የባለሞያ ቡድኑ ሰብሳቢ አቶ ታደሰ አሰፋ፡- ለባለሞያ ቡድኑ ይህ ታሪካዊ ዕድል ተሰጥቶን ችግር ፈቺ ጥናት እንድናጠና በመደረጋችን ምስጋናችን ከፍ ያለ ነው፡፡ የጥናት ሰነዱ የካህናት፣ የምእመናንና የሰንበት ት/ቤቶች ወጣቶች ሐሳብ የተካተተበት በመኾኑ ከአኹን በኋላ የመላው የቤተ ክርስቲያኒቱ አማኞች ሰነድ ነው ብለን እናምናለን፡፡ ለዝግጅቱ መሳካት አስተዋፅኦ ያደረጉ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ የሀ/ስብከቱ ሓላፊዎችና አገልጋዮች፣ የክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት …

የማዕከላዊት አፍሪቃ ሪፓብሊክ ሰሜናዊ ጎረቤት ፣ ቻድ፣ ከአካባቢው ሃገራት ፤ በጦር ኃይል ይበልጥ የደረጀች መሆኗ ይነገርላታል። በፕሬዚዳንት ኢድሪስ ደቢ የምትራው ቻድ፤ የማዕከላዊት አፍሪቃ ሪፓብሊክን ውዝግብ ለመፍታት ፤ ራሷ በምትፈለገው መልክ ውሳኔ

በየመን እስር ቤት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እስረኞች የፍትህ ያለህ እያሉ ነው። ከ 15 ዓመታት በላይ በየመን እስር ቤት ውስጥ እየተሰቃዩ እንደሚገኙ የገለጹት እነዚሁ ኢትዮጵያውያን እስረኞች ያለኣንዳች ማስረጃ ከ 25 ዓመት እስከ ይሙት በቃ ተፈርዶብናል ባይ ናቸው።

የአንድን ሀገር ወግ፤ ባህል፤ ታሪክ እና ሁለንተናዊ ጉዞን ለማወቅ፤ የህዝቦችዋን ባህላዊ የበዓል አከባበር፤ ስነ-ፅሁፎችዋን በተለይ ደግሞ ስነ- ግጥሞችዋን ተመልከት ሲሉ አንዳንድ ምሁራን ይገልፃሉ። በአሁኑ ወቅት በርካታ ገጣምያን በግጥም መድረኩ ሲሳተፉ ይታያል፤ በግጥም፤ እምቅ አድናቆትን በግጥም እምቅ ፍላጎትን፣

ካርቱሞች፥ የጠላቶቻቸዉን ቁርጥር መቀነስ፥ የደከመ ምጣኔ ሐብታቸዉን መጠገን ይሻሉ።አማፂያኑ፥ጁባዎች ዉጊያ ሲገጥሙ የዲፕሎማሲ፥ የገንዘብ፥ የመሳሪያ ምንጫቸዉ ካናቱ ተበጥብጧል።ሌፍ እንደሚሉት የደቡብ ሱዳን ጦርነት ለደቡብ ኮርዶፋን «ሳይደግስ አይጣላም» አይነት ነዉ-የሆነዉ።ቢያንስ ለጊዜዉ።

የካቲት ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሶማሊ ክልል በቀላፎ አካባቢ የሚኖሩ 19 የየረር ባሬ ጎሳ የአገር ሽማግሌዎች በክልሉ ውስጥ የተፈጸመውን ከፍተኛ እልቂት ለጠ/ሚንስትሩ አቤት ለማለት ወደ አዲስ አበባ በሄዱበት ወቅት  አካባቢውን በሚጠብቁ ልዩ ሃይሎች ተይዘው መታሰራቸውን ከስፍራው የደረሰን መረጃ አመልክቷል። ከእስር ያመለጡ አንዳንድ ሽማግሌዎች በትናንትናው እለት ወደ አዲስ አበባ በመሄድ ከዚህ ቀደም በልዩ …

የካቲት ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦሮሚያ ክልል በቡሌ ሆራ ወረዳ፣ በሀገረማርያም ከተማ ከአርሴማ ቤተክርስቲያን ጋር በተያያዘ የተነሳውን የውስጥ ችግር ተከትሎ ችግሩን ለመፍታት የተመረጡት የሰበካ ጉባኤ አባላት ታስረው የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ከተጠየቀባቸው በሁዋላ ህዝቡ ባሰማው ከፍተኛ ተቃውሞ የአገር ሽማግሌዎቹ በዛሬው እለት የተፈቱ ሲሆን፣ ህዝቡ በድል አድራጊነት ስሜት በሆታ አጅቦ ወደ ቤተክርስቲያን ወስዷቸዋል። …

የካቲት ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ አሸባሪ ካላቸው ግንቦት ሰባት እና ሌሎች ፖለቲካ ድርጅቶች ጋር ግንኙነት አላቸው ተብለው የተጠረጠሩ በርካታ የአዲስ አበባና አማራ ክልል ወጣቶች ወደ ማዕከላዊ እስር ቤት እየተጋዙ መሆኑን የአይን እማኞች ተናገሩ፡፡ ኢህአዴግ በጀመረው አዲስ አሰሳ በሀገሪቱ አንድንድ ቦታዎች ኢንተርኔትን ጨምሮ ስልክ እንዳይሰራ የተደረገ ሲሆን በአንዳንድ አካባቢዎችም የመከላከያ ሀይል ተበትኗል፡፡ …

የካቲት ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአዲስ አበባ መስተዳድር የካቲት 2፣ 2006 ዓም ከእድር ተጠሪዎች ጋር ባደረጉት ስብሰባ እያንዳንዱ እድር በነፍስ ወከፍ 8 ሺ ብር ለአባይ ግድብ ማሰሪያ እንዲከፍል ታዟል። ትእዛዙ የተጣለው የካቲት 2 ቀም 2006 ሲሆን፣ 650 እድሮች በነፍስ ወከፍ 8 ሺ ብር ይከፋላሉ። በዚሁ ከላይ በወረደው መመሪያ መንግስት ከእድሮች በአንድ ጊዜ …

የካቲት ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በቅርቡ በጋዜጠኛ መሳይ መኮንንና የኢሳት የኮምፒዩተር ባለሙያ በሆነው ተቀማጭነቱ ቤልጂየም በሆነው የኢሳት ባልደረባ ላይ የተገኙ ባእድ የመሰላያ ሶፍትዌሮች ከጣሊያኑ ሃኪንግ ቲም የተላኩ መሆናቸውን ሲትዝን ላብን በመጥቀስ ታዋቂው ጋዜጣ ዋሽንግተን ፖስት ዘግቧል። ጋዜጣው ባወጣው ሰፊ ዘገባ መረጃዎችን ከኮምፒዩተሮች ላይ ለመውሰድ የሚያስፈልገው ባእድ ሶፍትዌር የተላከው ከጣሊያን ኩባንያ ጋር ቢሆንም፣ …

(ለ1966ቱ አብዮት 40ኛ ዓመት ማስተዋሻ)
በአብዮቱ ዘመን አንድ ጓድ ከዚህ ቀጥሎ የተጠቀሰውን ቃለ መጠይቅ በመስጠቱ ለ17 ዓመታት ወኅኒ ተወርውሮ ነበር፡፡ በ1983 ዓም ከወኅኒ ሲወጣ ሰውዬው አርጅቷል፡፡ ከዘራውን ተደግፎ ቤቱ በረንዳ ላይ ይቀመጥና ቃለ መጠይቁ የታተመበትን ጋዜጣ እያየ ‹‹ይህን ቃለ መጠይቅ የሰጠሁት ዛሬ ቢሆን ኖሮስ?›› ብሎ ይጠይቃል፡፡ ለሰውዬው መልስ ለመስጠት ቃለ መጠይቁን አንብቡት፡፡

ጋዜጠኛ፡- ለእርስዎ ሀብት ክፍፍልን በተመለከተ በካፒታሊዝምና በሶሻሊዝም መካከል ያለው ልዩነት ምንድን ነው?

ጓድ፡- በካፒታሊዝም እኩል ያልሆነ የሀብት ክፍፍል ሲኖር፣ በሶሻሊዝም ደግሞ እኩል የሆነ የድኽነት ክፍፍል አለ

ጋዜጠኛ፡- ጭቆናን በተመለከተ በካፒታሊዝምና በሶሻሊዝም መካከል ልዩነቱ ምንድንነው?

ጓድ፡- በካፒታሊዝም ሰው ሰውን ይጨቁናል፣ በሶሻሊዝም ግን ፓርቲ ሰውን ይጨቁናል

ጋዜጠኛ፡- ለምሳሌ በሰሐራ በረሃ ውስጥ ሶሻሊስት ሪፐብሊክ ቢመሠረት ምን ለውጥ ሊያመጣ ይችላል ብለው ያስባሉ?

ጓድ፡- ከሦስት ዓመታት በኋላ ሀገሪቱ አሸዋ ከውጭ ማስመጣት ትጀምራለች

ጋዜጠኛ፡- በሶሻሊዝም አስተሳሰብ ደመወዝና ሠራተኛን እንዴት ይገልጧቸዋል?

ጓድ፡- በሶሻሊዝም ሠራተኛም በሚገባ የሠራ ለመምሰል ጥረት ያደርጋል፣ መንግሥትም ተገቢውን ደመወዝ የከፈለ ለመምሰል ጥረት ያደርጋል

ጋዜጠኛ፡- ገበያ የሚመራው በአቅርቦትና ፍላጎት ነው ይባላል፡፡ ይህንን ሃሳብ በሶሻሊዝም እንዴት ይገልጡታል?

ጓድ፡- በሶሻሊዝም የፈለግከውን ነገር መርጠህ አትገዛም፤ ነገር ግን የቀረበልህን ነገር ትገዛና፣ ከገዛህ በኋላ እንድትፈልገው ይደረጋል፡፡

ጋዜጠኛ፡- አንዳንድ ሰዎች የሶሻሊስት ፓርቲው ጋዜጣ በጣም ትልቅ ነው ይላሉ፤ ለምንድን ነው ትልቅ የሆነው?

ጓድ፡- ምክንያቱም ሰው እርሱን መያዝ ስለሚያፍር፣ የጋዜጣው ስፋት ስታነበው ፊትህን ለመሸፈን የሚበቃ መሆን አለበት

ጋዜጠኛ፡- በዓለም ላይ ሰባቱ አስደናቂ ነገሮች የሚባሉ አሉ፡፡ በሶሻሊዝም አስተሳሰብ ሰባቱ የዓለም አስደናቂ ነገሮች ምን ምን ናቸው ብለው ያስባሉ?

1.         ሁሉም ሰው ሥራ አግኝቷል

2.       ሁሉም ሰው ሥራ ቢያገኝም ቅሉ ማንም ሰው ግን ሥራ እየሠራ አይደለም(ስብሰባ፣ ግምገማ፣ የፓርቲ ሥራ፣ የአካባቢ ልማት ማኅበር ሥራ አለበት)

3.       ማንም ሰው ሥራ እየሠራ ባይሆንም እንኳን ሁሉም ሰው ግን ሀገሪቱ ያወጣችውን የዕድገት ዕቅድ ግቡን እንዲመታ አድርጓል

4.       ምንም እንኳን ሁሉም ሰው ዕቅዱን ተግባራዊ ቢያደርገው፣ ነገር ግን ምንም ዓይነት ውጤት አልተገኘም

5.       ምንም እንኳን ምንም ዓይነት ውጤት ባይገኝ፣ ነገር ግን ሁሉም ሰው የፈለገው ነገር ሁሉ እንዲኖረው ተደርጓል

6.       ምንም እንኳን ሁሉም ሰው የፈለገው ነገር ሁሉ ቢኖረው፣ ሁሉም ሰው ግን በሆነው ነገር ርካታ የለውም

7.       ምንም እንኳን ሁሉም ሰው በሆነው ነገር ሁሉ ርካታ ባይኖረው፣ ፓርቲው ግን የሕዝቡን 100%ድጋፍ አለው፡፡

እነዚህ ናቸው ሰባቱ አስደና ቂነገሮች፡፡

ጋዜጠኛ፡- ፓርቲው የሚመራባቸው ሦስቱ መሠረታውያን ሕግጋት ምንድን ናቸው?

ጓድ፡- ሶሻሊዝም ሩጫ ነው፤ በዚህ ሩጫ ውስጥ የፓርቲው መርሖዎች ሦስት ናቸው፡፡ የመጀመሪያው ሩጫው እንደተጀመረ ሯጮቹን ሁሉ ማሰናከልና የመሪነቱን ቦታ መያዝ ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ የሩጫውን ፍጥነት መቆጣጠር መቻል ነው፡፡ የመጨረሻውም በተቻለ መጠን ሩጫውን ሳያጠናቅቁ የመሮጫው ትራክ ላይ ረዥም ጊዜ ለመቆየት መቻልነው፡፡

ጋዜጠኛ፡- አንድ የእርስዎ ጓድ በአብዮታዊው ጦር ተይዘው በቀደም ወደ ወኅኒ ቤት ገብተዋል፡፡ ምን ጎድሎባቸው ነው ፀረ አብዮት የሆኑት፤ አብዮቱ ሁሉን ነገር አሟልቶላቸው ነበር?

ጓድ፡- ጓዱን የያዙት ሰዎችም ይህንን ነበር የጠየቁት፡፡ እርሱ ወደ አሜሪካ ለመሄድ በዝግጅት ላይ ነበር፡፡ ዝግጅቱን ሲያጠናቅቅ የመውጫ ቪዛ እንዲሰጠው አመለከተ፡፡ ይህንን የሰሙ ወታደሮች ከሌሊቱ በስምንት ሰዓት ወደ ቤቱ መጡ፡፡ በሩን ሰብረው ገቡና ‹‹አብዮቱ ቤት ሰጥቶሃል፣ መኪና ሰጥቶሃል፣ መሬት ሰጥቶሃል፣ የንግድ ድርጅት ሰጥቶሃል፣ሥልጣን ሰጥቶሃል፣ ከውጭ ዕቃ ያለ ቀረጥ እንድታስገባ ዕድል ሰጥቶሃል፤ ለምንድን ነው ወደ አሜሪካ መሄድ የፈለግከው›› ሲሉ ጠየቁት፡፡ እርሱም ተናድዶ ‹‹እንዲህ ከሌሊቱ በ8 ሰዓት እኔ ሳልፈቅድላችሁ በሬን ሰብራችሁ በመግባት እንዳትረብሹኝ ስለምፈልግ ነው አገር ጥዬ የምሄደው›› ብሎ መለሰላቸው፡፡ ለዚህ ነው ያሠሩት፡፡

ጋዜጠኛ፡- የእርስዎ ጓድ ብቻ ሳይሆኑ የጎረቤትዎ ልጅም መታሠሩን ሰምተናል፤ ልጁ በጣም ትንሽ ልጅ ነው፡፡ ደግሞም በጣም የታወቀ ዋናተኛ ነው፡፡ የታሠረውም ባለፈው ግዮን ሆቴል ዋና ተለማምዶ ሲመለስ ነው ይባላል፡፡ ምክንያቱን ሊነግሩን ይችላሉ?

ጓድ፡- እንደ ሰማሁት ከሆነ ልጁ የታወቀ ዋናተኛ ነው፡፡ አባቱ በሌለው ገንዘብ ከፍሎለት ግዮን ሆቴል ዋና ይለማመዳል፡፡ የፓርቲያችን ሊቀ መንበር በዚያ ቀን ዋና ለመዋኘት ግዮን ሄደው ነበር፡፡ በአጋጣሚ ዋና እየተለማመዱ ሳለ ወደ መካከል ሄደው ሊሰምጡ ደረሱ፡፡ አጃቢዎቻቸው ዋና የሚችሉ አልነበሩም፡፡ ልጆች ናቸው ተብለው በአካባቢው እንዲንቀሳቀሱ የተፈቀደላቸው የታሠረው ልጅና ሁለት ጓደኞቹ ብቻ ነበሩ፡፡ ሮጠው ገቡና ሊቀ መንበሩን ከመስመጥ አዳኗቸው፡፡ ጓድ ሊቀ መንበርም ለዚህ ውለታቸው አንዳች ሽልማት ሊሰጧቸው ፈለጉና ልጆቹን ጠየቋቸው፡፡ አንደኛው ልጅ ብስክሌት መረጠ፤ ሁለተኛው ልጅ ደግሞ የመጨዋቻ መኪና ጠየቀ፤ ይኼ የጎረቤቴ ልጅ ግን የአካል ጉዳተኞች መሄጃ ጋሪ መረጠ፡፡ ጓድ ሊቀ መንበርም በጣም ተገረሙና ‹‹ምን ያደርግልሃል፤ አንተ ሙሉ ጤነኛ ነህ›› አሉት፡፡ ልጁም ‹‹አባቴ እርስዎን ከሞት ማዳኔን ከሰማ እግሬን ይሰባብረዋል፤ ለዚያ ብዬ ነው›› አላቸው፡፡ በዚህ ተናደው ነው ያሳሠሩት፡፡

ጋዜጠኛ፡- ባለፈው ሰሞን ለሥራ ጉብኝት ወደ ቻይና ተጉዘው ነበር፡፡ በዚያ ጊዜ በአንድ ቻይናዊ፣ ኢትዮጵያዊና ዴንማርካዊ የፓርቲ ሰዎች መካከል የተፈጠረ ነገር እንደነበር ሰምተናል፡፡ ሊነግሩን ይችላሉ?

ጓድ፡- አዎ፤ አራታችን በአንድ ወንዝ ዳር ቆመን ስንዝናና አንድ ጋዜጠኛ መጣና ‹‹ሥጋ ለማግኘት ሲባል ሰልፍ ስለመያዝ ምን ታስባላችሁ?›› ሲል ጠየቀን፡፡ ዴንማርካዊው ‹‹ሰልፍ ማለት ምንድን ነው?›› ሲል መልሶ ጠየቀ፤ ቻይናዊውም ቀጠል አደረገና ‹‹ሥጋ ምንድን ነው?›› ሲል አከለበት፡፡ የኛው ፖለቲከኛ ደግሞ ‹‹ማሰብ ማለት ምንድን ነው?›› ብለው ጋዜጠኛውን መልሰው ጠየቁት፡፡ ይኼ ነው ታሪኩ፡፡

ጋዜጠኛ፡- በዚሁ አጋጣሚ አብዮታዊ መሪያችን በቻይና ለነበሩ ጋዜጠኞች የሃሳብ ነጻነትን አስመልክቶ አስደናቂ ነገር ተናግረዋል ይባላል፤  ምን ነበር?

ጓድ፡- ጋዜጠኛው የሃሳብ ነጻነት እያሉ ምዕራባውያን ሶሻሊስት ሀገሮችን ለመበጥበጥ ይሞክራሉ፤ እናንተ ይህንን ችግር እንዴት ፈታችሁት? ብሎ ጠየቃቸው፡፡ እርሳቸውም ‹እኛ መጀመሪያውኑ ሃሳቡ እንዳይኖር ስላደረግነው ነጻነት መስጠት አይጠበቅብንም› ብለው መልሰውለት በጣም ተደንቆ ነበር፡፡ ?

ጋዜጠኛ፡ – እኛ ራሳችን ስሕተታችንን ገምግመን ማሻሻል ባለመቻላችን ሌሎች ስሕተቶቻችንን ዐውቀው እየተጠቀሙበት ነው የሚል ትችት ሰንዝረው ነበር፡፡ አንድ ማሳያ እንኳን ሊነግሩንይችላሉ፡፡

መልስ፡- ይህንን ድክመት እንኳን ነጻ ሆኖ የሚከታተለን ሕዝብ ይቅርና ፀረ አብዮት ናቸው ብለን ያሠርናቸው እንኳን በሚገባ ዐውቀውታል፡፡ አንድ ቀላል አስቂኝ ነገር ልንገርሽ፡፡ አንድ ባልዋ ፀረ አብዮት ሆኖ የታሠረባት ሴትዮ አለች፡፡ ሴትዮዋ ድኽነቱ ሲመራት በቤቷ ጓሮ ድንች ተክላ መሸጥ ፈለገች፡፡ ግን ጉልበት ከየት ይምጣ፡፡ ሰው እንዳትቀጥር፣ ገንዘብ ከየት ይገኝ፡፡ በመጨረሻ ለባልዋ እንዲህ የሚል ደብዳቤ ጽፋ በወኅኒ ቤቱ በኩል ላከችለት ‹‹በጓሯችን ድንች ልተክል ነበር፡፡ ነገር ግን ማን ይቆፍርልኛል፤ አንተ እንዳታግዘኝም ገና ሁለት ዓመት ይቀርሃል›› ባልዋም ‹‹ጓሮውን ስትቆፍሪ ተጠንቀቂ፤ እጅግ ውድ የሆኑ ነገሮችን ደብቄበታለሁ›› ብሎ መልሶ ላከላት፡፡ ደብዳቤው በደረሳት ሌሊት ፖሊሶች መጥተው የተደበቀውን ነገር ፍለጋ የቤቷን ጓሮ ከጥግ እስከ ጥግ ቆፋፈሩት፡፡ እርሷም በድንጋጤ ከረመችና ‹‹ስድስት ፖሊሶች መጥተው የሆነ ነገር ፍለጋ ጓሮውን በቁፋሮ እንዳልነበረ አደረጉት፤ ያልቆፈሩት መሬት የለም፤ ምን ባደርግ ይሻለኛል?›› ስትል ጻፈችለት፡፡ ባሏም ‹‹አሁንማ ቆፍረውልሻል ድንችሽን ትከይ›› ብሎ መለሰላት፡፡

ጥያቄ፡- ይኼ የመጨረሻ ጥያቄያችን ነው፡፡ ባለፈው ጊዜ በአውሮፕላን ሲጓዙ አንድ ያልታወቀ ፍጡር አውሮፕላኑን እየተከተለ አስቸግሮ ነበር ይባላል፡፡ ፓይለቱና አስተናጋጆቹ ሊያባርሩት አልቻሉም፡፡ በአውሮፕላኑ የነበሩት የሃይማኖት አባቶችም ከዐቅማቸው በላይ ሆኖ ነበር፡፡ እርስዎ ግን የሆነ ነገር ሲያሳዩት እንደ ጢስ በኖ እንደ ጉም ተኖ ጠፋ ይባላል፡፡ ምን እንዳሳዩት ሊነግሩን ይችላሉ?

መልስ፡- እነርሱ ይህንን ያህል ገንዘብ እንሰጥሃለን አሉት፤ አልሄደም፤ የሃይማኖት አባቶችንም አልፈራም፡፡ ወደ እኔ ቀረብ ሲል ‹‹የወጣት ሊግ አባል ነው የማደርግህ›› ስለው በድንጋጤ ጥሎ ጠፋ፡፡

አመሰግናሉ፤ ስለ ቃለ መጠይቁ

አደራ ይኼ ቃለ መጠይቅ ከታተመ የሆነ ቦታ አንድ ቅጅ እንዲቀመጥ፡፡ ምናልባት ከሃያ ዓመት በኋላ እንዳገኘው

(መነሻ ሃሳብ Jokes of the Velvet Revolution)

ኳታር፣ ዶሃ

© ይህ ጽሑፍ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት የወጣ ነው

የአንድነት አባል በመሆኑ በሚያስተምርበት ትምህርት ቤት አስተዳደር የተለያዩ ዛቻዎችና ማስጠንቀቂያዎች እየደረሱበት እንደሆነ የሚናገረው መምህር አማኑኤል መንግስቱ “ከዚህ በፊትም ያለምንም ምክንያት ከማስተምርበት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አንስተው ወደ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አውርደውኛል፡፡” በማለት በመንግስት ኃላፊዎች የደረሰበትን በደል ለፍኖተ ነፃነት አስረድቷል፡፡ ተደጋጋሚ ዛቻ እየደረሰበት መሆኑንና በቅርቡም ከስራው ሊያፈናቅሉት እንዳቀዱ ጨምሮ አስረድቷል፡፡ መምህር አማኑኤል ላይ እየደረሰ ስላለው […]

ፖለቲካ ጥበብ ነው፤ አንዳንዶች ‘የማመቻመች ጥበብ’፣ አንዳንዶች ‘የማጭበርበር ጥበብ’፣ ሌሎች ‘art of possible’ ይሉታል። አንዳንዴ እውነተኛ የሕዝብ ተቆርቋሪዎች እያሉ አስመሳዮች ያሸንፋሉ፤ ሐሳብ አፍላቂዎቹ እያሉ ሰራቂዎቹ ይመሰገናሉ። ሌሎች ፖለቲካ ጫወታ (game) ነው ይሉታል። ለብዙዎች የጨቀየ ጫወታ ነው፤ ለጥቂቶች ግን ጥበብም ጫወታም ነው። ተጫዋቾቹ ደግሞ በጨዋታው ሕግ (rule of the game) መሠረት መጫወት አለባቸው።

በእኛ አገር ‘ፖለቲካ’ እና ‘ፖለቲከኝነት’ ዛሬም አፍላ ነው። እስከዛሬ ጉልቤው ገዢ ነው፣ ገዢው ወሳኝ ነው። ምንም ዓይነት ፖለቲካዊ ጥበብ የሚጠይቅ የፖለቲካ ፉክቻ የለም። በአገራችን የፖለቲካ ፓርቲዎች ዕድሜ 40 አይሞላም። በጠብ መንጃ ተነድቶ ሥልጣን ላይ የወጣ እንጂ በፖለቲካ ፉክክር ተንጓሎ የወጣ ፓርቲ የለም።

የፖለቲካ ፓርቲዎች ተቃዋሚ እና ገዢ ተብለው ፉክክር ውስጥ የገቡት በኢሕአዴግ ዘመን ነው። ሆኖም ከምርጫ 97 በኋላ ኢሕአዴግ በዴሞክራሲ ጉዳይ ላይ ስልታዊ ማፈግፈግ በማድረጉ ፓርቲዎች ትግሉን ከዜሮ እንዲጀምሩ አስገድዷቸዋል፤ ያውም በጠበበ ምኅዳር።

ከምርጫ 97 ወዲህ በተደረጉ የፖለቲካ ሽኩቻዎች ውስጥ ኢሕአዴግ በዝረራ ያሸነፈባቸው አጋጣሚዎች ብዙ ናቸው። ለዚህ መንስኤው ከኢሕአዴግ ዴሞክራሲያዊ ንፉግነት ባሻገር የተቃዋሚዎቹም ድክመት ተጠቃሽ ነው። ተቃዋሚዎች ፕሮግራሞቻቸውን በማስተዋወቅ እና ደጋፊ በማበርከት ረገድ ጉልህ ችግር አለባቸው። ሕዝቡ ተቃዋሚ መሆናቸውን አውቆ እንዲሁ እንዲመርጣቸው ይፈልጋሉ እንጂ የሚመርጥበትን ምክንያት ሊያስረዱት አይከጅሉም። ስለተቃዋሚዎች ድክመት ብዙ ተብሏል፤ እኔም አሁን አንዱን ነቅሼ ላወራ ነው – ሰው ፊት አቀራረብ (presentability)።

የተቃዋሚ አመራሮች ለፖለቲካ ክርክር፣ ለጋዜጣዊ መግለጫ ወይም ለቃለ ምልልስ ሕዝብ/ካሜራ ፊት ሲቀርቡ የሚኖራቸው አለባበስ፣ ንቃተ-ፊት እና አነጋገር ዝርክርክነት ሰዎች “ሲሪዬስሊ” እንዳይወስዷቸው ከሚያደርጉ  እንቅፋቶች አንዱ ነው። እዚህጋ ሁለት ትችቶች ሊነሱ ይችላሉ፤ አንደኛው ‘ፖለቲከኞች ማስመሰል አለባቸው ወይ?’ የሚለው ነው። የጫወታው ሕግ የሚጠይቅ ከሆነ አዎ! ሰዎች መጀመሪያ በሚያዩት ነገር ተማርከው ጆሮ ይሰጣሉ፣ አነጋገሩን አድምጠው ነገሩን ያጤናሉ። የመጀመሪያውን ፈተና ያላለፈ ቀጣዩን የመደመጥ ዕድል አያገኝም፣ ያንን ዕድል ያገኘ አነጋገሩን ካላሳመረ ነገሩን ገዢ አያገኝም። ሦስተኛው ደረጃ ላይ ያለው የመጨረሻው እና ወሳኙ ፈተና ነው።

‘የለም፤ ይህንን መጽሐፉን በሽፋኑ የሚዳኙትንም ጭምር መታገል አለብኝ’ የሚል ፖለቲከኛ፣ ፖለቲከኛ ሳይሆን አራማጅ (ለውጥ አማጭ) ነው መሆን የሚችለው።

ሮብ ያንግ የተባለ “Power Dressing” የተሰኘ መጽሐፍ ደራሲ ከፎርብስ ጋር ባደረገው ቃለ ምልልስ ፖለቲካን በሚያህል የአገር ዕጣ ፈንታ በሚወሰንበት ጉዳይ ስለአለባበስ ማውራት ብዙ ሰዎችን ያሳፍራቸዋል፣ ግን አማራጭ የለም ብሏል። “Politics wants to present itself as a serious institution about substantive issues, rather than a popularity contest based on what the contenders look like. But the fact is that fashion… can be mighty powerful political currency.”

አንዱና ትልቁ ችግር ፖለቲከኞች ራሳቸውንና ሕዝቡን ከአለባበሱ እና አቀራረቡ አልፈው ለመመልከት ቢሞክሩም ሕዝቡ የእነሱን አለባበስና አቀራረብ አስቀድሞ መገምገሙን አለማቆሙ ነው። ስለዚህ በጥቃቅን የአቀራረብ (presentability) ሳቢያ ትልቁ ቁምነገር ሰሚ ከሚያጣ፣ ትንሽ ዋጋ መክፈል ያዋጣል።

የፖለቲካ ፓርቲዎቻችን በተለይ ተቃዋሚዎች ይህንን ጉዳይ በቅጡ ያጤኑት አይመስልም። አቶ ይልቃል (ኢ/ር) ሰማያዊ ፓርቲን ወክለው የሰጧቸው ቃለምልልሶች ላይ የወጡ ፎቶዎቻቸው በሙሉ ጉስቁልቁል ያሉና ኮታቸው ተዛንፎ ወይም ከትከሻቸው የሰፋ መስሎ ነው። ዛሬ (የካቲት 6/2006) መግለጫ ሲሰጡ ያየኋቸው የሁለት ተቃዋሚ ፓርቲ አመራር አባላት፣ ጠረጴዛው ኋላ ሳያቸው ለአቀራረባቸው እንዳልተጨነቁ ያሳብቅባቸዋል። አለባበሳቸው የአዘቦት ዓይነት ነው፤ ‘ፎርማል’ በሚባል ሁኔታ እንኳን አልለበሱም። አንዱ ሲናገር ሌለኞቹ አንዱ አገጩን ተደግፎ፣ ሌላኛው በዚህንኛው ንግግር ያልተደሰት በሚመስል አኩርፎ፣ አንደኛውም ጉስቁል ባለ መልኩ ተቀምጠው ያደምጡታል። በኔ እምነት፣ አንዱ ሲናገር ሌላኛው በተቻለ መጠን የፊት ገጽታውን ሳያዘባርቅ፣ ቀጥ ብሎ ቢቀመጥ ሌላው ቢቀር የታዳሚዎችን ሐሳብ ከተናጋሪው አይሰርቅም።

ሌላው ጉዳይ የንግግር ዘዬ ጉዳይ ነው። በፖለቲካ አምባ፣ አንደበተ ርቱዕነት ወሳኝ ቁም ነገር ነው። እነ ልደቱ አያሌው፣ ብርሀኑ ነጋ፣ መለስ ዜናዊ፣ ሀብታሙ አያሌው የዚህ አንደበተ ርቱዕነት ማሳያ ናቸው። ይህ የሚያውቁትን አሳምሮ፣ የማያውቁትን አድበስብሶ የማሳለፊያ ጥበብ ለፖለቲከኞች ቁልፍ በመሆኑ ሌላው ዓለም ሥልጠና ሳይቀር ይወስዱበታል። የመጨባበጥ ሒደት፣ የእንግዶች /ካሜራ/ ፊት እንቅስቃሴ፣ የእጅ ውዝዋዜ ሳይቀሩ ይጠናሉ። ግለሰቦችን በአንቱታ እና ትክክለኛ ማዕረጋቸውን ሳያዛንፉ መጥራትም ራሱን የቻለ በልምምድ የሚገኝ ጥበብ ይጠይቃል፤ ትርፍም አለው።
የእኛ ፖለቲከኞች ለዚህ ቁብ አይሰጡትም። መወዳደሪያ እሴት ነው ብለው የሚያስቡም አይመስሉም። በመንግሥት በጀት ፕሮቶኮል የሚቀጠርላቸው ጠቅላይ ሚኒስትራችን ሳይቀሩ በኔልሰን ማንዴላ ቀብር ላይ ከሰው ሁሉ የተለየ አለባበስ ለብሰው የታዩት፣ እዚህ ግባ የማይባል ንግግር ያደረጉት በዚሁ ሳቢያ ነው። አነዚህ የአቀራረብ ቅንብሮች ተደማምረው ነው አንድን መሪ ሞገስ ያለው (charismatic) ነው፣ አይደለም የሚያስብሉት። ሰዎቹ፣ ብንወዳቸውም ብንጠላቸው አገራችንን ወክለው ሲቀርቡ ሞገስ ቢኖራቸው መልካም ነው።

በጥቅሉ ሲታይ ግን ተቃዋሚዎች ከገዢው አንፃር የመሪ-ሞገስ አልባ ናቸው ማለት ይቻላል። ገፅታ አይቶ በሚዳኝ ሕዝብ ውስጥ እየኖሮ ለአቀራረብ አለመንጠንቀቅ ዋጋ ያስከፍላል። ያንን ዋጋ ደግሞ ተቃዋሚዎች አይችሉትም።

መኢአድና አንድነት ፓርቲ በአንድነት ፓርቲ ጽ/ቤት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጡ፡፡
ከአንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) እና ከመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) የተሰጠ መግለጫ !!!!
ብአዴን ኢህአዴግ የአማራን ህዝብ የመምራት የሞራል ልዕልና የለውም፤ ህዝብ ያዋረዱ አመራሮቹም ለፍርድ ሊቀርቡ ይገባል፡፡

Image
የኢትዮጵያ ህዝብ እንደሚገነዘበው በዚህች ታሪካዊት እና የጥቁር ህዝብ ድል ማዕከል፤ የነፃነት ተምሳሌትና የአፍሪካ ህዝብ ኩራት በሆነች ሀገር የኋላ ዘመን ውጣ ውረድ ውስጥ ሰፊው የአማራ ህዝብ ከመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር በአንድ ተሰልፎ ለሀገር ግንባታ ተኪ የሌለው ሚና ተጫውቷል፡፡ በዚህም የተነሳ በአምባገነኖች ጡጫ ተደቁሷል፡፡ ዛሬም እንደ ትላንቱ በገዢዎቹ እየተረገጠ ያለ ህዝብ ነው፡፡
ይህ ህዝብ እንደትላንቱ ሁሉ ዛሬም በየጋራው እና በየሸንተረሩ ተበታትኖ የኔ እንዳይላት እንኳን በተነፈገው ኩርማን መሬት አፈር እየገፋ ለመኖር መዳረጉ ሳያንስ የኢህአዴግ ፖለቲካ ሌላ ሰቀቀን ጨምሮ ‹‹ጨቋኝ ገዥ መደብ የነበረ፤ ትምክህተኛ›› በሚል ጎራ መድቦ ያልዘራውን ግፍ እንዲያጭድ እያደረገው እንደሆነ ይስተዋላል፡፡
የአማራ ህዝብ እንደሌላው ጭቁን የኢትዮጵያ ህዝብ ሁሉ ዘመኑ ባነበራቸው የአገዛዝ ሥርዓቶች የጭቆና ቀንበር ተጭኖት፤ የግፍ ፅዋ የተጋተ መሆኑ ከመላው የኢትዮጵያ ህዝብ የተሰወረ አይደለም፡፡
ይሁን እንጂ ይህንን ህዝብ እወክላለሁ የሚለው የትላንቱ ኢህዴን የዛሬው ብአዴን ያፈራቸው አመራሮች ስልጣን በመቆናጠጥ የገዛ ህዝባቸውን ከመናቅና ከማዋረድ አልፈው ‹‹ትላንት ሽርጣም ያለህ ትምክህተኛ አንገቱን ይድፋ ዛሬ ተራው ያንተነው›› በማለት በግፍ እንዲገደል ማድረጋቸው ሰቆቃው ከህዝብ ህሊና ሳይወጣ አቶ መለስ ‹‹ጫካ መንጣሪ ሞፈር ዘመት›› ብለው እንደተሳለቁበት ሁሉ በሳቸው ራዕይ አስቀጣይ በዛሬዎቹ የብአዴን አመራሮችም ያው ዘመቻ ተጠናክሮ መቀጠሉ አገዛዙ የደረሰበትን አሳፋሪ ደረጃ በግልፅ ያሳያል፡፡
የክልሉ ምክትል ፕሬዘዳንት እና የብአዴን ጽህፈት ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ አለምነው መኮንን በቅርቡ አደረጉት ተብሎ የተደመጠው አስነዋሪ ንግግርም የክልሉን ህዝብ ብቻ ሳይሆን መላውን የኢትዮጵያ ህዝብ የናቁ እና ያዋረደ፤ የሀገሪቷን ህገ- መንግስት በግልፅ የጣሰ የወንጀል ተግባር ነው፡፡ በተጨማሪም የአማራን ህዝብ ከሌሎች ወንድሞቹ ለመነጠልና አንገቱን ደፍቶ እንዲኖር የተደረገ ዘመቻ ነው፡፡
የኢህአዴግ አገዛዝ በመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ከተጫነበት ጊዜ ጀምሮ በሁሉም ክልል ያለው ህዝብ በራሱ ቋንቋ ተናጋሪዎች በግፍ እየተገዛ፤ ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቱ ተገፍፎ በድህነት አረንቋ ውስጥ እየኖረ ቢሆንም የአማራን ህዝብ እንወክላለን እንደሚሉት ብአዴኖች የሚመራውን ህዝብ በአደባባይ በተደጋጋሚ የዘለፈ፤ ያዋረደ እና አንገት ያስደፋ ድርጅት አለ ለማለት ይቸግራል፡፡
የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) እና አንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የአማራን ህዝብ የመምራት የሞራል ልዕልና የሌለውን ብአዴን ኢህአዴግን ለመታገል መላውን አባላትና ደጋፊዎቻችንን ከጎናችን በማሰለፍ በፅናት እና በብቃት መታገል ያለብን ወሳኝ ጊዜ ላይ እንደሆንን እንገነዘባለን፡፡
መላውን ህዝብ ከዳር እስከ ዳር አንቀሳቅሰን ሰላማዊ ትግሉን ፍሬያማ በማድረግ አገዛዙ እንዲለወጥ እና የኢትዮጵያ ህዝብ ሉዓላዊ የስልጣን ባለቤት እንዲሆን ለማድረግ የጀመርነውን ሰላማዊ ትግል አጠናክረን የምንቀጥል መሆኑን እያረጋገጥን የካቲት 16 ቀን 2006 ዓ.ም በባህር ዳር ከተማ ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ በስርዓቱ ላይ ያለንን ተቃውሞ እናሰማለን፡፡ ይህ ትግል ህዝብ ያዋረዱ አመራሮች በተገቢው ፍጥነት ለፍርድ እስኪቀርቡ በሌሎች የሀገራችን ክፍሎችም ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡
የባህርዳር እና አካባቢው ነዋሪዎችም በነቂስ በመውጣት ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ተቃውሞውን እንዲገልፅ ሀገራዊ ጥሪ እናቀርባለን፡፡

ድል የህዝብ ነው !!!!
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር !!!
የካቲት 6 ቀን 2006 ዓ.ም
አዲስ አበባ

:evil:
ምንሊክ ሳልሳዊ :- ልብ ብለው ከሆነ በዚህ ሳምንት ሕወሓት/እሕኣዴግ በሁለት ጉዳዮች ላይ ተመርኩዞ የተለይዩ ተግባራትን ከውኖ ራሱን አጋልጦ አደባባይ ላይ አምባገነንነቱን አስመንጥሮ ተሽከርክሮ አሸባሪነትን እና አሸባሪዎችን እንዳቀፈ ጉዞውን እየተንገዳገደው ነው::

ሕወሓት በዚህ ሳምንት የራሱ የውስጥ ሽኩቻ እና የኢሕኣዴግ አባል ድርጅቶች የለውጥ እንቅስቃሴ አጣብቂኝ ውስጥ እንደከተቱት ለመውጣት በሚይደርገው መፍጨርጨር ሌላ አዳዲስ የሽብር ድርጊቶቹን ማንገውለል ይዟል:: ያው እንደተለመደው ድሮም እጆች ሁሉ ወደ ሕወሓት ቢያመለክቱም የአሁኑ ለየት ብሎ የራሱን ጣቶች ወደ ራሱ መቀሰሩ ነው::

ሕወሓት/ኢሕኣዴግ እና የሙስሊሙ ጥያቄዎች
ኢሕኣዸግ በህገመንግስቱ መሰረት በወንጀል መከሰስ አለበት::

ሓይማኖት እና ፖለቲካ እንደማይገናኙ መንግስት በሃይማኖት ጣልቃ እንደማይገባ በሕገመንግስቱ የተረጋገጠ ጉዳይ መሆኑ እየታወቀ በገዢው ፓርቲ በኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ላይ የተፈጸመው ወንጀል በሕገመንግስቱ መሰረት ወንጀለኛው ሕወሓት/ኢሕኣዴግ መሆኑ በይፋ ተረጋግቷል:: እስካሁን ድረስ መልስ ያልተገኘለት የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ጥያቄ በመንግስት ማነቆ እና በባለስልጣናቱ ሽብር የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ንጽሕናቸው እየታወቀ ወህኒ ቤት አስቀምጦ የራሱን ፖለቲካዊ መጅሊስ መገንብቱን በይፋ አምኗል:: በሽብር ስልት የገነባው መጅሊስ ላለው ስርኣት ትዛዥ የሚሆን እና የፖለቲካ ታማኞችን ያቀፈ መሆኑ በይፋ ማመኑ ሕወሓት ምን ያህል በሃይማኖቶች ውስጥ አብዮታዊ ዲሞክራሲን አስርጾ ለአገዛዙ በሚያመቸው መንገድ እንደቀረጸው አመነም አላመነም የታወቀውን ጉዳይ ግን በአቦይ ስብሃት በኩል ዘርግፎታል::ከቦሌ የተፈጠረው ሕገወጥ መጅሊስ በህያሉ እና አሸባሪው ሕወሓት እና መሪዎቹ ተጀምሮ እና ተስፋፍቶ እስከሽልምት ደርሶ መንግስት ሕገመንግስቱን እንደጣሰ እና በሃይማኖት ውስጥ ጣልቃ እንደገብ ሲያረጋግጥ የሙስሊሙን መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎችን ንጽሕና እንዳመነ እና ሴራው ለሽንፈት እንደዳረገው ተረጋግጥውል::

ሕወሓት ቅጥረኞቹ እና ተቃዋሚ ፓርቲዎች

እንደፈለጉ ቢናገሩ የማይታሰሩ ሰዎች አሉ አዎ አሉ ከተቃዋሚ ፓርቲ ከጋዜጠኞች እንዲሁም ከሌላው ዘርፍ…ስም መጠቃቀስ አስፈላጊ ባይሆንም ሕወሓት ይህን ሰሞን በየፓርቲው አስርጎ ባስገባቸው ቅጥረኞቹ አማካኝነት..የኣንድነት ኣባላትን
በፓርቲው ውስጥ ጥሩ እንቅስቃሴ የሚያደርጉትን እና ለገዢው ፈታኝ የሆኑ የፖለቲካ ሃሳቦችን የሚያመነጩትን ለይቶ …እንዲሁም የማይታሰሩ እንደፈለጉ የሚለፈልፉ እና የሚጽፉ ጋዜጠኞች እንደ እስክንድር ነጋ ያሉትን ጠንካሮችን አሳልፈው በ24 ሰዓት ያስያዙ ….. አሁንም ሌሎችን ከፕሬሱ እንዲወገዱ የሚሰሩ አስመሳዮች ወዘተ…..

የኣንድነት አመራሮች በሰበብ አስባብ የጻፉትን ጹሁፍ ተገን በማድረግ እና የፈጠራ ምርመራ ጀምሮ ለማዋከብ እና ለማወናበድ እንደገሃዳዊ ምክንያት ተያዘ እንጂ ዋናው የስርኣቱ አላማ ጠንካራ አመራር አባላትን በማሰር ከወዲሁ ፓርቲዉን ለማዳከም የታቀደ እና በውስጥ ቅጥረኞች እየተሰራ ያለው የብተና እና ፓርቲውን በቅጥረኞች ቁጥጥር ስር አውሎ ፓርቲውን ታማኝ ተቃዋሚ ለማድረግ የታቀዳ ሴራ ነው::

የሃይለማርያም መለሳዊ መግለጫ

ጠቅላይ ሚንስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ በወቅታዊ የሀገሪቱ ጉዳይ ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡ ሲሆን የህዳሴ ግድብ ግንባታና ከሱዳንና ግብጽ ጋር ያለውን ድርድር አስመልክቶ ድርድሩ እንዳላለቀ ፣ የኢትዮ ሱዳን የድንበር መካለልን በተመለከተ እየተናፈሰ ያለውን መሬት ለሱዳን ተሰጥቷል የሚለውን ወሬ አስመልክቶም ይህን መሰል ወሬዎች ምርጫ ሊደርስ አካባቢ መነዛታቸው አዲስ አይደለም ያሉ ቢሆንም የድንበሩን ጉዳይ በተመለከተ ካርቱም ሄደው የፈረሙት ፊርማ ሳይደርቅ እንደለመዱት ዘባርቀዋል::

እስከ 6 ወር ድረስ ህዝቡ ይዘናጋል በሚል እደምታ መግለጫቸውን የሰጥኡት የሕወሓቱ የሃሰት ስልጡን ሓይለማርያም የቴሌኮም ችግር በማስፋፊያው ስራ ሳቢያ የተፈጠረ ነው ከ6 ወራት በኋላ ለውጥ ይታያል ሲሉ ሰው ይታዘበኛል ያልፈጠረባቸው አቶ ሃይለማርያም አይን ቀቅለው ሳያበሏቸዋልቀሩም መሰል የአዲስ አበባ የውሃ ችግርንም በተመለከተ 24 ሰዓት ውሃ የሚያገኘው የከተማዋ ክፍል 75% ብቻ እንደሆነና የተቀረውንም ለማስተካከል መንግስት ይሰራል በማለት ከባድ የሆነ ውሸት ለጥፈው ዞር ብለዋል:: የውጭ ምንዛሪ እጥረትንና የባንኮች የብድር መስጠት ብቃት መመናመንን አስመልክቶ የተነሳውን ጥያቄ ጠቅላይ ሚንስትሩየእውቀት እጥረት ይሁን ሃቅን ማድበስበስ በቂ ማብራሪያ አልሰጡበትም፡፡ምንሊክ ሳልሳዊ

ከአንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) እና ከመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) የተሰጠ መግለጫ !!!! ብአዴን ኢህአዴግ የአማራን ህዝብ የመምራት የሞራል ልዕልና የለውም፤ ህዝብ ያዋረዱ አመራሮቹም ለፍርድ ሊቀርቡ ይገባል፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ እንደሚገነዘበው በዚህች ታሪካዊት እና የጥቁር ህዝብ ድል ማዕከል፤ የነፃነት ተምሳሌትና የአፍሪካ ህዝብ ኩራት በሆነች ሀገር የኋላ ዘመን ውጣ ውረድ ውስጥ ሰፊው የአማራ ህዝብ ከመላው […]

የካቲት 11 የተፈበረከው ሕወሃት ማለት እጅግ አሳፋሪ እና አሸባሪ የማፊያ ድርጅት ነው::

ሕወሓት ….. በምንሊክ ሳልሳዊ
= ህጻናትን በማደጎ እና በጉዲፈቻ ስም ይቸበችባል:: እንዲሁም በወሲብ ንግድ ውስጥ በመሰማራት
በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር የደላላ ኤጀንቶችን በማቋቋም ታዳጊ ወጣት ሴቶችን
ለሽያጭ ::ባለስልጣናቱ በብዙ መቶ ሺዎች ዶላሮች አፍሰዋል ::

= በስሩ ያደራጃቸውን ቡድኖች የዲፕሎማቲክ ካባ በማልበስ በአደንዛዥ እጽ ዝውውር ላይ እንዲሰማሩ እና ዲፕሎማቶች ከፍተሻ ነጻ ስለሆኑ በረቀቀ ስልት ካናቢስ ሃሺሽ እና መሰል ድራጎችን በማዘዋወር ስራ እና ንግድ ላይ ተሰማርቷል::

= ህገወጥ የሰው ዝውውር እና የአካላት ስርቆት ድርጊቶችን ይፈጽማል:: ወደ ተለያዩ የመካከለኛ ምስራቅ እና ደቡብ አፍሪካ የመሳሰሉ ሃገራት በህገወጥ መንገድ ሰዎችን በማዘዋወር ከባድ ወንጀል እየተሰራ ሲሆን ይህንን ስራ የሚሰሩ አካላትን ሰርቀው ሰውን በመግደል የሚከብሩ ደላሎች ከባለስልታናት ትእዛዝ የሚወርድላቸው እና ሕወሓት በአባልነት የመዘገባቸው ነው::

= በግብጽ እና በየመን በረሃዎች እንዲሁም በሱዳን ሊቢያ ድንበር ላይ ስደተኞችን በማፈን የተለያዩ የገንዘብ መጠኖችን በመጠየቅ ቤተሰብን በማስጨነቅ ሴቶችን በመድፈር አከላትን አውጥቶ በመሸጥ ስራ ላይ የተሰማሩት የሕወሓት አባላት የሆኑ ግለሰቦች ናቸው::

= የአገሪቷን መሬት ለውጭ ባለሃብቶች በመሸጥ ወገንን ለስራ ጥነት ለስደት ለመፈናቀል የሚዳርጉት በሕወሓት ሃይሎች የሚመሩት በአቋራጭ የከበሩ አባላቱ ናቸው::ከተላያዩ አከባቢዎች ለውጪ ኢንቨስተሮች በሚል ስም የተሸጡ መሬቶች የሽያጭ ገቢያቸው የት እንደሄደ እንደማይታወቅ እና ሸጡ የተባሉት ክልሎች እንኳን ለአከባቢው ነዋሪዎች ካሳ ያልከፈሉበት እና ያላቋቋሙበት ሁኔታዎች በገፍ ታይተዋል::

= በተለያዩ ጊዜያት በአዲስ አበባ እና በክልሎች ቦንቦችን በማፈንዳት ንጹሃን ዜጎችን በመግደል እና በማቁሰል የሽብር ስራ ላይ የተሰማራው ሕወሓት የተቃወሙትን ሁሉ የሚወነጅልበት አንዱ ብልሃቱ ቢሆንም ሞኝነቱ አዘንብሎ ተገኝቷል::አልቸባብን እና ሃማስን ከመሳሰሉ አሸባሪ ከሞባሉ ድርጅቶች ጋር የሁለትዮች ምስጢራዊ ስምምነት በመፍጠር ምስራቅ አፍሪካ እና መካከለጫው ምስራቅ ላይ ከፍተኛ ስጋት ለመፍጠር እና ዜጎቹን ለማስፈራራት እጅግ አሳፋሪ እና ዘግናኝ ድርጊቶችን ፈጽሟል: በመፈጸም ላይ ይገኛል:: ምንሊክ ሳልሳዊ

የሀ/ስብከቱ ጽ/ቤት ደግሞ በነገው ዕለት ለቋሚ ሲኖዶሱ ያስረክባል የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከትን የተቋማዊ ለውጥ አመራር ሲያጠና የቆየው የባለሞያ ቡድን በዛሬው ዕለት የአደረጃጀትና አሠራር ጥናት ሰነዱን ለሀ/ስብከቱ በይፋ ያስረክባል፡፡ ዛሬ፣ የካቲት ፮ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም ረፋድ ላይ በሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት በሚካሔደው የርክክብ እና ምስጋና መርሐ ግብር፣ 15 አባላት ያሉት የባለሞያ ቡድኑ ከአንድ ሺሕ በላይ አጠቃላይ ገጾች …

አሰግድ ኣረጋ (ኮለምበስ – ኦሃዮ)
ጤፍ Teff. Photo by Peter Bregg

ሰሞኑን ስለጤፍ ምርታችን የባዕዳኑ ብዙኀን መገናኛ አጀብ እያሉን ነው፤ ለዘመናት የተደበቀው የዘሩ ገመና መጋለጡን እየነገሩን ነው፤ ስለያዘው ንጥረ ነገር፣ ስለጤናማነቱ፣ በምዕራቡ ገበያ ስለመፈለጉ፣ ከሁለም በላይ ስለ ውጭ ምንዛሪ ምንጭነቱ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም Prof. Al-Mariamፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም – ነጻነት ለሀገሬ)

ፈረሰኛው ረሃብ ኢትዮጵያ ላይ አያነጣጠረ ነው!
ባለፈው ሳምንት ኤንቢሲ/NBC የተባለው የዜና ወኪል በኢትዮጵያ እየተንፏቀቀ በመጣው ረኃብ ላይ ያደረገውን ጥናታዊ ዘገባ ዋቢ በማድረግ በማርቲን ጌይስለር አማካይነት ከዚህ በታች የተመለከተውን ሀተታ ለአየር አብቅቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

እንደ መግቢያ ቅጥፈት የስብዕና መሽርሽር ምልክት ነው፡፡ የግለሰቦች ስብሰብ በሚፈጠረው ማህበረሰብ ውስጥ የስብዕና መሸርሸር ሲበራከት ማህረሰበባዊ አደጋ ሰላማዊ አኗኗሩን ማነዋወጥ ይጀምራል ፡፡ ማህበራዊ ቀውስ በሰፈነበት ደግሞ ከግለሰቦቹ ውድቀት የሚነሳው ገፊ ምክንያት እንደ ማህበረሰብ የተገነቡ የጋራ እሴቶችን ይንዳል፡፡ ባህል ፤ ሃይማኖት ፣ታሪክ ፣ወግ እና ልማዶች ሁሉ መሰረታዊ ይዘታቸውን የላቁና የሰው ልጅ እንደ እንስሳ በቀላሉ ከእንቱ ነገሮች […]

ታላላቆቹ መንግሥታት ፤ ዩናይትድ ስቴትስ፤ ሩሲያ፣ ቻይና ፣ ህንድና ሌሎችም ኅዋን በማሰስ ፤ ጨረቃንና ማርስን ዒላማ በማድረግ ፉክክራቸውን እንደቀጠሉ ናቸው። አዳዲስ የኅዋ ጣቢያዎችን የማቋቋም እቅድም አላቸው። የተጠቀሱት ሀገራት ብቻ ሳይሆኑ ፤

የካቲት ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአርሴማ ቤተክርስቲያን የተነሳውን የውስጥ ችግር ተከትሎ ችግሩን ለመፍታት የተመረጡት የሰበካ ጉባኤ አባላት ታስረዋል። በህዝቡ የተመረጡት 15ቱ ሽማግሌዎች ችግሩን ለመፍታት በሚንቀሳቀሱበት ጊዜ የቀጠናው ሃላፊ የሆኑት አቡነ ገብርኤል የሰበካ ጉባኤ አባላቱ እንዲበተኑና ችግሩን ለመፍታት እንደሚሞክሩ መግለጻቸው ህዝቡን አስቆጥቷል። ጳጳሱ  ለፌደራል ፖሊሶች በማመልከት የአገር ሽማግሌዎች እንዲታሰሩ ማድረጋቸውን የሚናገሩት የአካባቢው ነዋሪዎች፣ …

የካቲት ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአማራ ተወላጆች ላይ በጅምላ ፀያፍ ስድብ የሰነዘሩት የብአዴኑ አመራር እና የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የ አቶ ኣለምነው መኮነን መኖሪያ ቤት በድንጋይ መደብደቡን ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ የዘገበ ሲሆን፣ ዜናውን ተከትሎ ኢሳት ባደረገው ማጣራት የባለስልጣኑ መኖሪያ ቤት በ11 ፖሊሶች ሌትና ቀን እየተጠበቀ ነው። አቶ አለምነው የአማራው ህዝብ የትምክህት ለሃጩን …

የካቲት ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ  በጽ/ቤታቸው ለአገር ውስጥ ጋዜጠኞች በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ከፎርቹን ጋዜጣ ማኔጂንግ ኤዲተር አቶ ታምራት ገብረጊዮርጊስ በቀረበላቸው ጥያቄ በመቆጣት ዘለፋ ሰነዘሩ፡፡ አቶ ታምራት ለጠ/ሚኒስትሩ ያቀረቡት ጥያቄ በአሁን ሰዓት አገሪትዋን የሚመራት ማንነው ነው የሚል ይዘት ያለው ሲሆን ጠ/ሚኒስትሩም ብስጭታቸውን በምላሻቸው ወቅት አንጸባርቀዋል፡፡ ጠ/ሚኒስትሩ ለዚህ ጥያቄ ቀጥተኛ …

አሜሪካዊዉ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር እንደሚሉት የደቡብ ሱዳን፣ የማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ እና የኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክን ጦርነት፣ግጭትና ፖለቲካዊ ቀዉስን ለማስቆም ለማስቆም በሚደረገዉ ጥረት መንግሥታቸዉ ጉሉሕ አስተዋፅኦ እያደረገ ነዉ

የዓለም ኣገሮች እንደየ ገቢያቸው በዓለም ባንክ ትንቢያ መሰረት የበለፀጉ መካከለኛ ገቢ ያላቸው እና ደኃ ኣገሮች ተብለው በሶስት ይከፈላሉ። በዚሁ መሰረት ዓመታዊ የኣገር ውስጥ ጥቅል ገቢያቸው ለህዝብ ቁጥር ተካፍሎ የእያንዳንዱ ዜጋ የነብስ ወከፍ ገቢ በዓመት ከ 12 000 የአሜሪካን ዶላር በላይ ከሆነ ከፍተኛ

ለደቡብ ሱዳን ነፃነት በጋራ የታገሉት የሐገሪቱ ፖለቲከኞች ካለፈዉ ታሕሳስ ጀምሮ የለየለት ዉጊያ ገጥመዋል።ጦርነቱን ለማስቆም የሚደረገዉ ሁለተኛ ዙር ድርድር ከታቀደለት ቀን ተሸጋሽጎ ቢጀመርም ተፋላሚ ወገኖች መካሰሳቸዉ መቀጠሉ ነዉ የተሰማዉ።

የካቲት ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የክልሉ የፍትህ ቢሮ በክልሉ ውስጥ ለሚገኙ ፍርድ ቤቶች በጻፈው ደብዳቤ ማንኛውም ባለጉዳይ አቤቱታዎችን በኮምፒዩተር ካላስጻፈ ጉዳዩ እንዳይታይለት ወስኗል። በክልሉ የሚገኙ ዳኞች በበኩላቸው ውሳኔው የህዝቡን የኑሮ ሁኔታ እና የእድገት ደረጃ ግምት ውስጥ ያላስገባ ነው ይላል። ዳኞች እንደሚሉት አብዛኛው ህዝብ አቤቱታዎችን አስጽፎ የሚያቀርበው በወረቀትና በእስክር ቢቶ ሆኖ ሳለ፣ የድሆችን …

የካቲት ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የግብፅ የውኃና መስኖ ሚኒስትር መሐመድ አብዱል ሙታሊብ ከኢትዮጵያ አቻቸው ጋር የሁለትዮሽ ውይይት ለማድረግ በጠየቁት መሠረት ባለፈው ሰኞ አዲስ አበባ ቢገቡም፣ የዓባይ ግድብ ግንባታ እንዲቆም በመጠየቃቸው ውይይቱ በሰዓታት ውስጥ ተቋረጠ፡፡ ሪፖርተር እንደዘገበው  የግብፅ ሚኒስትር ከኢትዮጵያ አቻቸው አቶ አለማየሁ ተገኑና ከባልደረቦቻቸው፣ እንዲሁም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከተወከሉ ባለሙያዎች ጋር ባለፈው …

የካቲት ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአማራ ክልል ቋሪትና ጃቢጠህናን ወረዳዎች ይካሄድ የነበረው መረን የለቀቀ ህገወጥ የአራጣ ብድር ስርዓት በአስከተለው ቀውስ ከ250 በላይ ጠንካራ ነጋዴዎች ተሰደዋል ተባለ፡፡ ከፍተኛ ማታለል የነበረበት ይህ ህገወጥ የአራጣ ብድር ስርዓት ነጋዴዎችን ባዶ ያስቀረና ያሰደደ ከመሆኑ ባለፈ ብዙዎችን ለእብደትና ለቤት መፍረስ ዳርጓል ሲሉ ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉና ከ121 ሺህ ብር …

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲና የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ብአዴንን በመቃወም በባህርዳር ከተማ ህዝባዊ የተቃውሞ ሰልፍ ጠሩ፡፡ ፓርቲዎቹ ነገ በ4 ሰዓት በአንድነት ፓርቲ ጽ/ቤት በጋራ መግለጫ እንደሚሰጡ ይጠበቃል፡፡ ለተቃውሞ ሰልፉ አስፈላጊው የማሳወቅ ተግባር መጠናቀቁ ታውቋል፡፡ አንድነትና መኢአድ እሁድ የካቲት 16 ቀን 2006 ዓ.ም የጠሩት የተቃውሞ ሰልፍ መነሻ ምክንያት እንዲያስረዱ በፍኖተ ነፃነት የተጠየቁት የአንድነት ፓርቲ የፖለቲካ ጉዳዮች […]

የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (ሸንጎ) Ethiopian People's Congress for United Struggle (Shengo)Ethiopia Zare (ረቡዕ የካቲት 5 ቀን 2006 ዓ.ም. Feb. 12, 2014)፦ የአማራ ክልል ም/ፕሬዝዳንት አቶ አለምነው መኮንን በአማራው ላይ የሰነዘሩትን ፀያፍና በዘር ጥላቻ ላይ ያዘነበለ ስድብ በማውገዝ፤ “የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ” ትናንት የካቲት 4 ቀን 2006 ዓ.ም. መግለጫ አወጣ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ነጋ ዓለማየሁ

ሰሞኑን የአማራ ክልል ባለሥልጣን ናቸው የተባሉ ሰው በአማራው ሕዝብ ላይ የጅምላ ስድብ ሲሳደቡ ተደምጠዋል። ሰውየውን ስሙንም ሰምቼው አላውቅም። እንዲህ አይነቱን ሰው አንቱ ማለትም የሚገባ አልመሰለኝም። ሀገሪቱን የሚመራው መንግሥት ከየት አምጥቶ እንዳስቀመጠው እራሱ ነው የሚያውቀው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

አስገራሚው የሳውዲው “ኮራጅ ” አባት ምክር

ነቢዩ ሲራክ
ነገሩ እንዲህ ነው፤ ከ20 ዓመት በፊት ሳውዲው ወጣት ራሱን ለሁለተኛ ደረጃ ፈተና ከማዘጋጀት ይልቅ በረቀቀ መንገድ ለፈተናው መልስ የሚሆነውን ማጭበርበሪያ የመልስ ወረቀት አዘጋጅቶ ለፈተና ይቀርባል። ፈተናውን በረቀቀ መንገድ አጭበረብሮ ሰርቶታልና ፈተናውን በተገቢ ውጤት አልፎ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ለማለፍ በቃ!

ሙሉውን አስነብበኝ …

ብልህ የጥንቶቹንም ለመከተል አይፈልግም፤ ዘልዓለማዊ ነው የሚባል ደረጃ ለመመደብም ሆነ ለማስቀመጥ አይሻም፡፡ ይልቁንም የራሱን ዘመን መርምሮ ለዚያ የሚያዋጣውን ዘዴ ይዘይዳል፡፡“የብልህ አመራር ማለት ገዢው የሱ ሰዎች ልክ እሱ ያዘዘውን ያሰቡ እንዲመስላቸው ማድረግ ነው፤” ትላለች የሩሲያዋ ታላቋ ካቴሪን፡፡ ቀጥላም “ይሄን ለማድረግም፤ አንድ እርምጃ ከህዝቡ ፍላጐት መቅደምና ከአልቀበል – ባይነቱ ጋር መላመድ ነው” ትለናለች፡፡ ልብ ያለው ልብ ይበል! ራመድ ብለን የንግሥቲቱን አካሄድ ስንመረምር ለውጥን ያለጉልበት በዘዴ እንዴት ለማምጣት እችላለሁ? የማለት፤ ጥበባዊ ፍላጐትን የመቀዳጀት ጥያቄን ይሰርጽብናል፡፡ የኛ ዕቅድ፣ መርህ፣ ስትራቴጂ ወዘተ. ከሰማይ በወረደ ኃይልም አይታጠፍም፣ አይቀየርም፣ የምንለውን፤ በልባምነት አውጠንጥነን እንድናይ የሚያግዘን አስተውሎት ነው፡፡

ተቃዋሚዎቻችንን ወይም በግልባጩ ገዢዎችን የምናይበትን ሁኔታ በሁለት ታዋቂ የሰንጠረዥ ጨዋታዎች ምሳሌነት ለማፀኸየት እንሞክር፡፡ አንደኛው፤ ቼዝ ነው፡፡ ሁለተኛው፤ ጐ የሚባለው ጨዋታ ነው ፡፡ ቼዝ ጨዋታ፤ በጠባብ ሜዳ የምንጫወተው ሠንጠረዥ ነው፡፡ 32 ጠጠሮች አሉት – አለቃና ምንዝር የሆኑ። ከሁለቱም ወገን የሚሠለፉ፡፡ የቼዝ ጨዋታ የጠላትን ወታደርና መኮንኖች ግንባር ለግንባር እየገጠሙ መደምሰስ ነው፡፡
በአንፃሩ በ “ጐ” ጨዋታ፣ ከቼዝ ስድስት ጊዜ በሰፋ ሰፊ ሜዳ በየጐራው 52 ጠጠሮችን በጥቁርና በነጭ አሰልፎ መፋለም ሲሆን፤ ዘዴው እያንዳንዱን ጠላት በመክበብ ከእናት ክፍሉ ለይቶ መጠጊያ ማሳጣት ነው፡፡ ከዚያም እንዲሟሽሽና ሽባ እንዲሆን ማድረግ ነው፡፡

በሰፊው ማሰብ፣ ትንሽ ቦታ ሰውቶ፣ ቀስ በቀስ ሰፊ ቦታ መያዝ፤ በመጨረሻም ማሸነፍ ነው፡፡ ሁለቱን ስልቶች ጠንቅቆ ማወቅ ለኢትዮጵያ የፖለቲካ ሠንጠረዥ እጅግ ጠቃሚ ነው! ቅልጥፍናን ከገዢ መሬት በላይ የማየት ክህሎት ይኑርህ ነው ነገሩ!
እጅ መስጠት የሚጀምረው ከአንጐል ውስጥ ነው፡፡ ስለዚህ አስቀድመህ የባላንጣህን አዕምሮ ክበብ ይላሉ፤ የፖለቲካ ፀሐፍት ቀስቅስ፣ ግንዛቤ ፍጠር፣ አንቃ ነው፡፡ የማዖን የጦር ዘዴ ለአዕምሮ ጦርነት ማሰብ ድንቅ ነው፡፡

“ጠላት ሲገፋ አፈግፍግ፡፡ ጠላት ካምፕ ውስጥ ሲያርፍ እረፍት – ንሳው፡፡ ጠላት ሲዳከም አጥቃው፡፡ ጠላት ሲያፈገፍግ አንተ ግፋ፡፡” ዘመኑ የአዕምሮ ትግል ወቅት ነውና አዕምሮህን አስላ፡፡ እቅድህን አጥራ፡፡ ስትራቴጂህን በጥንቃቄ ቀንብብ እንደማለት ነው፡፡ ይሄ ሁሉ ሲሆን ግን ከብጤህ፣ ከእኩያህ፣ ከአምሳያህ፣ የፖለቲካ አዕምሮ – ፈርጁ ከአዐምሮ – ፈርጅህ የሚጣጣም የፖለቲካ ባልንጀራ አበጅተህ ወቅቱ በሚፈቅደው ዛፍ ጥላ ሥር ሆነህ፣ ንጋት፣ ቀትርና ጨለማ ለይተህ፣ መጓዝ እንዳለብህ ማወቅ ነው ታላቁ ቁምነገር፡፡ እንዲያው በጥቅም – ቀደም – አካሄድ ለእለት – እንጀራ የተጐዳኘኸውን ወይም ብረት – ድስትና ሸክላ – ድስት ሳትለይ የተወዳጀኸውን ሁሉ የፖለቲካ ወዳጄ ነው ብለህ ከተጓዝክ “ከማይመጥነው ሰው ጋር የሚካኤል ማህበር ጠጣ፤ ተራውን ሳያጠጣ ሞተ” ከመባል አታመልጥም!!#MinilikSalsawi

“አሜሪካኖች ነጻ እንድታወጡን አንጠይቃችሁም። የኢትዮጵያ ህዝብ እንዴት ነጻ እንደሚወጣ ያውቃል። እናንተ ግንበነጻነት መንገዱን ላይ ዕንቅፋት አትሁኑበት … ዶናልድ ያማሞቶ ከዛሬ ስምንት ዓመት በፊት ኢትዮጵያ በመንታመንገድ ላይ ነች ብለኸን ነበር መቼ ነው መንገዱን የምናቋርጠው? ከመንገዱ ላይ ገለል በሉልን” አቶ ኦባንግ ሜቶ
እንዴት እዚህ ተደረሰ?

የኢህአዴግን የአገዛዝ ዘመን ተቃዋሚዎችን አጃቢ አድርጎ የህግ ሽፋን በመስጠት የሚያራዝመው ዋና ተቋም ምርጫ ቦርድ፣ የፕሬስ ነጻነት፣ የመናገርና የመሰብሰብ ነጻነት፣ የህግ የበላይነት፣ ሕግን የማክበርና የማስከበር ሃላፊነት፤ ወዘተ በኢትዮጵያ ነጻ ከሆኑ ኢህአዴግ ከፊትለፊቱ ካለው ምርጫ የመዝለል አቅም እንደሌለው ይታመናል። ስለዚህም እነዚህን ጉዳዮች ለድርድር አያቀርባቸውም። ኢህአዴግ ከጅምሩ በህዝብ የማይታመነውና እውቅና የሚነፈገው ራሱን በነጻ አውጪ ስም (ህወሃት) የሰየመ መንግስት ስለሆነ ነው።

ነጻ አውጪ እየተባለ አገር መምራቱም አቅዶ፤ ተልሞና መድረሻውን አስልቶ የሚጓዝ ስለመሆኑ ያሳብቅበታል። ለዚህም ይመስላል ስርዓቱ በሙስና የሸተተ፣ በግፍ የገለማ፣ የሚመራውን ህዝብ የሚገል፣ የሚያስር፣ የሚያሰቃ፣ መንግስት ሆኖ የሚሰርቅ፣ ብሔራዊ ክብርን የሚጠላ፣ ህብረትንና አንድነትን የሚጠየፍ፣ ጎሳና ጠባብ አመለካከት ላይ የተቀረጸ፣ በተራና በወረደ ተግባሩ ለመንግስትነት የማይመጥን መሆኑን የተረዱት አጋሮቹ አሁን ያመረሩበት ደረጃ ስለመዳረሳቸው ምልክቶች እንዳሉ አቶ ኦባንግ ሜቶ ለጎልጉል ተናግረው ነበር።
ኢህአዴግ ከአሜሪካ ጋር የመሰረተው ግንኙነት ከቶውንም ንፋስ እንደማይገባው ተከታዮቹ ሙሉ በሙሉ ያምናሉ። በተለይም የህወሃት ሰዎች አሜሪካ ከህወሃት ጋር ያሰረችው ቀለበት የሚወይብ አይመስላቸውም። የአሜሪካና የ”ህወሃት ፍቅር” ትምክህት የሆነባቸው የአሜሪካን ባለስልጣናት ህወሃት ኢትዮጵያን እስከ ዘላለም እንዲመራ ልዩ ቅባት እንደቀቡት የሚናገሩም አሉ። አሜሪካ ለህወሃት/ኢህአዴግ የምትሰጠው ጭፍን ድጋፍ ሊጤን እንደሚገባው በማሳሰብ ተስፋ ሳይቆርጡ የታገሉና የሚታገሉ ደግሞ ይህ ትምክህት አንድ ቀን እንደሚተነፍስ በእምነት ሲናገሩ ቆይተዋል።

ኢህአዴግን በዲፕሎማሲና በሰከነ የትግል ስልት መታገል ይበልጥ አዋጪ እንደሆነ ከሚያምኑት ወገኖች መካከል አቶ ኦባንግ ሜቶ ቅድሚያውን ይይዛሉ። አቶ ኦባንግ የሚመሩት ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) የሚያራምደውን እምነት አስመልክቶ “ከወረቀትና ፒቴሽን ከማስፈረም ያልዘለለ” በማለት የሚቃወሙና የሚተቹ የመኖራቸውን ያህል ልብና ቀልብ ሰብስበው የሚከተሏቸው ወገኖች ቁጥር ከቀን ቀን እየጨመረ ነው። እምነትም እየተጣለባቸው ነው።

በወገኖቻቸው ብቻ ሳይሆን በውጪው ዓለም ያላቸው ተቀባይነት፣ ብሎም አመኔታ እንዲሁ ከፍተኛ ነው። የኢትዮጵያ ወኪል ተደርገው እየተወሰዱም ነው። አቶ ኦባንግ ኢትዮጵያን በመወከል በተለያዩ ታላላቅ መድረኮች ሲሳተፉ የሚያቀርቧቸው ንግግሮችም ቀልብ የሚገዙና መልዕክታቸው የሰፋ በመሆኑ ሰፊ አድማጭ አላቸው። ሰሞኑንን በአሜሪካ ምክርቤት (ኮንግረስ) የጸደቀውን ድንገተኛ ውሳኔ አስመልከቶ “ኢህአዴግ ሳይወድ በግዱ በሩን በርግዶ ይከፍታል” ባይ ናቸው። ውሳኔውንና የውሳኔውን አካሄድ ከአነሳሱ ጀምሮ ጠንቅቀው እንደሚያውቁት ያመለከቱት አቶ ኦባንግ “አሜሪካ እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰችው እንዲሁ ከመሬት ተነስታ ሳይሆን በከፍተኛ ትግል ነው። ትግሉ ተጠናክሮ ይቀጥላል የአውሮፓ አገሮችም የአሜሪካን ፈለግ እንዲከተሉ ሥራችንን አጠናክረን ጀምረናል” ብለዋል።
አዲሱ ውሳኔ ሕግ እና የኢህአዴግ ህልውና!

እያነጋገረ ያለው የእርዳታን አጠቃቀም አስመልክቶ ጥር 31 ቀን 2014 በአሜሪካን ኮንግረስ የፀደቀው አዲስ ውሳኔ ሕግ ነው። ውሳኔው አሜሪካ የምትሰጠው ርዳታ በትክክል ህዝብን ሳይጎዳ በስራ ላይ መዋሉንና አለመዋሉን እንዲቆጣጠር ለአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መ/ቤት (State Department) ትዕዛዝ የተላለፈበት ነው። እንግዲህ ይህ ትዕዛዝ ይፋ ከሆነበት ጊዜ ጀምሮ የሚነሱት መከራከሪያዎች በርካታ ቢሆኑም በምላስ “ነጻ ነኝ” የሚለውና በግብር “ለጌቶቹ ጥሩ ባሪያ” በመሆን 22 ዓመት የዘለቀው ኢህአዴግና ከአሜሪካ ግንኙነታቸው በነበረበት መንገድ ስለመዝለቁ ጥያቄ የሚያስነሳ እንደሆነ አብዛኞች ይስማማሉ። አሜሪካ ከዚህ ውሳኔ የደረሰችው በወፍ ዘራሽ ሳይሆን በሂደት እንደሆነ በመጥቀስ አቶ ኦባንግ ሜቶ ከሚያቀርቡት ሃሳብ ጋር ይስማማሉ።

የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪ ድርጅቶች መረጃ ላይ ተንተርሰው ለሚያወጡት ሪፖርት “ተራ የማበሻቀጪያና የማጣጣያ” መልስ በመስጠት፣ ሲለውም ተቃዋሚዎችን የሚደግፉና የኢህአዴግ የኢኮኖሚና የፖለቲካ እምነት /የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ጎዳና/ “ቅንቅን” የሆነባቸው የምዕራብ አገራት “ተላላኪ” በማስመሰል አሁን ድረስ ሲዘልፋቸው መቆየቱ አይዘነጋም። ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ እንደሚሉት አሁን አዲስ ለጸደቀው የአሜሪካ ቅድመ ሁኔታ ላይ ያተኮረ የርዳታ መርሃ ግብር እነዚህ ክፍሎች በቁጥጥርና በክትትል በኩል ሪፖርታቸው ዋና ግብዓት ስለሚሆን ኢህአዴግ መንታ ፈተና ውስጥ እንደሚወድቅ ቅድመ ትንበያዎች አሉ።

በዚሁ መነሻ ኢህአዴግ የህልውናው መሰረት የሆነውን እርዳታ ለማግኘት “የፖለቲካ አመለ ሸጋ ሆኖ የዘጋቸውን በሮች ከፍቶ የሚመጣውን የህዝብ ወሳኝነት መቀበል፣ አሊያም በሂደት ሰልሎና ተሽመድምዶ መክሰም የመጨረሻው እድል ፈንታው ይሆናል” የሚሉ ወገኖች ጥቂት አይደሉም።

ኢህአዴግ በመንታ መንገድ ላይ – የህጉ ተጽዕኖ ከፖለቲካና ኢኮኖሚ አንጻር
ውሳኔውን ከፖለቲካው እንደምታና ከኢኮኖሚው ጣጣ ጋር በማያያዝ አስተያየት የሰጡን እንደሚሉት ከሆነ ጉዳዩ አደጋ አለው። እንደሚታወቀው የኢህአዴግ አገዛዝ ከጠቅላላው የምዕራብ መንግስታት ከሶስት ቢሊዮን ዶላር በላይ ዕርዳታ በየዓመቱ ያገኛል። ይህ ከፍተኛ መጠን ያለው ዕርዳታ ከአጠቃላይ አመታዊ በጀቱ 50% የሚሆነውን ይሸፍንለታል። ከአሜሪካን ብቻ አንድ ነጥብ ስምንት ቢሊዮን ዶላር በየዓመቱ በዕርዳታ መልክ ያገኛል። ይህም ከአሜሪካ የሚገኘው ርዳታ ብቻውን የበጀቱን አንድ ሶስተኛውን ይሸፍንለታል።
በዚህ መነሻ የኮንግረሱ ውሳኔ በኢህአዴግ አገዛዝ ላይ ያልጠበቀው ዱብ ዕዳ እንደሆነ በጀርመን የልማት ኢኮኖሚክስ ባለሙያው (Development Economist) ዶ/ር ፈቃዱ በቀለ ይናገራሉ። ይህ እሳቸው “ዱብዕዳ” ያሉት ውሳኔ የፖለቲካ ውዝግብ ማስነሳቱ የማይካድ ነው። ኢህአዴግ ከአውሮፓና ከአሜሪካ የሚያገኘውን ድጎማና ርዳታ ለምን ተግባር ሲያውለው እንደነበር ከማንም በላይ ጠንቅቆ ስለሚያውቀው ከቅድመ ሁኔታ ጋር የተያያዘ የዕርዳታ አሰጣጥ ከኢኮኖሚ ይልቅ የፖለቲካና የስነልቦናው ተፅዕኖው እንደሚያስከትልበት እኚሁ ምሁር ያስረዳሉ።

ከአጠቃላዩ የማክሮ ኢኮኖሚ አንጻር ውሳኔው ሊያስከትል የሚችለውን ተጽዕኖ በዝርዝር በማስቀመጥ አስቀድሞ መናገር ባይቻልም አሉታዊ ተጽዕኖ ሊኖረው እንደሚችል መገመት እንደማያዳግት ዶ/ር ፈቃዱ ከጎልጉል ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል። “ከአጭርና ከመካከለኛ ጊዜ አንፃር ስንመለከተው የአገዛዙን የኢኮኖሚ አካሄድ ጥያቄ ውስጥ ሊያስገባ ይችላል” ያሉት ባለሙያው፣ “… ወደፊት አዳዲስ የስራ መስክ መክፈት፣ በኢኮኖሚው ዕድገት፣ በውጭ ምንዛሪ ግኝትና በውጭ ሚዛን ዕድገት ላይ ሊኖረው የሚችለው ተፆዕኖም ቢሆን ይህ ነው ብሎ መናገር አይቻልም። ይሁንና የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እርስ በርሱ የተያያዘ ስላልሆነና፣ አብዛኛው ህዝብም በኢንፎርማልና ከእጅ ወደ አፍ በሚገኝ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ውስጥ የሚተዳደርና የሚሳተፍ ስለሆነ ሊጎዳ የሚችለው በዘመናዊ መስክ የተሰማራውን ሰራተኛና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ነው” በማለት ቅድመ ግምታቸውን ያስቀምጣሉ።

ሲያብራሩም ከቅድመ-ሁኔታና ከጥብቅ ቁጥጥር ጋር የተያያዘ በዕድገት ስም የሚፈስ ዕርዳታ በአጠቃላይ ሲታይ በህዝቡ ኑሮ መዛነፍ ላይ የሚኖረው ተፅዕኖ ዝቅተኛ መሆኑንን የሚያመለክቱት ዶ/ር ፈቃዱ፣ ከ10-11በመቶ “ያለማቋረጥ” አደገ በሚባለው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከኢትዮጵያ ህዝብ ኑሮ መሻሻል ጋር ተያያዥነት እንደሌለው ይናገራሉ። ቅድመ ሁኔታ የተቀመጠለት እርዳታ ቢቀነስ ወይም እንዳለ ቢታገድ በተመሳሳይ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ የሚያመጣው አሉታዊ ውጤት ምን ሊሆን እንደሚችል ከወዲሁ በቁርጥ ማስቀመጥ እንደሚያዳግትም ባለሙያው ይጠቁማሉ። በዚህ ዓይነቱ የዕርዳታ አካሄድ እስካሁን የተጎዳው ህዝብ በመሆኑ የዕርዳታው መቀነስ ወይም መታገድ አገዛዙን እንጂ በዚያ አካባቢ የሚኖረውን ህዝብ በቀጥታ የሚመለከት አይሆንም። በህዝብ ኑሮ ላይ የሚከተለውን ማህበራዊ ኪሳራ ተምኖ ማስቀመት ቢችግርም “ወያኔ ቅድመ ሁኔታውን ተግባራዊ የሚያደርግ ከሆነ በተለይም በቀጥታ በኗሪው ህዝብ ህይወት ላይ አዎንታዊ ውጤት ማሳየቱ ግን የማይቀር ነገር ነው” ሲሉ ግርድፍ ምልከታቸውን ያኖራሉ። በሴፍቲኔት፣ በአነስተኛና ጥቃቅን፣ ወዘተ የህዝቡን ኑሮ እየቀየርኩ ነው የሚለው “ልማታዊው” ኢህአዴግ እንዲህ ዓይነት በቅድመ ሁኔታ የተወጠረ ዕርዳታ በሕዝቡ ኑሮ ላይ ቀውስ ያመጣል በማለት የራሱን ቅንብር እንደሚሰራ የሚከራከሩም አሉ፡፡

ፖለቲካዊ ይዘቱን የዳሰሱት ዶ/ር ፈቃዱ ሁለት መሰረታዊ ጉዳዮችን በመጠቆም ለውይይት የሚጋብዝ ፍንጭ ሰጥተዋል። “ውሳኔ ሕጉ ያካተታቸው ቅድመ ሁኔታዎች ከረዥሙ አጠቃላዩ የማክሮ ኢኮኖሚ ሁኔታ አንፃር ስናየው ግን በዕውነቱ እንደዚህ ዓይነቱ ከቅድመ-ሁኔታ ጋር የተያያዘ ዕርዳታ ላይጎዳው ይችላል። አገዛዙ ከምዕራቡ አገራት የሚመጣበትን ግፊት የሚቋቋም መስሎት የሚታየው ከሆነ ፊቱን ወደ ቻይናና ወደ ሌሎች ቅድመ ሁኔታን ከማያሰቀድሙ አገሮች ዕርዳታ በማግኘት ከአሜሪካን የሚሰጠውን ዕርዳታ ሊያካክስና በነበረበት ሁኔታ ለመቀጠል መንፈራገጡ” አንደማይቀርም አመላክተዋል። ይህ ግምታቸው ግን ጥርጣሬያቸው እንዳለ ሆኖ ነው።

“ኢትዮጵያ ካለችበት የጂኦ ፖለቲካ፣ የአፍሪካ ህብረት ዕምብርትና መቀመጫም ስለሆነች ቻይናዎች ከራሳቸው የንግድ መርህ አንጻር ዕርዳታውን ከመስጠት ወደኋላ ሊሉ አይችሉም” ሲሉ የጉዳዩን ሌላ መልክ ያሳዩት ዶ/ር ፈቃዱ፣ አማራጩ ከአሜሪካንም ሆነ ከተቀረው የምዕራቡ ዓለም ጋር ተላትሞ ወደ ቻይና ፊትን በማዞር የሚደመደም ከሆነ አገዛዙ ዕድሜውን ለማሳጠር ራሱ እንደወሰነ የሚቆጠርበት ይሆናል። ኢህአዴግ አምርሮና የመጣው ይምጣ በሚል ቅድመ ሁኔታዎችን አላሟላም፣ ዕርዳታችሁንም አንፈልግም የሚል ከሆነ አሜሪካን አማራጭ ለመፈለግ ልትሞክርና ይህንንም እንደማስፈራሪያ ተጠቅማ ልትለሳለስ” እንደምትችል ዶ/ር ፈቃዱ አመላክተዋል።

እንደወያኔ የሚታዘዝላት ድርጅትና መሪ እስካላገኘ ድረስ ኢህአዴግ ላይ አደጋ እንዲነግስ ወይም ከነጭራሹ እንዲወገድ አሜሪካ ትሰራለች ብለው እንደማያምኑም ገልጸዋል። “እንዲያውም” አሉ ዶ/ር ፈቃዱ “በኮንግረሱ የፀደቀው ህግና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር (State Department) እንዲቆጣጠረው የተደረገው የዕርዳታ አሰጣጥ ዘዴ፣ የኦባማ አስተዳደር ሌላ መንገድ ፈልጎ ኮንግረሱን በማለፍ፣ በቀጥታ ከአሜሪካን የውጭ ዕርዳታ አሰጣጥ ጋር ባልተያያዘ መንገድ የኢህአዴግን አገዛዝ በተዘዋዋሪ ሊረዳበት የሚችልበት መንገድ እንደሚኖር መጠራጠር ይቻላል” ሲሉ ሃሳባቸውን ያጠናክራሉ። ገደቡ በተለይም አገዛዙ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሰላም ጥበቃን፣ የፀረ-ሸበርተኝነትን፣ የድንበር ጥበቃንና እንዲሁም የመከላከያ አዛዡን ስታፍ ሰራተኞች ስለማይመለከት ተጽዕኖው በወታደሩ ላይ ዝቅ ያለ መሆኑንን አንደማሳያ ይጠቁማሉ።

ፍርድ ቤቶችን ከፖለቲካ ተፅዕኖ ቁጥጥር ስር ውጭ ማድረግ፣ የሚዲያ፣ ሀሳብን በነጻነት የመግለጽና የመሰብስብ ነፃነት፣ እንዲሁም ሌሎች በቅድመ ዕርዳታው መስፈርት ሆነው የተዘረዘሩትን አንኳር ጉዳዮች ኢህአዴግ አጥብቆ የሚፈራቸውና ህልውናውን አደጋ ላይ የሚጥሉት በመሆናቸው በቀላሉ ለመቀበል የሚያዳግተው መስፈርቶች እንደሆኑ ለማንም ግልጽ ነው ሲሉ ዶ/ር ፈቃዱ ተናግረዋል። ይልቁኑም “እስካሁን ድረስ ለምን ዘገዩ? የሚመለከተው አካልም ሆነ የኦባማ አስተዳደር እስካሁን ድረስ ምን አስጠበቃቸው? አሁን ምን አዲስ ነገር ታያቸው? እስካሁን ድረስ የኢትዮጵያ ህዝብ ይሰቃይ ላይ አልነበረም ወይ? ለ22 ዓመታት የአገዛዙ የጭቆና ድርጊት ከአሜሪካ መንግስት የተሰወረ ጉዳይ ነበር ወይ? የሚሉት ጉዳዮች ሲነሱ የጸደቀውን ህግ ጉዳይ በጣም እንቆቅልሽ ያደርገዋል” በማለት ከጉዳዩ ጀርባ አንድ በጊዜ ሂደት እየጠራ የሚሄድ ጥቅል ጉዳይ ስለመኖሩ አመላካች እንደሆነ ምሁሩ ያስረዳሉ። በዚሁ መነሻ ፓለቲካዊ ትርጉሙ በቀላሉ ሊታለፍ የማይችልና ለአገዛዙ አስቸጋሪ ሁኔታ የሚፈጥርበት እንደሚሆን መገመቱ ከባድ እንዳልሆነ ይገልጻሉ።

“በሌላ ወገን ግን ለነፃነትና ለዲሞክራሲ ለሚደረገው ትግል አዎንታዊ ተፅዕኖ ያለውን ያህል፣ የራሱ የሆነ አሉታዊ ተፅዕኖም ሊኖረው ይችላል። ምናልባት አገዛዙ የተወሰኑ ነገሮችን የሚያሟላ ከሆነ ተቃዋሚው ኃይል ወደ መመቻመች /ኮምፕሮማይዝ/ ውስጥ በመግባት ለአጠቃላይ ነፃነት የሚደረገው ትግል አደጋ ውስጥ እንዲወድቅ ያደርገዋል። ይህ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ህዝብ የነጻነትና የብልጽግና ጉዳይ የዓለም አቀፍ ኮሚኒቲው በሚፈልገው አካሄድ ብቻ የሚወሰን ይሆናል ማለት ነው” ሲሉ አጠቃላይ ስጋታቸው ያስቀመጡት ዶ/ር ፈቃዱ፣ አጠቃላይ ህዝቡን የሚጠቅም የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የሀብት ክፍፍል፣ በተለይም የመሬት ጥያቄ፣ እስከዛሬ ድረስ የተፈጠረው አዲስ የይዞታና የህብረተሰብ ግኑኝነት፣ የኢትዮጵያ ህዝብና ዲሞክራቶች በሚፈልጉት መንገድ ላይፈቱ በሚችሉበት ሁኔታ መሰናክል ይደርስበታል። ስለዚህ ይህ ዓይነቱ ውሳኔ ህግ የዛሬው አገዛዝ ወደፊት በስልጣን ዙሪያ ሊኖረው የሚችለው ተሳትፎ፣ የኃይል አሰላለፍ ጉዳይና የፓለቲካው አወቃቀርና አካሄድ ጉዳይ ላይ፣ የኢኮኖሚያዊና የህብረትሰብ ግኑኝነት፣ ማለትም የሀብት ክፍፍልና አዲስ ሀብት በአዲስ የኢኮኖሚ ፖሊሲ መሳሪያ የመፍጠር ጉዳይ፣ የማህበራዊ ጥያቄ ጉዳይ፣ እነዚህና ሌሎች ለአገሪቱ የወደፊት እንደህብረተሰብ መኖርና መገንባት አንፃር በሰፊው ካልታየና ተቃዋሚ በሚባለው ጭንቅላት ውስጥ ካልተብላላ አደጋም ሊኖረው ይችላል።

በሌላ አነጋገር የዕድገታችንን ጉዞ ሊያጣምመው ይችላል። ምክንያቱም ይህ ዓይነቱ ውሳኔ ህግ እስከተወሰነ ደረጃ ድረስ ቢሟላና አገዛዙም እንደፖለቲካ ኃይል ተፎካካሪ ሆኖ የሚቆይ ከሆነ ወደፊት ለሚወሰዱ አገርን የሚጠቅሙ የዕድገት ዕርምጃዎች መሰናክል እንደሚሆን መጠርጠር ይቻላል። በሌላ አነጋገር የኢትዮጵያ ህዝብ ከዚህ አገዛዝ ባሻገር ሊገነባው የሚችለው አዲስ ኢትዮጵያ የብዙ ዓመታት ህልም ሆኖ ሊቀር እንደሚችል የራሳቸውን አማራጭ ምልከታ አስቀምጠዋል። ሌላኛውንም መንገድ አካተዋል።
በሌላው በኩል ደግሞ ይህ ውሳኔ ህግ በገዢው መደብ ውስጥ ቅራኔን መፍጠሩ እንደማይቀር፣ ህይወታቸውን ከአሜሪካን መንግስት ጋር ያያዙ ኃይሎች፣ በተለይም ግፊቱ እየበዛ ሲሄድ ወደፊት የሚመጣባቸውን አደጋ በማጤን ውሳኔ ህጉን በከፊልም ሆነ መሉ በሙሉ ተግባራዊ እናድርግ በሚሉ (ዘመናዊ ወያኔዎች) እና ውሳኔ ህጉን አንቀበልም በሚሉ አክራሪ ኃይሎች መሀከል ፍጥጫ መፈጠሩ እንደማይቀር ዶ/ር ፈቃዱ ግምገማቸውን አኑረዋል።

ቀጥሎስ?
በጉዳዩ ዙሪያ ከጎልጉል ጋር ወደፊት ሰፊ ቃለ ምልልስ ለመስጠት ፈቃዳቸውን የገለጹት አቶ ኦባንግ “እዚህ የተደረሰው በወፍ ዘራሽ ዝም ተብሎ አይደለም፤ ብዙ ተለፍቶ ነው። የአውሮፓ አገራት ተመሳሳይ ጥያቄ ሲቀርብላቸው አሜሪካን ምክንያት ሲያደርጉ ነበር። አሁን ሊያቀርቡ የሚችሉት አንዳችም ምክንያት የለም። አጠናክረን ስራችንን እንሰራለን። ሰክነን እንታገላለን። ኢህአዴግ ሳይወድ በግዱ በሩን ይከፍታል” ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። ከአውሮፓ አገራት ጋር አጋሮቻቸው በመሆን ስራቸውን በአዲስ መልክ እያጠናከሩ መሆናቸውን አስታውቀዋል። ይህንን አዲስ ህገ ውሳኔ በማስረጃነትና በማቅረብ የአውሮፓ መንግሥታም ተመሳሳይ እርምጃ እንዲወስዱ፤ በሚሰጡት ዕርዳታም ሆነ ድጎማ ላይ ኢህአዴግን ተጠያቂ በማድረግ የፖለቲካ ምህዳሩ እንዲሰፋ መርዳት ባይችሉም እንኳን ኢትዮጵያውያን ለሚያደርጉት ትግል እንቅፋት እንዳይሆኑ አበክረን እንወተውታለን ብለዋል አቶ ኦባንግ፡፡

አዲስ ስለ ጸደቀው ውሳኔ ህግ ለተጠየቁት “ብዙ ለመናገር ጊዜው ገና ነው። ኢትዮጵያዊያን በጎሳና በዘር የደም አዙሪት ውስጥ እየፈሩ እንዲኖሩ ሲደረግ የነበረው ድጋፍ ግን ማክተሚያው የተቃረበ ይመስለኛል፤ ኢህአዴግ እኔ ሥልጣን ከለቀቅሁኝ በአገሪቷ ውስጥ ደም መፋሰስ ይሆናል፤ ኢንተርሃምዌ የዘር ዕልቂት ይካሄዳል፤ የአፍሪካ ቀንድም ቀውስ ውስጥ ይገባል፣ ወዘተ በማለት እየዘላበደ የተቃዋሚውን ኃይል ከማዳከም አልፎ ሕዝቡ ፍራቻ ውስጥ በማስገባት አሜን ብሎ እንዲኖር የተጠቀመበት ማደንዘዣ ኃይሉ እየደከመ መጥቷል፤ ይኽኛው የውጭው ነው” የሚል ጥቅል መልስ ሰጥተዋል።

የመንታው መንገድ መሃንዲስ – ቻይና?
ቻይና ከኢህአዴግ በተለይም ከህወሃት ከፍተኛ ሰዎች ጋር አላት ከሚባለው “የተለወሰ ሽርክና” አንጻር አሜሪካ የምትሰጠውን የበጀት ድጎማና ርዳታ በየዓመቱ እየሸፈነች ኢህአዴግን ትታደጋለች የሚለው ጉዳይ ቻይና ከምትከተለው መሰረታዊ የንግድ እምነትና አንጻር በዜሮ የሚባዛ እንደሆነ ይነገራል። ቻይና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ነዳጅና ማዕድን እየተከተለች የምትገባበት ኢንቨስትመንት እያከሰራት እንደሆነ የሚናገሩ ክፍሎች ቻይና የሃይል ሚዛኑን ተመልክታ ርምጃዋን ከማስተካከል ያለፈ ስራ እንደማትሰራ ይናገራሉ።

በሌላ በኩል ደግሞ ሰሞኑን ይፋ ሆኖ የሰነበተውና የቻይናን “የዓይን ቀለም” የቀየረው የጃፓኑ ጠ/ሚ/ር የኢትዮጵያ ጉብኝትና የፖለቲካ መሞዳሞድ በቻይናና በኢህአዴግ መካከል የግንኙነት መሻከር እንደሚፈጥር የፖለቲካ እሳቤ አለ፡፡ ኢህአዴግ ከቻይና ታሪካዊ ጠላት ጃፓን ጋር በግልጽ ይህንን ዓይነቱን “ያደባባይ ፍቅር” ማሳየቱና የፖለቲካ ቅርጫ ውስጥ መግባቱ የምዕራቡ ወዳጅ ከሆነችው ጃፓን ጋር በመወገን በምዕራባውያን የድጎማ ዕቀባ ጭስ እንዳይታፈን መተንፈሻ እየፈለገ መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡
ሰጥቶ በመቀበል፣ አበድሮ በመውሰድና የአምባገነኖችን ህልውና ለማስጠበቅ የሚውል ቴክኖሎጂን በመገንባት አፍሪካን እያለበች ያለችው ቻይና ኢህአዴግ ከምዕራባውያን የሚያኘው እርዳታ ቢቋረጥበት ከብድር በዘለለ በየዓመቱ ሌሎቹ እንደሚያደርጉት በጀት እየደጎመች የኢህአዴግን ነፍስ ለመጠበቅ የምትምልበት ዘመን ሊኖር እንደማይችል ከግምት በላይ የሚናገሩ ክፍሎች፣ ኢህአዴግ መለሳለስ በመሳየት ቆዳውን ሊቀይር ይችላል የሚለው እምነት አላቸው። አሜሪካ አሁን የያዘችው አቋም ከምትከተለው አዲሱ ፖሊሲዋና በሂደት የኢትዮጵያ ጉዳይ ተመርምሮ የተያዘ ስለሆነ እንደ HR2003 በውስዋስ (ሎቢ) ሊቀለበስ የሚችል እንዳልሆነ አጥብቀው ይናገራሉ።

ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር መጀመሪያ ላይ ለጎልጉል አስተያየት የሰጡ ዲፕሎማት ጠቅሰን ገመዱ በኢህአዴግ ላይ እየከረረ እንደሚሄድ በዘገብን ወቅት “ኢህአዴግ በቅርቡ የአውሮፓ ህብረት ተወካዮች እስር ቤቶችን እንዳይጎበኙ እንደከለከለው ማድረግ አይችልም … በደቡብ ሱዳን ያለው የፖለቲካ ቀውስ፣ በሶማሊያ ጭብጡ ያለየለት ሁከት፣ በኤርትራ ያለው የዛለ መንግስት እጣፈንታና የኢትዮጵያን ህዝብ በዘር ከፋፍሎ ጥቂቶች እንዲበለጽጉ ያደረገው ኢህአዴግ መጨረሻው አሜሪካንን በእጅጉ ሃሳብ ላይ ጥሏታል። በዚህም የተነሳ ኢትዮጵያ ውስጥ እየሰፋ የሄደው ቁርሾና የጥላቻ ፖለቲካ ሳይፈነዳ ኢህአዴግን ማረቅ የአሜሪካ ቀዳሚ አጀንዳ ሆኗል። ይህንን አጀንዳ አሜሪካ በቀላሉ ተጭበርብራ የምትቆልፈው አይሆንም። ኢህአዴግ በጎሳ ደምና እኔ ከሌለሁ አገርና አፍሪካ ቀንድ ይተራመሳል በሚል የሚነግደውን ንግድ አሜሪካኖቹ ተረድተዋል ብለን ነበር፡፡ የአሜሪካው ምክርቤት እንደራ የሆኑት ክሪስ ስሚዝ “በሽብር ዙሪያ ከአሜሪካ ጋር ተባብሮ መስራት ህዝብን ለማፈንና ረግጦ ለመግዛት ዋስትና አይደለም” በማለት መናገራቸውን ከዲፕሎማቱ አስተያየት ጋር አክለን ነበር፡፡

አዲስ የወጣውን ውሳኔ ህግ አሜሪካ በኢህአዴግ ላይ ፊቷን እያዞረች መሆኗን ማሳያ ነው በማለት የሚወስዱ ክፍሎች ይህ ህግ ከቀድሞው HR2003 ፈጽሞ የተለየ እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ የዛሬ አስር ዓመት፤ HR2003 በምክር ቤት ደረጃ የእንደራሴዎችን ከፍተኛ ድጋፍ ካገኘ በኋላ የሕግ መወሰኛ ም/ቤት (ሴኔት) አጽድቆት በፕሬዚዳንቱ ተፈርሞ የአሜሪካ ፖሊሲ እንዳይሆን በመደረጉ ተቋማዊና አስተዳደራዊ ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ ጉዳዮች መከኑ። በወቅቱ የህጉ መርቀቅና እንዲጸድቅ የተጀመረው እንቅስቃሴ ያስበረገገው ኢህአዴግ ጡረተኛ የሴኔት አባላት ከሚመሩት ዲኤልኤ ፓይፐር ከተባለ የውስዋስ (ሎቢ) ቡድን ጋር ከፍተኛ በጀት በጅቶ ታገለ። ባፈሰሰላቸው መጠን ወትዋቾቹ ባልደረቦቻቸውን ጠመዘ&#48

የአንድ ብሄር የበላይነት እና አድሏዊነት ካልተወገደ ሰራዊቱ እንዳይታመስ ያሰጋል::

በወያኔ እና በኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት የጦር መኮንኖች እና ወታደሮች መሃል ጋብ ያለው ጡዘት ጊዜውን እየጠበቀ እየገነፈለ መሆኑን ውስጥ አዋቂ ምንጮች ለምንሊክ ሳልሳዊ በላኩት መልእክት ጠቁመዋል::በሕወሓት ጄኔራሎች የሚመራው የመከላከያ ሰራዊቱ የበታች የጦር መኮንኖችን ከዚህ ቀደም ለመከላከያ ደህንነት ቢሮ ባስተላለፈው መመሪያ መሰረት ከሰራዊቱ መቀነስ ያለባቸው የቀድሞ የብኣዴን እና የኦሕዴድ ታጋዮች የነበሩ የጦር መኮንኖች ዝርዝር ተጠንቶ ለኢታማጆር ሹሙ የቀረበ እና ይህንንም መሰረት አድርጎ መኮንኖቹን ከሰራዊቱ ውስጥ ለመቀነስ መታቀዱን ምንጮቹ ገልጸዋል::

እንደ ምንጮቹ መረጃ ከሆነ ከቀረቡት 2369 ከምክትል መቶ አለቅነት እስከ ኮሎኔልነት ማእረግ ያላቸው የቀድሞ የበረሃ ታጋዮች የአሁን መኮንኖች ውስጥ አላስፈላጊ የሚባሉት ተጣርተው ከሰራዊቱ በዳረጎት የሚቀነሱ ሲሆን ከደርግ ስርኣት ጋር ቁርኝት የነበራቸው ከብሄራዊ ውትድርና ሰራዊቱን የተቀላቀሉት በቦርድ እና በጤንነት እክል በጡረታ የሚሰናበቱ እንዲሁም በማስጠንቀቂያና በደምወዝ ቅጣት የሚታለፉ እንዳሉም ታውቋል:: ይህንን ሁሉ ችግር የፈጠረው በመሃከላቸው የተነሳው የአንድ ብሄር የበላይነት እና አድሏዊነት የዘር ቆጠራ የፖለቲካ ሕዝባዊ ጥያቄዎች እና የሕገመንግስት ተግባራዊነት ክርክር የጫረው አለመግባባት ሲሆን በሰርኣቱ ውስጥ የተጠየቀው የጥቅማ ጥቅም ጥያቄም ሌላኛው መነካከሻ መሆኑን ምንጮቹ ተናግረዋል::

ይህ በእንዲህ እንዳለ በሃገር ውስጥ እና በአለማቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተቃውሞ እየደረሰበት ያለውን የወያኔውን የአሸባሪነት ሕግ በሕገመንግስቱ ውስጥ ለማካተት ጥናት ሊጀመር ሲሆን ከዚህ ቀደም እንደነበረው የአደገኛ ቦዘኔዎች ሕግ በሂደት አይን እያየ አሁን ያለውን የአሸባሪነት ህግ ማክሰም የሚል ሃሳብ ተይዞ ጥናቱ እንደሚካሄድ ታውቋል::ምንልክ ሳልሳዊ

እንዳለ ጌታ ከበደ

(የ2005 ዓም የ‹በጎ ሰው› ሽልማት ተሸላሚ)

በልቦለድ መጻሕፍቱና በፕሬስ ውጤቶች ላይ በሚያወጣቸው መጣጥፎች የምናውቀው እንዳለ ጌታ ከበደ ‹‹ማዕቀብ›. የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ እያስነበበን ነው፡፡ መጽሐፉ ስለሳንሱር፣ ስለ ደራስያንና  ስለ አሮጌ መጻሕፍት አከፋፋዮች የሚተርክ ነው፡፡

የእንዳለ ጌታ ‹ማዕቀብ›› ለየት ያሉ ነገሮችን ያሳየናል፡፡ ሳንሱር በንጉሡ፣ በደርግና በኢሕአዴግ ዘመን ምን ጠባይ እንደነበረው፣ እነማን በሳንሱር እንደታረዱ፣ እንደተደረቱና እንደተቦጨቁ ይተርካል፡፡ ትረካው ሳንሱር ያሳቀቃቸውን ደራስያን ብቻ ሳይሆን በሳንሱር መሥሪያ ቤቱ ተቀምጠው ሳንሱር ሲያደርጉ የነበሩ ሰዎችንም ትረካ ያካተተ ነው፡፡

የሳንሱር ስም ሲጠራ እንደ ሰይጣን ስም ቆጥረውት ‹በስመ አብ› የሚሉ ደራስያን ያሉትን ያህል ‹‹ሳንሱር መኖር ነበረበት፣አሁንም መኖር አለበት›› ብለው የሚያስቡ የሳንሱር ባለሞያዎችንም አስተያየትና ሙግት ታነቡበታላችሁ፡፡ በዚህ የሳንሱር ትረካ ከዚህ በፊት ያልሰማናቸው፣ ብንሰማቸውም በተሟላ ሁኔታ ያልሰማናቸውን የሀገራችንን የደራስያን መከራዎችና ተጋድሎዎች ታነባላችሁ፡፡ ኢትዮጵያ እንዴት ታላላቅ የሃሳብና የድርሰት ሰዎቿን እንዳጣች ታያላችሁ፤ ማስፈራራት፣ ግርፋት፣ እሥር፣ አካላዊ ጥቃት፣ ስደትና ግድያ ስለተፈጸመባቸው ደራስያን እያስነበበ ወደኋላ ይዟችሁ ይነጉዳል፡፡

ያውም የሚያወራችሁ እንዳለ ጌታ አይደለም፡፡ የሚያቀርብላችሁም ደረቅ የጥናት ጽሑፍ አይደለም፤ ራሱ ሳንሱር ነው በሰውኛ የራሱን ታሪክ የሚተርክላችሁ፡፡

ሳንሱርን ስትሻገሩ ደግሞ የኢትዮጵያን ደራስያንን የሕይወት ገጠመኝ ይጋብዛችኋል፡፡ ከልደት እስከ ሞት በሚተርክ የሕይወት ታሪክ አጻጻፍ መንገድ አይደለም፡፡ ከታሪካቸው አንድን ሳቢ ጉዳይ መርጦ፣ አንዳንዱን ራሱ ያየውን፣ አንዳንዱን የሰማውን፣ አንዳንዱን ደግሞ ያነበበውን፡፡ አንዳንዱ አስገራሚ፣ አንዳንዱ አሳዛኝ ሌላው ደግሞ አናዳጅ ታሪክ ነው፡፡ እንዳለ ጨዋነት በተሞላበት መንገድ የደራስያኑን ክፉና ደግ ገጽታ ያሳየናል፡፡ ሱስና መጠጥ እንዴት አድርጎ የብዙዎችን ታላላቅ ደራስያን ሕይወት እንደቀጠፈ በኀዘን እናያለን፡፡ በሕይወታቸው ዘመን ታዋቂ የነበሩት ደራስያን የነበራቸውን የድህነት ሕይወት እንታዘባለን፡፡ አንዳንዶቹ በቅዱሳን ገድል ላይ የምነባቸውን የደግነት ሥራዎች  ሳናውቃቸው እንዴት ይሠሩ እንደነበር አይታችሁ ትደነቃላችሁ፡፡

በመጨረሻው ክፍል በሀገራችን ታሪክ ታላቅ ቦታ ካላቸው ነገር ግን ምንም ቦታ ካልተሰጣቸው ወገኖች አንዱ የሆኑትን የአሮጌ መጻሕፍት አከፋፋዮች ታሪክ የያዘውን ክፍል ታገኛላችሁ፡፡ እጅግ መሳጭ ታሪክ፣ ብዙ የማናውቃቸው የሀገራችን ጉዶች፡፡

 የራስዋ የሆነ ፊደል ባላት ሀገር መጻሕፍት ፀረ አብዮት ሆነው እንዴት እንደተቃጠሉ፤ እንዴት የታሪክ መዛግብት በኪሎ እንደተሸጡ፣ ዛሬ የምንኮራባቸው የድርሰት ሀብቶቻችን እንዴት ተወግዘው ከመደርደሪያ እንደተባረሩ ይተርክልናል፡፡ ተራኪው እንዳለ አይደለም፡፡ እየዞረ ያነጋገራቸው ከአርባ ዓመት እስከ ሃያ ዓመት በአሮጌ መጻሕፍት ሽያጭ የተሠማሩ ክቡራን ናቸው፡፡

እነማን ነበሩ እዚያ የሚመጡት? እነማንን ያደንቃሉ? ማን ምን ዓይነት መጽሐፍ ይገዛ ነበር? እነማን አንባቢ ናቸው? እነማን ደግሞ የንባብ ፀር፣ ጉዳችንን ይዘረግፉላችኋል፡፡ የታላላቅ ሰዎችን መጽሐፍ ልጆቻቸው አውጥተው የሸጡበት ታሪክ፣ በልጆቻቸው የተሸጠባቸውን መጽሐፍ አባቶች መልሰው የገዙበት ገጠመኝ፤ የታላላቅ ሰዎች ፊርማ ያረፈባቸው መጻሕፍት እንዴት ወደ አሮጌ ተራ እንደሚመጡ ያወጓችኋል፡፡ ዕውቀትን ለሕዝብ ለማከፋፈል ሲሉ አሮጌ መጻሕፍት ሻጮች የተቀበሉትን ስቃይና መከራ ይተርኩላችኋል፡፡

እኔ እንዲያውም በአዲስ አበባ ከተማ የሚሠሩ አደባባዮች በማናውቃቸው የውጭ ኩባንያዎች ስም ከሚጠሩ ምናለ አንዱን እንኳን ‹የአሮጌ መጻሕፍት ሻጮች አደባባይ›› ብንለው ብዬ አስቤያለሁ፡፡ እነርሱ ነበሩ የመረጃ መቀባበያዎቻችን፣ እነርሱ ነበሩ የታሪክ ምንጮቻችን፣ እነርሱ ነበሩ አያሌ መጻሕፍትን ከመቃጠል አድነው ለዘመናችን ያደረሷቸው፡፡

ዋጋው 60 ብር ብቻ ነው፡፡ ከጀመራችሁት ደግሞ ሳትጨርሱ አታቆሙትም፡፡ አንቡትና ተደሰቱ፡፡

መልካም ንባብ

በቅርቡ ለንባብ ካበቃው መጽሐፍ ጋር በተያያዘ የስም ማጥፋት ክስ የተመሰረተበት የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ ሆነው ደራሲ ዳንኤል ተፈራ ዛሬ በድጋሚ ማዕከላዊ እንዲቀርብና በድጋሚ የተከሳሽነት ቃሉን ከሰጠ በኋላ በመኪና ሊብሬ ዋስ ከእስር ተፈቷል፡፡ ኢህአዴግ በመንግስት እና በተለጣፊ ፓርቲዎች አማካኝነት በአንድነት ፓርቲ አመራሮችና አባላት ላይ የእስር ዘመቻ መክፈቱ ይታወቃል፡፡

የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የብአዴን ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ አለምነው መኮንን መኖሪያ ቤት በድንጋይ መደብደቡን የፍኖተ ነፃነት ምንጮች ጠቆሙ፡፡ የፍኖተ ነፃነት ምንጮች እንጠቆሙት ባሳለፍነው ሳምንት የካቲት 1 እና የካቲት 2 ቀን 2006 ዓ.ም(ቅዳሜና እሁድ) ለሊት በተደጋጋሚ ማንነታቸው ባልታወቀ ግለሰቦች መኖሪያ ቤታቸው በድንጋይ መደብደቡን ተከትሎ ቤታቸው ቀንና ለሊት በፖሊስ እየተጠበቀ ይገኛል፡፡ አቶ አለምነው መኮንን የአማራን […]

“ኢትዮጵያዊ ነኝ፤ ኢትዮጵያዊ ማንነት አለኝ” ብዬ ስል የራሴ (የግሌ) ማንነት የለኝም ማለት አይደለም። የአከባቢ ማንነት የለኝም ማለት አይደለም። የክልል (የብሄር) ማንነት የለኝም ማለት አይደለም። ወይም እነዚህ የተለያየ ደረጃ ያላቸው ማንነቶቼ መጥፋት አለባቸው ማለት አይደለም። እኔ ኢትዮጵያዊ ነኝ ስል የራሴን ማንነት አልቀበልም ማለት አይደለም። የራሴ ማንነት ስላለኝ ነው ኢትዮጵያዊ ማንነት ሊኖረኝ የቻለው። እኔ የግል ማንነት ባይኖረኝ […]