የሰማያዊ ፓርቲ አባላት መታሰር

13 የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ትናንት መታሠራቸውን የፓርቲው ፕሬዚደንት ኢንጅንየር ይልቃል ጌትነት አስታወቁ። የፓርቲው መሪ ለዶቼ ቬለ እንዳስረዱት፣ ግለሰቦቹ የታሠሩት ፓርቲው ለፊታችን እሁድ ሊያካሂደው ላሰበው ሰልፍ ቅስቀሳ ሲያካሂዱ እና ወረቀት ሲያድሉ በነበረበት ጊዜ ነው።