ጠ/ሚንስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ፤ የኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት፤ ዛሬ ባካሄደው 26ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ በመገኘት መንግሥታቸው ባለፉት ዘጠኝ ወራት ያከናወነውን የአቅድ አፈጻጸም ማቅረባቸውን ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር የላከልን ዘገባ ያስረዳል።

ፖሊስ ቅስቀሳው ላይ ያልነበሩ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችንም እያሰረ ነው፡፡ በትላንትናው እለት በቅስቀሳ ላይ እያሉ የታሰሩትን አባላትና ደጋፊዎች ሁኔታ ለማጣራት ወደ የካ ፖሊስ ጣቢያ ያቀኑ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላትን ፖሊስ አስሯቸዋል፡፡
በዛሬው ቀን ካሳንቺስ ስድስተኛ ፖሊስ ጣቢያ የታሰሩት 1. ብሌን መስፍን 2. አስናቀ በቀለ 3. መስፍን 4. ተስፋዬ አሻግሬ 5. እዮብ ማሞ 6. ኩራባቸው 7. ተዋቸው ዳምጤ የካ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው የሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች 1. ፍቅረ ማሪያም አስማማው 2. እያስፔድ ተስፋዬ 3. ጋሻው መርሻ 4. ተስፋዬ መርኔ 5. ሀብታሜ ደመቀ 6. ዘሪሁን ተስፋዬ 7. ጌታነህ ባልቻ 8. ንግስት ወንዲፍራው 9. ሜሪን አለማየሁ ናቸው
(የሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል ሰልፉ እውቅና እንደተሰጠው የገለጸበት ቅጽ ተያይዟል)

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ፣ በዘርና በጎሣ ላይ ያተኮረው የደቡብ ሱዳን የጀምላ ግድያ እጅግ እንዳሳሰበው ገለጠ። የመንግሥታቱ ድርጅት ዋና ጸሐፊ ቃል አቀባይ እንዳሉት ድርጅቱ የጅምላ ጭፍጨፋውንና ለግድያው መባባስ አስተዋጽዖ ያደረጉትን አካላት አውግዟል።

ፖለቲካ አንድ ሰው በአንድ ሃገር ወይም ህብረተሰብ ያለው ስርዓት ወይም የመንግስት ፖሊሲዎችንና አገዛዝን በተጨባጭ በመተንተንና በመገምገም ከአመለካከቱና ከዕምነቱ ጋር አገናዝቦ በመደገፍ ሥርዓቱ ወይም ሁኔታው እንዲቀጥል ለማድረግ ወይም በመቃወም ሥርዓቱ ወይም ሁኔታው እንዲቀየር ለማድረግ አቋም ይዞ አቋሙንም ተግባራዊ ለማድረግ የሚንቀሳቀስበት የሥራ ዓይነት (Business) ነው፡፡ ስለዚህም ትክክለኛ ፖለቲከኞች የመንግስት ሥልጣን የያዘውም አካልም ሆነ ያልያዙት እና ሌላ አማራጭ […]

ንቅናቄው የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃና ፍትሐዊ ምርጫ (Millions of Voices for Free & Fair Election) የሚል መሪ ቃል ይኖረዋል፡፡ ከህዝብ ግንኙነት ያገኘነው መረጃ እንደሚያመለክተው ማክሰኞ ዕለት የአንድነት ስራ አስፈፃሚ አስቸኳይ ስብሰባ ካደረገ በኋላ ትግሉን ወደ ህዝቡ ማውረድና ህዝቡ የትግሉ ባለቤት እንዲሆን ለማስቻል የተጀመረው ንቅናቄ ተጠናክሮ የሚቀጥልበት ሁኔታ ላይ ተወያየ፡፡ ስራ አስፈፃሚው ወቅቱ 24 ሰዓት የሚሰራበት መሆኑን […]

የአዲስ አበባ አስተዳደር ሚያዚያ 15 ቀን ለሰማያዊ ፓርቲ በጻፈው ደብዳቤ፣ የሰማያዊ ፓርቲ ሚያዚያ 19 ቀን ሊያደርግ ላሰበው ሰላማዊ ሰልፍ፣ በአስተዳደሩ ሕጋዊ አሰራር መሰረት፣ የሚገባዉን የእውቅና ፎርሞ እንዲሞላና ወደ ቅስቀሳ እንዲሰማራ ጠየቀ። «የእወቅና ጥያቄ ፎርም ሳትሞሉ ሕጉን በመጣስ ወደ ተለያዩ የተግባር እንቅስቃሴ የገባችሁ ስለሆነ ከዚሁ ተግባራችሁ ታቅባችሁ ወደ ህጋዊ አሰራር በመግባት ማሟላት የሚገባችሁን አማልታችሁ የ ወቅና […]

ፖሊስ ያሠራቸውን የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ችሎት ፊት አቅርቧል፡፡

ፖሊስ ሰዎቹን የያዛቸው ላልተፈቀደ ሠልፍ ቅስቀሣ በማድረግና የተደበቀ ዓላማቸውን ከግብ ለማድረስ ሕዝብን ሲቀሰቅሱ አግኝቻቸዋለሁ ብሎ ነው፡፡

በቁጥጥሩ ሥር የቆዩትን አሥራ ሦስት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ፖሊስ በሁለት የአዲስ አበባ ፍርድ ቤቶች ዛሬ አቅርቧል፡፡

ሰባቱ በዋስ ሲፈቱ ስድስቱ ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቶባቸዋል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የመለስካቸው አምሃን ዘገባ ያዳምጡ፡፡

እስከዛሬ ድረስ በቀረቡ የዋናው ኦዲተር መሥሪያ ቤት ሪፖርት ተለይተው በወጡ ጉልህ ግድፈቶች ምንም የሕግ እርምጃ ተወስዶ እንደማያውቅ የወቅቱ የፓርላማው የመንግሥት አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሊቀመንበር አስታወቁ፡፡

የቋሚ ኮሚቴው ሊቀመንበር እንደራሴ ግርማ ሰይፉ አክለውም “ጠቅላይ ሚኒስትሮቹም እስከዛሬ እርምጃ አልወሰዱም” ብለዋል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የመለስካቸው አምሃን ዘገባ ያዳምጡ፡፡

 

ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የክትባት ሽፋን በማሳደግ ላይ ባለመውና ዛሬ በተጀመረው የዓለም ክትባት ሣምንት ዜጎች ሁሉ ተሣታፊ እንዲሆኑ ፕሬዚዳንት ሙላቱ ተሾመ ጥሪ አቀረቡ፡፡

ለዝርዝሩ ፕሬዚዳንቱ በብሔራዊ ቤተመንግሥት የሰጡትን መግለጫ የተከታተለውን የእስክንድር ፍሬውን ዘገባ ያዳምጡ፡፡

የሰማያዊ ፓርቲ ሚያዚያ 19 ቀን በአዲስ አበባ ለጠራው ሰልፍ፣ ቅስቀሳ ያደረጉ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት መታሰራቸውን የሰማያዊ ፓርቲ በፌስ ቡክ ገጹ ገለጸ። በአዲስ አበባ አስተዳደር አካባቢ ከተገኙ ምንጮቻችን በደረሰን ዘገባ መሰረት፣ የአዲስ አበባ አስተዳደር ከደህንነት ሃላፊዎች ፣ ሚያዚያ 19 ቀን ለሰማያዊ እንዲፈቀድ መመሪያ መስጠታቸውን በመግለጽ ፣ «እስከ አሁን የሰማያዊ ፓርቲ፣ ለሚያዚያ 19 ቀን ሰልፍ የእውቅና ደብዳቤ […]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በዓለም ዙሪያ በአጽዋማት ጊዜ ብቻ ፤ ከሥጋና ከእንስሳት ተዋጽዖዎች የሚታቀቡ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች መኖራቸው የታወቀ ነው። ዘወትር የሚጾሙት በተለይ «ቤጋንስ» የሚባሉት የሚከተሉት የአመጋገብ ስልት መንስዔ ምን ይሆን? ከጤንነት አኳያስ አመጋገቸው ምን ያህል የተሟላ ነው?

ከ 60 በላይ ብሔር ብሔረ ሰቦች በሚኖሩባት በደቡብ ሱዳን ውጊያው ካለፉት አራት ወራት ወዲህ እንደቀጠለ ነው። የዲንካ ጎሣ ተወላጅ በሆኑት በፕሬዚደንት ሳልቫ ኪር እና ከኑዌር ጎሣ በሚወለዱት በቀድሞው ምክትላቸው

13 የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ትናንት መታሠራቸውን የፓርቲው ፕሬዚደንት ኢንጅንየር ይልቃል ጌትነት አስታወቁ። የፓርቲው መሪ ለዶቼ ቬለ እንዳስረዱት፣ ግለሰቦቹ የታሠሩት ፓርቲው ለፊታችን እሁድ ሊያካሂደው ላሰበው ሰልፍ ቅስቀሳ ሲያካሂዱ እና ወረቀት ሲያድሉ በነበረበት ጊዜ ነው።

ኢጣልያ ባለፉት 48 ሰዓታት ከ1,000 የሚበልጡ ስደተኞችን ማዳኗን የሀገሪቱ የባህር ኃይል ትናንት አስታውቋል። ከሰሜን አፍሪቃ ወደ አውሮPA ለመግባታ ሲሞክሩ የመስመጥ አደጋ የሚያሰጋቸውን ስደተኞች ለማዳን ባለፉት ጊዚያት አንዳንድ ድርጅቶች ተቋቁ መው እየተንቀሳቀሱ ነው።

በ2003 ዓም ወደ ኢትዮጵያ በሕገወጥ መንገድ በመግባታቸው እና የኢትዮጵያ መንግሥት አሸባሪ ከሚለው ከኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ አውጪ ግንባር ታጣቂዎች ጋር አብራችኋል በሚል ተከሰው 438 ቀን ታስረው የነበሩትን ስዊድናውያኑ ጋዜጠኛ

Ethiopian Journalists Forum is a young independent journalists association that undergone its founding assembly two months ago. The Forum, therefore, has – according to law – three months of time since its assembly to be counted as one of registered associations to work towards its goal while processing to acquire license. It is now in this period of grace. However, government media (especially Addis Zemen) launched a campaign against the Forum even before it gets its license and start functioning.

The Ethiopian government has never been a friend to any civil society. The ‘charity law’ that extremely limits foreign financing of civil societies that work on rights issues and the 70/30 project cost regulation which also indirectly limits awareness creating activities, both, were passed because the government undermines (or even dislikes) the role of civil societies in the democratization process. In this regard, we can’t expect love of a new association from a ‘head’ that killed thousands of civil societies in passing restrictive rules and regulations. 

In addition to that, the independent media and Ethiopian government never had a friendly relationship; the former strongly criticize the latter which gags them in a negative response to it. So, ‘journalists association’ means to our government the sum of two evils. In this premise, it’s no wonder that the Ethiopian government is not optimist about the upcoming Forum. But, why is it so pessimist about an association that isn’t even proved will stand strong?

Addis Zemen published many stories that label the new journalists’ Forum as agent for ‘color revolution’. ETv produced a documentary without directly mentioning the Forum but by condemning both the ‘color revolution’ and media use as a tool promoting it. It hated the Forum enough to label it before its establishment. But, its fear of civil societies and the media are not the only factors that made the government this much overwhelmed of the Forum. The already existing journalists’ Associations have fueled the fire.

Anteneh Abraham is an all-time president of Ethiopian National Journalists Union (ENJU). His Association always has the same stand with the government. It claims there are no journalists who are jailed for what they have written. The president, as the saying goes ‘more catholic than the pope’, is more EPRDFite than EPRDF in itself. He was the first person to accuse this newly born Forum for being a ‘foreign agent’ in Addis Admass newspaper. Why? Because Anteneh knew that the Forum will reveal ENJU’s real identity.

ENJU is a relatively and undeservedly accepted union of journalists in a few international societies. It’s even a member of International Forum of Journalists (IFJ) and yet it never considered the imprisonment and exiling of journalists a challenge to the media. All the journalists it has as members are from Walta and Fana Broadcasting Corporate (FBC) – both are mouthpieces of the government as they are businesses run by TPLF heads.

The new Forum, while processing the license, has been informed from the ‘Charity Agency’ that there is a compliant from the existing Associations. The compliant is not clear for me yet. But, it is a compliant from ENJU and others.

These Associations, wearing two hats, want to fool the international community and get recognition while at the same time attend for sweet dishes with the ruling party i.e. serving the needs of it. This can’t sustain if EJF comes to life. Therefore, to stop or not to stop this Forum before formation is a battle for life for these fake journalists’ Associations. They won’t stop it unless one of them are successfully defeated. Unfortunately, the fake Associations have one thing that the Forum hasn’t: they have the government’s support.

ሀገራችን ኢትዮጵያ የብዙ ምሁራን መፍለቂያ ለመሆኗ አለም ይመሰክርላታል፡፡ አንቱ የተባሉ ምሁራንን በማፍራት ለዓለም አበርክታለች፡፡ ለዚህም ማሳያ የሚሆነው በአለም ካሉ ታላላቅ ዩንቨርስቲዎች እና የምርምር ተቋማት እስከ አመራነት ድረስ ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች መገኘታቸው ነው፡፡ እነዚህ ምሁራን በተሰማሩበት ስራ መስክ የሚያስመዘግቡት ውጤት እና በስራቸው ተሸላሚ መሆን ላነሳነው ሀሳብ ማጠናከሪያነት ያገለግለናል፡፡ እጅግ የሚያሳዝነውና ልብ የሚሰብረው ግን ሀገራችን ከእነዚህ ውድ ልጆቿ ተገቢውን ዋጋ አለማግኘቷ ነው፡፡ ሀገራችን የወላድ መካን እየሆነች ነው፡፡ ይህ ደግሞ ሆነ ተብሎ የሚቀነባበር ሴራ መሆኑን እንገነዘባለን፡፡
ሀገራችን ኢትዮጵያ የብዙ ምሁራን መፍለቂያ ብትሆንም ቅሉ በተከታታይ ስልጣኑን የጨበጡት ጭፍን አንባገነኖች በሚያራምዱት አግላይ ምሁር ፖሊሲ ምክንያት እውቀታችሁን እና ገንዘባችሁን በምትወዷት ሀገራችሁ ኢንቨስት አድታደርጉ ሁኔታዎች ባለመመቻቸታቸው የስደትን መራራ ጽዋ እንድትጨልጡ ተገዳችኋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በተለይ ባለፉት 10 አመታት በተቃዋሚዎች መዳከም የሚያታግል ኃይል አጥታችሁ እንደቆያችሁም እናምናለን፡፡

ፓርቲያችን ሰማያዊ እያንዳንዱ ዲያስፖራ ሀገር ቤት ያለውን ዜጋ ያክል የኢትዮጵያዊነት መብት አለው ብሎ ያምናል፡፡ ይህ ይረጋገጥ ዘንድም አጥብቆ ይታገላል፡፡ በተለያየ ሁኔታና ወቅት አንባገነኖችን በሀገር ውስጥ እንደታገላችሁ እናምናለን፡፡ ለዚህ ትግላችሁና ለከፈላችሁት ዋጋም እውቅና እንሰጣለን፡፡ በስርዓቶቹ ጨካኝ ዱላ እና ሰቆቃ ብዛት ውድ ሀገራችሁን ትታችሁ የሥደትን ኑሮ ትገፉ ዘንድ ቢበየንባችሁም ስለ ኢትዮጵያ ከመብሰልሰል እንዳልዳናችሁና ሀሳባችሁ ሀገር ቤት ስለ መሆኑ መስካሪ አያሻም፡፡

ውድ የሀገራችን ልጆች እናንተ የሰው ሀገር በምታለሙበት በአሁኑ ሰዓት ሀገራችን ኢትዮጵያ የጉልበት ሰራተኛ ሳይቀር ከቻይናና ከህንድ በከፍተኛ ክፍያ እያስመጣች ትገኛለች፡፡ ይህ ደግሞ የእጅ አዙር ቅኝ ግዛት ስለ መሆኑ ለእናንተ መንገር ለቀባሪ እንደ ማርዳት ያለ ነው፡፡ ይህ በእውነት ለአንድ ሀገር ወዳድ ዜጋ እንደ እግር እሳት ያንገበግባል፡፡ ልማታዊ መንግስት ነኝ በሚል የቃላት ጋጋታ ብቻ ከድሃው ወገናችሁ በሚሰበስበው ገንዘብ የሰከረው ጉልበታም መንግስት ዴሞክራሲና ልማት አንድ ላይ አብረው አይሄዱም በሚል ማሳሳቻ በየ ጊዜው ጉልበቱን እያፈረጠመ የሄደው በአብዛኛው እናንተ ከምትኖሩበት ከምዕራባውያን ሀገራት በሚቀበለው እርዳታ መሆኑ ሀቅ ነው፡፡
ዳያስፖራው በነጻነት መኖር ምን ማለት እንደሆነ በተግባር ያውቀዋል፡፡ ነጻ ሆኖ መስራት ለሀገር ልማት ግንባታ ያለውን ጠቀሜታም ሀገር ቤት ካለው ህዝብ በተሻለ ሁኔታ ይገነዘባል፡፡ ድህነትና አንባገነንነት ባመጣው ጦስ ኢትዮጵያዊ ክብራችን ተገፎ በየ በረሃው ዜጎቻችን እንደ እንስሳት ሲታረዱ፣ እህቶቻንን በቡድን ሲደፈሩ፣ ወገኖቻችን ልብና ኩላሊታቸው ወጥቶ ለገበያ ሲውል እንደማየት ያለ ዘግናኝ ተግባር ምን አለ?!! ይህ ህገ ወጥ ተግባር ሊፈጸምባቸው አይገባም ብላችሁ ያሳያችሁት ለወገን መቆርቆር ይበል የሚያስብልና ሊበረታታ የሚገባው ነው ብለን እናምናለን፡፡
በተለይ የሳውዲ መንግስት በዜጎቻችን ላይ የወሰደባቸውን ህገ ወጥ ተግባር ለማውገዝ ያደረጋችሁትን ርብርብና ለሀገራችን በአንድ ሆ ብላችሁ መቆማችንሁን በድጋሚ እያመሰገንን አንባገነኑን ኢህአዴግ ለመታገል በሚደረገው ትግል አጋራነታችሁን ስለምንገነዘብ ከጎናችን በመሆን ለምታሳዩት ውጣ ውረድ እውቅና እንሰጣለን፡፡ ከዚህ በፊት ያሳያችሁትን የትግል ቁርጠኝነት እንደምትደግሙት በማመን ያላችሁን የገንዘብ አቅም፣ የእውቀትና የተሰሚነት ሚና በመጠቀም የአንባገነኑን ስርዓት አፈና በማጋለጥ ከጎናችን እንድትሰለፉ ስንል እንጠይቃለን፡፡ ዳያስፖራው ያለውን የኢኮኖሚ ነጻነት፣ የሚዲያ ነጻነትና፣ ሀገር ቤት ካለው ጋር ሲነጻጸር ያለው የለሻለ የትምህርት ደረጃና ልምድ፣ እንዲሁም በእርዳታ ሰጭ ሀገራት ያለው የተሰሚነት አቅም ተጠቅሞ ሀገር ቤት ያለውን ትግል በማገዝ ነጻ የምንወጣበትን ቀን ሊያፋጥን እንደሚገባ ፓርቲያችን ያምናል፡፡

ፓርቲያችን የህግ የበላይነትን ለማስፈን ሁሉንም የሀገሪቱን ዜጋ ያሳተፈ ትግል በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ ዘርፈ ብዙ ትግል ውስጥ ደግሞ ሚያዝያ 19/2006 ዓ.ም ‹‹የተነጠቁ መብቶቻችን እናስመልስ›› በሚል መሪ ቃል ታላቅና ደማቅ ሰላማዊ ሰልፍ ያካሂዳል፡፡ በመሆኑም ይህን ሁሉን አቀፍ የሆነ ሰላማዊ ትግል በሞራል፣ በእውቀትና በምክር፣ እንዲሁም በገንዘብ በማገዝ የትግሉ አጋር ትሆኑ ዘንድ ጥሪያችን እናስተላልፋለን፡፡

ከአገራችሁ እርቃችሁ የምትኖሩ በመሆናችሁ አዲስ አበባ ውስጥ አብራችሁን ባትቀሰቅሱ፣ ሰላማዊ ሰልፍ ባትወጡና ባትታሰሩም መረጃውን ለዓለም ህዝብ በማድረስ ከፍተኛ ሚና እየተጫወታችሁ ቆይታችኋል፡፡ በዚህ ሰልፍም አገር ቤት ለሚኖሩ ቤተሰብ፣ ጓደኛ እንዲሁም ሌላው ህዝብ በስልክ፣ በማህበራዊ ድህረ ገጽና የተለያዩ መልዕክት ማስተላለፊያዎች በመጠቀም ህዝቡን የማነቃቃት አቅምና አጋጣሚ ተጠቅማችሁ በትግል ጉዟችን ተሳታፊ እንድትሆኑ ጥሪ እናቀርባለን፡፡

ኑ ራሳችንን ነጻ በማውጣት የአገራችንን እጣ ፈንታ እንወስን!

ዞን ዘጠኝ ከተመሠረተ ድፍን ሁለት ዓመት ሊሞላው ከአንድ ወር ያነሰ ጊዜ ቀረ፡፡ ከዞን 9 ነዋሪዎች ለመጨረሻ ጊዜ ከዞኑ ጽሑፍ ያነበቡት ደሞ የዛሬ ስድስት ወራት ገደማ ነው፡። ዳግመኛ በብርታት መመለሳችንን ልናሳውቅ ስንነሳ ምነው ‹እስከዛሬ የት ነበራችሁ?› የሚል ጥያቄ መነሳቱ ስለማይቀር አጭር መልስ ለመስጠት መሞከራችን አግባብ ነው፡፡
የመጥፋታችን አንዱና ትንሹ ምክንያት የግል ቁርጠኝነታችንን በነበረበት ሁኔታ መቀጠል አለመቻሉ ነበር፡፡የቡድን አራማጅነት ሙሉ በሙሉ የበጎ ፍቃደኝነት ስራ እንደመሆኑ መጠን በግል ህይወታችንና በበጎ ፍቃደኝነት በምንሰራው የቡድን አራማጅነታችን መካከል ሚዛን መጠበቅ ከብዶን አንገዳግዶናል፡፡ ይህ ተግዳሮት ግን ብቻውን አልነበረም፡፡ አገራችን ኢትዮጵያ ሐሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት በሚገባ የሚታፈንባቸው አገራት አንዷ መሆኗን ከዚህ ቀደም ከምናውቃቸው ምሳሌዎች በተጨማሪ በተለይ ባለፋት ስድስት ወራት በተግባር አይተነዋል፡፡
ለነገሩ የዜጎች ሐሳብን መግለጽ በገዢዎቻችን ዓይን የነውር ያክል እንደሚቆጠር የተረዳነው ገና ቡድናችን ሥራውን በይፋ የጀመረ ሰሞን አንድ ዞን ዘጠኛዊ ላይ በደረሰ ግልጽ ማስፈራሪያ ነበር፡፡ ከማኅበራዊ አውታሮች እምብዛም ያልወረዱ እንቅስቃሴዎችን ዝም ብለን ስንቀጥል፣ በከፊል የተረሳን መስሎንም ነበር፡፡ ከወራት በፊት መልሶ የት ወጡ፣ የት ገቡ፣ ምን አደረጉ የሚሉ ጥያቄዎች እና ክትትሎች በዙሪያችን እየተደረጉ እንደሆኑ እና በአንድም በሌላም መንገድ፣ ከዞኑ አባላቶችና ወዳጆችም ጭምር ከ‹‹ደኅንነቶች›› በመጡ መልዕክቶች የማናውቀው ስህተት እየተፈለገብን እንደሆነ አውቀናል፡፡
ይህም እስከዛሬ የምናወቀውን ሐሳብን በነጻነት የመግለጽ አፈናን በተቋማትና በባለሞያዎቹ ላይ ብቻ ሳይሆን እንደ ዞን ዘጠኝ ባሉ እጅግ በጣም ኢመደበኛ በሆኑ የግለሰቦች ስብስቦችን ሰለባ የማድረግ አቅም እንዳለው እንድንረዳ እድል ሰጥቶናል፡፡ በዚህ እውነታውን የማየት፣ የማሰብና የሥራችንን ዓላማ በስህተት የተረዱ ናቸው ብለን ካሰብናቸው አካላት ጋር ካደረግነው ውይይት በመነሳት ‹ዝምታ ወርቅ› አለመሆኑን አውቀን ተመልሰናል፡። ከዚህ በኋላ የሚከሰቱ እና ከእንቅስቃሲያችን የሚያርቁንን የግል፣ የቡድን ወይም የውጪ ግፊት ጉዳዮችን በፍጥነት ለዞን ዘጠኝ ነዋሪያን ከነዝርዝር ምክንያቱ ለማቅረብ ቃል እንገባለን፡፡
ሁለቱ አመት ጉዞአችን እንዳደረግነው ሁሉ የተለያዩ ጽሁፎችን ማቅረብ ዘመቻዎችን በማዘጋጀት የተለያዩ ርእሰ ጉዳዮች ላይ ማወያየታችንን እንቀጥላለን፡፡ በሚቀጥለው የሦስተኛ ዓመት የመነሻ ጉዞአችን የተለመዱ የዞኑን ስራዎች ጨምረን አዳዲስ እና ትኩረት የሚገባቸው ወቅታዊ ሥራዎችን ለውይይት ይዘን ለመቅረብ እንሞክራለን፡፡ ሦስተኛ ዓመታችን ከሚጀምርበት ጊዜ አንስቶ እንደተለመደው በወቅታዊ ጉዳዎች ላይ የሚያተኩሩ ሦስተ ዘመቻዎችን እና ተያያዥ ሥራዎችን ይኖሩናል። ዓመቱ በየአምስት ዓመቱ የሚካሄደው ብሔራዊ ምርጫ ዓመት በመሆኑም ጭምር የሥራዎቻችን ትኩረት ወደዚያ ቢሳብ ነዋሪዎች እንደሚረዱት ተስፋ እናደርጋለን፡፡ ብዙ የዞኑ ነዋሪያን እንደሚያስታውሱትና ዞኑ ዋና እሴት የሆነው የንግግርና ተዋስኦን ለማበረታታት እና ትውልዱ የራሱ ትርክት እንዲኖረው የበኩላችንን አስተዋእጾ ለማድረግ የምናደርገው ጥረትም ይቀጥላል፡፡ በዚህም መሠረት ጽሑፎቻችሁን ብታጋሩን ለነዋሪያን የመወያያ ርዕስ ለማድረግ መሞከሩን ሥራ አጠናክረን እንገፋበታለን ፡፡ ሁላችንም የዞን9 አባላት ሃሳብን በነጻነት ለመግለጽ መብት ፣ ለዴሞክራሲ ውይይትና ለሰብአዊ መብት አራማጅ መሆን ህገ ወጥና ሊደበቅ የሚገባው ተግባር ነው ብለን ስለማናምን የአራማጅነት ሚናችን በመጪው ሶስተኛ አመትም እንደበፌቱ ይቀጥላል፡።
መጥፋታችን ያሳሰባቸው፣ የዞን 9 አስተዋእጾን በበጎ የሚያስታውሱ ምክንያት እስከመጠየቅ ጀምሮ እስከማበረታቻ ድረስ ሲለግሱ የነበሩ ግለሰቦችን በማመስገን የምንጀምረው የእናንተ አስተያየት ለመመለስ ካሰብንበት ጊዜ ጀምሮ አንዱ ማበረታቻ መሆኑን ስለምናምን ነው፡፡ ጥያቄዎች ጠይቃችሁ ያልመለስንላችሁ፣ እንደተለመደው ጽሑፎቻችሁን ልካችሁ ያላስተናገድናቸው፣ ለኢሜይል መልእክቶቻችሁ ምላሽ ላልሰጠናችሁ ምናልባትም ብዙ ጠብቃችሁን በቦታው ላላገኛችሁን ሁሉ ይቅርታችሁ ይገባናል፡፡
አሁንም፤ ስለሚያገባን እንጦምራለን!!

ውይይቱ ቀጣዩ የአሰላለፍ ስልትና የምት አቅጣጫ የሚወሰንበት ሊኾን ይችላል ተሳታፊዎች ፍረጃዎችንና ክሦችን በመረጃና በሐሳብ የበላይነት ማጋለጥ ይገባቸዋል (አፍሮ ታይምስ፤ ቅጽ ፩ ቁጥር ፯፤ ማክሰኞ እና ረቡዕ፤ ሚያዝያ ፲፬ – ፲፭ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም.) ገዥው ግንባር ኢሕአዴግ በሃይማኖት ይኹን በማንኛውም ሽፋን የሚደረግን የፖሊቲካ ግጭት ለመመከት በሚል በአዲስ አበባ በተለያዩ አደረጃጀቶች ውስጥ ከታቀፉ አባሎቹ ጋራ ውይይት በማካሔድ …

[email protected] ከፋሲካ/ትንሳኤ ቀን (ሚያዚያ 12) በስተቀር፣ ከመጋቢት 28 ጀምሮ ያሉ እሁዶችን ( መጋቢት 28 ፣ ሚያዚያ 5፣ ሚያዚያ 19 ቀን) የአንድነት ፓርቲ ሰልፍ ለማድረግ ቢያሳውቅም ከአስተዳደሩ እውቅና እስከአሁን ማግኘት አልቻለም። አገዛዙ የአንድነትን ሰልፍ ለምን እንደፈራ አልገባኝም። አንድነት ጠንካራ ድርጅታዊ መዋቅር ያለው እንደመሆኑ ሚሊዮኖች ይመጣሉ የሚል ጥርጣሬ ስላለም ሊሆን ይችላል። በአንጻሩ ሌላ የፖለቲካ ድርጅት የሰማያዊ ፓርቲ፣ […]

ከአዲስ አበባ የደረሰን ዜና እንደሚጠቁመው፣ የአንድነት ፓርቲ ሚያዚያ 19 ሰልፍ ለማድረግ ቢጠይቅም፣ የፖሊስ አዛዞች በዚያን ቀን በቂ ጥበቃ ማዘጋጀት አንችልም በማለታቸው፣ አስተዳደሩ ሚያዚያ 26 ቀን እንዲደረግ ጠይቆ የነበረ ሲሆን፣ ለሚያዚያ 26 የእውቅና ደብዳቤ ለመዉሰድ ወደ አስተዳደሩ ጽ/ቤት ያመሩት የአንድነት ከፍተኛ አመራሮች፣ የእውቅና ደብዳቤ ሳይቀበሉ መመለሳቸውን ያነጋገርናቸው የአንድነት አመራር አባል ገለጹ። የአስተዳደሩ ሃላፊዎች፣ ከደህንነት ጽ/ቤት ለአንድነት […]

ኢትዮጵያ በቢሊዮኖች ብር የሚቆጠር ገንዘብ በተለያዩ ምክንያቶች ማጣቷን ዋና ኦዲተር ገመቹ ዱቢሶ አስታወቁ፡፡

ዋና ኦዲተሩ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡት የ2005 በጀት ዓመት ሂሣብ ሪፖርት ባለበጀት መሥሪያ ቤቶች ሂሣባቸውን በወቅቱ ዘግተው ለኦዲት አለማቅረባቸውም እየተባባሰ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ለተጨማሪና ዝርዝር የተያያዘውን የመለስካቸው አምሃን ዝርዝር ያዳምጡ፡፡

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ቅዳሴው በቤተ መንግሥት ደብረ ገነት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን ይከናወናል ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስ ‹‹ከኹለት ጊዜ በላይ›› በጸሎተ ቅዳሴ አገልግለውበታል የግብጽ ፕሬዝዳንታዊ ዕጩዎች በትንሣኤ ሌሊት ጸሎተ ቅዳሴ ላይ ተሳተፉ (ቅጽ ፩ ቁጥር ፯፤ ማክሰኞ እና ረቡዕ፤ ሚያዝያ ፲፬ – ፲፭ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም.) ከዕለተ ሢመታቸው አንሥቶ ኢአማኒ (non-believer) እንደኾኑ በተለያዩ ሚዲያዎች ሲነገርባቸው የቆዩት የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ዶ/ር …

ስምንተኛዉ የጀርመን አፍሪቃ የኃይል አቅርቦትና ፍላጎት መድረክ ባለፈዉ ሳምንት ከሚያዝያ 5 ቀን 2006ዓ,ም አንስቶ ለሶስት ቀናት ነበር በጀርመኗ ሰሜናዊ ግዛት ሃምበርግ ላይ የተካሄደዉ። የዚህ ዓመት የመድረኩ መሪ ቃል ለዘላቂ ጉድኝት አዲስ ኃይል የሚል ነበር።

በዩክሬን የተባባሰውን ቀውስ ያረግባል ተብሎ ተስፋ የተጣለበት የጄኔቫው ስምምነት እስካሁን ተግባራዊ መሆን አልቻለም ። ከስምምነቱ በኋላም የዩክሬን ውጥረት ተባብሶ ቀጠለ እንጂ አልቀነሰም ።

በንግዱ ዓለም ለተሰማራችሁት ኢትዮጵያውያን በሙሉ፤
በአሁኑ ወቅት ስልጣን ላይ ያለው ፓርቲ ሁሉንም የኢኮኖሚ መስክ ጠቅልሎ በመያዙ በአገሪቱ ኢኮኖሚ የሚገባችሁን አስተዋጽኦ እያደረጋችሁ እንዳልሆነ እንረዳለን፡፡ ለይስሙላ ብቻ ነጻ ገበያን ‹‹ፈቅጃለሁ!›› የሚለው ገዥው ፓርቲ ኢኮኖሚውን በራሱ ድርጅቶች ተቆጣጥሮ ለስልጣን መቆያ መሳሪያ አድርጎታል፡፡ የመንግስት ድርጅት የሚባሉትም ቢሆኑ ኢኮኖሚው ጠቅልለው ለተመሳሳይ አላማ መሳሪያ በመሆን ላይ ናቸው፡፡ ይህን ተከትሎም አገራችን ነጻ ገበያና የግል ባለሃብቶች የተዳከሙባት ግንባር ቀደም አገር ሆናለች፡፡
ይህ በአንድ ኃይል የተጠቀለለ የኢኮኖሚ ስርዓት እናንተ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት በነጻነት እንዳትሰሩ ከማድረጉም ባሻገር ህዝባችን በኑሮ ውድነት እንዲታመስ አንድ ምክንያት ሆኗል፡፡ በተለይ በቅርብ አመታት ከስርዓቱ ጋር አብሮ መሄድ ያልቻለውን የንግዱን ማህበረሰብ ለስርዓቱ እጁን እንዲሰጥ ለማድረግ እንዲመች ከሚሰራው ስራ ጋር የማይመጣጠን ግብር በመጫን ላይ መሆኑን ለመረዳት ችለናል፡፡ ሱቅ በደረቴ የሚሰሩ፤ እንጀራ ጋግረው የሚሸጡ እናቶች፤ የጀበና ቡናና ሌሎቹንም አነስተኛ ስራዎች የሚሰሩ ወጣት ኢትዮጵያውያን ሳይቀሩ የማይችሉት ግብር ተጨኖባቸዋል፡፡ የንግድ ፈቃድ እድሳት፤ የመስሪያ ቦታና ሌሎችም ነጋዴው በኢትዮጵያዊነቱና ለህዝብ በሚሰጠው ጥቅም ሊያገኛቸው የሚገባቸው መብቶች በሙስና ለፓርቲ ባለው ቅርበትና በሌሎች በዚህ ስርዓት በተሳሳቱ አሰራሮች የንግዱን ማህበረሰብ አስረው ይዘውታል፡፡
ነጋዴውን የሚፈራው ህወሓት/ኢህአዴግ የራሱን ነጋዴዎች ደጋፊ ማህበር አቋቁሟል፡፡ ይህም ነጋዴውን በነጻነት ከመስራት ይልቅ የኢሕአዲግ ተለጣፊ እንዲሆን ካለው ፍላጎት መሆኑ የሚያጠራጥር አይደለም፡፡ በአንጻሩ ሌሎች የንግዱ ማህበረሰብ አካላት የራሳቸውን ነጻ የነጋዴ ማህበር ሲያቋቁሙ አይታዩም፡፡ የመስሪያ ቦታ፤ ግብር እና ሌሎችም ነጋዴው የሚጣልበት ግዴታና የሚገባው መብት ላይ ያለውን ኢፍትሃዊነት ለማስተካከል ጥረት የሚያደርግ የንግዱ ማህበረሰብ አካል አይታይም፡፡
ህወሓት/ኢህአዴግ በሁሉም የኢኮኖሚ መስኮች ሊሳካለት ባለመቻሉ እንዲሁም ነጻ ገበያ ተግባራዊ እንዲሆን አለመፍቀዱ የአገራችን ኢኮኖሚ ከመቸውም ጊዜ በተለየ ሁኔታ ተባብሷል፡፡ በዚህም ምክንያት ኢትዮጵያውያን በሰፊው የሚያመርቷቸው ምርቶችም ጭምር ለህዝብ የሚደፈሩ አልሆኑም፡፡ የእነዚህ ምርቶች እጥረት ሲከሰት ጥያቄውን ከእሱ ትከሻ ለማውረድ የሚከሰው የንግዱን ማህበረሰብ ነው፡፡ ይህም በመሆኑ ‹‹ዘይት የደበቀ፣ ስኳር ያልሸጠ፣…›› እየተባለ በሰበብ አስባቡ የስርዓቱ ግፍ ገፈት ቀማሾች ሆናችኋል፡፡
አገራችን ኢትዮጵያ ድሃ ከሚባሉት አገራት ቀዳሚውን ተርታ መያዟን ለንግዱ ማህበረሰብ ማስረዳት ለቀባሪው አረዱት ይሆናል፡፡ የንግዱ ማህበረሰብ ይህን መሰረታዊ ችግር ከስር ከመሰረቱ ለመፍታት በሚደረገው ትግል የራሱን አስተዋጽኦ እያደረገ ባለመሆኑ አገሪቱን ከገባችበት አረንቋ ለማውጣት የራሱን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት መጠቆም ተገቢ ሆኖ አግኝተነዋል፡፡ ይህን ለማድረግም መጀመሪያ የራሱን ነጻነት በማስከበር፣ በመደራጀት የንግዱን ማህበረሰብና ኢትዮጵያውያን አቅርቦቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ የሚያገኙበትን አጋጣሚ መፍጠር አስፈላጊ ነው፡፡ በተለይ በተለይ የራሱን የፖሊሲ ችግር ተለጣፊ ባልሆኑት የንግዱ ማህበረሰብ አካላት ላይ ለማላከክ የማይታክተውን የገዥውን ፓርቲ ተግባር በማጋለጥ እና ከህዝብ ጎን በመቆም ግዴታችሁን መወጣት ይገባችኋል እንላለን፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ ሚያዚያ 19/2006 ዓ.ም ጃን ሜዳ ‹‹የተነጠቁ መብቶቻችንን እናስመልሳለን!›› በሚል ሰላማዊ ሰልፍ ጠርቷል፡፡ መብታችሁን የተነጠቃችሁት የንግዱ ማህበረሰብ አካላትም የራሳችሁንና የቀሪ ኢትዮጵያውያንን መብት ለማስመለስ በሰልፉ ቀዳሚ ተሳታፊ እንድትሆኑ ፓርቲያችን ጥሪውን አቅርቦላችኋል፡፡
ኑ ራሳችንን ነጻ በማውጣት የአገራችንን እጣ ፈንታ እንወስን!

ሀገር የመገንጠል ዓላማ ይዞ የተነሳው የህወሓት ጁንታ፣ በስውር እና በአደባባይ የጫካ ልማዱን መሰረት አድርጎ ሲገድል መኖሩ አዲስ ባይሆንም፣ ከሰሞኑ መረር ያለ እርምጃ ‹‹ግድያ›› ማሰቡን ከጓዳው የወጣ የወሬ ምንጭ ደረሰን፡፡ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት በአዲስ አበባ አስተዳደር ጽ/ቤት ተገኝቼ ነበር፡፡ የመገኘቴ ዓላማም የፊታችን እሁድ ሚያዚያ 26 የሚደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ አስመልክቶ የዕውቅና ደብዳቤውን ለመስጠት የተያዘውን ቀጠሮ በማክበር ነበር፡፡ […]

—— በአዲስ አበባ የሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቂያ ክፍል ኦፊሰር መሆናቸውን ለስድስት በተዳበሏት ቢሮ ውስጥ በምትገኝ ጠረጴዛ ጠርዝ ላይ የተቀመጠች ማስታወቂያ ትመሰክራለች፡፡ ግለሰቡ አቶ ማርቆስ ብዙነህ ይባላሉ፡፡የተዳከመ ገጽታ ተላብሰው ያደረጓትን ነጠላ ጫማ በእግራቸው እያጫወቱ እንግዶችን ይቀበላሉ፡፡ሲናገሩ እጅግ በጣም በዝግታ በመሆኑም የሚሉትን ለመስማት ጆሮን ፈገግታ ወደ ተለየው ፊታቸው ማስጠጋት ግድ ይላል፡፡ ከፊታቸው የቀረበላቸውን ወረቀት እየተመለከቱ ‹‹ ተነጋግረን መልስ […]

በተያዬ ጊዜ ሰማያዊ ፓርቲን የሚመለከት በርካታ ጽሁፎችን ለማየት ሞከርኩ ሁሉም ሰማያዊ ፓርቲን የሚወቀሱ ሆነው አገኘኋቸው፡፡ እኔ በእርግጥ ሰማያዊ ፓርቲ በተደጋጋሚ ብቻውን በመሄድ የዚህን ሀገር ትግል እንደሚለውጥ ሲናገር መስማቱ የዕለት ተዕለት ጉዳይ ሆኖ ቢሰነብትም ቅሉ በእነርሱ ከመቀየም ፓረቲውን ወደፓረቲ ደረደጃ እንዲድግ ቢሰራ ጥሩ ነው እላለሁ፡፡ ይህንን የሰማያዊ ፓርቲ የተናጠል ጉዞ ደግሞ በርካቶች የጠሉት ይመስላል፡፡ እኔ ግን […]

ማንነታቸው ግልጽ ያልሆኑ የደህንነት ሰራተኞች፣ ለአዲስ አበባ አስተዳደር ባስተላለፉት መመሪያ መሰረት፣ ሚያዚያ 19 ቀን ሰላማዊ ሰልፍ ሰማያዊ ፓርቲ እንዲያደርግ እውቅና ሊሰጥ እንደሆነ፣ ከአዲስ አበባ አስተዳደር አካባቢ ያሉ ምንጮቻችን ገለጹ። አስተዳደሩ ሚያዚያ 19 ቀን ሰልፉን ለማድረግ፣ አስቀድሞ የአንድነት ፓርቲ ደብዳቤ ቢያስገባም፣ በዚያ ቀን ሌሎች ዝግጅቶች ስላሉ ለሚያዚያ 26 ቀን ለሰልፉ እውቅና እንደሚስጡ ባሳወቁት መሰረት፣ የአንድነት ፓርቲ […]

ነገረ ኢትዮጵያ ቁጥር 9 ወቅታዊና አገራዊ ጉዳዮችን ይዛ ቀርባለች፡፡

በተለያየ ምክንያትጋዜጣዋን ኮፒ በዕለቱ ያላገኛችሁ ይኸው መረጃ ይደርሳችሁ ዘንድ በፒዲ ኤፍ ለቀናታል
PDF ያንብቧት!

ፕ/ር አለማየሁ፣ ፕ/ር መሳይ፣ አቶ ታዲዮስ ታንቱ፣ ግርማ ሞገስ፣ ታምራት ታረቀኝና ሌሎችም ጥልቅ ትንታኔ ሰጥተውባታል፡፡ ጋዜጣዋ በርዕሰ አንቀጽዋ በፋሲካው ስለ ነጻነት፣ ፍትህ፣ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያውያንን አስበን እንድንውል ትመክራለች፡፡
በጎንደር የሚፈርሱት 30 ሺህ ቤቶች፣ ኢትዮጵያውያን ዛሬም ‹‹አገራችሁ አይደለም ውጡ!›› እየተባሉ መሆናቸውን፣ አርሶ አደሮች መሬታቸውን ያለ ካሳ መነጠቃቸውንና ሌሎች ትኩስ ወሬዎችን አካትታለች፡፡ ሰለሞን ተሰማ ጂ ለዚህ ትውልድ ‹‹ጥራኝ ጎዳናው፣ ጥራኝ መንገዱ›› እንደሚያስፈልገው ይተነትናል፡፡
በላይ ማናዬ በአገልግሎት እጥረትና በሎሎችም ችግሮች ውስጥ ያለውን ህዝብ ‹‹አይ አንተ ህዝብ ትግስትህ!›› በሚል የችግሩን ጥልቀትና የህዝቡን በዝምታ መገዛት ያስነብበናል፡፡ ጌታቸው ሺፈራው ‹‹የዘመኑ የፖለቲካ ሰማዕታቶች››ን ስለ ፖለቲካው ፋሲካ ቅርበትና ርቀት በአንደበታቸው የሚናገሩትን ጽፏል፡፡

የሰብአዊ መብት ተሟጋቹ ደረጀ መላኩ ስለ ኢትዮጵያ ስትራቴጃዊ ጠቀሜታና ከአሜሪካ ጋር ስላላት ግንኙነት ጥልቅ ትንታኔ ሰጥቶባታል፡፡ ሳሙኤል አበበ ‹‹ማጅራት መችው ፖሊስም የህዝብ ነውን?›› በሚል ‹‹ፖሊስ የህዝብ ነው!›› የሚሉትን ይሞግታል፡፡ ሌሎች ጉዳዮችም ተዳስሰውባታል!

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ (ከአዲስ አበባ)

ልዕለ ኃያሏ ሀገረ-አሜሪካን ዛሬ ለተጎናፀፈችው የሕግ የበላይነት የተከበረበት ሥርዓት መሰረት የጣሉት እነ ቶማስ ጃፈርሰን በነፃነት አዋጃቸው ላይ ‹‹ሁሉም ሰዎች በእኩልነት የተፈጠሩ ናቸው›› በማለት ሲደነግጉ፤ እንግሊዛዊው ደራሲ ጆርጅ ኦርዌል ደግሞ “Animal Farm” በሚለው መፅሐፉ፣ ጉልበታም ‹‹ገዥ›› አድርጎ በሳላቸው ገፀ-ባሕሪያት አማካኝነት ‹‹…አንዳንድ እንስሳት (ሰዎች) ግን የበለጠ እኩል ናቸው›› ይለናል። በርግጥ ሁለቱም አይነት አስተዳደሮች መሬት ወርደው ዓለማችንን ዲሞክራት እና አምባ-ገነን በማለት በሁለት ጎራ የከፈሉ የመሆናቸው ጉዳይ አከራካሪ አይደለም።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም

አንድ በሀርቫርድ የኒቨርሲቲ ያጋጠመኝን ነገር መግቢያ ላድርገውና ልቀጥል፤ በአንድ ሴሚናር (የጥናት ውይይት) ላይ አንድ ጥቁር አሜሪካን ፕሮፌሰር ወደአሜሪካ በባርነት በመጡት አፍሪካውያን ላይ የተፈጸመውን ግፍ በመዘርዘር አስረድቶ አሁን ለእነሱ ልጆችና የልጅ ልጆች ካሣ መከፈል አለበት የሚል ክርክር አነሣ፤ ካሣውን የመክፈል ግዴታ የሚጣለው ማን ላይ ነው? ካሣውንስ የመቀበል መብት የሚሰጠው ለማን ነው? የሚሉ ጥያቄዎችን ሳናነሣ ብዙ ሌሎች ጥያቄዎች ይኖራሉ፤

ሙሉውን አስነብበኝ …

ከ ሁለት ሺ ዓመታት በፊት በኢትዮጵያዊው ጃንደረባ የተገለጠው ኢየሩሳሌምን ለመሳለም የሚደረገው ጉዞ ዛሬ የሺዎች ጉዞ ሆኗል፡፡ በእግር ተጉዘው ኢየሩሳሌም ለመድረስ ሱዳንን፣ ግብጽና የሲና በረሃን ያቋርጡ የነበሩት፤ ያለበለዚያም በመካ በኩል ተሻግረው በዮርዳኖስ በኩል ይገቡ የነበሩት አባቶቻችን ክብር ይግባቸውና፣ በኢየሩሳሌም ያቆዩትን ቦታ ለመሳለምና የትንሣኤ በዓልንም በትንሣኤው ቦታ ለማክበር ኢትዮጵያውያን ከሰባ ሺ ብር በላይ እየከፈሉ ይጓዛሉ፡፡

ከዛሬ ሃምሳ ዓመት በፊት የኢትዮጵያውያን ምእመናን የኢየሩሳሌም መታሰቢያ ድርጅት በአዲስ መልክ የኢየሩሳሌምን ጉዞ ሲጀምር በአንድ ድርጅት ብቻ ይከናወን የነበረው ጉዞ፣ ዛሬ ከሃያ በላይ በሚሆኑ አጓጓዦች በኩል ከመላው ዓለም ኢትዮጵያውያን ይሰባሰባሉ፡፡ ከሃምሳ ዓመታት በፊት ከኢትዮጵያ በሚመጡ ተሳላሚዎች የተጀመረው ጉዞ ዘንድሮ ከ27 ሀገሮች በመጡ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ወደሚከናወንበት ደረጃ ደርሷል፡፡ ከዓመታት በፊት በአብዛኛው በሽማግሌዎችና በእናቶች ብቻ ይደረግ የነበረው ጉዞ ዛሬ ከሦስት ወር ጽንስ እስከ 94 ዓመት አዛውንት ተካትተውበት የሚደረግ ሆኗል፡፡

ከዐሥር ዓመታት በፊት የትንሣኤ በዓል በዴር ሡልጣን ሲከበር በአንደኛው የገዳሙ አጥር ጥግ ተሰባስበው ይታዩ የነበሩት ተሳላሚዎች ዛሬ ግቢው ጠቧቸው፣ መንገዶችን አጨናንቀው፣ ጠጠር መጣያ እስከ ማሳጣት ደርሰዋል፡፡ ወይም አንድ የእሥራኤል ጋዜጠኛ እንዳለው ‹‹ነጭ ጎርፍ በፍኖተ መስቀል በኩል ሲፈስ የሚታይበት ተአምር›› ላይ ደርሰዋል፡፡ ድንበር የለያያቸው ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ዜግነት ሳያግዳቸው፣ ሃይማኖት አገናኝቷቸው በአንድ የሚያመልኩበት፣ አንድ ማዕድ የሚቆርሱበት፣ የዘመድ ወግ የሚያወጉበት ሥፍራ ሆኗል፡፡

ይህ ሁሉ እግዚአብሔር የሰጠን ዕድል ቢሆንም ከተጠቀምንበት ነገር ያልተጠቀምንበት ይበልጣል፡፡ የዚህ ዋነኛ ምክንያቱ ደግሞ አስተሳሰባችን ከጠላት ተኮር ሥነ ልቡና ባለመላቀቁ ነው፡፡ ልክ ነው ግብጻውያን አሁንም በዴር ሡልጣን ገዳማችን ላይ ግፍ ይፈጽማሉ፡፡ አሁንም ችግር ይፈጥራሉ፤ አሁንም ገዳሙ እንዳይጠገን ይከላከላሉ፤ ህልውናችን ያበሳጫቸዋል፤ ብዛታችን ያንገበግባቸዋል፡፡ በግብጻውያን ምክንያት የተቀበልናቸው ብዙ መከራዎች አሉ፡፡ እንዳንሠራ የታገድናቸው ነገሮች አሉ፡፡ ግን የሁሉም ነገር መነሻና መድረሻ ግብጻውያን ናቸው ብለን መደምደም አንችልም፡፡ አንዳንዴም ‹‹እኛን የጨረሰን የራሳችን ጠማማ ነው›› እንዳሉት ዛፎች ለግብጻውያን ችግር ፈጣሪነት መነሻ እኛው ሆነን እንገኛለን፡፡

ታሪክ እንኳን እንደሚያስተምረን የዴር ሡልጣን ዋናው በር በግብጻውያን እጅ የቀረው ቁልፉ ለኢትዮጵያውያን እንዲሰጥ በተወሰነ ጊዜ በንጉሥ ምኒሊክ ተወካይና በገዳሙ ተወካይ መካከል ‹‹ቁልፉን መረከብ ያለብን እ ኔ ነኝ›› በሚል በተነሣው ውዝግብ ምክንያት ነበር፡፡ ዛሬ በየዓመቱ በስቅለት ቀን መብራት ይዘን እንለፍ አንለፍ የሚለው ውዝግብ የተፈጠረበት አንዱ ምንያት የኛው ጳጳስ በሰጡት ፈቃድ ነው፤ በገዳሙ በር አጠገብ ያሉት የብረት ቅስቶች የተገነቡት የኛው ጳጳስ በሰጧቸው ፈቃድ ነው፡፡

ግብጻውያን ጠንካራ ብሔራዊ ኮሚቴ አቋቁመን የዴር ሡልጣንን ነገር ዓለም ዐቀፋዊ አጀንዳ እንዳናደርገው አላገዱንም፤ ግብጻውያን በየዓመቱ የሚመጡ ምእመናንን በሚገባ እንዳናስገነዝብ አላገዱንም፤ ግብጻውያን እያንዳንዱ አጓጓዥ እንደ አይጥና ድመት እንዲተያይ አላደረጉም፤ ግብጻውያን በኢትዮጵያና በግብጽ ቤተ ክህነት በኩል ድርድር እንዳይጀመር አላደረጉም፤ ግብጻውያን ለሀገሩ የሚመጥኑ አባቶችን እንዳንመድብ አልያዙንም፤ ግብጻውያን ስለ ገዳማችን ተገቢውን መረጃ እንዳናስተላልፍ እጃችንን አልቆለፉንም፤ ግብጻውያን ምእመናን ተሳላሚዎችን አስተባብረን ሥራ እንዳናሠራ አላሳገዱንም፡፡

ጠላት ሁለት ጊዜ ይጎዳሃል፡፡ የመጀመሪያው በጠላትነቱ የሚሠነዝረው ጥቃት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በእርሱ እያመካኘህ ችግርህን ወደ ውስጥ እንዳታይ ማድረጉ ነው፡፡ ከሁለቱም የሚከፋው ሁለተኛው ነው ይባላል፡፡ የሁሉም ነገር ምክንያትና ሰበብ ጠላትህ ይሆናል፡፡ ሰዎችም በቀላሉ ይቀበሉሃል፡፡ አንተም ለማስረዳት ብዙ አትቸገርም፡፡ ለራስህም የችግርህ ሁሉ ምንጭ አድርገህ ትቀበለውና ሌሎች ነገሮችን አትመለከትም፡፡ አመለካከትህ ጠላት ተኮር ይሆናል፡፡


በኢየሩሳሌም ገዳሞቻችንም የሚታየው ይኼው ነው፡፡ ለማንኛውም ነገር ምክንያቶቹ ግብጻውያን ናቸው፡፡ ስለ ራሳችን ድክመት የሚያወራ የለም፡፡ ራሱን የሚወቅስም አልተገኘም፡፡ ብዙ ችግሮቻችን ግን ግብጻውያን ባይኖሩም የሚኖሩ ናቸው፡፡ ከጠባያችን፣ ከአሠራራችንና ከአካሄዳችን የሚመነጩ ናቸው፡፡ የግብጻውያኑ ችግርም መፍትሔ ያላገኘው እኛ ስለያዝነው ይመስለኛል፡፡ ነገሩን ጠበቅ አድርገን በመያዝ ብርቱ ሃይማኖታዊ፣ ዲፕሎማሲያዊና ፖለቲካዊ ጫና ለማሳረፍ የምናደርገው ጥረት አለመኖሩ፡፡ የዴር ሡልጣን ነገር ትዝ የሚለን ለትንሣኤ በዓል ጊዜ መሆኑ፤ ከዚያ በቀር ይህን ጉዳይ ሥራዬ ብሎ የያዘ አንድም ቤተ ክህነታዊ አካል አለመኖሩ፡፡ ግብጾችኮ ጉዳዩን በፓርላማ ደረጃ በብሔራዊ ኮሚቴ ነው የሚከታተሉት፡፡ እኛኮ እንኳን ፓርላማ ቤተ ክህነት የሚያውቀው ኮሚቴ የለም፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስም ቢሆን ከኢየሩሳሌም ገዳማት በሚቀርብ ጥያቄ ይወያያል እንጂ የኢየሩሳሌም ገዳማትን ጉዳይ በዝርዝር አጥንቶ፣ የድርጊት መርሐ ግብር ቀርጾ፣ አካል አቋቁሞ፣ ከሚመለከታቸው ጋር ኅብረት መሥርቶ ዘላቂና ተከታታይነት ያለው ሥራ አይሠራም፡፡ አብዛኛው የኢየሩሳሌም ገዳማትን የሚመለከተው አጀንዳም ‹‹አቡነ እገሌ ይነሡ አይነሡ›› በሚለው ላይ የሚያተኩር ነው፡፡

በፓትርያርኮች ደረጃ በግብጽ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን መካከል ውይይት ሲደረግም የኢየሩሳሌም ገዳማችን ጉዳይ አጀንዳ ሆኖ የተነሣበት ጊዜ የለም ማለት ይቻላል፡፡ ቢያንስ ውይይት ለመጀመር፣ ችግሩን ለመፍታትና አንዳች የስምምነት ደረጃ ላይ በየእርከኑ ለመድረስ የሚያስችል መግባቢያ እንኳን የለም፡፡ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በቅርቡ ወደ ግብጽ ይሄዳሉ፡፡ እስከ አሁን ባለኝ መረጃ ዴር ሡልጣን የአጀንዳቸው አካል የሆነ አይመስለኝም፡፡ ለግብጻውያን ግን ዴር ሡልጣን ከዓባይ ቀጥሎ ከኢትዮጵያን ጋር ላላቸው የዲፕሎማሲ ግንኙነት አንዱ አጀንዳቸው ነው፡፡

ይህንን በዚህ እንተወውና ለመሆኑ ወደ ኢየሩሳሌም ገዳማት የምንመድባቸው አባቶች መመዘኛቸው ምንድን ነው? የሃይማኖት ትምህርት፣ የእምነት ጽናት፣ ለጸሎትና ለአገልግሎት ያላቸው ፍላጎት፣ ለመማር ያላቸው ትጋት፣ ከአካባቢው ጋር ተዛምደው ለመኖር ያላቸው ዝግጁነት፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ አምባሳደር ለመሆን ያላቸው ችሎታ ይታያል? ከዐሥር ዓመታት በላይ ተቀምጠው ዐረብኛና ዕብራይስጥ የማይችሉ ከሆነ ኢየሩሳሌም መኖር ጥቅሙ ምንድን ነው? አገልግሎቱ ሲሆን ከሀገር ቤት ካልበለጠ ካልሆነም እንደ ሀገር ቤቱ ካልሆነ በኢየሩሳሌም ገዳማት መኖሩ በአሜሪካ ከመኖር ልዩነቱ ምንድን ነው? በኢየሩሳሌም ገዳማችን ደረጃውን የጠበቀ፣ አባቶችን ለዓለም አቀፋዊ አገልግሎት የሚያበቃ ትምህርት ቤት ከሌለን ኢየሩሳሌም መመደብ ከሥጋዊ ዕድል በዘለለ ጥቅሙ ምንድን ነው? የራሳችን የቅብዐ ቅዱስ ማዘጋጅ፣ የዕጣን መቀመሚያ፣ የንዋያተ ቅድሳት ማዘጋጃ፣ የመስቀል መሥሪያ፣ ከሌለን ኢየሩሳሌም መመደብ ጥቅሙ በዶላር ደመወዝ ማግኘት ነው ማለት ነው፡፡

የኢየሩሳሌም ገዳማችን ቤተ ክርስቲያናችን ከሌሎች አብያተ ክርስቲያናት ጋር ያላትን ግንኙነት የሚያጠናክሩ፣ ከአካባቢው ባለ ሥልጣናት ጋር በሚገባ ተግባብተው የገዳማችንን መብት የሚያስከብሩ፣ በልዩ ልዩ ሞያ ሠልጥነው ለነገዋ ቤተ ክርስቲያን ተስፋ የሚሆኑ፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን ለማወቅ የሚመጡትን ምሁራን በደረጃቸው የሚያናግሩ፣ በማንኛውም መድረክ ተገኝተው ቤተ ክርስቲያንን ሊወክሉ የሚችሉ፣ ልዩ ልዩ የገቢ ምንጭ ፈጥረው የገጠር አብያተ ክርስቲያናትን የሚረዱ ተቋማትን የማያፈሩ ከሆነ መነኮሳቱ ‹‹አረዳ ጠባቂ›› ከመሆን ያለፈ ለቤተ ክርስቲያን በቁዔታቸው ምንድን ነው? መቼም ይህንን ሁሉ ያላደረግነው በግብጻውያን ምክንያት ነው አንልም፡፡


በዚህ በትንሣኤ ሰሞን ከዐሥር ሺ በላይ ኢትዮጵያውያን ምእመናን በኢየሩሳሌም ተገኝተው ነበር፡፡ ነገር ግን እነርሱን በአንድ ጉባኤ ለማስተባበር፣ ስለ ገዳማቱ ሁኔታ በቂ ግንዛቤ ለመፍጠር፣ ፕሮጀክት ቀርጾ ያንን እንዲተገብሩ ለማድረግ፣ ምእመናኑን ለማስተማርና ለማነጽ፣ ጥረት ሲደረግ አላየሁም፡፡ ከዚያ ይልቅ የሀገር ቤቱ አሠራር አልለቀን ብሎ አንዳንድ ቁራጭ ጧፍ ለመሸጥ ነበር መከራ ስናይ የከረምነው፡፡ ውኃ አዙሮ ለመሸጥ ነበር ጥረት ሲደረግ የነበረው፡፡ ምእመናኑን በሚገባ አስረድቶ፣ ዘላቂ ነገር እንዲሠሩ አወያይቶ፣ ለልጅ ልጅ የሚተርፍ ነገር ከመሥራት ይልቅ አንድ ሺ ጧፍ ሽጦ አንድ ሺ ዶላር ለማግኘት መድከሙ በዋናው አልጋ ላይ መተኛት ሲቻል በትራሱ ላይ እንደ መተኛት ነው፡፡

ተሳላሚ ምእመናኑም ራሳቸውን እንደ ቱሪስት ቆጥረው ተሳልሞ ለመጓዝ ከመትጋት ባለፈ የገዳሙን ሁኔታ ለማወቅ፣ ዘላቂና ችግር ፈች ሥራ ለመሥራት፣ አልከፈት ያለውን የቤተ ክህነት በር በሚገባ አንኳኩቶ ለማስከፈት አልቻልንም፡፡ አጓጓዦቹም ምእመናኑ ተገናኝተው፣ ተዋውቀውና ተወያይተው፣ በአንድ ኢትዮጵያዊ መንፈስ አንድ ሥራ እንዲሠሩ ጥረት ሲያደርጉ አይታዩም፡፡ እንዲያውም ተጓዦቻቸው ባለመተዋወቅና በመፈራራት የጎሪጥ እንዲተያዩ ያደርጓቸዋል፡፡

እነዚህን ለምሳሌነት የጠቀስኳቸው በግብጻውያን ብቻ እያመካኘን በመቀመጣችን ያልሠራነው ሥራ ምን ያህል ዋጋ እያስከፈለን መሆኑን ማየት እንድንችል ነው፡፡ ግብጻውያን ርስታችንን ከመንጠቃቸው በላይ በእነርሱ እያመካኘን የኛን ሥራም እንዳንሠራ አድርገውናል፡፡ አሁን ለዴር ሡልጣን መልካም ዘመን ነው፡፡ ኢትዮጵያ በግብጽ ላይ አንገቷን ቀና አድርጋለች፣ የአካባቢው የፖለቲካ ምሕዳር እየተቀየረ ነው፡፡ ምእናንም በብዛት ወደ ኢየሩሳሌም እየመጡ ነው፡፡ ከመላው ዓለምም ተሳላሚዎች እየበዙ ነው፡፡ ይህንን እግዚአብሔር የሰጠንን ዕድል ካልተጠቀምን እንነጠቃለን፡፡ ስለዚህ በአዲስ አስተሳሰብ፣ በአዲስ መንፈስና በአዲስ መንገድ መነሣት አለብን፡፡

እንዴት? በቀጣይ ዐሥር ነገሮችን እጠቁማሁ፡፡

ዴር ሡልጣን፣ ኢየሩሳሌም

“የተነጠቁ መብቶቻችን እናስመልስ” በሚል መሪ ዓላማ ስማያዊ ፓርቲ ያደረገው ጥሪ የተከበረ ግብ ቢሆንም፤ ውጥንቅጥና ውስብስብ በሆነው፡ ሕወሃት በፈንጂ ባጠረው የተግል ጎዳና የሰማያዊ ፓርቲ ብቸኛ ጉዞ መምረጡን በክፍተኛ ኃዘንና ቅሬታ እንድመለከተው ተገድጃለሁ። ጥያቄው ስማያዊ ፓርቲን የመቀበልና አለመቀበል ጉዳይ መደረግ የለበትም። መግለጽም ካስፈለገ፡ ለሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አድናቆት አለኝ። ይህንንም በተደጋጋሚ በዚህ ድህረ ገጽ ላይ አስረግጬ መስክሪያለሁ። በኢትዮጵያና […]