የሊቢያ ዉጊያ፤ ኔቶና የድርድር ጥያቄ
ሕዝባዊ ሠላማዊ አመፅ ወደ ጠመንጃ ዉጊያ ከተቀየረ ወዲሕ ግን ሕዝባዊዉ ድል በመጀመሪያ ፍጥነቱ አልቀጠለም።ኮሎኔል ሙዓመር ቃዛፊም የአመፁባቸዉን ሐይላት በሐል ከመደፍለቅ አላመነቱም።ታንክ፥ መድፍ፥ ተዋጊ ጄት፥ ሔሊኮብተር፥ የታጠቀዉ የቃዛፊ ታማኝ ጦር አማፂያኑ የሚቆጣጠሯቸዉን ከተሞች እያጠቃ ነዉ።
ሕዝባዊ ሠላማዊ አመፅ ወደ ጠመንጃ ዉጊያ ከተቀየረ ወዲሕ ግን ሕዝባዊዉ ድል በመጀመሪያ ፍጥነቱ አልቀጠለም።ኮሎኔል ሙዓመር ቃዛፊም የአመፁባቸዉን ሐይላት በሐል ከመደፍለቅ አላመነቱም።ታንክ፥ መድፍ፥ ተዋጊ ጄት፥ ሔሊኮብተር፥ የታጠቀዉ የቃዛፊ ታማኝ ጦር አማፂያኑ የሚቆጣጠሯቸዉን ከተሞች እያጠቃ ነዉ።
ረበደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በምትገኘው የጅማ ከተማ በአሰንዳቦ አካባቢ ባለፈው ሳምንት በተፈጠረ ግጭት የወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያን ተቃጥለዋል።
የ16 ሰዎች ህይወት የጠፋበት፤ በመቶዎች የሚቆጠሩ ቤቶች የተቃጠሉበት ግጭት በደቡብ ኢትዮዽያ ተቀስቅሷል። በአርባ ምንጭ ዞን በምትገኘው ካምባ ወረዳ በሁለት ቀበሌዎች በተፈጠረው የድንበር ይገባኛል ጥያቄ የተፈጠረው ግጭት እንዳልበረደ አንድ የአይን እማኝ ተናግረዋል። ግጭቱ የተቀሰቀሰው ካለፈው የካቲት ሶስት ጀምሮም እንደሆነ ተገልጿል። ዮሀንስ …
መገናኛ ዘዴዉ ለሕዝባዊዉ አመፅ መሠረት አይሁን እንጂ የኑሮ ዉድነት፥ ሥራ አጥነት፥ የዲሞክራሲ እጦት፥ የመናገር፥ የመሰብሰብ መብት የተነፈገዉ ሕዝብ በጣሙን ወጣቱ የየገዢዎቹን ጠንካራ አፈና ተጋፍጦ እንዲያምፅና አመፁን ለማቀጣጠል ቤን ዓሊን ከቱኒዝ፣ ሙባረክን ከካይሮ አብያተ-መንግስታት ያሽቀነጠረዉ፣ የቃዛፊን እና የሳሌሕን በትረ-ሥልጣን የሚገዘግዘዉ፣ከአልጀርስ እስከ …
በሊቢያ ምስራቃዊ እና ምዕራባዊ ክፍል በሞአማር ጋዳፊ ደጋፊ ወታደሮችና በሕዝባዊው ዓማጺያን መካከል የሚካሄደው ውጊያ ተባብሶ እንደቀጠለ ነው። በዉግያዉ ሁለቱም ወገኖች በአገሪቷ የሚገኙ ቁልፍ ቦታዎችን በእጃቸዉ ለማስገባት በመጣር መሆኑ ተመልክቶአል።
ጋና በባህር ጠረፍዋ ከሚገኘው ግዙፍ የነዳጅ ዘይት ንጣፍ ካለፈው ታህሳስ ወዲህ የነዳጅ ዘይት ማምረት ጀምራለች።
በጅቡቲ የፖለቲካ ተቃዋሚዎች በስልጣን ላይ የሚገኙት ፕሬዝደንት ለሶስተኛ ጊዜ የስልጣን ዘመን መነሳታቸዉን አስመልክተዉ ተቃዉሞ ካነሳሱ ሶስት ሳምታት ተቆጠሩ።
በሰሜን አፍሪቃ ከቱኒዚያ የተነሳዉ ያሰሚን የተሰኘዉ ህዝባዊ አመጽ ወደአጎራባች የመካከለኛዉ ምስራቅ አገራት እንደተዛመተ ሁሉ በአፍሪቃዉ ቀንድም አንኳኩቷል።
ካለፉት በርካታ ሳምንታት ወዲህ በየመን በአስር ሺህ የሚቆጠር ህዝብ በሀገሪቱ ፕሬዚደንት አሉኢ አብዱላ ሳሌህ አንጻር ተቃውሞውን እንደቀጠለ ይገኛል።
የዐባይ ወንዝ ተፋሰስ አገሮች የውሃ አጠቃቀም አዲስ ውል ፣ ባለፈው ዓመት በግንቦት ወር አዲስ አበባ ውስጥ ሲፈረም፣ በዚያ ወቅት፤
ዓለም በ 2008 ዓ.ም. ከደረሰበት ከባድ የፊናንስና የኤኮኖሚ ቀውስ እርግጥ ቀስ በቀስ እያገገመ መሄዱ አልቀረም። ይሁን እንጂ ቀውሱ በተለይም በዓለምአቀፉ የምንዛሪ ስርዓት ላይ ጥሎት የሄደው ችግር በቀላሉ የሚገመት አይደለም።
የኢትዮጵያ አርበኞች የኢጣሊያ ጦርን ቅኝ ገዢ ጦርን አድዋ ላይ ድል ያደረጉበት አንድ መቶ አስራ-አምስተኛ አመት በአል ዛሬ በመላዉ ኢትዮጵያ እየተከበረ ነዉ።
«መታወቅ ያለበት ሞቃዲሾ ዉስጥ ጠንካራ ማዕከላዊ መንግሥት መመሥረት በሶማሊያ ሁኔታ አይሠራም።የሚያስፈልገዉ ሥልጣኑን ለአካባቢ መስተዳድሮች የሚያጋራ መንግሥት ነዉ።የሽግግር መንግሥቱ ማድረግ ያለበትም ይሕንን ነዉ
ቦን የሚገኘው በምህጻሩ ቢክ በመባል የሚታወቀው ዓለም አቀፍ ኮንቨርሽን ማዕከል የተባለው መንግስታዊ ያልሆነው ድርጅት እአአ ለ 2009 ዓም የዓለም ሀገሮች ለጦሩ ዘርፍ ያዋሉትን ወጪ የተመለከተበትን መዘርዝር ሰሞኑን አወጣ።
የኢትዮጵያ ጥንታዊ አርበኞች እስካፍንጫዉ የታጠቀዉን የኢጣሊያ ቅኝ ገዢ ሐያል ጦር ካሸነፋባቸዉ ምክንያቶቹ ዋና ዋናዎቹ ኢትዮጵያዊዉ የታሪክ ምሑር ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘዉዴ እንደሚሉት ሰወስት ናቸዉ።
ሊቢያ ውስጥ በተቀጣጠለው ሕዝባዊ ዓመጽ የተነሳ በርካታ አፍሪቃውያን በከፍተኛ ሁኔታ መቸገራቸው ተገለፀ። የችግሩ ገፈት ቀማሾች በተለይ ጥቁር አፍሪቃውያን እንደሆኑም ለማወቅ ተችሏል። አፍሪቃውያኑ ከሀዲ በሚል ተፈርጀው የጥቃት ሰለባ እየሆኑ ነው።
የጀርመን መከላከያ ሚኒስትር የባየርን (ባቬርያ) ክርስቲያን ሶሻል ኀብረት ፓርቲ አባል ካርል ቴዎዶር ትሱ ጉተንበርግ ከአካዳሚ ማዕረጋቸው ጋር
በጋምቤላ ሕዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት መዠንገር ዞን ጎደሬ ወረዳ ጉማሬ ቀበሌ የሚገኝ የተፈጥሮ ደን የለበሰ መሬት ለመዋዕለ ነዋይ አፍሳሽ ኩባንያ መሰጠቱ አሁንም እያነጋገረ ነዉ።
የኢትዮጵያ ቅጥረኛ ወታደሮች ወደ ሊቢያ ዘምተዋል የሚለዉን ዘገባም አምባሳደሩ አስተባብለዋል
የሊቢያው ፕሬዚዳንት ሙዓማር ቃዳፊ በሀገር ውስጥም ሆን በውጭ ጫናው እየበረታባቸው እንደሆነ ተገለፀ። ትናንት ከዋና ከተማዋ ትሪፖሊ አቅራቢያ በተቀሰቀሰ ግጭት በርካታ ሰልፈኛ እንደተገደለ ታውቓል። በአንፃሩ የአሜሪካ ጦር ወደ ሊቢያ እየተጠጋ እንደሆነም ተዘግቧል። ማንተጋፍቶት ስለሺ የሊቢያ ወቅታዊ ሁኔታን በተመለከተ የሚከተለውን አጠናቅሯል።
የጀርመን መከላከያ ሚንስትር ካርል ቴዎዶር ሱ ጉተንበርግ ዛሬ ስልጣናቸውን ለቀቁ።
ሰሜን አፍሪቃንና መካከለኛ ምሥራቅን ያናወጸው የሕዝብ እንቅስቃሴ በወቅቱ በተለይም በሊቢያ የአገዛዙን አስከፊ ገጽታ በሚገባ ሲያጋልጥ ማለቂያውን ለመገመት ደግሞ አዳጋች ሆኖ ቀጥሏል።
በሰሜን አፍሪካና በአንዳንድ የአረብ ሀገራት የሚገኙ ወጣቶች የመብት ጥያቄን በማንገብ ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎችን ሲያከናውኑ ዋነኛ መሳሪያቸው አድርገው የተነሱት የመረጃ ፍሰትን ነው። እናስ ታዲያ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች በሌሎች ሐገራት ስለሚገኙ ወጣቶች እንቅስቃሴ ምን ያህል ግንዛቤው አላቸው? መረጃዎችንስ በዋናነት ከየት ነው የሚያገኙት?
በሊቢያ የተቀጣጠለዉ ሕዝባዊ ዓመፅ ዛሬም አልበረደም። የጋዳፊን መሰናበት የሚጠይቁት ተቃዋሚዎች ከዋና ከተማ ትሪፓሊ 50ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚትገኘዉን አል ዛዉያ ከተማን በሳምንቱ ማለቂያ ይዘዋል።
የሊቢያ ሶሻሊስት ጀምሕሪያ የመስከረም አንዱ ታላቅ አብዮት መሪ-የከንግዲሕ እርምጃቸዉ 6.5 ሚሊዮን ሕዝባቸዉን ማወክ፥ ተቃዋሚያቸዉን መግደል፥ ከአፍሪቃ አረተኛዋን ሰፊ፥ ሐብታም ሐገር ሊቢያን በጎሳ ጠርዝ የሚከፋፍል እንዳይሆን በርግጥ ያሰጋል።
የቅመማ ቅመም ምርት ውጤት ካለፉት ብዙ ዓመታት ወዲህ ብዙ ትኩረት እያገኘ መጥቶዋል።
በአዲስ አበባ፡ በኦሮሚያ እና በደቡብ ብሄረሰብ ብሄረሰቦች ትናንት የካቲት ሀያ የ 2003 ዓም ሀገር አቀፍ የማሟያ ምርጫ ተካሄደ።
የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታ ም/ቤት ሊቢያ ውስጥ የሞአማር ጋዳፊ አገዛዝ የሕዝቡን እንቅስቃሴ ለመቅጨት በሲቪሉ ነዋሪ ላይ ያደረሰዉን ጥቃት በማስመልከት በሞአመር ጋዳፊ እና ተከታዮቻቸዉ ላይ ዉሳኔዉን አጸደቀ።
በሊቢያ መሪ ኮሎኔል ሙአመር ኧል ጋዳፊ አንጻር ካለፈው ሳምንት ወዲህ የተጀመረው የህዝብ ተቃውሞ ዛሬም በብዙ የሀገሪቱ ከፊል ተስፋፍቶ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው።
በቱኒዝያ የያስሚን ዓብዮት ካበቃ ወዲህ ሙስሊም አክራሪዎች በሀገሪቱ ሊኖራቸው የሚችለው ተሳትፎ ብዙ እያነጋገረ ነው።
የሊቢያው ቀውስ ተቀጣጥሏል። ሞአመር ጋዳፊ አልቄይዳ ሊቢያን እየበጠበጠ ነው ይላሉ። አብዛኞቹ የምስራቅ ሊቢያ ከተሞች በተቃዋሚዎች እጅ ላይ ወድቀዋል።
ለ 3 ወራት ኒውዮርክ አሜሪካ ውስጥ በህክምና ላይ ቆይተው የተመለሱት የስዑዲ ዐረቢያው ንጉሥ አብደላ፣ 36 ቢሊዮን ዶላር ገደማ የሚሆን ገንዘብ ለአገሪቱ ዜጎች በድጎማ መልኩ እንዲቀርብ ደንግገዋል።
ለአስር ቀናት የዘለቀዉ የበርሊኑ አለም አቀፍ የሲኒማ ትዕይንት ከአለም ዙርያ ለዉድድር የቀረቡ አራት መቶ ፊልም መካከል አሸናፊን በመምረጥ ባለፈዉ እሁድ ምሽት በደማቅ ዝግጅት ተጠናቆአል።
በዓለም የመጀመሪያው በስዕል ተደግፎ የተጻፈ መጽሐፍ ቅዱስ በኢትዮዽያ ተገኘ። መጽሐፍ ቅዱሱ የተገኘው በሰሜን ኢትዮዽያ በትግራይ ክልል አድዋ አከባቢ በሚገኘው የአባ ገሪማ ገዳም ውስጥ ነው።
ብርቱ ተቃውሞ የገጠማቸው የሊቢያው ዓብዮታዊ መሪ ሙአመር ኧል ጋዳፊ ጋዳፊ በስልጣን ለመቆየት የመጨረሻ ተስፋቸውን በአፍሪቃውያን ቅጥረኛ ወታደሮች ላይ ማሳረፋቸውን የመገናኛ ብዙኃን እና የተቃዋሚ ወገኖች የሚያወጡዋቸው ዘገባዎች ያመለክታሉ።
በዛሬው ሳይንስና ኅብረተሰብ ቅንብራችን፣ የህይወትን ሥረ-መሠረት ለማወቅ ፤ በየብስ ፤ በባህርና በኅዋ የሚደረገውን ምርምር እንዳስሳለን።
የኢትዮጵያ ቅጥረኛ ወታደሮች የሊቢያን መንግሥት ደግፋዉ አመፀኛዉን ሕዝብ እየወጉ ነዉ የሚለዉን ዘገባ አምባሳደር አይሌ አጣጥለዉ ነቅፈዉታል።
ትሪፖሊ የሚኖሩ ሌሎች ኢትዮጵያዉያን ስደተኞች እንደገለፁት ግን ቤንጋዚ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን መገደል፥ መደብደብ መታሠራቸዉንም ሰምተዋል።እዚያዉ ትሪፖሊ ደግሞ ቢያንስ ሁለት ኢትዮጵያዉያን መገደላቸዉንም ገልፀዋል
ተቃዋሚ ድርጅት «ለሁለት የመከፈሉን» አደጋ አስወገድኩ ያለዉ 14 የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላቱን ካስወገደና በርካታ የላዕላይ ምክር ቤት አባላትን ካባረረ በሕዋላ ነዉ
በሊቢያ የተቀጣጠለው ህዝባዊ አመፅ የሀገሪቱን ጦር ለሁለት መክፈሉ ተገለፀ። የጦሩ አንደኛ ወገን ለሙዓመር ቃዳፊ ታማኝነቱን ሲያሳይ፤ ሌላኛው ወገን ህዝባዊ አመፁን መቀላለሉ ተዘግቧል።
የተመድ የጸጥታዉ ምክር ቤት የሊቢያ መንግስት ተቃዋሚዎቹን ማዋከቡን አዉግዞ፤ ጥቃት እንዲያቆም ጠየቀ።
በያዝነው በጎሮጎሮሳውያኑ 2011 ዓ.ም በ 7 የጀርመን ፌደራል ክፍለ ግዛቶች ከሚጠበቁት ምርጫዎች አንዱ ባለፈው ዕሁድ በሁለተኛዋ የጀርመን ትልቅ ከተማ በሀሐምቡርግ ተካሂዷል ።
በጋምቤላ ሕዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት መዠንገር ዞን ጎደሬ ወረዳ ጉማሬ ቀበሌ የተፈጥሮ ደን የመመንጠር አደጋ ላይ ወድቋል።
በሊቢያ የህዝብ አመፅ ይቃጣል ተብሎ ሳይታሰብ ፤ ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ ፣ተጀምሮ እንደቀጠለ ነው። ይሁንና በግብፅ የታየውን ቁጥብነት ያላንጸባረቁት የአገሪቱ የጦር አኤሮፕላኖችና ሄሊኮፕተሮች፣ ለተቃውሞ አደባባይ በወጣው ህዝባቸው ላይ መተኮሳቸው ከተዘገበ ወዲህ በዓለም ዙሪያ ፤
የኢትዮጵያ መንግስት በመሰረታዊ ሸቀጦች ላይ ከጥቂት ጊዜ በፊት የዋጋ ተመን አስቀምጦዋል።
በሊቢያ ሰልፈኞች ላይ መንግስት የወሰደው እርምጃ በዓለም ዙሪያ ከፍተኛ ውግዘትን አስከትሏል። የመንግስታቱ ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በሰው ልጅ ላይ የተፈጸመ ወንጀል ሊሆን ይችላል እያለ ነው። ቱርክ ለሊቢያ ባለስልጣናት ጠንካራ ማስጠንቀቂያ ሰዳለች።
የአልጀዚራ ቴሌቭዥን ፣ የእንግሊዝኛው ሥርጭት፣ ዩናይትድ እስቴትስ ውስጥ ያለው ተመልካች ቁጥር እጅግ መጨመሩ ተገለጠ።
ቤን አሊን፥ ከቱኒዝ፥ ሙባረክን ከካይሮ አሽቀንጥሮ የጣለዉ አዲሱ ሕዝባዊ አመፅ የአረቡን አለም እየናጠ በአዲስ ጎዳና እየዘወረዉም ነዉ። የፕሬዝዳንት ጆርጅ ደብሊዉ ቡሽና የጠቅላይ ሚንስትር ቶኒ ብሌሯ ዲሞክራሲያዊት ኢራቅም ከአዲሱ ሕዝባዊ ነዉጥ አላመለጠችም
የሶማሊያ መዲና መቅዲሾ የሳምንቱን የዕረፍት ቀናት ቅዳሜና ዕሁድን በጦርነት አሳልፋለች። ዛሬ ጠዋትም በአጥፍቶ ጠፊ የቦምብ ጥቃት ስትናጥ አርፍዳለች።
በቴህራን መንግሥት ኢራን ውስጥ ተይዘው የነበሩ ሁለት የጀርመን ጋዜጠኞች ከአራት ወራት እስር በኋላ መለቀቃቸዉን የጀርመን የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ።