ሐምሌ ፭( አምት )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሻለቃ ኃይሌ ፕሬዚዳንት የመሆን ፍላጎት እንዳለው ለዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን መግለጹን ተከትሎ ኢህአዴግ መራሹ ራዲዮ ፋና ባልተለመደ መልክ ዜናውን ደጋግሞ እንዳራገበው አንድ የፖለቲካ ተንታኝ ጠቅሰው ፣ ሀይሌ የሰጠውም መግለጫ ሆነ የሬዲዮ  ፋና ዘገባ በድንገት የሆነ ሳይሆን ታቅዶበት የተደረገእንደሚሆን ግምታቸውን አስቀምጠል፡፡ በአሁኑ ወቅት በስልጣን ላይ የሚገኙት መቶ አለቃ …

በማናዬ በላይ
     IV.       ቻዉ ቻዉ ሂንዱይዝም
    አምበድከር በሂንዱ ዉስጥ ሆኖ ሐይማኖቱን ለማስተካከል ያደረገዉ ጥረት ፍሬ አልባ ከሆነ በኋላ በ1935 ባዘጋጀዉ ዮላ ኮንፍረንስ ላይ ሂንዱ ሆኜ ብወለድም ሂንዱ ሆኜ ግን አልሞትም በማለት በግልፅ የአይነኬ አባላትን የሂንዱ ሐይማኖትን ትተዉ ሌላ ሐይማኖት እንዲይዙ ሰበከ፡፡ እንደ አንበርከር እይታ ሂንዱይዝም እኩልነት፤ ፍትህ እና ወንድማማችነት የጎደለዉ ሐይማኖት ነዉ፡፡ በእርግጥም ትክክል ነበር፡፡ የእምነቱ ተከታዮችን በደረጃ የሰደረ፤ አገልጋይ ተገልጋይ፤ አዋቂ አላዋቂ፤ ቆሻሻ ንፁኅ፤ እና ሌላም ሌላም ብሎ በዉልደት የሚከፋፍል ሐይማኖት ሂንዲ ብቻ ሲሆን ያለዉም በህንድ ብቻ ነዉ፡፡ ለተወሰኑ አመታት አምበድከር የየትኛዉ እምነት ተከታይ እንደሆነ ግልጽ አልነበረም፡፡ የተለያዩ ሐይማኖት ተወካዮች ቀርበዉ ያናግሩት ነበር በመጨረሻ ከታሪካዊ፤ ሀገራዊ ፋይዳዉና ከእምነቱ ፍልስፍና ተነስቶ ቡድሂዝምን መርጧል፡፡
         V.        አምበድከር እና የፖለቲካ ጥያቄ
      ዶ/ር አምበድከር የማኅበራዊ እና ሐይማኖታዊ ጥያቄዉ የፖለቲካ ስልጣን ከሌለ ዉጤታማ አይሆንም የሚል እምነት አለዉ፡፡ እንደ አምበድከር እምነት ነፃነት ያለ ማኅበራዊ ፍትህ ፋይዳ የሌለዉ የጨቛኝ ቅያሬ ብቻ ነዉ፡፡ ዶ/ር አምበድከር ከህንድ ነፃነት በፊት እንግሊዞችን ከዚያም የህንድ ፖለቲካ ሲስተም የተቆጣጠረዉን የኮንግረስ ፓርቲ እና እንደ መንፈሳዊ አባታቸዉ የሚያመልኩት ጋንዲ ጋር በተደጋጋሚ በመጋፈጥ ለሹድራ መብት ሲታገል ቆይቷል፡፡ የአምበድከር የፖለቲካ ትግል በጉልህ የሚጀምረዉ እንግሊዝ የአበርከርን የሹድራ አባላት መሪነት ሚና ተቀብለዉ ለንደን በሚከናወነዉ የጠረጴዛ ዙርያ ኮነፍረንስ ጥሪ ሲያቀርቡለት ነዉ፡፡
      በዚህ ለንደን ላይ በ1930ዎቹ ለሁለት ጊዜ በተከናወነዉ ኮንፍረንስ አምበድከር የአይነኬዎችን ጥያቄ አንግቦ በአሳማኝ አንደበቱ ኮንግረስ ፓርቲ ተወካይ የነበረዉን ጋንዲን በእንግሊዞች ፊት ተከራክሮ የወቅቱ ጠ/ሚር የነበሩት ራምሴ ማክዶናልድን በማሳመን አይነኬዎች እንደ ሙስሊሞች እና ክርስቲያኖች ከሂንዱ ተነጥለዉ የተለየ የምርጫ እና ዉክልና ይሰጣቸዉ ዘንድ በወቅቱ ከቅኝ ገዢያቸዉ እንግሊዝ ዉሳኔን አሰጠ፡፡  በመጀመሪያዉ ኮንፍረንስ ማሀተመ ጋንዲ ባይሳተፍም በሁለተኛዉ ተሳትፎ ዉጤታማ ለመሆን አልቻለም ነበር፡፡ የአምበድከር እና ጋንዲ ግጭት በግልፅ የሚጀምረዉ እዚህ ነዉ፡፡ (የሚቀጥለዉን ርዕስ ይመልከቱ፡፡)
      አምበድከር በ1926 የቦምቤ ህግ አዉጭ ምክር ቤት አባል በመሆን፤ በ1936 የሌበር ፓርቲ በማቋቋም፤ በ1942 የሹድራ ካስት ፌዴሬሽን በማቋቋም በአጠቃላይ ህይወቱ እስካለፈበት 1956 ድረስ ሙሉ ጊዜዉን ለሹድራ ካስት አባላት ንቃተ ህሊና፤ ማኅበራዊ እና ፖለቲካዊ ዉክልና እንዲሁም ካስት ስርዓትን ለማስወገድ በሙሉ አቅሙ ከመስራቱ ባሻገር በእሱ ዘመን ካመጣቸዉ ዉጤቶች በተጨማሪ ከእርሱ በኋላ ለተፈጠሩት የሹድራ መነሳሳት አርዓያ ነበር፡፡
      አምበድከር ይታገል የነበረዉ ትምህርት ለተነፈጋቸዉ፤ በአጉል ሐይማኖት እና ባህል ተጠፍንገዉ ለሚኖሩ አብዛኞች የህንድ ዜጎች ሲሆን ከዚህ ጋር ተያይዞ በበላይ ካስት ሂንዱ በየወቅቱ የሚፈጠርበትን ከማኅበረሰቡ የመነጠል ድርጊቶች መቋቋሞ የትግሉ ዋንኛ አካል ነበር፡፡ ለዚህም ነዉ ከነፃነት በኋላ በምርጫ ተወዳድሮ ያልተመረጠዉ፡፡ ከዚያ ቀደም ብሎ የሎክ ሳብሀ (የህንድ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት) እንዲሁም በምርጫ በተሸ ነፈበት ወቅት ቦምቤን ወክሎ የራጃ ሳብሀ (የክልሎች ተወካይ ም/ቤት) አባል ነበር፡፡
         VI.        አስተዋፅኦ
        ዶ/ር አምበድከር ማኅበራዊ ፍትህ ከፖለቲካ ለዉጥ መቅደም አለበት የሀገር ነፃነትን ከህዝብ ነፃነት መለየት የለብንም ሁሉም በሀገሪቷ የሚገኝ ቡድን እኩል የፖለቲካ ዉክልና ሊኖረዉ ይገባል የተጨቆነ እኩል እስኪሆን ድረስ የተለየ ዉክልና ተጠቃሚ ሊሆንም ይገባል የሚለዉ እሳቤዉ አሁን ህንድ ለምትከተለዉ የዉክልና ስርዓት መነሻ ነዉ፡፡ ጨቛኝን በመለመን፤ ርህራሔ በመጠየቅ እና ችሮታ ላይ በመንተራስ የሚገኝ ፍትህ አለመኖሩም ይልቁንስ ራስን በማሳደግ፤ ለራስ ክብር በመስጠት፤ ቆራጥ በሆነ ሰላማዊ ትግል እንጂ መብትህን ከቀማህ ሰዉ ወይም ቡድን ችሮታን በመለመን የሚመጣ ፍትህ የለም የሚለዉ እሳቤዉም ከሱ በኋላ ለተደረጉ የፍትህ ጥያቄዎች መነሻ ነዉ፡፡
        አምበድከር ህይወት ለተነፈጉ ህይወት የሰጠ፤ ድምፅ ለሌላቸዉ የጮኾ የሹድራዎች መሪ ነዉ፡፡ ከአምበድከር በፊት የተሸነፉ፣ የተጨቆኑና የተረሱ አገልጋይነታቸዉን አምነዉ ይኖሩ የነበሩ አይነኬዎች በደል በጣም ሲበዛባቸዉ “Kabira kahe ye jag andha” (ማየት የተሳናት አለም) ብለዉ ከማንጎራጎር ያለፈ መብታቸዉን ለመጠየቅ አቅምም ይሁን ፍላጎት ያልነበራቸዉ ሹድራዎች ከአምበድከር በኋላ የፍትህ እና እኩልነት ጥያቄ አንግበዉ የሚታገሉ ጀግኖች ሆነዋል፡፡ ለዚህም ጠፍንጎ የያዛቸዉን የሂንዱ ሐይማኖት ጥለዉ ወደ ሌላ ይሄዱ ዘንድ አምበድከር ያደረገዉ ሐይማኖታዊ ትግል እጅጉን የሚደነቅ ነበር፡፡
        ከህንድ ነፃነት ማግስት የህንድ ዉስብስብ ማኅበረሰብ የሚወክል ሕገ መንግስት አርቃቂ በባትሪ ኮንግረስ ፓርቲ በሚፈልግበት በ1946 የህንድን ማህበረሰብን በተሻለ የሚያዉቀዉ ምሁር ባለመገኘቱ ምንም እንኳን ፍልስፍናዉና ጥያቄዉ ከሀገር አንድነት መሻት በቀር ከኮንግረስም ይሁን አይከናቸዉ ከሆነዉ ጋንዲ ጋር ባይጣጣምም አምበድከርን ለዚህ ስራ ከማጨት ዉጭ አማራጭ አልነበራቸዉም፡፡ ዶ/ር አምበድከር ከኮንግረስ ፓርቲ ሕገ መንግስት እንዲያረቅ የቀረበለትን ጥያቄ ተቀብሎ ሙሉ ጊዜዉን በመስጠት እስካሁን የሚገለገሉበትን እና በ1950 የፀደቀዉን የህንድ ሕገ መንግስት ያረቀቀ ታላቅ ሰዉ ነዉ፡፡ ለአይነኬዎች እኩልነት ሕገ መንግስታዊ እንዲሆን ከማድረጉ ባሻገር የተለየ የሪሰርቬሽን ስርዓት እንዲኖር በማድረግ እስካሁን ሲመሰገን ይኖራል፡፡
        ዶ/ር አምበድከር ከነፃነት በኋላ የህንድ የመጀመሪያዉ የሕግ ሚኒስቴር ሆኖ አገልግሏል፡፡ አምበድከር አርቅቆት የነበረዉን የሂንዱ ኮድ ቢል የኮንግረስ ፓርቲ ባለመቀበሉና አናፀድቅም በማለታቸዉ በ1951 በፍቃዱ ስራዉን ለቀቀ፡፡
        አምበድከር ለሹድራ ንቃተ ህሊና ማደግ የመሰረተዉ People Educational Society በአሁን ሰዓት በመላዉ ሀገሪቱ ከመጀመሪያ ደረጃ እስከ ዩኒቨርሲቲዎች በመክፈት በማገልገል ላይ ይገኛል፡፡ ከዚህ ባሻገር የተለያዩ መጽሔቶችን በማዘጋጀት ለሹድራ ንቃት ትልቅ አስተዋፅኦ አድርጓል፡፡ የካስት ስርአት የማያዉቅ በእኩልነት ፍትህ እና ወንድማማችነት የሚያምነዉ ቡድሂዝም በህንድ እንዲስፋፋና ሹድራ ከተጫነባቸዉ ሐይማኖታዊ ቀንበር እንዲላቀቁ እና እንዲነቁ አድርጓል፡፡
        ዶ/ር አምበድከር ያለዉን የሚፈፅም የተግባር ሰዉ ከመሆኑ ባሻገር በአጠቃላይ ለማህበረሰቡ ከ20 በላይ መጻሕፍትን ጽፎ ያበረከተ ታላቅ ሰዉ ነዉ፡፡ ከፊሎቹን ለማየት ያክል፡- The problem of Rupee, Annihilation of Caste, Thought on Pakistan, Who were the Shudras?, Ancient Indian Commerce, Buddha and his Dharma, Essay on Untouchables, what congress and Gandhi have done to untouchables እና ሌሎችም፡፡
        ይቀጥላል፡፡
        — 
        ጸሐፊውን ለማግኘት [email protected] ላይ ይጻፉላቸው፡፡

        ኮሌጁ እንዲዘጋ የውሳኔ መነሻ የሰጠው ከአቡነ ጢሞቴዎስ ተጽዕኖ ያልወጣው የኮሌጁ ቦርድ ነው አቤቱታቸውን ለመንግሥት አካላት ያሰሙት ደቀ መዛሙርቱ ‹‹ቅ/ሲኖዶስ እና ምእመናን የከፈቱት ኮሌጁ የሚዘጋው በመቃብራችን ላይ ነው!›› በሚለው አቋማቸው ጸንተዋል፤ በአስተዳደር ሕንጻው ዙሪያ የሚያደርጉትን ቁጥጥር አጠናክረዋል

        ሐምሌ 4 ቀን 2005 ዓ.ም ደሴ በፖለቲካ ቅስቀሳ ተናውጣላች። በአንድ በኩል፣ አንድነት ሕዝቡ ሕገ መንግስታዊ መብቱን የመጠቀም ፣ ሃሳቡን በነጻነት የመግልጽ፣ መሪዎቹን በፈለገ ጊዜ የመሾምና የመሻር መብት እንዳለው እያስተማረ፣ በዜጎች ላይ እየደረሰ ያለዉን የግፍ ቀንበር በመቃወም፣ እግዚአብሄር የሰጠዉን፣ የአለም አቀፍ ሕግ ሆነ የኢትዮጵያ ሕገ መንግስት የፈቀደለትን መብት በመጠቀም ደሴዎች ድምጻቸውን እንዲያሰሙ በላወድ ስፒከር እየቀሰቀሰ ነዉ። […]

        ሐምሌ 4 ቀን 2005 ዓ.ም አንድነት ፓርቲ በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ የከተማው መስተዳደሮችና የፀጥታ ኃይሎች ፓርቲው ህጋዊ የማሳወቅ ስራውን መስራቱን ገልፀው ሰልፉን መከልከል እንደማይችሉ ካረጋገጡ በኋላ፣ በከተማው ያሉ የቀበሌ ሰራተኞች መደበኛ ስራቸውን ጥለው በሰላማዊ ሰልፉ ዙሪያ በየቤቱ እየዞሩ ማስፈራራትና ሰላማዊ ሰልፉ ላይ ማንም እንዳይገኝ፣ ሰልፉ ህገወጥ ነው በሚል ቅስቀሳ እየሰሩ መሆናቸውን ከስፍራዉ የደረሱ ዜገባዎች ይጠቁማሉ።፡ «ነዋሪው […]

        «ማንኛዉም ፖለቲካዊ ለዉጥ ቢደረግ ተጠያቂ እንሆናለን ብለዉ ያስባሉ።ለዚሕም ነዉ የሕዝብ ጥያቄን የሚያነሳ፥ የሕዝብን ጉዳይ የሚናገርን የሚያፍኑት።እኛ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት እንዲመሠረት ጥሪ እያቀረብን ነዉ።አሁን የምናየዉ ግን የዲሞክራሲ ምሕዳሩ በጣም እየጠበበ ነዉ።»

        በአገራችን የኪነ-ጥበብ መድረክ ለረጅም ዓመታት ያገለገሉ እና በአሁኑ ወቅት በበሽታ በእድሜ አቅም አንስዋቸዉ ተረስተዉ የሚገኙ ታዋቂ ሰዎችን ለመርዳት በጀርመን አገር የተቋቋመዉ ማዕከል የዛሬ 10 ቀን ግድም ከኢትዮጵያ 6 ታዋቂ የመድረክ ሰዎችን ጋብዞ በተለያዩ የአዉሮጳ አገራት የመጡ ከያንያን በተገኙበት ባህላዊ የመድረክ ዝግጅትን አካሂድዋል።

        ቢንላደን እንዳይያዙ በመጠበቅ ከለላ አድርገዋል ሲል በስም የጠቀሰው ባለሥልጣን ባይኖርም ከአሁኑም ሆነ ከቀድሞ ባለሥልጣናት ድጋፍ ያደረገላቸው እንደማይጠፋ ጠቅሷል ። ምዕራባውያን ተንታኞች ግን የፓኪስታን የደህንነት ባለስልጣናት ቢንላደን የኖሩበት የነበረውን ቤት ለይተው ማወቅ ያለመቻላቸው ምክንያት ቸልተኝነት ነው የሚለውን አይቀበሉም ።

        የብሪታንያ ፓርላማ በኢትዮጵያ ጉዳዮች ላይ ሲወያይ አመሸ። ሃዉስ ኦፍ ኮመን በመባል የሚታወቀዉ የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ትናንት ማምሻዉን የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታና ያለፉት 22ዓመት እንዲሁም ወደፊት እያንዣበበ የመጣ ያለዉን ችግር የዳሰሰ ጉባኤ ተካሂዷል።

        ሐምሌ ፬( አራት )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሀምሌ 7፣ 2005 ዓ/ም በደሴና ጎንደር ከተሞች አንድነት ፓርቲ የጠራቸው የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፎች በታቀደላቸው ጊዜ እንደሚካሄዱ ከመንግስት እውቅና የተሰጣቸው ቢሆንም፣ የገዢው ፓርቲ ካድሬዎችና ባለስልጣናት የቅስቀሳ ወረቀቶችን የሚበትኑትን ሰዎች ከማሰር እና ከማስፈራራት አልፈው ፣ ከአዲስ አበባ የሄዱ የፓርቲው አመራሮች አልጋ እንዳያገኙ የሆቴል ባለንብረቶችን እስከ ማስፈራራት መድረሳቸውን የፓርቲው አመራሮች …

        ሐምሌ ፬( አራት )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መስተዳድሩ-ለፓርቲው በጻፈው ደብዳቤ- መድረክ ለእሁድ ሐምሌ 7 ቀን 2005 ዓመተ ምህረት ከጧቱ 3፡00 ሰዓት እስከ 6 ፡00 ሰዓት የሚቆይና ከስድስት ኪሎ ተነስቶ በአራት ኪሎ፣ በፒያሳና በቸርችል ጎዳና በማድረግ  መዳረሻው ድላችን ሐውልት የሚያደርግ ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ ያቀረበውን ጥያቄ እንደተመለከተው በመጥቀስ፤ሰላማዊ ሰልፉ የሚደረግበት የጉዞ መስመር  በአሁኑ ጊዜ እየተዘረጋ ባለው …

        ሐምሌ ፬( አራት )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ብሄራዊ ኮንግረስ የወጣቶች ሊግ ሊቀመንበር ጁሊየስ ማሌማ ኢኮኖሚክ ፍሪደም ፋይተር የተሰኘ ፓርቲ መስርቷል። ወጣቱ ፖለቲከኛ በነጮች የተያዙት የአገሪቱ መሬት ለህዝቡ እንዲከፋፈል እና  ዋና ዋና የማእድን ፋብሪካዎች በመንግስት ቁጥጥር ስር እንዲውሉ እንደሚታገል አስታውቋል። ማሌማ ፓርቲው ጸረ ካፒታሊዝም መሆኑም ገልጿል። “እኛ ጥቁሮች በዚህ አገር ስንኖር የምናሳያው …

        ከአዲስ አበባ 401 ኪሎ ሜትር በስተሰሜን በምትገኘው ታሪካዊቷ የወሎ ክፍለ ሀገር(የአሁኑ ደቡብ ወሎ ዞን)ከተማ ደሴ ልክ እንደ አዲስ አበባ የክረምቱ ዝናብና ብርድ ቢያስቸግርም የነዋሪዎቿ እና የንግድ እንቅስቃሴዎቿ የምን አዲስ አበባ ያሰኛል፡፡ ይበልጥ ደግሞ ሲዘፈንላት የኖረው የነዋሪዎቿ ውበት፣ ተግባቢነትና በሙስልም ክርስቲያኑ በፍቅር ተግባቦት የሚያስቀና ኑሮ እንጉርጎሯዊ አድናቆት ይሰማል፡፡ ይህ ደግሞ በተግባርም እውነት መሆኑንን ስመለከት አቦ ደሴዎች […]

        ጀርመን በቢራ ዓይነት የታወቀ ሀገር ነው ፤ በብዛትም ይጠጣል፤ በዓመት በነፍስ ወከፍ ሲሰላ እያንዳንዱ ሰው 112,5 ሊትር ያህል ቢራ ይጠጣል ማለት ነው። ትኩሱ መጠጥ ቡና ደግሞ ፣ አሁንም ከዚያ ልቆ ፣ የአንደኝነቱን ሥፍራ እንደያዘ ነው ።

        ዴቼቬለ ያነጋገራቸው አስተያየት ሰጭዎች አትሌት ኃይሌ ገ/ስላሴ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ትርጉም ያለው ተፅእኖ የሌለውን የፕሬዝዳንትነት ሥልጣን ከመመኘት ይልቅ ተሰሚነቱን ተጠቅሞ ፋይዳ ያለው አስተዋፅኦ ቢያደርግ ይሻላል ብለዋል ።

        የፓርቲዉ አባላትና ደጋፊዎች የታሠሩትም ፊርማ ለማሰባሰብ፥ ሠልፍና ስብሰባዉን ለማደራጀት ሲንቀሳቀሱ ነዉ።ከሰኔ ሃያ-ሁለት እስከ ሰላሳ በነበረዉ አንድ ሳምንት ብቻ ዘጠኝ የፓርቲዉ አባላት በፀጥታ አስከባሪዎች ታስረዋል።አብዛኞቹ የታሠሩት ሰሜን ጎንደር ነዉ።አንዱ ታስረዉ ተለቀዋል።አስራ-አንደኛዉ ከግድያ ሙከራ አምልጠዋል።

        በግብፅ በተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎችና በህዝቡ መካከል ልዩነቱ መስፋቱና ፍጥጫውም ማየሉ የግብፅን የፖለቲካ ሂደት ይብሱን እንዳያሰናክለው ሃገሪቱንም ወደ ፖለቲካ ትርምስ እንዳይከታት የሚያሰጋ ነው ሲል የአውሮፓ ህብረት አሳሰበ።

        ዶቼቬለ ያነጋገረው አንድ ሙስሊም በፆሙ ወራትም ቢሆን ሙስሊሙ ከዚህ ቀደም ለመንግሥት ያቀረባቸው 3 ጥያቄዎች እንዲመለሱ በተጨማሪ የታሰሩት የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላትም እንዲፈቱ መጠየቁን እንደማያቋርጥ አስታውቋል ።

        በዩ ኤስ አሜሪካና በአውሮፓ ሕብረት መካከል የሚካሄደው ትራንስ አትላንቲክ የንግድና መዋዕለ ነዋይ ሽርክና ውል ድርድር ባለፈው ሰኞ ዋሺንግተን ላይ ተጀምሯል።

        ሐምሌ 3 ቀን 2005 ትናንት በማለዳ ነበር ተነስቼ ከሰሚት ወደ ሳሪስ ያቀናሁት፡፡ የሐምሌን ቀዝቃዛ የጠዋት አየር እየተመገብኩ ከጓደኞቼ ጋር ከተቀጣጠርኩበት ሐበሻ ካፌ ስደርስ ሰዓቴ ከጥዋቱ 1፡30 (7፡30 AM) ይል ነበር፡፡ ሁላችንም ከየአቅጣጫዉ በዚያች አነስተኛ ካፌ ከተሰባሰብን በኋላ ቁርስ ቢጤ እንደ …

        የቃሊቲ ዉሎ ከነእስክንድር ነጋ ጋር – በበትረ ያዕቆብ Read more »

        ሐምሌ 3 ቀን 2005 ዓ.ም የአንድነት ፓርቲ አመራር አባላት፣ በጎንደርና በደሴ የሚያደርጉትን ቅስቀሳ ቀጥለዉበታል። በደሴ ወረቀቶች እየተበተኑ፣ ፔትሽኖችም እየተሞሉ ሲሆን፣ በመኪና ላይ በመሆንና በየሰፈሩ በመዘዋወር በላውድ ስፒከር የትግል ጥሪ እየተላለፈ ነዉ። እንደዚያም ሆኖ ግን ገዢው ፓርቲ ኢሕአዴግ፣ ባህሪዉ ነዉና፣ አፍራሽ እርምጃዎችን ከመዉሰድ አልተቆጠበም። ላለፉት ሃያ አመታት እንዳደረገዉ፣ የሕዝብን መሰረታዊ የዴሞክራሲ ጥያቄዎችንና ሕገ መንግስታዊ መብቶች ለማፈን […]

        ሐምሌ ፫( ሦስት )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኢትዮጵያ ያለውን የሰብአዊ መብቶች ጥሰት፣ የኑሮ ውድነት እና የፍትህ እጦት ለመቃወም ፓርቲው በጎንደርና በደሴ የጀመረውን ቅስቀሳ ወረቀቶችን በመበተን፣ እና በመኪና ላይ በመሆን በየሰፈሩ በመዘዋወር በድምጽ ማጉያ የትግል ጥሪ እያስተላለፈ ነው። በደሴ ከተማ በማስተባበር ላይ የሚገኙት የአንድነት ፓርቲ ብሄራዊ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ዘካርያስ የማነብርሃንና የፍኖት ነጻነት ጋዜጠኛ …

        ሐምሌ ፫( ሦስት )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መንግስት በ10/ 90 ወይም በ20 / 80 የቁጠባ ስርአት የኮንዶሚኒየም ቤት ለመስራት የሚፈልጉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገንዘባቸውን የመንግስት ንብረት በሆነው በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብቻ እንዲያስቀምጡ ትእዛዝ ማስተላለፉ የግል ባንኮችን የሚያዳክም ነው የሚል ትችት ሲቀርብ ሰንብቷል። ገንዘባቸውን በግል ባንኮች ያስቀምጡ የነበሩ ደንበኞች ደንበኝነታቸውን  እየሰረዙ በንግድ ባንክ ማስቀመጥ ከጀመሩ …

        ሐምሌ ፫( ሦስት )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአሜሪካን ኤምባሲ በተካሄደው የአምባሳደሮቹ ስብሰባ ላይ በቅርቡ የተመሰረተውንና በአዲስ አበባ ከተማ በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች የተገኙበትን ሰላማዊ ሰልፍ ማካሄድ የቻለውን ሰማያዊ ፓርቲን ብቻ ጠርተው አነጋግረዋል። በተለምዶ ‘‘የኢትዮጵያ ለጋሾች ቡድን’’ የሚል መጠሪያ ያለውና የአሜሪካንን ጨምሮ በርካታ የአውሮፓ ሀገራት አምባሳደሮች በአባልነት የሚገኙበት የለጋሾች ቡድን በተለያዩ ጊዜያት በሀገሪቱ የሚንቀሳቀሱ ከፍተኛ የተቃዋሚ …

        ሐምሌ ፫( ሦስት )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከአካባቢው ያገኘነው መረጃ እንደሚያመለክተው የመከላከያ ሰራዊት አባላትና ልዩ ፖሊሶች በቶዮታ ፒክ አፕ መኪኖች ላይ ሆነው በየመንደሩ በመዞር ህዝቡን ሰብስበው እያነጋገሩ ነው። ወታደሮቹ ” የማንነት ጥያቄዎችን ያቀረባችሁት እናንተ ናችሁ ወይስ ጸረሰላም ሀይሎች ናቸው?” በማለት ጥያቄ ሲጠይቁ መዋላቸው ታውቋል። ድርጊቱ በሚቀጥሉት ቀናት በተማሳሳይ መንገድ ይደረጋል ተብሎ የሚጠበቀውን የተቃውሞ ሰልፍ …

        ፖሊስ የጠቅላይ ቤተ ክህነቱን ዋና ሥራ አስኪያጅ አነጋግሯል በተቃውሞው የተበሳጩት የኮሌጁ ሊቀ ጳጳስ ራሳቸውን ስተው እንደነበር ተጠቁሟል ‹‹አልፈው በመቃብራቸው ላይ መሣቅ እንፈልጋለን›› – የጥላቻው ምሬት ‹‹በተራዘመው መርሐ ግብር ሳቢያ የተጨመረው በጀት ለብክነት እየተዳረገ ነው›› /ደቀ መዛሙርቱ/ ዛሬ ጠዋት ወደ መንበረ ፓትርያሪክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ያመሩት የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ደቀ መዛሙርት በመንበረ ፓትርያሪኩ ቅጽር …


         

        በሚኪያስ በቀለ
         “Any law that uplifts human personality is just. Any law that degrades human personality is unjust. One has not only a legal but a moral responsibility to obey just laws. Conversely, one has a moral responsibility to disobey unjust laws… for an unjust law is no law at all.” Dr. Martin Luther King
        የመንግሥት ወይስ የሕዝብ ሕግ?
        በኢትዮጵያ ውስጥ የፀረ ሽብር አዋጅ የወጣው በ2001 ዓ.ም ላይ ሲሆን የአዋጁ ረቂቅ የተለያዩ የአለም ዓቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ደርጅቶች እና የተቃዋሚ ፓርቲዎች አዋጁ የዜጎችን የሰብኣዊ መብቶች አደጋ ውስጥ ስለሚከት መስተካከል እንደሚኖርበት ድምፃቸውን አሰምተው ነበር፡፡ ነገር ግን መንግሥት ትችቶቹን ከቋፍ ሳይከት አዋጁን በ2001ዓ.ም ከ547 የፓርላማ አባላቶቿ ውስጥ 378ቱ በተገኙበት በ268 የአዎንታ ድምጽ፣ በ91 ተቃውሞ እና በ1 ድምፀ ተአቅቦ የፀረ ሽብር አዋጅ ቁጥር 652/2001 ኅብረተሰቡን ከአደጋ ለመጠበቅ በሚል አወዛጋቢውን ሕግ አውጥቶ ማስፈጸም ጀምሯል፡፡
        አዋጁ በወጣበት ቀን “ባለራዕዩ” የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስቴት መለስ ዜናዌ የአዋጁን ትክክለኛነት (Ligitimacy) ለፓርላማው ሲያብራሩ “… አዋጁን ስናረቀቅ ከአሜሪካ፣ ከእንግሊዝ እና ከአውሮፓ አገራት ጥሩ ጥሩውን ቃል በቃል….ለምሳሌ በነዚህ ሃገራት ባለው ሕግ አሸባሪ ብሎ የመፈረጅ ሥልጣን የሕግ አስፈፃሚው ሲሆን እኛ ግን የሕግ አውጪው ሥልጣን እንዲሆን አድርገናል…” ብለው ነበር፡፡ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስቴር በዓለማችን የሕግ የበላይነት ከሰፈነባቸው አገራት የፀረ ሽብር አዋጁን “ቃል በቃል” መገልበጣቸው ሕጉን ትክክለኛ ሊያስብለው እንደሚችል ገልጸዋል፡፡ ለሰው ልጆች ሁሉ የሚሠራ የተፈጥሮ ሕግ (Universal law) እንደመኖሩ አንድ ሕግ
        ሲወጣ ሀገሪቷ ካላት ሁኔታ እና በሕጉ ከሚተዳደሩት ማኅበረሰቦች አንፃር መሆን እንዳለበት (Capable of being complied with) በማወቅ ይሁን ባለማወቅ ጠ/ሚኒስትሩ የዘነጉት መሠረታዊ የሕግ አወጣጥ መርሕ ነው፡፡ የሰው ልጅ የመኖር (የሕ.መ.አ.15*) እና ከማንኛውን የአካል አደጋዎች የመጠበቅ (የሕ.መ.አ.16*) በዓለማችን ላይ ሁሉ ዕኩል የሚሠሩ የተፈጥሯያዊ መብቶች አሉት፡፡ ነገር ግን እነዚህን መብቶች ለመጣስ በየሃገራቱ ብቻ አይደለም በየኅብረተሰቡ የተለያዩ አደጋዎች እንደመኖራቸው መብቶቹን ለማስጠበቅ የሚወጡት ሕጎች (እንደ ፀረ ሽብር ሕግ) ከቦታ ቦታ እና ከጊዜ ጊዜ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ የተለያዩ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡ ሕግ ሲረቀቅ የሌላ ሀገሮች ተመሳሳይ ሕግጋት (raison d’etre) መመልከት ተገቢ ቢሆንም በሕጉ የሚተዳደረውን ማኅበረሰብ ጥያቄ መመለስ ዋነኛው አላማው ነው፡፡ (Law must deliberately meet one of the prevalent ‘needs’ of the society) የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ የራሱ የሆነ የአስተሳሰብ እና የአኗኗር ዘይቤ አለው፡፡ ኢትዮጵያ እና አሜሪካ፣ እንግሊዝ ወይም አውሮፓ ዕኩል ለሽብር ጥቃት የተጋለጡ አገሮች አይደሉም፡፡ የኢትዮጵያ የፀረ ሽብር አዋጅም ኢትዮጵያን ከሽብር አደጋዎች ለመጠበቅ እንዲያስችል ተደርጎ መረቀቀ ይኖርበታል እንጂ ከሌላ ሀገር ሕጎች ላይ ቃል በቃል መገልበጥ የለበትም፡፡

        የሰብኣዊ መብት የሚያስከፍል የሽብር ጥቃት በኢትዮጵያ?
        የሰብዓዊ መብት መንግሥት በመልካም ፍቃዱ አይሰጠንም፣ የሰው ልጆች ሆነን ስለተፈጠርን ብቻ የምናገኘውና በቀለም፣ በዘር፣ በሀብት እና በመሳሰሉት ሳንለያይ ያለምንም አድሎ የምንጠቀመው በነጻ በእግዚያብሄር አማሳል ስለተፈጠርን ብቻ የሚኖረን መብት ነው፡፡ መንግሥት መብቱን ባይሰጠንም የመጠበቅ ኃላፊነቱ ግን የሱ፤ የሀገር (የመንግሥት) ኃላፊነት እንጂ የግለሰቡ (የእኛ) ኃላፊነትም አይደለም፡፡ የሰብኣዊ መብትን የመጠበቅ ኃላፊነት የመንግሥት ነው ስንል መብቶቻችን እንዳይገፈፉ በሕግ አግባብ የመጠበቅ፣ መብቶቻችን ሲገፈፉ አግባብ ባለው የፍርድ አካሄድ የማስጠበቅ እና ሕግ የተላለፈውን መቅጣት አለበት እንደ ማለት ነው፡፡ ችግሩ የሰብኣዊ መብቶቻችን የማስጠበቅ ኃላፊነቱ የመንግሥት እንደመሆኑ መብቶቻችንንም ለመጣስ የመጀመሪያው እራሱ መንግሥት ነው፡፡
        ይሄም የሥልጣን ፍቅር ያሰከረው፣ ሥልጣን እና/ወይም መሣሪያ ከሕዝብ የሚበልጥ መስሎ የሚታየው መንግሥት ላይ በብዛት ይታያል፡፡ መንግሥት የሰብኣዊ መብቶች ሊጥስ ከሚችልባቸው አጋጣሚዎች ዋነኛው የኅብረሰቡን ጥቅም (Public interest) ለማስጠበቅ የተወሰኑ ግለሰቦች የሰብኣዊ መብት መጣስ ይኖርባታል በሚል ነው፡፡ የኢትዮጵያው የፀረ ሽብር አዋጁም የብዙኃኑን ሠላም ለማስጠበቅ በሚል የግለሰቦችን ሰብኣዊ መብት እየጣሰ መፈፀም ከጀመረ ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ ነገር ግን የተላየዩ ሰብኣዊ መብቶችን የሚያስጥስ የሽብር አደጋዎች በኢትዮጵያ ውሰጥ የሉም፡፡ ይልቁንም ከአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ፖሊሲ በዊኪሊኪስ ድረ ገጽ አማካኝነት ሾልኮ የወጣው መረጃ (Ref. No. #06ADDISABABA2708) ተፈፀሙ ከተባሉት የሽብር ጥቃቶች በጳጉሜ 1 ቀን 1998 ዓ.ም ተፈፀመ የተባለው ሦስት የቦንብ ጥቃት እራሱ የኢትዮጵያ መንግሥት እንደፈፀማቸው እና ኤርትራንና ኦነግን ተጠያቂ እንዳደረገ ይገልጻል፡፡
        የሌለን ሽብር መፍጠር ይልሃል ይህ ነው፡፡ ስለዚህ የሽብር ጥቃት በማያሰጋበት እና “አሸባሪ” በሌለባት ኢትዮጵያ የተለያዩ የሰብኣዊ መብቶችን እየገፈፉ የፀረ ሽብር አዋጅን ማስፈፀም ከአደጋ የሚጠብቀው ሕዝቡን ወይስ መንግሥትን? የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ በመጀመሪያ የፀረ ሽብር አዋጁ በሕገ መንግሥት ውስጥ ከተካተቱት የሰብኣዊ መብቶች ውስጥ የትኛዎቹን ይጥሳል? የሚለውን መመለስ ያስፈልጋና ጥቂቶቹን እንሆ፡፡
        ከፍተኛ ጥንቃቄ (Due Deligence) ለሰላማዊ ሰልፍ
        የሠላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ሲታሰብ ንብረቶችን ማጥፋት፣ በፖሊስ ላይ ጥቃት መፈፀም እና የመሳሰሉት ወንጀል ከመሆናቸው ባሻገር ሠላማዊ የሚለውን ጽንሰ ሐሳብ ይሸረሽሩታል፡፡ ነገር ግን እነዚህ ተግባራት ወንጀል ቢሆኑም ሽብር አይደሉም፡፡ ይልቁንም “ማንኛውንም ሰው ወይም ቡድን የፖለቲካ፣ ሃይማኖታዊ፣ ወይም የአይዲዎሎጂ ዓላማን ለማራመድ በማሰብ በመንግሥት ላይ ተፅዕኖ ለማሳደር… የሕዝብ አገልግሎት ለከፍተኛ አደጋ ያጋለጠ፣ የያዘ፣ በቁጥጥር ስር ያደረገ፣ ያቋረጠ፣ ወይም ያበላሸ እንደሆነ…” የሽብር ድርጊት እንደተፈፀመ የፀረ ሽብር አዋጁ ይደነግጋል (የፀ.ሽ.አ.አ.3(6)*) ነገር ግን የሕዝብ አገልግሎት ማቋረጥ ኅብረተሰቡን ምን ዓይነት አሳሳቢ አደጋ፤ ለዛውም እንደ ሽብር የሚቆጠር አደጋ ውስጥ እንደሚጥል ግልጽ አይደለም፡፡ ደግሞም የሠላማያዊ ሰልፍ ሲደረግ በመቶዎች፣ በሺሕዎች ወይም በሚሊዮኖች የሚቆጠር ሕዝብ በወጣበት የትራንስፖርት እና የመሳሰሉት የሕዝብ አገልግሎቶች ሊያቋርጥ ይችላል፡፡ የቴሌኮሙኒኪሽን፣ የመብራት ኃይል፣ የውኃና ፍሳሽ ወይም ሌላ የመንግሥት ሠራተኞች ተቃውሞ ኖሯቸው ከሥራ የመቅረት አድማ ቢያደርጉ የሕዝብ አገልግሎት ሊቋረጥ ይችላል፡፡ በዚህ ዓይነት የሠላማዊ ሰልፍ የሚያደርጉት ሆኑ የሥራ መቆም አድማ ያደረጉት የሽብር ድርጊት ፈፀሙ ሊባል ነው? የሠላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብት (የሕ.መ.አ.30(1)*) በተዘዋዋሪ ተገፈፈ ማለት ይሄ ነው፡፡ ለዚህም ነው የተለያዩ ባለሙያዎች እና ድርጅቶች አዋጁ የሽብር ድርጊቶችን ሲያብራራ አደናጋሪ (vague) እና ሰፊ (broad) ስለሆነ መሻሻል ይገባዋል እያሉ የሚጮሁት፡፡ እንደዚህ ዓይነት ሰፊ ክፍተት መተው በፍ/ቤቶች የተለያዩ ትርጉሞች እንዲሰጡት ከማድረጉ ባሻገር የፍትሕ ሚኒስቴር የፈለገውን ሰው እና/ወይም ድርጅት በሽብር ወንጀል ከሶ ችሎት ለመገተር መንገዱን ክፍት ያደረገዋል፡፡
        የመረጃ ነጻነት እንደዋዛ
        ታዋቅው የሕግ ሊቅ እና ፈላስፋ Seneca የሰው ልጅ ከተፈጥፎ ጋር በነጻነት ያለማንም ጣልቃ ገብነት መኖር ይኖርበታል ይላል፡፡
        “Man is a sprit and his ultimate goal is the perfection of his reason in that sprit. Because man is a rational animal, his ideal state is realized when he has fulfilled the purpose for which he was born. And what is it that reason demands of him? Something very easy – that he live in accordance with his own nature.”
        Man is a rational animal! የሰው ልጅ የሚያገናዝብ እንስሳ ነው፡፡ የሚያግናዛበው በአካባቢው ከሚያገኛቸው እውነታዎች አንፃር ነው፡፡ ስለዚህ የሰው ልጅ ስለፈለገው ነገር ማወቅ ይፈልጋል፡፡ ከፈለው መረጃ ላይ፡፡ ያገኘውን መረጃ አገናዝቦ የፈለገው አቋም የመያዝ መብትም አለው፡፡ መንግሥትን ጨምሮ ማንም ሰው ይህንን ዕወቅ ይህንን አትወቅ እንዲለው አይፈልግም፡፡ የማወቅ፣ የማገናዘብ፣ አቋም የመያዝ ብቻ አይደለም አቋሙን ለፈለገው ሰው ያለምንም ፍርሐት የማሳወቅ መብት አለው፡፡ ምክንያቱም ሰው ነውና፡፡
        መንግሥትን ከራሱ አማካሪዎች ይልቅ የተቃዋሚ ፓርቲዎች እና የነጻው ፕሬስ ካልተቸው ሁሌም ትክክል ነኝ ማለቱ አይቀርም፡፡ ምክንያቱም ትክክል መሆን ሥልጣን ላይ ለመቆየት ብቸኛው አማራጭ ነውና፡፡ እንኳን በዚህ ፓርላማው፤ የአንድ ፓርቲ ግለሰቦች በሞሉበት ሀገር እና የጦፈ ክርክር ባለበት ፓርላማም የኅብረተሰቡ እና የፕሬስ ትችት ለመንግሥት የሥራ ወሳኝ ነው፡፡ የፀረ ሽብር አዋጁ አንቀጽ 6 እንዲህ ይለናል፡፡ “…የሽብር ድርጊት እንዲፈፅሙ ወይም ለመፈፀም እንዲዘጋጁ ወይም በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ መንገድ የሚያበረታቸው ወይም በማናቸውም ሌላ ሁኔታ የሚገፋፋቸው እንደሆነ አድርገው ይረዱታል ተብሎ ሊገመት የሚችል መልዕክት ሆን ብሎ ወይም በግዴለሽነት ያተመ ወይም ያሳተመ እንደሆነ….” ሽብርተኝነትን ማበረታታት ስለሆነ ከ10 እስከ 20 ዓመት ያስቀጣል፡፡ የሽብር ድርጊትን በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ የሚያበረታታ መልዕክት ምንድነው? ለሚለው አዋጁ ለሽብር ድርጊት ይገፋፋል ተብሎ የሚገመት መልዕክት ነው ብሎ ይመልሳል፡፡ ማን ነው አንድን መልዕክት ለሽብር ይገፋፋል የሚለውን ግምት የሚሰጠው? መንግሥት ወይስ ማን? ከሽብር ጋር ቀጥታ ግንኙነት ያለው መልዕክት ሲያስተላልፍ ማለት ሲቻል ሽብር ይገፋፋል ተብሎ የሚገመት መልዕክት ነው ብሎ እስከ 20 ዓመት እስር መቅጣት ለምን አስፈለገ? በዚህ ዓይነት አቃቢ ሕግ ሽብርን ያበረታታል ብሎ ካሰበ ማንኛውንም የመንግሥት ትችት የሽብር ድርጊትን አበረታታ ብሎ ሊከሰው ነው ማለት ይሆናል፡፡ ለዛውም የሽብር ድርጊት በሚያወዛግብ ሁኔታ በተብራራበት የሕግ ማዕቀፍ፡፡
        ማበረታታት (Encouragement) ከሚል ማነሳሳት (Incitement) በሚል ጠንካራ እና ሕጋዊ መርሕ መተካት ይቻል ነበር፡፡ ማነሳሳት (Incitement) የወንጀል ሕጋችን ሲያብራራው “ሌላውን ሰው በመጎትጎት፣ ተስፋ በመስጠት፣ በገንዘብ፣ በስጦታ፣ በማስፈራራት ወይም በማናቸውም ሌላ ዘዴ አንድ ወንጀል እንዲያደርግ ያግባባ እንደሆነ…” አነሳሹ የሚቀጣው ወንጀሉ ቢያንስ ተሞክሮ (Attempt) እንደሆነ” (የወ.ሕ.አ.36(1)*) ነው ይላል፡፡ ሌሎች ወንጀሎችን ማነሳሳት እንደዚህ ባለው ጠባብ ሕግ ለዛውም የተባለው ወንጀል ዝግጅትን (Preparation) አልፎ ወንጀሉ ቢያንስ ከተሞከረ ብቻ (Attempt ላይ ከደረሰ) እያስቀጣ ሽብርን ያህል ለኅብረተሰቡ አደገኛ የሆነ ወንጀል “ሽብርን ያበረታታል ተብሎ ስለታሰበ” ብቻ እስከ 20 ዓመት ማስቀጣቱ አግባብ አይደለም፡፡
        ይህ ሲባል የነጻው ፕሬስ የሕትመት መልዕክቶች በሙሉ ሽብርን አይቀሰቅሱም እና አያስቀጡም ማለት አይደለም፡፡ ነገር ግን የሚያስቀጣው መልዕክት ከሚያደርስው የአደጋ አጣዳፊነት (Imminent) እና ወሳኝነት (Neccessity) አንፃር መመርመር ይኖርበታል፡፡ አደገኛ መልዕክትን መተርጎም ለፍ/ቤቶች ብቻ ሳይሆን ጠበብ ባለ የሕግ ማዕቀፍ መካተቱ ለሀገሪቷ የሚጠቅሙትን መልዕክቶች በተቃራኒው አደገኛ ናቸው ብሎ ከመቅጣት ይሰውራልና ቢታሰብበት አይከፋም፡፡ ከዓለማችን የተሰባሰቡ የሕግ ሊቆች እና ከተባበሩት መንግሥታት የተሾሙ ባለሙያዎች በተገኙበት በተረቀቀው የጁሃንስፐርጉ መርሕ ላይ ለኅብረተሰቡ አደጋ የሚያጋልጡ መልዕክቶች ማስቀጣት ያለባቸው ሦስት ሁኔታዎችን (Pre conditions) ሲያሟሉ እንደሆነ ይገልጻል፡፡ “መልዕክቱ አፋጣኝ አደጋን ለማድረስ የተሳበ ከሆነ (Immenint)፣ መልዕክቱ አደጋውን ማድረሱ እርግጥ ከኖነ (Probable) እና በመልዕክቱ እና በሚደርስው አደጋ መካከል የተቀራረበ ግንኙነት ካለው (Cause and Effect)” ናቸው፡፡ የፀረ ሽብር አዋጁ ግን እነዚህን መዘርዝሮች ማሟላት አይደለም አንዱንም አያካትትም፡፡ እነ ውብሸት ታዬ፣ እስክንድር ነጋ፣ ርዕዮት ዓለሙ እና የመሳሰሉት ነገ ጠባ ሰለቸኝ ደከመኝ ሳይሉ ለኅብረተሰቡ መረጃን በማድረስ፣ በመንግሥት ላይ ትችት በማቅረብ የሚሠሩ ታታሪ ጋዜጠኞች ናቸው ብለው የዓለም ዓቀፍ ድርጅቶች ሲሸልሟቸው የደከሙላት ኢትዮጵያ ግን የሽብር ድርጊትን አበረታታቹኋል ብላ ማረሚያ ቤት የላከቻቸው፡፡ አራሚዎቹን ወደ ማረሚያ፡፡ ይህ አካሄድ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 29 የተገለፀውን የአመለካከት እና ሐሳብን በነፃ የመያዝና የመግለጽ መብት ከመጣሱ ባሻገር ኅብረተሰቡ በፍትሕ ስርዓቱ ላይ ያለውን አመኔታ እንዲያጣ ምክንያት ሆኗል፡፡
        በሃያማኖት ጣልቃ ገብነትን መቃወም እንደ ሽብር
        መንግሥት ሕዝቡን ለመቆጣጠር እና ያለምንም ስጋት ሥልጣን ላይ ለመቆየት ካሉት አማራጮች ውስጥ ዋነኛው በሃይማኖት ውስጥ ጣልቃ መግባት ነው፡፡ ምክንያቱም የሰው ልጅ በሃይማኖቱ አይደራደርም፣ የሃይማኖች አባቶች ትክክል ነው ያሉት የእግዚአብሔር/የአላህ ቃል ነውና ለቃሉ መገዛት ግድ ይሆናል፡፡ ፈጣሪ የሾመውን ፈጣሪ ያውርደው እንዲሉ፡፡ በጣልያን በ15ኛው ክፍለ ዘመን የተወለደው የሕግ ሰው Nicolo Machiavelli ለመሳፍንት መመሪያ በጻፈው The Prince በተሰኘው መጽሐፉ መንግሥት በሃይማኖት ሕዝቡን እንዴት መቆጣጠር እንደሚችል ሲገልጽ፤
        “…touching which all difficulties are prior to getting possession, because they are acquired either by capacity or good fortune, and they can be held without either; for they are sustained by the ancient ordinances of religion, which are so allpowerful,èandèofèsuchèaècharacterè thatè theèprincipalitiesèmayèbeè held no matter how their princes behave and live.” ይላል፡፡
        የኢትዮጵያ መንግሥትም በችሎታ (Capacity) ወይም በተወዳጅነት (good fortune) ኅብረተሰቡን መቆጣጠር ስለማይችል፤ ከፋፍለህ ግዛ (Divide and rule) ከሚለው የማካቬሊ መርሕ በተጨማሪ በተለያዩ ሃይማኖቶች ውስጥ ጣልቃ መግባቱ የአደባባይ ሚስጥር ከሆነ ሰንብቷል፡፡ ነገር ግን የሙስሊሙ ኅብረተሰብ በሕገ መንግሥቱ መሠረት ሃይማኖት እና መንግሥት የተለያዩ (የ.ሕ.መ.አ.11*) መሆን አለባቸው በሚል ሰፊ ተቃውሞ ለማድረግ በቅርቡ ወኔውን አግኝቷል፡፡ መንግሥት በሃይማኖታችን ጣልቃ እየገባ ነው፣ የአሕባሽ አስተምህሮት ማስፋፋት ይቁም በሚል በመንግሥት ላይ በኢትዮጵያ ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ሠላማዊ የሆነ ተቃውሞ ሲያደርጉ ተስተውሏል፡፡ ነገር ግን መንግሥት በተግላቢሽ የሃይማኖታዊ መንግሥት የማቋቋም ድብቅ አጀንዳ እንጂ ሕገ መንግሥታዊ ጥያቄ የላቸውም በሚል ከ500,000 በላይ የሙስሊሙን ኅብረተሰብ የአዎንታ ፊርማ አግኝቶ የተቋቋመውን የኮሚቴ አባላት በፀረ ሽብር አዋጁ ከስሶ ጉዳዩ በፍ/ቤት በመታየት ላይ ያገኛል፡፡ የክርክሩ ውጤት (ውሳኔ) የሚተላለፈው በገለልተኛ ፍ/ቤት ይሁን በሕግ አስፈፃሚው አካል ቀጭን ትዕዛዝ (የፍ/ቤቶችን ገለልተኝነት ሳልገጽ ማለፍ አግባብ ስለማይሆን) ግልጽ ባይሆንም ከሕጉ አንጻር ነጻ የመውጣት ዕድል ቢኖራቸውም ካለው ነባራዊ ሁኔታ እና ከበፊት ተሞክሮዎች ጥፋተኛ ሊባሉ የሚችሉበት አጋጣሚ የሰፋ ነው፡፡
        ለአደጋ የተጋረጠው የፍርድ አካሄድ (Due process of law)
        የፀረ ሽብር ሕጉ ለመስፈጸም ማስረጃ ለማሰብሰብ በሚደረጉ ተግባሮች፣ በፍርድ ቤት በሚኖረው አካሄድ፣ እና በማረፊያ ቤቶች የተከሳሾች እና ከጉዳዩ ተያያዥነት አላቸው ብሎ ፖሊስ የጠረጠራቸውን ግለሰቦች የሰብዓዊ መብት እንደሚጣስ ልብ ይሏል፡፡
        የወንጀል ተከሳሾች “ተገቢ በሆነ አጭር ጊዜ ውስጥ በመደበኛ ፍ/ቤት….የመሰማት” ሕገ መንግሥታዊ መብት አላቸው (የሕ.መ.አ.20(1)*)፡፡ ነገር ግን በፀረ ሽብር አዋጁ የሚከሰሱ ተጠርጣሪዎች ከወንጀል ስነ ስርዓት ሕጉ 14 ቀን በመጨመር የጊዜ ቀጠሮ ትንሹ 28 ቀን እንደሆን ከመደንጉ ባሻገር ይህ ጊዜ እስከ 4 ወራት ሊዘልቅ እንደሚችል ይደነግጋል (የፀ.ሽ.ሕ.አ. 20(3)*)፡፡
        ሌላው የፀረ ሽብር አዋጁ የሚጥሰው የግለሰብን የነጻንት መብት ሲሆን (Right to privacy) “በሽብርተኝነት የተጠረጠረን ሰው የስልክ፣ ፋክስ፣ የሬድዮ፣ የኤሊክትሮኒክስ፣ የፖስታ እና የመሳሰሉትን ግንኙነቶች ለመጥለፍ ወይም ለመከታተል…. ጠለፋውን ለማስፈፀም ወደ ማንኛውም ቤት ውስጥ በሚስጥር የመግባት… “መብትን ለፖሊስ እና ለደኅንነት መብቱን ይሰጣል (የፀ.ሽ.አ.አ.14(1)*)፡፡ በዚህ የተገኙትንም ማስረጃዎች በሚስጥር መጠበቅ እንዳለባቸውት ይደነግጋል (የፀ.ሽ.አ.አ.14(2)*)፡፡ ይህም የግል ሕይወት የመከበር እና የመጠበቅ የሰብኣዊ መብትን (የሕ.መ.አ.26) በግልጽ ከመጣሱ ባሻገር የተያዙት ማስረጃዎች በሚስጥር ሲጠበቁ አይታዩም፡፡ አኬልማዳ፣ ጀሀዳዊ ሃረካት እና የመሳሰሉት የኢቲቪ ዶክመንተሬዎች ማስረጃዎቹ በሚስጥር ከመያዝ ይልቅ ቀድሞ ተከሳሾችን ባደባባይ ለመወንጀል ጥቅም ላይ እንደዋሉ ያረጋግጣል፡፡ ይህም ወደ ሚቀጥለው የሰብኣዊ መብት ጥሰት ያሸጋግረናል፡፡
        ማንኛውም ተከሳሽ በፍርድ ቤት ቀርቦ እና ማስረጃ ተሰምቶ ጥፋተኛ እስከሚባል እንደ ነጻ ግለሰብ መቆጠር (presumption of innocence until proven guilt) እንደሚኖርበት ሕገ መንግሥታችን ቢደነግግም (የሕ.መ.አ.20(3)*) በቴሌቪዥን ዶክመንተሪዎች እና የተለያዩ የመንግሥት ኃላፊዎች ጭምር ተከሳሾች የሽብር ድርጊትን በመፈፀም ዙሪያ በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ ተሳትፈዋል በሚል መግለጫዎች ሲሰጡ ማየት የተለመደ ሆኗል፡፡ የሙስሊሞች ጉዳይ ‹‹መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ›› ጠበቃ የሆኑት አቶ ተማም አባቡልጋ እና የዓለም አቀፍ ሕግ ባለሙያው ዶ/ር ያዕቆብ የጅሃዳዊ ሃረካት በሚለው የዶክመንተሪ ፊልም የደንበኞቻችን ስም ጠፍቷል በሚል የ8 ሚሊዮን ብር የካሳ ክፍያን በፍ/ቤት ለመጠየቅ የፍትሐ ብሐር ክስ እንደጀመሩ በቅርቡ ሰምተናል፡፡ ክርክሩ ጠቅላይ ሚኒስቴሩን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊዎችን እንደተከሳሽ ማካተቱ የሕግ የበላይነትን ያሳየናልና በርቱ ብያለሁ፡፡
        የሚስጥሪያዊነት ስነ ምግባር በሽብር ምርመራ…
        የተለያዩ ባለሙያዎች ከሥራ ዘርፋቸው አንፃር የሚጠበቁባቸው የሥነ ምግባር ኃላፊነቶች አሉ፡፡ ከነዚህ ውስጥ አንዱ እና ዋነኛው ምስጥራዊነት (Confidentiality) ነው፡፡ ነገር ግን አዋጁ የባለሙያዎቹን ሥነ-ምግባር ወደ ጎን በመተው፤ ለሽብር እንኳን የባለሙያ ሥነ-ምግባር የሰብኣዊ መብትም ይጣሳል ይለናል፡፡ አዋጁ በማስረጃ አሰባሰብ አካሄዱ “…[ፖሊስ] ለምርመራው የሚረዳው መሆኑን በሚገባ የሚያምንበት መረጃ ወይም ማስረጃ ከማናቸውም የመንግሥት መሥሪያ ቤት፣ ባለሥልጣናት፣ ባንክ፣ የግል ድርጅት ወይም ግለሰብ እንዲሰጠው ሊጠይቅ ይችላል፡፡ መረጃ ወይም ማስረጃ የተጠየቀው ወገን መረጃውን ወይም ማስረጃውን የመስጠት ግዴታ አለበት” ይላል (የ.ፀ.ሽ.አ.አ.22*)፡፡ በዚህም ምክንያት ጠበቃ ደንበኛው የሕግ ወኪሌ ብሎ ያማከረውን፣ ሐኪም ታማማሚው ለሕክምና እንዲረዳው ብሎ የተናገረውን ሚስጥር ብቻ ሳይሆን የንስሐ አባት ይፀዩልኝ ዘንድ ብሎ የተነገራቸውን ጉድ ጭምር ለደኅንነት ወይም ለፖሊስ አንድም ሳይደብቁ የመናገር ግዴታ ይጥላባቸዋል፡፡ የፀረ ሽብር አዋጁ፡፡
        ለኢ-ፍትሐዊ ሕግ አንገዛም!!!
        በመግቢያዬ ላይ እንደገለጽኩት ዶ/ር ማርቲን ሉተር ኪንግ ትክክለኛ (Right) እና ፍትሐዊ (Just) ያልሆነ ሕግ ከመጀመሪያው አስገዳጅነት የለውም ይለናል፡፡ ሕብረተሰቡም ይህንን ሕግ የመቃወም ሕጋዊ ብቻ አይደለም የሞራልም ተጠያቂነት አለበት፡፡ በአንድ አገር ውስጥ ሕግ ሲወጣ የኅብረሰቡን አመለካከት እና ጥያቄ ግምት ውስጥ ካልከተተ ሕጉ የመንግሥት እንጂ የሕዝብ አይሆንም፡፡
        የመንግሥት ሕግ ደግሞ በጀርመኑ ናትዚ ጊዜ ያለውን ከፍተኛ ተግዳሮት አይተናል፡፡ የጀርመን ፕሮፌሰር Fuller ኢፍትሐዊ ውሳኔዎች የሚፈጠሩት በፍርድ ቤቶች ችግር ሳይሆን በዋነኛነት በሕግ አውጪዎቹ ድክመት እንደሆነ ይገልጻሉ፡፡ ሕጎች ይላሉ ፕሮፌሰር ፉለር Morality of duty ብቻ ሳይሆን Morality of Aspiration ያስፈልጋቸዋል፡፡ ይህም ማለት አንድ ሕግ በኅብረሰቡ ዘንድ ሊያስተዳድረን ይገባል የሚል እምነት ከሌላቸው በግዴታ ብቻ በሕጉ መገዛታቸው በቂ አይደለም፡፡ በሁለቱ መካከል ያለውን ልዩነት እና አንዱ ከሌላው ጋር ያላቸውን ቁርኝትና እንዲህ ብሎ ገልጾታል፡፡
        “The morality of aspiration…is the morality of the Good Life, of excellence, of the fullest realization of human powers…Where the morality of aspiration starts at the top of human achievement, the morality of duty starts at the bottom. It lays down the basic rules without which an ordered society is impossible, or without which an ordered society directed toward certain specific goals must fail of its mark.”
        ኢትዮጵያ ለሽብር ጥቃት ያን ያህል የሚያሰጋ ደረጃ ላይ እንደሌለች ሁላችንም የምናውቀው ኩነት ነው፡፡ በሱማሊያ ጦርነት መሳተፏ ከአልሻባብ ለሚሰነዘር ጥቃት ያጋልጣታል የሚል ስጋት ቢኖርም በአሁኑ ጊዜ ግን አሸባሪ ተብለው እየተፈረጁ የምናየው የሀገር ውስጥ ግለሰቦችን እና/ወይም ቡድኖችን እንጂ ከሱማሊያ የሚመጡትን አይደለም፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ደግሞ ምንም ጭቆና ቢደርስበት ከነበረው የረዥም ጊዜ የአስተሳሰብ ደረጃ (Moral standard) በዓለም አቀፍ ደረጃ የሽብር ድርጊት ተብለው የሚወሰዱትን እንደ አጥፍቶ ማጥፋት፣ የንፁሐንን ዜጋ ሕይወት ለመደራደሪያነት የማቅረብ ዓይነት ተግባራትን እንዳማይፈፅም እሙን ነው፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ በተራበበት ጊዜ እንኳን አመፅ/ሽብር አላስነሳም፡፡ ስለዚህ ለሽብር ጥቃት ርቃ የምት&#487

        የግብፅ የአስቸኳይ ሁኔታ አገልግሎት ኀላፊ ሙሐመድ ሱልጣን እንዳስታወቁት ቁጥራቸው ከ51 የማያንስ ሰዎች ሲገደሉ፤ 435 ቆስለዋል። የአዉሮጳ ኅብረት ድርጊቱን አዉግዟል።

        በዓለማችን የሕፃናትን ህይወት ስለሚቀጥፉ በሽታዎች ሲወሳ ብዙዎች ቶሎ የሚያስቧቸዉ HIV AIDS አለያም የወባ በሽታዎችን ነዉ። አንዳንድ ጥናቶች የተዘነጉት ችግሮች ይሏቸዋል ተቅማጥና የሳንባ ምችን፤ እነዚህ ሁለት በሽታዎች የሚያደርሱት ጉዳት አሁንም ባለመገታቱ የህጻናትን ህይወት ለመታደግ ከፍተኛ ትኩረት እንደሚያሻ እየተጠቀሰ ነዉ።

        ከ12 ዓመታት ጥበቃ በኋላ ባለፈው ሳምንት ሰኞ የቀድሞዋ የዩጎዝላቪያ ግዛት ክሮኤሽያ 28 ተኛዋ የአውሮፓ ህብረት አባል ለመሆን በቃታለች ። የአውሮፓ ህብረት እንዳለው ክሮኤሽያ ማሻሻያዎች እንድታደርግ የተሰጧትን የቤት ሥራዎች አሟልታለች ።

        ሐምሌ ፪( ሁለት )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት ምንጮች እንደገለጡት ካለፈው አርብ ጀምሮ ከማንነት ጥያቄ ጋር በተያያዘ በተፈጠረው ተቃውሞ ከ470 ያላናሱ ሰዎች እስከ ትናንት ድረስ ተይዘው የታሰሩ ሲሆን፣ ተቃውሞውን አስተባብረዋል ከተባሉት መካከል በዋና ከተማዋ ሰላም በር የሚኖሩ ከ13 በላይ የአገር ሽማግሌዎችና ታዋቂ ሰዎች ተመርጠው ወደ አርባ ምንጭ እስር ቤት መወሰዳቸው ታውቋል። ወደ  አርባምንጭ እስር …

        ሐምሌ ፪( ሁለት )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአዲስአበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ እንደሚሆኑ አስቀድሞ ሲነገርላቸው የነበሩት የቀድሞ የትራንስፖርት ሚኒስትሩ አቶ ድሪባ ኩማ የአስተዳደሩን ኃላፊነታቸውን ከአቶ ኩማ እጅ ተረክበዋል፡፡ በተለይ ሪፖርተር ጋዜጣ የምክትል ከንቲባነት ሥልጣን እንደሚይዙ የተነበየላቸው ወ/ሮ አዜብ መስፍን እንደተገመተው ወደስልጣኑ ያልመጡ ሲሆን በምክትል ከንቲባነት የቀድሞ ምክትል ከንቲባ አቶ አባተ ስጦታው ተሹመዋል፡፡ ዛሬ ማለዳ በአዲስ …

        ሐምሌ ፪( ሁለት )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አንድነት ፓርቲው ያወጣውን ህዝባዊ ንቅናቄ ተከትሎ፣ ወረቀቶችን በትነዋል የተባሉ ሰዎች በየቦታው እየታሰሩ በመሆኑ መንግስት ድርጊቱን እንዲያስቆምና የታሰሩትም እንዲፈቱ ጠይቋል። በሰሜን ጎንደር ዞን በምዕራብ አርማጭሆ አብርሃ ጅራ ከተማ አቶ አለልኝ አባይ፣ አቶ እንግዳው ዋኘው፣ አቶ አብርሃም ልጃለምና አቶ አንጋው ተገኝ ፣ በጎንደር ከተማ አቶ ማሩ አሻገረ  አቶ አምደማሪያም …

        ሐምሌ ፪( ሁለት )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አራጣ በማደበር ተከስሰው 25 ዓመት የተፈረደባቸው አየለ ደበላ በቅጽል ስማቸው አይ ኤም ኤፍ የቀብር ስነስርአት በቅድስት ስላሴ ካቴደራል በከፍተኛ ስነስርዓት ተፈጽሙዋል፡፡ አቶ አየለ የባንክን ሥራ ተክተው በመሥራት፣ አራጣ በማበደር፣ ግብር ባለመክፈልና በሌሎችም ክሶች ጥፋተኛ ተብለው በከፍተኛው ፍርድ ቤት በ22 ዓመታት እስርና በባንክ ያላቸው 12 ሚሊዮን ብር እንዲወረስ …

        በደቡብ ክልላዊ መንግስት ጋሞጎፋ ዞን የምትገኘው ቁጫ ወረዳ ሰላም በር ከተማና አካባቢዋ ላለፉት ሁለት ቀናት በመንግስት የጸጥታ ሃይሎች ስትታመስ መቆየቷን የፍኖተ ነጻነት ምንጮች ከስፋራው አጋልጠዋል፡፡ እንደ ምንጮቻችን ዘገባ በቁጫ ወረዳ የሚገኙ ከ200.000የሚልቁ ነዋሪዎች ያለ ፍላጎታቸው በጋሞጎፋ እንዲጠቃለሉ መደረጋቸውን ሲቃወሙ ቆይተዋል፡፡‹‹እኛ ጋሞ ወይም ወላይታ አይደለንም››በማለት የማንነት ጥያቄ ያነሱት ቁጫዎች የራሳችን ቋንቋና ከጋሞም ሆነ ከወላይታ የሚለየን ባህል […]

        የአንድነት ፓርቲ የህዝባዊ ንቅናቄ ግብረሀይል፣ የሶሻል ሚዲያ ኮሚቴ አባላት የነፃነት ታጋዮቹን አንዱአለም አራጌንና ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን ጎበኙ፡፡ የሶሻል ሚዲያ አባላቱ ትላንት በቃሊቲ እስር ቤት ባደረጉት ቆይታ የአንዱአለም እና የእስክንድር መንፈሳዊ ጥንካሬ እንዳስደሰታቸው ለፍኖተ ነፃነት ተናግረዋል፡፡ በጉብኝቱ ወቅት የነፃነት ታጋዮቹ አንዱአለም አራጌና ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ አንድነት ፓርቲ የጀመረውን ህዝባዊ ንቅናቄ አበረታች መሆኑን አስምረው ሁሉም ኢትዮጵያዊ በንቅናቄው […]

        የአጣሪ ኮሚቴው ሪፖርት እስኪፈጸም ድረስ ለፈተና ላለመቀመጥ ወስነዋል የኮሌጁ ቦርድ በአጣሪ ኮሚቴው ሪፖርት ላይ ከቋሚ ሲኖዶሱ ጋራ እየተወያየ ነው ‹‹ቦርዱ ለአቡነ ጢሞቴዎስ ተጽዕኖ ያደረና እርሳቸው የሚሉትን ብቻ የሚሰማ ነው፤ በችግራችን ጠይቆንም ይኹን ሰብስቦን አያውቅም፡፡›› /ደቀ መዛሙርቱ/