ ፓርቲዎች 20 አባሎቻቸውን አርብና ቅዳሜ በሚደረግ ውይይት ላይ እንዲያሳትፉ በደብዳቤ ያሳወቀ ሲሆን ኢዴፓን ጨምሮ ሌሎች ተቃዋሚ ፓርቲዎች በውይይቱ መሳተፋቸውን ሲያረጋግጡ ዋናዎቹ ተቃዋሚዎች ግን ቅድመ ሁኔታዎችን በማስቀመጥ በውይይቱ ሳይሳተፉ ቀርተዋል፡፡
ሠማያዊ ፓርቲ የመንግስት እቅድ ላይ ለውይይት ከመቀመጤ በፊት በብዙሃን ፓርቲ ዲሞክራሲ፣ በሰብአዊ መብት አያያዝ፣ የነፃ መገናኛ ብዙሃንና ሲቪክ ማህበራትን በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ መወያየት አለብኝ ሲል በቀጥታ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በፃፈው የምላሽ ደብዳቤ አስታውቋል፡፡
“በኢትዮጵያ ሰላምና እድገት እቅድ ላይ ከመወያየት በፊት በተጠቀሱት ጉዳዮች ላይ መወያየት አስፈላጊ ነው” ያለው የፓርቲው መግለጫ፤ መሠረታዊ ጉዳዮች መፍትሔ ባልተበጀላቸው ሁኔታ በዕቅዱ ዝርዝር አፈፃፀም ላይ መወያየት ለኢትዮጵያ እድገትና ብልጽግና ያመጣል ብሎ እንደማያምን በደብዳቤው አመልክቷል፡፡
የመላው ኢትዮጵያውያን አንድነት ድርጅት (መኢአድ) በበኩሉ፤ በውይይቱ ላይ እንዲሳተፉ ከመንግስት በቀረበለት ጥሪ ላይ ስራ አስፈፃሚ ተሰብስቦ መቅደም ያለባቸው ብሔራዊ ጉዳዮች አሉ በማለት ከመሳተፍ መቆጠብን እንደመረጠ ለአዲስ አድማስ አስታውቋል፡፡ ፓርቲው ስብሰባው ላይ ለመሳተፋ የማይችልባቸውን ሶስት ምክንያቶች ጠቅሷል፡፡ የብሔራዊ እርቅና መግባባት ላይ ያተኮረ ስብሰባ በቅድሚያ እንዲጠራም ጠይቋል፡፡
ግዙፉ ብሔራዊ እቅድ ሁሉንም አሣታፊ በሆነ መልኩ ከግብ እንዲደርስ መጀመሪያ ሁሉንም ተቃዋሚ ያሳተፈ የብሔራዊ መግባባትና እርቅ ጉባኤ መጠራት አለበት ያለው ፓርቲው፤ “የልማት መሠረቱ የዜጐችን ሰብአዊ መብት መጠበቅ ስለሆነ የመኢአድ አባላትም ሆኑ ሌሎች የተቃዋሚ አባላት እየተሰቃዩ፣ እየተሳደዱ፣ እየተዋከቡ ባለበትና አጠቃላይ የሰብአዊ መብታቸው በተገፋበት ሁኔታ እንዲሁም ዜጐች ክልልህ አይደለም በሚል እየተፈናቀሉ፣ በስብሰባው ላይ መገኘት ፍሬ ሊሰጥ የሚችል አይደለም” ብሏል፡፡ የሚካሄደው ውይይት ለሠፊው የኢትዮጵያ ህዝብ በሚዲያዎች በቀጥታ የሚሠራጭ ባለመሆኑ ሃሳባችን ተቆራርጦ የተሳሳተ መልዕክት ሊተላለፍ ይችላል በሚል ስጋት ከውይይቱ ራሱን ያገለለው ደግሞ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ነው፡፡
ትናንት በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የስብሰባ አዳራሽ በተደረገው የመጀመሪያ ቀን ውይይት መክፈቻ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ የተገኙ ሲሆን “የተለያዩ የፖለቲካ አቋሞች ቢኖሩም ያለን አንድ አገር በመሆኑ ሁሉም አካላት በአገሪቱ ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ መወያየትና ግብአት መስጠት አስፈላጊ ነው” ብለዋል፡፡ በጠዋቱ ክፍለ ጊዜ በመጀመሪያው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን አፈፃፀም ላይ በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የብሔራዊ ፕላን ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ጌታቸው አደም ጽሑፍ ካቀረቡ በኋላ የፓርቲ ተወካዮቹ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡
የኢዴፓ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ጫኔ ከበደ፤ የውይይት መድረኩ መዘጋጀቱ መልካም መሆኑን ጠቅሰው በመጀመሪያው የእቅድ ዘመን ላይ ተመዘገበ ተብሎ የቀረበው የኢኮኖሚ እድገት አሃዝ ላይ ጥርጣሬ እንዳላቸው ገልፀዋል፡፡ በተለይ የትምህርት ጥራትን ከማስጠበቅና ግብርናን ከማዘመን አንፃር የሚቀሩ ስራዎች እንዳሉ ጠቅሰዋል፡፡ የቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ተወካይ በበኩላቸው፤ የኑሮ ውድነቱ ላይ መንግስት ትኩረት አድርጐ አልሠራም፤ በቀጣይ በትኩረት ሊሠራ ይገባል ያሉ ሲሆን የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ ተወካይ ደግሞ ከመሠረተ ልማት ግንባታና ከሃብት ብክነት ጋር የተያያዙ አስተያየቶች ሰጥተዋል፡፡ ትናንት በመጀመሪያው የእቅድ አፈፃፀም ላይ ውይይት ሲደረግ የዋለ ሲሆን በዛሬው እለት በቀጣይ ሊተገበር በታሰበው ሁለተኛው እቅድ ላይ ውይይት ይካሄዳል ተብሏል፡፡ በውይይት መድረኩ ላይ ኢዴፓ፣ አንድነት፣ ቅንጅት እና ኢራፓን ጨምሮ 20 ያህል ሀገር አቀፍ ፓርቲዎች ተሣታፊ መሆናቸውም ታውቋል፡፡

ዘውዴ ረታ - የታሪኩ ቀንድ ስብራት (1927 – 2008)

‹‹… ዘውዴ! ከእኛ ጋር ተመሳሳይ ከሆነው ትውልድ መካከል እንደ አንተ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን መንግሥት አመራር በቅርብ የማየትና የመረዳት ዕድል ያገኘ ብዙ ሰው የለም፡፡ ቀጥሎ ደግሞ ያየውንና የተረዳውን፣ ጣዕም ባለው ጽሑፍ

አብራርቶ ለመግለጽ ተሰጥኦ ያለው እንደ አንተ የመሰለ ጸሐፊ ብዙ የለም፡፡ ስለዚህ በእኔ አመለካከት ሁለት የተጣመሩ ዕድሎች በአንተ እጅ ተይዘው ይገኛሉ፡፡ እነዚህም ታሪኩን የማወቅና የጽሕፈት ችሎታህ ናቸው፡፡ ስለዚህ እኔ አጥብቄ አደራ የምልህ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን መንግሥት ጉዳይ አንተ ዕድል አጋጥሞህ ያየኸውንና ከአዋቂዎች ዘንድ ቀርበህ ያጠናኸውን እውነተኛውን ታሪክ ገልጠህ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ጻፍለት፡፡ ለዚህ ሕዝብ ከአንተ በኩል ከዚህ የበለጠ የምታደርግለት ሊኖር አይችልም፡፡ አንተም አስበህ የጀመርከውን ለመፈጸም እግዚአብሔር ይርዳህ፡፡ … እኛም ወዳጆችህ፣ ዕድሜና ጤና አግኝተን የምትደክምበትን ለማንበብ ያብቃን…›› 

ከአሥራ ሁለት ዓመታት በፊት ነበር ታዋቂው የታሪክ ምሁር ፕሮፌሰር መርዕድ ወልደ አረጋይ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት አመራርን በቅርቡ የማወቅ ዕድል ለነበራቸው፣ ከእልፍኝ እስከ አደባባይ ከንጉሠ ነገሥቱ ያልተለዩትን ዘውዴ ረታን እውነተኛው ታሪክ ገልጠህ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ጻፍለት ብለው የተማፀኗቸው፡፡ 

ይህን የማበረታቻ ምክር መቼም ያልረሱት ዘውዴ ረታ አምና እጅግ ግዙፍ የሆነውን ‹‹የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት›› አንደኛ መጽሐፍ ከነገሡበት 1923 እስከ 1948 ዓ.ም. ድረስ የሚሸፍነውን ታሪክ ለንባብ አደባባይ ያዋሉት፡፡ 

የአዲሱ መጽሐፋቸውንም የተለየ ፋይዳም እንዲህ አስቀምጠውታል፡፡ ‹‹እንግዲህ ማንም ሰው በቀላሉ እንደሚረዳው ኢትዮጵያ የነፃነት ችግር ያጋጠማት በሁለት ኮሎኒያሊስት በሆኑ አገሮች ነው፡፡ የመጀመሪያው የፋሽስቱ የሙሶሊኒ የግፍ ወረራ ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ ነፃ አውጪዎች ነን ብለው በመጡት ወዳጆቻችን በምንላቸው በእንግሊዞች ወታደራዊ የሞግዚት አስተዳደር የተፈጸመብን በደል ነው፡፡ ከእነዚህ ከሁለቱም ኮሎኒያሊስቶች የኢትዮጵያን ነፃነት ለማስመለስ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት የደረሰበት መከራና ፈተና በቀላሉ የሚገመት አይደለም፡፡ ይህን ሁሉ በተለይ አዲሱ ትውልድ እንዲያውቀው ስለሚያስፈልግ፣ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ታሪኩ በተቻለ መጠን ተዘርዝሮ ቀርቦለታል፡፡›› 

ጋዜጠኛ፣ ዲፕሎማትና ስመጥር የታሪክ ጸሐፊ (ሦስት ዓይና) የነበሩት አምባሳደር ዘውዴ ረታ በዘመናዊት ኢትዮጵያ ታሪክ ከዳግማዊ አፄ ምኒልክ ዕረፍት በኋላ የነበረውን የልጅ ኢያሱን፣ የንግሥት ዘውዲቱ፣ ብሎም የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመን ታሪክ ትክክለኛውን ሒደት የዘመኑም ሆነ መጪው ትውልድ ማወቅ ያስፈልጋል በሚል ነበር የታሪክ መጽሐፋቸውን ‹‹ተፈሪ መኰንን ረዥሙ የሥልጣን ጉዞ›› ለኅትመት ያበቁት፡፡ ‹‹በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት የኤርትራ ጉዳይ 1941-1963›› ሌላው በመረጃና በማስረጃ የተደገፈ ታሪካዊ መጽሐፍንም እነሆ ብለዋል፡፡ 

የኤርትራን ጉዳይ የተመለከተው መጽሐፋቸው ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ እንዲገነዘበው በዶ/ር ኃይሉ ሃብቱ አማካይነት “THE ERITREAN QUESTION” በሚል ተተርጉሞ ለሕትመት ዝግጁ መሆኑም ይነገራል፡፡ 

የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ሕገ መንግሥቱ ከተሻሻለበት ከ1948 ዓ.ም. በኋላ የነበረውን በለውጥ የታጀበው ዓቢይ ዘመን የሚያወሳውን መጽሐፍ በማዘጋጀት ላይ ነበሩ አምባሳደር ዘውዴ ረታ፡፡ በተለይ በለንደን (እንግሊዝ)፣ ፓሪስ (ፈረንሣይ) እና ሮም (ኢጣሊያ) ኢትዮጵያን የሚመለከቱ ስለ ዘመነ ኃይለ ሥላሴ የሚያወሱ ሚስጥራዊ ሰነዶች በቅርቡ ክፍት መሆናቸውን ተከትሎ፣ ጥናትና ምርምር ለማድረግ ነበር መስከረም 12 ቀን 2008 ዓ.ም. ወደ ባሕር ማዶ ያቀኑት፡፡ ያለሙት የዘመናት ሕልም እውን ሳያደርጉት ተቀጨ እንጂ፡፡ ሞት ቀደማቸው፡፡ የጥናታቸው ቀዳሚ መነሻ ባደረጉት ለንደን ከተማ መስከረም 26 ቀን 2008 ዓ.ም. በድንገት አርፈዋል፡፡ 

በኢጣሊያና በቱኒዚያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው ያገለገሉት አቶ ዘውዴ ረት የተወለዱት በአዲስ አበባ ከተማ በ1927 ዓ.ም. ነው፡፡ የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን የተከታተሉት በፊት ደጃዝማች ገብረ ማርያም የአርበኞች ትምህርት ቤት በሚባለው፣ ከዚያም ሊሴ ገብረ ማርያም በተባለው ትምህርት ቤት ነበር፡፡ በኢትዮጵያ ሬዲዮ አንባቢነትና በቤተ መንግሥት ዜና አቅራቢነት ተቀጥረው ያገለገሉ ሲሆን፣ በፈረንሣይም በጋዜጠኝነት ተመርቀዋል፡፡ በኢትዮጵያ ድምፅ ዕለታዊ ጋዜጣና ወርኃዊው መነን መጽሔት ዳይሬክተርም ነበሩ፡፡ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የፓን አፍሪካን ኒውስ ኤጀንሲ ፕሬዚዳንት፣ የማስታወቂያ ረዳት ሚኒስትር፣ የውጭ ጉዳይ ምክትል ሚኒስትርም ነበሩ፡፡ በዘመነ ደርግ የስደት ዘመናቸውም በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ውስጥ በዓለም አቀፍ የእርሻ ልማት ፈንድ የመንግሥታት ግንኙነትና የፖለቲካ ኃላፊ ሆነው ለ13 ዓመታት አገልግለዋል፡፡ 

ሦስት ዓይናው ዘውዴ ረታ በኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ለሃያ ሁለት ዓመት በላይ ላበረከቱት ውጤታማ ተግባር ከንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት የምኒልክ የመኰንን ደረጃና የኢትዮጵያ የክብር ኮከብ አዛዥ መኰንን ኒሻን ተሸልመዋል፡፡ ከተለያዩ አገሮችም ኒሻኖችን የተሸለሙ ሲሆን፣ ከቅርብ ዓመታት ወዲህም በባሕር ማዶና በአገር ውስጥም ልዩ ልዩ ሽልማቶች ተበርክተውላቸዋል፡፡ 

ከ49 ዓመት በፊት ከወይዘሮ ገሊላ ተፈራ ጋር ጋብቻ መሥርተው ሦስት ልጆች ያፈሩት አምባሳደር ዘውዴ አስከሬን፣ በሳምንቱ መገባደጃ ከእንግሊዝ መጥቶ ሥርዓተ ቀብራቸው በአዲስ አበባ እንደሚፈጸም ከቤተሰቦቻቸው የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡ 

 

ኤልያስ ገብሩ አንጋፋው ጋዜጠኛ ሙሉጌታ ሉሌን በአካል አላውቀውም፤ በኢትዮጵያ የጋዜጠኝነት ሕይወት ግን ስማቸው ገንኖ ከወጡ ሰዎች መካከል በቀዳሚዎቹ ተርታ የሚሰለፍ መሆኑን ጠንቅቄ አውቃለሁ፡፡ የሞቱን መርዶ፣ አርአያ ተስፋማርያም በፌስ ቡክ ገጹ ጽፎት ካረዳን ጀምሮ፣ በምናቤ ሙሉጌታን ማሳላሰሌ አልቀረም፡፡ ድንገተኛ ሞቱ ልብ ይነካል፤ ከውድ ሀገር ርቆ መሞት ደግሞ ልብ ይሰብራል!!! ጋዜጠኛ መስፍን ነጋሽ ስለሙሉጌታ የተለየ የአጻጻፍ ዘዬውን […]

The post እስከመቼ ስደት …እስከመቼ በባዕድ ሀገር ሞት … እስከመቼ መንገላታት …እስከመቼ ሀዘን …. appeared first on ሳተናው .