በጀርመን ቀኝ ፅንፈኞች እየተጠናከሩ ይሆን?

በደቡብ ጀርመን ኑርንበርግ ከተማ አቅራቢያ ለስደተኞች በተሰናዱ መጠለያዎች ላይ ቃጠሎ ከደረሰ በኋላ ፤ ቃጠሎውም ሆን ተብሎ እንደደረሰ የሚጠቁሙ የፅንፈኞች ምልክቶች በመገኘታቸው ፖሊስ ምርመራውን አጠናቅሯል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በተለያዩ ከተሞች ዘረኝነትን የሚቃወሙ እና የሚደግፉ ሰልፎች በመካሄድ ላይ ይገኛሉ።