Source Addis Admass local newspaper addis abeba

Image

ራውዳ ጀማል ትባላለች፡፡ የሃያ ዓመት ወጣት ናት፡፡ ስለራስዋም ሆነ በሳኡዲ ስላሉ ኢትዮጵያውያን ወቅታዊ ሁኔታ ስታወራ እያለቀሰችና እየተወራጨች ነው፡፡ ለማነጋገር ስቀርባት “ወንድ ከሆናችሁ ጋዜጠኞች ነን፣ የህዝብ አፍ ነን ካላችሁ፤ እዚህ ተቀምጣችሁ፣ “ሁለት ሰው ሞተ” እያላችሁ ከምታቅራሩ ሳኡዲ ሂዱና በየቀኑ ሁለት ሶስት ሰው የሚሞትበትን እልቂት ተመልከቱ፣ “ሰዎቹን ምን እየሰራችሁ ነው?” ብላችሁም ጠይቁልን” አለችኝ። መቅረፀ ድምፄን ሶስት አራት ጊዜ ያስጠፋችኝ ቢሆንም በመጨረሻ ግን ለቃለ ምልልስ ፈቃደኛ ሆነችልኝ፡፡
ስንት ዓመት ቆይተሽ መምጣትሽ ነው?
ከሁለት ዓመት በኋላ ነው የመጣሁት፡፡ እስከ አስረኛ ክፍል የተማርኩት አዲስ አበባ ቢሆንም፤ የኮምቦልቻ ልጅ ነኝ፡፡
እንዴት ነበር የሄድሽው?
በፓስፖርት… በኮንትራት ነበር የሄድኩት … ካላስ! የሰውየው ልጆች ግን “የማይሆን” ፊልም ተመልከቺ እያሉ ያስቸግሩኝ ነበር፡፡ ሲመረኝ ጠፍቼ ወጣሁ፡፡ ከዚያም ከጓደኞቼ ጋር በነፃነት ቤት ተከራይተን እየኖርን፣ በ1800 ሪያል ተቀጥሬ መስራት ጀመርኩኝ፡፡ ቤተሰቤንም ገንዘብ እየላኩ እረዳ ነበር፡፡
ወደ አገርሽ እንዴት ተመለስሽ?
ውጡ ሲባል… ረብሻ ሲነሳ.. ጓደኞቻችን ሲሞቱ.. ሲደፈሩብን.. ‘ድሮም ስደተኛ ክብር የለውም’ ብዬ ተመልሼ መጣሁ..ከሚገሉኝ ከሚያበለሻሹኝ ብዬ እጄን ሰጠሁ፡፡ ብዙ ኢትዮጵውያኖች ችግር ላይ ናቸው.. እባካችሁ ድረሱላቸው፡፡ ብርዱም ፀሃዩም ሲፈራረቅባቸው.. ያሳዝናሉ፡፡ ብዙ ያልመጡ አሉ፤ መምጣት እየፈለጉ፡፡ ስቃይ ላይ ናቸው፡፡ እኔ አሁን አስራ ሶስት ቀን ታስሬ ነው የመጣሁት፡፡ እስቲ ስለ እስሩ ንገሪኝ … ሁለት ቀን ያለ ምግብ ያለ ውሃ ነው የታሰርነው። ከዛ በኋላ ግን ጥሩ ምግብ ሰጥተውናል፣ ጥሩ መኝታም አግኝተናል፡፡ ብዙዎቹ ግን ከእኛ የባሰ ችግር ላይ ናቸው፡፡ መጠለያ ያላገኙ አሉ… ኤምባሲያችንም አይሰማም እንጂ ስንት ጊዜ ደውለን ተናግረናል መሰለሽ፡፡ ግን የሚሰማ የለም፡፡ ከአገራችን ውጡ ካሉ በኋላ ትዕግስት ያጡና መልሰው ይዩዙናል፡፡ በዛን ጊዜ አበሻው፣ ሻንዛ/ጩቤ ይመዛል፡፡ ፖሊስ ራሱን ለማዳን ይተኩሳል። እኔ እንደውም ደህና ነኝ፤ እዛ ላሉት ድረሱላቸው። በምድረ ዱርዬ እየተደፈሩ ነው ያሉት /ለቅሶ/ ስንት ህፃናት አሉ የሚሞቱ፣ የሚታመሙ፡፡ ስንመጣ ደሞ፤ ሻንጣ አትያዙ ተብለን ተመናጭቀን…በጥፊ ተመትተን..መከራችንን በልተናል፡፡
ወንዶችና ሴቶች ለብቻ ነበር የተቀመጣችሁት?
የተቀመጣችሁት አትበይ! የታሰራችሁት በይ፡፡ … የሴት እስር ቤት ለብቻው ነው በሴቶችና በህፃናት ለቅሶ የተሞላ ነው፡፡ እኔ ራሴ ስድስት ያበዱ ሴቶችን ይዤ መጥቻለሁ…/ለቅሶ/
አሁን ቤተሰብ እየጠበቅሽ ነው?
ነበረ ግን ሻንጣዬ ጠፋብኝ፡፡ በርግጥ ጤነኛ ሆኖ መምጣትም ቀላል አይደለም፡፡ እዛ ያሉትን ጥለናቸው ስንመጣ እያለቀስን ነው፡፡ እስር ቤቱ ውስጥ አንድ እርጉዝ ሞታብናለች፡፡ እዛው እስር ቤት እያለን ምጥዋ መጣ፤ ግን የህክምና እርዳታ ባለማግኘትዋ ሞተች፡፡
እስር ቤት ያሉት ምን ያህል ይሆናሉ?
ሰማኒያ ክፍል አለ..በየክፍሉ ስልሳ አምስት ስልሳ አምስት ሰው ነው ያለው፡፡ መካሲመሺ እስር ቤት ይባላል፡፡ የወንድና የሴት እስር ቤት የተራራቀ ነው፡፡ በጣም ረጅም ከመሆኑ የተነሳ በመኪና እንጂ በእግር አይሞከርም፡፡ በአሁኑ ሰዓት በከተማው ያለው እስር ቤት ሞልቶ የመዝናኛና የስብሰባ አዳራሹን ሁሉ እስር
ቤት አድርገውታል፡፡ የተደፈሩት የሞቱት..ሴቶች ብዙ ናቸው፡፡ አንዷን እርጉዝ ለሶስት ሲደፍሯት ሞታለች፡፡
የሌሎች አገር ስደተኞችም እየወጡ ነው ተብሏል…
አዎ፡፡ ኢትዮጵያዊው ከበደሉ ብዛት የተነሳ እየተናነቀው እኮ ነው ግጭቱ የሚከረው፡፡
ሚስቱን እህቱን ከእጁ መንትፈው ሊወስዱበት ሲሉ ነው ጦርነት የሚነሳው፡፡ አበሻ ወንድ እየሞተ ያለው ‹‹ሴቶቻችንን አትንኩብን..›› ስለሚል እኮ ነው፡፡ ኤምባሲው ሊደርስላቸው ይገባል፡፡
አዲስ አድማስ ጋዜጣ

Written By: Kassahun Addis


The regime in Addis Ababa and its diplomatic missions around the globe spend more time bedeviling members of the Diaspora opposed to the lack of democracy in Ethiopia. While they should be working to promote the interest and safety of citizens abroad, they spend resources spying on individuals, dividing communities and fundraising. This is on top of unofficial import export business most embassy officials are engaged in.

The original picture

The photoshopped picture in the tigraionline.com article
This short piece is to put further light on how low these embassies go to achieve their goals. A picture caption of a story published on Tigraionline.com by the Public Relation head, Tsehaye Debalkew, of the embassy ask “What evidence do you want more than a picture?” (See the article written by Ato Tsehaye, an official working for Ethiopian embassy in DC, USA )

How far will the Ethiopian Embassy in Washington DC go to taint everyone opposed to the systemic and gross violation of basic human rights in the country as hate mongers, Eritrea loving, power mongers? Well, the answer is they will use basic paint program from their desktop and do amateurish Photoshop of pictures showing Ethiopians rallying against the Saudi abuse of their fellow country men and women.

Ato Tsehaye Debalkew accuses what he calls the “few Diaspora” of “character assassination.” The irony is that he, and the office he represents, manipulated a picture, or used manipulated picture, to assassinate the characters of the “few Diaspora” Then to add insult to our intelligence, he captioned it “What evidence do you want more than a picture?”

I wouldn’t have been surprised if sharing of this fake picture was only circulated in social media. Apparently there were already 50+ shares of this picture. Well, that is unregulated sphere and anyone can do anything. But coming from an official, spokesperson, of the embassy and carried by tigraionline, a semi official website, I felt obliged to put this together.

ምንሊክ ሳልሳዊ :-በወያኔ የመከላከያ ሰራዊት ውስጥ ውጥረት መፈተሩን ከውስጥ አዋቂ ምንጮች ተሰምቷል:: በወታደራዊ ጥቅማ ጥቅም እና በህገመንግሥቱ ዙሪአ ለተነሱ ጥያቄዎች መልስ የሚሰጥ አካል መጥፋቱ እና ዝም መባሉ ዉስጥ ውስጡን እየተብላላ ያለው የመኮንኖቹ ጥያቄ እንዳይፈነዳ የተሰጋ ሲሆን ከፈነዳ ሰራዊት ለሶስት ቦታ እንደሚከፈል ለምንሊክ ሳልሳዊ ምንጮቹ ጠቁመዋል::

መኮንኖቹ በትምህርት በስራ እና በማእረግ እድገት በቤተሰብ እንክብካቤ በደሞዝ ጭማሪ እና በሕገመንግስታዊ የህዝብ መብቶች ዙሪያ ጥያቄ ያነሱ ሲሆን ወታደራዊ ጥቅማ ጥቅሞች ለአንድ ብሄር አባላት ብቻ ተመድበው እየተሰራባቸው ነው ከተማ ውስጥ ታጥቀው የመሸጉ እና ህዝብን እያጠቁ የሚገኙት የአንድ ብሄር አባላት ናቸው እንዱሁም ከሃገራዊ ጥቅም ይልቅ የፓርቲ ጥቅም እየተስተዋለ ነው:ወታደሩ የጦር ሳይንስን እና ዲሲፕሊን በጎደለው መልኩ እየተስተዳደረ ነው በሰራዊቱ እና በሃገሪቱ ሁሉ ወቅታዊ ጉዳዮችን ሽፋን እና ማዘናጊያ በማድረግ የሙስና እና የዘረፋ መስፋፋት መልስ ሊያገኝ ይገባዋል ጄኔራል መኮንኖች አላቸው የተባለው ንብረት ይጣራ በሃገሪቱ የፖለቲካዊ እና የኢኮኖሚ ጥያቄዎች ሊመለሱ ይገባል የሚሉ እና ተመሳሳይነት ያላቸውን ጥያቄዎች ማንሳታቸው ታውቋል::የመከላከያ አባላቱ በኑሮ ውድነት እና በተቃዋሚዎች ህገመንግስታዊ መብቶች ላይ ያነሱት ጥያቄ አዛዦቹን ያስደነገጠ ከመሆኑም በላይ በአንድ ብሄር ላይ የተመሰረተ አስተዳደር እስከመቼ የሚለውም ጥያቄ መመለስ አለበት በሚል የእግር እሳት እየሆነባቸው ነው::

ይህ ከዚህ ቀደም የተጀመረው እና አሁንም በሰሜን እዝ እና በምስራቅ እዝ የተከሰተው የሰራዊቱ ህገመንግስታዊ ጥያቄ እና የጥቅማ ጥቅም አቤቱታ በመላው ሃገሪቱ ተስፋፍቶ በሁሉም የሰራዊት እዞች ውስጥ ጥያቄው መነሳቱን ምንጮቹ አመልክተዋል::በተለያዩ ጊዜያት እየተንከባለለ የመጣው ይህ የሰራዊቱ አቤቱታ እጅግ አደገኛ አዝማሚያ እያሳየ ሲሆን በዘረኝነት ላይ የተመሰረተ አስተዳደር እንዲወገድ እና ህገመንግስታዊ መብቶች እንዲከበሩ ጥያቄዎች ገፍተው መምጣታቸው ሲታወቅ ከፍተኛ የሕወሓት ጄኔራሎች በየቀኑ ካለማቋረጥ ምስጢራዊ ስብሰባዎችን እያደረጉ ከመሆኑም በላይ ከየእዙ የሚመጣላቸው ሪፖርት መፍታት የሚቻልበትን ጉዳይ እየተወያየ መሆናቸውን ከዚህ ቀደም ምንጮቹ ገልጸው ነበር::

ሌ/ጄ ሳሞራ የኑስ ጡረታ ወቶ በምትኩ የብኣዴን ሜ/ጄ አበባው ይተካሉ ሲባል ወያኔ በድንገት የመለስ የቅርብ ሰው የነበሩትን እና በአንድ ወቅት የአማር ክልል አቶ አያሌው ጎበዜን ላንቻ አከባቢ በመኖሪያ ቤታቸው ለ3 ወር አግተው ሲያሰቃዩ የነበሩት ሌ/ጄ ዮሃንስ ገብረመስቀልን በማእረግ ሾሞ ሳሞራ የኑስን ለመተካት የሚያደርገውን ሩጫ የብኣዴን አባላት መቃወማቸውን ተከትሎ ጄኔራል አባባውን ጨምሮ የብኣዴን መኮንኖችን ያገለለ የሕወሃት አባላት የሆኑ ጄኔራሎች ብቻ የተሳተፉበት በትግሪኛ የተመራ ስብሰባ መደረጉን ውስጥ አዋቂ ምንጮቹ ተናግረዋል::በስብሰባው ላይ ቀሪ ከፍተኛ ባለማእረግ መኮንኖች እና የመምሪያ ሃላፊዎች ለምን አልተሳተፉም የሚል ጥያቄ ከአንድ ስማቸው ካልተጠቀሰ ብርጋዴር ጄኔራል መነሳቱን ምንሊክ ሳልሳዊ ምንጮቹ ጠቁመዋል::

ይህ ስብሰባ ዋና አትኩሮቱ የነበረው በብሄር አደና ላይ ሲሆን እንደ ምንጮቹ መረጃ በአማራ እና በኦሮሞ መኮንኖች እየተመራ ያለውን የለውጥ ጥያቄ በማክሸፉ ዙሪያ እንደነበር እና አሁንም በስፋት የሕወሓትን የፓርቲ አቋም የሚቀበሉ እና የጥቅም ተጋሪ የሆኑ ሰዎችን ለመሾም የታቀደ ሲሆን እንዲሁም ከፖለስ ሰራዊት በከፍተኛ የማእረግ ሹመት ወደ ጦር ሰራዊቱ ለማምጣት የታሰበ ሲሆን በወታደራዊ ደህንነት ዙሪያ ሌላ ተጨማሪ ሰልጣኞችን ከፖሊስ ወስዶ በማሰልጠን ወደ ሰራዊት ማዘዋወር የሚሉ ውይይቶች ተካሂደውበታል:: አሁንም ስብሰባው የቀጠለ ሲሆን ተጨማሪ መረጃዎችን እንለቃለን::

በአፍሪቃ በእስራት የሚፈለጉት እና በወቅቱ በማዕከላይ አፍሪቃ ሬፓብሊክ ተሸሽገው የሚገኙት የዩጋንዳ ዓማፅያን ቡድን፣ በምህፃሩ የሎርድ ሬዚስተንስ አሚ፣ « ኤል አር ኤ » መሪ ጆሴፍ ኮኒ እጃቸውን ለመስጠት በማሰላሰል ላይ መሆናቸው ተሰማ።

Image

በሳውዲ አረቢያ በሚገኙ ወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለው መጠን የለሽ የመብት ጥሰት ለመቃወም በተለያዩ የዓለም አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን በየአገራቱ የሚገኙ የሳውዲን ኢምባሲዎችን በተቃውሞ እያጨናነቁ ነው። በወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ባለው ዘግኛኝ በደል የተሰማቸውን ጥልቅ የመጠቃት ስሜት ኢትዮጵያን በተቃውሞ ሰልፎቹ ላይ በሚያሰሟቸው መሪር የሐዘን እንጉሮችና የቁጭት ንግግሮች እየገለፁ ነው። ከሐዘንና ቁጭት ባለፈም ለበደል ለተጋለጡ ወገኖቻችን አስቸኳይ ሰብዓዊ ርዳታ ለማድረስ እና የዲፕሎማሲ ድጋፍን ለማሰባሰብ ዓለም ዓቀፍ ግብረ ኃይል ተቋቁሞ ሥራውን ጀምሯል።

ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ይህንን ዓለም ዓቀፍ ጥረት ለመደገፍ በውጭ አገራት የሚገኙ አባላቱ ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ መመሪያ አስተላልፏል።

ይህ ሁሉ በውጭ አገራት እየተደረገ ያለ ጥረት ነው። ኢትዮጵያዊያን ባሉበት አገራትና ከተማዎች ሁሉ በዚህ ጉዳይ ላይ በአንድነት መንቀሳቀሳቸው የሚያስደስት ነገር ነው። ሌላው ቀርቶ በሳዉዲ ዋና ከተማ ሪያድ ውስጥ እንኳን ኢትዮጵያውያን የሳውዲን መንግሥት ተቃውመው ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተዋል።

የሳውዲ መንግሥት በኢትዮጵያ ስደተኞች ላይ የያዘውን ጨካኝ አቋም እና በመንግሥት እውቅና በወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን በደል መቃወም ያልተቻለው በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ!!! ይህ እጅግ ያማል፣ ልብን ያደማል።

ወያኔ የሳውዲ የንግድ ሸሪኮቹን ለማስደሰት የፈንሳይን ግማሽ የሚያህል ለም መሬት በነፃ መስጠቱ በቂ አልመሰለውም። በአገራቸው ኢትዮጵያዊያንን ሲጨፈጭፉ፣ ሲገሉና ሲደፍሩ በቸልታ መመልከቱ በቂ የወዳጅነት ስጦታ መስሎ አልተሰማውም። እናም ሸሪኮቹ የበለጠ እንዲደሰቱና ከእስከዛሬ በበለጠ ገንዘብ እንዲደጉሙት ለማበረታታት አዲስ አበባ በሚገኘው ኤምባሲያቸው ፊት ለፊት ኢትዮጵያንን ደበደበላቸው።

ወያኔ ከሳውዲ ጋር ያለው ግኑኝነት “የቢዝነስ ሽርክና” ነው። ቢዝነሱም ኢትዮጵያዊያንን በቁማቸው መሸጥንም ያጠቃልላል። የወያኔ ሹማምንት እና የሳውዲም ቱጃሮች በዘመናዊ ባርነት ንግድ ውስጥ አቀባይና ተቀባይ ናቸው። ለዚህም ነው እየተነገደበት ያለው ምስኪን ኢትዮጵያዊ እጣ ፈንታ በአዲስ አበባና በሪያድ አንድ ዓይነት የሆነው። እዛ ዱላ፤ እዚህም ዱላ። እዛ እስር፤ እዚህም እስር። እዚያ ስድብ፤ እዚህም ስድብ። እዚያ ቶርቸር፤ እዚህም ቶርቸር። በባርያ ንግድ ውስጥ አቀባዩም ተቀባዩም ባርያዉን መግዛታቸው፣ መስበራቸው፣ መግደላቸው የማይቀር መሆኑ የታወቀ ነው።

ሌላው አሳዛኝ ጉዳይ ደግሞ የወያኔ ድኩማን ሹማምንት የሚሰጡት አስተያየት መስማት ነው። በሳውዲ ለሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ፍትህ ለመጠየቅ በመላው ዓለም እና በአዲስ አበባ ደግሞ በሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪነት ወደ ጎዳና በወጡ ኢትዮጵያዊያን የኮሚኒኬሽን ሚኒስትር ተብየው “የፋሺሽት መፈክር አንግቦ በተጎሳቆሉ ዜጎች ስም የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት መጣር ብሎም መንግሥት በዜጎቹ ግዴለሽ እንደሆነ አስመስሎ ማቅረብ” ሲል ተሳልቋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ተብየው ጨምሮ ሁሉም የወያኔ ሹማምንት “ሳውዲዎች በግዛታቸው ውስጥ ያሻቸውን የማድረግ “ሉዓላዊ” መብት አላቸው፤ መንግሥታችን የሳውዲ አረቢያን ሉዓላዊ መብት ያከብራል” እያሉ ይከራከራሉ። ለመሆኑ ይህንን የሚሉት ከልባቸው ነው? ፈጽሞ። ኢትዮጵያዊያንን ማሰቃየትና መግደል የቢዝነሳቸው አካል ስለሆነ ነው እንጂ የሉዓላዊነት ትርጉም ይህን ያህል ተምታቶባቸው አይደለም።

ሰብዓዊ መብቶች አገር፣ ድንበር፣ ዜግነት፣ ወይም ሌላ ማናቸው ሰው ሠራሽ ህግጋት ሊጥሷቸው እንደማይገቡ የወያኔ ሹማምንት ቢያንስ ሲነገር ሰምተው ያውቃሉ። ማንኛውም ሰው ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ መገደል፤ ሰቆቃ (ቶርቸር) እንዲደርስበት ማድረግ፤ ጾታዊ ጥቃት እንዲደርስበት ማድረግ እንደማይቻል ሰምተው ያውቃሉ። ሰብዓዊ መብቶች ሰዎች ሰው በመሆናቸው ብቻ ሊያገኙት የሚገባ ክብር መሆኑ በተሳተፉባቸው በርካታ ዎርክ ሾፖች ሰምተዋል። ያም ሆኖ ግን በዘመናዊው ዓለም እንስሳ እንኳን ያገኘውን ክብር ኢትዮጵያዊያን ተነፍገው በሪያድ ጎዳናዎች ሲታረዱ፤ በጭካኔ ሲደበደቡና ሲገረፉ፤ ሴቶች ሲደፈሩ፤ ሕፃናት በረሀብና በእርዛት ሲቀጡ የወያኔ ባለሥልጣኖች የበዳዮች አፈቀላጤ ሆነው የሚከራከሩት በዳዮቹ ሸሪኮቻቸው ስለሆኑ ነው።

ይህ ድርጊት በወያኔ እየደረሰብን ያለው በደል ምን ያህል ሥር የሰደደ እንደሆነ እና የኢትዮጵያዊያን ሰቆቃ ምንጭ የት እንዳለ አመላካች ሆኗል።

“ትግላችን የነፃነት ትግል ነው” ስንል “ከማን ነፃ ለመውጣት?” እያሉ የሚሳለቁ እንደነበሩና እንዳሉም ይታወቃል። በወያኔ አገዛዝ ኢትዮጵያዊያን ወደ ባርነት ማሽቆልቆላቸው ይህ ተጨባጭ ማስረጃ ነው። ከወያኔ የባርነት አገዛዝ ነፃ እስካልወጣን ድረስ ሌሎች አገሮች መብቶቻችን የሚያከብሩልን በየአገራቱ ልምድ እና ከወያኔ ጋር ባላቸው ሽርክና መጠን ነው።

ለሳውዲ መንግሥትና ቱጃሮቹ ከነዳጅ ቀጥሎ የሀብታቸው ምንጭ ከየአገሩ የሚመጣላቸው የድሀ ጉልበት ነው። የሳውዲ ቱጃሮች ድሆችን ከባርነት ባልተሻለ መንገድ ረግጠው በመግዛት ኑሮዓቸውን ያደለቡ ናቸው። ለወያኔ አገዛዝ ደግሞ ከቡና ቀጥሎ ከፍተኛው የገቢ ምንጩ ዜጎቹን በመሸጥ የሚሰበስበው ነው። ለወያኔ፣ ኢትዮጵያዊያን ወንዶችና ሴቶች ትርፍ አምጪ ሸቀጦች ናቸው። ወያኔና ሳውዲ – ሻጭና ገዢ ናቸው።

ባርያ ከሻጩ ነፃ ሳይወጣ ከአንድ ገዢ ነፃ ቢወጣ ሌላ ገዢ ስለሚመጣ ዘለቄታነት የለውም። እኛም ከወያኔ ነፃ ሳንወጣ ከሳውዲ ነፃ መወጣት አይቻለንም፤ ቢቻልም ነፃነታችን ዘላቂነት አይኖረውም።

ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በሳዉዲ አረቢያ በሚገኙ ወገኖቻችን ላይ በሚደርሰው ጥቃት ክፉኛ ተቆጥቷል። በዚህ የመከራና ጭንቅ ሰዓት ለወገኖቻችን ለመድረስ የሚቻለውን ጥረት ሁሉ ማድረግ እንዳለብን ያምናል። አባላቱ በነብስ አድን ርብርብ በግንባር ቀደምትነት እንዲሳተፉ መመሪያ አስተላልፏል። ይህ አጣዳፊ ሆኖም ጊዜዓዊ መፍትሔ ነው። በግንቦት 7 እምነት የችግሮቻችን ሰንኮፍ ያለው አዲስ አበባ ነው። ሰንኮፉን ሳንነቅል የሚደርስብንን ውርደት በዘላቂነት መቀልበስ አንችልም። ስለሆነም በችግር ላይ የወደቁትን ወገኖቻችን እየረዳን፤ የችግሮቻችን ምንጭ በሆነው ወያኔ ላይ የተባበረ ክንዳችንን እናንሳ ይላል።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

የጋራ ላይ ፉጨት!!
//ደመቀ ከበደ – ጣና ዳር//

‹‹ሀበሽ አባ ደፋር – አባ ሰው አይፈሬ
ጫማ የለም ከእግሩ – ተሰርቶ ጎፈሬ፤
ሀበሽ አባ ሞጋች – አባ ጎበዝ ጤፉ
ጋራ ላይ ያቅራራል – በጎቹ ሲጠፉ››
የሚሉት ቀረርቶ – የሚሉት ሽለላ
ስንት ወንድ ገደለ – ስንት ጎበዝ በላ፤
‹‹ደፋር ነው እያሉ – ጀግና ነው እያሉ
የሞት ሞቱን ሲሞት – ዳር ቆመው ያያሉ፤
ተውት ይሄን ሶታ – ይሄንን ጠንበለል
ጀግና ነህ አትበሉት – እንዲያው ይንጎማለል፤››
የሚሉት የእናት ወግ – የአባት ማስፈራሪያ
ስንት ወንድ አከሸፈ – እንደ ዘመን ድሪያ፤

እኔ ግን እላለሁ፤
ተውት ይኸን ጀግና – ይውጣ ወደ ጋራ
ይሸልል ይፎክር – እንዳሻው ያቅራራ
እንዳሻው ‹‹ቡ!›› ይበል – ያሻውን ይጣራ
ሰው እንዴት ይኖራል – እያየ መከራ!!

Image


በዚህ 20 አመት ውስጥ ለኢትዮጵያውያን የማይወጣ ዳገት የሆነው የኢህአዴግ ስርዓት ብቻ አይደለም፡፡ የተቃዋሚዎች መጠላለፍም ህዝብን ተስፋ ሲያስቆርጥ ኖሯል፡፡ እንዲያውም ተቃዋሚ ፓርቲዎች ገዥውን ለመቃወም ከሚያደርጉት በላይ እርስ በእርስ ለመጠላለፍ በርካታ ጊዜያቸውን የሚያጠፉ ሆነዋል፡፡

Image
ሰሞኑን ፌስ ቡክ ላይም የምናነበው ይህን መጠላለፍ ነው፡፡ ሳውዲ ውስጥ ዜጎቻችን ሰቆቃ እየደረሰባቸው ባለው ወቅት ሳይቀር ተቃዋሚዎች እርስ በእርሳቸው ይናቆራሉ፡፡ ምንም እንኳ ጭቅጭቁ ፌስ ቡክ ላይ ቢሆንም የፓርቲዎቹን አቋም ግን የሚያንጸባርቅ ሆኖ አግኝቸዋለሁ፡፡ የሚያስገርመው ደግሞ የሚናቆሩት ይህ ነው የሚባል የፖሊሲም ሆነ ሌላ የሚያጨቃጭቅ ልዩነት ያላቸው ፓርቲዎች አለመሆናቸው ነው፡፡
ተጨቃጫቂዎቹ የዚህ ትውልድ ወጣቶች መሆናቸው ደግሞ ይበልጡን ያስገርማል፡፡ አብዛኛዎቹ ደግሞ ሁለቱ ፓርቲዎች የተቀራመቷቸው የባለ ራዕይ ወጣቶች አባላት የነበሩ ናቸው፡፡ በእድሜ ከገፉት ፖለቲከኞች ይልቅ ወጣቶች ከመግባባትም አልፎ ሁለቱን ፓርቲዎች ማቀራረብ ነበረባቸው፡፡ የአንድነት አባላት ሰማያዊ ፓርቲ ያደረገውን ሰልፍ ሲነቅፉ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ደግሞ አንድነት መንግስትን ገፍቶ መሄድ እንዳልቻለ ይተቹታል፡፡ መተቻቸት አንድ ነገር ነበር፡፡ ሆኖም በሁለቱ አባላት መካከል የሚደረገው እሰጣ ገባ ከምክንያታዊነት ይልቅ በመጠላለፍ ላይ የተመሰረተ መሆኑ ነው፡፡ አንዳንዴ ደግሞ ጭራሹን ጥላቻም ይታከልበታል፡፡ ከአሁኑ ካድሬያዊ ባህሪም ይታይበታል፡፡
እንደ እውነት ከሆነ ሁለቱ ፓርቲዎች አብረው ሰላማዊ ሰልፍ መውጣት ነበረባቸው፡፡ ሆኖም በመካከላቸው ባለው የመጠላለፍና የመጠላላት ችግር ለየብቻቸው አድርገውታል፡፡ አንድነት ደግሞ ጭራሹን አልቻለም፡፡ በሰላማዊ ሰልፉ ላይ አንድነትና ሰማያዊ ክፍተቶች ታይቶባቸው ይሆናል፡፡ ግን እነዚህ ክፍተቶች ኢህአዴግ የፈጸመውን በደል እያለ ሁለቱን መነታረክ አልነበረባቸውም፡፡ ሰላማዊ ሰልፍ የመጨረሻው አይደለም፡፡ ሁለቱ ፓርቲዎች (ወጣቶቻቸውም) ሌሎች በርካታ ትግሎች ይጠብቃቸዋል፡፡ ባለፈው የታየውን ስህተት በሚቀጥሉት ማረም ይችሉ ነበር፡፡ አሁን የሚታየው ግን አንዱ የሌላውን ስህተት ሲያገን፣ አንዱ ውድቀቱን በሌላው ላይ ሲያላክክ፣ አሊያም በማይተቸው ሲተች ነው፡፡
በበኩሌ ‹‹ተባበሩ አሊያም ተሰባበሩ›› የሚለው መርህ አይመቸኝም፡፡ ቢያንስ ለገዥው ባለመተባበር ላይ ግን መተባበር የግድ ይላቸዋል፡፡ እርስ በእርሳቸው ሲናቆሩ ተስፋ የሚያስቆርጡት፣ የሚያስገዙት ህዝብን ነው፡፡ ከ97 በኋላ የተፈጠረው መከፋፈል፣ መናቆርና መጠራጠር በርካታ ዋጋ አስከፍሎናል፡፡ የፓርቲዎቹ አባላት ደግሞ ቀዳሚ ተጠቂዎች ናቸው፡፡ እናም መጠላለፉ ለገዥው ካልሆነ በስተቀር ለማንም የሚጠቅም አይደለም፡፡ ሀሳብን በነጻነት መናገር አንድ ነገር ነው፡፡ የሀሳቡን ጥቅምና ጉዳት ሳይመዝኑ መዘላለፍ፣ መናቆር ግን ፖለቲካችን በብስለት ላይ ያልተመሰረተ ለመሆኑ አመላካች ነው፡፡
በሚያስማማቸው መተባበር ቢችሉ መልካም ነገር ነው፡፡ መተባበር ባይችሉ እንኳን አንዱ ሌላውን ባለመጥለፍ ቢተባበር መልካም ይመስለኛል፡፡ አይደለም በአሁኑ ዘመን ፖለቲካ በ1970ዎቹ ታጣቂዎች ለገዥዎች ክፍተት ላለመፍጠር ልዩነታቸውን በሰላም ፈትተዋል፡፡ ሳይግባቡ ሲቀሩ እርስ በእስር ላለመጠላለፍ ጥረት አድርገዋል፡፡ ይህ እንዴት በዚህ ዘመን ያቅታል?
የፓርቲዎች ድክመት ለፖለቲካ ትግሉ እንቅፋት እየሆነ ነው ከተባለ እንኳ ችግሩ መፈታት ያለበት በመጠላለፍ አይደለም፡፡ በሰከነ መንገድ ተወያይቶ መፍታት፣ ተነጋግሮ መግባባት ካልተቻ የየራሱን ትግል አጠናክሮ ትክክለኝነቱን በማሳየት የሌላው መንገድ ስህተት መሆኑን ማሳየት ይገባል፡፡
በአሁኑ ወቅት ተግባራዊ እንቅስቃሴ እያደረጉ የሚገኙት እነዚህ ሁለቱ ፓርቲዎች ናቸው፡፡ ኢህአዴግን መቃወም ብቻ ለውጥ ሊያመጣ አይችልም፡፡ ህዝብ ተቃዋሚዎች የትግሉ ዳገት ላይ ሲደርሱ እርስ በእስር ተጓትተው እንደገና ተስፋ እንደማያስቆርጡት፣ ዋጋ እንደማያስከፍሉት፣ እንደገና ተከፋፍለው እንደማያስገዙት ካወቀ ብቻ ነው ሊከተላቸው የሚችለው፡፡ እንዲያው ቢከተላቸው እንኳ እነዚህን ስህተቶች ላለመድገም መዘጋጀት ይሆርባቸዋል፡፡ ከሁለቱም ፓርቲዎች አባል ባልሆንም ለመጠጋት ስሞክር ይች መጠላለፋቸው እምነት አሳጥጣ እንደገና ትገፈትረኛለች፡፡ ይህ ለሌሎችም ተመሳሳይ ይመስለኛል፡፡ ህዝብ ትግሉን በሙሉ ልብ ለመቃለቀል የሚፈራውም በዚህ ምክንያት ነው፡፡
በቅርብ ጊዜያት እንደምናየው መጠላለፍ ከሆነ አሁን የሚጠላለፉት ፓርቲዎች መካከል አንዱ ስልጣን ቢይዝ ከኢህአዴግ ባልተነሰነሰ ሌላኛውን ለማፈን ወደኋላ እንደማይል ነው፡፡ መሳሪያ ቢኖራቸው ደግሞ ተጨፋጭፈዋል፡፡ ህዝብ ተቃዋሚን የሚደግፈው ገዥውን ስለሚቃወም ብቻ ሳይሆን ገዥው የፈጠሩትን ስህተት የማይደግሙ ከሆኑ ብቻ ነው፡፡
ብዙውን ጊዜ ‹‹ብሄራዊ እርቅ›› ሲወራ በኢህአዴግና በተቃዋሚዎች መካከል ስላለው አለመግባባት ነው የሚወራው፡፡ ኢህአዴግ ለብሄራዊ መግባባትም ሆነ ለሌሎች ጉዳዮች እጁን ያልሰጠው ተቃዋሚዎች መካከል ባለው መጠላለፍ ነው፡፡ እውነቱን ለመናገር ይህ የተቃዋሚዎች መጠላለፍ ኢህአዴግ አጋር ፓርቲዎች ከሚሰሩለት በላይ ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቶለታል፡፡ ስለሆነም ከገዥው ጋር ከሚደረገው ትግል ቀድሞ ተቃዋሚዎች እርቅ፣ መግባባት…ብቻ ትግሉን ወደኋላ ከመጎተት የሚታደግ አንዳች መፍትሄ ያስፈልጋቸዋል፡፡ ካልሆነ ግን እንደተለመደው በትኩሳትና ሰሞነኛ ፖለቲካ ዳገቱ ላይ ደርሶ እርስ በእርስ ተከፋፍሎ፣ ህዝብን ተስፋ አስቆርጦ፣ ገዥዎችን አጠናክሮ ከመመለስ ያለፈ ውጤት ጠብ ሊል አይችልም፡፡ ይህ ደግሞ ትውልዱን ለማይወጣው ተገዥነት አሳልፎ ይሰጠዋል፡፡

ህዳር ፲፫(አስራ ሦስት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሳዑዲ ዓረቢያ ኢትዮጵያዊያን በአስከፊ ሁኔታ እንዲባረሩ ከተደረገ በኃላ  መንግስት በሳዑዲ ስፖንሰርነት ያጓጓዛቸውን ከ10ሺ በላይ ተመላሾች በካድሬዎች ማሰልጠኛ በሆነው የሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በማሳረፍ ባለሃብቶች እንዲረዱዋቸው በመማጸን ላይ ነው። የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ለተመላሾቹ ማቋቋሚያ መንግስት 50 ሚሊየን ብር  መመደቡን፣ ገንዘቡ ሊያድግ እንደሚችልና በማቋቋም ረገድ ችግር እንደሌለ …

ህዳር ፲፫(አስራ ሦስት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአዲስ አበባ መስተዳድር ትናንትና ዛሬ በቡራዩ አካባቢ ከ1 ሺ ያላነሱ ቤቶችን ማፍረሱን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል። ነዋሪዎች እንደሚናገሩት መስተዳድሩ ምንም አይነት መጠለያ ሳያዘጋጅ እና ማስጠንቀቂያ ሳይሰጥ እስከ ሙሉ የቤት እቃዎቻቸው ቤቶቻቸውን በድንገት በማፍረሱ ከፍተኛ ችግር ላይ ወድቀዋል። አለማየሁ የተባለ አንድ ወጣት የወላጆቹ ቤት ሲፈርስ በማየቱ ስሜቱን መቆጣጠር ተስኖት፣ …

ህዳር ፲፫(አስራ ሦስት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዩኒሴፍ ባወጣው ሪፖርት እንደማለከተው ይህን ችግር ለመቅረፍ የኮሚኒቲ አስተባባሪዎች ከፍተኛ  ሚና መጫወት አለባቸው። ኤርትራ ውጭ ላይ መጸዳዳትን በማስቀረት ከፍተኛ ድል ማስመዝገቡዋን ዩኒሴፍ ጠቅሷል። በመላው ኤርትራ ውጤታማ ስራ በመሰራቱ አገሪቱ ውጭ ላይ መጸዳዳትን ያስቆመች አገር የሚል ሰርተፊኬት እንደሚሰጣት ድርጅቱ ገልጿል። በአለም ላይ 34 በመቶ የሚሆኑ ዜጎች ንጹህ የመጸዳጃ …

ጀርመን እንድትቀበላቸው ያመለከቱ ተገን ጠያቂዎች ማመልከቻቸው ተቀባይነት እስኪያገኝ ረዥም ጊዜ በሚወስድ ሂደት ውስጥ ማለፍ አለባቸው ። ጉዳዩ የሚመለከታቸው የፌደራል ጀርመን የውጭ ዜጎችና የስደተኞች ጉዳይ መስሪያ ቤት ባልደረቦች አመልካቾቹን ስለ ሃገራቸው ሁኔታ ና የፖለቲካ ክትትል ይደረግባቸው እንደሆነ ይጠይቋቸዋል ።

እጨጌ ዕንባቆም የመናዊ
ልዩ መርሐ ግብር በደብረ አሚን ተክለ ሃይማኖት(መርካቶ) አዳራሽ

                                 ቀን –  ኅዳር 22 ቀን 2006 ዓም

                                 ሰዓት-  ከቀኑ በ8 ሰዓት


                               የመግቢያ ካርዱን ይውሰዱ


  • ከየመን በ16ኛው መክዘ መጥቶ የደብረ ሊባኖስ አበ ምኔት ስለሆነውና አያሌ መጻሕፍትን ስለደረሰውና ስለተረጎመው እጨጌ ዕንባቆም የመናዊ ልዩ ዝግጅት በተለያዩ ሊቃውንትና ምሁራን ይቀርባል

  • በመርሐ ግብሩ ላይ ለመሳተፍ የመግቢያ ካርዱን 
  • ለም ሆቴል ማትያስ ሕንጻ ከሚገኘው አግዮስ መጻሕፍት መደብር፣ 
  • ከደብረ አሚን ተክለ ሃይማኖት(መርካቶ) ሰንበት ትምህርት ቤት ጽ/ቤት እና 
  • ከማኅበረ ቅዱሳን ጽ/ቤት ፊት ለፊት ከሚገኙ የመጻሕፍት ማከፋፈያ ሱቆች(የአርከበ ሱቆች) ማግኘት ይችላሉ፡፡
  • አስቀድመው የመግቢያ ካርዱን በመውሰድ አብረን ሊቃውንቱን እናስብ
አዘጋጆች

  • ምክሐ ደናግል ሰንበት ትምህርት ቤትና ዲያቆን ዳንኤል ክብረት

ሕጋዊ ፈቃድ በሌላቸው ኢትዮጵያውን ላይ የሚደርሰውን ችግር እና ጥቃት በመቃወም በተለያዩ ሀገራት ሰሞኑን የተቃውሞ ሰልፍ ሲካሄዱ ሰንብተዋል። ዛሬም በበርሊን እና በፓሪስ የሚገኙ ዜጎች አደባባይ ወጥተዋል።

‹‹ዘረኝነት›› እና ኢትዮጵያ ምን አገናኛቸው? /Minillik Salsawi/

ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነኝ በፌስ ቡክና በሌሎች አጋጣሚዎች ታዋቂና አንቱ የተባሉ ፖለቲከኞች ሳይቀር በኢትዮጵያ ያለውን ልዩነት ‹‹ዘር፣ ዘረኝነት፣ ዘረኛ›› እያለ ሲገልጹ ማየትና ማንበቤ ነው፡፡ ለመሆኑ ኢትዮጵያ ውስጥ ‹‹ዘር፣ዘረኝነት፣ዘረኛ›› አሉ? ለሰው ልጅ አመጣጥ ሳይንሳዊ አሊያም መለኮታዊ አመጣጥ ይሰጠዋል፡፡ አንደኛው ሰው ከዝንጀሮ መሰል እንሰሳ መጣ ሲል ሌላኛው አሁን ያለውን አካል ይዞ ነው የተወለደው በሚል ‹‹አምላክ ሰውን በአምሳያው ፈጠረ!›› ይለናል፡፡ የዓለም ህዝብ ከዝንጀሮ መጣ የሚሉት መነሻውን ወደ አፋር ሲጎትቱት በመለኮታዊው ግምገማቸው ወደ መካከለኛው ምስራቅ የተጠጋ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ በሁለቱ አመለካከቶች መሰረት የሰው ‹‹ዘር›› ምንጩ አንድ መሆኑንእንረዳለን፡፡ ግን ሰዎች በዚህ አልተወሰኑም፡፡ ሰውን ለመነጣጠል የሚያስችል ፖለቲካ ጨመረበት፡፡ በቆዳ ቀለሙ፣ በአኗኗሩ፣ በሰውነትና አካል ቅርጹ፣ እና በመሳሰሉት አናሳ ወይንም የበላይነቱ! ይህን መሰረት በማድረግ በ18ኛው ክፍለዘመን ጆሃን ብሉሜንባች የተባለ ጀርመናዊ የህክምና ባለሙያ አምስት ዋና ዋና የሰው ‹‹ዘር›› አይነቶችን አስቀምጦ ነበር፡፡ አውሮፓን ማዕከል አድርጎ የምዕራበዊያንን ነጮች ካውካሳይድ ብሎ ጠራቸው፡፡ የኤሲያዎቹን ‹‹ብጫ›› ህዝቦች ሞንጎሎይድ ብሎ አንድ ‹‹ዘር›› ውስጥ አስቀመጣቸው፡፡ አውስትራሊያና ኦሺኒያን ደግሞ ማሌዠያ የሚል ስያሜ ሰጣቸው፡፡ አሜሪካኖቹን አሜሪካውያን በሚል ሰየማቸው፡፡ ጥቁር አፍሪካውያንን በሙሉ ደግሞ ኢትዮጵያውያን የሚል ‹‹ዘር›› ውስጥ አስቀመጣቸው፡፡ ይህን አምነን እንቀበል ብንል እንኳ አማራ፣ ኦሮሞ፣ ትግሬ፣ አፋር፣ እና ሌሎች አፍሪካውያን አንድ ‹‹ኢትዮጵያ›› የሚባል ‹‹ዘር›› ውስጥ ናቸው፡፡ በአሁኑ ወቅት ደግሞ ከቀለም፣ የቅርጽና ሌሎች ፖለቲካ ያልተላቀቀው ‹‹ታሪክ›› የሚያስተምረው ሶስት የሰው ‹‹ዘር›› አሉ ብሎ ነው፡፡ ነጮቹን በድፍን ካውካሳይድ ይሏቸዋል፡፡ ጥቁሮቹን ኔግሮይድ ብለው ይሰይሙታል፡፡ ኢትዮጵያውያን በሙሉ ከዚህ ውስጥ እንገኛለን፡፡ ሞንጎሎይድ የሚሉት ደግሞ ወደ ቢጫ ይጠጋል የሚሉትን የኤሲያ ህዝብ ነው፡፡ ዘር ምን ያህል እውነት ነው? ………… በዘመናችን ‹‹ዘረን›› ከፖለቲካ መቀስቀሻነት ባለፈ ‹‹ሳይንሳዊ›› ትንታኔው የሚሰጡት ባይጠፉም በቆዳ ቀለም፣ አካላዊ ቅርጽና በመሳሰሉት የሚለየዩ ሰዎች በስነ ህይወታዊ ይህ ነው የሚባል የጎላ ልዩነት እንደሌላቸው የሚከራከሩት ተበራክተዋል፡፡ ለአብነት ያህል ዘር ከስነ ህይወታዊ በተለይም ከዘረመል ጋር የረባ ግንኙነት የሌለው መሆኑን በርካታ ጥናቶች አረጋግጠዋል፡፡ ለፖለቲካ መቀስቀሻም ቢሆን በአይን ቀለሙ ለማመሳሰል የተሞከረ ህዝብ በቆዳ ቀለሙ አይገናኝም፡፡ አሊያም በአፍንጫው፣ ወይንም በሌላው ነገሩ ይያያል፡፡ በመሆኑም ፖለቲከኞች አሊያም ሰውን የሚከፋፍሉት ‹‹አጥኚዎች›› ‹‹ዘር›› ብለው ሲመድቡ ለራሳቸው አስተሳሰብ ወይንም ጥቅም ቅርበት ያለውን በማጠጋጋት ብቻ ነው፡፡ በምዕራበዊያን አገራት ከእናቱ ወይንም ከአባቱ አንዱ ጥቁር የሆነው ጥቁር ይሉታል፡፡ ከዚህ በኋላ የእሱ የልጅ ልጆች ምንም ያህል ከነጭ ጋር ቢወላለዱና ነጭ ቢመስሉም ‹‹ኔግሮ›› የሚል ዘር ውስጥ መመደባቸው የግድ ነው፡፡ የኦባማ ልጆች ምንም ያህል ከነጭ ጋር ቢወላለዱ የልጅ ልጆቻቸው ጥቁር እንጅ ነጭ አይባሉም፡፡ ይህም የበላይ ነን የሚሉት ነጮች ለጥቁር ህዝብ ባላቸው የተሳሳተ አለመካከት የመጣ እንጅ የቀለም፣ የቆዳ አጠቃላይ የአካል ቅርጽ እንዳልሆነ የሚያሳይ ነው፡፡ ስለሆነም ይህ የሚያሳየን አብዛኛዎቹ ዘር ጥቃቅን ስነ ህይወታዊ ጉዳዮችን በማጋነን የመጣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ፈጠራ መሆኑን ነው፡፡ ዘር የፖለቲካ ፈጠራ በመሆኑ ፓስተር፣ ቄሱ፣ ሹሁና ሌላው የ‹‹ሀይማኖት›› አባት የሰው ልጅ ከአንድ አዳምና ሄዋን መጣ ብሎ ሳይጨርስ ስለተለያዩ ‹‹ዘሮች›› ፖለቲካዊ ትርጉም ያወሩልናል፡፡ ስለ ጥንታዊ ሰው የሚያጠናው ሳይንቲስት የሰው ዘር መገኛ ‹‹አፍሪካ ነች›› ብሎ ሳያበቃ ፖለቲካው በጎተተው መጠን ስለተለያዩ ዘሮች ከማውራት አይቆጠብም፡፡ እንደ አብዛኛዎቹ የወቅቱ ሀቀኛ ምሁራን ከሆነ የቆዳ ቀለም ልዩነትን ለመፍጠር ከዘረመል ይልቅ የአየር ንብረት ትልቅ ቦታ አለው፡፡ በአፍሪካ በርሃማ ቦታዎች የሚኖርና በአውሮፓ ግግር በረዶማ ቦታዎች የሚኖር ህዝብ አንድ አይነት የቆዳ ቀለም ሊኖረው አይችልም፡፡ ሆኖም በሂደት ተላምዶዊም ሆነ በሌላ ምክንያት ዘረመልም በቆዳ ቀለምና በመሳሰሉት ምንም አስተዋጽኦ የለውም ማለት አይደለም፡፡ ይልቁንስ የቆዳ ቀለምንና የመሳሳሉትን ልዩነት በመፍጠር ሚና የሚኖረው ዘረመል በጣም ጥቂትና በሰዎች መካከል ለመሰረታዊ ልዩነት መነሻ የሚሆን አለመሆኑ ነው፡፡ ከዚህ ይልቅ ‹‹ተመሳሳይ›› በሚባሉ ህዝቦች መካከል ያለው ስነ ህይወታዊ ልዩነትም በቀላሉ የሚታይ አይደለም፡፡ ከደም አይነት ጀምሮ ከቤተሰብ፣ ከጎሳና ብሄር፣ እንዲሁም ዘር የሚባለው በሙሉ የተለያዩ ናቸው፡፡ የአሜሪካን አንትሮፖሎጅ ማህበር እ.ኤ.አ በ1998 ባወጣው ጥናት ‹‹የሰውን ዘር በስነ ህይወታዊ ጥናት ድንበር ለይቶ መከፋፈል አይቻልም፡፡ 94 በመቶ ያህል የሰዎች ስነ ህይወታዊ ልዩነት አንድ ‹ዘር›› ውስጥ ናቸው በሚባሉት ውስጥም ይከሰታል፡፡›› የሚል መደምደሚያ ላይ ደርሷል፡፡ ይህ ማለትም አብዛኛው ልዩነት አንድ ዘር በሚባሉትም መካከል እንዳለ ነው፡፡ በተለያዩ ወቅቶች ‹‹ዘር›› ለሚባለው የተሰጠውም ይህንኑ ጥላቻ አዘል ፖለቲካ የሚያሳይ ነው፡፡ ለአብነት ያህል በ18ኛውና 19ኛው ክፍለ ዘመን በነጮቹ ዘንድ ጥቁር ግማሽ እንሰሳ እንደሆነ ሁሉ ይታመን ነበር፡፡ በ19ኛው እና 20ኛው ክፍለ ዘመን ለዚህ አሉታዊ አስተሳሰብን የሚቃረን የማርክሲዝም አስተሳሰብ ብቅ ብሏል፡፡ በ20ኛው ክፈለ ዘመን በተለይም በ1930 ጀምሮ ደግሞ ዘር ለጦርነት ምክንያት ሲሆን አካላዊ ሳይሆን ፖለቲካዊና በፖለቲከኞች ፈጠራ የመጣ ልዩነት መሆኑን አስመስክሯል፡፡ ይህም ዘር የሚባለው ‹‹ፈጠራ›› መሆኑን እንደሚያሳይ በርካቶች በመከራከሪያነት ያቀርቡታል፡፡ ኢትዮጵያና የዘር ጉዳይ ………… ዘር መኖሩን አምነው በጉዳዩ ጥናቶችን የሚያደርጉ ‹‹ምሁራን›› ዘርን የሚያስቀምጡት ከጎሳና ብሄር በላይ ነው፡፡ ለምሳሌ ያህል ጎሳ የሚባለው ‹‹አንድ አይነት አኗኗር፣ ስነ ልቦናዊ ሁኔታ፣ አለባበስ፣ ቋንቋ›› ውስጥ ከሚገኝ ‹‹ብሄር›› ከተባለው ማንነት በታች የሚገኝ ማንነት ነው፡፡ ሆኖም በርካቶች ዘርን ከጎሳና ከብሄር ጋር በማቀላቀል የቃሉን አውድ ሲያዛቡ ይስተዋላል፡፡ ፖለቲከኞች ዘር ሲሉ ምክንያቱን ስነ ህይወታዊ ምክንያት ይሰጡታል፡፡ እነ ሂትለር በጸጉር፣ በአይን ቀለም ጀርመናዊያንን ከሌሎቹ ሲያነጻጽሩ እንደነበሩት ማለት ነው፡፡ አሊያም ነጮቹ ራሳቸውን ከአፍሪካውያን፣ ከአረቦቹ አሊያም ከህንዶቹ ወይንም ከደቡብ አሜሪካውያን ጋር አነጻጽረው ልዩ እንደሚያደርጉት፡፡ ይህ ዘርን ከጎሳና ከብሄር ጋር የመቀላቀል አባዜ በኢትዮጵያም ከተለመደ ሰነባብቷል፡፡ በብሄር አሊያም በጎሳ የሚያምኑ የፖለቲካ ሀይሎችን የትኛውንም የፖለቲካ ጥበት ‹‹ዘረኝነት›› ብሎ መፈረጅ ለኢትዮጵያውያን አዲስ አይደለም፡፡ የኢህአዴግ መንግስት በሚያራምደው የብሄር ፖለረቲካ ‹‹በዘረኝነት›› ይወቀሳል፡፡ ሌሎችም ይህን የፖለቲካ ስልት በራሳቸው መልክ ይዘው ብቅ ሲሉ ‹‹የዘር ፖለቲካ›› ብለው የሚፈርጁት በርካቶች ናቸው፡፡ በአገራችን ከብሄርና ጎሳም ወረድ ሲልም ከእናት፣ አባትና ቤተሰብ የሚሳብን ዝምድና እና የ‹‹ደም›› ትስስር ለመግለጽ ‹‹ዘር›› ብሎ መጥራት የተለመደ ነው፡፡ ሆኖም ዘር፣ ዘረኝነት.. የሚባለው ፖለቲካዊ ፍች ከቤተሰባዊ ትስስር ይልቅ ‹‹race›› ከተባለው ጥቅል (ግን የተሳሳተ የፖለቲካ ፈጠራ) ማንነት የመጣ ነው፡፡ በእርግጥ ይህ በኢትዮጵያ ውስጥ የሰረጸው ጣሊያን ካደረሰችው ምስቅልቅል ጋር ተያይዞ እንደሆነ በርካቶች ይገልጻሉ፡፡ ጣሊያኖች ኢትዮጵያ ውስጥ በራሳቸው የሰለጠነ ልዩ ዘርና በኢትዮጵያ ኋላ ቀር ዘር መካከል ከፈጠሩት ንቀት አዘል ክፍፍል ባለፈ ኢትዮጵያውያንን በ‹‹ብሄርና ጎሳ›› ከፋፍለዋል፡፡ በመሆኑም ኢትዮጵያ ውስጥ የብሄር ፖለቲካ አዋጭ መሆኑን የሚያምኑት አካላትን ከጣሊያኑ ከፋፋይ ስርዓት ጋር በማዛመድ ‹‹ዘረኛ፣ ዘር፣ የዘር ፖለቲካ›› ብለው ይፈርጇቸዋል፡፡ ‹‹ዘር›› ፈጠራ መሆኑን ለጊዜው ረስተን ከአገራችን ህዝብ አኳያ ብንገመግመው ሰህተት መሆኑን እንረዳለን፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ብሄር አሊያም ጎሳ የሚባለው የቋንቋ ልዩነት ሲጠቀስ በዘር መክፈልም ሆነ ጎሰኛ አሊያም ጠባብ ብሄርተኛን ‹‹ዘረኛ›› ማለት የተሳሳተ ነው፡፡ የሚገርመው ደግሞ ኢትዮጵያ ውስጥ ‹‹በየዘረኝነት›› ስም የሚያወግዙት አካላት ኢትዮጵያ በጠባብ ማንነት መከፋፈል የለባትም የሚሉ ናቸው፡፡ ሆኖም ‹‹ዘር፣ዘረኛ፣ ዘረኝነት ፖለቲካ›› አለ የሚሉ ከሆነ በአካልም ቢሆን እጅጉን የተለያየ ነን ወደሚል እጅግ የሚቃረንና የተሳሳተ አመለካከት ያደርሳቸዋል፡፡ በጸጉር፣ በአይን ቀለም፣ በቆዳ ቀለም፣ በቁመት እጅጉን የተለያየን ነን እንደማለት ነው፡፡ ይህ ግን ስህተት ነው፡፡ የስርዓቱን ከፋፋይነት ለመግለጽ ከተፈለገ እንኳ ከጠባብ ብሄርተኝነት፣ጎሰኝነትና ጎጠኝነት ያለፈ ስም ሊሰጠው አይችልም፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ አማራ፣ ትግሬ፣ ኦሮሞ፣ ብሎ በዓይን ቀለም፣ በጸጉር፣ በአፍንጫ፣ በቆዳ ቀለም፣ በቁመት፣ በቅርጽ….መለየት አይቻልም፡፡ አሊያም አማራ፣ ኦሮሞ፣ ትግሬ… የሚባለው ህዝብ ውስጥ ተመሳሳይ የዓይን ቀለም፣ የቆዳ ቀለም፣ የአፍንጫ ርዝማኔና ቅርጽ…..ብቻ አካላዊ ማንነት አይኖርም፡፡ እንደ ሁመራና መተማ ያሉ በርሃማ አካባቢዎች የሚኖረው ህዝብ በአለባበስ፣ በአመጋገብና በአካል ገጽታ ከደጋው ትግርኛና አማርኛ ተናጋሪ ህዝብ ይልቅ በቆላማው አካባቢ ከሚኖረው የአፋርና የሶማሊ አካባቢ ህዝብ ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ በደጋው አካባቢ የሚኖረው ኦሮምኛ፣ አፋርኛ፣ሶማሊኛ፣ ትግርኛ፣ አማርኛ…..ተናጋሪ ህዝብ ተመሳሳይ ቋንቋ ከሚናገው ቆለኛ ህዝብ ይልቅ ሌላ ቋንቋ ከሚናገረው ደገኛ ህዝብ ጋር ተመሳሳይ ገጽታ፣ የኑሮ ዘይቤ፣አለባበስ…..ያለው ነው፡፡ ዘር ከፖለቲካ ፈጠራው አልፎ የደም ጉዳይ ቢሆን ኖሮ ኦሮምኛ ተናጋሪው አንድ አይነት ደም፣ አማርኛ ተናጋሪው ከኦሮምኛ ተናጋሪው የተለየ ሌላ የደም አይነት በኖረው ነበር፡፡ በዓለም ደረጃም ቢሆን ተመሳሳይ ነው፡፡ ዘር የተሳሰተ የፖለቲካ ቀመር ነው፡፡ ይህን የተሳሳተ የፖለቲካ ቀመር እንጠቀም ካልም ደግሞ ‹‹ዘርን›› ካመጡት ‹‹ምሁራን›› ምድብ ልንወጣ አንችልም፡፡ ስለሆነም ኢትዮጵያውያንን የግድ በዚህ በተሳሳተ ቀመር እንክፈላቸው ከተባለ በጥቁር ማንነት ስር እኩል ከጋና፣ ከሞዛምቢክ፣ ከኬንያ፣ ከአንጎላ፣ ከጥቁር አሜሪካና ጃማይካኖቹ ጋር ይመደቡ ይሆናል እንጅ ሌላ ‹‹ዘር›› አይገኝላቸውም፡፡ እንዲያውም ጆሃን ብሉሜንባች የተባለው ጀርመናዊ ለመላው ጥቁር ህዝብ ‹‹ኢትዮጵያዊ›› የሚል ዘር ነው የሰጠው፡፡ ከዚህ ባለፈ ኢትዮጵያውያንን በቋንቋና ሌሎች ጥቃቅን መሰረቶች ‹‹ዘር›› ብሎ መፈረጅ ግን በጥላቻ ከተሞላው ጀርመናውይም በላይ እንድንሳሳት ያደርገናል፡፡ እናም በበኩሌ ፖለቲከኞቻችን ስለ ኢትዮጵያ ፖለቲካ ሲወራ ‹‹ዘር›› የምትባለዋ ቋንቋ የተሳሳተች መሆኗን ተረድታችሁ ባትጠቀሙባት ይሻላል እላለሁ፡፡ ካልሆነ ግን ኦሮምኛ፣ አማርኛ፣ ትግርኛ፣ ሶማሊኛ፣ አገውኛ፣ አርጎብኛ…..ተናጋሪው አንዱ ከሌላው በአይን ቀለሙ፣ በጸጉሩ፣……….እንደሚለይ መረጃ ልታቀርቡልን የግድ ነው፡፡ ዝም ብሎ መከፋፈል አለ እንዴ?

http://66.147.244.58/~theethio/harartub … %E1%8A%93/

Abraha Desta
November 19
“ከህወሓት የባስክ ትሆናለህ” አሉኝ
———————————–

“ጨቋኝ ስርዓት አልፈልግም” ብዬ በፃፍኩት ላይ አንድ የፌስቡክ ወዳጄ “አንተ ራስህ ስልጣን ብትይዝ ከህወሓት የባስክ አምባገነን ትሆናለህ” አለኝ።

እኔም እላለሁ፣

ከህወሓት የተሻልኩ እንደምሆን እርግጠኛ አይደለሁም (ራሴ ለግዜው እንደ ፓርቲ ልቁጠር)። ስለ አንድ ነገር ግን እርግጠኛ ነኝ። እኔ ሰለማዊ ታጋይ ነኝ። ስልጣን የምይዘው በህዝባዊ ምርጫ እንጂ በጠመንጃ አይደለም። የምወዳደረው በሐሳብ እንጂ በሃይል አይደለም።

ስለዚህ ስልጣን ስይዝ የራሴ ወታደር፣ ፖሊስ፣ ዳኛ ወዘተ ይዤ አልመጣም። ስልጣን የምይዘው በሕገመንግስት መሰረት እስከሆነ ድረስ በኔና በወታደሮቹ ያለ ግንኙት ሕገመንግስታዊ ይሆናል። ስለዚህ ወታደሮቹ እንደፈለኩ የግሌ የስልጣን ጥም ለማርካት አላዝዛቸውም። ዳኞችም ነፃ ይሆናሉ።

ስለዚህ እኔ ስልጣን ከያዝኩ በኃላ ከህወሓት ካልተሻልኩ በህዝብ ምርጫ እንደወጣሁ ሁሉ በሚቀጥለው በህዝብ ምርጫ ከስልጣን እወርዳለሁ። ከስልጣን ላለመውረድ ምንም ዓቅም የለኝም፤ ምክንያቱም በምርጫ ስልጣን የያዘ አካል የግሉ ወታደርና ፖሊስ የለውም። የስልጣን መሰረቴ የህዝብ ድምፅ ከሆነ በስልጣን ለመቆየት ስል ህዝብን አልጨቁንም። ከጨቆንኩ ደግሞ ህዝቡ ያወርደኛል።

የኢህአዴግ መንግስት ሰለማዊ ትግልን አጨልሞብኝ በትጥቅ ትግል ስልጣን ከያዝኩ ግን አምባገነን የመሆን ዕድል አለኝ። ምክንያቱም የስልጣን ምንጬ ጠመንጃ እንጂ ህዝብ አይደለም። ለህዝብ ታማኝና አገልጋይ የምሆንበት ዕድል ይጠባል። ስለዚህ በምርጫ ስልጣን የያዘ መንግስት ቢያበላሽ እንኳ በምርጫ ይወርዳል። አሁን የቸገረን በጠመንጃ የመጣ መንግስት ነው።

ዓላማችን ስልጣን መያዝ ብቻ ሳይሆን ስልጣን በጠመንጃ ከመያዝ በምርጫ የምያዝበት ስርዓት መገንባት ጭምር ነው።

(ስልጣን የመያዝ ዕቅድም ፍላጎትም የለኝም። የኔ ፍላጎት በነፃነት የፈለኩትን ማድረግ ነው። እኔ የሌሎችን መብት ሳልዳፈር የፈለኩትን የማድረግ ነፃነት እንዲኖረኝ የህዝብ መንግስት ወይ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት መገንባት አለበት። ስልጣን መያዝ ነፃነትን ይገድባል)።

It is so!!!

“የኢትዮ-ኤርትራ ችግር መፍትሄ፣ ድንበር ማስመር ሳይሆን ድንበር ማፍረስ ነው”
——————————–

ኤርትራዊው ፕሮፌሰር ተከስተ ነጋሽ እንዲህ ተጠየቀ;

አዲስ አድማስ ጋዜጣ : የኤርትራ ህዝብ አሁን ያሉበትን የነፃነት ሁኔታ ከቀድሞው ጋር ሲያስተያዩት ምን ትርጉም ይሰጥዎታል?

ተከስተ ነጋሽ: እኔ እኮ በመጀመሪያም ኤርትራውያኖች ከማን ነው የሚገነጠሉት የሚል አቋም ነው ያለኝ። ማነው ከማን የሚገነጠለው? የደቡብ ወይም የኦሮሞ ህዝቦች እንገነጠላለን ቢሉ ኖሮ ምክንያት ነበራቸው፡፡ የኤርትራ የነፃነት ጥያቄ በተነሳበት ወቅት ኤርትራውያኑና ከላይ የጠቀስኳቸው ህዝቦች በኢትዮጵያ ውስጥ ያገኙትን እድል (Comparative advantage) ስናይ፣ ኤርትራውያኑ በጣም ተጠቃሚ ነበሩ፡፡ (በጣሊያን፣ በእንግሊዝ፣ በፌዴሬሽኑ ዘመን) በ1960ዎቹ የአዲስ አበባ ሀብታሞቹ እነሱ ነበሩ። በትምህርት መስክ ሃያ አምስት በመቶ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ተማሪዎች ኤርትራውያን ነበሩ። የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎችንም ካየሽ 25 በመቶ የሚሆኑት ኤርትራውያን ነበሩ፡፡ ከተማረው ሰላሳ አምስት በመቶው ክፍል ኤርትራውያን ነበሩ፡፡

ህዳር ፲፪(አስራ ሁለት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢሳት በደረሰው አስተማማኝ መረጃ መሰረት   በሳውድ አረቢያ ይኖሩ የነበሩ ኢትዮጵያውያን ለትምህርት ቤት መገንቢያ እና ለችግር ግዜ ይሆነናል በማለት ከግል ኪሳቸው እያወጡ በደረግ ዘመን ሲያጠራቅሙት የነበረውን ገንዘብ የቀድሞው ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ በሰጡት ትእዛዝ ገንዘቡ ተወርሶ በሪያድ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኢምባሲና የአምባሳደሩ መኖሪያ እንዲሁም ጅዳ የሚገኘው የቆንስላ ጽህፈት ቤት እንዲሰራበት …

ህዳር ፲፪(አስራ ሁለት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዘግይቶም ቢሆን ችግረኛ ኢትዮጵያውያንን ከሳውድ አረቢያ ማስወጣት የጀመረው የኢትዮጵያ መንግስት፣ እስካሁን ድረስ የተመላሾችን አሀዝ በተመለከተ የሚሰጠው መግለጫ ግን ህዝቡን ጥርጣሬ ላይ መጣሉን የኢትዮጵያው ዘጋቢያችን ገልጿል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስተሩ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሀኖም በቲውተር ወደ አገር ቤት የተመለሱት ኢትዮጵያውያን ቁጥር 10 ሺ 707 ነው በማለት ገልጸዋል። ይሁን እንጅ የእርሳቸው …

ህዳር ፲፪(አስራ ሁለት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በሰኞ ኖቬምበር 25፤ 2013 ከ ጠዋቱ 8:30 ጀምሮ ሚድራንድ በሚገኘው ፓን አፍሪካ ፓርላማ ፊት ለፊት ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ እንደሚያዘጋጁ ለኢሳት ተናግረዋል። በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በተዘጋጀው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ በመገኘት ድምጻቸውን እንዲያሰሙ ተማጽነዋል።

ህዳር ፲፪(አስራ ሁለት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 15ኛ ወንጀል ችሎት አቶ መላኩ ፈንታ ክሳቸው በየትኛው ፍርድቤት ይታይ የሚለውን ጉዳይ ፥ የህገመንግስት ትርጉም ያስፈልገዋል በሚል ለሕገመንግስት አጣሪ ጉባኤ መምራቱ አንዳንድ ከፍተኛ የኢህአዴግ ሹማምንትን እንዳላስደሰተ ታውቋል። ሰኞ ህዳር 10 ቀን 2006 ዓ.ም በነበረው የችሎት ውሎ አቶ መላኩ ፈንታበሚኒስትር ማዕረግ ተሸመው ሲያገለግሉ እንደነበሩና …

ህዳር ፲፪(አስራ ሁለት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በዛሬው እለት የአዲስ አበባ መስተዳድር በቡራዩ አካባቢ በወሰደው እርምጃ፣ ከ500 በላይ ቤቶችን ያፈረሰ ሲሆን በርካታ ቤተሰቦች ለከፍተኛ ችግር መዳረጋቸውን ለኢሳት ገልጸዋል። አመዲና ጎጥ በተባለ አካባቢ የሚኖር አንድ መስፍን የተባለ ወጣት ወላጆቼ በሰሩት ቤት መኖር ካልቻልኩ ምን ህይወት አለኝ በሚል ራሱን ማጥፋቱም ታውቋል። የቀበሌው ሊቀመንበር ህዝቡን ሰብስቦ ለማነጋገር …

ወደ አሥራ ሦስት ሺህ የሚጠጉ ኢትዮጵያዊያን እስከአሁን ከሣዑዲ አረቢያ አዲስ አበባ መግባታቸውን የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

ተመላሾቹን ለማቋቋም በፌደራል መንግሥቱና በክልል አስተዳደሮች የትብብር ሥራ እንደሚከናወንም መሥሪያ ቤቱ አመልክቷል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ ሳዑዲ አረቢያ ውስጥ በኢትዮጵያዊያን የሰብዓዊ መብቶች ረገጣ ተፈፅሟል የሚል ዜና ከወጣ ጀምሮ በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ድምፃቸውን እያሰሙ ነው፡፡

ዛሬ፣ ሐሙስ፣ ኀዳር 12 / 2006 ዓ.ም ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ደጅና ጀርመን ዋና ከተማ በርሊን ውስጥ ደግሞ በሳዑዲ አረቢያ ኤምባሲ አጠገብ ሰልፎች ተደርገዋል፡፡

ባለፉ ጥቂት ቀናት ውስጥም በእንግሊዝ፣ በጣልያን፣ በአውስትራሊያ፤ ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ደግሞ በዳላስ፣…

ሕጋዊ ፈቃድ በሌላቸው ኢትዮጵያውን ላይ የሚደርሰውን ችግር እና ጥቃት በመቃወም በተለያዩ ሀገራት ሰሞኑን የተቃውሞ ሰልፍ ሲካሄዱ ሰንብተዋል። ዛሬም በበርሊን እና በፓሪስ የሚገኙ ዜጎች አደባባይ ወጥተዋል።

Image
ልሂቃን ለስልጣናቸው ሲሉ ሊሰብሩት የሚጥሩትን ድልድይና ገመድ አጠናክረነው በሰላም አብረን መኖር የምንችለው፡፡

በእርግጥ እኛም ከኤርትራውያን የምንሻልበት ደረጃ ላይ አይደለንም፡፡እነሱም እንደኛው ናቸው፡፡ መከራ ውስጥ ሆነውም ቢሆን ግን በሳውዲ አረቢያ ሰቆቃ የደረሰባቸውን ዜጎች ድምጽ ከጎናችን ሆነው አሰምተዋል፡፡ በደቡብ አፍሪካው የአፍሪካ ዋንጫ ከጎናችን ሆነው የአገራችን ቡድን አበረታትተዋል፡፡
ድሮም ቢሆን ህዝብ በራሱ ተሳስቶ አያውቅም፡፡ ህዝብን የሚያወናብዱት ልሂቃን ናቸው፡፡ ኤርትራ በጣሊያን እጅ በነበረችበት ወቅት በርካቶቹ ወደ እናት አገራቸው ጠፍተው ገብተው በከፍተኛ ስልጣን አገራቸውን አስተዳድረዋል፡፡ እነ አብርሃም ደቦጭና ሞገስ አስግዶም ስለ እናት አገራቸው መስዋትነት ከፍለዋል፡፡ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር በፌደራል ስርዓት ስትቀላቀል ጨፍረዋል፣ ደስታቸውን በእምባ ሳይቀር ገልጸዋል፡፡ ይነሱም ይብዙም ኤርትራውያን በኢትዮጵያ መከራ ጊዜ ከጎናችን እርቀው አያውቁም፡፡
አጼ ኃይለስላሴ ፌደሬሽኑን ሲያፈርስ በኢትዮጵያውያን ድጋፍ ወይንም ግፊት አልነበረም፡፡ መንግስቱ ኃይለማሪያም በኤርትራውያን ላይ እርምጃ ሲወስድም ቢሆን እንዲሁ፡፡ ጀብሃና ሻዕቢያ በአረብ አገራት ድጋፍ ኤርትራን ለመገንጠል የጣሩት በህዝቡ ትዕዛዝና ግፊት አሊያም ድጋፍ አልነበረም፡፡ እንዲያውም ይህንን ተገንጣይነት ኤርትራውያን ‹‹እናት አገር ወይንም ሞት›› ብለው ተዋግተውታል፡፡ በኢትዮጵያ የነበሩት አስተዳደሮችም ሆነ ‹‹ወንበዴዎቹ›› ስህተት ግን ሁለቱን ህዝቦች መካከል ያለውን ድልድይ ለመስበር ሳይታክቱ ሰርተዋል፡፡
ህወሓትና ሻዕቢያ ስልጣን ከያዙ በኋላም ቢሆን የሁለቱ ህዝቦች ትስስር እንደፈለጉት ሊበጠስላቸው አልቻለም፡፡ የሻዕቢያና የህወሓት ካድሬዎች ሁለቱን ህዝቦች እየደበደቡ፣ እየዘረፉ፣ እያሰቃዩ ከአስመራና አዲስ አበባ ሲያስወጡ ህዝብ የተለያየው በእንባ ነበር፡፡
በእርግጥ የመንግስታት ፕሮፖጋንዳ፣ ካድሬዎች የሚፈጥሩት መከራና ኢኮኖሚያዊ ወይንም ሌላ ግንኙነት በመቋረጡ ምክንያት ህዝቦች ሊቆራረጡ ይችላሉ፡፡ ሁለቱ ህዝቦች መካከል ያለውን ግንኙነት ለመስበር የተደረገው ሙከራ ግን አልተሳካም፡፡ አዎ! ኤርትራውያን የአገሪቱ ‹‹መንግስት›› ሰላማዊ ሰልፈኞቹን ባሰረበትና በደበደበበት ወቅት ከጎናችን ሆነው ገመዱ ኃይለስላሴ፣ መንግስቱ ኃይለማሪያም፣ ኢሳያስ፣ መለስ፣ ህወሓት፣ ሻዕቢያ ሊበጥሱት የማይችሉ የደም ገመድ መሆኑ በድጋሜ አሳይተውናል፡፡
እናም እንደነሱው ከጎናቸው መቆም ይገባናል፡፡ በአሁኑ ወቅት ኢሳያስ ጠፋ፣ ታመመ እየተባለ ነው፡፡ አምባገነን መሪ ሲሞት፣ ሲታመም፣ ወይንም አምባገነኑ ስርዓት ምክንያት ስርዓት ሲናጋ የሚጎዳው ሀብትና ጥበቃ የሌለው ምስኪን ህዝብ ነው፡፡ ሀብት ያላቸው የኤርትራ ባለስልጣናት በፈለጉት አገር ሄደው ይኖራሉ፡፡ ጥበቃ ያላቸው አገር ውስጥም ቢሆን አንጻራዊ ሰላም ይኖራቸዋል፡፡ ድሃውና ሲጨቆን የነበረው ህዝብ ግን አምባገነኑ እያለም ሆነ ሞቱ ስጋት ውስጥ ነው፡፡ የአገር አደጋ አደጋ የሚሆነው ለድሃው ነው፡፡
ኢትዮጰያውያን መለስ ዜናዊ ጠፋ፣ ታመመ፣ ሞተ በተባለበት ወቅት አምባገነንነቱን ረስተን ‹‹አገር ትፈራርሳለች›› ብለን ተጨንቀናል፡፡ ኤርትራውያንም አሁን ተመሳሳይ ስጋት ውስጥ ናቸው፡፡ ሁለቱ ህዝብ በተለያየ ጊዜ ይከሰቱ እንጅ ተመሳሳይ መከራ፣ ስጋት ውስጥ ናቸው፡፡ ችግራቸው መሰረት ተመሳሳይ ነው፡፡ እናም እነዚህን ችግሮች መፍታት የሚችሉት አንዱ ከአንዱ ጎን በመቆም ብቻ ነው፡፡
ለችግሮቻቸው መፍትሄ ማምጣት እንኳን ባንችል ልክ እንደወትሮው፣ ልክ እንደባህላችን፣ ልክ እነሱ እንዳደረጉት ከጎባቸው መሆናችንን ማሳየት አለብን፡፡ ሲሆን ታሪክ፣ ደም፣ አምሮ መኖር በደመነፍስ እያነጋኘን እንደሆነ በቅርቡ አይተነዋል፡፡ የሁለቱ አምባገነን ስርዓቶች ፕሮፖንዳና መሰሪነት በርካቶቹን እሴቶቻችን ሸርሽሮት አብሮ መስራት እንደማይቻል የሚያስብ የዋህ (ካድሬ ቢኖር እንኳ) ጎረቤቶች ነን፡፡ የኤርትራ ችግር መቼም ቢሆን የኢትዮጵያውያን ችግር ነው፡፡ የኢትዮጵያ ችግር የኤርትራውያን ችግር ነው፡፡ ከሁለቱ አገራት መካከል አንዱ እንደ ሰው ተሰዶ ወይንም ሸሽቶ፣ አሊያም አጥሮ መኖር አይችልም፡፡ የሶማሊያና የሱዳን ችግር እንኳን ችግራችን ሆኗል፡፡
እናም በችግራቸው ጊዜ አብረናቸው መቆማችን ለእነሱ ብቻ ሳይሆን ለእኛም ጥቅም ነው፡፡ ስለሆነም ከኤርትራውያን ወንድምና እህቶቻችን ጎን አብረን መቆም ይኖርብናል፡፡ እንዲህ ሲሆንም ነው ልሂቃን ለስልጣናቸው ሲሉ ሊሰብሩት የሚጥሩትን ድልድይና ገመድ አጠናክረነው በሰላም አብረን መኖር የምንችለው፡፡ — with Getachew Shiferaw and 2 others.

በጦርነቶች እና በግጭቶች ምክንያት ከመኖሪያ ቦታቸው የተፈናቀሉ ወጣቶች የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ትኩረት ሰጥቶ የሚሰራው የአውሮጳ ህብረት የልጆች የሰላም ፕሮጀክት የአንድ ዓመት የስራ ክንውን እና ውጤት ብራስልስ ቤልጅየም

የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ድርጅት ሂዩመን ራይትስ ዋች በአንዳንድ የአፍሪቃ ሃገራት በመገናኛ ብዙሃንና በሰብዓዊ መብት ተከራካሪዎች ላይ ተጠናክሮ የቀጠለው ጥቃት እንዲቆም እርምጃ ይወሰድ ዘንድ ብራሰል ቤልጂግ ውስጥ ለተካሄደው የአፍሪቃና የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽኖች የሰብዓዊ መብቶች የጋራ መድረክ አሳስቧል ።

አዉሮጳን እርሱ ፤ ብሩህ ተስፋ እና ተስፋ የሚገኝበት አዲስ አበባ ነዉ ይሰኛል ባለፈዉ ወር መገባደጃ ላይ ዲ ቬልት የተሰኘዉ የጀርመን አንጋፋ ጋዜጣ ያስነበበዉ ርዕስ፣ በጀርመንኛ መጠርያዉ ዲ ቬልት ፤ ማለትም «ዓለም» በመባል የሚታወቀዉ ዕለታዊ የጀርመን ጋዜጣ በጎርጎረሳዉያኑ 1964 ዓ,ም ሁለተኛዉ የዓለም ጦርነት እንዳለቀ ጀምሮ የሚታተም ነዉ።

በውጪ ሐገር በስደት ላይ በሚገኘው ሕጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ የሚመራው የካምፓላ መካነሰላም መድሃንያለም ቤተክርስትያን በዩጋንዳ የህዳር ሚካዔልን የንግስ በዓል ኢትዮጵያዊያንና ኤርትራዊያን የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ምዕመናን በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ አንዳከበሩት በስፍራው የነበረው የፔን ዘ ኢትዮጵያ ዘጋቢ ገለፀ።
ከለሊቱ አስራአንድ ሠዓት ጀምሮ በማህሌት የጀመረው ክብረ በዓል በደብሩ መሪጌታ ይህይስ ዓለሙ ያሬዳዊ ዝማሬ ቀርቧል።<ውእቱ ሚካዔል መልዓከ ኃይለ ልዑል።ውእቱ ልዑለ መንበር ይስአለነ……>
በዕለቱ ቅዳሤ በርካታ ምዕመናን የታደሙ ሲሆን ከማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ አስራ ስምንት ከቁጥር አስራአምስት እስከ ሃያ አንድ በቆሞስ አባ ኃይለማርያም ተነቧል። ስርዓተ ቁርባን ከተከናወነ በኋላም በቆሞስ አባ አብዩ የዕለቱን በዓል በማስመልከት ኦሪት ዘፀአት ምዕራፍ አስራ አራት ከቁጥር አስራ ዘጠኝ ጀምሮ ያለውን ቃል በተመለከተ የወንጌል ማዕድ ቀርቧል።
የቅዳሤ ስርዓቱ እንዳበቃም ታቦተ ህጉ በካህናትና ምዕመናን ታጅቦ በክብርና በምስጋና ዜማ ታጅቦ በአውደ ምህረቱ ላይ መሪጌታ ይህይስ <አንተኑ ሚካዔል መና ዘአወረድከ።ወአንተኑ ለእስራዔል መና ዘአወረድከ።>በያሬዳዊ ዜማ ወረብ አቅርቧል።
የደብሩ አስተዳዳሪ ቀሲስ ፀሐይ ደስታ በበዓሉ ፍፃሜ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት እግዚአብሔር አምላክ እስራዔላዊያንን ከግብፅ የባርነት ቀንበር ነፃ የወጡበትን ዕለት በመዘከር ይህንን ታላቅ በዓል ቤተክርስትያን በድምቀት እንደምታከብረውና በዓሉ የስደተኞች በዓል ሊባል እንደሚችል ጠቁመው ስደተኞች ሁላችን እግዚአብሔር አምላክ እስራዔላዊያንን ከግብፅ የፈርዖን አገዛዝ እንዳዳናቸው ሁሉ እኛንም ለሐገራችን ያብቃን ሲሉ ቃለ ምዕዳን ሰጥተዎል።
በመጨረሻም የአምልኮ ነፃነት በተረጋገጠባት ዩጋንዳ ኤርትራዊያንና ኢትዮጵያዊያን የኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኞች የፖለቲካ ድንበር ሣያግዳቸው በአንድ ደብር ፈጣሪያቸውን ሲያመሠግኑ የዚህ ዜና ዘጋቢ ተመልክቷል።
Pen Ethiopian

Image

በኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰው ጥቃት እና የፈዘዘው ስርኣት የፖለቲካ ክስረት
መፍትሄው ኢሕኣዴግ የማይደፍረው ስር ነቀል ለውጥ ነው::

ምንሊክ ሳልሳዊ:-ኢትዮጵያውያን በመካከለኛው ምስራቅ በስፋት መሰደድ የጀመሩት ባለፈው 20 አመታት የወያኔው ጁንታ መንግስት ስልጣኑን ተቆጣጥሮ በህዝቦች ላይ በተለየ መልኩ የፈጠረውን አደገኛ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ቀውስ ተከትሎ መሆኑ እሙን ነው::ይህ ቀውስ የደረሰባቸው ወገኖቻችን ከተሰደዱባት ሃገር አንዷ ሳኡዲ አረቢያ ተጠቃሽ ናት::ሳኡዲ አረቢያ ከሃብቷ ብዛት የመጣ የስራ ፍቅር ባሌለው ወጣት ዜጋ የተሞላች እና ፔትሮ ዶላር ባሰከራቸው ቱጃሮች የምትተዳደር አገር መሆኗ እና የዜጎቿ የስራ አለመስራት የስራ እድሎችን ስላሰፋ የወያኔ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ተጠቂዎች ወደዚሁ መሰደድን መርጠዋል:: ይህንን ተከትሎም ይህን ሰሞን የአለም ዋና አጀንዳ የሆነው የኢትዮጵያውያን በሳኡዲ አረቢያ እየደረሰባቸው ያለ ስቃይ ነው::

ሰቆቃው ያደረሰው የሰብኣዊ መብት ጥያቄ ከሳኡዲ መንግስት ላይ ይልቅ ወደ ወያኔው ጁንታ ላይ እንዲተኮር ያደረገ ሲሆን የወያኔው ጁንታ ለከፍተኛ የፖለቲካ ኪሳራ ተዳርጓል::በኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰው አስደንጋጭ እና ሰብኣዊነትን ያለፈ ድርጊት በመንግስት ባለስልጣናት መሃከል የፈጠረው መረበሽ እስከአለመግባባት አድርሷቸዋል::ይህንን የወያኔን አቋም የተመለከተችው ሳኡድ አረቢያ በአለም አቀፍ ደረጃ የፖለቲካ የበላይነት ተቀናጅታለች::በከፍተኛ ደረጃ በአለም አቀፍ ደረጃ ባሉ ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ዘንድ ከፍተኛ የሆነ አትኩሮት አግኝቶ የአለም ጎዳናዎች ሳኡዲን እና ወያኔን በሚቃወሙ በሰላማዊ ሰልፍ እየተጥለቀለቁ ነው::ህገመንግስታዊ መብቶችን አለመከበሩን እና ለዜጎች አለመቆርቆርን በማሳየቱ በአለማቀፍ ደረጃ የኢትዮጵያውያንን ቁጣ ቀስቅሷል::ሚዲያዎች ከዜጎች የሳኡዲ ሰቆቃ ይልቅ በኢትዮጵያውያኑ ሰልፎች ላይ አትኩሮት ሰተዋል::

ከወያኔው መንግስት የሚንጸባረቁ አጀንዳዎች ለዘብተኛ አቋሞች በስህተት እንደተፈጠሩ ወቅታዊ ሁኔታኦች እያሳዩ ሲሆን ስርኣቱ አጣብቂኝ ውስጥ እና የፖለቲካ ኪሳራ ውስጥ እንደገባ ተረጋግጧል:: የሌላ ሃገር እምባሲዎች ዜጎቻቸውን በመጠበቅ ላይ ሲያተኩሩ የወያኔው ዲፕሎማቶች የዜጎች ንብረት የሆነውን ኤምባሲ በመዝጋት አገልግሎት አቁመዋል::
የደረሰውን ሰቆቃ ተከትሎ ስርኣቱ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በመተባበር ለሉአላዊ የዜግነት ክብር መነሳሳት ሲኖርበት እና ህዝብን ማቀፍ ሲኖርበት ለብሄራዊ ውርደት ዜጎችን ዳርጓል::የፖለቲካ ፓርቲዎች የጠሩትን ሰልፍ በሃይል እና በደብዳቤ በትኗል::የወያኔው ስርኣት የህዝቡን ቁጣ ባለማንበቡ በችኮላ ያልበሰለ ሃሳብ በማራመዱ የፖለቲካ ኪሳራውን አስፍቶታል::ህገመንግስታዊ መብቶችን አለመከበሩን እና ለዜጎች አለመቆርቆርን በማሳየቱ በአለማቀፍ ደረጃ የኢትዮጵያውያንን ቁጣ ቀስቅሷል::ሚዲያዎች ከዜጎች የሳኡዲ ሰቆቃ ይልቅ የወያኔን ስርኣት ጋጥወጥነት አትኩሮት ሰተውታል::

ለዚህ ሁላ ችግር መንስኤው ስርኣቱ በልማት ሽፋን የሚከተለው የፖለቲካ እና እና የኢኮኖሚ ፖሊሲ ችግሮች እንደሆኑ አግጥጦ ገሃድ ከመውጣቱም በላይ የአደባባይ ሃቅ ሆኖ ለለውጥ እንትጋ የሚሉ ድምጾች በመላው ሃገሪቱ ተንጸባርቀዋል:; የወያኔ ስርኣት ህዝብን የሚያሳትፍ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ፖሊሲ እስካልተከተለ ድረስ እና አሁን ባለው ሂደት ላይ ለውጥ እስካላደረገ ድረስ የስደት ችግሩ በስፋት እየቀጠል ይሄዳል:;ዛሬ ሳኡዲ ላይ የደረሰው ሰቆቃ ነገ በሌሎች ሃገራትም ይቀጥላል::ይህ ብሄራዊ ውርደት በታሪካችን አይተነው የማናውቅ ነው:;ኢትዮጵያውያን ከቀድሞው ጀምሮ በፖለቲካ ቢሰደዱም እንደዚህ አይነት ውርደትን አስተናግደው አያውቁም::የአሁኑ ውርደት ያለው ስርኣት ለዜጎቹ ደንታ ቢስ በመሆኑ የተወለደ ችግር ነው::በሃገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ተመዘገበ ከመባል ውጭ የተባለው እድገት ምንም አይነት ህዝባዊ ጠቀሜታ እንዳላሳየ በይፋ አስመስክሯል::የተማረው እና የሚሰራው ሃይል መሰደዱ ኢኮኖሚው እንደኮላሸ እንጂ እንዳደገ አያሳይም::የዚህ ሁላ መንስኤው ስርኣቱ የሚከተለው አፋኝ የፖለቲካ እና የእኮኖሚ ፖሊሲ ስለሆን ድጋሚ ሊከለስ እና ሊፈተሽ ይገባዋል::

የነቃ እና የተደራጀ አዲስ ፖሊሲ አስፈላጊ መሆኑ እሙን የሆነበት ጊዜ ላይ ደርሰናል::ስርኣቱ የሚከተለውን ፖሊሲ በአስቸኳይ ካልቀየረው የሚመጣው አደጋ ከፍተኛ ነው::በሃገሪቱ በልማት ስም እና በፖለቲካ ባላንጣነት በዜጎች ላይ የሚደርሰው ችግር የሙስና መንሰራፋት ሚዛናዊነት የጎደለው የምጣኔ ሃብት እንቅስቃሴ የግሉን ሴክተር የማዳከም ውስጣዊ ሴራ ዘር ተኮር የሆነ ፖለቲካ እና አድሎኣዊ አሰራር የትምህርት ጥራት መውረድ እና የስራ አጡ ቁጥር እንዲስፋፋ የሚደረጉ ደባዎች ዜጎች ምንም አይነት ጥያቄ እንዳያነሱ የሚደረጉ የፖለቲካ ዱላዎች ለድህነት መፈጠር እና የስደት መስፋፋት ምክንያት ሆነዋል::የህዝብ ቁጥርን ተከትሎ የሚደረግ የእድገት ፖሊሲ አለመመጣተን የሃገሪቱ ዜጎች ተዘዋውረው እንዳይሰሩ የተደረገ የጎሳ ፖለቲካ የተማሩ ዜጎችን የስራ እድል አጥብቦታል::አለ ተብሎ የሚወራለት የኢኮኖሚ እድገት ጥቂት የስርኣቱን ካድሬዎች ተጠቃሚ ያደረገ በመሆኑ ማንኛውም ነገር በካድሬዎች ዙሪያ እና በፓርቲ ስራዎች ዙሪያ ያተኮረ በመሆኑ ዜጎች በሃገራቸው ላይ ተስፋ እንዲቆርጡ አድርጓቸዋል::

ያለው ስርኣት ስርነቀል ለውጥ ለማምጣት ፖሊሲዎቹን እና የደረሱ የዜጎችን ችግር ከስሩ መሰረቱ መመርመር አለበት:: በፓርቲው አመራር ደረጃ ያሉ የስርኣቱ ባለስልጣናት ለስርነቀል ለውጥ ራሳቸውን ማዘጋጀት አለባቸው::በግል የንግድ ተቋማት ላይ ስርኣቱ ያለው አቋም ከመጀመሪያ ለውጦች አንዱ ነው የግል የንግድ ተቋማት መዳከም ምክንያቱ የስርኣቱ መራሽ የንግድ ድርጅቶች እና አድሏዊነት የፈጠረው የኢኮኖሚ ችግር ሲሆን መፍትሄውም የተዳከመውን የግሉን የንግድ እንቅስቃሴ እንዲያንሰራራ ማድረግ እና ለዜጎች በርካታ የስራ እድሎች እንዲከፍት ማበረታታን አንዱ ሲሆን የተለየ የፖለቲካ አቋም ያለው ዲያስፖራው በሃገሩ ጉዳይ እንዲሳተፍ እድሎችን ማመቻቸት እንዲሁ ለፖሊሲ ለውጥ ጅማሮ ሊሆን ስለሚችል ስደትን በስፋት ለመቀነስ እና ዜጎች ከሃገራቸው እንዳይወጡ ለማድረግ ይችላል::

በአሁን ሰአት ስርኣቱ እየተተቀመበት ያለው የኢኮኖሚ ፖሊሲ በተጭበረበረ ፖለቲካ ላይ የተገነባ ከመሆኑም ባሻገር ባልተማሩ እና ባልሰለጠኑ የፖለቲካ ታማኞች ስለሚተገበር በአግባቡ እየተተረጎመ ባለመሆኑ ውድቀትን አምጥቷል::የሃገሪቱ አጠቃላይ ሃብት እና የኢኮኖሚ ምሶሶ በጥቂት የፓርቲ ድርጅቶች እና ባለስልጣናት እጅ በቁጥጥር ስር ስለሆነ የግሉ ኢንቨስትመት በመዳከሙ እና ስርኣቱ ከዚህ አይነት የንግድ እንቅስቃሴ ካልወጣ በቀር ምንም አይነት ለውጥ መምጣት እንደማይቻል እሙን ሲሆን መፍትሄው የተቆጣጠረውን እና በግል መያዝ ያለባቸውን የንግድት ተቋማት እና የአገልግሎት ዘርፎች መልቀቅ ካልቻለ ችግሩ እየከፋ ዜጎችን ምንም ተጠቃሚ እንዳይሆኑ ያደርጋል::በአለም አቀፍ ደረጃ እንደሚታየው መንግስታት ህግ የማውጣት እና የማስፈጸም አቅም እንጂ ከትልቅ እንስከተራ ንግድ ድረስ እጃቸውን አስገብተው ሲሰሩ አይታይም::ያለው ስርኣት ወደ ቸርቻሪ ነጋዴነት በመቀየሩ ለዜጎች የስራ እድሉን አጥብቦታል::

ኢኮኖሚውን ከፍተኛ የጦር ጄኔራሎች እና የፓርቲ የንግድ ድርጅቶች በሞኖፖል ስለተቆጣጠሩት ዜጎች በስርኣቱ ፖለቲካ ካልተጠመቁ ድረስ ስራ የማግኘት እድል የላቸውም::ይህ ኢኮኖሚውን የመቆጣጠር የፖለቲካ ጭብርብሮሽ የኢንቨስትመት ሂደቱን ከማዳከሙም በላይ ዜጎች በሃገራቸው እና በስርኣቱ ላይ እምነት እንዲያጡ አድርጓል::ስርኣቱ ከነጋዴነት መውጣት ሰፊ የስራ እድሎች እንዲፈጠሩ እና ስደት እንዲቀንስ የሚረዳ ሲሆን ዜጎች በሃገራቸው ተሳፋ እንዳይቆርጡ ያደርጋል:: እንዲሁም የመንግስት የመገናኛ ቡዙሃን በሃሰት የተሞሉ መሆናቸው እና አስፈላጊውን መረጃ መስጠት አለመቻላቸው ሌላኛው የኢኮኖሚ ድቀት እና የስደት መንስኤ ናቸው:: በነጻነት የማይሰሩት እና ለፖለቲካው የእድሜ ማስረዘሚያ የሆኑት የመገናኛ ብዙሃን ቀረጥ የሚከፍላቸውን ህዝን እንዳያገለግሉ ከመደረጉም በላይ በሃሰት የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ወንጀሎችን በመፈብረክ የታወቁ ሆነዋል::

ሕዝቡ ስርኣቱ እስካልተመቸው ድረስ ስደትን ማቆም አይቻልም ጊዜአዊ እገዳውም ውጤታማ አይሆንም:: ሀገሪቱ ብዙ ሴቶች ወደ መካከለኛው ምስራቅ ሊሰደዱባት የቻለውም ከሴቶች እኩልነት ጋር በተያያዘም ችግር በመኖሩና ብዙ ስራ አለመሰራቱን የሚያሳይ ነው::በዚህ ዙሪያ የሚሰሩ ድርጅቶችም በነፃነት አለመቋቕውማቸው ሴቶችም እንደሰው አለመታየታቸው ነው::የፓርቲ ፖለቲካ መስበክ ሳይሆን በሴቶች እኩልነት እና ተሳትፎ ዙሪአ ኢኮኖሚው መዳበር ሲኖርበት አስፈላጊውን ኦረንቴሽንም መስጠን የስርኣቱ ግዴታ ነው::አሁን ባለው ሁኔታ ወደ ስራ የሚገባውን ወጣት የሚሸከም ኢኮኖሚ አልተፈጠረ:: የግል ሴክተሩም በርካታ ዜጎች እንዳይፈጥር ሆኖ እየሞተ መሆኑን ከዓለም ባንክ ሪፖርቶች ማየት ይቻላል::በዓለም ደረጃ በመንግስት ኢንቨስትመንት ኢትዮጵያ በዓለም ሦስተኛ ስትሆን፤ በግል ኢንቨስትመንት ከመጨረሻዎቹ ስድስተኛ ደረጃ ላይ ነን። ስለዚህ የግል ሴክተሩ ካልተስፋፋና ካላደገ ስራ ሊፈጠር አይችልም። በየዓመቱ ከዩኒቨርሲቲ የሚመረቀው ወጣት በዓመት ወደ መቶ ሺህ ሊጠጋ ነው። ይሄንን ኃይል መጦ የሚያስቀር የሚያደርግ ኢኮኖሚ መፈጠር የሚቻለው የግል ሴክተሩ ሲነቃቃ ነው። አሁን የግል ሴክተሩ በኮንስትሪክሽን ዘርፍ ላይ ውር ውር እያለ ነው። ይሄም ሴክተር ቢሆን፤ የቀን ሰራተኛ ከመሳብ ባለፈ ሙያተኛውን መቅጠር አልቻለም። ለዚያውም ትንሽ ሲሚንቶ መለሰን ሲጀምሩ ወደ መካከለኛው መስራቅ በተከበረ ወርሃዊ ደመወዝ ሲቀጠሩ ይታያል። ሀገሪቱ የተማረ የሰው ኃይል የላትም። ያሉዋትም ለባዕድ አገር እያገለገሉ ነው። በአንፃሩ የአገሪቱን የባቡር መንገድ እና ግድብ የሚሰሩት ቻይናና ሕንድ ናቸው። ስኳር ፋብሪካውንም የሚሰሩት ሕንዶች ናቸው። በሚያሳዝን መልኩ ሁለት ሚሊዮን የሚሆኑ ኢትዮጵያዊያን የተማሩም ሆነ ያልተማሩ ችሎታቸውን እየሸጡ ያሉት ለባዕድ ሀገር ነው። ከአፍሪካ እስከ ደቡብ ሱዳን፣ ቦትስዋና እና ደቡብ አፍሪካ ሳይቀር በርካታ ኢትዮጵያውያን ችሎታቸውን በጥሩ ዋጋ እየሸጡ ነው። ይሄን አሳዛኝ ታሪክ ለመቀየር የግል ሴክተሩ ማደግ ወሳኝ ነው ።

የግል ዘርፉ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ይረከብ ማለት ግድብ ይገንባ፣ የባቡር መንገድ ይዘርጋ ማለት አይደለም ነገር ግን የግል ዘርፉ ሊሰራቸው የሚችሉ ስራዎች ተለይተውና ተጠንተው መሰራት አለባቸው። የኅብረተሰብ ችግርም እየተበራከተ ስለሆነ ችግሩን መመርመር ያስፈልጋል ። የግል ዘርፉ ከካፌና ሆቴል ላይ ብቻ የሚሯሯጠው ለምንድነው? የቀጥታ የውጪ ኢንቨስትመንት ችግር በገፍ የማይመጣው ለምንድነው፣ አነስተኛና ጥቃቅን አደረጃጀት ምን ያህል ውጤት አምጥቷል? የተደራጀ ጠንካራ የግል ዘርፍ መፍጠር ነው ወይስ አነስተኛ ጥቃቅን ድርጅቶች የሚለው መታየት አለበት። የትኛው ነው ብዙ ኀሳብ የሚያመነጩት፣ የገበያ ሁኔታስ? ባንኮች አካባቢ ያለው ችግር ምንድነው? ለምን አያበድሩም ይሄ ሁሉ መፈተሽ አለበት ።የኢትዮጵያ የአረብ ገረድ አምራች ሆና መቅረት የለባትም ።

http://minilik-salsawi.blogspot.com/201 … st_21.html

የወረዳው ሊቀ መንበር ለስብሰባው በሚገባ መዘጋጀታቸው ሲወራ ነው የሰነበተው፡፡ ሕዝቡን ለፀረ ሽብርተኛት ዘመቻ በሚገባ ማንቀሳቀስ አለብኝ ብለዋል አሉ፡፡ አንድም ሰው ከዚህ ስብሰባ መቅረት እንደሌለበት በየሰፈሩ ሲወራ ነበር፡፡

የስብሰባው ቀን ሕዝቡ እግር ኳስ የሚያይ መስሎ አዳራሹን ሞላው፡፡ ቦታ የጠበባቸውም በመስኮት በኩል ጉርድ ፎቶ የሚነሡ ይመስል አንገታቸውን ብቻ አስግገው ያጮልቃሉ፡፡ እስካሁን ማንም ሊቀ መንበር ያልተናገረውን ንግግር ሊያደርጉ ነው ስለተባለ ሰው ምን እንደሚናገሩ ለመስማት ጓጉቷል፡፡ በተለይ አንዳንዱ የወረዳው ነዋሪ እንደ ክትባት ለሁሉ የታዘዘ የሚመስል ተመሳሳይ ንግግር መስማት ሰልችቶታል፡፡ ተናጋሪዎች እንደ ኮካኮላ ጠርሙስ አንድ ዓይነት ሆነው  እንደ ተመረቱ ሁሉ እንኳን ቃሎቻቸው ሳሎቻቸው እንኳን ስለሚመሳሰሉ አንዳንዱ ‹ይህንን ንግግር የት ነበር የሰማሁት›› እስከማለት ደርሷል፡፡ አሁን የኛ ወረዳ ሊቀ መንበር ይህንን እንደ ኮንዶሚንየም መልክ የተመሳሰለ ንግግር ሰብረው ሪኮርድ ሊያስመዘግቡ መሆኑን ስንሰማ ተገልብጠን መጣን፡፡

አንድ በስብሰባው ውስጥ ያገኘሁት ሰው ‹‹እነዚህ ባለ ሥልጣናት ግን አንድ ዓይነት ቃላት ከየት ነው የሚያገኙት?›› ብዬ ስጠይቀው ምን እንዳለኝ ታውቃላችሁ ‹‹የባለ ሥልጣናት መዝገበ ቃላት›› የሚባል ያልታተመ መጽሐፍ አለ፡፡ከዚያ ብቻ ነው ቃላት መምረጥ የሚችሉት፡፡ እዚያ ውስጥ የንግግር ቅጽ አላቸው፡፡ ወረዳውን፣ ቀኑን፣ የተሰብሳቢዎቹን ዓይነትና የበዓሉን ስም ብቻ ትቀይርና ንግግሩን ትወስዳለህ›› ብሎ ቀለደብኝ፡፡

አሁን ሊቀ መንበሩ እየገቡ ነው፡፡ ሕዝቡ አጨበጨበ፡፡ ፕሮግራሙን የሚመራው ሰው ማይክራፎኑን ያዘና ‹አሁን ስብሰባችንን የምናከናውንበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡›› ሲል ሕዝቡ አጉረመረመ፡፡ ግራ ገባው፡፡ ‹ይህ ሕዝብ ባይገባው ነው›› ብሎ አዘነልን፡፡ ‹‹ወረዳችን በዕድገት እመርታ ላይ መሆኗን ታውቃላችሁ፡፡ ልዩ ልዩ ጽሕፈት ቤቶችና አጋር አካላት ተሳልጠው በመሥራታቸውና ሙስናንና ብልሹ አሠራን አስወግደን ልማታዊ አስተሳሰብን በማምጣታችን …›› ሕዝቡ ትዕግሥት አጣ፤ አንድ ጎረምሳ እንዲያውም ‹‹ይህንነን ንግግር የዛሬ ሦስት ዓመት ሰምተነው ነበር፡፡›› ሲል ተሰብሳቢው ሳቀ፡፡

አንደኛዋ ወይዘሮማ ‹‹ምነው መንግሥት በየቦታው ተዋንያኑን ብቻ ነው እንዴ የሚቀይራቸው? የፊልሙን ስክሪፕትስ ለምን አይቀይረውም፡፡ ያ ይሄዳል ይሄ ይመጣል፤ ፊልሙ ያው ነው፡፡›› ሳቅና ጭብጨባ አጀባቸው፡፡ ሰውዬው ግራ እንደገባው ነው፡፡ ‹‹ይህ ንግግር ከራሴ የወጣ ነው፡፡ ይህንን ማን ተናግሮት ነው የዛሬ ሦስት ዓመት የሰሙት›› አለ ተገርሞ፡፡ ‹‹ባክህ ሃርድ ዌሩ ነው እንጂ ሶፍት ዌሩ ያው ነው፡፡ ወይ አብዴት አድርጉት ወይ ቀይሩት››  ወጣቱ ሲናገር በዐዋቂነቱ ተጨበጨበለት፡፡

የወረዳችን ሊቀ መንበር አዝማሚያው ስለገባቸው ማይክራፎኑን ከፕሮግራም መሪው ተቀበሉት፡፡ ‹‹ወደ መጣንበት ጉዳይ ብንገባ ይሻላል፡፡›› ሲሉ አንድ ካህን ድምጻቸውን ከፍ አደረጉና ‹‹ልክ ነው ከተአምሩ መቅድሙ ረዘመብንኮ›› አሏቸው፡፡ ሊቀ መንበሩ ፈገግ ብለው ወረቀታቸውን ከቦርሳቸው አወጡ፡፡ አሁን ስፒል ቢወድቅ የሚሰማበት ዝምታ ተፈጠረ፡፡ የሰው ጆሮ እንደ ዲሽ ተዘረጋ፡፡

ሊቀ መንበሩ ንግግራቸውን ቀጠሉ፡፡ ‹ፈጣሪ በቸርነቱ እስካሁን ሀገር አስፍቶ ጠላት አጥፍቶ አኑሮናል› ብለው ሲጀምሩ ሕዝቡ ቀጣዩን እንኳን ሳይሰማ አጨበጨበ፡፡ የተከበራችሁ የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባላት፣ የክፍለ ከተማ አመራሮች፣ የድርጅት ኃላፊዎች፣ የሥራ አስፈጻሚ አባላት፣ የወጣት ሊግ አመራሮች፣ የሴቶች ሊግ አመራሮች፣ የአነስተኛና ጥቃቅን አመራሮችና አባላት፣ የበጎ አድራጎት ድርጅት ኃላፊዎች፣ የአደረጃጀቶች ኃላፊዎች….. እያሉ እንደ ስም ጠሪ መምህር ወይም እንደ ሙሾ አውራጅ ሲዘረዝሩ ሊውሉ ነው ተብሎ ነበር የተጠበቀው፡፡

‹‹ድርጅታችንም እስካሁን በፈጣሪ ቸርነት፣ በታጋዮች መሥዋዕትነት፣ በአመራሩ ብስለትና በሕዝቡም ይሁንታ ይህንን ሀገር እየመራ መጥቷል፡፡›› ሲሉ ከጎኔ የነበሩት አንድ ሽማግሌ ‹‹ይኼ ነገር የሆነ የሆነ ነገር ሸተተኝ›› አሉኝ፡፡ በዚህ እድሜያቸው የሆነ ነገር ለማሽተት መቻላቸውን አደነቅኩና ‹‹ምን ሸተተዎት›› አልኳቸው፡፡ ‹‹ቆይ እስኪ ቀጣዩን እንስማው›› አሉ፡፡ እንደ ሬዲዮ አንቴና አንገታቸውን ወደ ላይ መዝዘው፡፡

ሊቀመንበራችን እንደ ቀጠሉ ናቸው ‹‹ደግሞም ሕዝባችን እስካሁን አሳፍሮን አያውቅም፤ ከእንግዲህም ያሳፍረናል ብለን አናምንም›› ሲሉ ጭብጨባው ቀለጠ፡፡ እኒያ ሽማግሌ ግን ወደ ላይ የዘረጉትን የአንገታቸውን አንቴና ወደ ውስጥ ሰበሰቡት፡፡ ከዚያም ራሳቸውን ወደ ቀኝና ግራ ወዘወዙ፡፡ ‹‹ይኼ የተከተፈ ንግግር ነው›› አሉ፡፡ በግራ በቀኝ፣ በፊት በኋላ የተቀመጡት ተሰብሳቢዎች ዘወር ዘወር እያሉ አዩዋቸው፡፡ ሊቀ መንበራችን ግን ቀጠሉ፡፡ ‹‹አሁን ግን አገር የሚያጠፋ፣ ገጽታ የሚለውጥ፣ ዕድገት የሚገታ፣ የሕዝብን ሰላም የሚያናጋ ጠላት መጥቶብናል›› ሽማግሌው አንገታቸውን አውልቀው መጣል ይፈልጋሉ መሰል ከአመድ እንደተነሣች አህያ ያርገፈግፉታል፡፡

‹‹እኛም ብሔር ብሔረሰቦች ፊታቸውን ወደ ልማት ማዞራቸውን፣ ሀገራችንም በአንጻራዊ ሰላም ላይ መሆኗን ተመልክተን፤ ዐቅማችንንም ለልማት እንጂ ለሌላ ነገር ማዋል የለብንም ብለን ዝም ብንለው፤ ደግሞ እያለፈ እንደ ዘንዶ አደጋ ማድረስ ጀመረ››፡፡ ሽማግሌው የአንገታቸው አልበቃ ብሏቸው በጫማቸው መሬቱን ይፎግሱ ጀመር፡፡ ‹‹አሁን ግን ሕዝባችንን አጋዥ አድርገን ሀገራችንን አሳልፈን አንሰጥም በማለት ተነሥተናል፡፡ ሕዝባችን ሆይ እስካሁን የበደልንህ አይመስለንም፡፡ አንተም አልበደልከንም፡፡ ዐቅም ያለህ በዐቅምህ እርዳን፤ ዐቅም የሌለህ ለሚስትህ/ለባልሽ፣ ለእምነትህ ስትል መረጃ በመጠቆም እርዳን፡፡›› አሁን ሽማግሌው እጃቸውን ከእጃቸው ጋር ማፋተግ ጀመሩ፡፡ ሊልጡት ነው እንዴ፡፡ ‹‹ወስልቶ ከዚህ ዘመቻ የቀረ ካለ ግን ይጣላናል፡፡ አንተወውም፤ ድርጅታችንን፤ እንምረውም››

‹‹ኦህ›› አሉ ሽማግሌው፡፡

‹ለዚህ አማላጅ የለንም፡፡ ፀረ ሽብር ዘመቻችን ተጀምሯልና የሀገራችን ሰው በዚሁ ወቅት በየራስህ ከትተህ እናግኝህ፡፡››

ሕዝቡ አጨበጨበ፡፡ ጭብጨባውም ረዘመ፡፡

ሽማግሌው ማንም ሳይቀድማቸው ተሥፈንጥረው ተነሡ፡፡

‹‹እሽ አባቴ›. አሉ ሊቀመንበሩ፡፡ ሽማግሌው ወኔ ይዟቸው የተነሡ መስሏቸው፡፡

‹‹ይህ ንግግር የማን ነው?›› አሉ፡፡ እየተንቀጠቀጡ፡፡ ሰው አጉረመረመ፡፡

‹‹እንዴት ማለት›› አሉ ሊቀ መንበሩ፡፡

‹‹ይህ ንግግር ዐፄ ምኒሊክ ለዐድዋ ዘመቻ ከተናገሩት ንግግር የተወሰደ አይደለም?›› አሉ ሽማግሌው፡፡

‹‹ነው›፡፡ ግን ሬሚክስ አድርጌ በአዲስ አቀራረብ ነው ያመጣሁት፡››

‹‹ምኑን ነው ሬሚክስ ያደረጉት››

‹‹ከዓላማዬ ልጀምርልዎት፡፡ የቀድሞ መሪዎችን ንግግር እንዲህ ሬሚክስ እያደረግን ካላቀረብነው ይረሳሉ፡፡ ትውልዱ አያስታውሳቸውም፡፡ ይህንን ያደረግኩት ለምኒሊክ ክብር ብዬ ነው፡፡ አላዩም ዘፋኞቻችንን፤ የቀድሞ ዘፋኞችን ዘፈን ሬሚክስ እያደረጉ በአዲስ አቀራረብ ሲያቀርቡ፡፡ እኔም እንደዚያው ነው ያደረግኩት፡፡ ሬሚክስ ያደረግኩት ደግሞ የምኒሊክን ባላባታዊ አስተሳሰብ ከአብዮታዊ ዲሞክራሲ አስተሳሰብ ጋር ነው፡፡ በአዲስ አቀራረብ ያልኩት ንግግሩን ልማታዊ፣ ሕዝባዊ፣ ፌዴራላዊ፣ ብዝኃነትን የያዘ አድርጌ ነው ያቀረብኩት፡፡›› አሉ ሊቀ መንበሩ፡፡

‹‹እና ዐፄ ምኒሊክን በአዲስ አቀራረብ አቀረቧቸው ማለት ነው›› አሉ ሽማግሌው፡፡

‹‹አዩ አባቴ ማዘመን ማለት ይኼ ነው፡፡ ታሪክን ማረም ይገባል፡፡ አዲስ መፍጠር ካልተቻለ የነበረውን ሬሚክስ እያደረጉ በአዲስ አቀራረብ ማቅረብ ነው፡፡ ሕዝቡም የሚወደው ይኼንን ነው›› አሉና ወደ ሕዝቡ ሲመለከቱ ጎረምሶቹ ‹‹ሼባው አቦ ተወና፣ እኛ ተመችቶናል›› አሏቸው ሽማግሌውን፡፡

ሽማግሌውም ‹‹በጦርነት ያልጠፋች ሀገር በሬሚክስ መጥፋቷ ነው በሉኛ›. ብለው ተቀመጡ፡፡ በአዲስ አቀራረብ በሬሚክስ ላስደሰቱን ለሊቀ መንበራችን ግን ጭብጨባው ቀለጠላቸው፡፡

© ይህ ጽሑፍ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት የወጣ ነው

ህዳር ፲፩(አስራ አንድ )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሳውድ አረቢያ ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ የላቸውም በሚል የሳውዲ ፖሊሶች እና ወጣቶች በኢትዮጵያውያን ሴቶች፣ ህጻናትና ወንዶች ላይ የፈጸሙትን የሰብአዊ መብት ጥሰት በመቃወም በተለያዩ የውጭ አገራት የሚካሄዱት የተቃውሞ ሰልፎች እንደቀጠሉ ሲሆን ፣ በዛሬው እለት በስዊዘርላንድ በርን በተካሄደው ተቃውሞ ኢትዮጵያውያኑ ስሜታቸውን ለመቆጣጠር ተስኖአቸው ታይተዋል። ኢትዮጵያውያኑ የሳውዲን መንግስትና የኢትዮጵያን መንግስት የሚያወግዙ …

ህዳር ፲፩(አስራ አንድ )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የጦር ፍርድ ቤቱ እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው በቅርቡ በኦጋዴን የተፈጸመውን የሰብአዊ መብት ጥሰት በተመለከተ፣ የክልሉ የወጣቶች ሊቀመንበርና የፕሬዚዳንቱ የግል ዌብሳት ማኔጀር እና አማካሪ የነበረው ወጣት አብዱላሂ ሁሴን በኦጋዴን የጦር ወንጀልና የሰብአዊ መብቶች ጥሰት መፈጸሙን የሚያሳይ ማስረጃ ለፍርድ ቤቱ አቃቢ ህግ ማቅረቡን ተከትሎ ነው። የጦር ፍርድ ቤቱ ዋና …

ተመስገንደሳለኝ

በረዥሙ የኢትዮጵያ ዘመነ መንግስት ታሪክ፣ በአስተዳደሩ ተመስግኖ በክብር የተሸኘ ገዥ ስለመኖሩ የሚያወሳ አንድም ድርሳን ፈልጎ ማግኘት የሚቻል አይመስለኝም፡፡ ሁሉም መንግስታት የተወገዱት በአመፅ አሊያም በተፈጥሮ ሞት ነውና፡፡ በ1983 ዓ.ም ወርሃ ግንቦት በጠብ-መንጃ ኃይል ሥልጣን የተቆናጠጠው ኢህአዴግ-መራሹ መንግስትም ቢሆን፣ በቀድሞዎቹ ገዥዎች ‹የብረት ጫማ› ውስጥ ተከልሎና ተደላድሎ ዕለተ-ስንብቱን በመጠባበቅ ላይ ያለ ይመስለኛል፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

ነብዩሲራክ

ትናንት እንደ ቀልድ …
በያዝነው የፈረንጆች 2013 ዓም በወርሃ መጋቢት አጋማሽ የሳውዲ አረቢያ መንግስት ” ህጋዊ ሰነድ ያልያዙትን አስወጣለሁ !” ብላ አወ ች ። ቀጠለና አፈሳ አሰሳው ተከተለ! አስፈሪው ያ ክፉ የጭንቅ ቀን በሳውዲው ንጉስ ሌላ የምህረት አዋጅ ተተክቶ ህገ ወጥ የተባሉትን ህጋዊ በሚያደርግ ህግ ተተካና የምህረቱ አዋጅ በያዝነው ህዳር መባቻ እንደሚያልቅ በተጠቆመው አዲስ የምህረት አዋጅ ተተካ !

ሙሉውን አስነብበኝ …