ከሓላፊነታቸው ውጭ የሚንቀሳቀሱ ፕሮቴስታንትና ጉዳዩን ፖሊቲካዊ ያደረጉ የደኅንነት አባላት ነን ባዮች የኮሌጁን ሓላፊዎች በመጫን ተጠርጣሪዎቹን ከተጠያቂነት ለማዳን እየሠሩ ነው፤ ተጠርጣሪዎቹ በኮሌጁ አስተዳደር የተከለከለ ስብሰባ በግቢው እንዲያካሒዱ ረድተዋቸዋል፡፡ በ‹ደኅንነት አባላቱ› የሚደገፉትና ‹‹የኢሕአዴግ ተወካዮች ነን›› የሚሉት ተጠርጣሪዎቹ፣ ለሃይማኖታቸው የቆሙትን ብዙኃኑን የኮሌጁን ደቀ መዛሙርት በስለትና በፌሮ ብረት የታገዘ ዛቻና ማስፈራራት እያደረሱባቸው ነው፤ ደቀ መዛሙርቱና የኮሌጁ አስተዳደር ጉዳዩን ለጸጥታ …


Source: Courtesy of www.adebabay.com/  PDF

 ይህ ጽሑፍ የእኔን የግል ምልከታና አስተያየት ብቻ የሚመለከት እንጂ በዚህ ጽሑፍ ውስጥ ስሙ የተጠቀሰውን ማኅበርም ሆነ ከእርሱ ጋር የአገልግሎት ግንኙነት ያላቸውን ተቋማት የማይመለከት መሆኑን አበክሬ በመግለጽ ልጀምር።  

  አንድ ብሒል አለ። ውሸትን ደጋግመው ቢናገሩት እንደ እውነት የሚቀበለው ሰው መፍጠር ይቻላል። ስለዚህም ሐሰተኞች ሐሰታቸውን ሳያሰልሱ በተናገሩት መጠን፦ አንደኛ ራሳቸውንም በሐሰታቸው እውነትነት ያሳምናሉ፤ ብሎም ሌሎችን ማሳመን ይችላሉ። ደጋግሞ የመናገር ጥቅሙ ይኼው ነው።

አንዳንድ እውነት የያዙ ሰዎች ደግሞ “እውነት እስከያዝን ድረስ ደጋግሞ መናገር ለምን ይገባል?” ብለው ያቀርባሉ። እውነት አላቸው። ፀሐይ ሲወጣ ጨለማ መሸሹ፣ ሻማ ሲለኮስ ብርሃን መፈንጠቁ ላይቀር “ጨለማን ማውገዝ ምን ጥቅም አለው?” ይላሉ። ይህም እውነት ነው። “ጨለማን ደጋግሞ ከማውገዝ አንድ ሻማ ማብራት” እንደተባለው። ነገር ግን ሐሰት ተደጋግማ በመነገሯ ተከታይ መፍጠር እስከቻለች ድረስ እውነትን ደጋግሞ በመናገር የሚመጣ ምን ችግር አለ? ሻማውንም እየለኮሱ እውነቱንም ደጋግሞ መናገሩስ? ስለዚህ በእውነት ተደጋግሞ መነገር፣ በሻማ መለኮስም አምናለኹ። ደጊመ ቃል እንዲሉ የኢትዮጵያ ሊቃውንት።

 እንኳን አገር ቤት ያለው አንባቢ ይቅርና እኛ ከአገራችን በብዙ ሺህ ማይሎች ርቀን የምንገኘው ሳንቀር በየዕለቱ የምንኮመኩመው አዲሱ ትኩስ ዜና የማኅበረ ቅዱሳን እና “የተጠመደለት ወጥመድ” ጉዳይ ነው። በማኅበራዊ ድረ ገጾች እና በጡመራ መድረኮች፣ እንዲህ በሕትመት ውጤቶች በሰፊው ሽፋን ያገኘ ጉዳይ ሆኗል። ብዙ ኢትዮጵያውያን (እምነት ሳይለይ) ይህንን ጣልቃ ገብነት በጽኑዕ እየተቃወሙት እያወገዙት ነው። “ማኅበረ ቅዱሳን አክራሪ የሚባል ከሆነ እኔም አክራሪነትን እወደዋለኹ” የሚሉ ሐሳቦች በብዛት ተጽፈው ተመልክቻለኹ።

“የአክራሪነቱ ነገር”፣ ነፍሳቸውን ይማረውና አቶ መለስ በፓርላማ ተናግረውት በነበረ ጊዜ፣ እኔን ጨምሮ ብዙ ፀሐፍት አስተያየታቸውን የሰጡበት ከመሆኑ አንጻር ወደዚያ መመለስ አይገባ ይሆናል። ማኅበሩ ከፓርቲ ፖለቲካ ጋር ግንኙነት እንዳለው በመንግሥት ሰዎች እና በደጋፊዎቻቸው የሚነሣውን ሐሳብ በተመለከተ ግን የግል አስተያየቴን ላሰፍር እወዳለኹ።

ማኅበሩ ፖለቲካ ውስጥ አለበት? ለመሆኑ ፖለቲካ ውስጥ መግባት/ አለመግባት ምንድነው? ማንኛውም ሰው የተባለ ፍጡር ፖለቲካዊ አመለካከት አለው። ፖለቲካ አልወድም የሚሉ ሰዎች ራሳቸው እንኳን ፖለቲካዊ አቋም አላቸው። ልዩነቱ እያወቁ ማወቅ እና ሳያውቁ መኖር ናቸው። የተለያዩ ሐሳቦች እስካሉ ድረስ፣ አስተዳደሮች፣ ገዢዎችና ተገዢዎች እስካለን ድረስ ፖለቲካዊ አመለካከቶች መኖራቸው ግድ ይመስለኛል። “ፖለቲካ እና ኮረንቲ በሩቅ” የሚለው ሰው ራሱ በኮረንቲ ከመጠቀም፣ ሕይወቱ በፖለቲካ ተጽዕኖ ሥር መውደቁ እስካለ ድረስ ፖለቲካ የማይነካው ኢትዮጵያዊ አይኖርም።

ይኼ በፖለቲካ ምሁራን ሳይሆን እኔን በመሳሰሉ ለፖለቲካው ዕውቀት ተርታ በሆንን ሰዎች ቋንቋ “ፖለቲካ ውስጥ መግባት ወይም አለመግባት” የምንለው የፓርቲ ፖለቲካ ውስጥ መግባት ማለታችን እንደሆነ ይሰማኛል። ፖለቲከኞች የምንላቸው እንደዚያ ያሉ ሰዎችን ነውና። ማኅበረ ቅዱሳን “ፖለቲካ ውስጥ ገባ/ አልገባም” የሚለውንም የምፈታው በዚሁ አንድምታውና አገባቡ ብቻ ነው።

ማኅበሩ በብዙ ሺህዎች የሚቆጠሩ አባላት አሉት። አባላቱ ሰዎች እንደመሆናቸው ፖለቲካዊ አመለካከት አላቸው። ማኅበሩን በአባልነት ለመቀላቀል የሚያበቃቸው ግን ይህ ፖለቲካዊ አመለካከታቸው አይደለም። የአባላቱ የዓላማ አንድነትና መሠረቱ ማኅበሩ የሚያራምደው ቤተ ክርስቲያናዊ አቋም ብቻ ነው። በሃይማኖትና በአገልግሎት ዓላማ አንድ ናቸው እንጂ በፖለቲካ ርዕዮት የተሰባሰቡ አይደሉም። ሲጀመርስ ስለ ፖለቲካ አመለካከታቸው የት ተጠያይቀው? የት ተገማግመው? የት ተለካክተው? በየትኛው ጊዜ?

ስለዚህም ማኅበሩ አንድ ሃይማኖታዊ አቋም ያራምዳል እንጂ “አንድ ፖለቲካዊ አቋም” የሚባል የለውም። ሊኖረውም አይችልም። ለምን? ምክንያቱም “ፖለቲካዊ አቋምን ለማራመድ” መጀመሪያ ፖለቲካዊ አቋም መያዝ ያስፈልገዋል። ያንን ለማድረግ ደግሞ አባላቱን በሙሉ በዚህ ፖለቲካዊ አቋም ማሳመን ያስፈልጋል፤ ያንን ማድረግ ደግሞ አስቸጋሪ ብቻ ሳይሆን ማኅበሩ የያዘውን ሃይማኖታዊ አቋም የሚጻረርና ማንም ሳይነካው እንዲፈርስ የሚያደርገው ድማሚት ነው።

እዚህ ላይ መነሣት ያለበት ቁምነገር፤ የማኅበሩ አባላት በሃይማኖታዊም ሆነ በፖለቲካዊ አስተሳሰባቸው ራሳቸውን የቻሉ (ማለትም ማመዛዘን የሚችሉ) ክርስቲያኖች እንጂ የአንድ ቡድን ጀሌዎች አለመሆናቸውን ነው። ራሱን የቻለ አስተሳሰብ ያለው ማንኛውም ሰው፣ አባል የሚሆንበትን ድርጅት ያያል፤ ይመዝናል፣ ያስባል። እንደማይጠቅመውና እንደማይስማማበት ከተረዳ ይተወዋል። ጀሌ ግን የተነገረውን ተቀብሎ እንደ በቀቀን ያስተጋባል፤ ሳያውቅ አባል ይሆናል፤ በጥቂት ጥቅም ይደለላል፣ የሚኖርለትም-የሚሞትለትም ቋሚ መርሕ አይኖረውም።

ማኅበረ ቅዱሳንን እና አባላቱን በአገራችን ላለፉት 40 ዓመታት በጠነነው የፖለቲካ ድርጅት ጀሌነት መገምገም ትክክል የማይሆነው ለዚህ ነው። አባላቱ አገልጋዮች እንጂ ካድሬዎች አይደሉም። አመራር ላይ የሚቀመጡት ሰዎች በተራቸው ለማገልገል እንጂ ከሌላው አባል የተለየ መርሕ ለማራመድ አይችሉም። እናራምድ ቢሉም አባላቱ ጀሌዎች ስላልሆኑ ሊከተሏቸው የሚችሉበት ምንም መንገድ አይኖርም። የአባላቱ አንድነት በሃይማኖት እና በሃይማኖት ብቻ ነው። በበሰለ ሚዛን የሚለካቸው ቢኖር ኖሮ በዘር፣ በቋንቋ፣ በፖለቲካ አቋም፣ በትምህርት ደረጃ፣ በዕውቀት፣ በዕድሜ ወዘተ ወዘተ የተለያዩ እንጂ እንደ ሜዳ አህያ አንድ ወጥ እና ልሙጥ አለመሆናቸውን ይገነዘባል።

ስለዚህ አንድ አባል በግልጽ አንድ የፖለቲካ ድርጅት ውስጥ ገብቶ የዜግነት ድርሻውን መወጣት ቢፈልግ ምን ማድረግ እንዳለበት ያውቃል። በማኅበሩ ውስጥ ያለውን የአመራር ኃላፊነት ማስረከብ ይኖርበታል። በዚህ ደረጃ በይፋ ከአመራርነታቸው በሰላም ተሰናብተው ወደፈቀዱት ይፋዊ የፖለቲካ መስመር መጓዝ የቻሉ ሊኖሩ እንደሚችሉ እገምታለሁ። ማኅበሩንም የፖለቲካ ድርጅታቸውንም መምራት የሚችሉበት መንገድ አይኖርም። እነርሱ ፖለቲካዊ ርዕዮተ ዓለማቸውን በማኅበሩ ላይ ለመጫን ቢፈልጉም እንኳን “የፍላጎት መላተም” (“conflict of interests”) ስለሚኖር ሊሳካላቸው አይችልም። የማኅበሩ አባላት በፖለቲካ መሳተፍ የዜግነት መብታቸው ሲሆን በማኅበሩ አገልግሎት መሳተፍ ደግሞ ሃይማኖታዊ የትሩፋት ሥራ እንደመሆኑ ማቻቻል የአባሉ ፈንታ ነው።

ማኅበሩ በፖለቲካ ውስጥ ገብቷል የሚለው (በተለይ በቤተ ክህነቱ ዙሪያ ያሉ ሰዎች) ከ1980ዎቹ ጀምሮ ሲያዜሙት የነበረ የሰለቸ ዜማ ነው። የሚነቅፉት ግን ማኅበሩ “ኢሕአዴግን አይደግፍም” ብለው ስላሰቡ እንጂ “ተቃዋሚ ነው ብለው ስላመኑ” ብቻ አይደለም። ለነገሩ እነዚህ መንግሥትን በዱላነት ለመጠቀም የሚፈልጉ፣ በመንፈሳዊም በዓለማዊም ሚዛን ቢመዘኑ ውኃ የማያነሱ ደመናዎች “ፖለቲካ” የሚሉት አጎብዳጅነትን ነው። መንግሥት እነሱን ይጠቀማል። እነሱም በአቅማቸው በመንግሥት ይጠቀማሉ።

ታዲያ ማኅበሩ የትኛውንም የፖለቲካ ድርጅት እንደማይደግፍ ነገሩን ሥራዬ ብሎ ለሚከታተል ለማንኛውም ሰው ግልጽ ሆኖ ሳለ በዚህ ጉዳይ መወንጀሉ ለምን አስፈለገ? ክርስቶስ አምላካችን ራሱ “ግብር አትክፈሉ ይላል? ለቄሳር አትገዙ ብሏል፤ ንጉሣችን ሳይሆን ንጉሥ ነኝ ብሏል” የሚል ፖለቲካዊ ክስ እንደቀረበበት ሃይማኖትን ብለው የሃይማኖት አገልግሎት ላይ የተሠማሩ ሰዎች በየዘመኑ የሚከሰሱበት ጉዳይ መሆኑን ማስተዋል ያስፈልገናል።

ቅዱስ ሉቃስ “ይህ ሕዝባችንን ሲያጣምም ለቄሣርም ግብር እንዳይሰጥ ሲከለክል ደግሞም፦ እኔ ክርስቶስ ንጉሥ ነኝ ሲል አገኘነው ብለው ይከሱት ጀመር” ሲል እንደጻፈው (ሉቃስ 23፥2)። በሌላው ዓለም ያለውን እንኳን ትተን በአገራችን ያለውን ብናስታውስ፣ ነገር ሰሪዎች በየዘመኑ የነበሩ ቅዱሳን አባቶቻችንን ከነገሥታቱ ጋር በማጋጨት በአደባባይ እስከመገረፍ ያደረሱበት ጊዜ፣ በግዞት በእስር እንዲማቅቁ ያደረጉበት ወቅት እንዳለ ታሪክ ያስተምረናል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫን እና የደብረ ሊባኖስ እጬጌ ጻድቁ አባ ፊሊጶስን ለአብነት ብናንሣ አባ ጊዮርጊስ እንደተጋዘ፣ አባ ፊሊጶስ በአደባባይ ራቁቱን እንደተገረፈ እናነባለን።

ከ1984 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት ላይ ያለ ማኅበር ትናንት እንደፈላ እንደ ክረምት አግቢ ሊታይ አይችልም። መንግሥት ይኼ ሁሉ ሐቲት አይጠፋውም። ማኅበሩ ተቃዋሚም ደጋፊም እንዳይደለ መግለጹ እስካሁን ጉንጭ አልፋ ከመሆን አልዘለለም። መደገፍ የማይችል አካል፣ ባይቃወምም እንኳን ገለልተኛ መሆኑ ለአደጋ ያጋልጠናል በሚል “ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው” የዶሮ ፍልስፍና የተቃኘ ነው።

ከዚህም ባሻገር አባላቱ ከአንድ ዘርና ቋንቋ፣ ባህልና ፖለቲካዊ አቋም የመጡ አለመሆናቸው፤ ይልቁንም ሕብረ ብሔረሰባዊና ኢትዮጵያዊ መሆናቸው እንቅልፍ የሚነሣቸው አካላት መኖራቸው ግልጽ ነው። “አዳሜ በየቅርጫትህ ግባ” ሲባል አንድ ቅርጫት ውስጥ የማይጨመሩ፣ ከሌላውም ቅርጫት ካለው ጋር ዝምድናና ፍቅር ያላቸው፤ ከቅርጫታቸው ውጪ የሚያስቡ ሰዎች ያሉበት ማኅበር መሆኑ የሚያስፈራቸው አሉ።

በውጪ አገር ባሉ የተለያዩ የመንግሥት ተቃዋሚ ቡድኖች ዘንድ ማኅበረ ቅዱሳን ሲጠረጠር እንደኖረ እነርሱም በፈንታቸው “ማኅበረ ቅዱሳን የኢሕአዴግ ደጋፊ መሆን አለበት” ሲሉ ኖረዋል። ለምን እንዲህ አላችሁ ሲባሉ ምክንያቱም “ይህንን የሚያህል ትልቅ ተቋም እንዴት ነጻና ፍፁም ሃይማኖታዊ ብቻ ሊሆን ይችላል? ጠርጥር ጠርጥር” የሚል ጥርጣሬ ያቀርባሉ።

ማኅበሩ አብሯቸው ጀብ ጀብ ላለማለቱ ምክንያቱ ዓላማውና ተፈጥሮው መሆኑን ለመቀበል የአገር ውስጡም የዳያስጶራውም ቡድን፣ እነዚያም እነዚያም ይኸው እንደተቸገሩ አሉ። እነዚያ “የዚያ ደጋፊ ነው” እንዳሉት፣ እነዚያም “የዚያ ደጋፊ ነው” እንዳሉት። ማኅበሩ ደግሞ “አነ ዘክርስቶስ፣ አነ ዘቤተ ክርስቲያን፤ እኔ የክርስቶስ ነኝ፣ እኔ የቤተ ክርስቲያን ነኝ” እንዳለ አለ። መጨረሻውን ደግሞ ዕድሜ ይስጠን እንጂ፣ እናየዋለን።

     ይቆየን – ያቆየን  
(ኤፍሬም እሸቴ)

Deje Selam is a venue of news, views and opinions about or related to the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church. [email protected]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በትናንቱ የአፍጋኒስታን ምርጫ ምንም እንኳን እስልምና አክራሪው የታሊባን ታጣቂ ቡድን ጥቃት እንደሚዘነዝር ዝቶ የነበረ ቢሆንም፤ ለምርጫው በርካታ ሕዝብ መውጣቱን እንደሚያደንቅ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) ገለፀ። ግድያ የታከለበት በርካታ ግጭት ቢከሰትም፤ የትናንቱን ምርጫ የተመድ ስኬታማ ሲል አድንቋል።

የዕለቱ ርዕሶች፤
ካሜሮን፤ ሶስት ታጋጆች የደረሱበት አልታወቀም
ናይጄሪያ፤ 30 የሚሆኑ ሞቱ በርካቶች ቆሰሉ
ማሌዢያ፤ የተሰወረው አይሮፕላን ፍለጋ እና ፍንጭ
አፍጋህኒስታን፤ ኦባማ ምርጫውን አወደሱ
ጀርመን፤ ወደ ሀገሪቱ ሕገ ወጥ የሚገቡት ስደተኞች ቁጥር ክፉኛ ጨመረ
ኢትዮጵያ፤ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ የፓሪሱን ማራቶን አሸነፈ

የሚሊዮኖች ድምፅ ለመሬት ባለቤትነት” በሚል መሪቃል በደሴ የተደረገው የተቃውሞ ሰልፍ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል፡፡ በስፍራው የሚገኙት የአንድነት ፓርቲ ከፍተና አመራሮችና የዞን አመራሮች በሰልፉ ለተሳተፈው የደሴ ህዝብ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ ‪የደሴ ነዋሪዎችም “እድሜ ለአንድነት አስተነፈሰን” በማለት ደስታቸውን ገልጸዋል። የሚሊዮኖች ድምጽ ለመሬት ባለቤትነት በሚል መሪ ቃል አንድነት ፓርቲ የጀመረውን ዘመቻ በማስመልከት የመጀመሪያውን ሰላማዊ ሰልፍ በደሴ ከተማ በተሳካ ሁኔታ ማድረጉ […]

የመሪዎቻችንን የክስ መከላከያዎች ለማሰራጨት እንረባረብ!

ኡስታዝ አቡበክር አህመድና ዳዒ ያሲን ኑሩ ያቀረቡት የክስ መከላከያ በጽሁፍና በድምጽ ተዘጋጅቶ ከታች በሚገኙት ሊንኮች ቀርቧል

1.የኡስታዝ አቡበክር አህመድ ክስ መከላከያው የፒዲኤፍ ጽሁፍ ሊንክ፡-

http://goo.gl/NRSNki

የኡስታዝ አቡበክር አህመድ ክስ መከላከያው የድምጽ ትረካ ሊንክ፡-

http://goo.gl/RSPs2Q

2.የዳዒ ያሲን ኑሩክስ መከላከያው የፒዲኤፍ ጽሁፍ ሊንክ፡-

http://goo.gl/abVvpS

የዳዒ ያሲን ኑሩ ክስ መከላከያው የድምጽ ትረካ ሊንክ፡-

http://goo.gl/FucbrB

መጋቢት 24 አህመዲን ጀበልና ኡስታዝ ያሲን ኑሩ የቀረቡበት ልዩ ዘገባ
በጣም አነስተኛ መጠን ያለው ሊንክ

http://goo.gl/7p9z81

መጋቢት 25 ኡስታዝ በድሩ ሁሴንና
ካሚል ሸምሱ የቀረቡበት ቢቢኤን ልዩ
ዘገባ በጣም አነስተኛ መጠን ያለው ሊንክ

http://goo.gl/TpX7ii

የመሪዎቻችንን የክስ መከላከያዎች
ለማሰራጨት እንረባረብ!
የመሪዎቻችንን የክስ መከላከያዎች ለማሰራጨት እንረባረብ!
to be continued ………..

Image

ጌታቸው ሽፈራው እንደጻፈው ፤- የመመረቂያ ጽሁፌን ለመጨረስ ደፋ ቀና እያልኩ ባለሁበት ወቅት ነው አንድ የማላውቀው ስልክ የተደወለልኝ፡፡ ይህ ስልክ አባል ባለመሆኔ ስራ እንደማላገኝ ተስፋ ወደመቁረጥ በተቃረብኩበት ወቅት ለስራ እንደምፈለግ አበሰረኝ፡፡ ስልኩ ከኢመድኤ (INSA) መሆኑ ተነግሮኛል፡፡

ይህን መስሪያ ቤት ስም ፈጽሞ ሰምቼው አላውቅም፡፡ ለጓደኞቼ ሳወራቸው ከእኔ በፊት አብዛኛዎቹ ተደውሎላቸው እንደነበር አጫወቱኝ፡፡ የህወሓት፣ የብአዴን፣ የኦህዴድ፣ የደኢህዴን ልጆች እርስ በእርሳቸው እንደተጠቋቆሙም ወሬ ደረሰኝ፡፡ በስተመጨረሻ እኔም መጠራቴ ነው፡፡ ሌላኛው ግራ የሚያጋባው ወሬ ግን መስሪያ ቤቱ የስለላ ተቋም እንደሆነ መስማቴ ነው፡፡ ሁለት ሆድ ሆንኩ፡፡ የኋላ ኋላ አይቶ መውጣቱ እንደሚሻል ወሰንኩ፡፡ አንድ በጣም የሚቀርበኝ ጓደኛዬ ስለተቋሙ ካጫወተኝ በኋላ እንዲቀጥሩኝ አባል መሆኔን (ሸውጄ) እንድነግራቸው አግባባኝ፡፡ አልፈለኩም፡፡

ለጥያቄ የተቀጠርንበት ቀን ደረሰ፡፡ ለፈተና ቀረብን፡፡ ጥያቄዎቹ ከጠበቅናቸው በላይ ናቸው፡፡ ከጠበቁት በላይ ስለ ኢትዮጵያ አንድነት በርካታ ጥያቄዎች ቀርበውልኛል፡፡ ከዚህ መርህ ያፈነግጣሉ የተባሉ ጓደኞቻችን ሳያልፉ ቀርተዋል፡፡ ፈተናውን አልፈን ለስልጠና በገባንበት ወቅት ደግሞ ሌላ ተስፋ ሰጭ ጉዳይ ተከሰተ፡፡ በነጻነት መከራከር ቻልን፡፡ በአንድ ትምህርት ዘርፍ (ፖለቲካል ሳይንስ) ለቅጥር ያለፍነው 12 ወጣቶች ሌሎቹን እንድናስተባብር በየ ውይይት ክበቡ ተሰባጠርን፡፡ ኢንሳን ብቻ ሳይሆን ፖለቲካውን የሚርቁትን ይቀይራሉ ተብለንም ‹‹12ቱ ሐዋሪያት›› የሚል ስም ወጣልን፡፡ በኋላ አንዷ የውጭ አገር እድል አግኝታ ስትወጣ ‹‹ይሁዳዋ!›› ብለን ተሳልቀንባታል፡፡ ይሁዳ ያወቀው ይህኔ ነው፡፡ ነገር ሳይበላሽና ሳይቆስሉ ቦታ መያዝን የመሰለ ነገር የለም፡፡

ስልጠናውን ጨርሰን ለአንድ አመት ያህል በነጻነት ሰራን፡፡ የማንኛውም ፖለቲካ ፓርቲ አባል መሆን ይቻላል፡፡ ነገር ግን ይህ አቋም ስራ ላይ ማንጸባረቅ አይፈቀድም ተባልን፡፡ ይህ ለእኛ ትልቅ ነገር ነበር፡፡ አሁን አሁን ሳስበው ግን ለኢንሳዎች ተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ ማለት ኢዴፓ ብቻ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ምክንያቱም አንዱ ‹‹አለቃ›› ስለጉዳዩ ተናግሮ ሳይጨርስ ‹‹ይህን ስል ግን የኢዴፓን አቋም እዚህ (ስራ) ላይ ማንጸባረቅ ይቻላል ማለት አይደለም፡፡›› ሲል አስታውላለሁ፡፡

ብቻ ያ ጊዜ ለመስሪያ ቤቱ መልካም አመለካከት የነበረን ጊዜ ነው፡፡ ጅራትና ምንድን ነበር ወደኋላ የሚመጣው? በእርግጥ ከዚህ በፊት ኢንሳ ጠለፋና ሌሎቹንም ነገሮች እንደሚሰራ መስማት ጀመረናል፡፡ ስለ ጉዳዩ እርግጠኛ ባንሆንም የት ነው የምትሰራው ተብሎ ‹‹ኢንሳ!›› ለማለት የሚያኮራ አልነበረም፡፡ ብዙዎቹ ጓደኞቻችን ‹‹ሰላይ!›› እንመስላቸው ነበር፡፡ የእኛ አገር ችግር ይህ ነው፡፡ ስለላን ገዥዎች አበላሸተውታል፡፡ ህዝቡም ሆነ ሰላይን መልሶ መሰለል የሚባል ነገር አያውቅም፡፡ ዝም ብሎ መራቅ፡፡ ዝም ብሎ ማማት ብቻ ነው፡፡
አሁን ጅራትና ጉድ ጭራሹን እየፈጠጡ መጡ፡፡ የፖለቲካ ፓርቲ አባል መሆን አትችሉም ተባለ፡፡ መጀመሪያ የነበረን ተስፋ ሁሉ እንደገና ተስፋ አጣ፡፡ ይህ በሆነበት ወቅት ነው፣ የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ እንደ አንዳች ክፉ ነገር የሚጠሉትና የሚጠየፉት አቶ መለስ ሰንደቅ አላማውን ከላይ ወደታች ገለበጡት፡፡

እኔም እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ‹‹ሰውዬው ለምን ሰንደቅ አላማውን ገለበጡት?›› የሚል ጥያቄ አነሳሁ፡፡ ከቀናት በኋላ ይህን ሰንደቅ አላማው ላይ የጻፍኩትን ትንሽዬ ነገር ተከትሎ 12 አስቂኝ ከስሶች ቀረቡብኝ፡፡ አብዛኛዎቹ ህገ መንግስቱን ካለመቀበል፣ የፖለቲካ ቡድኖች (እነማን እንደሆኑ እነሱው ይወቁት) አባል ሆነሃል እና ጽንፈኝነት ጋር የተለነቀጡ ናቸው፡፡ በዝርዝር የአሰብ ወደብን የኢትጵያ ነው ብለሃል፣ ኢትዮጵያ የውጭ ብድር አለባት ብለሃል፣ የጋዳፊን ፎቶ ግራፍ አጋርተሃል (ሸር አደርገሃል)፣ ከጉራፈርዳ ስለተባረሩት አርሶ አደሮች ጽፈሃል፣ ኢህአዴግን ግንባራም ብለሃል……የሚሉት ይገኙበታል፡፡

በእነዚህ ክሶች መሰረትም ለ2 ወራት ያህል ከስራ ታገድኩ፡፡ በዚህ ወቅትም ለክሶቼ መልስ እንድሰጥ ታዝዣለሁ፡፡ እናም ክሱ እንዲነሳልኝ የክሶቹን ፍሬ ቢስነት ጠቅሼ ተከራከርኩ፡፡ አይ እኔ ሞኙ! ህግ በሌለበት፡፡ በዚህ ክርክር የዲስሊን ኮሚቴ አባል ናቸው የተባሉ የህወሓት አባላት ልክ እንደ ከሳሽ ‹‹እንዴት ጠቅላይ ሚኒስትሩን ታንቋሽሻለህ›› የሚል ክስ አቅርበው ተከራክረውኛል፡፡ የብአዴን አባላት ደግሞ እነሱን ተከትለው አስተጋብተዋል፡፡ ያም ሆነ ይህ ‹‹በከፍተኛ ወንጀል›› ተባረርኩ፡፡ በዚህ ወቅት አንድ የብአዴን ካድሬ ያለኝ መቼም ሊረሳኝ አይችልም፡፡ የቅርብ አለቃዬ ስለነበር ስለ ነበረኝ ስነምግባር፣ ስለ ስራ አፈጻጸም፣ ክስ የተባሉት የማያስከስሱኝ መሆኑን ገልጬ መባረሬ አግባብ አለመሆኑን አሳወቁት፡፡ እሱም ‹‹ዋናው ታማኝ መሆን ነው፡፡›› ብሎኝ አረፈው፡፡ ኢህአዴግ ብትሆን አትባረርም ነበር ለማለት ነው፡፡ የሚገርመው ይህ ካድሬ ፌስ ቡክ ላይ እራሱን ፈላስፋ አድርጎ ስለነጻነትና ፍትህ ሲዛላብድ የሚውል መሆኑ ነው፡፡

ከተባረርኩ ከሳምንት በኋላ መሰናዘሪያን ተቀላቀልኩ፡፡ ከወራት በኋላ (ጥቅምት 20) ደግሞ አቶ መለስ የማይወዱት ሰንደቅ አላማ በዓል ተከበረ ተባለ፡፡ በእውኑ ግን ተከብረው የዋሉት ሟቹ ሰውዬ ናቸው፡፡ ጥቅምት 21 መሰናዘሪያ በፊት ገጽ አንድ ጽሁፍ (የእኔው ነው) ይዛ ወጣች፡፡ መለስ የገለበጡትን ሰንደቅ አላማ አንግባ ‹‹እውን ኢህአዴግ ሰንደቅ አላማውን ያከብረዋልን?›› የሚል ነው፡፡ መሰናዘሪያ በሳምንቱ አልተመለሰችም፡፡ አታሚው ኢህአዴጎችን ሰንደቅ አላማው ላይ የተጻፈው ጽሁፍ ስላስቆጣቸው እንዳያትም እንደነገሩት አስታወቀን፡፡ በቃ ዳግም ተባረርኩ ማለት ነው፡፡ አሁን ሌላ ስራ መፈለግ ይጠበቅብኛል፡፡ የኢንሳን ልምድ ሳሳይ ደግሞ በርካቶች ይበረግጋሉ፡፡ በግል ሚዲያው ብጽፍም በቋሚነት ለማሰራት አቅም አልነበራቸውም፡፡ አንዳንዶቹ ደግሞ ከገዥው ፓርቲም በላይ ለሚዲያውም ሆነ ለሰራተኛው በዝባዥና ገዳዮች ሆነው አግቻቸዋለሁ፡፡

እንዲህ እንዲህ ስል ለሁለት አመት ያህል ቋሚ ስራ መፈለግ ነበረብኝ፡፡ አራት አመት ያህል ደግሞ ከቤተሰብ ጋር ተቆራርጫለሁ፡፡ 18 አመት ያህል አስተምራኝ፣ ስራ ይዠያለሁ ያልኳትን እናቴን እንዴት ተባርሬያለሁ ልበላት? በፖለቲካ አቋሜ ተባረርኩ ብላት ደግሞ ከዚህ ሁሉ የባሰ ይሆናል፡፡ እናም ዝም ብዬ ስራ ፍለጋ መኳተኑን ያዝኩት፡፡ መነኩሴዋን እናቴን አይኗን ሳላያት አራት አመት ሞላ፡፡ ዛሬ ነገ እሄዳለሁ ስል ቀኑ ነጎደ፡፡ ከዛሬ ነገ አግይቼ አይኗን አያታለሁ ያልኳት እናቴም እንደሳሳኋት፣ እሷም እንደሳሳች ለወዲያው ላንገናኝ ተለያየን፡፡ እናቴ አለፈች፡፡ ያለ አግባብ የተፈናቀልኩበትን ስራ ልይዝ፣ ከያዥኩ ከጥቂት ጊዜም በኋላ ‹‹ልረጋጋ!›› ላይ ታች ስል ለረዥም ጊዜ የተለየኋት እናቴ አመለጠችኝ፡፡

በእርግጥ እናቴ ወርቅን በባሌስትራ ከሚቀይሩት ወገን አይደለችም፡፡ መሬት አልሸጠችም፡፡ ህዝብን በጠባብ ማንነት አልከፋፈለችም፡፡ አገር አላስገነጠለችም፡፡ ሰንደቁን አላዋረደችም፣ አልዘቀዘቀችም፡፡ የህዝብ መብት አላፈነችም፡፡ የህዝብ ገንዘብ ወደ ውጭ አላሸሸችም፡፡ ንጹሃንን አልገደለችም፣ አላሰረችም፡፡ አላፈናቀለችም፡፡ እናቴ ንጹህ ነች፡፡ የእሷ ነፍስ የገነት ነፍስ ነች፡፡ ሌሎች ግን የሞት ሞታቸውን ሞተዋል፡፡ ትውልድም አጥንታቸውን እንደረገመ ይኖራል፡፡

እኔም እላለሁ፡፡ ሞት ማለት የሞት ሞት ሲሆን ነው፡፡ ይህን እናቴ አልሞተችውም፡፡ ምስኪኗ ወላጅ እናቴ የክብር ሞቷን ስትሞት አሁን ለእኔ የቀረኝ አንዲት እናት ብቻ ናት፡፡ እናት አገር ኢትዮጵያ! አገር ብትኖር ወላጅ እናቴ ተቀብራበታለች፡፡ እኔም አልቅሸበታለሁ፡፡ አዎ! ወላጅ እናት ባትሞት እጅጉን መልካም ነበር፡፡ ከሞተች ግን ምን ይደረጋል? ብቻ እናት አገር አትሙት!

እናቴ ሆይ! አምባገነኖቹ ፊቴ ላይ የደቀኑብኝን አቀበት ለመውጣት ስጥር አንቺ አምልጠሽኛል፡፡ አሁን ብችል እናት አገርን ለማዳን ከሌሎቹ ጋር ሆኜ ጠጠር ለመጣል፣ ጥረቴ ለዚህ ባይበቃ እንኳ የራሴን መብት ለማስከበር፣ ይህንን ደግሞ ባልችል ሆድ አደር ላለመሆን አቀበቱ ላይ ነኝ፡፡ ሞት አይቀርምና አንድ ቀን እንደምሞት አውቀዋለሁ፡፡ የሞት ሞት መሞት ግን አልፈልግም፡፡ ደግሞም ከአንቺ ጋር ያለያየኝን አቀበቱን ወጥቼ ሜዳው ሳልደርስ ባልከተልሽ ደስ ይለኛል፡፡ በዚህ አንቺም እንደማትቀየሚኝ አውቃለሁ፡፡ እስከዚያው ግን አምላክ ነፍስሽን በገነት ያኑራት!


የሕወሓት የበላይነት እስከመቼ ?? … መሸዋወድ እስከየት?

ምንሊክ ሳልሳዊ :- የቀድሞውን ወታደራዊ ስርኣት ለመጣል የአሁኑን የሽምቅ ሽብራዊ መንግስት ለማንገስ በበረሃትግል የተሳተፉት የኢሕኣዴግ ድርጅቶች በሃገሪቱ የትግል ታሪክ ውስጥ ጉልህ ድርሻ አላቸው::በኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ስራትን ለማስፈን እጅ ለእጅ ተያይዘን በጋራ ታግለን ህዝባዊ ነጻነትን እናረጋግጣለን በማለት ጫካ የተደባለቁት ድርጅቶች የትግራይን ህዝብ ነጻ በማውጣት ታላቋን ትግራይን እፈጥራለሁ ያለውን ሕወሓት የትግሉ ስኬት ሲከሽፍበት ኢሕዴንን እና ኦሆዴድን በመንተራስ ተረማምዶ ለስልጣን ከበቃ 22 ድፍን አመታትን አስቆተረ::

በ22 አመት የስልጣን ቆይታው የኢሕዴንን እና የኦሆዴድን የትግል አስታውጾ ላማኮላሸት እና ከታሪክ ሂደት መስመር ለማሳት የተጠቀመባቸው ዘዴዎች እና ወታደራዊውን እና የደህንነቱን ተቋም በአንድ ብሄር በማጠር አባል ድርጅቶቹ እና አባላቱ መላወሻ እንዲያጡ ሲሰራ በአደባባይ ታይቷል::ከአቶ ታምራት ላይኔ የፖለቲካ ጠለፋ ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ ቁጥራቸው ይህ ነው የማይባሉ የኢሕዴን ታጋዮች እና ካድሬዎች በተለያዩ የወንጀል ልጣፎች ከያሉበት ተጠልፈው ወደ ሞት እስር እና ስደት ተግዘዋል:: የኦህዼድ አባላትንም እንዲሁ በመጥለፍ በፖለቲካዊ የኦነግ ታርጋ በማሰር በመግደል እና በተለያዩ ጥቅማጥቅሞች በማሸት አንደበታቸውን አሽጎታል:: ይህ የሕወሓት ስራ ማንም የሚያውቀው እና ጸሃይ የሞቀው ሃቅ ነው:: ቢተነተን የማያልቀው የሕወሓት የውስጥ እና የውጭ ሽብር የሚጋለጥበት ቀን መድረሱት የብኣዴን እና የኦህዴድ አባላት ተግተው በመስራት ላይ መሆናቸውን ሌሎችንም ካድሬዎች እንዲንቀሳቀሱ አድርጓል::

የብኣዴን እና የኦህዴድ አመራሮች እና ካድሬዎቻቸው ራሳቸውን ከሕወሓት የበላይነት የማላቀቅ ግዴታ አለባቸው::የሕወሓት የበላይነት ከምን የመጣ ነው? ትግል ከሆነ ሁሉን እኩል ድርሻ ያለውን ትግል በጋር ታግለው ነው ወታደራዊውን ስርኣት ያስወገዱት ለሕወሓት ብቻ ማን ይህን እድል ሰጠው? ሕወሓት ብቻውን አልታገለም ብኣዴንም የራሱ ድርሻ ኦሕዴድም የራሱ ድርሻ አለው:; የአማራውና የኦሮሞው ህዝብ ኢሕዴን/ብኣዴንን አይተው ኦሕዴድን አይተው እንጂ ለሕወሓት ሲሉ የእትዮጵያን መሬት በመምራት አልተባበሩም ስለዚህ የብኣዴን እና የኦሕዴድ አመራሮች እና ካድሬዎች ሊገነዘቡት የሚገባው ጉዳይ ትግሉ ሕወሓት ብቻ የመራው ያደራጀው ያሸነፈው አለመሆን እና የድርጅቶቹም ድርሻ እኩል መሆኑን ነው::

በመከላከያው እና በደህንነቱ ዘርፍ ከፍተኛውን ቦታ በመቆጣጠር ሌላውን የእንጀራ ልጅ ያደረጉት ሕወሓቶች የበረሃውን ዳገት እና ቁልቁለት እነሱ ብቻ የተወጡት አድርገው በማቅረብ የቀሪውን ታጋይ ደም እና ድካም ጥላሸት እየቀቡት ነው::የሕወሓት የበላይነት እንዲያበቃ በመከላከያው እና በደህንነት ተቋማት ውስጥ ያሉ የብኣዴን እና የኦሕዴድ ታጋዮች የራሳቸውን አስታውጾ ሊያበረክቱ ይገባል::የፖለቲካ ባርነት እንዲቆም ትግሉን የማቀጣጠል ሃላፊነት አለባቸው::ምንሊክ ሳልሳዊ

አዲስ አበባ የሚገኘው የአንድነት ቢሮ በከፍተኛ ሁኔታ በፖሊስ እና በደህንነት ሃይሎች ተከቧል። የደሴው ሰልፍ በተሳካ ሁኔታ እየተካሔደ ነው።

Image

ደሴ በህዝቦቿ አንድነት ደምቃለች ። #Ethiopia #Dessie #UDJ #EPRDF #Demonstration
#MillionsVoicesforlandownership

በደሴው የተቃውሞ ሰልፍ ላይ ከአስር ሺ በላይ የሚሆን ህዝብ ፍርሃትን ሰብሮ የደሴ ጎዳናዎች ላይ ወጥቷል።
ህዝቡ አሁንም ወደ ሰላማዊ ሰርፉ በመጉረፍ እየተቀላቀለ ነው። መብቱን እና ነጻነትን በማወቅ ጥያቀዎቹን ለማሰማት የአንድነት ፓርቲ ጥሪን ተከትሎ አደባባይ የወጣው ህዝብ በመፈክር እና በዝማሬ ብሶቱን እያሰማ ነው።
“ኢህአዴግ እንዴት ቢንቀን ነው በ30 ብር አበል ነፃነታችንን ለመንጠቅ የሚሞክረው?”
ለሰልፍ ተሳታፊ የቀረበ ጥያቄ
ፖሊስ መንገድ በመዝጋት እየሞከረነው ሆኖም ሰልፈኛው ግን ጥሶ በማለፍ ላይ ነው፡፡
ተቃውሞ ሰልፍ ላይ ከሚስተጋቡ መፈክሮች ውስጥ
-መሬት ከካድሬው ወደ ህዝቡ ይመለስ
– አንድነት ኃይል ነው
– የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ

airport new design.jpgአዲስ አበባ ፣ መጋቢት 27 ፣ 2006 (ኤፍ.ቢ.ሲ.) ከሁለት ወራት በኋላ ግንባታው የሚጀመረው አዲሱ የኤርፖርት ተርሚናል የዲዛይን ስራ ተጠናቀቀ።

የኢትዮጵያ ኤርፖርቶች ድርጅት እንዳለው በ225 ሚሊዮን ዶላር የሚገነባው ተርሚናል 22 ሚሊዮን መንገደኞችን ማስተናገድ የሚችል ነው።

የድርጅቱ የህዝብ ግንኙነትና የኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ወንድም ተክሉ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ለተርሚናሉ ግንባታ የሚውለው ገንዘብ ከቻይናው ኤግዚም ባንክ በብድር የተገኘ ነው።

የብድር ስምምነቱ በትላንትናው ዕለት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጸደቀ ሲሆን የተርሚናሉ የዲዛይን ስራ ሲ.ፒ.ጂ በተሰኘ የሲንጋፖር ኩባንያ ተዘጋጅቶ ዛሬ ለድርጅቱ ቀርቧል።

ግዙፍና ዘመናዊ ነው የተባለለት የመንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናል የእንግዳ ሳሎን፣ የመሰብሰቢያ አዳራሽና ኢንተርኔት ካፌን በውስጡ አካቷል።

በኤርፖርቱ በስተምስራቅ በኩል የሚያርፈው ይህ ዘመናዊ ተርሚናል ከሁለት ወራት በኋላ በቻይናው ሲ.ሲ.ሲ.ሲ ኩባንያ የግንባታ ስራው ይጀመራል።

አቶ ወንድም ድርጅቱ ከዚሁ ፕሮጀክት ጋር የሚያያዝ የአውሮፕላን ማረፊያ ሜዳ የማስፋፊያ ስራም አማከናወኑንና ይህም ቀድሞ 19 አውሮፕላኖችን ብቻ ይይዝ የነበረው የማረፊያ ሜዳ 45 ግዙፍ አውሮፕላኖችን እንዲያስተናግድ አስችሎታል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም

የአዲስ አበባን መኪናዎች በተለይም በጫት የሚሽከረከሩት ታክሲዎችን በማንኛውም መስቀልኛ መንገድ ላይ ለአምስት ደቂቃ ቆሞ የተመለከተ ሰው በቀላሉ እንደሚረዳው ‹እኔ ካላለፍሁ ማንም አያልፍም!› በሚል መመሪያ መኪናዎቹ ተቆላልፈው እንዲቆሙ ማድረግ ነው፤ እንደሚመስለኝ የአባቶቻችንን ዕዳ እየከፈልን ነው፤ ዱሮ በደጉ ዘመን ሁለት ኢትዮጵያውያን መስቀልኛ መንገድ ላይ ሲገናኙ አንተ-እለፍ አንተ-እለፍ እየተባባሉ የሰማዕታቱንና የቅዱሳኑን ስም እየጠሩ ይገባበዙ ነበር!

ሙሉውን አስነብበኝ …

ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ

ግፍ ከበዛበት ወህኒ የአክብሮት ስላምታየ ይድረሳችሁ!

እነሆ ለሁለተኛ ጊዜ ለአፍታ ያህል እድሉን አግኝቸ ወህኒ የመውረዴን እውነታ ላስረዳችሁ ግድ አለኝ ። ዛሬ አስረግጨ የምነግራችሁ ወህኒ የመውረዴ ምክንያት ሚስጥር ግምሽ እድሜየን ህግና ስርአቷን አክበሬ የኖርኩባትን የሳውዲት አረቢያን ህግ ተላልፊ አይደለም ! የስደተኛው ጉዳይ ያገባኛል በሚል የማቀርበው መረጃ ቅበላየ የማይመቻቸው ፣ ያመማቸው ከተሴረውና እየተሴረ ካለው እገታ ጀርባ ስለመኖራቸው አልጠራጠርም ። … ዛሬ በዚህ ዙሪያ ብዙ አልልም!

ሙሉውን አስነብበኝ …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ወጣት የርዋንዳ ዜጎች በሀገራቸው እአአ 1994 ዓም በተካሄደው የጎሣ ጭፍጨፋ የሞቱትን ለማሰብ 2014 ዓም ከገባ ወዲህ አንድ ማስታወሻ ችቦ በመላይቱ ሀገር ይዘው በመዘዋወር ላይ ይገኛሉ። እአአ የፊታችን ሰኞ፣ ሚያዝያ ሰባት፣ 2014 ዓም ችቦው መዲናይቱ ኪጋሊ ይገባል። በዚሁ ዕለት የጎሣው ጭፍጨፋ የተጀመረበት 20ኛ ዓመት ይታሰባል።

ዛሬ በአለማችን ላይ መንግስታቶች ሊመሩት እና ሊያስተዳድሩት በላው ሕዝብ ላይ የሰብሃዊ መብት ረገጣ እስራት እና ግድያ በሕዝባቸው ላይ እንደሚያደርሱ ይታወቃል በተለይም የአፍሪካ መሪዎች እና መንግስታቶች በአንባ ገነንት እና የሕዝባቸውን ሰብሃዊ መብት በመርገጥ ግንባር ቀደም ተጠቃሾች ሲሆኑ ከእነዚህም ውስጥ አገራችን ኢትዮጵያ አንዶ ናት :: በአሁኑ ሰአት በሀገራችን ኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ያለው መንግስት ከጊዜ ወደ ጊዜ አይን […]

ነገ መጋቢት 28 ቀን 2006 ዓ.ም በሚደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ቅድቀሳእ በደመቀ ሁኔታ እየተከናወነ እንደሆነ ተገልጸ። አቶ ሃብታሙ አያሌዉ ከስፋራዉ ይሄን አስተላልፈዋል ፡ ===================== “እረ ደሴ ደሴ ገራዶ ረጋዶ…….. አለቀልሽ ልቤ አንድነትን ወዶ” ይህንን የማጀቢያ ዘፈን እያሰማ ህዝቡ ከጎናችን ተሰለፈ …… ደሴ በአንድነት አባላትና ደጋፊዎች እንደደመቀች፤ ትንቅንቁም እንደቀጠለ …..ለዚህ ሰዓት ደርሰናል…ነጻነት ከፍርሃት አይገኝም!!! ድል የህዝብ ነው!! […]

የፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ባልደረቦች ክስተቱን በፎቶግራፍ አንስተዋል —————– የአንድነት ከፍተኛ አመራሮችን ያካተተውን የቅስቀሳ ቡድን ተግባር ለማደናቀፍ ፖሊሶችና ደህንነት ነን የሚሉ ግለሰቦች በስውር ቪዲዮ በመቅረፅ እና ስለሙስሊሙ የመብት ጥያቄ የሚስተጋቡ መፈክሮችን ለማስቆም ሙከራ አድርገዋል፡፡ በተለይም የከተማዋ የፀጥታ ዘርፍ ሀላፊ ቅስቀሳው በተደረገባቸው ስፍራዎች በመገኘት የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችን ለማስፈራራትና ከቅስቀሳ ቡድኑ አባል ላይ የቅስቀሳ ቁሳቁስ ለመንጠቅ ሲሞከር […]

ጥንተ ስቅለቱ በዩጋንዳ ምድር
በልዩ ድምቀት እየተከበረ ነው።
መንበረ ፓትርያርኩን በሰሜን አሜሪካ ባደርገው በስደት ላይ በሚገኘው ሕጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ የሚመራው የካምፓላ መካነሠላም መድሐንያለም ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን የደብሩ ማሕበረ ካህናትና ማህበረ ምዕመናን የጌታችን መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጥንተ ስቅለቱን ዛሬቅዳሜ መጋቢት ሃያ ሰባት በከፍተኛ መንፈሣዊ ሥነ ሥርዓት እየተከበረ ነው።በአሁኑ ሠዓት የዕለቱ ቅዳሤ እየተከናወነ ሲሆን የዕለቱ ወንጌል ከማቴዎስ ምዕራፍ ሃያስምንት ተነቦአል።በቀጣይምበዓሉን በተመለከተ የወንጌል ማዕድ በደብሩ አስተዳዳሪቀሲስ ፀሐይ ደስታ ይቀርባል ። ታቦተ ኅጉ ይወጣል ዑደት ይደረጋል ።በመሪጌታ ይሄይስ ዓለሙ መሪነት በደብሩ ፈለገ ህይወት ሰንበት ትቤትመዘምራን ወረብ ይቀርባል።

<ሃሌ ሉያ መርሕ በፍኖት
ሞገሦሙ በፍኖት።
ዝንቱ መስቀል ለአዳም ዘአገብዖ ውስተ ገነት።>
በመጨረሻም ቃለ ምዕዳንና ፀሎተ ቡራኬ ተሠጥቶ የበዓሉ ፍፃሜ እንደሚሆን ከደብሩ ሠበካ ጉባዔ አስተዳደር ጽ/ቤት የወጣው መግለጫ ጠቁሞአል።

አክሊለሠማያት ዘ መካነሠላም

ረዳት ፓይለት ሃይለመድህን አበራን ለማስመለስ የኢህአዴግ ልኡካን በጄኔቫረዳት ፓይለት ሃይለመድህን አበራን ወደ ኢትዮጵያ ለማስመለስ በአቶ አስመላሽ ወልደ-ስላሴ የተመራከፍተኛ የኢህአዴግ ልኡካን ቡድን ጄኔቭ፣ ስዊዘርላንድ ከርሞ ባለፈው ሳምንት ተመልሷል።በፓርላማው የህግ እና የአስተዳደር ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሊቀ-መንበር የሆኑት አቶ አስመላሽ ወልደ-ስላሴ የተመራውይህ ቡድን ከሜይ 13፣ 2014 ጀምሮ የስዊዘርላንድ መንግስት አካላት ጋር በሃይለመድህን ጉዳይ ላይ ለቀናት ተወያይቷል።ስዊዘርላንድ ረዳት ፓይለቱን አሳልፋ እንድትሰጥም ቡድኑ ብዙ ሙከራ አድርጎ እንደነበርና ሙካራው ሁሉ ሳይሳካመቅረቱንም ለማወቅ ችለናል።ቡድኑ የስዊስ ፌዴሬሽን የህግ አካላትን ለማሳመን ካቀረበው ምክንያት ዋነኛው፣ ረዳት ፓይለት ሃይለመድህንአበራ የአእምሮ በሽተኛ መሆኑን እና ይህንንም ከራሱ ቤተሰብ አባላት እንዳረጋገጡላቸው ገልጸዋል። የስዊዝ መንግስት ግንጥያቄውን ውድቅ አድርጎታል።

Image

ለዚህም የሰጠው ዋነኛ ምክንያት፤ የሞት ፍርድን ተግባራዊ ለሚያደርግ መንግስት ማንንምአሳልፌ አልሰጥም የሚል ሲሆን ይህ ባይሆንም፣ በስዊዘርላንድ እና በኢትዮጵያ መሃል ተጠርጣሪ እስረኛን የማስመለስ ውልየለም ብለዋል።በተያያዘ ዜና ወንድሙ ዶ/ር እንዳላማው አበራ እና በጀርመን የምትኖር እህቱ ሃይማኖት አበራ ጄኔቭ ድረስበመምጣት የረዳት ፓይለት ሃይለመድህን አበራን ከሚገኝበት እስር ቤት ጎብኝተውታል። የስዊስ ጠበቆችም የፓይለቱመብት እንዲከበር አጥብቀው እየሰሩ ይገኛሉ። መገናኛ ብዙሃን ላይ ሲደሰኩሩ የነበሩ አንዳንድ የኢትዮጵያ የህግ ባለሞያዎችእዚህ ጉዳይ ላይ እንዲተባበሩ ሲጠየቁ አሳፋሪ ምላሽ መስጠታቸውንም ጉዳዩን በቅርብ ከሚከታተሉት ኢትዮጵያውያንለመረዳት ችለናል።ረዳት ፓይለት ሃይለመድህን አበራ ባለፈው የካቲት 10፣ 2006 ዓ.ም. የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነውንቦይንግ 767 አግቶ ጄኔቭ ስዊዘርላንድ ላይ በማሳረፍ እዚያው የፖለቲካ ጥገኝነት መጠየቁ ይታወሳል። የአለም ዜና ርዕስሁሉ ትኩረት ስቦ የነበረው ይህ ልዩ ክስተት የኢትዮጵያን የሰብአዊ መብት ሁኔታና የአስተዳደር በደል አደባባይ በማውጣቱየገዢው ፓርቲ አባላትን እጅግ እንዳበሳጨ ይነገራል።አንዳንድ መገናኘ ብዙሃን እንደገለጹት የአጎቱ ድንገተና ህልፈት ርዳት ፓይለቱን አስቆጥቶት ነበር። የሃይለመድህንአበራ አጎት፤ ዶ/ር እምሩ ሥዩም ህይወት በድንገት ማለፍ ለብዙዎች ያልተፈታ እንቆቅልሽ ነው። ዶ/ር እምሩ ሥዩም የአዲስአበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር ነበሩ።በአለም ዙሪያ ያሉ ኢትዮጵያውያን ወጣቱ ፓይለት ሃይለመድህን አበራን መደገፋቸውን እንደቀጠሉ ሲሆን በረዳትፓይለቱ ስም የተከፈቱ ድረ-ገጾች እና የፌስቡክ መድረኮች ላይ ሰፊ ዘመቻ በማድረግ ላይ ይገኛል።የስዊዝ ቴሌቭዥን በረዳት ፓይለት ሃይለመድህን አበራ ዙርያ አንድ ዘጋቢ ፊልም የሰራ ሲሆን ይህ ዘገባ ለትንሽግዜ እንዲዘገይ ተደርጓል። ዘጋቢ ፊልሙ አየር ላይ ያልዋለበት ምክንያት የረዳት ፓይለት ሃይለመድህን አበራ ጠበቆችእንዲዘገይ በመጠየቃቸው ነው ሲሉ ጉዳዩን የሚከታተሉት ኢትዮጵያውያን ገልጸዋል።

( አረጋዊለደጀሰላም እንደጻፉት መጋቢት 27/2006 ዓ.ም፤ April 5/2014)፦ ታላቁ የእግዚአብሔር ነቢይ የማይቀረውን የኢየሩሳሌምን ጥፋትና በከላውዴዎን ንጉስ እጅ፣ ለከለዳውያን ሠራዊትና፣ ለባቢሎን ሕዝብ ተላልፋ መሰጠቷን እግዚአብሔር ራሱ በተረዳ ነገር በገለጠለት ጊዜ ነቢዩ ኤርምያስ ልብሱን ቀዶ፣ በራሱም ላይ ትቢያ ነስንሶ፣ በቤተ መቅደስ ውስጥ ከባሮክ ጋር እያለቀሱ ተቀመጡ፡፡ ነቢዩ ኤርምያስ እግዚአብሔርንም ሁለት ታላቅ ነገሮች ለመነው። ጉዳዮቹም፦  

፩ኛ. ተሰውረው እግዚአብሔርን ስለሚያገለግሉባቸው ንዋያተ ቅድሳት ዕጣ ፈንታ  እና
፪ኛ. ስለ ኢትዮጵያዊው አቤሜሌክ ጉዳይ ነበር፡፡

 

ኤርምያስም እንዲህ ሲል ተናገረ፤ “ ጌታዬ ሆይ፤ እለምንሃለሁ፣ ሕዝቡን ብዙ ዘመን ለጠበቃቸው፣ እኔን ባሪያህ ኤርምያስንም ከሃገሩ ሰው ሁሉ ይልቅ ለጠበቀኝ ለኢትዮጵያዊው ለአቤሜሌክ የማደርገውን ግለጥልኝ፡፡ እርሱ ከረግረግ ጒድጓድ አወጣኝ፣ እንዳያዝን የከተማዋን ጥፋት ያይ ዘንድ አልወድለትም” (ተረፈ ባሮክ ፪፥ ፰-፱)።
ኢትዮጵያዊው አቤሜሌክ በነቢዩ በኤርምያስ እንደተመሰከረለት በዚያ ዘመን ከነበረ ማንኛውም እስራኤላዊ ወይም የኢየሩሳሌም ነዋሪ ይልቅ የከተማዋ ለባዕዳን ወረራ ተላልፋ መሰጠት እና ከዚያም ጋር ተያይዞ የሚመጣውን የጥፋት ዘመን ቢመለከት እጅግ የሚያዝንና በኃዘኑም አብዝቶ የሚጎዳ መሆኑን ነበር፡፡
እንግዲህ ነቢዩ  ኤርምያስ “…. እንዳያዝን የከተማዋን ጥፋት ያይ ዘንድ አልወድለትም” ብሎ እንደማለደለትና የኃያሉ የእግዚአብሔር ቸርነት ተደርጎለት አቤሜሌክ እንደዋዛ ለ66 ዓመታት አንቀላፍቶ የወዳጆቹን የእስራኤላውያንን መከራና ስቃይ እንዲሁም የሚወዳትን የኢየሩሳሌምን በጠላት መወረርና መጥፋቷን ሳያይ ቀርቷል፡፡
አባቶቻችን እንኳንስ ለታላቋ ውድ ሀገራቸው ለኢትዮጵያ አንድነት እና ነጻነት፣ ለቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናቸው ልዕልና እና ክብር ይቅርና በፍቅርና በሰላም ለተወዳጇቸው ሁሉ ከራስ በላይ የሚታመኑ የልብ ወዳጅ የሚሆኑ እና የወዳጆቻቸውን ጥፋት በቸልታ የማይመለከቱ የእውነትና የደግነት አውራ መሆናቸውን በብዙ የተከበሩና የታመኑ የዓለማችን ታሪካዊ መዛግብት ላይ ሰፍሮ እናገኛለን፡፡ ይልቁንም በታላቁ መጽሐፍ፡፡
እውነት ነው! እነዛ ቅዱሳንና ጽኑዓን አባቶቻችን በዘመናቸው ከተነሱባቸው ሀገር አፍራሽ፣ ሃይማኖት ለዋጭና፣ ታሪክ አቆሻሽ የሀገር ውስጥና የባዕዳን ጠላቶች ጋር ተጋድለው፣ ኊልቆ መሣፍርት የሌለው ውድ ሕይወታቸውንና ንብረታቸውን ሰውተው እነሆ ዛሬ እኛ በታላቅ ክብርና ሞገስ የምንኖርባትን ብቸኛዋን የክርስቲያን ደሴት አውርሰውናል።
እነሆ ዛሬ ሌላ እውነትም አለን፤ 
ዛሬ በእኛ ዘመን ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በጠና ታማለች፡፡ አዎ የመናፍቃንና የኢአማንያን የተቀናጀና የተቀነባበረ የጥቃት ዘመቻ ተከፍቶባታል፡፡ የማይተባበሩት ተባብረውባት፣ አንድ የማይሆኑት በአንድነት ዘምተውባት፣ በቤቷ የተሰገሰጉት የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ መናፍቃን ከዘመኑ አብዮታዊ ዲሞክራሲያውያን ጋር አብረው እነሆ ሊያጠፏት ዘምተውባታል፡፡
ታላቋ ሀገራችን ኢትዮጵያም እንዲሁ ተዘምቶባታል፡፡ ለፍቅር ሳይሆን ለጥላቻ፣ ለእርቅ ሳይሆን ለበቀል፣ ወደ አንድነት ሳይሆን ወደ መበታተን የሚወስዳት የእነ ዮዲትና ግራኝ ውላጆች፣ የእነ ሞሶሎኒ ደባና ሴራ ራሱን አዘምኖና አደራጅቶ በማን አለብኝነት ዳግም ህልውናዋ ላይ ተዘምቶባታል፡፡
እነሆ ዛሬ፤
፨ ለእኛ እንደ አቤሜሌክ የቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን እና የታላቋን ኢትዮጵያ ሀገራችን ከተደቀነባቸው የወል ጥፋት የሚሰውረን እንደ ኤርምያስ ያለ ነቢይ ከወዴት እናገኝ ይሆን? እንደ ጻድቁ አባታችን እንደ አቡነ ጴጥሮስ ተዋሕዶን ለተኩላ፣ ኢትዮጵያን ለባንዳ አሳልፈን እንዳንሰጥ የሚገዝተን ጀግና መሪ ወዴት እናመጣ ይሆን?
፨ ዛሬ እንደ ቀደሙት አባቶቻችን ትናንት የክርስትና መሰረት እና ደሴት ለነበሩት ዛሬ ግን በግፍ የሚረግፉትን የሶርያና የግብጽ ክርስቲያን ወንድሞቻችንን መታደግ ባንችልም፤
፨ በሀገራችን ገዳማቱና አብያተ ክርስቲያናቱ በቃጠሎ ሲወድሙ፣ ካህናቱና ምዕመኑ በቀያቸው እንደ በግ ሲታረዱና በግፍ ሲሳደዱ፣ ግድ የሚለው የቤተ ክርስቲያን መሪ እንዲሁም የዜጎቹ መሳደድ የሚያሳስበውና ሀገራዊ ኃላፊነት የሚሰማው መንግሥት እና ተቋም የኖራል በሚልና ለችግሮች ሁሉ ተገቢው መፍትሔ በሚመለከተው አካል ይሰጣል በሚል በኢትዮጵያዊ ጨዋነትና በክርስቲያናዊ ሆደ ሰፊነት ፍትህን በትዕግስት መጠበቃችን፤
፨ ቅዱስ ሲኖዶሱ በመንግሥት ባለሥልጣናት ሲደፈርና ብፁዓን አባቶቻችን በዘመኑ ጋጠወጦች ሲጎሸሙና ሲዋከቡ፣ ይልቁንም ለዘመናት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በሁለት ሲኖዶስ ስር እንድትቆይ ያደረጋትን ውጫዊ ሴራ ለማክሸፍ አባቶቻችን በተጉ ጊዜ በመንግሥት አላስፈላጊ ጣልቃ ገብነትና በቤተ ክህነቱ ውስጥ በተሰገሰጉ የፕሮስታንታዊ ተሐድሶ ኑፋቄ አራማጆች ደባ የዕርቁ ሂደት ሲከሽፍ እያየን እንዳላየን ማለፋችን፤  
፨ ይልቁንም በአለፉት ሁለት አሥርት ዓመታት ቤተ ክርስቲያናችን ከየአቅጣጫው ከተጋረጡባት የመናፍቃን የተቀነባበረ ወረራና ጥቃት፣ ከአክራሪ እስልምና ጅሃዳዊ ዘመቻ፣ በእቅፏ ተሰግስገው ከሚገዘግዟትና  በጎጥ ተደራጅተው ከሚቦጠቡጧት ሙሰኛ ካድሬዎች ዘረፋ ከመታደግ መዘግየታችን፤ ወዘተ ያሳበየው የጥፋት ሃይል፤
በሌላ በኩል፤
፨ ጥንታዊ ገዳማቶቻችን በቀለብ፣ በአልባሳት፣ በውኃ፣ በመብራት፣ በንዋየ ቅድሳት፣ ወዘተ እጥረት እንዳይዘጉና ቅዱሳን አባቶችና እናቶቻችን እንዳይሰደዱ፤ የአብነት ጉባዔያት በመምህራን ደሞዝ፣ በተማሪዎች ቀለብና አልባሳት ማጣት ተማሪዎች እንዳይበተኑና ቤተ ክርስቲያናችን ተተኪ እንዳታጣ፤
፨ ይልቁንም በሀገራችን ከተማሪው አብዮት ጋር ተያይዞ በተከሰተውና ዘመን በወለደው የግራ ዘመም የፖለቲካ አስተሳሰብ ምክንያት ከክርስቲያናዊ ሕይወት በተጻራሪው የሚሄደውንና እንደዋዛ የተፈጠረውን የትውልድ ክፍተት ለመሙላት፣ እንዲሁም ወጣቱን ትውልድ ከተጀመረው የክህደት ቁልቁለት ለመታደግ በየአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናቱና በከፍተኛ የትምህርት ተቋማቱ ሌት ከቀን እየባዘነ ያደራጀ፣ ያስተማረና፣ ቤተ ክርስቲያን የወላድ መሐን እንዳትሆን የታደገን ክፍል፤
፨ አንዳንድ አምባገነን የመንግሥት ባለሥልጣናት በተለያዩ መድረኮች ያለ ስሙ ስም፣ ያለ ምግባሩ ምግባር በመስጠት ለመወንጀል ሲሞክሩ በዝምታ መመልከታችን ቤተ ክርስቲያናችንን በሚመሩት አባቶቻችን ጭምር ሲነገር መስማታችን አስደንጋጭ ከመሆኑም ባሻገር መጭውን ጊዜ ከወዲሁ በአንድነትና በጥንቃቄ እንድንመረምርና የመፍትሄ አቅጣጫም እንድናስቀምጥ የግድ የሚል ሆኖ ይሰማኛል፡፡
ስለሆነም ሁላችን የተዋሕዶ ልጆች በአንድነት በማኅበረ ቅዱሳን አባላትና አመራሮች ላይ የተከፈተውን የስም ማጥፋት ዘመቻ በማውገዝና በመንግሥትና በቤተ ክህነቱ ውስጥ ተሰግስገው በሚገኙ የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ኑፋቄ አራማጆች አማካኝነት እየተወሰደባቸው ያለውን የማዋከብና የማሸማቀቅ እርምጃ በአስቸኳይ እንዲቆም አስፈላጊውን የተቀናጀ እንቅስቃሴ ከወዲሁ ማድረግ ይኖርብናል፡፡ ካልሆነ የአቤሜሌክ የልጅ ልጆች የሀገራችንና የቤተ ክርስቲያናችንን ጥፋት በዓይናችን ከማየት ማን ይታደገን ይሆን?
በመጨረሻም፤
ምን አልባት ለዘመናት በቤተ ክርስቲያናችን ላይ ሰፍኖ የኖረው እና እንደ ታሪካዊ እርግማንና ውርደት የምቆጥረው በአባቶቻችን ላይ የተፈፀመው የመከፋፈልና የማሰደድ ስትራቴጂ በማኅበረ ቅዱሳን አመራሮች ላይም ለመድገም መታሰቡና የማኅበሩንም ቢሮ ለመዝጋት ብሎም በተለጣፊ የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ኑፋቄ አራማጆች ለመተካት የተጠነሰሰው ሴራና በቅርቡም በኢቴቪ እየተሰራነው የሚባለው “ማኅበረ-ቅዱሳናዊ ሐረካት” ፊልም ለሚያመጣው ውዝፍ መዘዝ ብቸኛው ተጠያቂ አሁን በሥልጣን ላይ የሚገኘው የሀገሪቱ መንግሥትና የመንግሥቱን አመራር በበላይነት የያዘው ኢሕአዴግ ብቻ መሆኑን ከወዲሁ ማስገንዘብም ማሳሰብም ወደድኩ፡፡
  
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
መጋቢት ፳፩, ፻፪፲፬
Deje Selam is a venue of news, views and opinions about or related to the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church. [email protected]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በአፍጋኒስታን የምርጫ ዋዜማ ለመዘገብ ወደዚያ አምርተው ከነበሩ ጋዜጠኞች መካከል አንዲት ጀርመናዊት የፎቶግራፍ ጋዜጠኛ በዛሬው ዕለት መገደሏ ተነገረ። ካናዳዊቷ ባልደረባዋ ቆስላለች። አፍጋኒስታን ዛሬም ፀጥታዋ መረጋጋትን አይጠቁምም።ታሊባኖች ፣ 6 ዓመታ

የጀርመን ፌደራል ጦር እጎአ ከ2010 አንስቶ የሶማሊያ ወታደሮችን በማሠልጠን ይሳተፋል። እስካሁን ሥልጠናው የሚሰጠው ዩጋንዳ ነበር። የጀርመን የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ትናንት ባካሄደው ስብሰባ ባሳለፈው ውሳኔ መሠረት ከአሁን በኋላ የጀርመን ወታደሮች ስልጠናውን ሶማሊያ ውስጥ መስጠት ይጀምራሉ።

የአንድነት ፓርቲ «ህግን እያከበርን የማስከበር ኃላፊነታችንን እንወጣለን» በሚል ርእስ ዛሬ መጋቢት 26 ቀን 2006 ዓ.ም ይፋ ባደረገው መግለጫ «የአዲስ አበባ ከተማ ሠላማዊ ሠልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል በመጋቢት 26 ቀን 2ዐዐ6 ዓም በቁጥር አ.አ ከስ/1ዐ/3ዐ.4/236 በላከልን ደብዳቤ ሠላማዊ ሠልፉን ለማድረግ በጠየቅንበት ቀን ተመሳሳይ የህዳሴ ግድብ ፕሮግራሞች ስላሉ ተለዋጭ ቀን እንድናቀርብ ጠይቆናል፡፡ በዚሁ መሠረት ለመጋቢት 28 ቀን […]

የአዲስ አበባ አስተዳደር መጋቢት 26 ቀን ለአንድነት ፓርቲ በላከው ደብዳቤ ፣ አንድነት መጋቢት 28 ቀን ሊያደርግ ያሰበዉ ሰላማዊ ሰልፍ ፣ ለሌላ ጊዜ እንዲተላለፍ ጠየቀ። ሰልፉ በታሰበበት ቀን ሌሎች ዝግጅቶች እንዳሉ የገለጸዉ የአስተዳደሩ ደብዳቤ «ተጨማሪ መስመርና ቦታ በመጥቀስ (ሰልፉን) የምታካሂዱበትን ሌላ ቀን ጭምር እንድታሳዉቁን እንገልጻለን» ሲል አስተዳደር ሕግና ስርዓቱን በጠበቀ መልኩ ምላሽ ሰጧል። በመጋቢት 28 ቀን […]

  (By “Abel Sog Sos”)

እስኪ እውነቱን እንነጋገር!
አሁን ባለንበት ዘመን ሃገርን ስለመውደድ የምንማረው/የተማርነው ከየት ነው? ከቤተ እምነቶች ወይስ ከስነ ዜጋና ስነ ምግባር ወይም “ሲቪክስ” ኮርስ? የጸረ ሙስና ኮሚሽን ሳይቋቋም ማን ነበር የራስ ያልሆነን ስላለመውሰድ ያስተማረው? አሁንስ ቢሆን? የሃይማኖት ተቋማት አይደሉምን?

እድሜ ለማኅበረ ቅዱሳንና ወጣቱ በየግቢጉባዔያቱ ተኮትኩቶ ባይወጣ ምን ይውጠን ነበር? አገሩ ሁሉ ሙሰኛ በሙሰኛ ይሆን አልነበር! (መንግስት እንዲያውም ቢያውቅበት ሊደግፈው ይገባ ነበር፤ የ’ርሱን ስራ ማኅበረ ቅዱሳን እየሰራለት ስለሆነ!)
በመልካም ገጽታ ግንባታ (የተዋስኳት ከኢቲቪ ነው።) ከመንግስት ባልተናነሰ የሃገር ሃብት የሆኑ ቅዱሳት መካናትን ጠብቆ በማቆዬት የአንበሳውን ድርሻ ማኅበረ ቅዱሳን አይወስድም?
የእናት ጡት ነካሽ ፖለቲከኛ ሁላ ዛሬ ማኅበሩን አፍርሰው የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያንን የተኩላ መፈንጫ ለማድረግ ከላይ ታች ማለቱን ተያይዘውታል፤ ቤተክህነቱ ውስጥ በተሰገሰጉ “አማኝ መሳይ” ካድሬዎች በኩል።
በጣም የሚገርመኝ ነገር ቢኖር በቁም ሳሉ ሊያፈርሷት የታተሩ ሁሉ በኋላ ግብአተ መሬታቸው እንደ ሥላሴ ባሉ ታላላቅ ካቴድራልና አድባራት ሲፈጸም “እገሌ ታላቅ ሰው ነበሩ። እትት እትት” ተብሎላቸው ይቀበራሉ። የሚቀብሯትን የምትቀብር ቤተክርስቲያን!
ማኅበረ ቅዱሳንን መቅበር ማሰብ ከብርቱውና ኃያሉ አምላክ ጋር መታገል ነው፤ እግዚአብሔር ወድዶና ፈቅዶ የመሰረተው ማኅበር ነውና።


Deje Selam is a venue of news, views and opinions about or related to the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church. [email protected]

 
·ዕለቱ አርብ ነው!
ኢየሱስ ይሰቀል!
ይሰቀል ኢየሱስ!
በርባን ግን ይፈታ!
2 ሺህ ዘመን
ይኸው ትጮሃለች
ዓለም አፍ አውጥታ።

በቀያፋ ምክር 
በካህናት አድማ
በጲላጦስ ስልጣን 
በግፈኞች ጡጫ
ዛሬም ይወገራል 
ጌታ ይሰቀላል።
እውነት ነው!
በድምጽ ብልጫና
በቲፎዞ መድረክ
ለምትመራ ዓለም
ሌባውን አንግሶ
ንፁሁን ከመሸጥ
ሌላ አይጠበቅም።
መጋቢት 2006 .ዓም

Deje Selam is a venue of news, views and opinions about or related to the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church. [email protected]

በመኪና እየተዘዋወሩ የአንድነት አባላትና ደጋፊዎች የደሴን ሕዝብ ሲቀሰቅሱ ዉለዋል። ከደሴ 12 ኪሎሚዕት ርቃ በትምገኘዋ የኩታበር ከተማ ተመሳሳይ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የነበሩ ዜጎችን ፖሊሲ አስቆሞ ለማሰር ሞክሮ የነበረ ሲሆን በአካባቢው የነበረ ሕዝቡ ፖሊስን ከቦ « አታስሯቸዉም» ምንም አይነት ችግር ሳይፈጠር ፖሊሶች ገለል እንዳሉ ከደሴ የደረሰን መረጃ ይጥቁማል። የአንድነት አመራሮች ወደ ደሴ ነገ ጠዋት ያመራሉ :: የአንድነት ከፍተኛ […]

በአዲስ አበባ፣ በዛሬው ቀን በተደረገው ቅስቀሳ ከአምሳ ሶስት በላይ አባላትና ደጋፊዎች በሺሆች የሚቆጠሩ በራሪ ወረቀቶችን ሲያድሉ ዉለዋል። ከሃምሳ ሶስቱ ወጣቶች ስድስቱ ታስረዋል። እስረኞችን ለማስፈታት ወደ ፖሊስ ጣቢያዎቹ የሄዱት የአንድነት የአመራር አባላት፣ ለምን እስረኞች እንደታሰሩ የፖሊስ አዛዦችን ሲጠይቁ « ሰልፉ የተፈቀደ ሰልፍ ስላልሆነ ፣ ነገሩን እስክናጣራ ነው እንጂ አላሰርናቸው» የሚል ምላሽ ተሰጧቸዋል። «ለሰልፍ ፍቃድ አይጠየቅም። ማሳወቅ […]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብት ጉዳይ ሪፖርት አቅራቢ ፤ በኤርትራ ሳይቋረጥ የቀጠለው የሰብአዊ መብት ጥሰት በተለይም በብሔራዊ የውትድርና አገልግሎት ረገድ የሚታየው እጅግ የሚያሳስብ ነው ሲሉ ድርጅቱ ሁኔታውን እንዲከታተሉ ያሠማራቸው ወ/ት ሼይላ

«ዴሞክራሲ የለም! ሰልፍ ማድረግ አይቻልም! አርፋችሁ ተቀመጡ ! » የሚሉን ከሆነ ይንገሩን ። የአገሪቷ ሕግ የሚለው ግልጽ ነው። ዜጎች ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ሙሉ መብት አላቸው። አስተዳደሩ በይፋ ሕግ ወጥ ተግባር ነው እየፈጸመ ያለው። ሕጉ እንዲህ ነው የሚለው ፡ “ሰላማዊ ሰልፉ ወይም ህዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባው በሌላ ጊዜ ወይም በሌላ ስፍራ ቢደረግ ይሻላል የሚል አስተያየት ካለውም ምክንያቱን […]

«ዩክሬን ለወደፊቱ የትልቅ ገበያ ትስፋ አላት።»ተስፋዉ በርግጥ አማላይ ነዉ። የዩክሬን እዉነታ ከሚባለዉ መቃረኑ እንጂ ቀቢፀ-ተስፋዉ። የዩክሬን ሕዝብ የነብስ ወከፍ ገቢ የሞንጎሊያን እንኳን አያክልም። 3800 ዶላር። ኢንዱስትሪዎችዋ-አሮጌ ናቸዉ። ብልጣብልጥ፤ አታላይ፤አጭርበርባሪ ነጋዴ ፤ደላላ፤ ባለሥልጣናት ከብረዉባታል።

ኬንያ በተጠርጣሪ አሸባሪዎች ላይ ዘመቻ ከፍታለች ። ፖሊስ ከዚህ ሳምንት መጀመሪያ አንስቶ በአሸባሪነት የተጠረጠሩ ግለሰቦችን በቤት ለቤት አሰሳ እያደነ በማሰር ላይ ነው። እስከ ትናንት ድረስ ከአንድ ሺህ የሚበልጡ ሰዎች መታሰራቸው ተገልጿል።

በደቡብ ኢትዮጵያ በምትገኘው የቡታጂራ ከተማ የሚገኘው ሀኪም ቤት ከአውሮጳ ህብረት በተገኘ 40 ሚልዮን ዩሮ ርዳታ የእናቶችን እና የሕፃናትን ሞት ለመቀነስ የሚያስችል ፕሮዤ ጀምሮ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል። የተመ የሕፃናት መርጃ

4ኛው የአፍሪቃ መንግሥታት እና የአውሮጳ ህብረት ጉባዔ ትናንት ብራስልስ፣ ቤልጅየም በተከፈተበት ወቅት፣ ስለ ኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ይዞታ እና ስለ ፕሬስ ነፃነት የተመለከተ ሴሚናር በዚችው ከተማ ተካሂዶዋል። ሴሚናሩን የጠሩት እና ያዘጋጁት

የዓረብኛ ሥነ-ፅሁፍ በኢትዮጵያ በተሰኝባቀረብነዉ ዝግጅት ላይ በኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ቋሚ ባልደረባ አቶ አህመድ ዘካርያ በኢትዮጵያ የተገኙት የዓረብኛ ሥነ-ፅሁፎች በዓረብኛ ፊደላት ይቀመጡ እንጂ ቋንቋዉ አገርኛ እንደሆነ በዝርዝር ገልፀዉልናል።