ሃብትና ስልጣን አስክሮአቸው፣ በዚህች ደሃ ሃገርና ሕዝብ ላይ ተፈናጠው ሁለት አስርተ አመታት ያስቆጠሩ አምባገነን መሪዎቻችን የሃገርና የሕዝበ ፍቅር አጥተው በምዝበራ ለመክበር ብቻ፣ ሕዝብንም በሃገሩ በሰላም የመኖር መብቱን ቀምተው ተደላድለው ለመቀመጥ ዘንድሮም እንደ አምናው በሽብር ስም በጫኑብን የአፈና መረብ ሸብበው ሕዝቡን ከዳር እዳር ማስጨነቃቸው ሳያንስ አሁን ደግሞ ለዚህ እኩይ ተልኳቸው ላሰለጠኑዋቸው የስርዓቱ ሰዎች (ደህንነቶች) በዴሞክራሲና በመልካም […]

ዛሬ ሐምሌ 8 ቀን 2005 ዓ.ም መንግስት የአንድነት ፓርቲ የአዲስ አበባ ዞን የወረዳ አመራሮችንና አባላትን በዘመቻ ማሰር ጀምሯል፡፡ እስከአሁኗ ሰዓትም 42 የሚሆኑ የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ አባላት በፖሊሲ ቁጥጥር ስር ይገኛሉ፡፡ የፍኖተ ነፃነት ጋዜጠኞች ተዘዋውረው እንደዘገቡት 42 የሚሆኑ የአንድነት ፓርቲ አባላት በፖሊስ እንዲታሰሩ ተደርጓል፡፡ የአንድነት ፓርቲ በአዲስ አበባ እያሰራጨ ያለውን ህጋዊ በራሪ ወረቀት ለህዝብ በማደላቸው […]

የኮሌጁ የቀን መርሐ ግብር እስከ መስከረም አጋማሽ ፳፻፮ ዓ.ም ድረስ እንዲቋረጥ ተወስኗል ደቀ መዛሙርቱ በቀጣይ ርምጃዎቻቸው ላይ እየመከሩ ነው የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ደቀ መዛሙርት ኮሌጁን ‹‹በሰላማዊ መንገድ›› ለቀው እንዲወጡ የፓትርያሪኩ ልዩ ጽ/ቤት በይፋ አዘዘ፡፡ ልዩ ጽ/ቤቱ ዛሬ፣ ሐምሌ ፰ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም ከቀትር በኋላ በኮሌጁ የለጠፈው ማስታወቂያ፣ የኮሌጁ ደቀ መዛሙርት ማስታወቂያው ከወጣበት ከዛሬ ሐምሌ …

የተቃዉሞ ሠልፍ መደረጉን፥ አንዳዶች ገዢዉ ፓርቲ ላለፉት ስምንት ዓመታት ይከተለዉ ከነበረዉ መርኹ የመለሳለሱ ምልክት ይሉታል።ተቃዋሚ ፓርቲዎች የመጠናከራቸዉ ማሳያ ነዉ-ባዮችም አሉ። ሌሎች ደግሞ ቢያንስ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን የሚደግፈዉ ሕዝብ ተቃዉሞዉን ለማሰማት ዶክተር ነጋሶ እንዳሉት የመቁረጡ አብነት ነዉ።

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትኅ ፓርቲ ፤«የሚሊዮኖች ድምፅ ለነጻነት »በሚል መሪ ቃል ለ 3 ወራት ያወጣውን የህዝብ ንቅናቄ እቅድ ትናንት በጎንደርና ደሴ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፍ እንዲከናወን በማድረግ ጀመረ። ከትናንቱ ሰልፍ በፊት ፣ ህዝብ ለሰልፍ እንዲወጣ

ሐምሌ ፰( ስምንት )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አርብ ፣ ሀምሌ 6 2005 ዓም በእነ አቶ ተሻለ ኮርኔ መዝገብ የተከሰሱ 69 የኦሮሞ ተወላጆች ፍርድ ቤት መቅረብ ሲገባቸው፣ ፍርድ ቤት የሚወስዳቸው ፖሊስ ያጣሉ። በቅጽል ስሙ ሻእቢያ እየተባለ የሚጠራውን የእስር ቤቱን ሀላፊ ሲጠይቁት ቀጠሮአቸው ለ4 ወር መራዘሙን ይነግራቸዋል። እስረኞቹም ” ከ2 አመታት በላይ የላፍትህ ታስረን በመጨረሻ …

ሐምሌ ፰( ስምንት )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፓርቲው በደሴና እና በጎንደር የተሳኩ የተቃውሞ ሰልፎችን ባካሄደ ማግስት ከ30 በላይ አባሎቹ በዋና ከተማዋ የተቃውሞ ፊርማ ሲያሰባስቡ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለዋል። ባለፉት ሳምንታትትም በተመሳሳይ መንገድ የታሰሩ እና የፍርድ ቤት ውሳኔ በመጠባበቅ ላይ ያሉ አባላት አሉ። አንድነት ፓርቲ ለ3 ወራት በሚቆየው የተቃውሞ እንቅስቃሴ  በዋና ዋና ከተሞች ሰላማዊ ሰልፎችን …

ሐምሌ ፰( ስምንት )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎች ሕዝበ ክርስቲያኑ ከጎናቸው እንዲቆም በመጠየቅ ትናንት በአመታዊ የሥላሴ ክብረ በዓል ላይ  መፈክሮችን ሲያሰሙ ውለዋል። ተማሪዎቹ ሲያሰሙዋቸው ከነበሩት መፈክሮች መካከል፦የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅን መዝጋት ታሪክን ማጥፋት/ማበላሸት ነው!፣የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ችግራችንን ይመልከት!፣ሙስናንና ኑፋቄን የሚያደቅ ክንድ አለን!የምንማረው በምእመናን ብር ነው፡፡ ሌቦች ሆይ፣ እጃችኹ ይሰብሰብ! …

ሐምሌ ፰( ስምንት )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፌዴራል የሥነምግባርና የጸረ ሙስና ኮምሽን በቅርቡ ባካሄደው የአሰራር ሥርዓት ጥናት በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የግዥ አፈፃፀም ለሙስና እና ብልሹ አሠራር የተጋለጠ ነው ብሎአል፡፡ በፖሊስ ኮምሽኑ የተጠና የጠቀሜታ ዝርዝር /ስፔስፊኬሽን/ አዘገጃጀት አሰራር አለመኖር፣ ግዥዎችን በዕቅድና በፕሮግራም አለመፈፀም፣ በጀት መኖሩ ሳይረጋገጥ የግዥ ሂደቶችንማከናወን፣ በግዥ መመሪያው ከተቀመጠው የገንዘብ መጠን በላይ ግዥ …

በነገው ዕለት በመንበረ ፓትርያሪኩ በሚያካሂዱት ከፍተኛ የተቃውሞ ትዕይንት ምእመኑ ከጎናቸው እንዲሰለፍ ጥሪያቸውን አቅርበዋል አቡነ ጢሞቴዎስ ደቀ መዛሙርቱን በፖሊቲከኝነት መወንጀል ጀምረዋል የተማሪዎች መማክርት የኮሌጁን አስተዳደር በሕግ ለመጠየቅ እየተዘጋጀ ነው ምእመናን ቤተ ክርስቲያን ከመሳለምና ገንዘብ ከመስጠት/ከመመጽወት ባሻገር ስለ ቤተ ክርስቲያናቸው ጉዳይ በመጠየቅ ቀጥተኛ ተሳታፊ መኾን እንደሚገባቸው የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ደቀ መዛሙርት አሳሰቡ፡፡ ደቀ መዛሙርቱ ማሳሰቢያውን ያስተላለፉት፣ …

የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅን መዝጋት ታሪክን ማጥፋት/ማበላሸት ነው! የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ችግራችንን ይመልከት! ልጆቹን የማይጠይቅ አባት አለን? ሙስናንና ኑፋቄን የሚያደቅ ክንድ አለን! የምንማረው በምእመናን ብር ነው፡፡ ሌቦች ሆይ፣ እጃችኹ ይሰብሰብ! ጢሞቴዎስ ሆይ፣ አደራህን ጠብቅ፡፡ (፩ኛጢሞ. ፬÷፳) ችግራችንን የሚሰማንና መፍትሔ የሚሰጠን አባት ዐጣን! የቅ/ሲኖዶሱ አባላት ትኩረት ይስጡን! ሙስናን በቃል ሳይኾን በተግባር እንዋጋ! ተማሪዎች ሙስናን በመዋጋታቸው […]

ሐምሌ 7 ቀን 2005 ዓ.ም የጎንደር ከተማ የገዢዉ ፓርቲ ካድሬዎችን ታላቅ አሳፋሪ አፈና ጥሶ በመሄድ ድምጹ በታላቅ ጀግንነት አሳምቷል። የአንድነት ድህረ ገጽ ላይ የወጣ በኦዶዮ የታጀበ ዝርዝር ሸገባ እንደ እንደሚከተለዉ አቅርበናል። እዚህ ይጫኑ !

አንድ ቢሊዮን ገደማ ህዝብ ባለው ክፍለ ዓለም 54 አባል ሃገራትን ያቀፈውና ዘንድሮ 50 ኛ ዓመቱን በማክበር ላይ የሚገኘው የአፍሪቃ ኅብረት በየጊዜው በሚከሠቱ የአህጉሩ ችግሮች መፈተኑ አልቀረም ። የኅብረቱ ኮሚሽን ሊቀመንበር ወይዘሮ እንኮሳዛና ድላማኒ

ክልሉ የፍትሕና ጸጥታ ዘርፍ እንዲሁም የፖሊስ ሓላፊዎች ለሁከት ፈጣሪዎቹ ወግነዋል

ደቀ መዛሙርቱ ለሦስተኛ ተከታታይ ቀን የኮሌጁን የምግብ ቤት አገልግሎት ተከልክለዋል የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ደቀ መዛሙርቱ ወደ ክረምት ዕረፍት ከመሄዳቸው በፊት የማጠቃለያ ፈተና እንዲወስዱና ተመራቂዎቹ እንዲሸኙ ጥረት እያደረገ ነው፤ በፓትርያሪኩ የመወሰን አቅም ላይ ጥርጣሬ የገባቸው የሚኒስቴሩ ሓላፊዎች ልዩ ጽ/ቤቱ ደቀ መዛሙርቱን በኀይል ከኮሌጁ ለማስወጣት ያቀረበውን የድጋፍ ጥያቄ ውድቅ ባደረጉበት አቋማቸው ጸንተዋል ፓትርያሪኩ በሚይዟቸው አቋሞች ረዳት ሊቀ ጳጳሱ …

የነገው አበባ ለምን ለፌደራል ፖሊስ ይሰጣል? ዳዊት ሰለሞን (ፍኖት ዘጋቢ) ሐምሌ 6 ቀን 2005 ዓ.ም አበባ የሰው ልጆች በአንድ ድምጽ «ፍቅራችንን ወክልልን» በማለት የመረጡት ይመስል የፍቅርን አደራ ተሸክሟል፡፡ከሶስተኛው አለም እስከ አንደኛው የሚገኙ የአዳም ልጆች «አበባን» የፍቅር ስጦታ በማድረግ ለሚወዱት ይቸሩታል፡፡የሚወዱት ሲሞትባቸውም ፍቅራቸውን ለሟቹ ለመግለጽ አስከሬኑ ላይ አበባ ያኖሩለታል፡፡ ወደ ደሴና ጎንደር እንምጣ፣ ነገ ከሌላው ጊዜ […]

ሐምሌ 6 ቀን 2005 ዓ.ም “ህገ መንግስት ተጥሷል !” ካልክ ድምጽህን በሰላማዊ ተቃውሞ አሰማ ! ይድረስ ትናንተም ሆነ ዛሬ ግፍ በነገሰባት ምድር፣ ኑሮን በመከራ ለምትገፋው ወገኔ ! ይድረስ መልካም አስተዳደር ጠፍቶ በደል ለተጫነብህ ፣ ፍትህ ርትዕ ተዛብቶ የአስተዳደር ሚዛኑ ኑሮህን ላጨለመው ወገኔ ! ይድረስ ከዲስኩር ባላለፈ “የእድገት ስላጣኔ መንገድ እየተጓዝክ ነው ” ለሚሉህ ፣ ይድረስ […]

ሐምሌ 6 ቀን 2005 ዓ.ም በደሴ አካባቢ ከሚገኙ ከተሞች(ከወረባቡና ሐይቅ)፣ በነገው የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ለመገኘት ወደ ከተማይቱ ለመምጣት ትራንስፖርት ያስፈልጋቸው የነበሩ ዜጎች፣ በከተማው አስተዳደር ስውር ትዕዛዝ መሰረት፣ ከዛሬ ምሽት ጀምሮ የትራንስፖርት መኪኖቹ ከአገልግሎት ውጪ እንዲሆኑ መታዘዛቸውን የየአካባቢዎቹ ነዋሪዎች ለሰልፉ አዘጋጆች በመደወል እየገለጹ ነው፡፡ ሁኔታው ያሳዘናቸው ሰዎች በቻሉት መንገድ ሁሉ ወደ ሰልፉ […]

ሐምሌ 6 ቀን 2005 ዓ.ም “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” የሚል መሪ ቃል በማንገብ ዕሁድ በሚካሄደዉ ህዝባዊ የተቃዉሞ ሰልፍ ላይ ሁሉም ተሳታፊ የሚከተሉትን ተግባራት ተግባራዊ ማድረግ ይጠበቅበታል፡፡ 1. ሰልፉን ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ማካሄድ፡፡ የተለያዩ ትንኮሳዎች ቢፈታተኑንም እንኳን ሰልፉ ስነ-ስርዓቱን በጠበቀ እና ጨዋነት በተሞላበት መልኩ ማካሄድ ይገባል፡፡ አንድ ጠጠር እንኳን ፍፁም መወርወር የለበትም፡፡ 2. የተመረጡ መፈክሮችን ብቻ […]

ሐምሌ 6 ቀን 2005 ዓ.ም የአገዛዙ ካድሬዎች ላለፉት በርካታ ሳምንታት የአንድነት ፓርቲ እያደረገ ያለዉን ሰላማዊና ሕዝባዊ ቅስቃሳ ከግቡ እንዳይደርስ ለማድረግ፣ በአለቆቻቸው ታዘው የተለያዩ የአፈና እንቅስቃሴዎችን ሲያደርጉ እንደነበረ በሰፊት ተዘግቧል። በርካታ ታሰረዋል፤ ወከባና እንግልትም ደርሶባቸዋል። ነገር ግን የአንድነት አባላትን ደጋፊዎች እንደዉም ሕዝቡ እግዚአብሄር የሰጣቸውን የዜግነት መብት ለማረጋገጥ ቀርተዉ የተነሱ ይመስላል። አፈናዉ የበለጠ እየጨመረ በመጣ ቁጥር የሕዝቡን […]

ሐምሌ 7 በጎንደርና በደሴ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ተሳተፉ!! ድምፃችሁንም በአደባባይ አሰሙ!! ————————————————————– ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ(አንድነት) የተሰጠ መግለጫ ————————————————————– ፓርቲያችን አንድነት ህጋዊና ሰላማዊ መንገድ የሚታገል ፓርቲ በመሆኑ የሚያደርጋቸውን ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች ኃላፊነት በተሞላበት ህጋዊ አግባብ ሲተገብር ቆይቷል፡፡ ፓርቲያችን “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት/Millions of voices for freedom” በሚል መሪ ቃል የጀመረውም ህዝባዊ ንቅናቄ የህዝባችንን መሰረታዊ ጥያቄዎችን ያነገበ […]

ሐምሌ 6 ቀን 2005 ዓ.ም ነገ እሁድ ጠዋት ሐምሌ 7 ቀን 2005 ዓ.ም. በጎንደር እና ደሴ ከተሞች ለሚደረገው ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ተፈቅዶ ከፖስተር መለጠፍ፣ በራሪ ወረቀት ከመበተን በተጨማሪ በድምፅ ማጉያ ሰልፉን ያዘጋጀው አንድነት ፓርቲ ቅስቀሳውን እያደረገ ይገኛል፡፡ ይንንም ተከትሎ በተመሳሳይ ጊዜ በደሴ ከተማ አራዳ ገበያ ህንፃ አንድነት ፓርቲ ተከራይቶ ያለውን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አከራዩ እንዲያስለቅቁ […]

በማዕከላይ አፍሪቃዊቱ ሬፓብሊክ ያማፅያን ቡድኖች የተሰባሰቡበት የየሰሌካ ህብረት የቀድሞውን ፕሬዚደንት ፍራንስዋ ቦዚዜን በመፈንቅለ መንግሥት አስወግዶ ሥልጣን ከያዘ ወዲህ ሀገሪቱ አሳሳቢ ሰብዓዊ ቀውስ ገጥሞዋታል።

በአምባገነኑ የኢህአዴግ መንግስት የሐሰት ዉንጀላ ለእስር የተዳረገዉ ታዋቂዉና ተወዳጁ ጋዜጠኛና የፖለቲካ ተንታኝ እስክንድር ነጋ ዲያስፖራዉ በሀገር ዉስጥ እየተካሄደ ባለዉ ሠላማዊ ትግል ላይ በአካል ተገኝቶ እንዲሳተፍ መልዕክት አስተላለፈ፡፡ የፖለቲካና የህሊና እስረኞችን በአካል ለመጠየቅ ቃሊቲ ለተገኙ ጋዜጠኞች እና የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ሕዝባዊ ንቅናቄ የግብር ሃይል አባላት አደራ ሲል ባስተላለፈዉ መልዕክቱ ከአገር ዉጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን ቀጣይ በሚካሄዱ […]

ጎንደሮች በሰልፉ ለመገኘት የትኛውንም ዋጋ እንከፍላለን እያሉ ነው! ሐምሌ 5 ቀን 2005 ዓ.ም በጎንደር የአንድነት አመራሮች ፖሊስ ካሜራ እየነጠቀ ነዉ ! ‹‹እኛ ሰላማዊ ታጋዮች ነን። የያዝነው ጥያቄ እንጂ መሳሪያ አይደለም» አቶ ዘካሪያስ የማነአብ ፣ የአንድነት ብሄራዊ ምክር ቤት ሰብሳቢ ———————————————————– በ30/10/2005 በጎንደር ሰላማዊ ሰልፍ ለማከናወን አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ያቀረበውን ጥያቄ የከተማው አስተዳደር ባቀረቡት ጥያቄ […]

ክንፉ አሰፋ

ስለ ኢትዮጵያውያን ብዙ የሚያውቁ ፈረንጆች ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ጠንቀቆ ማወቅ በጣም አስቸጋሪ እና ከባድ እንደሆነ ይናገራሉ። “ስለ ሕዝቡ ለመጻፍ የሚፈልግ አንድ ሰው ኢትዮጵያ በገባ ማዕግስት አንድ መጽሃፍ ሊጽፍ ይችላል፤ ይህ ሰው ሳምንት ሲቆይ አንድ መጣጥፍ ይጽፋል፣ ወር ሲቆይ ግን የሚጽፈው ይጠፋበታል።” ይላሉ። ይህ አባባል በከፊል ትክክል ይመስለኛል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

በሶማሊያ የግል መገናኛ ብዙኀኗ ቁጥርከቀድሞው እየጨመረ በመሄድ ላይ ነው ። የጋዜጠኞች ቁጥርም አድጓል ። በተለይ የመዲናይቱ የመቅዲሾ ነዋሪዎች የሚያዳምጡ የሚያዩዋቸው የቴሌቪዥንና የራድዮ ጣቢያዎች የሚያነቧቸው ጋዜጦችም በዝተዋል ። የሶማሊያ መገናኛ ብዙኀን ስርጭቶች አሁን ውጭ ላሉ ሶማሊያውያንም እየደረሱ ነው ።

በአዲስ አበባ አነዋር መስጊድ ለተወሰኑ ጊዜያት ጋብ ብሎ የነበረው የሙስሊሞች ተቃውሞ ዛሬ ቀጥሏል ። በወልድያም ተመሳሳይ ሠላማዊ ተቃውሞ ተካሂዷል ።

ሐምሌ 5 ቀን 2005 ዓ.ም በሰሜን ጎንደር ዞን ዋና ከተማ፣ ጎንደር፣ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ(አንድነት) ሐምሌ 7 ቀን 2005 ዓ.ም ለጠራው ህዝባዊ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ፣ ህዝቡ እንዳይገኝ ለማድረግ የከተማውና የዞኑ አስተዳዳሪዎች ከፍተኛ ውጥረትና ጭንቅ ላይ ናቸው፡፡ ይህንንም ተከትሎ ከፍተኛ አመራሮቹ የብአዴን/ኢህአዴግ አባላትንና የዞኑ የየወረዳው አመራሮችን በከተማው መምህራን ማኀበር አዳራሽ ትናንት ሐምሌ 4 ቀን 2005 […]

ትናንት በታሰበው የኢትዮጵያ የችግኝ ተከላ ቀን ሱናርማ የተባለው መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ያስተባበረው የዛፍ ተከላ ከደብረብርሃን ወጣ ብሎ በሚገኝ ቦታ ላይ ተካሂዷል ።

የአፍሪቃን የተፈጥሮና የሰዉ ሐይል ሐብትን ለማልማት ደግሞ የአፍሪቃ ሕብረት ኮሚሽን ፕሬዝዳት እንደሚያምኑት አፍሪቃ እራሷን ከርዳታ ተቀባይነት ወደ ንግድ ተሻራኪነት፥ ወደ ወረት መስሕብነት ቀስ በቀስ እየቀየረች ነዉ። በተለይ በወረት ፍሰት እና ወጣቶችን በማሰልጠኑ መስክ ጀርመን እንድትሳተፍ ዙማ ጋብዘዋል።

ባለፈው የሳምንት መጨረሻ በዚሁ በቦን አቅራቢያ በምትገኘው የኮሎኝ ከተማ ሰመርጃም የተሰኘዉ የሬጌ የሙዚቃ ድግስ ተካሂዷል። በዚሁ ድግስ በሺዎች የሚቆጠሩ ከተለያየ ሀገር የመጡ ታዳሚዎችና የሙዚቃ ባንዶች ተገኝተዋል።

ሐምሌ 5 ቀን 2005 ዓ.ም – የደሴ ከንቲባ «ሰልፉ ይተላለፍ አሉ»። በጽሁፍ እስካልቀረበ ድረስ አንድነት ጥያቄዉን ዉድቅ አደረገው! – በጎንደርና በደሴ ለፌደራልና ለክልል ፖሊሶች አበባ ይበረከታል! የደሴ ከንቲባ ሰልፉ ለሳምንት እንዲራዘም ጠየቁ። ነገር ግን የአንድነት አመራር አባላት ሕጉ እንደሚፈቅደው በጽሁፍ እስካልቀረበላቸው ድረስ ከንቲባዉ በቃል የጠየቁትን እንደማይቀበሉ አረጋግጠዉላቸዋል። በጎንደር የከተማዋ አስተዳዳሪዎች «ሕዝቡ እናንተን አይሰማም። አምሳ ሰው […]

  ሐምሌ ፭( አምት )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአዲስ አበባ በአንዋር መስጊድ ከፍተኛ ህዝብ በተገኘበት ተቃውሞ ተካሂዷል። መንግስት የለም ወይ፣ የሼክ ኑር ኢማም ግድያ ድራማ ነው፣ ድራማው ይብቃ፣      መሪዎቻችን ይፈቱ፣ መሀይም አይመራንም፣ በፍትህ እጦት ድፍን አንድ አመት መንግስት ራሱ ገዳይ ራሱ ከሳሽ፣ ። አሸባሪው  መንግስት ነው፣  ፍትሕ ማዳን። ፍትህ እያሉ ቃሊቲ ገቡ …

ሐምሌ ፭( አምት )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰሞኑን በሁለቱ ከተሞች በተካሄዱት ስብሰባዎች ህዝቡ በመልካም አስተዳደር ችግሮች እየተሰቃየ እንደሚገኝ በድፍረት ለመንግስት ተወካዮች ሲገልጽ ተሰምቷል። በእንጅባራ አንድ ነጋዴ ሲናገሩ የመንግስት ባለስልጣናት የሚያቀረቡዋቸው ሪፖርቶች ለራሳቸው የሚጠቅሙ እንጅ ህዝቡ የሚያያቸው አይደሉም በማለት በማስረጃ አስደግፈው አቅርበዋል። ነጋዴው እንዳሉት እቃዎች ሳይገዙ እንደተገዙ ተደርጎ ይወራረዳሉ፣ ጥራት ያላቸው እቃዎች አይገዙም፣ የመንግስት መጋዘኖችም …

ሁለተኛው ጉዳይ
(ባለፈው ሳምንት ከወላጆች ጋር በሁለት ጉዳዮች ለመነጋገር ተነሥቼ ነበር፤ የመጀመሪያውን ሳምንት አቅርቤአለሁ፤ በየቦታው መወያያ መሆኑን ፍንጭ አግኝቻለሁ፤ እስኪ ሁለተኛውን ዛሬ ላቅርብ)
አንዲት እኅት እንዲህ አወጋችኝ
ለዶክትሬት ጥናቷ ከአሜሪካ ትመጣና አጎቷ ቤት ታርፋለች፡፡ አጎቷ ‹አላቸው› ከሚባሉት የከተማችን ባለ ሀብቶች አንዱ ነበር፡፡ ሁለት ወንዶች ልጆች አሉት፡፡ ልጆቹ የሰባትና የዐሥር ዓመት ልጆች ናቸው፡፡ ልጆቹ በተደጋጋሚ ይታመማሉ፡፡ በሳምንት ቢያንስ አንድ ጊዜ ከሐኪም ቤት አይጠፉም፡፡ ‹‹አንድ ጊዜ እኔ ምሳ ስበላ ልጆቹን ጠራኋቸውና አብረን እንድንበላ ጋበዝኳቸው፡፡ እንጀራ እንደማይበሉ ነገሩኝ፡፡ ምንድን ነው ታዲያ የምትበሉት? አልኳቸው፡፡ ከሱፐር ማርኬት የሚገዛ አንድ የምግብ ዓይነት ነገሩኝ፡፡ ሞግዚታቸውም ያንን ይዛላቸው መጣች፡፡ በዚያ ጊዜ አንዳች ነገር ከነከነኝና ምሳዬን ከጨረስኩ በኋላ ወደ ማዕድ ቤቱ ገብቼ ሞግዚቷን ጠየቅኳት፡፡ ምንድን ነው እነዚህ ልጆች አዘውትረው የሚበሉት? እስኪ አሳይኝ? አልኳት፡፡ መደርደሪያውን ስትከፍተው ሁሉም ከሱፐር ማርኬት የሚገዙ የተፈበረኩ ምግቦች ናቸው፡፡ እጅግ በጣም ገረመኝ፡፡ 

በቀጣዩ ቀን ከልጆቹ ጋር ብስክሌትና ኳስ አብሬ ተጫወትኩ፡፡ ብዙ ጊዜ ወላጆቻቸውን ስለማያገኙ ከእኔ ጋር በመጨዋታቸው ደስ አላቸው፡፡ ከሰዓትም አብሬያቸው እንድጫወት ለመኑኝ፡፡ እኔም ይህንን አጋጣሚ ተጠቅሜ ከእኔ ጋር አብረው ምሳ ከበሉ ብቻ እንደምጫወት ነገርኳቸው፡፡ ቅር እያላቸው ለጨዋታው ሲሉ ተስማሙ፡፡ ቋቅ እያላቸውም በምሳ ሰዓት እንጀራውን በወጥ አብረውኝ በሉ፡፡ ቃል እንደገባሁትም አብሬያቸው ተጫወትኩ፡፡ በቀጣዩ ቀን ከባልትና ቤት የገንፎ እህል ገዝቼ መጣሁ፡፡ ከዚያም ገንፎ ሠራሁና አብረን እንድንበላ ጋበዝኳቸው፡፡ እንደምንም በሉልኝ፡፡ ቆሎ የሚባለውን ነገርማ ነክተውት ቀርቶ አይተውት አያውቁም፡፡ እኔ ግን ቆሎ ለጥርሳቸው ጥንካሬ እንደሚጠቅም፤ ኳስ ተጫዋች መሆን ከፈለጉ ደግሞ መጠንከር እንዳለባቸው፤ ለዚህም ከልዩ ልዩ ጥራጥሬ የተሠራው ቆሎ እንደሚጠቅም ነገርኳቸው፡፡ አብሬያቸው እየተጫወትኩ ስለምነግራቸው ተቀበሉኝ፡፡
በመጀመሪያው ቀን ለጥርሳቸው እንዳይከብዳቸው ለዘዝ ያለ ቆሎ እንዲበሉ አደረግኩ፡፡ ኳስ እንጫወትና በዕረፍት ሰዓት ቆሎ በልተን ውኃ እንጠጣለን፡፡ የተሰጠውን ያህል ያልበላ ይቀጣል እያልን ጨዋታ አደረግነው፡፡ ቂጣውንም በዚህ መልክ ነበር ያስለመድኳቸው፡፡ ማር የተቀባ ቂጣ መብላት አልለመዱም፡፡ ብስክሌት ለመንዳት ግን ቂጣ አስፈላጊ መሆኑን ነገርኳቸውና በብስክሌታቸው ጭኜ ስንነዳ እንበላ ነበር፡፡
እንዲህ እያደረግኩ ሰምተዋቸውም ተመግበዋቸውም የማያውቋቸውን ምግቦች አስለመድኳቸው፡፡ የሚገርምህ ነገር በየሳምንቱ ሐኪም ቤት መሄዱ ቀረ፡፡ ለካስ የእነዚህ ልጆች ችግር የምግብ ችግር ነበር፡፡ ከሱፐር ማርኬት የሚመጡ ምግቦችን እንጂ በባህላችን የሚዘጋጁና ለልጆች የሚያስፈልጉ ነገሮችን የያዙ ተፈጥሯዊ ምግቦችን አይመገቡም ነበር፡፡ ለካስ ልጆቹ እየበሉ የሚራቡ ነበሩ፡፡
ወላጆቻቸው ገንዘብ አላጡም፤ መግዛት የማይችሉም አይደሉም፡፡ ነገር ግን ልጆቻቸውን የወደዱ የሚመላስቸው፣ ልጆቻቸውንም የተከባከቡ የሚመስላቸው ከየሱፐር ማርኬቱ የሚገዙ የተፈበረኩ ምግቦችን በመግዛት፣ በጣፋጮች በማንበሽበሽ፣ ለልጆቹ ስሜት እንጂ ለልጆቹ ጤንነት የማይጠቅሙ የተፈበረኩ ምግቦችን በመስጠት ነው፡፡ ለእነርሱ ዘመናዊነት ማለት የታሸገ ምግብ ነው፣ ጣፋጭ ምግብ ነው፤ የሚገዛ ምግብ ነው፡፡ ርግጥ ነው ልጆቹ ደስ ይላቸዋል፡፡ ‹‹ማሚ እወድሻለሁ፤ ዳድ እወድሃለሁ›› እያሉ ደስታቸው እንዲጨምር ያደርጉታል፡፡ ደጋግመውም እንዲገዙላቸው የሚፈልጉት ይህንኑ ይሆናል፡፡ እነርሱም ብላ አትብላ ከሚለው ጭቅጭቅ ይድኑ ይሆናል፡፡ ነገር ግን ልጆቹን እየገደልናቸው ነው፡፡ በሁለት መንገድ፡፡
በአንድ መልኩ ማኅበራዊነትን እናሳጣቸዋለን፡፡ አንድ ልጅ ሀገሩን እንዲወድድ፣ ለሀገሩ እንዲያስብና ማኅበረሰቡን ዐውቆ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ ‹ማኀበር› socialization ያስፈልገዋል፡፡ ከማኅበረሰቡ ጋር መግባባት፣ መላመድና ማኅበረሰቡን መሆን፡፡ ከማኀበሪያ መንገዶች አንዱ ደግሞ አብሮ መብላትና መጠጣት ናቸው፡፡ እነዚህ ልጆች ሠርግ፣ ማኅበር፣ ተዝካር፣ ግብዣ እንዴት ነው የሚቀበሉት?  ነገስ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች እንዴት ነው የሚሠሩት? በሌላም በኩል እዚህ ሀገር የሱፐር ማርኬት ምግቦች በዘላቂነት አይገኙም፡፡ ይቀያየራሉ፡፡ ዛሬ ወደ ሀገር ውስጥ ገብቶ ልጆችህ የለመዱት ምግብ ነገ የለም ትባላለህ፤ ያን ጊዜ ልጆቹን ሌላ ነገር ማስለመድ ችግር ይሆንብሃል፡፡
ምን ይሄ ብቻ፡፡ ብዙ ጊዜ የታሸጉ ምግቦች የሚሠሩባቸው ነገሮች ልጆችን ያቃዥቧቸዋል፡፡ ስሜታውያን አድርገው ዕረፍት አልባ ያደርጓቸዋል፡፡ ያን ጊዜ ልጆቹ ረባሾች፣ ቀዥቃዣዎች፣ የማይሰሙ፣ ቀልበ ቢሶች ተደርገው በወላጆቻቸው፣ በቅርብ ዘመዶቻቸውና በሌላው ማኅበረሰብ እንዲነወሩ ያደርጋቸዋል፡፡ ይሄም ለልጆቹ ከማኅበረሰቡ ጋር አለመቀላቀል አንዱ ምክንያት ይሆናል፡፡
ሁለተኛው ጉዳት ደግሞ ልጆቹን የቅንጦት ረሃብ ውስጥ መጣሉ ነው፡፡ ዛሬ ዛሬ በምዕራቡ ዓለም ተፈጥሯዊ ምግቦችን መመገብ የሥልጣኔና የጤንነት ምልክቶች ናቸው፡፡ ውድ ምግቦችም ተፈጥሯዊ ምግቦች ናቸው፡፡ እኛ ሀገር እነዚህን ተፈጥሯዊ ምግቦች ብዙ ጊዜ የሚያገኙት ‹ድኾች› ናቸው፡፡ እስኪ ዝም ብለህ እይ በከተሞቻችንኮ የተጠበሰ በቆሎ መብላት፣ ቆሎ መብላት፣ ንፍሮ መብላት እየቀረ ነው፡፡ እነዚህ ምግቦችኮ ያልያዙት የንጥረ ነገር ዓይነት አልነበረም፡፡ ገንፎ እንኳንስ ከምግብ ዝርዝራችን ከአራስ ቤትም እየጠፋ ነው፡፡ እኔ የጃፓኖች ምግብ ቤት ገብቼ ከዶሮ ሥጋ ጋር የተቀቀለ በቆሎ ነበር ያቀረቡልኝ፡፡ አሁን እኛ ሀገር እንግዳ ጠርተህ የተቀቀለ በቆሎ ብታቀርብ ስምህ ነው የሚጠፋው፡፡ አንተ ራስህ ግሪክ ሀገር የተጠበሰ በቆሎ በሰባት ዶላር መግዛትህን ስትናገር ሰምቼሃለሁ፡፡ እኛ ሀገር ግን የተጠበሰ በቆሎ ምብላት የድህነት ምልክት ነው፡፡
ልጆቻችንኮ የተመጣጠነ ምግብ እየተመገቡ አይደለም፡፡ ይህ የሆነው በማጣታችን ምክንያት ብቻ አይደለም፡፡ ርግጥ ነው በምግብ እጥረት የሚጎዱ ሚሊዮን ልጆች አሉን፡፡ እኔ ግን የማወራህ በቅንጦት ረሃብ ውስጥ ስላሉት ልጆች ነው፡፡ ድንች እንደ ልብ በሚገኝበት ሀገር፣ በርካሽ ገዝቶ ቀቅሎ ማብላት ሲቻል እንዴት የታሸገ ድንች ጥብስ እናበላቸዋለን፡፡ እኛ በውድ ዋጋ ገዝተን ከምናበላቸው የታሸገ የድንች ጥብስ ይልቅ እነዚህ መንገድ ዳር የተቀቀለ ድንች ገዝተው (እምቦቲቶ) የሚበሉት ይበልጣሉ፡፡ እነርሱ ጋር ችግሩ ንጽሕናው ነው፡፡ በይዘቱ ግን ትክክለኛውና ጤነኛው የእነርሱ እምቦቲቶ ነው፡፡ ቡላና የገብስ ቂጣ እንደልብ በሚገኝባት ሀገር እየኖርን እንዴት ልጆቻችንን በታሸገ ዱቄት እናሳድጋቸዋለን?
ይኼ ፈጽሞ ልጅን መውደድ ሊሆን አይችልም፡፡ የማይሆኑ ምግቦችን እየመገብን ልጆቻችን በትምህርታቸው ሰነፍ ሆኑ ብለን ደግሞ እናማርራለን፡፡ እኔ ድሮ ድሮ የገጠር ልጅ ለምን ጎበዝ እንደሚሆን አሁን ነው የገባኝ፡፡ ገጠርኮ ልጆች ሁሉንም ዓይነት ምግብ ይበላሉ፡፡ የሚዘሩትንና የሚያበቅሉትን ተወው፡፡ ከጫካ የሚገኙ፣ ጤናማ የሆኑና በንጥረ ነገሮች የበለጸጉ ስንት ምግቦች ነበሩ፡፡ እነዚህ ምግቦች እኔ ሕጻን እያለሁ ከገበያ በቀላሉ እናገኛቸው ነበር፡፡ አሁን እንኳን ከተማ ገጠር መገኘታቸውንም እንጃ፡፡ እነ እንኮይ፣ እነ ሾላ፣ አነ ባምባ፣ እነ ኮሽም፣ እነ ግብጦ፣ የት ሄዱ፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የምታገኛቸው ከ500 ዓመት በላይ የኖሩት አበውኮ እነዚህን ተፈጥሯዊ ፍራ ፍሬዎች ነበር የሚመገቡት፡፡
የገጠሩም ሰው ዛሬ ዛሬ ሥልጣኔ የሚመስለው ልክ እንደ ከተማው ያለ አመጋገብ ነው፡፡ እነርሱ የሚያወጡት ቅብዐ ኑግ እኛ ከዱባይ ከምናስመጣው ዘይት እንደሚበልጥ ልንነግራቸው ይገባል፡፡ ልጅን መውደድ ማለት የሱፐር ማርኬት ምግብ መመገብ ሳይሆን በአካባቢው የምናገኛቸውን ምግቦች እያፈራረቁ እያመጣጠኑ መመገብ ማለት መሆኑን መንገር አለብን፡፡ ይህ አስተሳሰብ በመዛባቱ የተነሣ ቤተሰቦቻቸው በትክክለኛ መንገድ የሚያሳድጓቸው ልጆች እንኳን እንደ ሌሎቹ የተፈበረኩ ምግቦችን ስላልበሉ እያማረሩ ናቸው፡፡ ምክንያቱም ሬዲዮውና ቴሌቭዥኑ በእነዚህ ምግቦች ማስታወቂያዎች የተሞሉ ናቸዋ፡፡
ሲሆን ሲሆን በየብሔረሰቡ ያሉትን ምግቦች አጥንተን ወደ ሀገራዊው ባህል እንክተታቸው፡፡ አንደኛ በቀላሉ ይገኛሉ፡፡ እኛው ጋ ነዋ የሚበቅሉት፤ ሁለተኛ የተፈጥሮ ናቸው፡፡ ከጎጂ ነገሮች ነጻ ይሆናሉ፡፡ ሦስተኛ አሠራራቸው ቀላል ይሆናል፤ በባህል ተሞክረውና ተፈትነው የወጡ ናቸውና፡፡ እነ ጣልያንኮ ፒዛን ከኤርትራ ነው የወሰዱት፡፡ የትግራይ ሰዎች ቂጣውን በቅቤና በአዋዜ የመብላት የቆየ ባህል ነበራቸው፡፡ ጣልያኖች አዋዜውን በቲማቲም ተኩትና ፒዛን አመጡት፡፡ ዛሬ ልጆቻችን ፒዛ ነው እንጂ ቂጣ አንወድም ሲሉ ዝም እንላቸዋለን፡፡
ባይሆን ባህላዊ ምግቦችን ለልጆች በሚጣፍጣቸውና በሚስባቸው መንገድ እንዴት እናቅርባቸው? ብለን ወላጆች መምከር አለብን፡፡ እንደ ምዕራባውያኑ ልጆቹ ከተጎዱና ለአደጋ ከተጋለጡ በኋላ ጉዳዩ ሀገራዊ ጉዳይ እንደሚሆን ጥርጥር የለኝም፡፡ እንዲያውም ከከተማው ይልቅ የገጠሩ ሕዝብ በባለሞያዎች የሚሰጠውን ሃሳብ እየተቀበለ የልጆቹን አመጋገብ እያስተካከለ መሆኑን አንዳንድ ቦታዎች አይቻለሁ፡፡ ጭብጦውን እንዲቀይሩ አይደለም፡፡ ጭብጦውን ከልዩ ልዩ እህሎች በተፈጨ ዱቄት እንዲሠሩት ነው ያስተማሯቸው፡፡ ካገኙ ትንሽ ወተት እንዲያደርጉበት፣ ከተቻለ ደግሞ ቅቤ እንዲጨምሩበት ነው የሚያስተምሯቸው፡፡ ክክ ወጡን እንዲተውት አይደለም የነገሯቸው፤ ክኩን የአተር ብቻ ከማድረግ የሌሎችንም ጥራጥሬዎች እንዲያደርጉት ነው፡፡ ››
ለእኔ እያብራራችልኝ በሄደች ቁጥር ንዴቷ እየጨመረ መጣ፡፡ ሞያዋም፣ ትምህርቷም ስቧት ብዙ ነገር ታዝባለች፡፡ ነገር ግን ከዘመዶቿ ጋር እንኳን በዚህ ጉዳይ መስማማት አልቻለችልም፡፡
‹‹ምናልባትኮ ወላጆች ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት ሲልኩ አልበላም ስለሚሏቸው ይሆናል›› አልኳት፡፡
‹‹ልጆችኮ አልበላም የሚሉት ከብዙ ነገር አንጻር ነው፡፡ የምግቡ አዘገጃጀት፣ የጓደኞቻቸው ተጽዕኖ፣ የመመገቢያው ዕቃ፣ ሌሎችም አብረው መታየት አለባቸው፡፡ እንዲያውም እነዚህ ከሱፐር ማርኬት የሚገዙ ምግቦች ልጆቹን ለሌሎች ምግቦች ማለማመጃ ሊሆኑን ይችላሉ፡፡ ሌሎች ምግቦችን ለሚመገቡ ልጆች እንደ ሽልማት በመስጠት፡፡ በሌላም በኩል ልጆቻችን በራሳቸው እንዲተማመኑ ማስተማርም አለብን፡፡ ማሳመን አለብን፡፡ ራሳቸውን እንዲሆኑ፡፡ ይሄ ባህሌ ነው፤ ይህንን እወዳለሁ እንዲሉ፡፡››
ሃሳቧ እጅግ አብዝቼ እንዳስብ አድርጎኛል፡፡ በተለይም ‹የቅንጦት ረሃብ›› ያለችው ነገር ልክ ነው እያልኩ ከራሴ ጋርም ከቤተሰቤ ጋርም ብዙ ሰዓታት ተነጋግሬበታለሁ፡፡ እስኪ ወላጆች ተነጋገሩበት፡፡ ወቅቱ ትምህርት ቤቶች የተዘጉበት በመሆኑ የልጆቻችንን አመጋገብ ለማስተካከል ምቹ ጊዜ ላይ ነን፡፡  ለመሆኑ በየቤታችን የቅንጦት ረሃብ የለም? በየቤታችን የልጆቻችን አመጋገብ የታሰበበት ነው? ስለምንገዛላቸው እንጂ ስለሚመገቡት ነገር እናስባለን፡፡ እኛ ገዛን፣ ሞግዚቶቻቸውስ ይመግቧቸዋል? እስኪ የሰሞኑ የቤተሰብ አጀንዳ ይኼ ይሁን፡፡

ሐምሌ ፭( አምት )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ በሀላፊነት ላይ የሚገኙ የድርጅቱ  ሠራተኛ እንደተናገሩት በምክትል ጠ/ሚኒስትር ማዕረግ የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትር የሆኑት አቶ ሙክታር ከድር በቦርድ ሰብሳቢነት ወደመድን ድርጅት ከመጡ ካለፉት ሁለት ዓመታት ወዲህ ዘረኝነትና ግልጽ የሆነ ዘረፋ በድርጅቱ ውስጥ በመንሰራፋቱ  በርካታ ባለሙያዎች ድርጅቱን ለመልቀቅ እየተገደዱ ነው። ችግሩን ቦርዱ ተመልክቶ ሠራተኛውን እንዲያወያይ በተደጋጋሚ …