ሊቢያ ፣ ግድያና ተቃውሞ

በሊቢያ ሰልፈኞች ላይ መንግስት የወሰደው እርምጃ በዓለም ዙሪያ ከፍተኛ ውግዘትን አስከትሏል። የመንግስታቱ ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በሰው ልጅ ላይ የተፈጸመ ወንጀል ሊሆን ይችላል እያለ ነው። ቱርክ ለሊቢያ ባለስልጣናት ጠንካራ ማስጠንቀቂያ ሰዳለች።