ኦብነግ ‘የተጠለፉ’ ያላቸው መሪዎቹ ሆስፒታል እንደሚገኙ ገለፀ – ፌብሩወሪ 12, 2014
ONLF – Ethiopia – Hassan Abdulagi, Dina Mufti
ONLF – Ethiopia – Hassan Abdulagi, Dina Mufti
አስገራሚው የሳውዲው “ኮራጅ ” አባት ምክር ነገሩ እንዲህ ነው …ከ20 ዓመት በፊት ሳውዲው ወጣት ራሱን ለሁለተኛ ደረጃ ፈተና ከማዘጋጀት ይልቅ በረቀቀ መንገድ ለፈተናው መልስ የሚሆነውን ማጭበርበሪያ የመልስ ወረቀት አዘጋጅቶ ለፈተና ይቀርባል። ፈተናውን በረቀቀ መንገድ አጭበረብሮ ሰርቶታልና ፈተናውን በተገቢ ውጤት አልፎ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ለማለፍ በቃ ! ከዚያም በታዋቂው ዩኒቨርሲቲ ትምህርቱን ተከታትሎ ይመረቃል። ይህ ሁሉ አልፎ […]
ክፍል አንድ በቀናት አቆጣጠር ሰባተኛው እረድፍ በምትይዘው በዕለተ ቅዳሜ ከዚህ ቀደም በጸረ ሽብር አዋጁ ዙሪያ ካደረግነው የተሟሟቀ ክርክር በኋላ ከገዥ ፓርቲ ጋር በሃሳብ ክርክር ለ11 ሰዓታት የተሟገትነው ቅዳሜ ጥር 17 ቀን 2006 ዓ.ም ባለፈው ሳምንት ነበር፡፡ ይህ መድረክ የተዘጋጀው በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በጋዜጠኝነት እና ኮሚዩኒኬሽን የድህረ ምረቃ ተመራቂ ተማሪዎች ከትምህርት ቤቱ ጋር በመተባበር እንደነበረ ከደረሰን […]
ESAT Radio Daily Broadcast to Ethiopia. Frequency Details: 7 days a week Short Wave (SW) from 8:00 pm to 9:00 pm (Local Ethiopian Time) 19 Meter Band 15355 kHz, 15360 kHz, 15365 kHz, 15370 kHz, 15380 kHz, 15385 kHz and 15390 kHz Download/Listen
(በጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ፤ ከዝዋይ ማረሚያ ቤት) ምንጭ ኢትዮ-ምኅዳር ጋዜጣ
የነገሮች ሁሉ መድረሻ እስር ቤቶች እየሆኑ መጥተዋል፡፡
‹‹ይህንን ስለመሳሰሉ ጉዳዮች መወያየት ክልክል ነው፡፡›› በማለት በተንጎላጀጀ ድምፅ ጠባቂው ተናገረ፡፡ ቀጠል አደረገናም ‹‹መነጋገር የምትችሉት ስለቤተሰብ ጉዳዮች ብቻ ነው›› በማለት ተናገረ፡፡ ይህን ከላይ ያለውን ሐሳብ የሚመለከት ማንኛውም አንባቢ፣ ጉዳይ የተፈፀመው እዚህችው እማማ ኢትዮጵያ ሰማይ ስር ባሉ አጃኢበኛ እስር ቤቶች፣ ቤተሰብ መጠየቂያው እንደሆነ መጣራቱ አይቀርም፡፡
ይሁንና በመግቢያው ላይ ያለው ጽሑፍ ተቀንጭቦ የተወሰደ ‹እናት› ከተሰኘውና እ.ኤ.አ. በ1906 ከታተመው የስመ ጥሩው ሩስያዊ ደራሲ ማክሲም ጎርኪይ ታሪካዊ ልቦለድ ገፅ 102 ላይ ነው፡፡ የዛሬ 108 ዓመት አካባቢ ማለት ነው፡፡ አቤት ርቀቱ!… ይህ ርቀት ግን ለእኛ ምንም ማለት ያልሆነ ይመስላል፤ ለምን? ቢሉ ዛሬም ይህንንና ይህን የመሳሰለውን አስፍተን እየሠራን እንገኛለን፡፡ እንዲያውም በአንዳንድ ሁኔታዎች እየተጓዝን ያለነው የቁልቁለት ሩጫ በእጅጉ አሳሳቢ ሆኖ ይገኛል፡፡
የነገሮች ሁሉ መድረሻ እስር ቤቶች እየሆኑ መጥተዋል፡፡
‹ጠበቅ ያለ እርምጃ፣ የማያዳግም እርምጃ፣ የማስወገድ እርምጃ፣…› ወዘተ የሞሉ ከሕግ መርሕዎች ሳይሆን ከጥላቻ ፖለቲካ የሚመነጩ ፀያፍ አነጋገሮችን በሕዝብ የመገናኛ ዘዴዎች ሲተላለፉ እየሰማን እየታዘብን ነው፡፡ ቃል በቃል ‹ቀይ ሽብር ይፋፋም› ብሎ ማወጅ የቀራቸው የሕግም የግብረገብም ሚዛን ያልወጣላቸው ቀረርቶች በተለይ በእስር ቤት የምንገኝ ኢትዮጵያውያንን እየሰበሰቡን ይገኛሉ፡፡
ዝዋይ የአገራችን ‹ሳይቤሪያ ግዞት›
በኢ.ቴ.ቪ. የአብዮታዊ እርምጃ ፕሮግራሞች በቀረቡ ማግስት አሁን በዝርዝር ብለው የብዙ ቤተሰቦችን ስሜት ሊያሸማቅቁ የሚችሉ ሰቆቃና እንግልቶች በአስደማሚ ስልት ተቀናብረው ተፈፃሚ ይሆናሉ፡፡ እስኪ የተወሰኑትን እንይ፡፡ ማንኛውም ታሳሪ ቤተሰብ በቅርብ ሊጎበኘው በሚችለው እስር ቤት ይታሰር የሚለው ሕግ የተሻረው በእኛ ላይ ነው፡፡ ዝዋይ የአገራችን ‹ሳይቤሪያ ግዞት› ማለት ናት፡፡ ቤተሰብ ያን ያህል የበርሃ ጉዞ አቋርጦ የእኛዋ ሳይቤሪያ ሲደርስ በአድካሚና ግብረ-ገብ በጎደለው ፍተሻ መከራውን ማየቱ አንሶ ጆሮ ግንዱ ላይ በቆሙ የቤተሰብ አገናኞች ቤተሰባዊ ገመናውን አሳልፎ ይሰጣል፡፡ ሕፃናት ልጆች ወላጆቻቸው አንድ ላይ ሆነው ናፍቆታቸውን መወጣት አይችሉም፡፡ አንዳንድ ጊዜ ፖሊሶቹ ሲዘናጉልን ልጆቻችንን አቅፈን እንስማለን፡፡ ይህ ከሆነ ቁጣና ዘለፋው ምንም አይደለም፡፡ ግን በሁኔታው ሕፃናቱ ክፉኛ ይበረግጋሉ፣ የእኛ ስጋት ይጋባባቸዋል፤ በዚህም መንፈሳቸው እርብሽብሽ ብሎ ወደቤታቸው ይመለሳሉ፡፡
ሁኔታው በዚህ አያበቃም፡፡ ምንም እንኳን የመጠየቂያ ሰዓቱ በግልፅ የተቀመጠ ቢሆን ከቤተሰቦቻችን ጋር ገና መነጋገር ስንጀምር ‹‹በቃ… ቶሎ ጨርሱ›› የሚባልባቸው ጊዜዎች ብዙ ናቸው፡፡ ቀጥሎ የሚመጣው የእስር ቤት ማኅበራዊ ጉዳዮችን ማለትም ለሳሙና፣ ለምግብ ማጣፈጫ፣ ለሻይ ለቡና፣ ለውስጥ አልባሳት፣ ለውኃ ማከሚያ/ውኃ አጋር/ ወዘተ፤ ገንዘብ የሚያስፈልገን ቢሆንም እና እንደሚያስፈልጉ ቢታወቅም ጉዳዩ ለይቶለት የማሰቃየት፣ ማንገላታት፣ መበቀል ሆኗልና ለአንድ ወር ከአንድ መቶ ብር በላይ መጠቀም እንዳንችል የተከለከልን የመሆኑ አሳፋሪ ሐቅ ነው፡፡ ይህ እየተፈፀመ ያለው ደግሞ ዝዋይ እስር ቤት ውስጥ ብቻ ነው፡፡ በዚህ የተነሳም ለመግለጽ በሚከብድ ሁኔታ ሰብኣዊ ክብራችንን የማዋረድ ሙከራዎች እየተፈፀሙ ነው፡፡
በአገራችን ላይ እኔ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቴን የጨረስኩት ዝዋይ በመሆኑ ብዙ ወዳጅ ዘመዶቼ በእዚህ ይገኛሉ፡፡ ሆኖም ለአካባቢው ነዋሪዎች በሳምንት እንዲጠይቁን የተፈቀደላቸው አንድ ቀን /ረቡዕ/ ብቻ ሲሆን ‹‹የት ነው የምታውቁት? እንዴት አወቃችሁት? ምንድን ነው የሚያመላልሳችሁ?›› በሚሉትና በሌሎችም ጥያቄዎች ተደናግጠው መምጣቱን እርግፍ አድርገው ትተውታል፡፡
ሀገሩ ሞቃታማ ነውና በዚያ ላይ በእያንዳንዱ ቤት እስከ 150 ሰው ይታሰርበታል፡፡ ይህ ሁሉ ተደማምሮ እስረኛው የቱንም ያህል ፅዳቱን ለመጠበቅ ቢሞክርም የተባዩ መርመስመስ የእነ ትኋን እንዲህ መራባት፤ ለማሰብ እንኳን ይዘገንናል፡፡ ሌሊቱን ሙሉ ገላን ሲቆፍሩ ማደር ነው፡፡ ሊናገሩት ይከብዳል፣ አንባቢንም ቅር ያሰኛል፤ ግን ይህ የፊልም ትረካ ሳይሆን በእማማ ኢትዮጵያ ልጆች ላይ ሆን ተብሎ እየተፈፀመ ያለ ደባ ነው፡፡ […] ግን የባሰ አታምጣ ማለት ነው!
የዝዋይን ልጅ ውሃ ጠማው
ግን የባሰ ነገር አለ፡፡ አፈር ቅጠል የማይል ምግብ ይቀርብናል፡፡ ‹በደንባራ በቅሎ ቃጭል ተጨምሮ› ከፍተኛ የውኃ እጥረት /ዝዋይ ሀይቅ አናት ላይ ተቀምጠን/ አለ፡፡ የእስር እስር እንዲሉ ጄኔራል መኮንኖቹን ጨምሮ አብዛኛዎቹ አባሪዎቻቸውና ሌሎች ሌሎች የተወሰንን እስረኞች የምንገኘው በልዩ ቅጣት ጭለማ ቤት ውስጥ ነው፡፡ ይህንን ሁሉ እንደምንም ለመቋቋም ጥረት ማድረግ ይቻል ይሆናል፡፡ አዲሱ ስልት ግን መዘዙ በጣም አደገኛ በመሆኑ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ፣ እያንዳንዱ ሃይማኖት ያለው፣ ፈርሐ እግዚአብሔር ያለው፣ እያንዳንዱ የመሠረታዊ ሰብኣዊ መብቶችና ነጻነቶች መከበር የሚያሳስበው እያንዳንዱ ሰው የሆነ ሰው ሁሉ ሊያውቀው ይገባል ስንል ድምፃችንን እናሰማለን፤ በሕክምና ንፍገት ወደሞት እየተገፋን ነው፡፡
ሕመም ካልታከመ መጨረሻው ሞት ነው፡፡ የሞቱም ሰዎች አሉ!
ከወር በፊት ገደማ ወጣቱ የአንድነት ፓርቲ አባል ናትናኤል መኮንን ለሕክምና በሪፈር ወደ ቃሊቲ ተልኮ የነበረ ቢሆንም፣ የዛኑ ዕለት ሕክምናውን ተነፍጎ ከሌሊቱ 5፡00 ሰዓት አካባቢ እንዲመለስ ተደርጓል፡፡ እስካሁን በሕመሙ እየተሰቃየ ይገኛል፡፡ የኢብአፓ ሊቀመንበር የነበረው ዘሪሁን ገ/እግዚአብሔር እንደዚሁ ለተጨማሪ ሕክምና ሪፈር ተብሎ ሲጠባበቅ ከቆየ በኋላ ዘዴው ተፈፃሚ ሆነበት እጁን አጣጥፎ ተቀምጧል፡፡ ከሕመሙ ጋር በተያያዘ በአካሉ ላይ አሳሳቢ ሁኔታ እየታየበት ይገኛል፡፡ ከዚህ ቀደም ገልጬው የነበረው የእኔ የኩላሊት ሕመም አሁን ለመቀመጥም፣ ለመንቀሳቀስ እያወከኝ የሚገኝ ሲሆን፣ እኔን ከቃሊቲ ዝዋይ ለማምጣት የተደረገው የተቀናጀ መረብ ሩብ ያህሉን ለሰብኣዊነት አውለውት ቢሆን ኖሮ እኔም ፋታ፣ እነሱም እርካታ ባገኙ ነበር፡፡ ሕመም ካልታከመ መጨረሻው ሞት ነው፡፡ የሞቱም ሰዎች አሉ!
የጄኔራል መኮንኖቹ አባሪዎች የነበሩት ኮረኔል ተስፋዬ ኃይሉ እና ኢንጂነር ክፍሌ ስንሻው፣ በዶክተር መረራ በሚመራው ኦሕኮ ፓርቲ አባል የነበሩት አሕመድ ነጃሺ፣ በጭለማ ቤት የከረመው ተስፋሀን ጨመዳ፣ የቤንሻንጉሉ አዛውንት ወዘተ ተገቢውን ሕክምና በማጣት ሕይወታቸውን ያጡ የእማማ ኢትዮጵያ ልጆች ናቸው፡፡ እንዴት ሕክምና ይከለከላል!? ግፍና ጭቆና ተቃውመው ደማቸውን ያፈሰሱና አጥንታቸውን የከሰከሱ ታጋዮችን በሥልጣን ማግስት ከፍርድ በመለስ በየእስር ቤቱ ያሉ ኢትዮጵያዊ ወገኖቻቸው በሕክምና እጦት ሲረግፉ በእርካታ ማርመምን ከየት ተማሩት!? የኢትዮጵያ ሕዝብስ ምን ይላል!? ሰው የሆኑ ሰዎች ሁሉ ከቶ ምን ይላሉ!?
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ!
ምንሊክ ሳልሳዊ:-አሜሪካ ውስጥ ያፈንዳ የገደለ ይተኮሰ የፈጀ …. አሜሪካዊ ዜጋ አሸባሪ ተብሎ ሲከሰስ ሲዘለፍ አላየንም ይልቅ እብድ ንክ ምናምን በሚል ከእስር ቤት ወደ ፍርድ ቤት እና ምርመራ ይሄዳል:: አሜሪካንም እኮ የአሸባሪዎች ህግ አላት:: ሆኖም ዜጎቿን አታጠምድበትም:: ከሌላ አገር ዜጋ ጋር አያይዛ ቲለጥፈዋለች … የአሜሪካ ዜግነት እንኳን ቢኖረው ኦሪጂኑን ነው የምትጠራው እንጅ አሜሪካዊ አሸባሪ ብላ አደባባይ ዜጎቿን በንዝህላልነት አታስርም አትገልም አታንገላታም:: ሌሎችም አገራት እንዲሁ …በአሸባሪነት ህግ ዜጋን አያጠምዱም :: የአሸባሪነት ህግ ከምንጩ በአሸባሪነት አሜሪካን የመዘገበቻቸውን አሸባሪ ድርጅቶች (ሕወሓትን ይጨምራል) ለመዳኘት የወጣ ነው::
እዚህ ጋ ግን ሲመጡ እኛ አገር የህጉ ትርጉም ለየት ብሎ እያየነው ነው::በዚህ ህግ ይዳኛሉ የተባሉት እነ አልቃይዳ እና የታጠቁ መሰሎቹ ሳይሆኑ የተዳኙበት የራሳችን ዜጎች የሆኑ ኢትዮጵያውያን ያውም ያልታጠቁ ብእር እና ወረቀት ያነገቡ የህዝብን ነጻነት እና መብት ያስተማሩ ወዘተ… ናቸው:: በአለም አቀፍ ደረጃ አሸባሪነትን ለመቆጣጠር የተባለው ዜጎችን ማጥመድ መሆኑ አሳሳቢነቱ እንደተጠበቀ ሆኖ በሃገራችን አሸባሪነ የተባሉት ግን የማናውቃቸው ሰዎች ሳይሆኑ መንግስትን በይፋ የተቃወሙ ለውጥ የጠየቁ የፖለቲካ መሪዎች ጋዜጠኞች እንዲሁም ሃይማኖታዊ ነጻነታቸውን የጠየቁ የሃይማኖት ምሁራን ናቸው::እንዲሁም የሰብኣዊ መብታቸው ተጥሶ ከህጉ ውጪ በላያቸው ላይ ከባድ እና አደገኛ የሆነ ፕሮፓጋንዳ እየተካሄደባቸው ሳይመሰከርባቸው እና ማስረጃ ሳይቀርብባቸው ወንጀለኛ ተደርገው እንዲታዩ ተደርጓል::
ይህ የሽብር ህግ በተለያየ ጊዜ እንዲስተካከል እና እንዲለወጥ እንዲሻሻል ዜጎችን ማጥመድ እንዲያቆም .. የተለያዩ ቡድኖች አገሮች እና ኢትዮጵያውያን የገዛ የወያኔ ስርኣት አባላት ሳይቀሩ እየተናገሩ ነው :: ግን የወያኔው ጁንታ ይህንን ለስልጣን ማስረዘሚያ እና ለተቃዋሚዎች ማፈኛ እየተጠቀመበት ነው::በአለም አቀፍ ደረጃ አሸባሪ እንደሆነ የሚታወቀው ሕወሓት ምእራባውያን እየነቁ እንዳይነቁ አድርጎ እያጭበረበራቸው በሚያገኘው የብድር እና የእርዳታ ገንዘብ ዜጎችን ለማፈን እና ለመግደል እየተጠቀመበት ነው::ይህ የሽብር ህግ የማያፍናቸው አፋኞቹን የአገሪቱ ባለስልጣናት እና በተቃዋሚ ውስጥ የተሰገሰጉ ባላንጣዎችን የሚያሳፍኑ ብቻ ነው::
ይህንን ህግ በተመለከት መፍትሄ ከማምጣት ይልቅ በየጊዜው ለማፈኛነት መጠቀምን የመረጠው የወያኔ ጁንታ ከትግራይ እስከ ሞያሌ ከጋምቤላ እስከ መልካጀብዱ እና ጎደ በሃገሪቱ በተለያዩ ማእዘናት ዜጎችን በማሳደድ ሰርተው እንዳይኖሩ እንዲፈናቀሉ የፖለቲካ እምነታቸውን እንዳያራምዱ እንዳይጽፉ እንዳያነቡ በማድረግ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ሽብርን እየነዛ አሸባሪ እያረገ በማሰር ከአገር ተሰደው እንዲወጡ በማድረግ እና በመግደል ጭምር ወንጀል እየፈጸመ ስለሚገኝ ህዝቦች በጋራ ታግለን ስርኣቱን መቃብር ልንከተው ይገባል::
ምንሊክ ሳልሳዊ:-ሕንፃ- መኪና -ቪላ -ኢሮ -ብርና ዶላር -ጠበንጃ እና ቦምብ- እየተቆጠረ ሙስና እንደሚወራልን ሁሉ … የሃገሪቷን ዜጎች የጎዳ ;ሕግን እና ህገመንግስትን ያጣመመ; የራሱ መንግስት ያለውን;የፖለቲካ ባላንጣዎችን እና የግል ቂምበቀሉን ተገን አድርጎ የተንቀሳቀሰ ; መብት ጥሰት የፈጸመውን ;የዜጎችን መብት ያፈነውን ;ህገወጥ ተግባር በዜጎች ላይ የፈጸመውን ;ከህገወጦች ጋር የተባበረን ተቆጥሮ ;በፖለቲካ ሙሰኝነት መች ነው ለፍርድ የሚቀርበው??
በሃገሪቱ የኢኮኖሚ አውታሮች ላይ በሕወሓት መሪነት እየተፈጸመ ያለው ደባ እጅግ በረቀቀ መንገድ ከመስፋፋቱም በላይ በሙስና ስም የሚጠመዱ ሰዎች በውስጥ የፖለቲካ ቁርሾ ላይ የተለየ ሃሳብ ያነገቡ እና ስውር እጆች የሚያጠምዷቸውን እንደሆነ እያየን ነው ይህ ራሱን ችሎ በገዢው ፓርቲ ውስጥ የሚካሄድ የውስጥ ሽኩቻን የታከከ ፖለቲካዊ ሙስና ነው::
በየድርጅቶች ውስጥ የተለየ ሃሳብ እና የትችት ሙድ ያላቸውን ሰዎች ወይንም ከነማን በነማን እየጦዙ ነው የቡድን ስሪት ተለጣፊ አመራሮችን ለማፈን ሃያልነትን መጠቀም የፖለቲካ ሙስና ነው::እስከዛሬ እርምጃ ተወሰደባቸው የተባሉ ሰዎች ከፖለቲካ ጋር በተገናኘ ችግር እንዳለ መረጃዎች ሲጠቁሙ በግል ቂም በቀለም የታሰሩ ሰዎች አላግባብ እየተንገላቱ ሲሆን ከዚሁ ጋር በተያያዥነት የእስር ቤት ውስጥ ያለውን ሁኔታ ተቃዋሚን እንዲሰልሉ የተያዙ አስመሳይ የሙስና እስረኞች እንዳሉ የታወቀ ጉዳይ መሆኑ በራሱ የፖለቲካ ሙስና ነው::
በጠበንጃ ሃይል የያዙትን ስልጣን ተጠቅመው በምርጫ በህዝብ ተመርጠናል የሚሉ አካላት ህዝባዊ አገልግሎት ከመስጠት ይልቅ አነስተኛ እና ጥቃቅን ሆድ አደር ካድሬዎችን በማሟሟቅ ላወጡት እና ላጸደቁት ህጋቸ ተገዢ ከመሆን ይልቅ እንደፈለጉ እና እንዳሻቸው ራሳቸውን ከአገሪቱ መናብርታት እኩል በማሰለፍ ያለውን የፖለቲካ ምህዳር መጥበብ ተገን አድርገው እና ተጠቅመው የሚፈልጉትን እየጠቀሙ የማይፈልጉትን እያጠቁ ይገኛሉ::ፖለቲካዊ ሥልጣንን በመጠቀም ያላግባብ ዜጋን መጉዳት በራሱ ፖለቲካዊ ሙስና ነው፡፡
የግል ቂም በቀል የፖለቲካ አመለካከት እና ተመሳሳይ ጉዳዮችን በማጣቀስ ልዩነት ጠላትነት የሚመስላቸው ያልበሰሉ የስርኣቱ ካድሬዎች የግል ጸበኞቻቸውን የፖለቲካ ባላንጣዎቻቸውን ለፖለቲካ የንግድ ድርጅቶቻቸው አስጊ የሆኑትን ጠንካራ ነጋዴዎች በሙስና አልተሳሰር ያሉ ኢንቨስተሮችን የፖለቲካ ባላንጣ ቤተሰቦችን እንደ ጠላት በማየት መሬት እንዳያገኙ መከልከል፣ ፈቃድ መሰረዝ እና አለመስጠት ፣ የያዙትን መንጠቅ፣ የባንክ አካውንታቸውን ማገድ እና ብድር እንዳያገኙ ማከላከል ፣ የብቃት ማረጋገጫ እንዳትሰጧቸው፣ የሥራ ፈቃዳቸው እንዳይታደስ፣ ወዘተ እየተባለ መጉዳት፣ ማንከራተትና ሕገወጥ ተግባር በመፈጸም ስልጣንን ያለአግባብ የሚጠቀሙ ያልበሰሉ ፖለቲከኞች የሚፈጸሙት የፖለቲካ ሙስና በአገሪቱ አግጥጦ እየታየ ነው፡፡
ራሳቸው ያወጡትን እና አፈጻጸሙ እና አተረጓጎሙን እንኩዋን በተግባር ያልተረዱትን ሕግ በመጣስ ባለስልጣናት የግል እና የወል ጠላቶቻቸውን ድርጅቶቻቸውን ማሳሸግ ማጉላላት ማዘረፍ ማስደብደብ ባልሆነ ወንጀል መክሰስ፣ ፋይል ማስከፈትና ማስፈረድ በተግባር ይታያል፡፡ ጎን ለጎን ዘመድ እና ወዳጅ ለሆነና ከራስ ፍላጎት ጋር የሚስማማ ሥራ ላለው ደግሞ ሕግ ቢጣስም እንዳይጠየቅ፣ እንዳይያዝ፣ እንዳይከሰስ፣ ከተከሰሰም ፋይሉ እንዲዘጋና ክሱ እንዲሰረዝ ይደረጋል፡፡ ይህ ሁሉ የማይቻል ከሆነም ሳይያዝ ወደ ውጭ አገር እንዲሸሽ በማድረግ ከኢኮኖሚ ሙስና ይልቅ ከፖለቲካ ሥልጣን አጠቃቀም አንፃር ሲታይ ግን ሥልጣንን መከታ በማድረግ የሚፈጸም አደገኛ የፖለቲካ ሙሰኛ ነው፡፡ ሕንፃ- መኪና -ቪላ -ኢሮ -ብርና ዶላር -ጠበንጃ እና ቦምብ- እየተቆጠረ ሙስና እንደሚወራልን ሁሉ … የሃገሪቷን ዜጎች የጎዳ ;ሕግን እና ህገመንግስትን ያጣመመ; የራሱ መንግስት ያለውን;የፖለቲካ ባላንጣዎችን እና የግል ቂምበቀሉን ተገን አድርጎ የተንቀሳቀሰ ; መብት ጥሰት የፈጸመውን ;የዜጎችን መብት ያፈነውን ;ህገወጥ ተግባር በዜጎች ላይ የፈጸመውን ;ከህገወጦች ጋር የተባበረን ተቆጥሮ ;በፖለቲካ ሙሰኝነት መች ነው ለፍርድ የሚቀርበው??
ከትላት በስቲያ እሁድ የካቲት 2\2006 ከጠዋቱ 3፡30 ጀምሮ ስድስት ኪሎ በሚገኘው የስብሰባ ማእከል በተካሄደው በዚህ የሽልማት ስነስርዐት ላይ የህወሃት አባት የሚባሉት አቦይ ስብሃትን ጨምሮ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አቶ ድሪባ ኩማ ፣ የአዲስ አበባ
ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ ሃላፊ አቶ ፀጋዬ ሀይለማሪያም ፣ የህገ ወጡ መጅሊስ ፕሬዚደንት ዶክተር አህመድ አብዱረህማን ፣ የፌዴራሉ ህገ ወጥ መጅሊስ ምክትል ፕሬዚደንት ታጋይ (ሸይክ ከድር ) ፣ የአንዋር መስጂድ ኢማም ሀጂ ጡሃ ሃሩን ፣ የ10 ሩም ክፍለ ከተማ ሃላፊዎች ፣ የወረዳና የክፍለ ከተሞች መጅሊስ አመራሮች እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ፡፡
ከሽልማቱ በኋላ ንግግር ያደረጉት አቦይ ስብሃት መንግስት በሙስሊሙ ጉዳይ ጠልቃ እንደገባ የሚያረጋግጠውንንግግራቸውን አድርገዋል ፡፡ አቦይ ስብሃት በአዳራሹ ለተገኘው ሰው ባደረጉት ንግግር
“ … ማንኛውም ነገር ከፍተኛ ጥረት ከተደረገበት ስኬት ይኖረዋል ፡፡ የሙስሊሙ ትግል ሲጀመር በጣም ተደናግሮን ነበር ፡፡ በኋላ ብዙ አስበንበት ስናበቃ ለምን መንግስትን የሚደግፍ መጅሊስ አናቋቁምም አልንና ጥረት ጀመርን ፡፡እኔ እራሴ ሄጄ ግዴላችሁም ከየክፍለ ከተማው ሙስሊም ሆነው መንግስትን የሚደግፉ ሁለት ወይም ሶስት ሰዎችን ብቻ ፈልጉልኝ አልኩ …፡፡ የጀመርነው ከቦሌ ክፍለ ከተማ ነው ፡፡ ወደ አምስት ሰዎችን አገኘንና እነሱን አደራጀን ፡፡ በኋላ ሌሎችም ክፍለ ከተሞች የቦሌን ተሞክሮ እንዲተገብሩ አደረግን ፡፡
ሁሉም ክፍለ ከተሞች ጥቂት ሙስሊሞችን አደራጁ ፡፡ ከዚህ በኋላ ነገሩ ሁሉ የተቃና ሆነ ፡፡ እኛም በሁሉም ክፍለ ከተሞች በተወሰኑ ሰዎች
መደራጀቱን ስናውቅ ጉዳዩን የአዲስ አበባ ፍትህ ቢሮና ክፍለ ከተሞች እንዲረከቡንና በበላይነት እንዲቆጣጠሩት አደረግን ፡፡ እንዲህ
እያለ የሄደው ጥረት አሁን አክራሪዎችን ለማቆም የሚያስችል ጉልበት እንድናገኝ ረድቶናል … ” ብለዋል ፡፡
ይህ የአቶ ስብሃት ነጋ ንግግር መንግስት በሙስሊሙ ጉዳይ ጠልቃ አልገባሁም እያለ ከሚያስተባብለው ጋር የሚጋጭ እንደሆነ ተገልፇል ፡፡ በበርካታ ጉዳዮች ንግግር ያደረጉት አቦይ ስብሃት ኢስላምን የሚያጥላላ ንግግርም አድርገዋል ፡፡ “ቅድም የፌዴራሉ መጅሊስ ምክትል ሰብሳቢው ሸህ ከድር እንዳለው የዱሮው እስልምና ሌላ ነው ፡፡ እኔ ከድርን በፊት ጀምሮ ትግራይ ውስጥ አውቀዋለሁ ፡፡ ምርጥ የህወሃት ታጋይ ነበር ፡፡ አብሮን ታግሏል ፡፡ አሁን ደግሞ ሙስሊሙን እያገለገለ ነው ፡፡ እስልምና እነዚህ የታሰሩት ሰዎች እንደሚሉት አይመስለኝም ፡፡
እስልምና እነዚህ ሰዎች እንደሚያሳዩት ዓይነት ዕምነት ከሆነ እንደ ዕምነት አያስፈልግም ፡፡ ፈፅሞ ሰዎቹ ለሀገር አይሆኑም ” ብለዋል ፡፡ በዚህ
ንግግራቸው በቦታው የነበሩ ሙስሊሞችም ጭብጨባ ለግሰዋቸዋል ፡፡
ኢትዮጵያዊው ዓረናና ኤርትራዊው ህወሓት!
ዓረናዎች “ህወሓት ኤርትራን ያስቀድማል። በመሆኑም ህወሓት የሻዕቢያ ተላላኪ ነው” ስንል ህወሓቶች ደግሞ “ዓረና ከትግራይን ህዝብ ጠላቶች ከሆኑ እንደነ አንድነት ፓርቲ ጋ ለመዋህድ ጥረት እያደረገ ነው” ይላሉ።
እርግጥ ነው፤ ዓረና ኢትዮጵያዊ ነው። ከኢትይጵያውያን ድርጅቶች ጋርም አብሮ ይሰራል። ከአንድነት፣ ደቡብ ሕብረት፣ የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ እና ሌሎች ኢትዮጵያዊ ፓርቲዎች ጋር ለመዋሃድና አብሮ ለመስራት ዝግጁ ነው።
ዓረና እንደ ህወሓት ኤርትራዊ አይደለም። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም ለመጉዳት ከሻዕብያ ጋር በማበር አይሰራም። ኢትዮጵያውያንን በጠላትነት እየፈረጀ የሻዕብያ አገልጋይ አይሆንም። ምክንያቱም እኛ ኢትዮጵያውያን እንጂ ኤርትራውያን አይደለንም። ኤርትራውያንን ለመጥቀም ኢትዮጵያውያንን አንበድልም። ስለዚህ ከሻዕብያ በላይ አንድነት ፓርቲን እናስቀድማለን። ምክንያቱም አንድነት ፓርቲ ኢትዮጵያዊ ነው። ኢትዮጵያም የሁላችን የጋራ ነች። ምናልባት ከሻዕብያ ጋር አብረን የምንሰራው የኢትዮጵያና የኤርትራ የጋራ ጥቅም የሚከበርበት መድረክ ሲፈጠር ብቻ ነው።
ዓረናና ህወሓት አልተሳሳቱም። ዓረና ከኢትዮጵያውያን ጋር ይሰራል። ምክንያቱም ኢትዮጵያዊ ነው። ህወሓት የሻዕብያ ተላላኪ ነው። ምክንያቱም ህወሓት ኤርትራዊ ነው። ህወሓት ኤርትራዊ መሆኑ ችግር የለውም። ችግር የሆነው ህወሓት ኤርትራዊ ሁኖ፣ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም ለኤርትራ አሳልፎ እየሰጠ ግን የኢትዮጵያ መንግስትነት መቆጣጠሩ ነው። ለኤርትራውያን እየሰራ ኢትዮጵያውያንን እወክላለሁ ማለቱ ነው ችግሩ። ህወሓት ለኤርትራ መቆም የሚያስደስተው ከሆነ ኤርትራን ያስተዳድር፤ የኤርትራን ህዝብ ይወክል። ኢትዮጵያን እያስተዳደረ፣ የኢትዮጵያ ህዝብን እወክላለሁ እያለ ለኤርትራ ጥቅም መስራቱ፣ ኤርትራውያንን መወከሉ ግን ወንጀል ነው። ህወሓት የኢትዮጵያ መንግስትነት ከተቆጣጠረ ለኢትዮጵያውያን ጥቅም መስራት ነበረበት።
ህወሓት የኢትዮጵያ ስልጣን ይዞ ኤርትራን ለማስገንጠል ይሰራል፣ ዓሰብን ለኤርትራ ይሰጣል፣ ዓሰብ የኛ መሆኑ ስንከራከር ህወሓት ከኤርትራውያን በላይ ዓሰብ የኤርትራ መሆኑ ይሟገታል። ለኤርትራውያን መቆም ካለበት ለምን ወደሚወክለው ኤርትራ አይሄድም?
ዓረና ከኢትዮጵያውያን ድርጅቶች መዋሃዱን ይቀጥላል። ህወሓትም ለኤርትራውያን ማገልገሉ ይቀጥል። በዚሁ መሰረት “ዓረና ከአንድነት ፓርቲ ጋር እየተወሃደ ነው” ብላች ሁ ክሰሱን። ለኛ ችግር አይሆንም፤ ምክንያቱም በኢትዮጵያውነታችን አምነን በኢትዮጵያ ለኢትዮጵያውያን አማራጭ የፖለቲካ አቅጣጫ የሚያቀርብ ጠንካራ ሀገራዊ ፓርቲ የመመስረት ዕቅድ አለን። ህወሓትም ሻዕብያን ማገልገሉ ይቀጥል ምክንያቱም ህወሓት የኤርትራ ተወካይ (በኢትዮጵያ) መሆኑ እናውቃለን።
ህወሓት ግን ዓረና ከአንድነት ጋር የመዋህዱ ዜና ሲሰማ እንዲህ ከተደናገጠ ከሌሎች ኢትዮጵያዊ ድርጅቶች ጭምር ስንዋሃድስ ምን ሊሆን ነው? ዓረና ከአንድነት ብቻ ሳይሆን ከሌሎች ብዙ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ድርጅቶች ጋርም ይወሃዳል። ጠንካራ ሀገራዊ ፓርቲ መመስረት እንፈልጋለንና።
ህወሓት ኤርትራን ሲያስበልጥ ዓረና ግን ኢትዮጵያንን ያስቀድማል።
It is so!!! Abrha Desta
News, Ask the Doctor, Agriculture and Business
ብዙዉን ጊዜ አደገኛ ከሚባሉት የጤና ችግሮች ልብና ከልብ ጋ የተገናኙት በዋነኝነት ይጠቀሳሉ። በዓለማችን በአብዛኛዉ ለሞት ከሚያደርሱ የጤና እክሎችም አንዱ በመሆኑም ይታወቃል።
የደ/ሱዳን ኣማጺያን ከድርድሩ እራሳቸውን እንደሚያጋሉ ያስጠነቀቁት፤ ትላንት ከአዲስ ኣበባ እንደተገለጸው በሁለት ምክኒያቶች ነው። አንደኛው ያልተፈቱት አባሎቻቸው በኣስቸኩዋይ ካልተለቀቁ እና ሁለተኛው ደግሞ በዚያች ሀገር የሚገኙ የኡጋንዳ ወታደሮች ሀገሪቱን ለቀው ካልወጡ በሚል ነበር በቀጣዩ ድርድር ላይ እንደማይካፈሉ ያስታወቁት።
አፍሪቃ ውስጥ ርሀብ፣ የርስ በርስ ጦርነት እና ሌሎች ክስተቶች ከሚስተዋሉባቸው ሃገራት ተርታ ሶማልያ በምሳሌነት ትጠቀሳለች።
የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ሐይለማርያም ደሳለኝ በወቅታዊ የሀገሪቱ ጉዳዮች እና ሀገሪቷን ከጎረቤት ሀገራት ጋር በሚያስተሳስሯት ነጥቦች ላይ ትናንት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።
የካቲት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከፍተኛ የግብርና ምርት እንደተገኘ በመንግስት የመገናኛ ብዙሀን በሚገለጽበት በአሁኑ ወቅት ከ3 ሚሊዮን በላይ ዜጎች አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ካላገኙ ህይወታቸው አደጋ ላይ እንደሚወድቅ መረጃዎች አመልከተዋል። የዓለም ባንክ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት በመግብ ለስራ የታቀፉ ዜጎችን ሳይጨምር ከ3 ሚሎዮን ያላነሱ ኢትዮጵያውያን አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል። በምስራቅ አማራ፣ በደቡብ ምስራቅ ትግራይ፣ በአፋር …
የካቲት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የደህንነት ሃላፊ ከነበሩት ከአቶ ወልደስላሴ ወልደ ሚካኤል ጋር በግብረ-አበርነት የተከሰሱት የህወሃት ታጋዮች ከደሞዛቸው ጋር ፈጽሞ የማይመጣጠን ሃብት አግበሰው መገኘታቸው ታውቋል። በተለያዩ አለመግባባቶች የተነሳ እየተመሰረቱ ያሉ ክሶች የህወሃት ተጋዮች በህገወጥ መንገድ የሰበሰቡትን የሃብት መጠን ለማወቅ እየረዳ መሆኑን የገለጸው ዘጋቢያችን ከአቶ ወልደስላሴ ጋር በግብረ አበርነት የተከሰሱት የህወሃት ታጋዩ የአቶ …
የካቲት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የደብረዘይት አየር ኃይል አባል የነበረው ምክትል መቶ አለቃ ዳንኤል የሽዋስ የኢህአዴግን ስርአት በመቃወም የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊትን መቀላለቀሉን ግንባሩ ለኢሳት በላከው መግለጫ አስታውቋል። ም/መ/አለቃ ዳንኤል የሽዋስ የ L-39 ስኳድሮን ተዋጊ ጀት አብራሪ እንደነበር መረጃው ያመለክታል። ም/መ/አ ዳንኤል የሽዋስ “ተቃዋሚዎችን ትደግፋለህ ከእነሱም ጋር የጠበቀ ግኑኝነት አለህ በሚል …
የካቲት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ግንባሩ ለኢሳት በላከው መረጃ ፣ ከኢህአዴግ መንግስት ጋር ድርድር ለማድረግ በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ተገኝተው በኢትዮጵያ የደህንነት ሃይሎች ታፍነው የተወሰዱት የኦብነግ አመራሮች፣ የደረሰባቸውን ከፍተኛ ድብደባ ተከትሎ በአንድ ወታደራዊ ሆስፒታል ውስጥ ሲታከሙ ታይተዋል። የመንግስት የደህንነት ሰራተኞች ” ባለስልጣኖቹ በገዛ ፈቃዳቸው እጃቸውን እንደሰጡ ለማሳመን ያደረጉት ከፍተኛ ጥረት ባለመሳካቱ አሰቃቂ …
የካቲት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ጠ/ሚ/ሃይለማርያም ደሳለኝ፣ በደቡብ ሱዳን የሚገኘው የዩጋንዳ ጦር በሂደት ለቆ ካልወጣ አካባቢው የጦርነት ቀጠና ሊሆን ይችላል ብለዋል። ሁሉም ሃይሎች የራሳቸው የሆነ ፍላጎት አላቸው ያሉት አቶ ሃይለማርያም፣ በደቡብ ሱዳን ሰላም ይመጣ ዘንድ የዩጋንዳ ጦር ጁባን ለቆ መውጣት አለበት ሲሉ አሳስበዋል ። አቶ ሃይለማርያም የገለጹት አቋም የደቡብ ሱዳንን መንግስት የሚያስከፋ …
አማኑኤል ዘሰላም
“ስልክ ጠላፊው ሰላይ ‘ጋዜጠኛ'” የሚል አንድ ጽሁፍ አነበብኩ። ሲያትል የሚኖር አንድ ኢትዮጵያዊ ናቸው የጻፉት። የአውራምባ ታይምስ ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደን አጠንክረው ይተቻሉ። በቅርቡ በድረ ገጾችና ፌስቡክ የተለቀቀው፣ አቶ አበበ ገላው የተናገሩትን አንዳንድ አባባሎችን የያዘ ኦዲዮ ነው። ይህ ኦዲዮ አቶ አበበ፣ ሳያውቁት የተቀዳ ነው። ይህ አይነቱም ንግግርን በሚስጠር የመቅዳት የፓፓራዚ ተግባር በጣም አሳዛኝ ከመሆኑም በተጨማሪ ነውርም ነው።
ግርማ ካሳ
አዲሱ የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው፣ ለገዢው ፓርቲ ኢሕአዴግ የሰላምና የእርቅ ጥሪ ማቅረባቸው ይታወሳል። “ኢሕአዴግ እኛን እንደ ጠላት እና ሽብርተኛ ማየቱን ማቆም አለበት። እኛም ደግሞ ኢሕአዴግን እንደ አውሬ ማየት ማቆም አለብን። ከጥላቻ ፖለቲካ በመውጣት ችግሮቻችንን በሰላም መፍታት መማር አለብን” ሲሉ ነበር፣ ለአገር በሚጠቅሙ በጋራ ጉዳዮች ዙሪያ ከኢሕአዴግ ጋር ለመስራት፣ ያሉትን ልዩነቶችን በውይይት ለመፍታት አንድነት ፍላጎት እንዳለው የገለጹት።
የእነ “… ወይም ሞት” ፖለቲካ
ያሬድ ኃይለማርያም ከብራስልስ
ከ1960ዎቹ የተማሪዎች ንቅናቄ ጀምሮ የአገራችንን ፖለቲካ የተጠናወተው የ”…. ወይም ሞት” አስተሳሰብ ከአስርት አመታት በኋላም አለቅ ብሎን ዛሬም እኔ ከምደግፈው ፓርቲ ወይም የፖለቲካ ቡድን ወይም አስተሳሰብ ውጭ ያለው መንገድ ወይም አማራጭ ሁሉ ገደልና ሞት ነው ብለው የሚያስቡ ፖለቲከኞችና ዓጃቢዎችን ቁጥር በብዙ እጥፍ አባዝቶ ቀጥሏል።
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ!
ሁለተኛዉ ዙር የሶርያ መንግሥትና የመንግሥቱ ተቃዋሚዎች ህብረት ድርድር ዛሬ በጄኔቭ ስዊትዘርላንድ ተጀመረ። ሁለቱ ተፋላሚ ሃይላት ባለፈው ወር መጨረሻ ያደረጉት የመጀመርያዉ ዙር ድርድር ያለምንም ዉጤት ነበር የተጠናቀቀው። በሳምንቱ መጨረሻ የተመድ ለሶርያውያኑ የሆምስ ከተማ አስፈላጊውን የሰብዓዊ ርዳታ ማድረስ አልቻለም።
ምስራቃውያን “ልማታዊ መንግሥታት ናቸው” የተባሉት በምዕራባውያን ነበር። የኢትዮጵያ መንግሥት ግን ራሱ ነው “ልማታዊ” በማለት ራሱን መጥራት የጀመረው። ከዚያ በኋላ ቃሉ፣ በመንግሥት ኃላፊዎችና በተለይም በኢቴቪ በተደጋጋሚ ከመነሳቱና ካለቦታው ከመደንጎሩ የተነሳ የሚወክለው መንግሥት የሚከተለውን የኢኮኖሚ ስርዓት መሆኑ ቀርቶ በቀላሉ ሲታይ “የሚጠፉ ጥፋቶችን እንዳላየ አልፎ፥ ስለሚለሙ ልማቶች ብቻ ማውራትን”፣ ወይም በጥልቁ ሲመረመር “ገዢው ፓርቲን ከነቆሻሻው መደገፍን” ይመለከታል። ራስን ማዕረግ የመስጠት ጦሱ ይኸው ነው።
ኢሕአዴግ ደጋፊዎቹን ወጣቶች “የልማት ሠራዊት” ነው የሚላቸው፤ ቀሪው እንደጥፋት ሠራዊት ነው የሚቆጠረው። ሌላው ቢቀር ሁለቱንም አለመሆን አይፈቀድለትም። ኢሕአዴግ ራሱን ብቻ ልማታዊ አድርጎ የመቁጠሩ ነገር በስህተት የመጣ አይደለም፤ የፖለቲካ ፍልስፍና ጉዳይ ነው። በተለይ ሰሞኑን ፓርቲው በመንግሥትነት ስሙ ተጠቅሞ በሚያዘጋጃቸው ስብሰባዎች ላይ የታይዋን እና ደቡብ ኮርያ ስም ተደጋግሞ በምሳሌነት ይጠቀሳል፤ ሁለቱም “ለልማት ሲባል ዴሞክራሲን ሰውተው ነው እዚህ የደረሱት” በሚል። ልማታዊነት ለዴሞክራሲ አያጣድፍም እንደማለት።
ክፋቱ ኢሕአዴግ እምነቱን በፀባይ ለማሳመን አለመፈለጉንም ይጨምራል። እንዲህ እያለ እያወራም ግን ‘ዴሞክራሲያዊ ነኝ፣ ያለመሆን ፍላጎትም የለኝ’ እያለ በአደባባይ እየዋሸ ያታልላል። ግን መልሶ፣ “ሁሉም ነገር ወደልማታዊነት ግንባር” ይላል – በራሱ የልማታዊነት ብያኔ። የለም፣ እኔ በራሴ ብያኔ እሠራለሁ ብሎ ነገር የለም። ለምሳሌ፤
ልማታዊ ተቃዋሚዎች
ኢሕአዴግ ተቃዋሚዎች “ልማታዊ” እንዲሆኑ ይፈልጋል። “ልማታዊ ተቃዋሚዎች” ማለት የሁለት አሐዙ ዕድገትን ያለመጠየቅ የሚያምኑ፣ ስለፖለቲካው ምኅዳር መጥበብ ትንፍሽ የማይሉ እና ሌላው ቀርቶ በምርጫ ሲሸነፉ በኢቴቪ ቀርበው ይህ እንደሚሆን ቀድመውም ያውቁ እንደነበር የሚመሰክሩና የተሸነፉት በራሳቸው ድክመት መሆኑን የሚናገሩ… ናቸው። የሚወዳደሩት ውድድሩን ለማድመቅ ነው -ልክ እንደታላቁ ሩጫ ብዙኃን። ምሳሌ የአቶ መሳፍንት መኢብንን እና የአቶ አየለ ጫሚሶን ቅንጅትን መጥቀስ ይቻላል። በአጭሩ እነዚህ ፓርቲዎች፣ ተቃዋሚም፣ አማራጭ ፓርቲም አይደሉም፤ ደጋፊ ፓርቲዎች ናቸው።
“ደጋፊ የፖለቲካ ፓርቲዎች” (AKA ልማታዊ ፓርቲዎች) ዋነኛ ሥራ ራስን ተቃዋሚ ነን ብሎ ለሕዝብ መንገር፣ በገዢው ፓርቲ የተከፋውን ሕዝብ ልብና ቀልብ ማግኘት፣ ቀልቡን ለሰጠው ሕዝብ ፓርቲዎቹ ስለሚታገሉለት ሳይሆን ኢሕአዴግ ስለሚሠራቸው ሥራዎች ማውራት፣ ለኢሕአዴግ ድምፅ ማስገኘት ካልተቻለ “ልማታዊ ካልሆኑት ፓርቲዎች” ድምፅ መቀማት/መከፋፈል ናቸው።
ገዢው ፓርቲ እነሱን በማበርከት የአጥቂነት ሚናውን እየተወጣ ነው። እነሱ ደግሞ የማያገኙት የሥልጣን ጥማቸው የኢሕአዴግ ጉዳይ አስፈፃሚ አድርጓቸዋል።
ከኢሕአዴግ መሥመር በማይጋጠም አቅጣጫ የሚሄዱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ደግሞ ሕልውናቸውን አደጋ ላይ በሚጥል ቀጭን ሽቦ ላይ እንዲራመዱ ይደረጋሉ።
ልማታዊ ጋዜጠኝነት
ልማታዊ ጋዜጠኝነትም በገዢው ብያኔ መሠረት የኢኮኖሚ እና ፖለቲካ እርምጃዎችን አዎንታዊ ፋይዳን ብቻ ማውራት ነው። ለምሳሌ ከጣሊያን ብድር ለማግኘት ተብሎ ለሳሊኒ ያለጨረታ ፕሮጀክት መሰጠቱ ምን ያክል ገንዘብ ድሀዪቱን አገር ያከስራታል የሚለውን ማውራት ልማታዊ አይደለም። ፕሮጀክቱ መጀመሩ፣ ሲጠናቀቅ የሚኖረውን ፋይዳ ማውራት ግን ልማታዊ ነው።
በኢትዮጵያ 35 በመቶ የመረጃ ጥያቄዎች በሕዝብ ግንኙነት አባሎች ይጨናገፋሉ የሚለው ልማታዊ አይደለም፣ 65 በመቶ የሚሆኑ የመረጃ ጥያቄዎች ምላሽ ያገኛሉ የሚለው ግን ልማታዊ ነው። የሁለቱ ዜናዎች ልዩነት የትኩረት አቅጣጫቸው ነው። የመጀመሪያው ሊስተካክል የሚገባውን ሲያወራ፣ ሁለተኛው የተሳካውን ያወራል። ሁለቱም ውስጥ ተቃራኒው ቢኖርም የዜናዎቹ አንባቢዎች ግን እንዲያተኩሩ የተፈለገውን ብቻ የማስተዋል ዕድላቸው ሰፊ ነው። ስለዚህ ልማታዊ ጋዜጠኝነት በተሳሳተ ብያኔው ሙገሳ አዝማሪነት ሆኗል ማለት ነው። እናም፣ ዜናው ላይ የተጠቀሰው ጥናት በመንግሥት ስለተሠራ እንጂ የመረጃ ንፍገቱ ከ35 በመቶ በላይ ነው፤ ለምሳሌ የግል ጋዜጠኞች የጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ካልሆነ በቀር መረጃ ጠይቀው የሚሰጣቸው የለም የሚል አስተያየት የሚያስተናግድ ጋዜጠኛ ከመጣ ጭራሹኑ ቦታ የለውም።
ልማታዊ አራማጅነት
አራማጅነት (activism) በባሕሪው ምናባዊ በሆኑ መሠረታውያን ላይ የቆመ የለውጥ እንቅስቃሴ ነው። አንድ አራማጅ ይህ ለውጥ እንዲመጣ እፈልጋለሁ ካለ፣ የሚመጣውን ለውጥ የመጨረሻ ግብ እያለመና ሁሉንም ነገር ከዚያ ግብ (ወይም ለዚያ ግብ ከሚኖረው ፋይዳ) አንፃር እየመዘነ የሚሄድ ነው።
ለምሳሌ እንደኛ ባለ ጠቅላይገነንነት (authoritarianism) ስርዓት ውስጥ ዴሞክራሲ እንዲመጣ የሚሠራን አራማጅ እንውሰድ። ይህ አራማጅ በነባራዊው ሁኔታ ያሉ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለውጥ እንደማያመጡ ያምናል እንበል። እንዲያውም እነሱ ራሳቸው ሚናቸውን ለመወጣት ለውጥ ይፈልጋሉ፤ ዴሞክራሲ ይፈልጋሉ። ጋዜጠኞችም ሐሳባቸውን ለመግለጽ ነጻነት ይፈልጋሉ፤ እነሱም ዴሞክራሲ ይፈልጋሉ። ስለዚህ አራማጁ የሚያስቀምጠው መለኪያ እነዚህን እውን የሚያደርጉትን መለኪያዎች ነው።
ነገር ግን፣ በኢሕአዴግ የእያንዳንዱ ዜጋ “የልማታዊ” መሆን የውስጠ ታዋቂ መመሪያ መሠረት ገዢውን ማበረታታት እንጂ መተቸት ያስቀስፋል። አራማጁ ስለፖለቲካ ምኅዳር ሲያወራ፣ ገዢው ስለመሠረተ ልማቱ አውራ ይለዋል፤ ስለመሠረተ ልማቱ የአገነባብ ሒደት ሁሉንም በዕኩል አሳታፊነት/ጠቃሚነት ጉዳይ ሲያወራ፣ ስለተገኘው ስኬት አውራ ይባላል። ስለዚህ እንኳን ለሌሎች ዴሞክራሲን በአማጭነት ሊያግዝ የራሱንም ማስጠበቅ ይቸገራል። በዚህ አራማጁን “ልማታዊ” የማድረግ አካሄድ አራማጁ የኢሕአዴግ ሕልም አስፈፃሚ ብቻ ነው መሆን የሚችለው።
አራማጆች በኢትዮጵያ መሠረታዊ መነሻቸውን ሳይስቱ ከቆዩ (“ልማታዊ” አንሆንም ካሉ፥) በገዢው ስያሜ ይሰጣቸዋል። የመጀመሪያው ‘አሸባሪ’ ነው። ‘ፅንፈኞች፣ የኒዮ ሊበራል ተላላኪዎች፣ ፀረ-ልማቶች…” የሚሉትም ይገኙበታል። እነዚህ ስያሜዎች ምናልባትም እራሱን እንደፈጣሪ መልዕክተኛ ለሚቆጥር አራማጅ አስበርጋጊ ናቸው። ስያሜዎቹ፣ ከተራ ውንጀላ ወደ ክስ መዝገብነት ሲቀየሩ የበለጠ ያሸማቅቃሉ።
በመጨረሻም፣ ልማታዊ አራማጆች ይፈጠራሉ። እነርሱም ልማት ስለሚያመጣቸው ነጻነቶች፣ ሕገ መንግሥቱ ስለሰጣቸው መብቶች፣ ባልተለወጠ መንግሥት ስር ዜጎች ራሳቸውን እንዲለውጡ ይተውታሉ። በልማታዊ መንግሥት፣ በልማታዊ ተቃዋሚዎች፣ በልማታዊ ጋዜጠኞች፣ በልማታዊ አራማጆች እና በተሳሳተው የመሸነጋገያ “የልማታዊ” ትርጉም፥ ባለህበት አዝግምi
አንድ ዘመን ሥርዓተ መንግስቱ በመቆየትም ሆነ አባላቱ የአሥራ ሰባተኛው ክፍለ ዘመን የተረት ዓለም ሰዎች ስለ መሰሉን- ሁሉም ነገር ስለገለማን አዲስ ሥርዓት፣ አዲስ መሪ፣ አዲስ ዘመን መናፈቅ ይዘን ነበር። ሰዓሊ ሁሉ፣ ደራሲ ሁሉ፣ ጸሐፌ -ተውኔት ሁሉ እጁን የሚያሟሸው በቴዎድሮስ ሥዕል፣ ተውኔትና ታሪክ ሆነ። ብርሃኑ ዘሪሁን- የቴዎድሮስ እንባ -(መጽሐፍ) ከዚያ በፊት ደጃዝማች ግርማቸው ተክለሐዋርያት- ቴዎድሮስ (ተውኔት) አቤ […]
የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ አውጭ ግንባር – ኦብነግ በቅርቡ ኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ውስጥ “ተጠልፈውብኛል” ባላቸው ሁለት ከፍተኛ የአመራር አባላቱ ላይ ድብደባና የሥቃይ አያያዝ መድረሱን ግንባሩ አስታውቋል፡፡
Interview with Alemayehu Tegenu, Minister of Water, Ethiopia
Ethiopia – Egypt water Ministers meeting in Addis
ESAT Radio Daily Broadcast to Ethiopia. Frequency Details: 7 days a week Short Wave (SW) from 8:00 pm to 9:00 pm (Local Ethiopian Time) 19 Meter Band 15355 kHz, 15360 kHz, 15365 kHz, 15370 kHz, 15380 kHz, 15385 kHz and 15390 kHz Download/Listen
ወጣቱ ፖለቲከኛና ደራሲ አቶ ዳንኤል ተፈራ ፖሊስ ጣቢያ እንዲቀርብ መጠየቁ በስፋት መዘገቡ ይታወቃል። አቶ ዳንኤል መጀመሪያ ላይ እንዲቀርብ የተጠየቀዉ በስልክ፣ ሲሆን፣ ሕጋዊ መጥሪያ ወረቀት ካልመጣለት በቀር ለመቅረብ ፈቅደኛ ሳይሆን እንዳልቀረ ለማወቅ ተችሏል። ከአቶ ዳንኤል ተፈራ በተጨማሪ፣ የአንድነት ብሄራዊ ምክር አባል የሆኑትና በርካታ መጽሃፍት በመጻፍ የሚታወቁት አዛዉንቱ አቶ አንዳርጌ መስፍንን፣ ፖሊስ ለመከሰስ እንደተዘጋጀ፣ እንዲቀርቡም እንዳዘዘ ለማረጋገጥ […]
የኢትዮጵያና የግብፅ የውኃ ሚኒስትሮች ዛሬ አዲስ አበባ ላይ ያደረጉት ስብሰባ ያለስምምነት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ለቪኦኤ ዛሬ ማምሻውን ገልፀዋል፡፡
«ከንቲባ ድሪባ ኩማና ኮሚሽነሩ መከራከሪያቸውን ለፍ/ቤት ያቀርባሉ » «አንድነት፣ የመንግስት አካላትን በተከታታይ እከሳለሁ ብሏል» አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ (አንድነት)፣ የአዲስ አበባ ከንቲባና የፖሊስ ኮሚሽነራቸው ላይ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት 8ኛ ወንጀል ችሎት ክስ የመሰረተ ሲሆን ተከሳሾች መልሳቸውን ይዘው እንዲቀርቡ ለየካቲት 24 ቀን 2006 ዓ.ም ቀጠሮ ተሰጠ፡፡ አንድነት ፓርቲ፤ “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” የተሰኘ አገር አቀፍ የ3 ወር […]
ሌላኛው ሰሞነኛ ጉራማይሌ የፖለቲካችን ገፅ አንጋፋውን የኦሮሞ ልሂቅ ሌንጮ ለታን የተመለከተው ርዕሰ-ጉዳይ ነው፡፡ ኦነግን በመመስረትም ሆነ ፖለቲካዊ ቁመና ይዞ ህልው እንዲሆን ከዮሀንስ ለታ በላይ ማንም የለፋ እንደሌለ ይነገራል፤ ዮሀንስ ከጓዶቹ ጋር ተባብሮ ድርጅቱን ሲመሰርት ካነገበው አጀንዳ አኳያ ያለውን ተዛምዶ ገልፆ ባይነግረንም፣ ከልጅነት እስከ ጎልማሳነት ይታወቅበት የነበረውን መጠሪያ ስሙን ‹ሌንጮ› በሚል ቀይሮታል፡፡ ኦነግ እስከ 1983 ዓ.ም […]
የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራርና የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊዉ ወጣት ብርሃኑ ተክለ ያሬድ ድርጅታቸው «ውህደት ፈጽሞ አያስፈልግም ብሎ የማያምን እንደሆነ የገለሱ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ግን ዉህደት እንደማይታሰብ አሳወቁ። ፓርቲዉ ከሌሎች ድርጅቶ ጋር አብሮ ለመስራት እና ለመዋሃድ ፈጽሞ የተዘጋ በር እንደሌለው የገለጹት አቶ ብርሃኑ ከዉህደት በፊት ግን መቅደም ያላባቸው ጉዳዮች (የቤት ስራዎች) እንዳሉ ይናገራሉ። መሰራት ያላባቸውን የቤት […]
በዘመነ ኢህአዴግ ከታሪክ ተጠያቂነት በፍፁም ሊያመልጡ ከማይችሉ የፖለቲካ ድርጅቶች መካከል ብአዴን እና ኦህዴድ በግንባር ቀደምትነት ይሰለፋሉ፡፡ ሁለቱም ‹እንወክለዋለን› በሚሉት ሕዝብ ላይ ተደጋጋሚ ክህደት ለመፈፀማቸው፣ ደርዘን ያለፉ ድርሳናትን ማዘጋጀት እንደሚቻል እናውቃለን፡፡ አልፎ ተርፎም ህወሓትን ከመሰለ የማፍያ ቡድን ጋር ግንባር ፈጥረው ‹‹ወከልነው›› የሚሉትን የማህብረሰብ ክፍል ህልውና ማድቀቃቸው እውነት ነው፡፡ በርግጥ ምንም እንኳ የሀገር አንድነትን አደጋ ላይ የጣለ […]
News, Sports, African Topics and Health
በሺዎች የሚቆጠሩ ታዳጊ ኢትዮጵያዉያን እንደሚማሩበት የሚገለፀዉ በጅድ የኢትዮጵያ ዓለም ዓቀፍ ትምህርት ቤት ከተመሠረተ ከ15ዓመታት በላይ እንደሆነዉ ይነገራል።
የኦሎምፒክ ውድድሮች ኣጀማመር፣ የታሪክ ድርሳናት እንደሚጠቁሙት፣ ከ2700 ዓመታት በፊት ነበር፣ ከክርስቶስ ልደት በፊት፣ 776 ዓ ዓለም ገደማ መሆኑ ነው፣ በጥንታዊቷ ግሪክ፣ ኦሎምፒያ በምትባል ከተማ።
የጀርመኑ የልማት ትብብር ሚኒስቴር ጌርድ ሙለር ባለፈዉ ዓርብ በአዲስ አበባ ከኢትዮጵያ መንግስትና ከአፍሪቃ ህብረት ባለስልጣናት ጋር ባደረጉት ውይይት አፍሪቃ በሀገራቸው የውጭ ፖሊሲ ላይ ትልቅ ትኩረት ማግኘቷን አስታወቁ። ሚንስትሩ እንዳስረዱት፣
የካቲት ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በከተማው ውስጥ የሚገኙ የመንግስት ተሽከርካሪዎች ፣ የግል ባለንብረቶችና ባለታክሲዎች በመላ አገሪቱ የጠፋውን ነዳጅ ተከትሎ ነዳጅ ለማግኘት ላይ ታች እየተንከራተቱ ሲሆን፣ የነዳጅ መጥፋቱን ተከትሎ የትራንስፖርት ታሪፊም ጨምሯል። ዘጋቢያችን እንዳለው ዛሬ ከቦታ ቦታ ሲንቀሳቀስ 0.25 ሳንቲም ተጨማሪ ገንዘብ ለመክፈል ተገዷል፡ ነዳጅ ማደያዎችን ተዘዋውሮ የተመለከተው ዘጋቢያችን፣ በከተማው የሚገኙ ነዳጅ ማደያዎች …
የካቲት ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከታህሳስ ወር 2006 ዓም ጀምሮ በመዲናዋ ሌሊት የሚጻፉ የተቃውሞ ጽሁፎችን ማየት የተለመደ እየሆነ መምጣቱን ነዋሪዎች ይናገራሉ። ትናንት ሌሊት በአስኮ መስመር ጀኔራል ዊንጌት ከሚገኘው አደባባይ ጀምሮ አወሊያ፣ካኦጄጄ፣ አስኮ የሚወስደውን ዋና መንገዱን በመሃል በሚከፍለው እስከ 2.5 ሜትር ቁመት ባለው ግድግዳ ላይ የሙስሊሙን የመብት ጥያቄና የትግል ቀጣይነት የሚያንፀባርቁ ጽሁፎች በተለያዩ …
ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
ይህ ጽሑፍ የሚያተኩረው ዋናው ምንጩ በሆነው፤ እ.አ.አ በ2013 (2006 ዓ/ም) ታትሞ ለንባብ በደረሰው፤ ካርልሔንዝ ዴሽነር (Karlheinz Deschner) “እግዚአብሔርና ፋሺሽቶቹ – የቫቲካን ሕብረት ከሙሶሊኒ፤ ፍራንኮ፤ ሒትለርና ከፓቬሊች ጋር” “God and The Fascists – The Vatican Alliance with Mussolini, Franco, Hitler, and Pavelic” በተሰኘው መጽሐፍ በተካተተው ማስረጃ ላይ ነው። የጽሑፌ ዓላማም በፋሺሽቶች ኢትዮጵያ ላይ ስለ ተፈጸመው እጅግ […]
የዕለቱ ዜና
በያዝነዉ ሳምንት ማክሰኞ ፊስቡክ የመገናኛ መረብ ከተመሰረተ 10ኛ ዓመቱን ደፈነ። በፊስ ቡክ ፤ህዝባዊ ቅስቀሳ፤ በፌስቡክ አብዮት፤ በፌስቡክ መማመር፤ በፊስ ብክ ትዉዉቅ፤ እንዲሁም በፌስቡክ ስድድብ ሌላም ሌላም ይታያል። በአሁኑ ግዜ የኢንተርኔት አገልግሎት የማግኘት እድሉ ያላቸዉ፤ የፊስ ቡክ መረብን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ተጠቃሚ ናቸዉ።
የዕለቱ ዜና
ፓርቲያችን አንድነት በተደጋጋሚ ከገዥው ፓርቲ ህግን ከለላ በማድረግ እና የመንግስትን ሥልጣን በመጠቀም የሚደርስበትን ከፍተኛ አፈና ተቋቁሞ የኢትዮጵያን ህዝብ ሉዓላዊ የስልጣን የበላይነት ለማረጋገጥ ትግሉን አጠናክሮ መቀጠሉ ከማንም የተሰወረ አይደለም፡፡ በተለይም ፓርቲያችን በመላው የሀገራችን ክፍል የዘረጋውን መዋቅር በህዝባዊ አቅም ወደ ተሻለ ደረጃ በማሸጋገር በአምስት ዓመት ስትራተጂክ ዕቅዱ መሰረት እያከናወነ ያለው ህዝባዊ ንቅናቄ እና በተሳካ ሁኔታ ጠቅላላ ጉባዔ […]
የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ የሆነው ወጣቱ ፖለቲከኛና ደራሲ ዳንኤል ተፈራ ማዓከላዊ ወንጀል ምርመራ በመቅረብ ቃሉን እንዲሰጥ በፌደራል ፖሊስ ታዘዘ፡፡ ፍኖተ ነፃነት ምንጮችን ዋቢ በማድረግ አቶ ዳንኤል ተፈራን ጨምሮ በአራት የአንድነት ፓርቲ አመራሮችና አባላት ላይ ክስ ለመመስረት ጥረት እየተደረገ መሆኑን መዘገቧ ይታወሳል፡፡ በቅርቡ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ አስራት ጣሴ፣ […]