አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲና የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ብአዴንን በመቃወም በባህርዳር ከተማ ህዝባዊ የተቃውሞ ሰልፍ ጠሩ፡፡ ፓርቲዎቹ ነገ በ4 ሰዓት በአንድነት ፓርቲ ጽ/ቤት በጋራ መግለጫ እንደሚሰጡ ይጠበቃል፡፡ ለተቃውሞ ሰልፉ አስፈላጊው የማሳወቅ ተግባር መጠናቀቁ ታውቋል፡፡ አንድነትና መኢአድ እሁድ የካቲት 16 ቀን 2006 ዓ.ም የጠሩት የተቃውሞ ሰልፍ መነሻ ምክንያት እንዲያስረዱ በፍኖተ ነፃነት የተጠየቁት የአንድነት ፓርቲ የፖለቲካ ጉዳዮች […]

የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (ሸንጎ) Ethiopian People's Congress for United Struggle (Shengo)Ethiopia Zare (ረቡዕ የካቲት 5 ቀን 2006 ዓ.ም. Feb. 12, 2014)፦ የአማራ ክልል ም/ፕሬዝዳንት አቶ አለምነው መኮንን በአማራው ላይ የሰነዘሩትን ፀያፍና በዘር ጥላቻ ላይ ያዘነበለ ስድብ በማውገዝ፤ “የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ” ትናንት የካቲት 4 ቀን 2006 ዓ.ም. መግለጫ አወጣ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ነጋ ዓለማየሁ

ሰሞኑን የአማራ ክልል ባለሥልጣን ናቸው የተባሉ ሰው በአማራው ሕዝብ ላይ የጅምላ ስድብ ሲሳደቡ ተደምጠዋል። ሰውየውን ስሙንም ሰምቼው አላውቅም። እንዲህ አይነቱን ሰው አንቱ ማለትም የሚገባ አልመሰለኝም። ሀገሪቱን የሚመራው መንግሥት ከየት አምጥቶ እንዳስቀመጠው እራሱ ነው የሚያውቀው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

አስገራሚው የሳውዲው “ኮራጅ ” አባት ምክር

ነቢዩ ሲራክ
ነገሩ እንዲህ ነው፤ ከ20 ዓመት በፊት ሳውዲው ወጣት ራሱን ለሁለተኛ ደረጃ ፈተና ከማዘጋጀት ይልቅ በረቀቀ መንገድ ለፈተናው መልስ የሚሆነውን ማጭበርበሪያ የመልስ ወረቀት አዘጋጅቶ ለፈተና ይቀርባል። ፈተናውን በረቀቀ መንገድ አጭበረብሮ ሰርቶታልና ፈተናውን በተገቢ ውጤት አልፎ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ለማለፍ በቃ!

ሙሉውን አስነብበኝ …

ብልህ የጥንቶቹንም ለመከተል አይፈልግም፤ ዘልዓለማዊ ነው የሚባል ደረጃ ለመመደብም ሆነ ለማስቀመጥ አይሻም፡፡ ይልቁንም የራሱን ዘመን መርምሮ ለዚያ የሚያዋጣውን ዘዴ ይዘይዳል፡፡“የብልህ አመራር ማለት ገዢው የሱ ሰዎች ልክ እሱ ያዘዘውን ያሰቡ እንዲመስላቸው ማድረግ ነው፤” ትላለች የሩሲያዋ ታላቋ ካቴሪን፡፡ ቀጥላም “ይሄን ለማድረግም፤ አንድ እርምጃ ከህዝቡ ፍላጐት መቅደምና ከአልቀበል – ባይነቱ ጋር መላመድ ነው” ትለናለች፡፡ ልብ ያለው ልብ ይበል! ራመድ ብለን የንግሥቲቱን አካሄድ ስንመረምር ለውጥን ያለጉልበት በዘዴ እንዴት ለማምጣት እችላለሁ? የማለት፤ ጥበባዊ ፍላጐትን የመቀዳጀት ጥያቄን ይሰርጽብናል፡፡ የኛ ዕቅድ፣ መርህ፣ ስትራቴጂ ወዘተ. ከሰማይ በወረደ ኃይልም አይታጠፍም፣ አይቀየርም፣ የምንለውን፤ በልባምነት አውጠንጥነን እንድናይ የሚያግዘን አስተውሎት ነው፡፡

ተቃዋሚዎቻችንን ወይም በግልባጩ ገዢዎችን የምናይበትን ሁኔታ በሁለት ታዋቂ የሰንጠረዥ ጨዋታዎች ምሳሌነት ለማፀኸየት እንሞክር፡፡ አንደኛው፤ ቼዝ ነው፡፡ ሁለተኛው፤ ጐ የሚባለው ጨዋታ ነው ፡፡ ቼዝ ጨዋታ፤ በጠባብ ሜዳ የምንጫወተው ሠንጠረዥ ነው፡፡ 32 ጠጠሮች አሉት – አለቃና ምንዝር የሆኑ። ከሁለቱም ወገን የሚሠለፉ፡፡ የቼዝ ጨዋታ የጠላትን ወታደርና መኮንኖች ግንባር ለግንባር እየገጠሙ መደምሰስ ነው፡፡
በአንፃሩ በ “ጐ” ጨዋታ፣ ከቼዝ ስድስት ጊዜ በሰፋ ሰፊ ሜዳ በየጐራው 52 ጠጠሮችን በጥቁርና በነጭ አሰልፎ መፋለም ሲሆን፤ ዘዴው እያንዳንዱን ጠላት በመክበብ ከእናት ክፍሉ ለይቶ መጠጊያ ማሳጣት ነው፡፡ ከዚያም እንዲሟሽሽና ሽባ እንዲሆን ማድረግ ነው፡፡

በሰፊው ማሰብ፣ ትንሽ ቦታ ሰውቶ፣ ቀስ በቀስ ሰፊ ቦታ መያዝ፤ በመጨረሻም ማሸነፍ ነው፡፡ ሁለቱን ስልቶች ጠንቅቆ ማወቅ ለኢትዮጵያ የፖለቲካ ሠንጠረዥ እጅግ ጠቃሚ ነው! ቅልጥፍናን ከገዢ መሬት በላይ የማየት ክህሎት ይኑርህ ነው ነገሩ!
እጅ መስጠት የሚጀምረው ከአንጐል ውስጥ ነው፡፡ ስለዚህ አስቀድመህ የባላንጣህን አዕምሮ ክበብ ይላሉ፤ የፖለቲካ ፀሐፍት ቀስቅስ፣ ግንዛቤ ፍጠር፣ አንቃ ነው፡፡ የማዖን የጦር ዘዴ ለአዕምሮ ጦርነት ማሰብ ድንቅ ነው፡፡

“ጠላት ሲገፋ አፈግፍግ፡፡ ጠላት ካምፕ ውስጥ ሲያርፍ እረፍት – ንሳው፡፡ ጠላት ሲዳከም አጥቃው፡፡ ጠላት ሲያፈገፍግ አንተ ግፋ፡፡” ዘመኑ የአዕምሮ ትግል ወቅት ነውና አዕምሮህን አስላ፡፡ እቅድህን አጥራ፡፡ ስትራቴጂህን በጥንቃቄ ቀንብብ እንደማለት ነው፡፡ ይሄ ሁሉ ሲሆን ግን ከብጤህ፣ ከእኩያህ፣ ከአምሳያህ፣ የፖለቲካ አዕምሮ – ፈርጁ ከአዐምሮ – ፈርጅህ የሚጣጣም የፖለቲካ ባልንጀራ አበጅተህ ወቅቱ በሚፈቅደው ዛፍ ጥላ ሥር ሆነህ፣ ንጋት፣ ቀትርና ጨለማ ለይተህ፣ መጓዝ እንዳለብህ ማወቅ ነው ታላቁ ቁምነገር፡፡ እንዲያው በጥቅም – ቀደም – አካሄድ ለእለት – እንጀራ የተጐዳኘኸውን ወይም ብረት – ድስትና ሸክላ – ድስት ሳትለይ የተወዳጀኸውን ሁሉ የፖለቲካ ወዳጄ ነው ብለህ ከተጓዝክ “ከማይመጥነው ሰው ጋር የሚካኤል ማህበር ጠጣ፤ ተራውን ሳያጠጣ ሞተ” ከመባል አታመልጥም!!#MinilikSalsawi

“አሜሪካኖች ነጻ እንድታወጡን አንጠይቃችሁም። የኢትዮጵያ ህዝብ እንዴት ነጻ እንደሚወጣ ያውቃል። እናንተ ግንበነጻነት መንገዱን ላይ ዕንቅፋት አትሁኑበት … ዶናልድ ያማሞቶ ከዛሬ ስምንት ዓመት በፊት ኢትዮጵያ በመንታመንገድ ላይ ነች ብለኸን ነበር መቼ ነው መንገዱን የምናቋርጠው? ከመንገዱ ላይ ገለል በሉልን” አቶ ኦባንግ ሜቶ
እንዴት እዚህ ተደረሰ?

የኢህአዴግን የአገዛዝ ዘመን ተቃዋሚዎችን አጃቢ አድርጎ የህግ ሽፋን በመስጠት የሚያራዝመው ዋና ተቋም ምርጫ ቦርድ፣ የፕሬስ ነጻነት፣ የመናገርና የመሰብሰብ ነጻነት፣ የህግ የበላይነት፣ ሕግን የማክበርና የማስከበር ሃላፊነት፤ ወዘተ በኢትዮጵያ ነጻ ከሆኑ ኢህአዴግ ከፊትለፊቱ ካለው ምርጫ የመዝለል አቅም እንደሌለው ይታመናል። ስለዚህም እነዚህን ጉዳዮች ለድርድር አያቀርባቸውም። ኢህአዴግ ከጅምሩ በህዝብ የማይታመነውና እውቅና የሚነፈገው ራሱን በነጻ አውጪ ስም (ህወሃት) የሰየመ መንግስት ስለሆነ ነው።

ነጻ አውጪ እየተባለ አገር መምራቱም አቅዶ፤ ተልሞና መድረሻውን አስልቶ የሚጓዝ ስለመሆኑ ያሳብቅበታል። ለዚህም ይመስላል ስርዓቱ በሙስና የሸተተ፣ በግፍ የገለማ፣ የሚመራውን ህዝብ የሚገል፣ የሚያስር፣ የሚያሰቃ፣ መንግስት ሆኖ የሚሰርቅ፣ ብሔራዊ ክብርን የሚጠላ፣ ህብረትንና አንድነትን የሚጠየፍ፣ ጎሳና ጠባብ አመለካከት ላይ የተቀረጸ፣ በተራና በወረደ ተግባሩ ለመንግስትነት የማይመጥን መሆኑን የተረዱት አጋሮቹ አሁን ያመረሩበት ደረጃ ስለመዳረሳቸው ምልክቶች እንዳሉ አቶ ኦባንግ ሜቶ ለጎልጉል ተናግረው ነበር።
ኢህአዴግ ከአሜሪካ ጋር የመሰረተው ግንኙነት ከቶውንም ንፋስ እንደማይገባው ተከታዮቹ ሙሉ በሙሉ ያምናሉ። በተለይም የህወሃት ሰዎች አሜሪካ ከህወሃት ጋር ያሰረችው ቀለበት የሚወይብ አይመስላቸውም። የአሜሪካና የ”ህወሃት ፍቅር” ትምክህት የሆነባቸው የአሜሪካን ባለስልጣናት ህወሃት ኢትዮጵያን እስከ ዘላለም እንዲመራ ልዩ ቅባት እንደቀቡት የሚናገሩም አሉ። አሜሪካ ለህወሃት/ኢህአዴግ የምትሰጠው ጭፍን ድጋፍ ሊጤን እንደሚገባው በማሳሰብ ተስፋ ሳይቆርጡ የታገሉና የሚታገሉ ደግሞ ይህ ትምክህት አንድ ቀን እንደሚተነፍስ በእምነት ሲናገሩ ቆይተዋል።

ኢህአዴግን በዲፕሎማሲና በሰከነ የትግል ስልት መታገል ይበልጥ አዋጪ እንደሆነ ከሚያምኑት ወገኖች መካከል አቶ ኦባንግ ሜቶ ቅድሚያውን ይይዛሉ። አቶ ኦባንግ የሚመሩት ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) የሚያራምደውን እምነት አስመልክቶ “ከወረቀትና ፒቴሽን ከማስፈረም ያልዘለለ” በማለት የሚቃወሙና የሚተቹ የመኖራቸውን ያህል ልብና ቀልብ ሰብስበው የሚከተሏቸው ወገኖች ቁጥር ከቀን ቀን እየጨመረ ነው። እምነትም እየተጣለባቸው ነው።

በወገኖቻቸው ብቻ ሳይሆን በውጪው ዓለም ያላቸው ተቀባይነት፣ ብሎም አመኔታ እንዲሁ ከፍተኛ ነው። የኢትዮጵያ ወኪል ተደርገው እየተወሰዱም ነው። አቶ ኦባንግ ኢትዮጵያን በመወከል በተለያዩ ታላላቅ መድረኮች ሲሳተፉ የሚያቀርቧቸው ንግግሮችም ቀልብ የሚገዙና መልዕክታቸው የሰፋ በመሆኑ ሰፊ አድማጭ አላቸው። ሰሞኑንን በአሜሪካ ምክርቤት (ኮንግረስ) የጸደቀውን ድንገተኛ ውሳኔ አስመልከቶ “ኢህአዴግ ሳይወድ በግዱ በሩን በርግዶ ይከፍታል” ባይ ናቸው። ውሳኔውንና የውሳኔውን አካሄድ ከአነሳሱ ጀምሮ ጠንቅቀው እንደሚያውቁት ያመለከቱት አቶ ኦባንግ “አሜሪካ እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰችው እንዲሁ ከመሬት ተነስታ ሳይሆን በከፍተኛ ትግል ነው። ትግሉ ተጠናክሮ ይቀጥላል የአውሮፓ አገሮችም የአሜሪካን ፈለግ እንዲከተሉ ሥራችንን አጠናክረን ጀምረናል” ብለዋል።
አዲሱ ውሳኔ ሕግ እና የኢህአዴግ ህልውና!

እያነጋገረ ያለው የእርዳታን አጠቃቀም አስመልክቶ ጥር 31 ቀን 2014 በአሜሪካን ኮንግረስ የፀደቀው አዲስ ውሳኔ ሕግ ነው። ውሳኔው አሜሪካ የምትሰጠው ርዳታ በትክክል ህዝብን ሳይጎዳ በስራ ላይ መዋሉንና አለመዋሉን እንዲቆጣጠር ለአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መ/ቤት (State Department) ትዕዛዝ የተላለፈበት ነው። እንግዲህ ይህ ትዕዛዝ ይፋ ከሆነበት ጊዜ ጀምሮ የሚነሱት መከራከሪያዎች በርካታ ቢሆኑም በምላስ “ነጻ ነኝ” የሚለውና በግብር “ለጌቶቹ ጥሩ ባሪያ” በመሆን 22 ዓመት የዘለቀው ኢህአዴግና ከአሜሪካ ግንኙነታቸው በነበረበት መንገድ ስለመዝለቁ ጥያቄ የሚያስነሳ እንደሆነ አብዛኞች ይስማማሉ። አሜሪካ ከዚህ ውሳኔ የደረሰችው በወፍ ዘራሽ ሳይሆን በሂደት እንደሆነ በመጥቀስ አቶ ኦባንግ ሜቶ ከሚያቀርቡት ሃሳብ ጋር ይስማማሉ።

የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪ ድርጅቶች መረጃ ላይ ተንተርሰው ለሚያወጡት ሪፖርት “ተራ የማበሻቀጪያና የማጣጣያ” መልስ በመስጠት፣ ሲለውም ተቃዋሚዎችን የሚደግፉና የኢህአዴግ የኢኮኖሚና የፖለቲካ እምነት /የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ጎዳና/ “ቅንቅን” የሆነባቸው የምዕራብ አገራት “ተላላኪ” በማስመሰል አሁን ድረስ ሲዘልፋቸው መቆየቱ አይዘነጋም። ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ እንደሚሉት አሁን አዲስ ለጸደቀው የአሜሪካ ቅድመ ሁኔታ ላይ ያተኮረ የርዳታ መርሃ ግብር እነዚህ ክፍሎች በቁጥጥርና በክትትል በኩል ሪፖርታቸው ዋና ግብዓት ስለሚሆን ኢህአዴግ መንታ ፈተና ውስጥ እንደሚወድቅ ቅድመ ትንበያዎች አሉ።

በዚሁ መነሻ ኢህአዴግ የህልውናው መሰረት የሆነውን እርዳታ ለማግኘት “የፖለቲካ አመለ ሸጋ ሆኖ የዘጋቸውን በሮች ከፍቶ የሚመጣውን የህዝብ ወሳኝነት መቀበል፣ አሊያም በሂደት ሰልሎና ተሽመድምዶ መክሰም የመጨረሻው እድል ፈንታው ይሆናል” የሚሉ ወገኖች ጥቂት አይደሉም።

ኢህአዴግ በመንታ መንገድ ላይ – የህጉ ተጽዕኖ ከፖለቲካና ኢኮኖሚ አንጻር
ውሳኔውን ከፖለቲካው እንደምታና ከኢኮኖሚው ጣጣ ጋር በማያያዝ አስተያየት የሰጡን እንደሚሉት ከሆነ ጉዳዩ አደጋ አለው። እንደሚታወቀው የኢህአዴግ አገዛዝ ከጠቅላላው የምዕራብ መንግስታት ከሶስት ቢሊዮን ዶላር በላይ ዕርዳታ በየዓመቱ ያገኛል። ይህ ከፍተኛ መጠን ያለው ዕርዳታ ከአጠቃላይ አመታዊ በጀቱ 50% የሚሆነውን ይሸፍንለታል። ከአሜሪካን ብቻ አንድ ነጥብ ስምንት ቢሊዮን ዶላር በየዓመቱ በዕርዳታ መልክ ያገኛል። ይህም ከአሜሪካ የሚገኘው ርዳታ ብቻውን የበጀቱን አንድ ሶስተኛውን ይሸፍንለታል።
በዚህ መነሻ የኮንግረሱ ውሳኔ በኢህአዴግ አገዛዝ ላይ ያልጠበቀው ዱብ ዕዳ እንደሆነ በጀርመን የልማት ኢኮኖሚክስ ባለሙያው (Development Economist) ዶ/ር ፈቃዱ በቀለ ይናገራሉ። ይህ እሳቸው “ዱብዕዳ” ያሉት ውሳኔ የፖለቲካ ውዝግብ ማስነሳቱ የማይካድ ነው። ኢህአዴግ ከአውሮፓና ከአሜሪካ የሚያገኘውን ድጎማና ርዳታ ለምን ተግባር ሲያውለው እንደነበር ከማንም በላይ ጠንቅቆ ስለሚያውቀው ከቅድመ ሁኔታ ጋር የተያያዘ የዕርዳታ አሰጣጥ ከኢኮኖሚ ይልቅ የፖለቲካና የስነልቦናው ተፅዕኖው እንደሚያስከትልበት እኚሁ ምሁር ያስረዳሉ።

ከአጠቃላዩ የማክሮ ኢኮኖሚ አንጻር ውሳኔው ሊያስከትል የሚችለውን ተጽዕኖ በዝርዝር በማስቀመጥ አስቀድሞ መናገር ባይቻልም አሉታዊ ተጽዕኖ ሊኖረው እንደሚችል መገመት እንደማያዳግት ዶ/ር ፈቃዱ ከጎልጉል ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል። “ከአጭርና ከመካከለኛ ጊዜ አንፃር ስንመለከተው የአገዛዙን የኢኮኖሚ አካሄድ ጥያቄ ውስጥ ሊያስገባ ይችላል” ያሉት ባለሙያው፣ “… ወደፊት አዳዲስ የስራ መስክ መክፈት፣ በኢኮኖሚው ዕድገት፣ በውጭ ምንዛሪ ግኝትና በውጭ ሚዛን ዕድገት ላይ ሊኖረው የሚችለው ተፆዕኖም ቢሆን ይህ ነው ብሎ መናገር አይቻልም። ይሁንና የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እርስ በርሱ የተያያዘ ስላልሆነና፣ አብዛኛው ህዝብም በኢንፎርማልና ከእጅ ወደ አፍ በሚገኝ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ውስጥ የሚተዳደርና የሚሳተፍ ስለሆነ ሊጎዳ የሚችለው በዘመናዊ መስክ የተሰማራውን ሰራተኛና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ነው” በማለት ቅድመ ግምታቸውን ያስቀምጣሉ።

ሲያብራሩም ከቅድመ-ሁኔታና ከጥብቅ ቁጥጥር ጋር የተያያዘ በዕድገት ስም የሚፈስ ዕርዳታ በአጠቃላይ ሲታይ በህዝቡ ኑሮ መዛነፍ ላይ የሚኖረው ተፅዕኖ ዝቅተኛ መሆኑንን የሚያመለክቱት ዶ/ር ፈቃዱ፣ ከ10-11በመቶ “ያለማቋረጥ” አደገ በሚባለው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከኢትዮጵያ ህዝብ ኑሮ መሻሻል ጋር ተያያዥነት እንደሌለው ይናገራሉ። ቅድመ ሁኔታ የተቀመጠለት እርዳታ ቢቀነስ ወይም እንዳለ ቢታገድ በተመሳሳይ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ የሚያመጣው አሉታዊ ውጤት ምን ሊሆን እንደሚችል ከወዲሁ በቁርጥ ማስቀመጥ እንደሚያዳግትም ባለሙያው ይጠቁማሉ። በዚህ ዓይነቱ የዕርዳታ አካሄድ እስካሁን የተጎዳው ህዝብ በመሆኑ የዕርዳታው መቀነስ ወይም መታገድ አገዛዙን እንጂ በዚያ አካባቢ የሚኖረውን ህዝብ በቀጥታ የሚመለከት አይሆንም። በህዝብ ኑሮ ላይ የሚከተለውን ማህበራዊ ኪሳራ ተምኖ ማስቀመት ቢችግርም “ወያኔ ቅድመ ሁኔታውን ተግባራዊ የሚያደርግ ከሆነ በተለይም በቀጥታ በኗሪው ህዝብ ህይወት ላይ አዎንታዊ ውጤት ማሳየቱ ግን የማይቀር ነገር ነው” ሲሉ ግርድፍ ምልከታቸውን ያኖራሉ። በሴፍቲኔት፣ በአነስተኛና ጥቃቅን፣ ወዘተ የህዝቡን ኑሮ እየቀየርኩ ነው የሚለው “ልማታዊው” ኢህአዴግ እንዲህ ዓይነት በቅድመ ሁኔታ የተወጠረ ዕርዳታ በሕዝቡ ኑሮ ላይ ቀውስ ያመጣል በማለት የራሱን ቅንብር እንደሚሰራ የሚከራከሩም አሉ፡፡

ፖለቲካዊ ይዘቱን የዳሰሱት ዶ/ር ፈቃዱ ሁለት መሰረታዊ ጉዳዮችን በመጠቆም ለውይይት የሚጋብዝ ፍንጭ ሰጥተዋል። “ውሳኔ ሕጉ ያካተታቸው ቅድመ ሁኔታዎች ከረዥሙ አጠቃላዩ የማክሮ ኢኮኖሚ ሁኔታ አንፃር ስናየው ግን በዕውነቱ እንደዚህ ዓይነቱ ከቅድመ-ሁኔታ ጋር የተያያዘ ዕርዳታ ላይጎዳው ይችላል። አገዛዙ ከምዕራቡ አገራት የሚመጣበትን ግፊት የሚቋቋም መስሎት የሚታየው ከሆነ ፊቱን ወደ ቻይናና ወደ ሌሎች ቅድመ ሁኔታን ከማያሰቀድሙ አገሮች ዕርዳታ በማግኘት ከአሜሪካን የሚሰጠውን ዕርዳታ ሊያካክስና በነበረበት ሁኔታ ለመቀጠል መንፈራገጡ” አንደማይቀርም አመላክተዋል። ይህ ግምታቸው ግን ጥርጣሬያቸው እንዳለ ሆኖ ነው።

“ኢትዮጵያ ካለችበት የጂኦ ፖለቲካ፣ የአፍሪካ ህብረት ዕምብርትና መቀመጫም ስለሆነች ቻይናዎች ከራሳቸው የንግድ መርህ አንጻር ዕርዳታውን ከመስጠት ወደኋላ ሊሉ አይችሉም” ሲሉ የጉዳዩን ሌላ መልክ ያሳዩት ዶ/ር ፈቃዱ፣ አማራጩ ከአሜሪካንም ሆነ ከተቀረው የምዕራቡ ዓለም ጋር ተላትሞ ወደ ቻይና ፊትን በማዞር የሚደመደም ከሆነ አገዛዙ ዕድሜውን ለማሳጠር ራሱ እንደወሰነ የሚቆጠርበት ይሆናል። ኢህአዴግ አምርሮና የመጣው ይምጣ በሚል ቅድመ ሁኔታዎችን አላሟላም፣ ዕርዳታችሁንም አንፈልግም የሚል ከሆነ አሜሪካን አማራጭ ለመፈለግ ልትሞክርና ይህንንም እንደማስፈራሪያ ተጠቅማ ልትለሳለስ” እንደምትችል ዶ/ር ፈቃዱ አመላክተዋል።

እንደወያኔ የሚታዘዝላት ድርጅትና መሪ እስካላገኘ ድረስ ኢህአዴግ ላይ አደጋ እንዲነግስ ወይም ከነጭራሹ እንዲወገድ አሜሪካ ትሰራለች ብለው እንደማያምኑም ገልጸዋል። “እንዲያውም” አሉ ዶ/ር ፈቃዱ “በኮንግረሱ የፀደቀው ህግና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር (State Department) እንዲቆጣጠረው የተደረገው የዕርዳታ አሰጣጥ ዘዴ፣ የኦባማ አስተዳደር ሌላ መንገድ ፈልጎ ኮንግረሱን በማለፍ፣ በቀጥታ ከአሜሪካን የውጭ ዕርዳታ አሰጣጥ ጋር ባልተያያዘ መንገድ የኢህአዴግን አገዛዝ በተዘዋዋሪ ሊረዳበት የሚችልበት መንገድ እንደሚኖር መጠራጠር ይቻላል” ሲሉ ሃሳባቸውን ያጠናክራሉ። ገደቡ በተለይም አገዛዙ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሰላም ጥበቃን፣ የፀረ-ሸበርተኝነትን፣ የድንበር ጥበቃንና እንዲሁም የመከላከያ አዛዡን ስታፍ ሰራተኞች ስለማይመለከት ተጽዕኖው በወታደሩ ላይ ዝቅ ያለ መሆኑንን አንደማሳያ ይጠቁማሉ።

ፍርድ ቤቶችን ከፖለቲካ ተፅዕኖ ቁጥጥር ስር ውጭ ማድረግ፣ የሚዲያ፣ ሀሳብን በነጻነት የመግለጽና የመሰብስብ ነፃነት፣ እንዲሁም ሌሎች በቅድመ ዕርዳታው መስፈርት ሆነው የተዘረዘሩትን አንኳር ጉዳዮች ኢህአዴግ አጥብቆ የሚፈራቸውና ህልውናውን አደጋ ላይ የሚጥሉት በመሆናቸው በቀላሉ ለመቀበል የሚያዳግተው መስፈርቶች እንደሆኑ ለማንም ግልጽ ነው ሲሉ ዶ/ር ፈቃዱ ተናግረዋል። ይልቁኑም “እስካሁን ድረስ ለምን ዘገዩ? የሚመለከተው አካልም ሆነ የኦባማ አስተዳደር እስካሁን ድረስ ምን አስጠበቃቸው? አሁን ምን አዲስ ነገር ታያቸው? እስካሁን ድረስ የኢትዮጵያ ህዝብ ይሰቃይ ላይ አልነበረም ወይ? ለ22 ዓመታት የአገዛዙ የጭቆና ድርጊት ከአሜሪካ መንግስት የተሰወረ ጉዳይ ነበር ወይ? የሚሉት ጉዳዮች ሲነሱ የጸደቀውን ህግ ጉዳይ በጣም እንቆቅልሽ ያደርገዋል” በማለት ከጉዳዩ ጀርባ አንድ በጊዜ ሂደት እየጠራ የሚሄድ ጥቅል ጉዳይ ስለመኖሩ አመላካች እንደሆነ ምሁሩ ያስረዳሉ። በዚሁ መነሻ ፓለቲካዊ ትርጉሙ በቀላሉ ሊታለፍ የማይችልና ለአገዛዙ አስቸጋሪ ሁኔታ የሚፈጥርበት እንደሚሆን መገመቱ ከባድ እንዳልሆነ ይገልጻሉ።

“በሌላ ወገን ግን ለነፃነትና ለዲሞክራሲ ለሚደረገው ትግል አዎንታዊ ተፅዕኖ ያለውን ያህል፣ የራሱ የሆነ አሉታዊ ተፅዕኖም ሊኖረው ይችላል። ምናልባት አገዛዙ የተወሰኑ ነገሮችን የሚያሟላ ከሆነ ተቃዋሚው ኃይል ወደ መመቻመች /ኮምፕሮማይዝ/ ውስጥ በመግባት ለአጠቃላይ ነፃነት የሚደረገው ትግል አደጋ ውስጥ እንዲወድቅ ያደርገዋል። ይህ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ህዝብ የነጻነትና የብልጽግና ጉዳይ የዓለም አቀፍ ኮሚኒቲው በሚፈልገው አካሄድ ብቻ የሚወሰን ይሆናል ማለት ነው” ሲሉ አጠቃላይ ስጋታቸው ያስቀመጡት ዶ/ር ፈቃዱ፣ አጠቃላይ ህዝቡን የሚጠቅም የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የሀብት ክፍፍል፣ በተለይም የመሬት ጥያቄ፣ እስከዛሬ ድረስ የተፈጠረው አዲስ የይዞታና የህብረተሰብ ግኑኝነት፣ የኢትዮጵያ ህዝብና ዲሞክራቶች በሚፈልጉት መንገድ ላይፈቱ በሚችሉበት ሁኔታ መሰናክል ይደርስበታል። ስለዚህ ይህ ዓይነቱ ውሳኔ ህግ የዛሬው አገዛዝ ወደፊት በስልጣን ዙሪያ ሊኖረው የሚችለው ተሳትፎ፣ የኃይል አሰላለፍ ጉዳይና የፓለቲካው አወቃቀርና አካሄድ ጉዳይ ላይ፣ የኢኮኖሚያዊና የህብረትሰብ ግኑኝነት፣ ማለትም የሀብት ክፍፍልና አዲስ ሀብት በአዲስ የኢኮኖሚ ፖሊሲ መሳሪያ የመፍጠር ጉዳይ፣ የማህበራዊ ጥያቄ ጉዳይ፣ እነዚህና ሌሎች ለአገሪቱ የወደፊት እንደህብረተሰብ መኖርና መገንባት አንፃር በሰፊው ካልታየና ተቃዋሚ በሚባለው ጭንቅላት ውስጥ ካልተብላላ አደጋም ሊኖረው ይችላል።

በሌላ አነጋገር የዕድገታችንን ጉዞ ሊያጣምመው ይችላል። ምክንያቱም ይህ ዓይነቱ ውሳኔ ህግ እስከተወሰነ ደረጃ ድረስ ቢሟላና አገዛዙም እንደፖለቲካ ኃይል ተፎካካሪ ሆኖ የሚቆይ ከሆነ ወደፊት ለሚወሰዱ አገርን የሚጠቅሙ የዕድገት ዕርምጃዎች መሰናክል እንደሚሆን መጠርጠር ይቻላል። በሌላ አነጋገር የኢትዮጵያ ህዝብ ከዚህ አገዛዝ ባሻገር ሊገነባው የሚችለው አዲስ ኢትዮጵያ የብዙ ዓመታት ህልም ሆኖ ሊቀር እንደሚችል የራሳቸውን አማራጭ ምልከታ አስቀምጠዋል። ሌላኛውንም መንገድ አካተዋል።
በሌላው በኩል ደግሞ ይህ ውሳኔ ህግ በገዢው መደብ ውስጥ ቅራኔን መፍጠሩ እንደማይቀር፣ ህይወታቸውን ከአሜሪካን መንግስት ጋር ያያዙ ኃይሎች፣ በተለይም ግፊቱ እየበዛ ሲሄድ ወደፊት የሚመጣባቸውን አደጋ በማጤን ውሳኔ ህጉን በከፊልም ሆነ መሉ በሙሉ ተግባራዊ እናድርግ በሚሉ (ዘመናዊ ወያኔዎች) እና ውሳኔ ህጉን አንቀበልም በሚሉ አክራሪ ኃይሎች መሀከል ፍጥጫ መፈጠሩ እንደማይቀር ዶ/ር ፈቃዱ ግምገማቸውን አኑረዋል።

ቀጥሎስ?
በጉዳዩ ዙሪያ ከጎልጉል ጋር ወደፊት ሰፊ ቃለ ምልልስ ለመስጠት ፈቃዳቸውን የገለጹት አቶ ኦባንግ “እዚህ የተደረሰው በወፍ ዘራሽ ዝም ተብሎ አይደለም፤ ብዙ ተለፍቶ ነው። የአውሮፓ አገራት ተመሳሳይ ጥያቄ ሲቀርብላቸው አሜሪካን ምክንያት ሲያደርጉ ነበር። አሁን ሊያቀርቡ የሚችሉት አንዳችም ምክንያት የለም። አጠናክረን ስራችንን እንሰራለን። ሰክነን እንታገላለን። ኢህአዴግ ሳይወድ በግዱ በሩን ይከፍታል” ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። ከአውሮፓ አገራት ጋር አጋሮቻቸው በመሆን ስራቸውን በአዲስ መልክ እያጠናከሩ መሆናቸውን አስታውቀዋል። ይህንን አዲስ ህገ ውሳኔ በማስረጃነትና በማቅረብ የአውሮፓ መንግሥታም ተመሳሳይ እርምጃ እንዲወስዱ፤ በሚሰጡት ዕርዳታም ሆነ ድጎማ ላይ ኢህአዴግን ተጠያቂ በማድረግ የፖለቲካ ምህዳሩ እንዲሰፋ መርዳት ባይችሉም እንኳን ኢትዮጵያውያን ለሚያደርጉት ትግል እንቅፋት እንዳይሆኑ አበክረን እንወተውታለን ብለዋል አቶ ኦባንግ፡፡

አዲስ ስለ ጸደቀው ውሳኔ ህግ ለተጠየቁት “ብዙ ለመናገር ጊዜው ገና ነው። ኢትዮጵያዊያን በጎሳና በዘር የደም አዙሪት ውስጥ እየፈሩ እንዲኖሩ ሲደረግ የነበረው ድጋፍ ግን ማክተሚያው የተቃረበ ይመስለኛል፤ ኢህአዴግ እኔ ሥልጣን ከለቀቅሁኝ በአገሪቷ ውስጥ ደም መፋሰስ ይሆናል፤ ኢንተርሃምዌ የዘር ዕልቂት ይካሄዳል፤ የአፍሪካ ቀንድም ቀውስ ውስጥ ይገባል፣ ወዘተ በማለት እየዘላበደ የተቃዋሚውን ኃይል ከማዳከም አልፎ ሕዝቡ ፍራቻ ውስጥ በማስገባት አሜን ብሎ እንዲኖር የተጠቀመበት ማደንዘዣ ኃይሉ እየደከመ መጥቷል፤ ይኽኛው የውጭው ነው” የሚል ጥቅል መልስ ሰጥተዋል።

የመንታው መንገድ መሃንዲስ – ቻይና?
ቻይና ከኢህአዴግ በተለይም ከህወሃት ከፍተኛ ሰዎች ጋር አላት ከሚባለው “የተለወሰ ሽርክና” አንጻር አሜሪካ የምትሰጠውን የበጀት ድጎማና ርዳታ በየዓመቱ እየሸፈነች ኢህአዴግን ትታደጋለች የሚለው ጉዳይ ቻይና ከምትከተለው መሰረታዊ የንግድ እምነትና አንጻር በዜሮ የሚባዛ እንደሆነ ይነገራል። ቻይና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ነዳጅና ማዕድን እየተከተለች የምትገባበት ኢንቨስትመንት እያከሰራት እንደሆነ የሚናገሩ ክፍሎች ቻይና የሃይል ሚዛኑን ተመልክታ ርምጃዋን ከማስተካከል ያለፈ ስራ እንደማትሰራ ይናገራሉ።

በሌላ በኩል ደግሞ ሰሞኑን ይፋ ሆኖ የሰነበተውና የቻይናን “የዓይን ቀለም” የቀየረው የጃፓኑ ጠ/ሚ/ር የኢትዮጵያ ጉብኝትና የፖለቲካ መሞዳሞድ በቻይናና በኢህአዴግ መካከል የግንኙነት መሻከር እንደሚፈጥር የፖለቲካ እሳቤ አለ፡፡ ኢህአዴግ ከቻይና ታሪካዊ ጠላት ጃፓን ጋር በግልጽ ይህንን ዓይነቱን “ያደባባይ ፍቅር” ማሳየቱና የፖለቲካ ቅርጫ ውስጥ መግባቱ የምዕራቡ ወዳጅ ከሆነችው ጃፓን ጋር በመወገን በምዕራባውያን የድጎማ ዕቀባ ጭስ እንዳይታፈን መተንፈሻ እየፈለገ መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡
ሰጥቶ በመቀበል፣ አበድሮ በመውሰድና የአምባገነኖችን ህልውና ለማስጠበቅ የሚውል ቴክኖሎጂን በመገንባት አፍሪካን እያለበች ያለችው ቻይና ኢህአዴግ ከምዕራባውያን የሚያኘው እርዳታ ቢቋረጥበት ከብድር በዘለለ በየዓመቱ ሌሎቹ እንደሚያደርጉት በጀት እየደጎመች የኢህአዴግን ነፍስ ለመጠበቅ የምትምልበት ዘመን ሊኖር እንደማይችል ከግምት በላይ የሚናገሩ ክፍሎች፣ ኢህአዴግ መለሳለስ በመሳየት ቆዳውን ሊቀይር ይችላል የሚለው እምነት አላቸው። አሜሪካ አሁን የያዘችው አቋም ከምትከተለው አዲሱ ፖሊሲዋና በሂደት የኢትዮጵያ ጉዳይ ተመርምሮ የተያዘ ስለሆነ እንደ HR2003 በውስዋስ (ሎቢ) ሊቀለበስ የሚችል እንዳልሆነ አጥብቀው ይናገራሉ።

ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር መጀመሪያ ላይ ለጎልጉል አስተያየት የሰጡ ዲፕሎማት ጠቅሰን ገመዱ በኢህአዴግ ላይ እየከረረ እንደሚሄድ በዘገብን ወቅት “ኢህአዴግ በቅርቡ የአውሮፓ ህብረት ተወካዮች እስር ቤቶችን እንዳይጎበኙ እንደከለከለው ማድረግ አይችልም … በደቡብ ሱዳን ያለው የፖለቲካ ቀውስ፣ በሶማሊያ ጭብጡ ያለየለት ሁከት፣ በኤርትራ ያለው የዛለ መንግስት እጣፈንታና የኢትዮጵያን ህዝብ በዘር ከፋፍሎ ጥቂቶች እንዲበለጽጉ ያደረገው ኢህአዴግ መጨረሻው አሜሪካንን በእጅጉ ሃሳብ ላይ ጥሏታል። በዚህም የተነሳ ኢትዮጵያ ውስጥ እየሰፋ የሄደው ቁርሾና የጥላቻ ፖለቲካ ሳይፈነዳ ኢህአዴግን ማረቅ የአሜሪካ ቀዳሚ አጀንዳ ሆኗል። ይህንን አጀንዳ አሜሪካ በቀላሉ ተጭበርብራ የምትቆልፈው አይሆንም። ኢህአዴግ በጎሳ ደምና እኔ ከሌለሁ አገርና አፍሪካ ቀንድ ይተራመሳል በሚል የሚነግደውን ንግድ አሜሪካኖቹ ተረድተዋል ብለን ነበር፡፡ የአሜሪካው ምክርቤት እንደራ የሆኑት ክሪስ ስሚዝ “በሽብር ዙሪያ ከአሜሪካ ጋር ተባብሮ መስራት ህዝብን ለማፈንና ረግጦ ለመግዛት ዋስትና አይደለም” በማለት መናገራቸውን ከዲፕሎማቱ አስተያየት ጋር አክለን ነበር፡፡

አዲስ የወጣውን ውሳኔ ህግ አሜሪካ በኢህአዴግ ላይ ፊቷን እያዞረች መሆኗን ማሳያ ነው በማለት የሚወስዱ ክፍሎች ይህ ህግ ከቀድሞው HR2003 ፈጽሞ የተለየ እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ የዛሬ አስር ዓመት፤ HR2003 በምክር ቤት ደረጃ የእንደራሴዎችን ከፍተኛ ድጋፍ ካገኘ በኋላ የሕግ መወሰኛ ም/ቤት (ሴኔት) አጽድቆት በፕሬዚዳንቱ ተፈርሞ የአሜሪካ ፖሊሲ እንዳይሆን በመደረጉ ተቋማዊና አስተዳደራዊ ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ ጉዳዮች መከኑ። በወቅቱ የህጉ መርቀቅና እንዲጸድቅ የተጀመረው እንቅስቃሴ ያስበረገገው ኢህአዴግ ጡረተኛ የሴኔት አባላት ከሚመሩት ዲኤልኤ ፓይፐር ከተባለ የውስዋስ (ሎቢ) ቡድን ጋር ከፍተኛ በጀት በጅቶ ታገለ። ባፈሰሰላቸው መጠን ወትዋቾቹ ባልደረቦቻቸውን ጠመዘ&#48

የአንድ ብሄር የበላይነት እና አድሏዊነት ካልተወገደ ሰራዊቱ እንዳይታመስ ያሰጋል::

በወያኔ እና በኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት የጦር መኮንኖች እና ወታደሮች መሃል ጋብ ያለው ጡዘት ጊዜውን እየጠበቀ እየገነፈለ መሆኑን ውስጥ አዋቂ ምንጮች ለምንሊክ ሳልሳዊ በላኩት መልእክት ጠቁመዋል::በሕወሓት ጄኔራሎች የሚመራው የመከላከያ ሰራዊቱ የበታች የጦር መኮንኖችን ከዚህ ቀደም ለመከላከያ ደህንነት ቢሮ ባስተላለፈው መመሪያ መሰረት ከሰራዊቱ መቀነስ ያለባቸው የቀድሞ የብኣዴን እና የኦሕዴድ ታጋዮች የነበሩ የጦር መኮንኖች ዝርዝር ተጠንቶ ለኢታማጆር ሹሙ የቀረበ እና ይህንንም መሰረት አድርጎ መኮንኖቹን ከሰራዊቱ ውስጥ ለመቀነስ መታቀዱን ምንጮቹ ገልጸዋል::

እንደ ምንጮቹ መረጃ ከሆነ ከቀረቡት 2369 ከምክትል መቶ አለቅነት እስከ ኮሎኔልነት ማእረግ ያላቸው የቀድሞ የበረሃ ታጋዮች የአሁን መኮንኖች ውስጥ አላስፈላጊ የሚባሉት ተጣርተው ከሰራዊቱ በዳረጎት የሚቀነሱ ሲሆን ከደርግ ስርኣት ጋር ቁርኝት የነበራቸው ከብሄራዊ ውትድርና ሰራዊቱን የተቀላቀሉት በቦርድ እና በጤንነት እክል በጡረታ የሚሰናበቱ እንዲሁም በማስጠንቀቂያና በደምወዝ ቅጣት የሚታለፉ እንዳሉም ታውቋል:: ይህንን ሁሉ ችግር የፈጠረው በመሃከላቸው የተነሳው የአንድ ብሄር የበላይነት እና አድሏዊነት የዘር ቆጠራ የፖለቲካ ሕዝባዊ ጥያቄዎች እና የሕገመንግስት ተግባራዊነት ክርክር የጫረው አለመግባባት ሲሆን በሰርኣቱ ውስጥ የተጠየቀው የጥቅማ ጥቅም ጥያቄም ሌላኛው መነካከሻ መሆኑን ምንጮቹ ተናግረዋል::

ይህ በእንዲህ እንዳለ በሃገር ውስጥ እና በአለማቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተቃውሞ እየደረሰበት ያለውን የወያኔውን የአሸባሪነት ሕግ በሕገመንግስቱ ውስጥ ለማካተት ጥናት ሊጀመር ሲሆን ከዚህ ቀደም እንደነበረው የአደገኛ ቦዘኔዎች ሕግ በሂደት አይን እያየ አሁን ያለውን የአሸባሪነት ህግ ማክሰም የሚል ሃሳብ ተይዞ ጥናቱ እንደሚካሄድ ታውቋል::ምንልክ ሳልሳዊ

እንዳለ ጌታ ከበደ

(የ2005 ዓም የ‹በጎ ሰው› ሽልማት ተሸላሚ)

በልቦለድ መጻሕፍቱና በፕሬስ ውጤቶች ላይ በሚያወጣቸው መጣጥፎች የምናውቀው እንዳለ ጌታ ከበደ ‹‹ማዕቀብ›. የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ እያስነበበን ነው፡፡ መጽሐፉ ስለሳንሱር፣ ስለ ደራስያንና  ስለ አሮጌ መጻሕፍት አከፋፋዮች የሚተርክ ነው፡፡

የእንዳለ ጌታ ‹ማዕቀብ›› ለየት ያሉ ነገሮችን ያሳየናል፡፡ ሳንሱር በንጉሡ፣ በደርግና በኢሕአዴግ ዘመን ምን ጠባይ እንደነበረው፣ እነማን በሳንሱር እንደታረዱ፣ እንደተደረቱና እንደተቦጨቁ ይተርካል፡፡ ትረካው ሳንሱር ያሳቀቃቸውን ደራስያን ብቻ ሳይሆን በሳንሱር መሥሪያ ቤቱ ተቀምጠው ሳንሱር ሲያደርጉ የነበሩ ሰዎችንም ትረካ ያካተተ ነው፡፡

የሳንሱር ስም ሲጠራ እንደ ሰይጣን ስም ቆጥረውት ‹በስመ አብ› የሚሉ ደራስያን ያሉትን ያህል ‹‹ሳንሱር መኖር ነበረበት፣አሁንም መኖር አለበት›› ብለው የሚያስቡ የሳንሱር ባለሞያዎችንም አስተያየትና ሙግት ታነቡበታላችሁ፡፡ በዚህ የሳንሱር ትረካ ከዚህ በፊት ያልሰማናቸው፣ ብንሰማቸውም በተሟላ ሁኔታ ያልሰማናቸውን የሀገራችንን የደራስያን መከራዎችና ተጋድሎዎች ታነባላችሁ፡፡ ኢትዮጵያ እንዴት ታላላቅ የሃሳብና የድርሰት ሰዎቿን እንዳጣች ታያላችሁ፤ ማስፈራራት፣ ግርፋት፣ እሥር፣ አካላዊ ጥቃት፣ ስደትና ግድያ ስለተፈጸመባቸው ደራስያን እያስነበበ ወደኋላ ይዟችሁ ይነጉዳል፡፡

ያውም የሚያወራችሁ እንዳለ ጌታ አይደለም፡፡ የሚያቀርብላችሁም ደረቅ የጥናት ጽሑፍ አይደለም፤ ራሱ ሳንሱር ነው በሰውኛ የራሱን ታሪክ የሚተርክላችሁ፡፡

ሳንሱርን ስትሻገሩ ደግሞ የኢትዮጵያን ደራስያንን የሕይወት ገጠመኝ ይጋብዛችኋል፡፡ ከልደት እስከ ሞት በሚተርክ የሕይወት ታሪክ አጻጻፍ መንገድ አይደለም፡፡ ከታሪካቸው አንድን ሳቢ ጉዳይ መርጦ፣ አንዳንዱን ራሱ ያየውን፣ አንዳንዱን የሰማውን፣ አንዳንዱን ደግሞ ያነበበውን፡፡ አንዳንዱ አስገራሚ፣ አንዳንዱ አሳዛኝ ሌላው ደግሞ አናዳጅ ታሪክ ነው፡፡ እንዳለ ጨዋነት በተሞላበት መንገድ የደራስያኑን ክፉና ደግ ገጽታ ያሳየናል፡፡ ሱስና መጠጥ እንዴት አድርጎ የብዙዎችን ታላላቅ ደራስያን ሕይወት እንደቀጠፈ በኀዘን እናያለን፡፡ በሕይወታቸው ዘመን ታዋቂ የነበሩት ደራስያን የነበራቸውን የድህነት ሕይወት እንታዘባለን፡፡ አንዳንዶቹ በቅዱሳን ገድል ላይ የምነባቸውን የደግነት ሥራዎች  ሳናውቃቸው እንዴት ይሠሩ እንደነበር አይታችሁ ትደነቃላችሁ፡፡

በመጨረሻው ክፍል በሀገራችን ታሪክ ታላቅ ቦታ ካላቸው ነገር ግን ምንም ቦታ ካልተሰጣቸው ወገኖች አንዱ የሆኑትን የአሮጌ መጻሕፍት አከፋፋዮች ታሪክ የያዘውን ክፍል ታገኛላችሁ፡፡ እጅግ መሳጭ ታሪክ፣ ብዙ የማናውቃቸው የሀገራችን ጉዶች፡፡

 የራስዋ የሆነ ፊደል ባላት ሀገር መጻሕፍት ፀረ አብዮት ሆነው እንዴት እንደተቃጠሉ፤ እንዴት የታሪክ መዛግብት በኪሎ እንደተሸጡ፣ ዛሬ የምንኮራባቸው የድርሰት ሀብቶቻችን እንዴት ተወግዘው ከመደርደሪያ እንደተባረሩ ይተርክልናል፡፡ ተራኪው እንዳለ አይደለም፡፡ እየዞረ ያነጋገራቸው ከአርባ ዓመት እስከ ሃያ ዓመት በአሮጌ መጻሕፍት ሽያጭ የተሠማሩ ክቡራን ናቸው፡፡

እነማን ነበሩ እዚያ የሚመጡት? እነማንን ያደንቃሉ? ማን ምን ዓይነት መጽሐፍ ይገዛ ነበር? እነማን አንባቢ ናቸው? እነማን ደግሞ የንባብ ፀር፣ ጉዳችንን ይዘረግፉላችኋል፡፡ የታላላቅ ሰዎችን መጽሐፍ ልጆቻቸው አውጥተው የሸጡበት ታሪክ፣ በልጆቻቸው የተሸጠባቸውን መጽሐፍ አባቶች መልሰው የገዙበት ገጠመኝ፤ የታላላቅ ሰዎች ፊርማ ያረፈባቸው መጻሕፍት እንዴት ወደ አሮጌ ተራ እንደሚመጡ ያወጓችኋል፡፡ ዕውቀትን ለሕዝብ ለማከፋፈል ሲሉ አሮጌ መጻሕፍት ሻጮች የተቀበሉትን ስቃይና መከራ ይተርኩላችኋል፡፡

እኔ እንዲያውም በአዲስ አበባ ከተማ የሚሠሩ አደባባዮች በማናውቃቸው የውጭ ኩባንያዎች ስም ከሚጠሩ ምናለ አንዱን እንኳን ‹የአሮጌ መጻሕፍት ሻጮች አደባባይ›› ብንለው ብዬ አስቤያለሁ፡፡ እነርሱ ነበሩ የመረጃ መቀባበያዎቻችን፣ እነርሱ ነበሩ የታሪክ ምንጮቻችን፣ እነርሱ ነበሩ አያሌ መጻሕፍትን ከመቃጠል አድነው ለዘመናችን ያደረሷቸው፡፡

ዋጋው 60 ብር ብቻ ነው፡፡ ከጀመራችሁት ደግሞ ሳትጨርሱ አታቆሙትም፡፡ አንቡትና ተደሰቱ፡፡

መልካም ንባብ

በቅርቡ ለንባብ ካበቃው መጽሐፍ ጋር በተያያዘ የስም ማጥፋት ክስ የተመሰረተበት የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ ሆነው ደራሲ ዳንኤል ተፈራ ዛሬ በድጋሚ ማዕከላዊ እንዲቀርብና በድጋሚ የተከሳሽነት ቃሉን ከሰጠ በኋላ በመኪና ሊብሬ ዋስ ከእስር ተፈቷል፡፡ ኢህአዴግ በመንግስት እና በተለጣፊ ፓርቲዎች አማካኝነት በአንድነት ፓርቲ አመራሮችና አባላት ላይ የእስር ዘመቻ መክፈቱ ይታወቃል፡፡

የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የብአዴን ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ አለምነው መኮንን መኖሪያ ቤት በድንጋይ መደብደቡን የፍኖተ ነፃነት ምንጮች ጠቆሙ፡፡ የፍኖተ ነፃነት ምንጮች እንጠቆሙት ባሳለፍነው ሳምንት የካቲት 1 እና የካቲት 2 ቀን 2006 ዓ.ም(ቅዳሜና እሁድ) ለሊት በተደጋጋሚ ማንነታቸው ባልታወቀ ግለሰቦች መኖሪያ ቤታቸው በድንጋይ መደብደቡን ተከትሎ ቤታቸው ቀንና ለሊት በፖሊስ እየተጠበቀ ይገኛል፡፡ አቶ አለምነው መኮንን የአማራን […]

“ኢትዮጵያዊ ነኝ፤ ኢትዮጵያዊ ማንነት አለኝ” ብዬ ስል የራሴ (የግሌ) ማንነት የለኝም ማለት አይደለም። የአከባቢ ማንነት የለኝም ማለት አይደለም። የክልል (የብሄር) ማንነት የለኝም ማለት አይደለም። ወይም እነዚህ የተለያየ ደረጃ ያላቸው ማንነቶቼ መጥፋት አለባቸው ማለት አይደለም። እኔ ኢትዮጵያዊ ነኝ ስል የራሴን ማንነት አልቀበልም ማለት አይደለም። የራሴ ማንነት ስላለኝ ነው ኢትዮጵያዊ ማንነት ሊኖረኝ የቻለው። እኔ የግል ማንነት ባይኖረኝ […]

አስገራሚው የሳውዲው “ኮራጅ ” አባት ምክር ነገሩ እንዲህ ነው …ከ20 ዓመት በፊት ሳውዲው ወጣት ራሱን ለሁለተኛ ደረጃ ፈተና ከማዘጋጀት ይልቅ በረቀቀ መንገድ ለፈተናው መልስ የሚሆነውን ማጭበርበሪያ የመልስ ወረቀት አዘጋጅቶ ለፈተና ይቀርባል። ፈተናውን በረቀቀ መንገድ አጭበረብሮ ሰርቶታልና ፈተናውን በተገቢ ውጤት አልፎ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ለማለፍ በቃ ! ከዚያም በታዋቂው ዩኒቨርሲቲ ትምህርቱን ተከታትሎ ይመረቃል። ይህ ሁሉ አልፎ […]

ክፍል አንድ በቀናት አቆጣጠር ሰባተኛው እረድፍ በምትይዘው በዕለተ ቅዳሜ ከዚህ ቀደም በጸረ ሽብር አዋጁ ዙሪያ ካደረግነው የተሟሟቀ ክርክር በኋላ ከገዥ ፓርቲ ጋር በሃሳብ ክርክር ለ11 ሰዓታት የተሟገትነው ቅዳሜ ጥር 17 ቀን 2006 ዓ.ም ባለፈው ሳምንት ነበር፡፡ ይህ መድረክ የተዘጋጀው በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በጋዜጠኝነት እና ኮሚዩኒኬሽን የድህረ ምረቃ ተመራቂ ተማሪዎች ከትምህርት ቤቱ ጋር በመተባበር እንደነበረ ከደረሰን […]

(በጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ፤ ከዝዋይ ማረሚያ ቤት) ምንጭ ኢትዮ-ምኅዳር ጋዜጣ
የነገሮች ሁሉ መድረሻ እስር ቤቶች እየሆኑ መጥተዋል፡፡

‹‹ይህንን ስለመሳሰሉ ጉዳዮች መወያየት ክልክል ነው፡፡›› በማለት በተንጎላጀጀ ድምፅ ጠባቂው ተናገረ፡፡ ቀጠል አደረገናም ‹‹መነጋገር የምትችሉት ስለቤተሰብ ጉዳዮች ብቻ ነው›› በማለት ተናገረ፡፡ ይህን ከላይ ያለውን ሐሳብ የሚመለከት ማንኛውም አንባቢ፣ ጉዳይ የተፈፀመው እዚህችው እማማ ኢትዮጵያ ሰማይ ስር ባሉ አጃኢበኛ እስር ቤቶች፣ ቤተሰብ መጠየቂያው እንደሆነ መጣራቱ አይቀርም፡፡

ይሁንና በመግቢያው ላይ ያለው ጽሑፍ ተቀንጭቦ የተወሰደ ‹እናት› ከተሰኘውና እ.ኤ.አ. በ1906 ከታተመው የስመ ጥሩው ሩስያዊ ደራሲ ማክሲም ጎርኪይ ታሪካዊ ልቦለድ ገፅ 102 ላይ ነው፡፡ የዛሬ 108 ዓመት አካባቢ ማለት ነው፡፡ አቤት ርቀቱ!… ይህ ርቀት ግን ለእኛ ምንም ማለት ያልሆነ ይመስላል፤ ለምን? ቢሉ ዛሬም ይህንንና ይህን የመሳሰለውን አስፍተን እየሠራን እንገኛለን፡፡ እንዲያውም በአንዳንድ ሁኔታዎች እየተጓዝን ያለነው የቁልቁለት ሩጫ በእጅጉ አሳሳቢ ሆኖ ይገኛል፡፡

የነገሮች ሁሉ መድረሻ እስር ቤቶች እየሆኑ መጥተዋል፡፡

‹ጠበቅ ያለ እርምጃ፣ የማያዳግም እርምጃ፣ የማስወገድ እርምጃ፣…› ወዘተ የሞሉ ከሕግ መርሕዎች ሳይሆን ከጥላቻ ፖለቲካ የሚመነጩ ፀያፍ አነጋገሮችን በሕዝብ የመገናኛ ዘዴዎች ሲተላለፉ እየሰማን እየታዘብን ነው፡፡ ቃል በቃል ‹ቀይ ሽብር ይፋፋም› ብሎ ማወጅ የቀራቸው የሕግም የግብረገብም ሚዛን ያልወጣላቸው ቀረርቶች በተለይ በእስር ቤት የምንገኝ ኢትዮጵያውያንን እየሰበሰቡን ይገኛሉ፡፡

ዝዋይ የአገራችን ‹ሳይቤሪያ ግዞት›

በኢ.ቴ.ቪ. የአብዮታዊ እርምጃ ፕሮግራሞች በቀረቡ ማግስት አሁን በዝርዝር ብለው የብዙ ቤተሰቦችን ስሜት ሊያሸማቅቁ የሚችሉ ሰቆቃና እንግልቶች በአስደማሚ ስልት ተቀናብረው ተፈፃሚ ይሆናሉ፡፡ እስኪ የተወሰኑትን እንይ፡፡ ማንኛውም ታሳሪ ቤተሰብ በቅርብ ሊጎበኘው በሚችለው እስር ቤት ይታሰር የሚለው ሕግ የተሻረው በእኛ ላይ ነው፡፡ ዝዋይ የአገራችን ‹ሳይቤሪያ ግዞት› ማለት ናት፡፡ ቤተሰብ ያን ያህል የበርሃ ጉዞ አቋርጦ የእኛዋ ሳይቤሪያ ሲደርስ በአድካሚና ግብረ-ገብ በጎደለው ፍተሻ መከራውን ማየቱ አንሶ ጆሮ ግንዱ ላይ በቆሙ የቤተሰብ አገናኞች ቤተሰባዊ ገመናውን አሳልፎ ይሰጣል፡፡ ሕፃናት ልጆች ወላጆቻቸው አንድ ላይ ሆነው ናፍቆታቸውን መወጣት አይችሉም፡፡ አንዳንድ ጊዜ ፖሊሶቹ ሲዘናጉልን ልጆቻችንን አቅፈን እንስማለን፡፡ ይህ ከሆነ ቁጣና ዘለፋው ምንም አይደለም፡፡ ግን በሁኔታው ሕፃናቱ ክፉኛ ይበረግጋሉ፣ የእኛ ስጋት ይጋባባቸዋል፤ በዚህም መንፈሳቸው እርብሽብሽ ብሎ ወደቤታቸው ይመለሳሉ፡፡

ሁኔታው በዚህ አያበቃም፡፡ ምንም እንኳን የመጠየቂያ ሰዓቱ በግልፅ የተቀመጠ ቢሆን ከቤተሰቦቻችን ጋር ገና መነጋገር ስንጀምር ‹‹በቃ… ቶሎ ጨርሱ›› የሚባልባቸው ጊዜዎች ብዙ ናቸው፡፡ ቀጥሎ የሚመጣው የእስር ቤት ማኅበራዊ ጉዳዮችን ማለትም ለሳሙና፣ ለምግብ ማጣፈጫ፣ ለሻይ ለቡና፣ ለውስጥ አልባሳት፣ ለውኃ ማከሚያ/ውኃ አጋር/ ወዘተ፤ ገንዘብ የሚያስፈልገን ቢሆንም እና እንደሚያስፈልጉ ቢታወቅም ጉዳዩ ለይቶለት የማሰቃየት፣ ማንገላታት፣ መበቀል ሆኗልና ለአንድ ወር ከአንድ መቶ ብር በላይ መጠቀም እንዳንችል የተከለከልን የመሆኑ አሳፋሪ ሐቅ ነው፡፡ ይህ እየተፈፀመ ያለው ደግሞ ዝዋይ እስር ቤት ውስጥ ብቻ ነው፡፡ በዚህ የተነሳም ለመግለጽ በሚከብድ ሁኔታ ሰብኣዊ ክብራችንን የማዋረድ ሙከራዎች እየተፈፀሙ ነው፡፡
በአገራችን ላይ እኔ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቴን የጨረስኩት ዝዋይ በመሆኑ ብዙ ወዳጅ ዘመዶቼ በእዚህ ይገኛሉ፡፡ ሆኖም ለአካባቢው ነዋሪዎች በሳምንት እንዲጠይቁን የተፈቀደላቸው አንድ ቀን /ረቡዕ/ ብቻ ሲሆን ‹‹የት ነው የምታውቁት? እንዴት አወቃችሁት? ምንድን ነው የሚያመላልሳችሁ?›› በሚሉትና በሌሎችም ጥያቄዎች ተደናግጠው መምጣቱን እርግፍ አድርገው ትተውታል፡፡

ሀገሩ ሞቃታማ ነውና በዚያ ላይ በእያንዳንዱ ቤት እስከ 150 ሰው ይታሰርበታል፡፡ ይህ ሁሉ ተደማምሮ እስረኛው የቱንም ያህል ፅዳቱን ለመጠበቅ ቢሞክርም የተባዩ መርመስመስ የእነ ትኋን እንዲህ መራባት፤ ለማሰብ እንኳን ይዘገንናል፡፡ ሌሊቱን ሙሉ ገላን ሲቆፍሩ ማደር ነው፡፡ ሊናገሩት ይከብዳል፣ አንባቢንም ቅር ያሰኛል፤ ግን ይህ የፊልም ትረካ ሳይሆን በእማማ ኢትዮጵያ ልጆች ላይ ሆን ተብሎ እየተፈፀመ ያለ ደባ ነው፡፡ […] ግን የባሰ አታምጣ ማለት ነው!

የዝዋይን ልጅ ውሃ ጠማው

ግን የባሰ ነገር አለ፡፡ አፈር ቅጠል የማይል ምግብ ይቀርብናል፡፡ ‹በደንባራ በቅሎ ቃጭል ተጨምሮ› ከፍተኛ የውኃ እጥረት /ዝዋይ ሀይቅ አናት ላይ ተቀምጠን/ አለ፡፡ የእስር እስር እንዲሉ ጄኔራል መኮንኖቹን ጨምሮ አብዛኛዎቹ አባሪዎቻቸውና ሌሎች ሌሎች የተወሰንን እስረኞች የምንገኘው በልዩ ቅጣት ጭለማ ቤት ውስጥ ነው፡፡ ይህንን ሁሉ እንደምንም ለመቋቋም ጥረት ማድረግ ይቻል ይሆናል፡፡ አዲሱ ስልት ግን መዘዙ በጣም አደገኛ በመሆኑ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ፣ እያንዳንዱ ሃይማኖት ያለው፣ ፈርሐ እግዚአብሔር ያለው፣ እያንዳንዱ የመሠረታዊ ሰብኣዊ መብቶችና ነጻነቶች መከበር የሚያሳስበው እያንዳንዱ ሰው የሆነ ሰው ሁሉ ሊያውቀው ይገባል ስንል ድምፃችንን እናሰማለን፤ በሕክምና ንፍገት ወደሞት እየተገፋን ነው፡፡

ሕመም ካልታከመ መጨረሻው ሞት ነው፡፡ የሞቱም ሰዎች አሉ!

ከወር በፊት ገደማ ወጣቱ የአንድነት ፓርቲ አባል ናትናኤል መኮንን ለሕክምና በሪፈር ወደ ቃሊቲ ተልኮ የነበረ ቢሆንም፣ የዛኑ ዕለት ሕክምናውን ተነፍጎ ከሌሊቱ 5፡00 ሰዓት አካባቢ እንዲመለስ ተደርጓል፡፡ እስካሁን በሕመሙ እየተሰቃየ ይገኛል፡፡ የኢብአፓ ሊቀመንበር የነበረው ዘሪሁን ገ/እግዚአብሔር እንደዚሁ ለተጨማሪ ሕክምና ሪፈር ተብሎ ሲጠባበቅ ከቆየ በኋላ ዘዴው ተፈፃሚ ሆነበት እጁን አጣጥፎ ተቀምጧል፡፡ ከሕመሙ ጋር በተያያዘ በአካሉ ላይ አሳሳቢ ሁኔታ እየታየበት ይገኛል፡፡ ከዚህ ቀደም ገልጬው የነበረው የእኔ የኩላሊት ሕመም አሁን ለመቀመጥም፣ ለመንቀሳቀስ እያወከኝ የሚገኝ ሲሆን፣ እኔን ከቃሊቲ ዝዋይ ለማምጣት የተደረገው የተቀናጀ መረብ ሩብ ያህሉን ለሰብኣዊነት አውለውት ቢሆን ኖሮ እኔም ፋታ፣ እነሱም እርካታ ባገኙ ነበር፡፡ ሕመም ካልታከመ መጨረሻው ሞት ነው፡፡ የሞቱም ሰዎች አሉ!

የጄኔራል መኮንኖቹ አባሪዎች የነበሩት ኮረኔል ተስፋዬ ኃይሉ እና ኢንጂነር ክፍሌ ስንሻው፣ በዶክተር መረራ በሚመራው ኦሕኮ ፓርቲ አባል የነበሩት አሕመድ ነጃሺ፣ በጭለማ ቤት የከረመው ተስፋሀን ጨመዳ፣ የቤንሻንጉሉ አዛውንት ወዘተ ተገቢውን ሕክምና በማጣት ሕይወታቸውን ያጡ የእማማ ኢትዮጵያ ልጆች ናቸው፡፡ እንዴት ሕክምና ይከለከላል!? ግፍና ጭቆና ተቃውመው ደማቸውን ያፈሰሱና አጥንታቸውን የከሰከሱ ታጋዮችን በሥልጣን ማግስት ከፍርድ በመለስ በየእስር ቤቱ ያሉ ኢትዮጵያዊ ወገኖቻቸው በሕክምና እጦት ሲረግፉ በእርካታ ማርመምን ከየት ተማሩት!? የኢትዮጵያ ሕዝብስ ምን ይላል!? ሰው የሆኑ ሰዎች ሁሉ ከቶ ምን ይላሉ!?

እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ!

ምንሊክ ሳልሳዊ:-አሜሪካ ውስጥ ያፈንዳ የገደለ ይተኮሰ የፈጀ …. አሜሪካዊ ዜጋ አሸባሪ ተብሎ ሲከሰስ ሲዘለፍ አላየንም ይልቅ እብድ ንክ ምናምን በሚል ከእስር ቤት ወደ ፍርድ ቤት እና ምርመራ ይሄዳል:: አሜሪካንም እኮ የአሸባሪዎች ህግ አላት:: ሆኖም ዜጎቿን አታጠምድበትም:: ከሌላ አገር ዜጋ ጋር አያይዛ ቲለጥፈዋለች … የአሜሪካ ዜግነት እንኳን ቢኖረው ኦሪጂኑን ነው የምትጠራው እንጅ አሜሪካዊ አሸባሪ ብላ አደባባይ ዜጎቿን በንዝህላልነት አታስርም አትገልም አታንገላታም:: ሌሎችም አገራት እንዲሁ …በአሸባሪነት ህግ ዜጋን አያጠምዱም :: የአሸባሪነት ህግ ከምንጩ በአሸባሪነት አሜሪካን የመዘገበቻቸውን አሸባሪ ድርጅቶች (ሕወሓትን ይጨምራል) ለመዳኘት የወጣ ነው::

እዚህ ጋ ግን ሲመጡ እኛ አገር የህጉ ትርጉም ለየት ብሎ እያየነው ነው::በዚህ ህግ ይዳኛሉ የተባሉት እነ አልቃይዳ እና የታጠቁ መሰሎቹ ሳይሆኑ የተዳኙበት የራሳችን ዜጎች የሆኑ ኢትዮጵያውያን ያውም ያልታጠቁ ብእር እና ወረቀት ያነገቡ የህዝብን ነጻነት እና መብት ያስተማሩ ወዘተ… ናቸው:: በአለም አቀፍ ደረጃ አሸባሪነትን ለመቆጣጠር የተባለው ዜጎችን ማጥመድ መሆኑ አሳሳቢነቱ እንደተጠበቀ ሆኖ በሃገራችን አሸባሪነ የተባሉት ግን የማናውቃቸው ሰዎች ሳይሆኑ መንግስትን በይፋ የተቃወሙ ለውጥ የጠየቁ የፖለቲካ መሪዎች ጋዜጠኞች እንዲሁም ሃይማኖታዊ ነጻነታቸውን የጠየቁ የሃይማኖት ምሁራን ናቸው::እንዲሁም የሰብኣዊ መብታቸው ተጥሶ ከህጉ ውጪ በላያቸው ላይ ከባድ እና አደገኛ የሆነ ፕሮፓጋንዳ እየተካሄደባቸው ሳይመሰከርባቸው እና ማስረጃ ሳይቀርብባቸው ወንጀለኛ ተደርገው እንዲታዩ ተደርጓል::

ይህ የሽብር ህግ በተለያየ ጊዜ እንዲስተካከል እና እንዲለወጥ እንዲሻሻል ዜጎችን ማጥመድ እንዲያቆም .. የተለያዩ ቡድኖች አገሮች እና ኢትዮጵያውያን የገዛ የወያኔ ስርኣት አባላት ሳይቀሩ እየተናገሩ ነው :: ግን የወያኔው ጁንታ ይህንን ለስልጣን ማስረዘሚያ እና ለተቃዋሚዎች ማፈኛ እየተጠቀመበት ነው::በአለም አቀፍ ደረጃ አሸባሪ እንደሆነ የሚታወቀው ሕወሓት ምእራባውያን እየነቁ እንዳይነቁ አድርጎ እያጭበረበራቸው በሚያገኘው የብድር እና የእርዳታ ገንዘብ ዜጎችን ለማፈን እና ለመግደል እየተጠቀመበት ነው::ይህ የሽብር ህግ የማያፍናቸው አፋኞቹን የአገሪቱ ባለስልጣናት እና በተቃዋሚ ውስጥ የተሰገሰጉ ባላንጣዎችን የሚያሳፍኑ ብቻ ነው::

ይህንን ህግ በተመለከት መፍትሄ ከማምጣት ይልቅ በየጊዜው ለማፈኛነት መጠቀምን የመረጠው የወያኔ ጁንታ ከትግራይ እስከ ሞያሌ ከጋምቤላ እስከ መልካጀብዱ እና ጎደ በሃገሪቱ በተለያዩ ማእዘናት ዜጎችን በማሳደድ ሰርተው እንዳይኖሩ እንዲፈናቀሉ የፖለቲካ እምነታቸውን እንዳያራምዱ እንዳይጽፉ እንዳያነቡ በማድረግ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ሽብርን እየነዛ አሸባሪ እያረገ በማሰር ከአገር ተሰደው እንዲወጡ በማድረግ እና በመግደል ጭምር ወንጀል እየፈጸመ ስለሚገኝ ህዝቦች በጋራ ታግለን ስርኣቱን መቃብር ልንከተው ይገባል::

ምንሊክ ሳልሳዊ:-ሕንፃ- መኪና -ቪላ -ኢሮ -ብርና ዶላር -ጠበንጃ እና ቦምብ- እየተቆጠረ ሙስና እንደሚወራልን ሁሉ … የሃገሪቷን ዜጎች የጎዳ ;ሕግን እና ህገመንግስትን ያጣመመ; የራሱ መንግስት ያለውን;የፖለቲካ ባላንጣዎችን እና የግል ቂምበቀሉን ተገን አድርጎ የተንቀሳቀሰ ; መብት ጥሰት የፈጸመውን ;የዜጎችን መብት ያፈነውን ;ህገወጥ ተግባር በዜጎች ላይ የፈጸመውን ;ከህገወጦች ጋር የተባበረን ተቆጥሮ ;በፖለቲካ ሙሰኝነት መች ነው ለፍርድ የሚቀርበው??

በሃገሪቱ የኢኮኖሚ አውታሮች ላይ በሕወሓት መሪነት እየተፈጸመ ያለው ደባ እጅግ በረቀቀ መንገድ ከመስፋፋቱም በላይ በሙስና ስም የሚጠመዱ ሰዎች በውስጥ የፖለቲካ ቁርሾ ላይ የተለየ ሃሳብ ያነገቡ እና ስውር እጆች የሚያጠምዷቸውን እንደሆነ እያየን ነው ይህ ራሱን ችሎ በገዢው ፓርቲ ውስጥ የሚካሄድ የውስጥ ሽኩቻን የታከከ ፖለቲካዊ ሙስና ነው::
በየድርጅቶች ውስጥ የተለየ ሃሳብ እና የትችት ሙድ ያላቸውን ሰዎች ወይንም ከነማን በነማን እየጦዙ ነው የቡድን ስሪት ተለጣፊ አመራሮችን ለማፈን ሃያልነትን መጠቀም የፖለቲካ ሙስና ነው::እስከዛሬ እርምጃ ተወሰደባቸው የተባሉ ሰዎች ከፖለቲካ ጋር በተገናኘ ችግር እንዳለ መረጃዎች ሲጠቁሙ በግል ቂም በቀለም የታሰሩ ሰዎች አላግባብ እየተንገላቱ ሲሆን ከዚሁ ጋር በተያያዥነት የእስር ቤት ውስጥ ያለውን ሁኔታ ተቃዋሚን እንዲሰልሉ የተያዙ አስመሳይ የሙስና እስረኞች እንዳሉ የታወቀ ጉዳይ መሆኑ በራሱ የፖለቲካ ሙስና ነው::

በጠበንጃ ሃይል የያዙትን ስልጣን ተጠቅመው በምርጫ በህዝብ ተመርጠናል የሚሉ አካላት ህዝባዊ አገልግሎት ከመስጠት ይልቅ አነስተኛ እና ጥቃቅን ሆድ አደር ካድሬዎችን በማሟሟቅ ላወጡት እና ላጸደቁት ህጋቸ ተገዢ ከመሆን ይልቅ እንደፈለጉ እና እንዳሻቸው ራሳቸውን ከአገሪቱ መናብርታት እኩል በማሰለፍ ያለውን የፖለቲካ ምህዳር መጥበብ ተገን አድርገው እና ተጠቅመው የሚፈልጉትን እየጠቀሙ የማይፈልጉትን እያጠቁ ይገኛሉ::ፖለቲካዊ ሥልጣንን በመጠቀም ያላግባብ ዜጋን መጉዳት በራሱ ፖለቲካዊ ሙስና ነው፡፡

የግል ቂም በቀል የፖለቲካ አመለካከት እና ተመሳሳይ ጉዳዮችን በማጣቀስ ልዩነት ጠላትነት የሚመስላቸው ያልበሰሉ የስርኣቱ ካድሬዎች የግል ጸበኞቻቸውን የፖለቲካ ባላንጣዎቻቸውን ለፖለቲካ የንግድ ድርጅቶቻቸው አስጊ የሆኑትን ጠንካራ ነጋዴዎች በሙስና አልተሳሰር ያሉ ኢንቨስተሮችን የፖለቲካ ባላንጣ ቤተሰቦችን እንደ ጠላት በማየት መሬት እንዳያገኙ መከልከል፣ ፈቃድ መሰረዝ እና አለመስጠት ፣ የያዙትን መንጠቅ፣ የባንክ አካውንታቸውን ማገድ እና ብድር እንዳያገኙ ማከላከል ፣ የብቃት ማረጋገጫ እንዳትሰጧቸው፣ የሥራ ፈቃዳቸው እንዳይታደስ፣ ወዘተ እየተባለ መጉዳት፣ ማንከራተትና ሕገወጥ ተግባር በመፈጸም ስልጣንን ያለአግባብ የሚጠቀሙ ያልበሰሉ ፖለቲከኞች የሚፈጸሙት የፖለቲካ ሙስና በአገሪቱ አግጥጦ እየታየ ነው፡፡

ራሳቸው ያወጡትን እና አፈጻጸሙ እና አተረጓጎሙን እንኩዋን በተግባር ያልተረዱትን ሕግ በመጣስ ባለስልጣናት የግል እና የወል ጠላቶቻቸውን ድርጅቶቻቸውን ማሳሸግ ማጉላላት ማዘረፍ ማስደብደብ ባልሆነ ወንጀል መክሰስ፣ ፋይል ማስከፈትና ማስፈረድ በተግባር ይታያል፡፡ ጎን ለጎን ዘመድ እና ወዳጅ ለሆነና ከራስ ፍላጎት ጋር የሚስማማ ሥራ ላለው ደግሞ ሕግ ቢጣስም እንዳይጠየቅ፣ እንዳይያዝ፣ እንዳይከሰስ፣ ከተከሰሰም ፋይሉ እንዲዘጋና ክሱ እንዲሰረዝ ይደረጋል፡፡ ይህ ሁሉ የማይቻል ከሆነም ሳይያዝ ወደ ውጭ አገር እንዲሸሽ በማድረግ ከኢኮኖሚ ሙስና ይልቅ ከፖለቲካ ሥልጣን አጠቃቀም አንፃር ሲታይ ግን ሥልጣንን መከታ በማድረግ የሚፈጸም አደገኛ የፖለቲካ ሙሰኛ ነው፡፡ ሕንፃ- መኪና -ቪላ -ኢሮ -ብርና ዶላር -ጠበንጃ እና ቦምብ- እየተቆጠረ ሙስና እንደሚወራልን ሁሉ … የሃገሪቷን ዜጎች የጎዳ ;ሕግን እና ህገመንግስትን ያጣመመ; የራሱ መንግስት ያለውን;የፖለቲካ ባላንጣዎችን እና የግል ቂምበቀሉን ተገን አድርጎ የተንቀሳቀሰ ; መብት ጥሰት የፈጸመውን ;የዜጎችን መብት ያፈነውን ;ህገወጥ ተግባር በዜጎች ላይ የፈጸመውን ;ከህገወጦች ጋር የተባበረን ተቆጥሮ ;በፖለቲካ ሙሰኝነት መች ነው ለፍርድ የሚቀርበው??

ከትላት በስቲያ እሁድ የካቲት 2\2006 ከጠዋቱ 3፡30 ጀምሮ ስድስት ኪሎ በሚገኘው የስብሰባ ማእከል በተካሄደው በዚህ የሽልማት ስነስርዐት ላይ የህወሃት አባት የሚባሉት አቦይ ስብሃትን ጨምሮ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አቶ ድሪባ ኩማ ፣ የአዲስ አበባ
ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ ሃላፊ አቶ ፀጋዬ ሀይለማሪያም ፣ የህገ ወጡ መጅሊስ ፕሬዚደንት ዶክተር አህመድ አብዱረህማን ፣ የፌዴራሉ ህገ ወጥ መጅሊስ ምክትል ፕሬዚደንት ታጋይ (ሸይክ ከድር ) ፣ የአንዋር መስጂድ ኢማም ሀጂ ጡሃ ሃሩን ፣ የ10 ሩም ክፍለ ከተማ ሃላፊዎች ፣ የወረዳና የክፍለ ከተሞች መጅሊስ አመራሮች እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ፡፡

ከሽልማቱ በኋላ ንግግር ያደረጉት አቦይ ስብሃት መንግስት በሙስሊሙ ጉዳይ ጠልቃ እንደገባ የሚያረጋግጠውንንግግራቸውን አድርገዋል ፡፡ አቦይ ስብሃት በአዳራሹ ለተገኘው ሰው ባደረጉት ንግግር
“ … ማንኛውም ነገር ከፍተኛ ጥረት ከተደረገበት ስኬት ይኖረዋል ፡፡ የሙስሊሙ ትግል ሲጀመር በጣም ተደናግሮን ነበር ፡፡ በኋላ ብዙ አስበንበት ስናበቃ ለምን መንግስትን የሚደግፍ መጅሊስ አናቋቁምም አልንና ጥረት ጀመርን ፡፡እኔ እራሴ ሄጄ ግዴላችሁም ከየክፍለ ከተማው ሙስሊም ሆነው መንግስትን የሚደግፉ ሁለት ወይም ሶስት ሰዎችን ብቻ ፈልጉልኝ አልኩ …፡፡ የጀመርነው ከቦሌ ክፍለ ከተማ ነው ፡፡ ወደ አምስት ሰዎችን አገኘንና እነሱን አደራጀን ፡፡ በኋላ ሌሎችም ክፍለ ከተሞች የቦሌን ተሞክሮ እንዲተገብሩ አደረግን ፡፡

ሁሉም ክፍለ ከተሞች ጥቂት ሙስሊሞችን አደራጁ ፡፡ ከዚህ በኋላ ነገሩ ሁሉ የተቃና ሆነ ፡፡ እኛም በሁሉም ክፍለ ከተሞች በተወሰኑ ሰዎች
መደራጀቱን ስናውቅ ጉዳዩን የአዲስ አበባ ፍትህ ቢሮና ክፍለ ከተሞች እንዲረከቡንና በበላይነት እንዲቆጣጠሩት አደረግን ፡፡ እንዲህ
እያለ የሄደው ጥረት አሁን አክራሪዎችን ለማቆም የሚያስችል ጉልበት እንድናገኝ ረድቶናል … ” ብለዋል ፡፡

ይህ የአቶ ስብሃት ነጋ ንግግር መንግስት በሙስሊሙ ጉዳይ ጠልቃ አልገባሁም እያለ ከሚያስተባብለው ጋር የሚጋጭ እንደሆነ ተገልፇል ፡፡ በበርካታ ጉዳዮች ንግግር ያደረጉት አቦይ ስብሃት ኢስላምን የሚያጥላላ ንግግርም አድርገዋል ፡፡ “ቅድም የፌዴራሉ መጅሊስ ምክትል ሰብሳቢው ሸህ ከድር እንዳለው የዱሮው እስልምና ሌላ ነው ፡፡ እኔ ከድርን በፊት ጀምሮ ትግራይ ውስጥ አውቀዋለሁ ፡፡ ምርጥ የህወሃት ታጋይ ነበር ፡፡ አብሮን ታግሏል ፡፡ አሁን ደግሞ ሙስሊሙን እያገለገለ ነው ፡፡ እስልምና እነዚህ የታሰሩት ሰዎች እንደሚሉት አይመስለኝም ፡፡
እስልምና እነዚህ ሰዎች እንደሚያሳዩት ዓይነት ዕምነት ከሆነ እንደ ዕምነት አያስፈልግም ፡፡ ፈፅሞ ሰዎቹ ለሀገር አይሆኑም ” ብለዋል ፡፡ በዚህ
ንግግራቸው በቦታው የነበሩ ሙስሊሞችም ጭብጨባ ለግሰዋቸዋል ፡፡

ኢትዮጵያዊው ዓረናና ኤርትራዊው ህወሓት!

ዓረናዎች “ህወሓት ኤርትራን ያስቀድማል። በመሆኑም ህወሓት የሻዕቢያ ተላላኪ ነው” ስንል ህወሓቶች ደግሞ “ዓረና ከትግራይን ህዝብ ጠላቶች ከሆኑ እንደነ አንድነት ፓርቲ ጋ ለመዋህድ ጥረት እያደረገ ነው” ይላሉ።

እርግጥ ነው፤ ዓረና ኢትዮጵያዊ ነው። ከኢትይጵያውያን ድርጅቶች ጋርም አብሮ ይሰራል። ከአንድነት፣ ደቡብ ሕብረት፣ የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ እና ሌሎች ኢትዮጵያዊ ፓርቲዎች ጋር ለመዋሃድና አብሮ ለመስራት ዝግጁ ነው።

ዓረና እንደ ህወሓት ኤርትራዊ አይደለም። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም ለመጉዳት ከሻዕብያ ጋር በማበር አይሰራም። ኢትዮጵያውያንን በጠላትነት እየፈረጀ የሻዕብያ አገልጋይ አይሆንም። ምክንያቱም እኛ ኢትዮጵያውያን እንጂ ኤርትራውያን አይደለንም። ኤርትራውያንን ለመጥቀም ኢትዮጵያውያንን አንበድልም። ስለዚህ ከሻዕብያ በላይ አንድነት ፓርቲን እናስቀድማለን። ምክንያቱም አንድነት ፓርቲ ኢትዮጵያዊ ነው። ኢትዮጵያም የሁላችን የጋራ ነች። ምናልባት ከሻዕብያ ጋር አብረን የምንሰራው የኢትዮጵያና የኤርትራ የጋራ ጥቅም የሚከበርበት መድረክ ሲፈጠር ብቻ ነው።

ዓረናና ህወሓት አልተሳሳቱም። ዓረና ከኢትዮጵያውያን ጋር ይሰራል። ምክንያቱም ኢትዮጵያዊ ነው። ህወሓት የሻዕብያ ተላላኪ ነው። ምክንያቱም ህወሓት ኤርትራዊ ነው። ህወሓት ኤርትራዊ መሆኑ ችግር የለውም። ችግር የሆነው ህወሓት ኤርትራዊ ሁኖ፣ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም ለኤርትራ አሳልፎ እየሰጠ ግን የኢትዮጵያ መንግስትነት መቆጣጠሩ ነው። ለኤርትራውያን እየሰራ ኢትዮጵያውያንን እወክላለሁ ማለቱ ነው ችግሩ። ህወሓት ለኤርትራ መቆም የሚያስደስተው ከሆነ ኤርትራን ያስተዳድር፤ የኤርትራን ህዝብ ይወክል። ኢትዮጵያን እያስተዳደረ፣ የኢትዮጵያ ህዝብን እወክላለሁ እያለ ለኤርትራ ጥቅም መስራቱ፣ ኤርትራውያንን መወከሉ ግን ወንጀል ነው። ህወሓት የኢትዮጵያ መንግስትነት ከተቆጣጠረ ለኢትዮጵያውያን ጥቅም መስራት ነበረበት።

ህወሓት የኢትዮጵያ ስልጣን ይዞ ኤርትራን ለማስገንጠል ይሰራል፣ ዓሰብን ለኤርትራ ይሰጣል፣ ዓሰብ የኛ መሆኑ ስንከራከር ህወሓት ከኤርትራውያን በላይ ዓሰብ የኤርትራ መሆኑ ይሟገታል። ለኤርትራውያን መቆም ካለበት ለምን ወደሚወክለው ኤርትራ አይሄድም?

ዓረና ከኢትዮጵያውያን ድርጅቶች መዋሃዱን ይቀጥላል። ህወሓትም ለኤርትራውያን ማገልገሉ ይቀጥል። በዚሁ መሰረት “ዓረና ከአንድነት ፓርቲ ጋር እየተወሃደ ነው” ብላች ሁ ክሰሱን። ለኛ ችግር አይሆንም፤ ምክንያቱም በኢትዮጵያውነታችን አምነን በኢትዮጵያ ለኢትዮጵያውያን አማራጭ የፖለቲካ አቅጣጫ የሚያቀርብ ጠንካራ ሀገራዊ ፓርቲ የመመስረት ዕቅድ አለን። ህወሓትም ሻዕብያን ማገልገሉ ይቀጥል ምክንያቱም ህወሓት የኤርትራ ተወካይ (በኢትዮጵያ) መሆኑ እናውቃለን።

ህወሓት ግን ዓረና ከአንድነት ጋር የመዋህዱ ዜና ሲሰማ እንዲህ ከተደናገጠ ከሌሎች ኢትዮጵያዊ ድርጅቶች ጭምር ስንዋሃድስ ምን ሊሆን ነው? ዓረና ከአንድነት ብቻ ሳይሆን ከሌሎች ብዙ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ድርጅቶች ጋርም ይወሃዳል። ጠንካራ ሀገራዊ ፓርቲ መመስረት እንፈልጋለንና።

ህወሓት ኤርትራን ሲያስበልጥ ዓረና ግን ኢትዮጵያንን ያስቀድማል።

It is so!!! Abrha Desta

የደ/ሱዳን ኣማጺያን ከድርድሩ እራሳቸውን እንደሚያጋሉ ያስጠነቀቁት፤ ትላንት ከአዲስ ኣበባ እንደተገለጸው በሁለት ምክኒያቶች ነው። አንደኛው ያልተፈቱት አባሎቻቸው በኣስቸኩዋይ ካልተለቀቁ እና ሁለተኛው ደግሞ በዚያች ሀገር የሚገኙ የኡጋንዳ ወታደሮች ሀገሪቱን ለቀው ካልወጡ በሚል ነበር በቀጣዩ ድርድር ላይ እንደማይካፈሉ ያስታወቁት።

የካቲት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከፍተኛ የግብርና ምርት  እንደተገኘ በመንግስት የመገናኛ ብዙሀን በሚገለጽበት በአሁኑ ወቅት ከ3 ሚሊዮን በላይ ዜጎች አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ካላገኙ ህይወታቸው አደጋ ላይ እንደሚወድቅ መረጃዎች አመልከተዋል። የዓለም ባንክ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት በመግብ ለስራ የታቀፉ ዜጎችን ሳይጨምር ከ3 ሚሎዮን ያላነሱ ኢትዮጵያውያን አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል። በምስራቅ አማራ፣ በደቡብ ምስራቅ ትግራይ፣ በአፋር …

የካቲት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የደህንነት ሃላፊ ከነበሩት ከአቶ ወልደስላሴ ወልደ ሚካኤል  ጋር በግብረ-አበርነት የተከሰሱት የህወሃት ታጋዮች ከደሞዛቸው ጋር ፈጽሞ የማይመጣጠን ሃብት አግበሰው መገኘታቸው ታውቋል። በተለያዩ አለመግባባቶች የተነሳ እየተመሰረቱ ያሉ ክሶች የህወሃት ተጋዮች በህገወጥ መንገድ የሰበሰቡትን የሃብት መጠን ለማወቅ እየረዳ መሆኑን የገለጸው ዘጋቢያችን ከአቶ ወልደስላሴ ጋር በግብረ አበርነት የተከሰሱት የህወሃት ታጋዩ የአቶ …

የካቲት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የደብረዘይት አየር ኃይል አባል የነበረው ምክትል መቶ አለቃ ዳንኤል የሽዋስ የኢህአዴግን ስርአት በመቃወም የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊትን መቀላለቀሉን ግንባሩ ለኢሳት በላከው መግለጫ አስታውቋል። ም/መ/አለቃ ዳንኤል የሽዋስ የ L-39  ስኳድሮን ተዋጊ ጀት አብራሪ እንደነበር መረጃው ያመለክታል። ም/መ/አ ዳንኤል የሽዋስ “ተቃዋሚዎችን ትደግፋለህ ከእነሱም ጋር የጠበቀ ግኑኝነት አለህ በሚል …

የካቲት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ግንባሩ ለኢሳት በላከው መረጃ ፣ ከኢህአዴግ መንግስት ጋር ድርድር ለማድረግ በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ተገኝተው  በኢትዮጵያ የደህንነት ሃይሎች ታፍነው የተወሰዱት የኦብነግ አመራሮች፣ የደረሰባቸውን ከፍተኛ ድብደባ ተከትሎ በአንድ ወታደራዊ ሆስፒታል ውስጥ ሲታከሙ ታይተዋል። የመንግስት የደህንነት ሰራተኞች ” ባለስልጣኖቹ በገዛ ፈቃዳቸው እጃቸውን እንደሰጡ ለማሳመን ያደረጉት ከፍተኛ ጥረት ባለመሳካቱ  አሰቃቂ …

የካቲት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ጠ/ሚ/ሃይለማርያም ደሳለኝ፣ በደቡብ ሱዳን የሚገኘው የዩጋንዳ ጦር በሂደት ለቆ ካልወጣ አካባቢው የጦርነት ቀጠና ሊሆን ይችላል ብለዋል። ሁሉም ሃይሎች የራሳቸው የሆነ ፍላጎት አላቸው ያሉት አቶ ሃይለማርያም፣ በደቡብ ሱዳን ሰላም ይመጣ ዘንድ የዩጋንዳ ጦር ጁባን ለቆ መውጣት አለበት ሲሉ አሳስበዋል ። አቶ ሃይለማርያም የገለጹት አቋም የደቡብ ሱዳንን መንግስት የሚያስከፋ …

አማኑኤል ዘሰላም

“ስልክ ጠላፊው ሰላይ ‘ጋዜጠኛ'” የሚል አንድ ጽሁፍ አነበብኩ። ሲያትል የሚኖር አንድ ኢትዮጵያዊ ናቸው የጻፉት። የአውራምባ ታይምስ ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደን አጠንክረው ይተቻሉ። በቅርቡ በድረ ገጾችና ፌስቡክ የተለቀቀው፣ አቶ አበበ ገላው የተናገሩትን አንዳንድ አባባሎችን የያዘ ኦዲዮ ነው። ይህ ኦዲዮ አቶ አበበ፣ ሳያውቁት የተቀዳ ነው። ይህ አይነቱም ንግግርን በሚስጠር የመቅዳት የፓፓራዚ ተግባር በጣም አሳዛኝ ከመሆኑም በተጨማሪ ነውርም ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ግርማ ካሳ

አዲሱ የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው፣ ለገዢው ፓርቲ ኢሕአዴግ የሰላምና የእርቅ ጥሪ ማቅረባቸው ይታወሳል። “ኢሕአዴግ እኛን እንደ ጠላት እና ሽብርተኛ ማየቱን ማቆም አለበት። እኛም ደግሞ ኢሕአዴግን እንደ አውሬ ማየት ማቆም አለብን። ከጥላቻ ፖለቲካ በመውጣት ችግሮቻችንን በሰላም መፍታት መማር አለብን” ሲሉ ነበር፣ ለአገር በሚጠቅሙ በጋራ ጉዳዮች ዙሪያ ከኢሕአዴግ ጋር ለመስራት፣ ያሉትን ልዩነቶችን በውይይት ለመፍታት አንድነት ፍላጎት እንዳለው የገለጹት።

ሙሉውን አስነብበኝ …

የእነ “… ወይም ሞት” ፖለቲካ

ያሬድ ኃይለማርያም ከብራስልስ
ከ1960ዎቹ የተማሪዎች ንቅናቄ ጀምሮ የአገራችንን ፖለቲካ የተጠናወተው የ”…. ወይም ሞት” አስተሳሰብ ከአስርት አመታት በኋላም አለቅ ብሎን ዛሬም እኔ ከምደግፈው ፓርቲ ወይም የፖለቲካ ቡድን ወይም አስተሳሰብ ውጭ ያለው መንገድ ወይም አማራጭ ሁሉ ገደልና ሞት ነው ብለው የሚያስቡ ፖለቲከኞችና ዓጃቢዎችን ቁጥር በብዙ እጥፍ አባዝቶ ቀጥሏል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

በጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ፤ ከዝዋይ ማረሚያ ቤት

(ከኢትዮ-ምኅዳር ጋዜጣ የተወሰደ)

‹‹ይህንን ስለመሳሰሉ ጉዳዮች መወያየት ክልክል ነው፡፡›› በማለት በተንጎላጀጀ ድምፅ ጠባቂው ተናገረ፡፡ ቀጠል አደረገናም ‹‹መነጋገር የምትችሉት ስለቤተሰብ ጉዳዮች ብቻ ነው›› በማለት ተናገረ፡፡ ይህን ከላይ ያለውን ሐሳብ የሚመለከት ማንኛውም አንባቢ፣ ጉዳይ የተፈፀመው እዚህችው እማማ ኢትዮጵያ ሰማይ ስር ባሉ አጃኢበኛ እስር ቤቶች፣ ቤተሰብ መጠየቂያው እንደሆነ መጣራቱ አይቀርም፡፡

ይሁንና በመግቢያው ላይ ያለው ጽሑፍ ተቀንጭቦ የተወሰደ ‹እናት› ከተሰኘውና እ.ኤ.አ. በ1906 ከታተመው የስመ ጥሩው ሩስያዊ ደራሲ ማክሲም ጎርኪይ ታሪካዊ ልቦለድ ገፅ 102 ላይ ነው፡፡ የዛሬ 108 ዓመት አካባቢ ማለት ነው፡፡ አቤት ርቀቱ!… ይህ ርቀት ግን ለእኛ ምንም ማለት ያልሆነ ይመስላል፤ ለምን? ቢሉ ዛሬም ይህንንና ይህን የመሳሰለውን አስፍተን እየሠራን እንገኛለን፡፡ እንዲያውም በአንዳንድ ሁኔታዎች እየተጓዝን ያለነው የቁልቁለት ሩጫ በእጅጉ አሳሳቢ ሆኖ ይገኛል፡፡

የነገሮች ሁሉ መድረሻ እስር ቤቶች እየሆኑ መጥተዋል፡፡ ‹ጠበቅ ያለ እርምጃ፣ የማያዳግም እርምጃ፣ የማስወገድ እርምጃ፣…› ወዘተ የሞሉ ከሕግ መርሕዎች ሳይሆን ከጥላቻ ፖለቲካ የሚመነጩ ፀያፍ አነጋገሮችን በሕዝብ የመገናኛ ዘዴዎች ሲተላለፉ እየሰማን እየታዘብን ነው፡፡ ቃል በቃል ‹ቀይ ሽብር ይፋፋም› ብሎ ማወጅ የቀራቸው የሕግም የግብረገብም ሚዛን ያልወጣላቸው ቀረርቶች በተለይ በእስር ቤት የምንገኝ ኢትዮጵያውያንን እየሰበሰቡን ይገኛሉ፡፡

በኢ.ቴ.ቪ. የአብዮታዊ እርምጃ ፕሮግራሞች በቀረቡ ማግስት አሁን በዝርዝር ብለው የብዙ ቤተሰቦችን ስሜት ሊያሸማቅቁ የሚችሉ ሰቆቃና እንግልቶች በአስደማሚ ስልት ተቀናብረው ተፈፃሚ ይሆናሉ፡፡ እስኪ የተወሰኑትን እንይ፡፡ ማንኛውም ታሳሪ ቤተሰብ በቅርብ ሊጎበኘው በሚችለው እስር ቤት ይታሰር የሚለው ሕግ የተሻረው በእኛ ላይ ነው፡፡ ዝዋይ የአገራችን ‹ሳይቤሪያ ግዞት› ማለት ናት፡፡ ቤተሰብ ያን ያህል የበርሃ ጉዞ አቋርጦ የእኛዋ ሳይቤሪያ ሲደርስ በአድካሚና ግብረ-ገብ በጎደለው ፍተሻ መከራውን ማየቱ አንሶ ጆሮ ግንዱ ላይ በቆሙ የቤተሰብ አገናኞች ቤተሰባዊ ገመናውን አሳልፎ ይሰጣል፡፡ ሕፃናት ልጆች ወላጆቻቸው አንድ ላይ ሆነው ናፍቆታቸውን መወጣት አይችሉም፡፡ አንዳንድ ጊዜ ፖሊሶቹ ሲዘናጉልን ልጆቻችንን አቅፈን እንስማለን፡፡ ይህ ከሆነ ቁጣና ዘለፋው ምንም አይደለም፡፡ ግን በሁኔታው ሕፃናቱ ክፉኛ ይበረግጋሉ፣ የእኛ ስጋት ይጋባባቸዋል፤ በዚህም መንፈሳቸው እርብሽብሽ ብሎ ወደቤታቸው ይመለሳሉ፡፡

ሁኔታው በዚህ አያበቃም፡፡ ምንም እንኳን የመጠየቂያ ሰዓቱ በግልፅ የተቀመጠ ቢሆን ከቤተሰቦቻችን ጋር ገና መነጋገር ስንጀምር ‹‹በቃ… ቶሎ ጨርሱ›› የሚባልባቸው ጊዜዎች ብዙ ናቸው፡፡ ቀጥሎ የሚመጣው የእስር ቤት ማኅበራዊ ጉዳዮችን ማለትም ለሳሙና፣ ለምግብ ማጣፈጫ፣ ለሻይ ለቡና፣ ለውስጥ አልባሳት፣ ለውኃ ማከሚያ/ውኃ አጋር/ ወዘተ፤ ገንዘብ የሚያስፈልገን ቢሆንም እና እንደሚያስፈልጉ ቢታወቅም ጉዳዩ ለይቶለት የማሰቃየት፣ ማንገላታት፣ መበቀል ሆኗልና ለአንድ ወር ከአንድ መቶ ብር በላይ መጠቀም እንዳንችል የተከለከልን የመሆኑ አሳፋሪ ሐቅ ነው፡፡ ይህ እየተፈፀመ ያለው ደግሞ ዝዋይ እስር ቤት ውስጥ ብቻ ነው፡፡ በዚህ የተነሳም ለመግለጽ በሚከብድ ሁኔታ ሰብኣዊ ክብራችንን የማዋረድ ሙከራዎች እየተፈፀሙ ነው፡፡
በአገራችን ላይ እኔ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቴን የጨረስኩት ዝዋይ በመሆኑ ብዙ ወዳጅ ዘመዶቼ በእዚህ ይገኛሉ፡፡ ሆኖም ለአካባቢው ነዋሪዎች በሳምንት እንዲጠይቁን የተፈቀደላቸው አንድ ቀን /ረቡዕ/ ብቻ ሲሆን ‹‹የት ነው የምታውቁት? እንዴት አወቃችሁት? ምንድን ነው የሚያመላልሳችሁ?›› በሚሉትና በሌሎችም ጥያቄዎች ተደናግጠው መምጣቱን እርግፍ አድርገው ትተውታል፡፡

ሀገሩ ሞቃታማ ነውና በዚያ ላይ በእያንዳንዱ ቤት እስከ 150 ሰው ይታሰርበታል፡፡ ይህ ሁሉ ተደማምሮ እስረኛው የቱንም ያህል ፅዳቱን ለመጠበቅ ቢሞክርም የተባዩ መርመስመስ የእነ ትኋን እንዲህ መራባት፤ ለማሰብ እንኳን ይዘገንናል፡፡ ሌሊቱን ሙሉ ገላን ሲቆፍሩ ማደር ነው፡፡ ሊናገሩት ይከብዳል፣ አንባቢንም ቅር ያሰኛል፤ ግን ይህ የፊልም ትረካ ሳይሆን በእማማ ኢትዮጵያ ልጆች ላይ ሆን ተብሎ እየተፈፀመ ያለ ደባ ነው፡፡ […] ግን የባሰ አታምጣ ማለት ነው!

ግን የባሰ ነገር አለ፡፡ አፈር ቅጠል የማይል ምግብ ይቀርብናል፡፡ ‹በደንባራ በቅሎ ቃጭል ተጨምሮ› ከፍተኛ የውኃ እጥረት /ዝዋይ ሀይቅ አናት ላይ ተቀምጠን/ አለ፡፡ የእስር እስር እንዲሉ ጄኔራል መኮንኖቹን ጨምሮ አብዛኛዎቹ አባሪዎቻቸውና ሌሎች ሌሎች የተወሰንን እስረኞች የምንገኘው በልዩ ቅጣት ጭለማ ቤት ውስጥ ነው፡፡ ይህንን ሁሉ እንደምንም ለመቋቋም ጥረት ማድረግ ይቻል ይሆናል፡፡ አዲሱ ስልት ግን መዘዙ በጣም አደገኛ በመሆኑ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ፣ እያንዳንዱ ሃይማኖት ያለው፣ ፈርሐ እግዚአብሔር ያለው፣ እያንዳንዱ የመሠረታዊ ሰብኣዊ መብቶችና ነጻነቶች መከበር የሚያሳስበው እያንዳንዱ ሰው የሆነ ሰው ሁሉ ሊያውቀው ይገባል ስንል ድምፃችንን እናሰማለን፤ በሕክምና ንፍገት ወደሞት እየተገፋን ነው፡፡

ከወር በፊት ገደማ ወጣቱ የአንድነት ፓርቲ አባል ናትናኤል መኮንን ለሕክምና በሪፈር ወደ ቃሊቲ ተልኮ የነበረ ቢሆንም፣ የዛኑ ዕለት ሕክምናውን ተነፍጎ ከሌሊቱ 5፡00 ሰዓት አካባቢ እንዲመለስ ተደርጓል፡፡ እስካሁን በሕመሙ እየተሰቃየ ይገኛል፡፡ የኢብአፓ ሊቀመንበር የነበረው ዘሪሁን ገ/እግዚአብሔር እንደዚሁ ለተጨማሪ ሕክምና ሪፈር ተብሎ ሲጠባበቅ ከቆየ በኋላ ዘዴው ተፈፃሚ ሆነበት እጁን አጣጥፎ ተቀምጧል፡፡ ከሕመሙ ጋር በተያያዘ በአካሉ ላይ አሳሳቢ ሁኔታ እየታየበት ይገኛል፡፡ ከዚህ ቀደም ገልጬው የነበረው የእኔ የኩላሊት ሕመም አሁን ለመቀመጥም፣ ለመንቀሳቀስ እያወከኝ የሚገኝ ሲሆን፣ እኔን ከቃሊቲ ዝዋይ ለማምጣት የተደረገው የተቀናጀ መረብ ሩብ ያህሉን ለሰብኣዊነት አውለውት ቢሆን ኖሮ እኔም ፋታ፣ እነሱም እርካታ ባገኙ ነበር፡፡ ሕመም ካልታከመ መጨረሻው ሞት ነው፡፡ የሞቱም ሰዎች አሉ!

የጄኔራል መኮንኖቹ አባሪዎች የነበሩት ኮረኔል ተስፋዬ ኃይሉ እና ኢንጂነር ክፍሌ ስንሻው፣ በዶክተር መረራ በሚመራው ኦሕኮ ፓርቲ አባል የነበሩት አሕመድ ነጃሺ፣ በጭለማ ቤት የከረመው ተስፋሀን ጨመዳ፣ የቤንሻንጉሉ አዛውንት ወዘተ ተገቢውን ሕክምና በማጣት ሕይወታቸውን ያጡ የእማማ ኢትዮጵያ ልጆች ናቸው፡፡ እንዴት ሕክምና ይከለከላል!? ግፍና ጭቆና ተቃውመው ደማቸውን ያፈሰሱና አጥንታቸውን የከሰከሱ ታጋዮችን በሥልጣን ማግስት ከፍርድ በመለስ በየእስር ቤቱ ያሉ ኢትዮጵያዊ ወገኖቻቸው በሕክምና እጦት ሲረግፉ በእርካታ ማርመምን ከየት ተማሩት!? የኢትዮጵያ ሕዝብስ ምን ይላል!? ሰው የሆኑ ሰዎች ሁሉ ከቶ ምን ይላሉ!?

እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ!

ሁለተኛዉ ዙር የሶርያ መንግሥትና የመንግሥቱ ተቃዋሚዎች ህብረት ድርድር ዛሬ በጄኔቭ ስዊትዘርላንድ ተጀመረ። ሁለቱ ተፋላሚ ሃይላት ባለፈው ወር መጨረሻ ያደረጉት የመጀመርያዉ ዙር ድርድር ያለምንም ዉጤት ነበር የተጠናቀቀው። በሳምንቱ መጨረሻ የተመድ ለሶርያውያኑ የሆምስ ከተማ አስፈላጊውን የሰብዓዊ ርዳታ ማድረስ አልቻለም።

ምስራቃውያን “ልማታዊ መንግሥታት ናቸው” የተባሉት በምዕራባውያን ነበር።  የኢትዮጵያ መንግሥት ግን ራሱ ነው “ልማታዊ” በማለት ራሱን መጥራት የጀመረው። ከዚያ በኋላ ቃሉ፣ በመንግሥት ኃላፊዎችና በተለይም በኢቴቪ በተደጋጋሚ ከመነሳቱና ካለቦታው ከመደንጎሩ የተነሳ የሚወክለው መንግሥት የሚከተለውን የኢኮኖሚ ስርዓት መሆኑ ቀርቶ በቀላሉ ሲታይ “የሚጠፉ ጥፋቶችን እንዳላየ አልፎ፥ ስለሚለሙ ልማቶች ብቻ ማውራትን”፣ ወይም በጥልቁ ሲመረመር “ገዢው ፓርቲን ከነቆሻሻው መደገፍን” ይመለከታል። ራስን ማዕረግ የመስጠት ጦሱ ይኸው ነው።

ኢሕአዴግ ደጋፊዎቹን ወጣቶች “የልማት ሠራዊት” ነው የሚላቸው፤ ቀሪው እንደጥፋት ሠራዊት ነው የሚቆጠረው። ሌላው ቢቀር ሁለቱንም አለመሆን አይፈቀድለትም። ኢሕአዴግ ራሱን ብቻ ልማታዊ አድርጎ የመቁጠሩ ነገር በስህተት የመጣ አይደለም፤ የፖለቲካ ፍልስፍና ጉዳይ ነው። በተለይ ሰሞኑን ፓርቲው በመንግሥትነት ስሙ ተጠቅሞ በሚያዘጋጃቸው ስብሰባዎች ላይ የታይዋን እና ደቡብ ኮርያ ስም ተደጋግሞ በምሳሌነት ይጠቀሳል፤ ሁለቱም “ለልማት ሲባል ዴሞክራሲን ሰውተው ነው እዚህ የደረሱት” በሚል። ልማታዊነት ለዴሞክራሲ አያጣድፍም እንደማለት።

ክፋቱ ኢሕአዴግ እምነቱን በፀባይ ለማሳመን አለመፈለጉንም ይጨምራል። እንዲህ እያለ እያወራም ግን ‘ዴሞክራሲያዊ ነኝ፣ ያለመሆን ፍላጎትም የለኝ’ እያለ በአደባባይ እየዋሸ ያታልላል። ግን መልሶ፣ “ሁሉም ነገር ወደልማታዊነት ግንባር” ይላል – በራሱ የልማታዊነት ብያኔ። የለም፣ እኔ በራሴ ብያኔ እሠራለሁ ብሎ ነገር የለም። ለምሳሌ፤

ልማታዊ ተቃዋሚዎች

ኢሕአዴግ ተቃዋሚዎች “ልማታዊ” እንዲሆኑ ይፈልጋል። “ልማታዊ ተቃዋሚዎች” ማለት የሁለት አሐዙ ዕድገትን ያለመጠየቅ የሚያምኑ፣ ስለፖለቲካው ምኅዳር መጥበብ ትንፍሽ የማይሉ እና ሌላው ቀርቶ በምርጫ ሲሸነፉ በኢቴቪ ቀርበው ይህ እንደሚሆን ቀድመውም ያውቁ እንደነበር የሚመሰክሩና የተሸነፉት በራሳቸው ድክመት መሆኑን የሚናገሩ… ናቸው። የሚወዳደሩት ውድድሩን ለማድመቅ ነው -ልክ እንደታላቁ ሩጫ ብዙኃን። ምሳሌ የአቶ መሳፍንት መኢብንን እና የአቶ አየለ ጫሚሶን ቅንጅትን መጥቀስ ይቻላል። በአጭሩ እነዚህ ፓርቲዎች፣ ተቃዋሚም፣ አማራጭ ፓርቲም አይደሉም፤ ደጋፊ ፓርቲዎች ናቸው።

“ደጋፊ የፖለቲካ ፓርቲዎች” (AKA ልማታዊ ፓርቲዎች) ዋነኛ ሥራ ራስን ተቃዋሚ ነን ብሎ ለሕዝብ መንገር፣ በገዢው ፓርቲ የተከፋውን ሕዝብ ልብና ቀልብ ማግኘት፣ ቀልቡን ለሰጠው ሕዝብ ፓርቲዎቹ ስለሚታገሉለት ሳይሆን ኢሕአዴግ ስለሚሠራቸው ሥራዎች ማውራት፣ ለኢሕአዴግ ድምፅ ማስገኘት ካልተቻለ “ልማታዊ ካልሆኑት ፓርቲዎች” ድምፅ መቀማት/መከፋፈል ናቸው።

ገዢው ፓርቲ እነሱን በማበርከት የአጥቂነት ሚናውን እየተወጣ ነው። እነሱ ደግሞ የማያገኙት የሥልጣን ጥማቸው የኢሕአዴግ ጉዳይ አስፈፃሚ አድርጓቸዋል።

ከኢሕአዴግ መሥመር በማይጋጠም አቅጣጫ የሚሄዱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ደግሞ ሕልውናቸውን አደጋ ላይ በሚጥል ቀጭን ሽቦ ላይ እንዲራመዱ ይደረጋሉ።

ልማታዊ ጋዜጠኝነት

ልማታዊ ጋዜጠኝነትም በገዢው ብያኔ መሠረት የኢኮኖሚ እና ፖለቲካ እርምጃዎችን አዎንታዊ ፋይዳን ብቻ ማውራት ነው። ለምሳሌ ከጣሊያን ብድር ለማግኘት ተብሎ ለሳሊኒ ያለጨረታ ፕሮጀክት መሰጠቱ ምን ያክል ገንዘብ ድሀዪቱን አገር ያከስራታል የሚለውን ማውራት ልማታዊ አይደለም። ፕሮጀክቱ መጀመሩ፣ ሲጠናቀቅ የሚኖረውን ፋይዳ ማውራት ግን ልማታዊ ነው።

በኢትዮጵያ 35 በመቶ የመረጃ ጥያቄዎች በሕዝብ ግንኙነት አባሎች ይጨናገፋሉ የሚለው ልማታዊ አይደለም፣ 65 በመቶ የሚሆኑ የመረጃ ጥያቄዎች ምላሽ ያገኛሉ የሚለው ግን ልማታዊ ነው። የሁለቱ ዜናዎች ልዩነት የትኩረት አቅጣጫቸው ነው። የመጀመሪያው ሊስተካክል የሚገባውን ሲያወራ፣ ሁለተኛው የተሳካውን ያወራል። ሁለቱም ውስጥ ተቃራኒው ቢኖርም የዜናዎቹ አንባቢዎች ግን እንዲያተኩሩ የተፈለገውን ብቻ የማስተዋል ዕድላቸው ሰፊ ነው። ስለዚህ ልማታዊ ጋዜጠኝነት  በተሳሳተ ብያኔው ሙገሳ አዝማሪነት ሆኗል ማለት ነው። እናም፣ ዜናው ላይ የተጠቀሰው ጥናት በመንግሥት ስለተሠራ እንጂ የመረጃ ንፍገቱ ከ35 በመቶ በላይ ነው፤ ለምሳሌ የግል ጋዜጠኞች የጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ካልሆነ በቀር መረጃ ጠይቀው የሚሰጣቸው የለም የሚል አስተያየት የሚያስተናግድ ጋዜጠኛ ከመጣ ጭራሹኑ ቦታ የለውም።

ልማታዊ አራማጅነት

አራማጅነት (activism) በባሕሪው ምናባዊ በሆኑ መሠረታውያን ላይ የቆመ የለውጥ እንቅስቃሴ ነው። አንድ አራማጅ ይህ ለውጥ እንዲመጣ እፈልጋለሁ ካለ፣ የሚመጣውን ለውጥ የመጨረሻ ግብ እያለመና ሁሉንም ነገር ከዚያ ግብ (ወይም ለዚያ ግብ ከሚኖረው ፋይዳ) አንፃር እየመዘነ የሚሄድ ነው።

ለምሳሌ እንደኛ ባለ ጠቅላይገነንነት (authoritarianism) ስርዓት ውስጥ ዴሞክራሲ እንዲመጣ የሚሠራን አራማጅ እንውሰድ። ይህ አራማጅ በነባራዊው ሁኔታ ያሉ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለውጥ እንደማያመጡ ያምናል እንበል። እንዲያውም እነሱ ራሳቸው ሚናቸውን ለመወጣት ለውጥ ይፈልጋሉ፤ ዴሞክራሲ ይፈልጋሉ። ጋዜጠኞችም ሐሳባቸውን ለመግለጽ ነጻነት ይፈልጋሉ፤ እነሱም ዴሞክራሲ ይፈልጋሉ። ስለዚህ አራማጁ የሚያስቀምጠው መለኪያ እነዚህን እውን የሚያደርጉትን መለኪያዎች ነው።

ነገር ግን፣ በኢሕአዴግ የእያንዳንዱ ዜጋ “የልማታዊ” መሆን የውስጠ ታዋቂ መመሪያ መሠረት ገዢውን ማበረታታት እንጂ መተቸት ያስቀስፋል። አራማጁ ስለፖለቲካ ምኅዳር ሲያወራ፣ ገዢው ስለመሠረተ ልማቱ አውራ ይለዋል፤ ስለመሠረተ ልማቱ የአገነባብ ሒደት ሁሉንም በዕኩል አሳታፊነት/ጠቃሚነት ጉዳይ ሲያወራ፣ ስለተገኘው ስኬት አውራ ይባላል። ስለዚህ እንኳን ለሌሎች ዴሞክራሲን በአማጭነት ሊያግዝ የራሱንም ማስጠበቅ ይቸገራል። በዚህ አራማጁን “ልማታዊ” የማድረግ አካሄድ አራማጁ የኢሕአዴግ ሕልም አስፈፃሚ ብቻ ነው መሆን የሚችለው።

አራማጆች በኢትዮጵያ መሠረታዊ መነሻቸውን ሳይስቱ ከቆዩ (“ልማታዊ” አንሆንም ካሉ፥) በገዢው ስያሜ ይሰጣቸዋል። የመጀመሪያው ‘አሸባሪ’ ነው። ‘ፅንፈኞች፣ የኒዮ ሊበራል ተላላኪዎች፣ ፀረ-ልማቶች…” የሚሉትም ይገኙበታል። እነዚህ ስያሜዎች ምናልባትም እራሱን እንደፈጣሪ መልዕክተኛ ለሚቆጥር አራማጅ አስበርጋጊ ናቸው። ስያሜዎቹ፣ ከተራ ውንጀላ ወደ ክስ መዝገብነት ሲቀየሩ የበለጠ ያሸማቅቃሉ።

በመጨረሻም፣ ልማታዊ አራማጆች ይፈጠራሉ። እነርሱም ልማት ስለሚያመጣቸው ነጻነቶች፣ ሕገ መንግሥቱ ስለሰጣቸው መብቶች፣ ባልተለወጠ መንግሥት ስር ዜጎች ራሳቸውን እንዲለውጡ ይተውታሉ። በልማታዊ መንግሥት፣ በልማታዊ ተቃዋሚዎች፣ በልማታዊ ጋዜጠኞች፣ በልማታዊ አራማጆች እና በተሳሳተው የመሸነጋገያ “የልማታዊ” ትርጉም፥ ባለህበት አዝግምi

አንድ ዘመን ሥርዓተ መንግስቱ በመቆየትም ሆነ አባላቱ የአሥራ ሰባተኛው ክፍለ ዘመን የተረት ዓለም ሰዎች ስለ መሰሉን- ሁሉም ነገር ስለገለማን አዲስ ሥርዓት፣ አዲስ መሪ፣ አዲስ ዘመን መናፈቅ ይዘን ነበር። ሰዓሊ ሁሉ፣ ደራሲ ሁሉ፣ ጸሐፌ -ተውኔት ሁሉ እጁን የሚያሟሸው በቴዎድሮስ ሥዕል፣ ተውኔትና ታሪክ ሆነ። ብርሃኑ ዘሪሁን- የቴዎድሮስ እንባ -(መጽሐፍ) ከዚያ በፊት ደጃዝማች ግርማቸው ተክለሐዋርያት- ቴዎድሮስ (ተውኔት) አቤ […]

የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ አውጭ ግንባር – ኦብነግ በቅርቡ ኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ውስጥ “ተጠልፈውብኛል” ባላቸው ሁለት ከፍተኛ የአመራር አባላቱ ላይ ድብደባና የሥቃይ አያያዝ መድረሱን ግንባሩ አስታውቋል፡፡

ወጣቱ ፖለቲከኛና ደራሲ አቶ ዳንኤል ተፈራ ፖሊስ ጣቢያ እንዲቀርብ መጠየቁ በስፋት መዘገቡ ይታወቃል። አቶ ዳንኤል መጀመሪያ ላይ እንዲቀርብ የተጠየቀዉ በስልክ፣ ሲሆን፣ ሕጋዊ መጥሪያ ወረቀት ካልመጣለት በቀር ለመቅረብ ፈቅደኛ ሳይሆን እንዳልቀረ ለማወቅ ተችሏል። ከአቶ ዳንኤል ተፈራ በተጨማሪ፣ የአንድነት ብሄራዊ ምክር አባል የሆኑትና በርካታ መጽሃፍት በመጻፍ የሚታወቁት አዛዉንቱ አቶ አንዳርጌ መስፍንን፣ ፖሊስ ለመከሰስ እንደተዘጋጀ፣ እንዲቀርቡም እንዳዘዘ ለማረጋገጥ […]

የኢትዮጵያና የግብፅ የውኃ ሚኒስትሮች ዛሬ አዲስ አበባ ላይ ያደረጉት ስብሰባ ያለስምምነት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ለቪኦኤ ዛሬ ማምሻውን ገልፀዋል፡፡

«ከንቲባ ድሪባ ኩማና ኮሚሽነሩ መከራከሪያቸውን ለፍ/ቤት ያቀርባሉ » «አንድነት፣ የመንግስት አካላትን በተከታታይ እከሳለሁ ብሏል» አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ (አንድነት)፣ የአዲስ አበባ ከንቲባና የፖሊስ ኮሚሽነራቸው ላይ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት 8ኛ ወንጀል ችሎት ክስ የመሰረተ ሲሆን ተከሳሾች መልሳቸውን ይዘው እንዲቀርቡ ለየካቲት 24 ቀን 2006 ዓ.ም ቀጠሮ ተሰጠ፡፡ አንድነት ፓርቲ፤ “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” የተሰኘ አገር አቀፍ የ3 ወር […]

ሌላኛው ሰሞነኛ ጉራማይሌ የፖለቲካችን ገፅ አንጋፋውን የኦሮሞ ልሂቅ ሌንጮ ለታን የተመለከተው ርዕሰ-ጉዳይ ነው፡፡ ኦነግን በመመስረትም ሆነ ፖለቲካዊ ቁመና ይዞ ህልው እንዲሆን ከዮሀንስ ለታ በላይ ማንም የለፋ እንደሌለ ይነገራል፤ ዮሀንስ ከጓዶቹ ጋር ተባብሮ ድርጅቱን ሲመሰርት ካነገበው አጀንዳ አኳያ ያለውን ተዛምዶ ገልፆ ባይነግረንም፣ ከልጅነት እስከ ጎልማሳነት ይታወቅበት የነበረውን መጠሪያ ስሙን ‹ሌንጮ› በሚል ቀይሮታል፡፡ ኦነግ እስከ 1983 ዓ.ም […]

የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራርና የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊዉ ወጣት ብርሃኑ ተክለ ያሬድ ድርጅታቸው «ውህደት ፈጽሞ አያስፈልግም ብሎ የማያምን እንደሆነ የገለሱ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ግን ዉህደት እንደማይታሰብ አሳወቁ። ፓርቲዉ ከሌሎች ድርጅቶ ጋር አብሮ ለመስራት እና ለመዋሃድ ፈጽሞ የተዘጋ በር እንደሌለው የገለጹት አቶ ብርሃኑ ከዉህደት በፊት ግን መቅደም ያላባቸው ጉዳዮች (የቤት ስራዎች) እንዳሉ ይናገራሉ። መሰራት ያላባቸውን የቤት […]

በዘመነ ኢህአዴግ ከታሪክ ተጠያቂነት በፍፁም ሊያመልጡ ከማይችሉ የፖለቲካ ድርጅቶች መካከል ብአዴን እና ኦህዴድ በግንባር ቀደምትነት ይሰለፋሉ፡፡ ሁለቱም ‹እንወክለዋለን› በሚሉት ሕዝብ ላይ ተደጋጋሚ ክህደት ለመፈፀማቸው፣ ደርዘን ያለፉ ድርሳናትን ማዘጋጀት እንደሚቻል እናውቃለን፡፡ አልፎ ተርፎም ህወሓትን ከመሰለ የማፍያ ቡድን ጋር ግንባር ፈጥረው ‹‹ወከልነው›› የሚሉትን የማህብረሰብ ክፍል ህልውና ማድቀቃቸው እውነት ነው፡፡ በርግጥ ምንም እንኳ የሀገር አንድነትን አደጋ ላይ የጣለ […]