የአንድነት ፓርቲ አቤቱታ

የፓርቲዉ አባላትና ደጋፊዎች የታሠሩትም ፊርማ ለማሰባሰብ፥ ሠልፍና ስብሰባዉን ለማደራጀት ሲንቀሳቀሱ ነዉ።ከሰኔ ሃያ-ሁለት እስከ ሰላሳ በነበረዉ አንድ ሳምንት ብቻ ዘጠኝ የፓርቲዉ አባላት በፀጥታ አስከባሪዎች ታስረዋል።አብዛኞቹ የታሠሩት ሰሜን ጎንደር ነዉ።አንዱ ታስረዉ ተለቀዋል።አስራ-አንደኛዉ ከግድያ ሙከራ አምልጠዋል።