በአፋር በተከሰተው ረሃብ ዜጎች እየተሰደዱ ነው
ሐምሌ ፴ (ሠላሳ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአካባቢው ነዋሪዎች እንደገለጹት ካለፈው ወር ጀምሮ ይጠበቅ የነበረው ዝናብ ባለመዝነቡ በርካታ የቀንድ ከብቶች ሲያልቁ፣ ነዋሪዎችም ቀያቸውን በመልቀቅ ምግብ ፍለጋ እየተሰደዱ ነው።ኢሳት ያነጋገራቸው ዜጎች እንደገለጹት፣ ነዋሪዎች የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታ እንዲደርስላቸው ለመንግስት ጥያቄ ቢያቀርቡም፣ እስካሁን ከመንግስትም ሆነ ከሰብአዊ መብት ድርጅቶች የቀረበላቸው ነገር የለም። በርካታ አርብቶአደሮች ውሃና ምግብ እናገኛለን በሚል …