ከፍተኛ የሐዘን መግለጫ ሰላማዊ ሰልፍ በሞስኮ

70 ሽህ የሚሆን የሞስኮ ነዋሪ በክሬምሊኑ ቤተ-መንግሥት ላይ የሰላ ትችት በማቅረባቸዉ የሚታወቁት የሩስያ መንግሥት ዋንኛ ተቃዋሚ ፖለቲከኛ ቦሪስ ኔምትሶፍ ግድያን በተመለከተ ሐዘኑን በሰልፍ ገለፀ። የሩስያዋ ሁለተኛ ሰፊ ከተማ በሆነችዉ በሳንክት ፒተርስበርግም ቢያንስ 2500 ተቃዋሚ ሰልፈኞች አደባባይ በመዉጣት ሐዘናቸዉን ገልፀዋል።