‹‹[ቅዱስ] ሲኖዶሱ አሁን ያለችውን ቤተ ክርስቲያን በብቃት የሚመራበት ደረጃ ላይ ነው ወይ? ለውጡ መጀመር ያለበት ከራሱ ከ[ቅዱስ] ሲኖዶሱ ነው፡፡›› ‹‹ወደፊት የሚመጡ ጳጳሳት ይኖራሉ፡፡ የጳጳሳቱ አመራረጥ የሕዝብን ይኹንታ የሚያገኝ ነው[ን] የሚለው ገና የሚታይ ነው፡፡›› ‹‹ዕርቀ ሰላሙን እኛ ቀድመን ብናመጣው ጥሩ ነው፡፡›› ሰባኬ ወንጌል እና ጸሐፊ ዲ/ን ዳንኤል ክብረት ከዕንቊ መጽሔት ጋራ ያደረገው የቃለ ምልልስ ቆይታ ሁለተኛ …

ዛሬ፣ መስከረም ፲፰ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም ለንባብ የበቃው አዲስ ጉዳይ ሳምንታዊ መጽሔት የ፳፻፭ ዓ.ም የዓመቱ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች፣ የዓመቱ ምርጦች እየተባለ በሌሎች ኅትመቶች ከወጡት ተቋማትና ግለሰቦች በተለየ አኳኋን በ፳፻፭ ዓ.ም ‹‹ተጽዕኖ አልባ መሪዎች ነበሩ›› ያላቸውን አምስት ግለሰቦችና አንድ ተቋም ለይቷል፡፡ መጽሔቱ ለልየታው የተጠቀመው÷ ግለሰቦቹና ተቋሙ ካለባቸው ሰፊ ሓላፊነት፣ ከተቀመጡበት ወሳኝ ቦታና ከሚጠበቅባቸው ውጤት በተቃራኒ በተገመገሙ ጥቅልና …

(አዲስ አድማስ፤ ቅጽ 13 ቁጥር 715፤ ቅዳሜ፣ መስከረም ፲፰ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም) ዓለማየሁ አንበሴ በአቃቂ ቃሊቲ ገላን ጉራ ፈለገ ግዮን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን፣ ባለፈው ነሐሴ ወር መጨረሻ ከሰማይ ወረደ ስለተባለው መስቀል፣ ቅዱስ ሲኖዶስ መርምሮ ውሳኔ* እንደሚያስተላልፍ በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የፓትርያርኩ ረዳትና የጅማ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ አስታወቁ፤ ሕዝቡ የቅ/ሲኖዶሱን ውሳኔ በትዕግሥት እንዲጠባበቅ …

‹‹የሰባት ወይራ ሆቴልን ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ እንዳይወስድብን ለመለመን›› በሚል በደብሩ አስተዳደር ያስወሰኑትን ግማሽ ሚልዮን ብር፣ ሢመተ ጵጵስናውን ይቃወማሉ የሚባሉ አባቶችን የማግባባት አቅማቸውን እንደሚያጠናክሩበት ጠቁመዋል፡፡ ከቃለ ዐዋዲው ድንጋጌ በተፃራሪ በሥልጣን ላይ የቆዩትና በአስተዳዳሪው ውሳኔ እስከ 7000 ብር በወር የሚከፈላቸው አብዛኞቹ የደብሩ ሰበካ ጉባኤ አባላት እና የጽ/ቤቱ ሠራተኞች፣ በአስተዳዳሪው የግማሽ ሚልዮን ብር ጥያቄ እንዲስማሙ በ‹ጥቅማቸው› መገደዳቸው ታውቋል፡፡ …

(ካህሳይ ገብረ እግዚአብሔር) የመስቀል በዓል ትውፊት የኢትዮጵያ ሕዝብ ለመስቀል ያለውን የጠለቀ ዕውቀት ያሳያል የመስቀል በዓል አከባበር የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ያልደረሰችበት፣ ወንጌል ያልሰበከችበት የኢትዮጵያ ክፍል እንዳልነበረ አመልካች ነው የመስቀል በዓል አከባበር መንፈሳዊነቱንና ባህላዊ ገጽታውን ሳይለውጥ ለዘመናት የቀጠለበት ምክንያት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የወንጌል ትምህርት በሕዝቡ ዘንድ እንዲሠርጽ ካደረገችው ጥረት ይመነጫል የመስቀል በዓል በኢትዮጵያ የሚከበረው ከየትኛውም …

(ዕንቊ መጽሔት፤ ቅጽ 6 ቁጥር 101፤ መስከረም ፳፻፮ ዓ.ም) መንግሥት የተወሰኑ አክራሪዎች የሚላቸው አካላት የሙስሊሙን ማኅበረሰብ እያወናበዱት ነው ሲል መግለጹ የሚታወቅ ነው፡፡ ከዚሁ ጉዳይ ጋራ በተያያዘ የተወሰኑ ሙስሊሞችም በቁጥጥር ሥር ውለዋል፡፡ ይኸው አጀንዳ አሁንም የሙስሊሙን ማኅበረሰብ በሚያረካና ዘላቂ አገራዊ ሰላም በሚያመጣ ኹኔታ መቋጫ አላገኘም፡፡ ይልቁንም መንግሥት ‹‹ሚዛን ለመጠበቅ›› በሚመስል መልኩ ‹‹በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን …

የሀ/ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ወደ አውስትራልያ ያመራሉ የሀ/ስብከቱ ሰንበት ት/ቤቶች ማ/ክፍል ሓላፊ የታገደውን አመራር ለሁከት እየገፋፋ ነው በአመራሩ የቃለ ዐዋዲ ጥሰትና ሃይማኖታዊ ሕጸጽ ምክንያት የታሸገው የድሬዳዋ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ሰንበት ት/ቤት ተከፍቶ አገልግሎቱን በጊዜያዊ ሥራ አመራር ቀጠለ፡፡ ሰንበት ት/ቤቱ እንዲከፈት የተወሰነው የካቴድራሉ ሰበካ ጉባኤ ከነሐሴ ፳፯ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም ባካሄደው ስብሰባ ሲኾን ይህም …

የአካዳሚክ እና አስተዳደር ዲኖችን መድበዋል ቋሚ ሲኖዶሱን ያጠያየቀው ምደባ አጽድቆቱን ይጠብቃል ዘላለም ረድኤት ባቀረበው የመልቀቂያ ደብዳቤ ይሰናበታል መምህራኑ ደመወዛቸው ታግዶ ያለውኃና መብራት ሁለት ሳምንት አስቆጥረው ነበር ቋሚ ቅ/ሲኖዶስ በዛሬው ዕለት ባካሄደው ሳምንታዊ መደበኛ ስብሰባው÷ ከሥልጣናቸው ተገልለው እንዲቆዩ የተወሰነባቸው ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ፣ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ መምህራንና ሠራተኞችን ከኮሌጁ መኖርያ ቤቶች የማስለቀቅ፣ ደመወዝ የማገድ፣ አዲስ ቅጥር …

አስተዳደሩና ማኅበረሰቡ የመረጣቸው አስተዳዳሪ ምደባ እንዲወሰንለት ጠይቋል ሊቀ ጳጳሱ ለምደባ ያቀረቧቸው ስድስት ሠራተኞች ማንነት እያጠያየቀ ነው ቋሚ ሲኖዶስ በአህጉረ ስብከቱ አስተዳደር ላይ የቀረቡ አቤቱታዎችን እየመረመረ ነው ለደቡብ አፍሪካ የቅዱስ ያሬድ ገዳም ከአ/አ አድባራት የተሰበሰበውና በሊቀ ጳጳሱ የግል አካውንት ተልኮ የነበረው አራት ሚልዮን ብር ጉዳይ ልዩ ትኩረት እንደሚሻ ተጠቁሟል ላለፉት ሦስት ወራት ያለአስተዳዳሪ የቆየው በምድረ ሱዳን …

መነኰሳቱ ገዳሙን ለቀው እንዲወጡ ዛቻና ማስፈራሪያ እየተደረገባቸው ነው አስተዳደሩ ለመነኰሳቱ ተደጋጋሚ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት አልፈቀደም ‹‹ከዚህ ቦታ ባትመጡ ይሻል ነበር፤ ብትውሉ አታድሩም!›› /ጥቃት ፈጻሚዎቹ/ በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀ/ስብከት ወንጪ ወረዳ ሐሮ ወንጪ ቀበሌ በሚገኘው የሐሮ ወንጪ መልአከ ሰላም ቅዱስ ገብርኤል አንድነት ገዳም ላይ የቦምብ ጥቃት መፈጸሙ ተገለጸ፡፡ ጥቃቱ የተፈጸመው ጳጉሜ ፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም ምሽት …

ከሰማይ ወረደ ተብሎ በጳጳሳት የተጎበኘው መስቀል ለሕዝብ ይታያል (አዲስ አድማስ፤ ቅጽ 13 ቁጥር 713፤ ቅዳሜ መስከረም ፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም) ዓለማየሁ አንበሴ በአቃቂ ቃሊቲ በቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ግቢ ውስጥ፣ ነሐሴ ፳፫ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም በቀስተ ደመና፣ በመብረቅ እና በነጎድጓድ ታጅቦ ከሰማይ እንደወረደ የተነገረው መስቀል፣ በጳጳሳት የተጎበኘ ሲኾን፣ ከሁለት ሳምንት በኋላ ለሕዝብ እይታ እንደሚቀርብ ተገለጸ፡፡ …

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤ አሜን በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፣ ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትኖሩ፣ የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችኹ፣ በሕመም ምክንያት በየሆስፒታሉ ያላችኹ፤ እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ኾናችኁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት፤ የዘመናት ፈጣሪ እግዚአብሔር አምላካችን እንኳን ከ፳፻፭ ዓ.ም ዘመነ ማቴዎስ ወደ ፳፻፮ ዓ.ም ዘመነ ማርቆስ በሰላም አደረሳችኹ!!! ‹‹ወሠርዐ ዕድሜኹ …

የአክራሪነት ውንጀላው በ‹‹አገር አቀፍ የሰላም ዕሴት ማጎልበቻ ጉባኤ›› ወቅት ማኅበሩንና አገልግሎቱን ከተቀበረ ፈንጂ ጋራ ያመሳሰለውና በአቶ ስብሓት ነጋ አጽንዖት የተሰጠው የአባ ዮናስ ጥቆማ ነው፤ የቅ/ሲኖዶስ ጽ/ቤት ለቋሚ ሲኖዶስ በአጀንዳነት እንደሚያቀርበው ተመልክቷል፡፡ ከዋልድባ ገዳም፣ ከዕርቀ ሰላም እና ከ፮ኛው ፓትርያርክ ምርጫ ጋራ በተያያዘ በግል ፕሬሶችና ኤሌክትሮኒክስ ሚዲያዎች ላይ የተሳተፉ የማኅበሩ አባላትና አገልጋዮች ናቸው የተባሉ ግለሰቦች ‹‹ጽንፈኛ የፖሊቲካ ኀይሎች …

ስብሓት የንግግራቸው መነሻ ያደረጓቸውና ወጣት ሲሉ የጠሯቸው መነኩሴ ማን ናቸው?   ‹‹የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ጉዳይ የሚያስተኛ አይደለም›› /አቶ ስብሓት ነጋ/ (ኢትዮ-ምኅዳር ቅጽ 01 ቁጥር 34፤ ረቡዕ ነሐሴ ፳፱ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም.) የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጋራ በመተባበር በአዲስ አበባ በአፍሪካ ኅብረት አዳራሽ ከነሐሴ ፳፩ – ፳፪ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. ‹‹የሃይማኖቶች በሰላም …

አመራሩ በታገደበት ቆይቶ የኑፋቄ ውዝግቡ በገለልተኛ ወገን እንዲጣራ ጠይቋል አመራሩ ኑፋቄው በአግባቡ እንዳይጣራ የተለያዩ ተጽዕኖዎችን ሲፈጥር ቆይቷል ብዙኀኑ የሀ/ስብከቱ አስተዳደር ጉባኤ አባላት በውሳኔው ቃለ ጉባኤ ላይ አልፈረሙም ‹‹ከዚህ በኋላ ለሚፈጠረው ችግር ሓላፊነቱን የሀ/ስብከቱ ጽ/ቤት ይወስዳል፡፡›› /ሰበካ ጉባኤው/   በፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ኑፋቄ ሕዋስ በመጠለፉና በቃለ ዐዋዲው ድንጋጌ መሠረት ለሰበካ ጉባኤው መመሪያ ባለመገዛቱ የመዘጋት ርምጃ የተወሰደበት የድሬዳዋ ደብረ …

ለወራት በአ/አ የተቀመጡት ሊቀ ጳጳሱ ትላንት ምሽት ወደ ደ/አፍሪካ ተጉዘዋል በሊቀ ጳጳሱ አስተዳደር የተማረሩና አስቸኳይ መፍትሔ የሚሹ አቤቱታዎች ለውጭ ግንኙነት መምሪያውና ለፓትርያሪኩ ልዩ ጽ/ቤት እየጎረፉ ነው ከዚህ በታች የምናቀርበውና ‹‹የአቡነ ያዕቆብ ሲሞናዊነት[ስምዖናዊነት] ሲገለጥ›› በሚል ርእስ የተጠናቀረው መልእክት የደረሰን በኬንያ – ናይሮቢ ከሚገኙ ምእመናን ነው፡፡ መልእክቱ÷ የመላው አፍሪቃ አህጉረ ስብከትን የተመለከተ ዘገባ በጡመራ መድረኩ ለንባብ ከበቃበት […]

አስተዳደሩን ይሰበስባሉ፤ ሠራተኛ ያባርራሉ፤ ቢሮ ያሽጋሉ፤ ደመወዝ ይከለክላሉ መምህራኑን ለዓመታት ከኖሩባቸው የኮሌጁ ቤቶች ለቀው እንዲወጡ አዝዘዋል እስከ ነሐሴ ፴ መኖርያ ቤቶቹን የማይለቁ መምህራን ደመወዛቸው ይታገዳል ‹‹ለጥያቄዎቻችን ሥር ነቀል ምላሽ አላገኘንም፤ ይብሱኑ በቀልና ተደጋጋሚ በደል እየተፈጸመብን ነው›› ያሉት መምህራኑ ለቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት አቤት ብለዋል በጊዜያዊ ሓላፊነት የተመደቡት ንቡረ እድ ኤልያስ ኣብርሃ ድምፃቸውን አጥፍተዋል   ቅዱስ ሲኖዶስ …

ችግሩ የውጭ ግንኙነት መምሪያውን አፋጣኝ ትኩረት ይሻል የመላው አፍሪቃ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በኾኑት ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ አስተዳደር ላይ በወጣው ዘገባ ዙርያ ከሚደርሱን አስተያየቶችና ትችቶች የሚበዙት ከደቡብ አፍሪቃ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያን ምእመናንና አገልጋዮች የሚላኩልን ናቸው፡፡ ብፁዕነታቸው በኤጲስ ቆጶስነት ከተሾሙበት ፲፱፻፺፯ ዓ.ም መጨረሻ ጀምሮ ለስምንት ዓመታት የቆዩበት ደቡብ አፍሪቃ መንበረ ሊቀ ጵጵስናው እና የአህጉረ …

የርምጃውን ጅምር የወሰደው የአ/አ መካነ ሰማዕት ቅ/ቂርቆስ ደብር ሰበካ ጉባኤ ነው፡፡ የደብሩ የስብከተ ወንጌል ክፍል ጥብቅ ክትትል እንዲያደርግ ማሳሰቢያ ተሰጥቶታል፡፡ ለሰ/ጉባኤው የእግድ ውሳኔ ዝርዝር መረጃ የሰጠው የደብሩ ሰንበት ት/ቤት ነው፡፡ ሰንበት ት/ቤቱ ከአምስት ዓመት በፊት ከመናፍቃን ኅትመቶች ገልብጦ ባዘጋጀው በራሪ ወረቀት ምክንያት ከማንኛውም አገልግሎት አግዶ ክትትልና ማጣራት ሲያደርግበት ቆይቷል፡፡ ዲ/ን ኀይሉ በነገሌ ቦረና የሀ/ስብከቱ ስብከተ …

በጥቅመኝነት ላይ የተመሠረተ የአገልጋዮች ምደባና ስምሪት፣ ለምእመናን ወቅታዊ ጥያቄ አፋጣኝ ምላሽ አለመስጠት፣ በዕቅበተ እምነት ሊቀ ጳጳሱ ይታይባቸዋል የሚባለው ቸልተኝነት እና የጎጠኝነት ዝንባሌ በዋናነት ተጠቅሰዋል፡፡ *       *      * ሊቀ ጳጳሱ ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ በቅርቡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መሥራች አባል ለኾነችበት ለመላው አፍሪቃ አብያተ ክርስቲያናት ጉባኤ በምክትል ፕሬዝዳንትነት መመረጣቸው ለውጭ ግንኙነታችን መልካም ዜና ነው፡፡ ከጉባኤው …

በዓሉን የአካባቢው ተጨማሪ የቱሪስት መስሕብ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ ነው መንፈሳዊ ይዘቱ እንዲጠፋ የሚሹ ግለሰቦች በበዓል ኮሚቴ መካተታቸው ቅር አሰኝቷል በበዓሉ አጋጣሚ ለቅ/ላሊበላ ደብር አስተዳደራዊ ችግር ትኩረት እንዲሰጥ ተጠይቋል የጾመ ፍልሰታ ለማርያምን ፍጻሜ ተከትሎ የሚከበረው የአሸንድዬ በዓል ከነገ ጀምሮ የዓለም አቀፍ ብርቅዬ ቅርስ ማእከልና የውብ ባህል መድረክ በኾነው ላሊበላ ከተማ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ይከበራል፡፡ የቅዱስ ላሊበላ …

ለሐውልቱ ሥራ የተዋዋለው ተቋራጭ አድራሻውን አጥፍቶ ጀርመን ከረመ በውሉ መሠረት ከነሐስ የሚሠራውን ሐውልት በ186 ቀን ሠርቶ ማስረከብ ነበረበት ለጥቅምት ፲፪ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም ‹‹ዝክረ አበው›› እንዲያደርስ ታዝዟል ነሐሴ ፲ ቀን ፳፻፬ ዓ.ም ሌሊት ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ የተለዩት የአምስተኛው ፓትርያሪክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ኅልፈት አንደኛ ዓመት መታሰቢያ ሥነ ሥርዐት በዛሬው ዕለት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት …

የአንደኛ ዓመት መታሰቢያ ሥነ ሥርዐት ነገ ይካሄዳል የቤተ ሰዎቻቸው የንብረት ይገባናል ጥያቄ ውሳኔ አላገኘም በ1.5 ሚልዮን ብር ጨረታ የተሰጠው የመቃብር ሐውልታቸው አልተሠራም ለ፳ኛ ዓመት በዓለ ሢመታቸው “የካንሰር፣ ቲቢና ኤድስ የሕክምናና ማገገሚያ ማእከል” ግንባታን እንደ ስጦታ ያበረከተው ‹‹ራእይ ለትውልድ›› እና በዓል አድማቂዎቹ ‹‹ዉሉደ ጳውሎስ›› የት ናቸው? አምስተኛው ፓትርያሪክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ አንደኛ ዓመት መታሰቢያ ነገ፣ …

በምደባ ቅር የተሰኙ ሓላፊዎች በየሆቴሉና ሬስቶራንቱ የዐመፅ ምክክር ይዘዋል ‹‹የቋሚ ሲኖዶሱ ምደባ በአተገባበር በደላሎች ተጠልፏል›› የሚል ቅሬታ አላቸው የረዳት ሊቀ ጳጳሱና ጽ/ቤታቸው ድርሻ የቋሚ ሲኖዶሱን ምደባ ማስፈጸም ብቻ ነው በዘላቂው የሀ/ስብከቱ መዋቅር ስፍራ የሚኖራቸው በጊዜያዊ ምደባቸው ብቃት ያሳዩ ሓላፊዎችና ሠራተኞች መኾናቸው ተገልጧል የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ለአደረጃጀትና አሠራር ለውጥ በሚያደርገው ቅድመ ዝግጅት ለዘረጋው የሽግግር ጊዜ መዋቅር …

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን v  በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ v  ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትኖሩ v  የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችኹ v  በሕማም ምክንያት በየሆስፒታሉ ያላችኹ v  የሕግ ታራሚዎች ኾናችኁ በማረሚያ ቤት የምትገኙ     ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት፤ የተወደዳችኹ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች፣ የቅድስት ድንግል ማርያም ወዳጆች ምእመናንና ምእመናት ልጆቻችን÷ እግዚአብሔር አምላክ …

መዋቅሩና ምደባው ለመሠረታዊው የቤተ ክርስቲያናችን ተልእኮ ትኩረት የተሰጠበት፣ ድጋፍ ሰጪው በባለሞያ ብቻ የሚመራበት፣ ሠሪውና ተቆጣጣሪው የተለየበት ነው የቁጥጥር አገልግሎቱ ሥልጣን ከሀ/ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ በላይ ኾኖ ተጠሪነቱ ለመንበረ ጵጵስናው ሀ/ስብከት ጠቅላላ መንፈሳዊ ጉባኤ ኾኗል፤ የጸሐፊ ሥራ መደብ ቀርቷል ራሳቸውን ከለውጡ ጋራ የሚያራምዱ ሓላፊዎችና ሠራተኞች በሥራ አፈጻጸማቸው የሚመዘኑበት፣ በዕድገትና ሥልጠና የሚበረታቱበትና የሚታገዙበት ኹኔታ ተመቻችቷል በተለያዩ ዓላማዎች …

የኮሌጁ ቦርድና የበላይ ሓላፊ መመስገን የምሩቃኑን ጉርምርምታን አሰምቷል የአስተዳደሩን ሙሰኝነት በቅኔው የነቀፈው ምሩቅ ፓትርያሪኩ የጀመሩትን ርምጃ ከዳር እንዲያደርሱ ጠይቋል ‹‹ጌታ ሆይ፣ ለቤተ ክርስቲያን ቅን መሪ የምትሰጥ መቼ ይኾን?›› /ምሩቃኑ ካሰፈሯቸው ጥቅሶች አንዱ/ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ በቀኑ መደበኛ እና በማታው ተከታታይ መርሐ ግብር ያስተማራቸውን 194 ደቀ መዛሙርት ትላንት ቅዳሜ፣ ሐምሌ ፳፯ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም ብፁዕ ወቅዱስ …

ዐሥራ አንዱ የተነሡት በዝውውር ነው፤ ቀሪዎቹ ሦስቱ ከአስተዳዳር ሥራ ውጭ ተደርገዋል ከአስተዳደር ሥራ ውጭ ከተደረጉት ውስጥ የደ/ጽጌ ቅ/ዑራኤል እና የደ/ሰላም ቅ/እስጢፋኖስ አስተዳዳሪዎች ይገኙበታል የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ጽ/ቤት ሙስናና ብልሹ አሠራር የገነገነባቸውን፣ የካህናትና ምእመናን አቤቱታ የበረታባቸውን 14 አድባራት አስተዳዳሪዎችን የማዘዋወር፣ ከአስተዳዳሪነት ሓላፊነት የማራቅ እና በጡረታ የማግለል ውሳኔ ማሳለፉ ተገለጸ፡፡ የአስተዳዳሪዎች ዝውውር የተካሄደባቸው አድባራት፡- የገነተ ጽጌ ቅዱስ …

‹‹በድል ኮረብታ ላይ ወጥታችኋል፤ መምህራን ኮርተናል›› /ሊቀ ማእምራን ደጉ ዓለም ካሣ/ ‹‹የተቃወምነው ሰውን ሳይኾን ሥርዐቱን ነው›› /የደቀ መዛሙርቱ መማክርት አመራር/ የደቀ መዛሙርቱ ምረቃ ሐምሌ ፳፯ ቀን ይካሄዳል በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የሐዲስ ኪዳን መምህር በኾኑት ሊቀ ማእምራን ደጉ ዓለም ካሣ አገላለጽ የኮሌጁ ደቀ መዛሙርት ያሣመሯት የዛሬ ሐምሌ ፳፭ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም ምሽት ለሚቀጥለው ትውልድ የተሰጠች …

በአሰበ ተፈሪ በዓላማ የሚመስሏቸውንና በጥቅም የገዟቸውን የሀ/ስብከቱን ሥራ አስኪያጅና ጸሐፊ በመያዝ የደ/ጽዮን ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ት/ቤት እና በወረዳው የማኅበረ ቅዱሳን ጽ/ቤቶች እንዲታሸጉ አድርገዋል፡፡ ራሱን ‹‹ማኅበረ ናታኒም›› እያለ የሚጠራው በቅ/ሲኖዶስ የተወገዘው ሃይማኖተ አበው ርዝራዥ፣ የደ/ጽዮን ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤን ምርጫ በአባላቱ ብቻ ባቋቋመው አስመራጭ ኮሚቴ በኩል ለመቆጣጠርና አባላቱን በማስመረጥ በደብሩ ተጽዕኖውን ለማጠናከር …

ከ15 – 20 ዓመት በሚያስቀጡ ቅርስን የማፍረስ፣ ከባድ የእምነት ማጉደል እና ሐሰተኛ ሰነድ የመፍጠር የወንጀል ተግባራት ይፈለጋሉ ‹‹ተራማጁ እና ልማታዊው›› በሚል የሚሞካሹት ቆሞሱ በመንበረ ጵጵስና ብፁዕ አቡነ ቄርሎስን የመተካት ምኞት ነበራቸው፤ በቀድሞው ዘመነ ፕትርክና ሁለት ጊዜ በሲሞናዊ መንገድ ለኤጲስ ቆጶስነት ለመታጨት ሞክረዋል፤ በውጭ ጉዟቸው በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ የሚመራውን ሲኖዶስ ማኩረፊያ አድርገውት ይኾን? ሙሰኝነታቸውንና የአስተዳደር …

የደብሩ ምእመናን በፍ/ቤቱ ውሳኔ ግራ ተጋብተዋል ዋና ጸሐፊው ከሥራቸው ታግደዋል፤ በምትካቸው ሌላ እንዲመደብ ተጠይቋል በሰነድ ማጭበርበር እና ሰነድ ማሸሽ በተፈጸመ ከፍተኛ ሙስና ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር የዋሉት የደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን ዋና ጸሐፊ ዲያቆን ምሩፅ ትኵዕ በኀምሳ ሺሕ ብር ዋስትና መለቀቃቸው ተገለጸ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ቦሌ ምድብ ችሎት የደብሩ ዋና …

በተጭበረበረ ውል ደብሩን ከ3 ሚልዮን ብር በላይ በማሳጣትና ሰነድ በማሸሽ ይጠየቃሉ ከጥቂት የሙዳይ ምጽዋት ገቢ ምርመራ ብቻ ከ2 ሚልዮን ብር በላይ ጉድለት ተገኝቷል የአብዛኛዎቹ የደብሩ ሕንጻ ሱቆች የኪራይ ውል በትክክለኛ ሰነድ የተፈጸመ አይደለም ለማተሚያ ቤት አገልግሎት በተከራየው ክፍል በጠቅላይ ቤተ ክህነቱ የማይታወቅ ሞዴላሞዴል እንደሚታተምበት ተጠቁሟል የፕሮቴስታንት ቤተ ጸሎት እንደሚያዘወትሩ የሚያሳዩ መረጃዎች ወጥተዋል   በአዲስ አበባ …

ሓላፊዎቹን የተመለከቱ የቅ/ሲኖዶሱ ውሳኔዎች በደብዳቤ ወጪ አልተደረጉም ንቡረ እዱ÷ አቡነ ጢሞቴዎስ ‹‹በሚሰጧቸው መመሪያ›› እንደሚሠሩ ተናግረዋል ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው መምህራንና ሠራተኞች የሥራ ዋስትና አደጋ ላይ ነው ዋነኛ ጥያቄያችን አልተመለሰም ያሉ መምህራን በተቃውሟችን እንቀጥላለን እያሉ ነው ነገ ፈተና የሚጀምሩት የዘንድሮ ምሩቃን ፈተናቸውን በጨረሱ ማግሥት ይመረቃሉ! ‹‹የተያዘው ጨዋታ ነው፤ መፍትሔ እንደሚሰጡን ከተናገሩ በኋላ እንደ ልጅ ሊያታልሉን እየሞከሩ ነው›› /ደቀ …

አቡነ ጢሞቴዎስ ጉዳያቸው ከሚታይበት ስብሰባ ላለመውጣት ሲለመኑ ውለዋል ኣቦይ ስብሐት አቡነ ጢሞቴዎስን ለማግባባት በቅ/ሲኖዶሱ ስብሰባ ላይ ተገኝተዋል ፓትርያሪኩ ስለ አቡነ ጢሞቴዎስ ብዙ ከመናገር ተጠንቅቀዋል፤ ተቆጥበዋል ደቀ መዛሙርቱና መምህራኑ ደስታቸውን በቅኔ፣ ወረብና መዝሙር እየገለጹ ነው የንቡረ እድ ኤልያስ ምደባ ግዙፍ ከሚያስነሣው ግዙፍ ጥያቄ ጋራ የምረቃው ቅድመ ዝግጅት ይቀጥላል. . .

መ/ር ፍሥሐ ጽዮን ደመወዝ በማስተማር ሥራ ብቻ ይወሰናሉ የአቡነ ጢሞቴዎስ ቀጣይነት እየተጤነ ነው አቡነ ጢሞቴዎስን የሚተካ ዋና ዲን እስኪሾም ኮሌጁ በጊዜያዊ ሓላፊ ሊመራ ይችላል ጥቅመኛው፣ ሀኬተኛው (ክፋተኛው) እና መናፍቁ ዘላለም ረድኤት በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ከያዘው የቀን መደበኛ መርሐ ግብር አስተባባሪነት እንዲወገድ ቋሚ ሲኖዶስ ከስምምነት ላይ ደረሰ፡፡ ቋሚ ሲኖዶሱ ከዚህ ዐቢይ የስምምነት ውሳኔ ላይ የደረሰው …

መ/ር ፍሥሐ ጽዮን ደመወዝ በማስተማር ሥራ ብቻ ይወሰናሉ የአቡነ ጢሞቴዎስ ቀጣይነት እየተጤነ ነው የቅ/ሲኖዶሱ አስቸኳይ ስብሰባ ነገ እንደሚካሄድ ይጠበቃል ጥቅመኛው፣ ሐኬተኛው (ክፋተኛው) እና መናፍቁ ዘላለም ረድኤት በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ከያዘው የቀን መደበኛ መርሐ ግብር አስተባባሪነት እንዲወገድ ቋሚ ሲኖዶስ ከስምምነት ላይ ደረሰ፡፡ ቋሚ ሲኖዶሱ ከዚህ ዐቢይ የስምምነት ውሳኔ ላይ የደረሰው በኮሌጁ አስተዳደርና በደቀ መዛሙርቱ መካከል …

የምክክር ጉባኤውን ተከትሎ በሀ/ስብከቱ እና በክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ጽ/ቤቶች የሓላፊዎችና ሠራተኞች ምደባ ይካሄዳል የክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ጽ/ቤቶችን በቢሮ ዕቃዎች ለማደራጀት የ1.6 ሚልዮን ብር በጀት ተመድቧል በ1.6 ሚልዮን ብሩ ጽ/ቤቶቹን ለማደራጀት የተቋቋመው የዕቃ ግዥ ኮሚቴ÷ ረዳት ሊቀ ጳጳሱን በሙስና ቀለበት ውስጥ በማስገባት የለውጥ ሂደቱን ለመቆጣጠር በሚያልሙ የለየላቸው ሙሰኞች የሚንቀሳቀስ መኾኑ ሀ/ስብከቱን ለከፋ ትችት እየዳረገው …

ደቀ መዛሙርቱ ጽ/ቤቱ ከመንግሥት በመነጋገር የደኅንነት ጥበቃ እንዲደረግላቸው ጠይቀዋል የልዩ ጽ/ቤቱን ለቃችኹ ውጡ ትእዛዝ ‹‹ሕግን የጣሰና ለከሳሽ ያደላ›› በሚል ተቃውመውታል የቅ/ሲኖዶሱ ዋና ጸሐፊ እና የጠ/ቤ/ክህነቱ ዋ/ሥራ አስኪያጅ ደቀ መዛሙርቱን እያረጋጉ ነው የፓትርያሪኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስ አቡነ እስጢፋኖስ ከደቀ መዛሙርቱ ጎን ቆመዋል ተብሏል ኹኔታው ያሳሰባቸው የማታ ተማሪዎች ተወካዮች ከቅ/ሲኖዶስ ጽ/ቤት ጋራ ተወያይተዋል የኮሌጁ መምህራን አቡነ ጢሞቴዎስ …

የኮሌጁ የቀን መርሐ ግብር እስከ መስከረም አጋማሽ ፳፻፮ ዓ.ም ድረስ እንዲቋረጥ ተወስኗል ደቀ መዛሙርቱ በቀጣይ ርምጃዎቻቸው ላይ እየመከሩ ነው የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ደቀ መዛሙርት ኮሌጁን ‹‹በሰላማዊ መንገድ›› ለቀው እንዲወጡ የፓትርያሪኩ ልዩ ጽ/ቤት በይፋ አዘዘ፡፡ ልዩ ጽ/ቤቱ ዛሬ፣ ሐምሌ ፰ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም ከቀትር በኋላ በኮሌጁ የለጠፈው ማስታወቂያ፣ የኮሌጁ ደቀ መዛሙርት ማስታወቂያው ከወጣበት ከዛሬ ሐምሌ …

በነገው ዕለት በመንበረ ፓትርያሪኩ በሚያካሂዱት ከፍተኛ የተቃውሞ ትዕይንት ምእመኑ ከጎናቸው እንዲሰለፍ ጥሪያቸውን አቅርበዋል አቡነ ጢሞቴዎስ ደቀ መዛሙርቱን በፖሊቲከኝነት መወንጀል ጀምረዋል የተማሪዎች መማክርት የኮሌጁን አስተዳደር በሕግ ለመጠየቅ እየተዘጋጀ ነው ምእመናን ቤተ ክርስቲያን ከመሳለምና ገንዘብ ከመስጠት/ከመመጽወት ባሻገር ስለ ቤተ ክርስቲያናቸው ጉዳይ በመጠየቅ ቀጥተኛ ተሳታፊ መኾን እንደሚገባቸው የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ደቀ መዛሙርት አሳሰቡ፡፡ ደቀ መዛሙርቱ ማሳሰቢያውን ያስተላለፉት፣ …

የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅን መዝጋት ታሪክን ማጥፋት/ማበላሸት ነው! የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ችግራችንን ይመልከት! ልጆቹን የማይጠይቅ አባት አለን? ሙስናንና ኑፋቄን የሚያደቅ ክንድ አለን! የምንማረው በምእመናን ብር ነው፡፡ ሌቦች ሆይ፣ እጃችኹ ይሰብሰብ! ጢሞቴዎስ ሆይ፣ አደራህን ጠብቅ፡፡ (፩ኛጢሞ. ፬÷፳) ችግራችንን የሚሰማንና መፍትሔ የሚሰጠን አባት ዐጣን! የቅ/ሲኖዶሱ አባላት ትኩረት ይስጡን! ሙስናን በቃል ሳይኾን በተግባር እንዋጋ! ተማሪዎች ሙስናን በመዋጋታቸው […]

ክልሉ የፍትሕና ጸጥታ ዘርፍ እንዲሁም የፖሊስ ሓላፊዎች ለሁከት ፈጣሪዎቹ ወግነዋል

ደቀ መዛሙርቱ ለሦስተኛ ተከታታይ ቀን የኮሌጁን የምግብ ቤት አገልግሎት ተከልክለዋል የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ደቀ መዛሙርቱ ወደ ክረምት ዕረፍት ከመሄዳቸው በፊት የማጠቃለያ ፈተና እንዲወስዱና ተመራቂዎቹ እንዲሸኙ ጥረት እያደረገ ነው፤ በፓትርያሪኩ የመወሰን አቅም ላይ ጥርጣሬ የገባቸው የሚኒስቴሩ ሓላፊዎች ልዩ ጽ/ቤቱ ደቀ መዛሙርቱን በኀይል ከኮሌጁ ለማስወጣት ያቀረበውን የድጋፍ ጥያቄ ውድቅ ባደረጉበት አቋማቸው ጸንተዋል ፓትርያሪኩ በሚይዟቸው አቋሞች ረዳት ሊቀ ጳጳሱ …

ኮሌጁ እንዲዘጋ የውሳኔ መነሻ የሰጠው ከአቡነ ጢሞቴዎስ ተጽዕኖ ያልወጣው የኮሌጁ ቦርድ ነው አቤቱታቸውን ለመንግሥት አካላት ያሰሙት ደቀ መዛሙርቱ ‹‹ቅ/ሲኖዶስ እና ምእመናን የከፈቱት ኮሌጁ የሚዘጋው በመቃብራችን ላይ ነው!›› በሚለው አቋማቸው ጸንተዋል፤ በአስተዳደር ሕንጻው ዙሪያ የሚያደርጉትን ቁጥጥር አጠናክረዋል

ፖሊስ የጠቅላይ ቤተ ክህነቱን ዋና ሥራ አስኪያጅ አነጋግሯል በተቃውሞው የተበሳጩት የኮሌጁ ሊቀ ጳጳስ ራሳቸውን ስተው እንደነበር ተጠቁሟል ‹‹አልፈው በመቃብራቸው ላይ መሣቅ እንፈልጋለን›› – የጥላቻው ምሬት ‹‹በተራዘመው መርሐ ግብር ሳቢያ የተጨመረው በጀት ለብክነት እየተዳረገ ነው›› /ደቀ መዛሙርቱ/ ዛሬ ጠዋት ወደ መንበረ ፓትርያሪክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ያመሩት የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ደቀ መዛሙርት በመንበረ ፓትርያሪኩ ቅጽር …

የአጣሪ ኮሚቴው ሪፖርት እስኪፈጸም ድረስ ለፈተና ላለመቀመጥ ወስነዋል የኮሌጁ ቦርድ በአጣሪ ኮሚቴው ሪፖርት ላይ ከቋሚ ሲኖዶሱ ጋራ እየተወያየ ነው ‹‹ቦርዱ ለአቡነ ጢሞቴዎስ ተጽዕኖ ያደረና እርሳቸው የሚሉትን ብቻ የሚሰማ ነው፤ በችግራችን ጠይቆንም ይኹን ሰብስቦን አያውቅም፡፡›› /ደቀ መዛሙርቱ/

ደብሩ በተጭበረበረ የሕንጻ ኪራይ ውል ከ2 ሚልዮን ብር በላይ ገቢ ማጣቱ ተነግሯል በቋሚ ሲኖዶስ አሻሽሎ ባጸደቀው ውስጠ ደንብ አስተዳደራዊ መዋቅሩን እያደራጀ የሚገኘው የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት በደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን ‹‹የፋይናንስ እንቀስቃሴና አሠራር›› ጋራ በተያያዘ በደብሩ ጽ/ቤት ተፈጽሟል የተባለውን ሙስናና ብልሹ አሠራር ሊያጣራ ነው፡፡ ከሀ/ስብከቱ ዐበይት አድባራት አንዱ በኾነው የደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተ …

ኢንፍሌሸንን ሊያመጡ ከሚችሉ መንስኤዎች መካከል ፈጣን የ ኢኮኖሚ እድገት ኣንዱ እንደሆነ የሚስማሙ ምሁራን በርግጥ ኣሉ። ኣንዳንድ ምሁራን ደሞ ኢንፍሌሽንን እድገት ሊያመጣው ኣይችልም ብለው ይናገራሉ። የ ሁለቱ ልዩነት ያረፈበት ነጥብ የሚመስለው ኢንፍሌሽን የሚለውን ጽንሰ ሃሳብ ባዩበት ወሰን ላይ ነው። የ መጀመሪያው …

ትዳርን የማሸነፍ ኣቅም ማጣት እድገትን ተከትሎ ኣይመጣም Read more »