Image
እንኳን ለአንድ መቶ አስራ ዘጠነኛው የአድዋ ድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!
ዋ!….ያቺ ዓድዋ
ዋ!….
ዓድዋ ሩቅዋ
የዓለት ምሰሶ አድማስ ጥግዋ
ሰማይ ጠቀስ ጭጋግ ዳስዋ
ዓድዋ….
ባንቺ ብቻ ሕልውና
በትዝታሽ ብፅዕና
በመሰዋዕት ክንድሽ ዜና
አበው ታደሙ እንደገና….
ዋ !
ዓድዋ የዘር ዐፅመ ርስትዋ
የደም ትቢያ መቀነትዋ
በሞት ከባርነት ሥርየት
በደም ለነፃነት ስለት
ዓድዋ
የኩሩ ትውልድ ቅርስርዋ
የኢትዩጵያነት ምሰክርዋ
ዓድዋ
የኩሩ ደም ባንቺ ጽዋ
ታድማ በመዘንበልዋ
ዐፅምሽ በትንሣኤ ነፋስ
ደምሽ በነፃነት ሕዋስ
ሲቀሰቀስ ትንሣኤዋ
ተግ ሲል ሲንር ትቢያዋ
ብር ትር ሲል ጥሪዋ
ድው -እልም ሲል ጋሻዋ
ሲያስተጋባ ከበሮዋ
ሲያስገመግም ዳኘው መድፍዋ
ያባ መቻል ያባ ዳኘው
ያባ ነፍሶ ያባ ቃኘው
ያባ በለው በለው ሲለው
በለው-በለው-በለው-በለው !
ዋ !…ዓድዋ…
ያንቺን ጽዋ ያንቺን አይጣል
ማስቻል ያለው አባ መቻል
በዳኘው ልብ በአባ መላው
በገበየሁ በአባ ጎራው
በአባ ነፍሶ በአባ ቃኘው
በለው ብሎ ፥ በለው -በለው !
ዋ !….ዓድዋ….
ዓድዋ የትላንትናዋ
ይኸው ባንቺ ሕልውና
በትዝታሽ ብፅዕና
በመስዋዕት ክንድሽ ዝና
በነፃነት ቅርስሽ ዜና
አበው ተነሡ እንደገና ።
….ዋ!….ያቺ ዓድዋ
ዓድዋ ሩቅዋ
የእለት ምሰሶ አድማስ ጥግዋ
ሰማይ ጠቀስ ጭጋግ ዳስዋ
ዓድዋ…..
የካቲት – (፲ ፱ ፻ ፷ ፬- ዓድዋ )
እሳት-ወይ-አበባ
ከጸጋዬ-ገብረ-መድኅን

“አንድም ቀን ስቀን አናውቅም!” አሉ ኮሎኔል መንግስቱ ሃይለማርያም። ይህን በሚሉ ጊዜ እፊታቸው ላይ ፈገግታ ይታይ ነበር -ምሬቱ እንዳለ ሆኖ። ኢሳያስ አፈወርቂ ሲስቁ አይተናቸው አናውቅም። ግን ኮስተር ብለው የሚናገሩት ነገር እኛኑ አያሳቀን ነው። “ካሳ ይገባናል! ካሳ ስጡን” ሲሉ አሳቁን። ቀጠል አድርገውም “ምጽዋና አሰብን ወያኔ ሳይሆን የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲጠቀምበት ፈልገው” እንደነበር ተናግረው አሳቁን። “…የሰራነው ጥፋት ስለሌለ የሚጸጥተን […]

“አንድም ቀን ስቀን አናውቅም!” አሉ ኮሎኔል መንግስቱ ሃይለማርያም። ይህን በሚሉ ጊዜ እፊታቸው ላይ ፈገግታ ይታይ ነበር – ምሬቱ እንዳለ ሆኖ። ኢሳያስ አፈወርቂ ሲስቁ አይተናቸው አናውቅም። ግን ኮስተር ብለው የሚናገሩት ነገር…

 ኤሊያስ ገብሩ -ጋዜጠኛ

‹‹የ‹አዲስ ነገር› ጋዜጣን ሳስብ ኩራት ይሰማኛል››
‹‹በዘመኑ የቴክኖሎጂ ውጤቶች ጋዜጠኝነትን ለመስራት ምን ያህል ተጠቀምንባቸው?!›› 
                                                          ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ 

‹‹በ ‹አዲስ ጉዳይ›› መጽሔታችን ብዙ እንሰራለን ብለን በአጭሩ ተቀጭተናል››

‹‹በሙያችን ለሀገራችን አበርክቶት መስጠት ይጠበቅብናል፡፡››
                                                          ጋዜጠኛ አስማማው ኃ/ጊዮርጊስ

‹‹በሀገራችን የነጻነት ጥያቄ ፊት ለፊት ፍጥጥ ብሎ መጥቷል››
‹‹…ብዙዎቻችን የምንሻው ነጻነት የሚመጣው ጥቂቶች በሚከፍሉት ዋጋ ብቻ አይደለም››
ጦማሪ ናትናኤል ፈለቀ

ባሳለፍነው ረቡዕ ጥር 18 ቀን 2007 ዓ.ም ከፍቃዱ ማህተመወርቅ እና ሳሙኤል አበበ ጋር ወደ ቂሊንጦ እስር ቤት አብርተን ነበር፡፡ ፍቃዱም ወደዞን አንድ፣ ሳሙኤል ወደዞን እኔ ደግሞ ወደዞን ሶስት ለጥየቃ ገባን፡፡ ከታሰሩ አንድ ዓመት ሊሞላቸው ያሉትን ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ እና አስማማው ኃ/ጊዮርጊስ፣ እንዲሁም የዞን 9 ጦማሪ ናትናኤል ፈለቀን አስጠራኋቸው፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

አቡ ዳውድ ኡስማን በአዲስ አበባ አዲስ ክ/ከተማ የህገ ወጡ መጅሊስ ሰብሳበቢ የሆነው አቶ አብዱ እና የክፍለከተማው የመስጂድ እና አውቃፍ ዘርፍ ሃላፊ የነበረው አቶ ሰኢድ በተለያዩ ክሶች ወደ እስር ቤት መግባታቸውን…

The post አስገራሚ ዜና! – በአዲስ አበባ አዲስ ክ/ከተማ የህገ ወጡ መጅሊስ አመራር የሆኑት አቶ አብዱ እና አቶ ሰኢድ በተለያዩ ክሶች ወደ እስር ቤት መግባታቸውን ታወቀ! appeared first on ሳተናው (Satenaw) – Latest & Current Ethiopian News, Breaking News,.

በግሩም ተ/ሀይማኖት ኢትዮጵያዊኖች በአረብ ሀገራት ስደታቸው ጥሩም መጥፎም ይገጥማቸዋል፡፡ ብዙ ጊዜ ራሳቸውን አጠፉ በሚል ሰበብም አሰሪዎቻቸው ይገሏቸዋል፡፡ እንዴት ሞቱ የሚል ማጣሪያ ወይም ምርመራ አይደረግም፡፡ ከተቻለ ሬሳቸው ይላካል ካልሆነም ፍሪጅ ውስጥ…

በጨረታ የተሰጠ የ61 ሚ. ሕንፃ በዲዛይን ክለሳ ስም ያለጨረታ ብር 175 ሚ. ተደርጓል ሢሦ ለማይሞላ ሥራ የተፈጸመው ከብር 25 ሚ. በላይ ክፍያ እንዲመረመር ተጠይቋል ሊቀ ጳጳሱ ያልፈቀዱት የብር 40 ሚልዮን የኪራይ ውል ከንግድ ባንክ ጋራ ተፈጽሟል ከባንኩ የተለቀቀው ብር 14 ሚ. ያህል ገንዘብ በሕገ ወጥ ክፍያ እንዳይባክን ተሰግቷል ያለውድድር በተሠራ ፕላን ከብር 12 ሚ. በላይ …

ባለፉት 5 ዓመታት ኢትዮጵያ በህገ ወጥ የገንዘብ ፍሰት ያጣችው ገንዘብ መጠን 10 ቢሊዮን ዶላር ይገመታል ። ኢትዮጵያም አጣች የተባለው ገንዘብ በሃገሪቱ ድህነትን ለመቀነስ የተወሰዱትን እርምጃዎች ሊያፋጥን ይችል እንደነበርም ነው የተገለፀው ።

በከፊል የተቀዳውን የፓስተሩን ንግግር የሰማሁት “ሰልማ” የተሰኘውን ፊልም አይቼ እንደተመለስኩ ነበር። በዚህ አመት ለአራት የኦስካር ሽልማት የበቃው “ሰልማ” ፊልም ኦፕራ ዊንፍሬን ጨምሮ ምርጥ አክተሮች ይተውኑታል። ፊልሙ እ.ኤ.አ. በ1965 በዩናይትድ ስቴትስ የጥቁሮች የመምረጥ መብት ገፈፋን ተከትሎ፣ ዶክተር ማርቲን ሉተር ይህ መብት እንዲከበር የሚያደርገውን ትንቅንቅ ያሳየናል። ፓስተር ሉተር ለዜጎች የመምረጥ መብት እንዲከበር ያለማቋረት በመስበኩ ሲደበደብ፣ ሲንገላታና ሲታሰር […]

መግቢያ፤ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር፤ ከተመሠረተ ጀምሮ የተለያዩ ስሞችን፣ መርኆዎችን፣ ተግባራትን፣ ባጠቃላይም ማንነትን ተከናንቧል። ይህ ማለት፤ በሂደቱ እየተቀያየረ የሄደ ድርጅት ነው። ሲነሳ፤ አሁን የያዘው እምነት፣ ግብና አሠራር አልነበረውም። እግረ መንገዱን ለዕለቱ የሚረዳውን የፖለቲካ አቋም እየውለበለበ ተጓዘ እንጂ፤ ዘላቂ የሆነ የፖለቲካ አቋም አልነበረውም። ይህ የሚነግረን፤ ይህ ድርጅት፤ አጋጣሚዎችን ተጠቃሚነትን፣ ሥልጣንን፣ ቂምና በቀልን፣ የሕልውናው መሠረቶች አድርጎ የተጓዘ […]

70 ሽህ የሚሆን የሞስኮ ነዋሪ በክሬምሊኑ ቤተ-መንግሥት ላይ የሰላ ትችት በማቅረባቸዉ የሚታወቁት የሩስያ መንግሥት ዋንኛ ተቃዋሚ ፖለቲከኛ ቦሪስ ኔምትሶፍ ግድያን በተመለከተ ሐዘኑን በሰልፍ ገለፀ። የሩስያዋ ሁለተኛ ሰፊ ከተማ በሆነችዉ በሳንክት ፒተርስበርግም ቢያንስ 2500 ተቃዋሚ ሰልፈኞች አደባባይ በመዉጣት ሐዘናቸዉን ገልፀዋል።


Minilik Salsawi – የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ እንከኖቻችን ጥቅል ውጤት ማስጨነቁና ማሳሰቡ የሀገርና የህዝብ ስሜት ላለው ሁሉ አይቀሬ ነው፡፡በሃገር ቤት ማናቸውንም የጥፋት ድርጊት የሚፈጽሙ ወገኖች ለሀገር እንደቆሙ፤ የህዝብ ልጆች እንደሆኑ አድርገው መጮሃቸውና ሀቀኛ መምሰላቸው፤ ሌላው እንዳይናገር በር ይዘጋል፡፡ በበፊት ስርአቶች የእጅእላፊ አሊያም ጉቦ እንዲሁም ብዝበዛ ይባል የነበረው የምዝበራና አገርን የማራቆት ተግባር፣ ዛሬ ሙስና የተባለውን ፤ በልማት እና ትራንስፍሮሜሽን ሲስተም ሃገር የሚያደማ እና የሚያቃጥል ሆኗል፡፡ አገር ትልቅ ለውጥ ላይ ናት፤ ከፍተኛ የትራንስፎርሜሽን ሂደት ላይ ነን እየተባለ፤ በተጭበረበረ የፖለቲካ እና በቅጥር ቁልል የኢኮኖሚ እድገት ፕሮፓጋንዳ እየማሉ በጐን የዝርፊያ የኮንትሮባንድ እና በአንድ ጀንበር ፎቅ ሠርቼ ልደር ዘመናዊ ምዝበራ ይታያል፡፡ ከፖለቲካ እና ፖለቲከኞች የተጠጋጉ ሁሉ በአንዴ ዘጋ/ዘጋች ዛሬ በኢትዮጵያ የተለመደ ቋንቋ ነው፡፡ እንደአንዳንድ የአፍሪካ ሃገሮች ዐይንያወጣ የቀን ተቀን ዘረፋ የሚመጣው ከላይ እስከታች እየተወሳሰበ ያለው ሙስና ፍፁም ወደፈጠጠ ደረጃ ሲደርስ ነው፡፡

አንድም ሙስናው በየአቅጣጫው መሆኑ፤ አንድም ደግሞ ቢሮክራሲያዊ መጠቅለያ መኖሩ እጅግ ሊፈታ በማይችልበት ደረጃ ውስብስብ አድርጎታል፡፡በዚህ ላይ የወያኔ ግለሰቦች አሻጥር ተደምሮበት፣ ከቁጥጥር ውጪ ወደሆነ ደረጃ ተሸጋግሯል፡፡ የኢትዮጵያውያን በሃስት ክስ በየእስር ቤቱ መታጎር፣ የመሬት አሰቃቂ አወሳሰድ፣ ከፍተኛ የኮሚሽንና የድለላ ሥራ፣ አደገኛ ወገናዊ አሠራር…በአስደንጋጭ የድህነት መቀመቅ ውስጥ ያለችውን አገር ከምትሸከመው በላይ ትከሻ አጉብጥ ሸክም ጭኖባታል፡፡ወያኔ ኢትዮጵያን እያቃጠለ ከኔ ጋር ብሩህ ተስፋ እያለ ያብዳል::በትንሹም በትልቁም ነገር ከማበድ ይሰውረን፡፡ የመሞቻ መሣሪያ ከማማረጥ ያድነን፡፡ያኔ በደርጉ ዘመን በሥራው አጋጣሚ በእጁ የገባውን የሕዝብ ገንዘብ ለግል ጥቅሙ በማዋሉ የሚለው የዜና ሐረግ ነበር ሬዲዮንና ቴሌቪዥን ያጣበበው፡፡ ዛሬ በወያኔው ስርአት ዳር እስከዳር በየሰው አፍ የሚወራ ነገር ሆኗል፡፡ ዝርፊያው ዓይነት በዓይነት ሆኗል፡፡ የአንድ ሰሞን ሕዝብ ማዘናጊያ እና ሆያሆዬ ዘገባ ተወርቶም በቀላሉ ይረሳል፡፡ለህዝብ የማይሳሳው የማይጨነቀው ወያኔ ለህብረተሰብ ቀጥተኛ መጥፊያ የሚሆኑ እንደመድሃኒት ያሉ የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ባመቸው መንገድ ሁሉ ተበርዘው ከተባዙ፣ ምን ያህል አሰቃቂ የሆነ ዕልቂት እንደሚያስከትሉ መገመት አያዳግትም፡፡ የሚያስገኙት ገንዘብ የትየለሌ፣ የሚፈጁት ህዝብ የትየለሌ!!ይህንን ስርአት በማስወገድ ራሳችንን ነጻ አውጥተን ሃገርን እና ወገንን ማዳን የዜግነት ሃላፊነት መሆኑን ልናውቅ ይገባል::

ሃገራችን እና ወገናችን በጨለማ ውስጥ እየዳከረ ባለበት በዚህ የወያኔ አገዛዝ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በመረባረብ የዜግነት ግዴታውን አውቆ ለህዝቦች መብት እና ነጻነት መታገል አለበን። ሃገሪቷ በዚህ አደጋ ውስጥ ባለችበት ሰአት ላይ ህዝብ አጣብቂኝ ውስጥ ገብቶ ለኑሮ ውድነት ለሞት ለስደት እየተዳረገ ኢትዮጵያዊነት እየተዋረደ ከመሆኑም ባሻገር ኢትዮጵያን እያቃጠለ ከኔ ጋር ብሩህ ተስፋ እያለ የሚያጭበረብረውን ወያኔን ከስሩ መንግሎ በመጣል በመቃብሩ ላይ የህዝብን ነጻነት ማረጋገጥ አሌ የማይባልበት ወሳኝ ወቅት ላይ መሆናችንን በማወቅ ከትግሎ ጎን አቅማችን በሚችለው ሁሉ በመቆም ነጻነታችንን ማረጋገጥ ግድ ይለናል::

– ምርጫ በመጣ ቁጥር እንክብካቤው ሰልችቶናል::ህክምና አተን ስንገላታ መች ደረሳችሁልን::የአዊ ነዋሪዎች
– የመኢአድ አመራሮች ከወያኔ የምርጫ ሜዳ ራሳቸውን እያወጡ ነው::ድርጅቱ ምርጫውን ጥሎ ይወጣል::

‪#‎Miniliksalsawi‬ – በምእራብ ጎጃም ዞን ወንበርማ ወረዳ የሚገኙ አርሶ አደሮችን በማዳበሪያ እዳ ምክንያት ፓሊስና የወረዳው አመራር ያለ ፍቤት ትእዛዝ ቤታቸውን እየፈተሸ ከብት ንብረታቸውን እየዘረፉ መሆኑን አንድ ወዳጀ አሁን አስታውቆኛል።አርሶ አደሮቹንም ወደ ማጎሪያ እስር ቤት እየከተቱዋቸው ነው።

ጉልበት ያለውም ቤተሰቦቹን ይዞ በመሰደድ ላይ ነው እንደ ታማኝ ምንጮች ገለፃ ህዝቡ በጣም ተማሯል::።ከ50 ሰዎች በላይ እንደታሰሩ ከአንድ ቀበሌ ብቻ “የርግን” ከምትባል ቀበሌ ለጊዜው ቁጥራቸው የማይታወቁ ሰዎች ሀገር ጥለው ሸሽተዋል::አንድ “ወገዳድ”በሚባል ቀበሌ የሚኖር ሰው እስር ቤት ክቆየ በሁአላ እንደወጣ በድብደባ ብዛት መሞቱ ታውቋል::
የታሳሪዎች ስም:-
1.አርሶ አደር ወርቄ
2. ” አዝመራው
3. ” ስለሽ

የመኢአድ ከፍተኛ አመራር የሆኑት ኢንጅነር ሽፈራዉ ከምርጫዉ ራሳቸዉን ያገለሉበትን ምክንያት አሳወቁ::
የሰሜን ቀጠና ሃላፊ የሆኑት ኢንጅነር ሽፈራዉ ሑሉንም ነገር ወያኔ በተቆጣጠረበት በምርጫ መሳተፍ ለአባገነንነቱ ሕጋዊ እዉቅና ከመስጠት ባሻገር ሰላማዊ ትግል እየተባለ ሕዝብን ከወዲሁ ዉጤቱ በታወቀ ላይ ማድከም እና ሌሎች የሰላማዊ ትግሎች ላይ እንዳያተኩር ማዘናጋት በመሆኑ ነው ብለዋል:: ኢንጅነር ሽፈራዉ ባለፈዉ ትብብሩ በጠራዉ ሰልፍ ላይ በማስተባበር ላይ እንዳሉ ለአንድ ሳንምንት በወያኔ ደህንነቶች ታፍነዉ ተወስደዉ ከፍተኛ ድብደባ እንደተፈጠመባቸዉ ይታወቃል::ለጊዜው ስማቸው ይፋ ያልሆነ አመራሮች ራሳቸውን ከወያኔ የምርጫ ሜዳ ያገለሉ ሲሆን ድርጅቱ ይህን ተከትሎ ምርጫውን ጥሎ ይወጣል ተብሎ እየተጠበቀ ነው::

በተያያዘ ዜና በአዊ ዞን ኮሶበር ከተማ መንግስት ምርጫውን ምክናያት በማድረግ እስካሁን ተኝተው ከርመው አዊ ዩኒቨርስቲን የመሰረት ድንጋዪ አስቀመጡ በተመሳሳይ የኮሶበር ሆስፒታልንም በቶሎ ቶሎ ድንጋይ አስቀምጠዋል::የካቲት አንድ ቀን ህብረተሰቡ ግን እስከዛሬ የት ነበራችሁ ልጆቻችን ተምረው ዩንቨርስቲ መግቢያ ውጤት አምጥተው እሩቅ ቦታ ሲመደቡ አቅም አንሶዋቸው እዚሁ እንደኛው ገበሬ ሆነው ሲቀሩ ልጆቻችንና ባልተበቶቻችን ህክምና አጥተው በመንገድ ሲቀሩ እንዲሁም ምራጫ በመጣ ቁጥር ቃል የገባችሁልን ከዚህ በፊት የት አሉ ብሎዋቸዋል::

“ በእኔ ሀላፊነት የተገዛላቸውን ሙሉ ልብስ ፤ የተዘጋጀላቸውን ፓስፖርትና የኪስ ገንዘብ አስረክቤ ለከፍተኛ ትምህርት ወደ ውጭ ሀገር ከሸኘሗቸው መሀከል ፕሮፌስር አሥራት ወልደየስ አልነበረበትም። ቀደም ሲል በእንግሊዞች አስተባባሪነት ከአንደኛ ደረጃ ትምህርት…

በአለም መፋረጃ ወቅት ላይ እንገኛለን። ካልጠፋ ቦታ ለሺ ዘመናት ስነምህዳሩን ጠብቆ ተከብሮ የኖረውን የዋልድባ ገዳምን ማረስ እንዲሁም የዝቋላ ገዳም ላይ እንውጣና ክርስትና ያልሆነ ሌላ እምነት /የእሬቻ በዓልን/ እናክብረበት  ማለት  ፍርጃ…

ሮተርዳም፣ ጥቅምት 28 ቀን 2015 – በስደት ስሙ አለማየሁ ስንታየው በመባል የሚታወቀው የህወሃት ሰላይ ከኔዘርላንድስ ተባረረ። አለማየሁ ስንታየሁ ቋሚ ነዋሪ ከነበረበት ከኔዘርላንድስ እንዲባረር የተደረገው በዚያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በከፈቱበት የስለላ ክስ መሆኑም ታውቋል። የሮተርዳም ከተማ ፍርድ ቤት በአለማየሁ ላይ የተመሰረተውን የስለላ ክስና ማስራጃ ለረጅም ጊዜ ሲመረምር ከቆየ በኋላ የግለሰቡ የመኖርያ ፈቃድ እና ቤት እንዲነጠቅ፣ የሆላንድን ምድርም […]

አንድ ወቅት ሎሬት ጸጋዬ አንድ ስብሰባ ላይ የተጠየቁት ጥያቄ ትዝ ይለኛል። <<ስለ አፄ ቴዎድሮስ ሁል ጊዜ እያሞገሱ ለምን ይጽፋሉ?>> ተብለው ሲጠየቁ <<አይ ሌላውንማ የኢትዮጵያ ጠላቶች ይጽፉታል>> ነበር ያሉት።  ስሞኑን ሎሬት…

-የኢትዮጵያ መንግሥት መረጃውን በተመለከተ ዝምታን መርጧል -የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የኢትዮጵያ የደኅንነት ተቋምን አድንቋል እ.ኤ.እ. በ2012 የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሆነው የተመረጡት የደቡብ አፍሪካ የቀድሞ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ንኮሳዛና ድላሚኒ…

ይህ ዘገባ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ዘገባ ነው ኢህአዴግ በዓለም ባንክ በኩል ከእንግሊዝ የዓለምአቀፍ ልማት ተራድዖ መ/ቤት ሊለግስለት ታቅዶ የነበረው 4.9 ቢሊዮን ዶላር (98ቢሊዮን ብር) የገንዘብ ድጋፍ ነጠፈበት፡፡ አቶ ሬድዋን አልነጠፈብንም…

ሮተርዳም፣ ጥቅምት 28 ቀን 2015 – በስደት ስሙ አለማየሁ ስንታየው በመባል የሚታወቀው የህወሃት ሰላይ ከኔዘርላንድስ ተባረረ። አለማየሁ ስንታየሁ ቋሚ ነዋሪ ከነበረበት ከኔዘርላንድስ እንዲባረር የተደረገው በዚያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በከፈቱበት የስለላ ክስ…

በደቡባዊ አፍሪቃ በምትገኘው ንዑሷ ሀገር ሌሶቶ ወይም በሌላ አጠራሯ ባሶቶ ውስጥ በዛሬው ዕለት ምክር ቤታዊ ምርጫ ተካሄደ። ከታቀደለት ጊዜ አስቀድሞ የተካሄደው ምክር ቤታዊ ምርጫ ቀደም ሲል የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ የተደረገባትን ሀገር ያረጋጋል ተብሎ ታስቧል።

የቀድሞው ጠ/ሚኒስተር መለስ ዜናዊ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት አፈጻፀም ሂደት ላይ የነበራቸው አቋም በወቅቱ ከነበረው የጋራ አመለካከት ሊከሰት የሚገባው ተፈጥሮአዊ ክስተት ነው እንጂ አገር ለመጉዳት በማሰብ አይደለም በማለት ጄኔራል ጻድቃን ገ/ትንሳኤ ገለጹት፡፡ ጄኔራሉ ይህንን የተናገሩት፤ በጦርነቱ ወቅት መለስ ለጦር መሣሪያ ግዥ በሚወጣው ገንዘብ መጠን ላይ ተቃውሞ ነበራቸው የሚለውን ስሞታ በመጥቀስ ላቀረብንላቸው በሰጡት ምላሽ ነው፡፡ አንዳንዶቻችን ኤርትራ ልትወረን ትችላለች ብንልም ሌሎች አትወረንም የሚል አመለካከት እንደነበራቸውም ጠቅሰዋል፡፡ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ኤታማጆር ሹም የነበሩት ጄኔራል ጻድቃን፡- ጦርነቱ ድንገት የመጣ ቢሆንም የመከላከያ ሀይሉን የማደራጀት ሥራ ሲሠራ የነበረ መሆኑን የገለጹት ጄኔራል ጻድቃን፤ በዚህም ረገድ በአንድ ሚሊየን ፓውንድ ክፍያ የእንግሊዝ ኤክስፐርቶችን በመቅጠር የአየር ሀይል እና የአየር መከላከያ ሲስተም ጥናት መሠራቱን፣ የመካናይዝድ፣ ፓራኮማንዶና ኮማንዶ ሀይሎች ስልጠና እና የመሳሰሉ እንዲሁም የአዲስ ምልምል ወታደር የትምህርት ደረጃ 10ኛ ክፍል እንዲሆን እና የነባሩንም ትምህርት የማሳደግ ተግባራት መካሄዳቸውን አውስተዋል፡፡ እነዚህ ይህም በጦርነቱ ወቅት የሠራዊታችንን ብዛት ከ55,000 ወደ 350,000 ሲያድግ ያንን ሊሸከም የሚችል አቅም እንዲኖር ማስቻሉን አስረድተዋል፡፡ በጦርነቱ ወቅት የሴንትራል ኮማንድ አባል የነበሩት ጄኔራል ጻድቃን፡- መለስ ዜናዊ ለጦር መሣሪያ ግዥ በሚወጣው ገንዘብ መጠን ላይ ተቃውሞ እንደነበራቸውና ‹‹ሌሎች ፕሮግራሞችን ሳናፋልስ ባለው በጀት ጦርነቱን እንፈጽም›› የሚል አቋም እንዳራመዱ ያረጋገጡ ቢሆንም፤ ያ አቋም ግን ሁሉም አመራር ይጋራው ከነበረው ለኢኮኖሚ ቅድሚያ ከመስጠት አመለካከት የሚመነጭ አድርገው እንደሚረዱት እንጂ፤ ‹‹አንዱን ለመወንጀል ሌላውን [ለማመስገን] አልጠቀምባቸውም›› ብለዋል፡፡ የጄኔራል ጻድቃን ገ/ትንሳኤን ሙሉ አስተያየት […]

የደርግ ሥርዐት መገርሰስን ተከትሎ የቀድሞው ሠራዊት እንዲበተን ቢደረግም 9,000 ገደማ ወታደራዊ ኤክስፐርቶች የአዲሱ መከላከያ ሠራዊት አካል ሆነው እንዲቀጥሉ መደረጉን ጄኔራል ጻድቃን ገ/ትንሳኤ አወሱ፡፡ ሰሞኑን ከሆርን አፌይርስ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ የቀድሞውን ሠራዊት የመበተን ውሳኔ ድህረ-ምክንያት (rationale)፤ ከአብዮታዊ ለውጥ ርዕዮተ-ዓለማዊ አመለካከት እና ከሠራዊቱ የደርግን ወንጀሎች ፈጻሚ የነበረ ከመሆኑ የመነጨ መሆኑን ጄኔራሉ አብራርተዋል፡፡ የቀድሞ ሠራዊት በመሰናበቱ የተጎዳ ቤተሰብ እንዳለ እንዲሁም የአፈጻጸም ሂደቱን በተመለከተም የሚቀርብ ትችት ሊኖር እንደሚችል እንደሚረዱ ከጠቀሱ በኋላ ውሳኔው በመሠረቱ ግን ትክክል ነበር ብለዋል፡፡ አሁንም መለስ ብለው ሲያስቡትም፤ የቀድሞው ሠራዊት ከአዲሱ የታጋይ ሠራዊት ጋር ተቀላቅሎ ይቀጥል ቢባል ሀገር ሊከላከል የሚችል፣ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ዋዜማ ላይ የነበረውን ሠራዊት ያህል ብቃት ያለው ሠራዊት አይሆንም ነበር፡፡ ይልቁንም የተለያዬ የፖለቲካ ሀይሎች የሚጎትቱት ሀይል ይሆን ነበር ብለዋል፡፡ በሌላ ሀገር ሄደው ያጋጠማቸውም ተሞክሮ ያንን አመለካከት እንዳጠናከረላቸው ነው የጠቆሙት፡፡ ይሁን እንጂ ከቀድሞ ሠራዊት ‹‹ክሬም›› የሆነውን ክፍል ወደአዲሱ ሠራዊት እንዲመለስ መደረጉን ጠቅሰው፤ ይህ ተቺዎች የሚዘሉት ሀቅ ነው ብለዋል ጄኔራል ጻድቃን ገ/ትንሳኤ፡፡ የሽግግር መንግስቱ ሠራዊት ቺፍ ኦፍ ስታፍ የነበሩት ጄኔራል ጻድቃን፤ ከቀድሞ ሠራዊት አባላት መሀል ከደህንነት እና ከኢሠፓ መዋቅር ግንኙነት ያልነበራቸው፣ ራሺያ ሄደው የሰለጠኑ፣ 9,000 ወታደራዊ ኤክስፐርቶች – 7,000 ከእግረኛ እና 2,000 ከአየር ሀይል – በአዲሱ ሠራዊት እንዲቀጥሉ ተደርጓል ብለዋል፡፡ በ1983 የህወሓት ታጋዮች ብዛት 85 ሺህ ገደማ የነበረ ሲሆን አዲሱ ሀገራዊ ሠራዊት ሲደራጅ ከ32-35ሺህ የሚሆኑት እንደተሰናበቱም አስታውሰዋል፡፡ የስልጠና፣ የጥናት እና […]

የካቲት ፳(ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ክልል ዋና ከተማ በአዋሳ የካቲት 14 ቀን 2007 ዓም በደረሰው ከፍተኛ የእሳት ቃጠሎ የሟቾች ቁጥር በመንግስት እንደተገለጸው አንድ ሳይሆን ከ20 በላይ መሆኑን ተገጂዎች ለኢሳት ገልጸዋል። ከፍተኛ ንብረት ከወደመባቸውና እሳቱ ሲነሳ በስፍራው ከነበሩት መካከል አንዱ ለኢሳት ሲናገር፣ እርሱ የ6 ሰዎችን የተቃጠለ አስከሬን ማየቱን፣ በስፍራው የሚገኙ ጓደኞቹ ደግሞ በአጠቃላይ …

የካቲት ፳(ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ወኪላችን እንደዘገበው በሰቆታ አካባቢ የተከሰተውን ከፍተኛ ድርቅ ተከትሎ አርሶደአሮቹ  ወደ ምእራብ ጎጃምና ሌሎች የአማራ ክልል አካባቢዎች በመሰደድ ላይ ናቸው። ተፈናቃዮቹ ከክልሉ ባለስልጣናትም ይሁን ከፌደራል መንግስቱ ምንም አይነት እርዳታ አለማግኘታቸውን ገልጸዋል። ብዙዎቹ ተፋናቃዮች ወጣት ወንዶችና ሴቶች ሲሆኑ፣ በሰፈሩባቸው አካባቢዎች ስራ ሰርተው ራሳቸውን እንዲያስተዳድሩ እየጠየቁ ነው። ተፈናቃዮቹ በዝናብ እጥረት ምክንያት …

የካቲት ፳(ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰሞኑን እንዳዲስ ተጠናክሮ በቀጠለው ሙስሊም ኢትዮጵያውያንን የማሰር ዘመቻውን በመቃወም ድምጻችን ይሰማ የጠራው ስልክን ለ12 ሰአታት የማጥፋት ዘመቻ በተሳካ ሁኔታ መካሄዱን ዘጋቢያችን ገልጿል፡፡ በርካታ ሙስሊሞች ስልኮቻቸውን አጥፍተው የዋሉ ሲሆን፣ በማህበራዊ የመገናኛ ብዙሃን የሚያደርጉትን እንቅስቃሴም አቁመው ውለዋል። በርካታ ክርስቲያኖችም ጥሪውን ደግፈው ስልካቸውን ዘግተው ውለዋል። እርምጃ የመንግስት ዋነኛ የገቢ ምንጭ በሆነው …

የካቲት ፳(ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በክልሉ ኢንዱስትሪና  ከተማ ልማት ቢሮ እና የተለያዩ ቢሮዎች  በየእለቱ ጉዳያቸውን ለማስፈጸም የሚመላለሱ ባለጉዳዮች በተለያየ ሰበብ ፈጻሚ በማጣት መቸገራቸውን ድርጅቱ ባዘጋጀው የአስተያየት መስጫ መዝገብ ላይ ማስፈራቸውን ከስፍራው የደረሰን መረጃ  ያሳያል። ከተለያዩ አካባቢዎች ጉዳይ ለማስፈጸም እንደመጡ የገለጹት ቅሬታ አቅራቢዎች  በተለይ በስብሰባ ሰበብ ለረዢም ጊዜ መጉላላታቸውን ባሰፈሩት የሃሳብ መስጫ ደብተር ላይ ለማንበብ ይቻላል። አስተያየት ሰጪዎች …

‹‹ያለ ኢኮኖሚ የበላይነት የፖለቲካ የበላይነት አይመጣም›› የሚለው የህውሃት ኢህአዲግ ፖለቲካ ኢኮኖሚውን ከመቆጣጠር ባለፈ ደጋፊዎቹን በኢኮኖሚ በማብቃትና በተጠቃሚነታቸውም ፖለቲካውን በመጠበቅ የበረኛነት ሚና እንዲጫወቱ በ97 ምርጫ ማግስት ከተወሰዱትርካሽ እርምጃዎች አንዱ በግምታዊ አቀማመጥ…

እንግዲያውስ ስትሰሙ እንዳትደነግጡ . . . . ረጋ ብላቹ አንብቡት፡፡ Ndrangheta syndicate ይባላል፡፡ ዋና መቀመጫውን በጣልያኗ ካላበሪያ ከተማ ያደረገው ይህ ግሩፕ እንደ ኤ .አ በ1960 ዓ . ም የተመሰረተ ሲሆን…

ስለየተለያዩ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች አናኗኗር እና ባህል ዘግቧል። ወጣቱ ጋዜጠኛ በኢትዮጵያ ተዘዋውሮ ስላየው ከመዘገብ ባለፈ ፤ከፊል ጉዞውን የሚገልፅ አንድ መፅሀፍም አሳትሟል።

የደቡብ ሱዳን ተቀናቃኝ ሃይሎች ድርድር በምሥራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ-መንግስታት አማካኝነት አዲስ አበባ ላይ በመካሄድ ላይ ይገኛል። ድርድሩን በጥሞና የሚከታተሉ የፖለቲካ ተንታኞች ድርድሩ ፋይዳ ቢስ ነው ሲሉ ይተቻሉ።

  የካቲት ፲፱(አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በመንግስት የመገናኛ ብዙሃን ውስጥ ተቀጥረው የሚሰሩ ጋዜጠኞች አብዛኞቹ የኢህአዴግ አባላት መሆናቸውን ኢሳት በደረሰው የአባላት ስም ዝርዝርና የስራ ድርሻ ሰነድ ለማረጋገጥ ችሎአል።…

ሌባ ለአመሉ ዳቦ ይልሳል ሆነና ነገሩ ይህንን እንኩአን እዉነቱን ሊነግሩን አልፈለጉም:: በጎነት እና አስተዋይነትን ወደ ርካሽ ፖሎቲካ አዞሩትና እንዴት ብሎ መጠየቅ ልማዱ ላልሆነው ህዝብ “በቅርቡ በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳድራ 20 ሚልዮን የአውስትራልያ ዶላር ተሸለመች” ብለዉት እርፍ::
ቅሌት!

በሪቱን ለማናገር የማሰነው ቡድን ከጎሮቤትም ሆነ ከቅርብ ቤተዘመድ ያገኘዉት ምላሽ የ20 ሚሊዮን ዶላሩን ታሪክ እና በሪቱ አሸነፈች ስለተባለዉ አዋርድ የሚያዉቁት ነገር እንደሌለ ነዉ:: ዛሬም ከአንድ ፖለቲከኛ አፍ የሚወጣውን ሁሉ ምንም ሳያጣራ ልክ ከላይ ከጸባዖት እንደመጣ ቃል ጋቢ አንጥፎ እየሰገደ በእልልታ የሚቀበል ምስኪን ሰው በዚህ በመረጃ ዘመን መኖሩ ያሳዝናል :: እዉነቱ ወዲህ ነዉ::

ነገሩን የመልቦርን ነዋሪ እና በሪቱ ጃለታን በቅርበት የምያዉቃት ጃራ ቦሩ (jaarraa boru) እንዲህ ይገልፀዋል::
ታሪኩ እንዲህ ነው᎗ ባሪቱ ጃለታ(ከመሃመድ አህመድ እና ከክሚያ የተወለደች: የምልኬሳ እና ዳሜሳ እህት:) ከምትኖርበት ሜልበርን ልዩ ስሙ ወራቢ (Werribee) ከምባል ከተማ ለእረፍት ከቤተሰቦችዋ ጋር ሃገር ቤት ሄዳ በነበረችበት ወቅት በመንግስት ምንም ትኩረት ያልተሰጠበትን የጋራ ሙለታን አከባቢ ትምህርት ቤቶች ለመጎብኘት እድሉን ታገኛለች:: ያንን ጉብኝት ካደረገች በኋላ መንፈሷ እረፍት ያጣል:: ነብሷ ትጨነቃለች:: ወደምትኖርበት ሜልበርን (ወራቢ) ስትመለስ በዚሁ ጉዳይ ትታመማለች:: ትምህርቷን መከታተል ይሳናታል:: በየሳይካያትሪስቱ ብትወሰድ ለመንፈሷ ጭንቀት ምንም መፍትሔ ታጣ:: በመጨረሻም በሽታውን ያልተናገረ መፍትሄ አያገኝም በምለው ፕሪንስፕል በመመራት ለትምህርት ቤቷ ፕሪንስፓል (ዳይሬክተር) “ኢትዮጵያ ያሉት ልጆች በሚያፈስ ቤት ውስጥ እንደዚያ አፈር ላይ ተቀምጠው በተጨናነቀ ሁኔታ ሲማሩ አይቼ ደስታ ራቀኝ፣ እንቅልፍ አጣሁ፤ ምግብ እንኳ መብላት አልቻልኩም::” ብላ ስታለቅስባቸው ጊዜ የተለያዩ ገንዘብ የማሰባሰቢያ ፕሮግራሞች ተካሂዶ የተለያዩ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑድርጅቶች ተረባርበው የዚህችን ሲበዛ ሰብዓዊነት የተሞላባትን ታዳጊ ወጣት መንፈስ ለመታደግ ባሳዩት ርብርቦሽ አንድ ትምህርት ቤት ለመስራት የሚያስችል ፈንድ ይገኝላታል:: ታዲያ ዶክተሩ እንደዚያ በስንት እንባ፣ ህመም እና ደጅ መጥናት የተገኘውን ገንዘብ የኢትዮጵያ ትምህርት ቤቶች ከውጭ ለሚጎበኛቸው እነኒያ በመንግስት ቸል የተባሉት ትምህርት ቤቶች ምን ያህል ሰዉን እንደሚያስለቅሱ ላለማንሳት እና ፖለቲካቸውን ለማሳመር እንዲመቻቸው ነው የሃያ ሚልዮኑን ቲዎሪ ይዘው ከች ያሉት::
አቶ ቴዎድሮስ ድፍን የሜልበርን ህዝብ የሚያውቀውን ታሪክ መልኩን ስለምን ለመለወጥ ፈለጉ:: የሆነ ሆኖ ዶክተሩን ሳላመሰግናቸው ላልፍ የማልፈልገው ግን ፈንዱን ወደ ትግራይ ሳያዞሩ እንደታቀደው ወደ ጋራ ሙለታ እንዲላክ መወሰናቸውን ነው:: በሪቱን እንኳን ደስ ያለሽ ልንላት ይገባል:: ያበባ እቅፍ ቱላማሪን አየር ማረፊያ ይጠብቃታል:: ዶክተር እርስዎን ግን ታዘብናችሁ::
Dagim Ahunim

Image

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ምርጫ ቦርድ የአባል ፓርቲዎችን ዕጩዎች ያለ አግባብ በመሰረዙና እስከዛሬ ድረስ ዕጩዎቻቸው በዝርዝር ባለማሳወቁ ምክንያት ለየካቲት 22/2007 ዓ.ም በ15 ከተሞች ሊያደርገው የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ላልተወሰነ ጊዜ ማስተላለፉን የትብብሩ ፀኃፊ አቶ ግርማ በቀለ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

አቶ ግርማ በቀለ ‹‹ምርጫ ቦርድ ዕጩዎችን እመዘግብበታለሁ ባለበት የጊዜ ሰሌዳ ውስጥ ዕጩዎቻችን በዝርዝር ሊያሳውቀን አልቻለም፡፡ በተለይ የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩዎችን ለመግለጽ ፈቃደኛ አልሆኑም፡፡ ከምንም በላይ ግን በዕጩዎች ስረዛና ወከባ በርካታ ጊዜ አጥፍቶብናል፡፡›› ሲሉም ሰልፉ የተራዘመበትን ምክንያት ገልጸዋል፡፡

ምርጫ ቦርድ የትብብሩን አባል ፓርቲዎች ዕጩዎች በዝርዝር ባለማሳወቁ፣ አባል ፓርቲዎቹ ለምርጫ ቦርድ ቅሬታ እያቀረቡ በመሆኑና አሁንም ድረስ ከምርጫ ቦርድ ጋር ያሉት ችግሮች ያልተፈቱ በመሆናቸው ትብብሩ ሰልፉ የሚደረግበትን ቀን ወደፊት ለህዝብ እንደሚያሳውቅ ገልጸዋል፡፡

እንደሚታወቀው የኢህአዴግ አገዛዝ ከጊዜ ወደ ጊዜ ጸረ ዲሞክራሲ አካሄዱ እየባሰበት የመጣና መሠረታዊ መብቶችን ሙሉ በሙሉ ሊባል በሚችል መልኩ ማፈኑን አጠናክሮ ቀጥሎበታል፡፡ በቅርቡ በአንድነትና በመኢአድ ፓርቲ ላይ አገዛዙ በሚያዝዛቸው የተቋማት ኃላፊዎች ቀጭን ትዕዛዝ የፓርቲዎቹ ሕልውና ለጥቂት ግለሰቦች ተላልፎ ተሰጥቷል፡፡ ይህ ዓይነቱ ህገ-ወጥ ድርጊት መቼዉም ቢሆን ተቀባይነት አይኖረውም! ለአገራችን የሠላማዊ የስልጣን ሽግግር ከባድ መሠናክል ሊሆን እንደሚችል ሁሉም ይገነዘባል ብለን እናምናለን፡፡ የኢህአዴግ የምርጫ ቦርድ እንዲህ ዓይነቱን ክፉ ስራ ሲወስን የአገራችንን የረጅም ሠላም አይተው ሣይሆን በአገዛዙ ቁንጮ ሰዎች በመታዘዝ በተቋም ስም የሚሠሩት የማደናገር የድንቁርና ተግባራቸዉ አንድ አካል ነው ብለን እናምናለን፡፡ ማህበራችን ይህን ድርጊት እጅጉን ያወግዛል። በመሆኑም ድርጊቱን በጋራ እንቃወማለን።

በምርጫ ቦርድ ስም የተወሰነው ህገ-ወጥ ውሣኔ ምክንያት መላ የአንድነትና የመኢአድ አባላት የፖለቲካ እንቅስቃሴአቸው ተገድቧል፡፡ ይሁን እንጂ ለአገራቸው ካላቸው ፅኑ ፍቅር አኳያ ትግሉን ለማስቀጠል ከሠማያዊ ፓርቲ ጋር አብሮ ለመሥራት የአባልነት ፎርም በመሙላት ትግሉን ቀጥለዋል፡፡ ይህ ዓይነቱ የአባላት ቆራጥ ውሣኔ ሊበረታታና ሞራል ሊሰጠው የሚገባ ነው ብለን እናምናለን! እኛም በሰሜን አሜሪካ የምንገኝ የሁለቱ የድጋፍ ማህበራት ሙሉ በሙሉ ድጋፋችንን እንደምንሰጥ እናረጋግጣለን፡፡

ስለሆነም በሰሜን አሜሪካ የምንገኝ የአንድነትና የሠማያዊ የድጋፍ ማህበራት በጋራ በኮሜቴ ደረጃ ተዋቅረን በዋና ዋና ጉዳዬች ላይ ማለትም በፋይናንስ፤ በእስረኞች ጉዳይ እና በዲኘሎማሲው ዙሪያ ሙሉ በሙሉ በትብብር አብረን እየሠራን የሰማያዊ ፓርቲንና ሌሎች በሃገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ሃይሎችን በጋራ ድጋፍ ለመስጠት ውሣኔ አሣልፈናል፡፡ በቀጣይም በጋራ የኮሚቴ ውይይቶችን እያደረግን ለሰማያዊ ፓርቲ የሚያስፈልጉ የሞራልና የማቴሪያል ርዳታ እንደምንሰጥ እናረጋግጣለን፡፡

የሰማያዊና የአንድነት ሰሜን አሜሪካ ድጋፍ ማህበራት

የካቲት 19 2007 ዓ/ም

የዚህች ሀገር ባለቤቶች ሁላችንምካልሆንን በቀር በተናጠል ማንም ባለ ግዛት ሊሆን አይችልም፡፡ ሉሲ አማራ ትሁን ኦሮሞ፣ አፋር ትሁን ሶማሌ፣ ጉሙዝ ትሆን ትግሬ፣ወላይታ ትሁን ጋሞ የሚያውቅ የለም፡፡ በአኩስምና አካባቢው በተገኙ የድንጋይ ላይ ጽሑፎች ነገሥታቱ የሚገዙትን ሀገር ሕዝቦች ስም ይዘረዝራሉ፡፡ እጅግ የሚገርመው ግን ዛሬ በኢትዮጵያ ፖለቲካና የግዛት ይገባኛል ጥያቄ የምንሻኮተው ብዙዎቹ ጎሳዎች/ነገዶች ስማችንየለም፡፡ ሁላችንም ለማለት በሚያስደፍር መልኩ ከተለያየ […]

በአሁኑ ወቅት አገራችን ኢትዮጵያ እጅግ ጥንቃቄ በሚያስፈልገው ጊዜ ትገኛለች፡፡ ሃላፊነት እሚሰማው ተቃዋሚ ፓርቲ እና ለህግ ተገዢ የሆነ ጥበበኛ ገዚ ፓርቲ ትሻለች፡፡ ዛሬ ኢትዮጵያ በብሄር ፍትጫ የተወጠረች እና ልትበጠስ ትንሽ የቀራት ስስ ክር ሆናለች፡፡ አገሪትዋ በአንድ በኩል ኢህኣዴግ እሚባል ላፀደቀው ህግ ደንታ የሌለው ጠበንጃ አምላኪ ጉጅሌ ስትታመስ በሌላ በኩል ደግሞ ኢህኣዴግን በማንኛውም መንገድ ከስልጣን ለማውረድ ብቻ […]

እንደሚታወቀው የኢህአዴግ አገዛዝ ከጊዜ ወደ ጊዜ ጸረ ዲሞክራሲ አካሄዱ እየባሰበት የመጣና መሠረታዊ መብቶችን ሙሉ በሙሉ ሊባል በሚችል መልኩ ማፈኑን አጠናክሮ ቀጥሎበታል፡፡ በቅርቡ በአንድነትና በመኢአድ ፓርቲ ላይ አገዛዙ በሚያዝዛቸው የተቋማት ኃላፊዎች ቀጭን ትዕዛዝ የፓርቲዎቹ ሕልውና ለጥቂት ግለሰቦች ተላልፎ ተሰጥቷል፡፡ ይህ ዓይነቱ ህገ-ወጥ ድርጊት መቼዉም ቢሆን ተቀባይነት አይኖረውም! ለአገራችን የሠላማዊ የስልጣን ሽግግር ከባድ መሠናክል ሊሆን እንደሚችል ሁሉም […]

የካቲት ፲፱(አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በመንግስት የመገናኛ ብዙሃን ውስጥ ተቀጥረው የሚሰሩ ጋዜጠኞች አብዛኞቹ የኢህአዴግ አባላት መሆናቸውን ኢሳት በደረሰው የአባላት ስም ዝርዝርና የስራ ድርሻ ሰነድ ለማረጋገጥ ችሎአል። በቀድሞው ኢቲቪ በአዲሱ አጠራሩ ኢቢሲ እና በኢትዮጵያ ሬዲዮ  ስር የሚሰሩ ዳይሬክተሮች፣ የዜና አዘጋጆች፣ የወቅታዊ ዘገባ አቀናባሪዎች፣ የስፖርት ጋዜጠኞች ፣ የካሜራ ባለሙያዎች፣ ቴክኒሻኖችና የተለያዩ የድጋፍ ሰራተኞች የህወሃት፣ …

የካቲት ፲፱(አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በትግራይ ክልል በብዙ መቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ብር በማውጣት ከአንድ ወር በላይ ሲያከብር የቆየውን የ40ኛ ኣመት የምስረታ በዓሉን የፊታችን እሁድ በአዲስአበባ ሚሌኒየም አዳራሽ በሚያካሂደው ድግስ ለማጠቃለል መዘጋጀቱ ታውቋል፡፡ በዚህ ዝግጅት ላይ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ አምባሳደሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የሚገኙ ሲሆን የዕለቱን የፌሽታ  በዓል …