ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ድርጅቱ በመንግሥት ይፈፀማል ካለው ስለላ ሰለባዎች መካከልም ተቃዋሚዎች ጋዜጠኞች እንዲሁም ፀረ መንግሥት እንቅስቃሴ አካሂዳችኋል ተብለው የታሰሩ ሰዎች ይገኙበታል ። መንግሥት ግን ለአንዳንድ የዜና ወኪሎች በሰጠው ምላሽ ዘገባውን አስተባብሏል ።

ማኅበሩ ትውልዳዊ ተልእኮውን ለአባቶች በመታዘዝና በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን በመወሰን የመፈጸም አሠራሩና ፍላጎቱ እንደጸና መኾኑንና ከዚኽ ውጭ በሌላ መንገድ የሚመጣ መፍትሔ ይኖራል ብሎ እንደማያምን የሥራ አመራር ጉባኤው አስታውቋል፡፡ መንግሥት አካሒዳለኹ ከሚለው የፀረ አክራሪነት ትግልና ቤተ ክርስቲያኒቱ በቅዱስ ሲኖዶስ ወስና የአፈጻጸም አቅጣጫ ከሰጠችበት የአደረጃጀትና አሠራር ለውጥ አፈጻጸም ጋራ በተያያዘ በተለያዩ አካላት የሚሰነዘሩበትን የስም ማጥፋት ዘመቻዎችና መሠረተ ቢስ …

 click here for pdf

ሰሞኑን ማኅበረ ቅዱሳንን በተመለከተ ‹‹ሊያፈርሱት ነው›› የሚል ዜና በኅትመት ሚዲያዎችም ሆነ በማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ ይታያል፣ ይሰማል፡፡ የቤተ ክርስቲያን ቅዱሳት መጻሕፍት ግን አንድ መንፈሳዊ ተቋም ሊፈርስ የሚችለው በውጭ ኃይል ጫናና ዐቅም ሳይሆን በውስጣዊ ምክንያቶች መሆኑን ይነግሩናል፡፡ ኢየሩሳሌምን ናቡከደነፆር ያፈረሳት ናቡከደነፆር ኃያልና ተዋጊ ስለነበረ አይደለም፡፡ የባቢሎኑ ናቡከደነፆር መሣሪያ እንጂ መነሻ አልነበረም፡፡ ኢየሩሳሌም የፈረሰችው እግዚአብሔር ኢየሩሳሌምን አሳልፎ ስለሰጣት ነበር፡፡ ኢየሩሳሌም የቃል ኪዳን ከተማ መሆኗ ቀርቶ ሕዝቡ በእግዚአብሔር ላይ የሚቀልዱባት፣ ካህናቱም በአገልግሎታቸው የሚያሾፉባት ከተማ ሆነች፡፡ በዚህም ምክንያት እግዚአብሔር አሳልፎ ሰጣቸው፡፡ ለዚህም ነበር ነቢዩ ዳንኤል በጸለየው ጸሎት ላይ ‹‹ኃጢአትን ሠርተናል፣ በድለንማል፣ ክፋትን አድርገናል፣ ዐምፀናልም፣ ባሪያዎችህንም ነቢያትን አልሰማንም›› በማለት የገለጠው፡፡

አሁንም የሚጠቅመን ነገር እግዚአብሔር ለሌሎች አሳልፎ እንዲሰጠን የሚያደርግ ነገር ሠርተናል ወይስ አልሠራንም? የሚለውን ማየት ነው፡፡ ለመዋጥ የሚያበቃ ምክንያት ከኛ ዘንድ ከሌለ በቀር አንበሳው ስላገሣ ብቻ አይውጠንም፡፡ እኛ ከእግዚአብሔር ጋር መሆናችንን ርግጠኞች እንሁን፡፡ እግዚአብሔር ከኛ ጋር ለመሆኑ ርግጠኞች ነንና፡፡ ውስጣችን ለእግዚአብሔር የተመቸ ለመሆኑ ርግጠኞች እንሁን፣ እግዚአብሔር ለእኛ የተመቸ ነውና፡፡ ከዚህ በኋላ ግን ማንኛውንም ነገር ለመቀበል ዝግጁ እንሁን፡፡ በክርስትና ውስጡ ውጩን ይስበዋል እንጂ፣ ውጩ ውስጡን አይስበውም፡፡ ‹‹ዝናብም ወረደ፣ ጎርፍም መጣ፣ ነፋስም ነፈሰ፣ ያንንም ቤት መታው በዐለት ላይ ስለተመሠረተ ግን አልወደቀም›› ይላልና፡፡ ያልወደቀው ስላልተመታ ሳይሆን መሠረተ ጽኑዕ ስለነበረ ነው፡፡

ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ ዐርፈው አቡነ ቴዎፍሎስ ዐቃቤ መንበር እያሉ ቤተ ክህነቱ ይታመስ ነበር አሉ፡፡ የቤተ ክህነቱ የዘር አስተሳሰብ እያቆጠቆጠ የመጣበት ዘመን ነበርና ‹‹ቀጣዩ ፓትርያርክ ማን ይሆን?›› ከሚለው ይልቅ ‹‹ቀጣዩ ፓትርያርክ ከነማን ወገን ይሆን?›› የሚለው ብዙዎችን የሚያስጨንቅበት ጊዜ ነበር፡፡ እንዲያውም አንዳንዶቹ እንደ ዘመነ ሴዴቅያስ የሐሰት ነቢያትን በሆኑት በመሰል ባሕታውያን በኩል ‹ቀጣዩ ፓትርያርክ እገሌ ነው፣ ራእይ አይቻለሁ›› ያሰኙም ነበር፡፡

በወቅቱ ዐቃቤ መንበር ለነበሩት ለአቡነ ቴዎፍሎስ ብዙ ሰዎች እየሄዱ ‹‹እገሌ ፓትርያርክ ቢሆኑ፣ ሕዝቡ እገሌን እያለ ነው፣ መኳንንቱ እገሌን እያሉ ነው፣ ባሕታውያኑ እገሌ ይሆናሉ ብለው ትንቢት እየተናገሩ ነው፣ ቤተ ክህነቱም እገሌን እያለ ነው›› እያሉ ይነግሯቸው ነበር፡፡ ሁሉንም የሰሙት አቡነ ቴዎፍሎስም ‹‹ባሕታውያኑም፣ ሕዝቡም፣ መኳንንቱም፣ ቤተ ክህነቱም ያሉትን ሰምቻለሁ፡፡ እግዚአብሔርስ ምን አለ?›› ብለው ጠየቁ ይባላል፡፡

አሁንም የሚጠቅመው ከልዩ ልዩ ቦታ በሚነፍሰው ነፋስ መሸበር ሳይሆን እንደ አቡነ ቴዎፍሎስ ‹‹እግዚአብሔርስ ምን አለ?›› ብሎ መጠየቅ ነው፡፡ ሁሉም የየራሱን ሊወስን፣ ሊፎክር፣ ሊነሣ ይችላል፡፡ እግዚአብሔር ካልወሰነ ግን የሚሆን አንዳች ነገር የለም፡፡ የእግዚአብሔርን ውሳኔ የሚያመጣው ደግሞ የወደረኞቹ ኃይል ሳይሆን የራሳችን ስንፍና ነው፡፡

ታዋቂው ገጣሚ ጸጋዬ ገብረ መድኅን በጻፈው የቴዎድሮስ የመቅደላ ስንብት ላይ ‹‹ከሠራሁት ነገር ይልቅ ያልሠራሁት ነው የሚቆጨኝ›› እንዳሉት፡፡ ያልሠራነው ነገር እንዳይኖር፣ ምክንያት የሆንነው ነገር እንዳይኖር፣ ልንፈጽመው ሲገባን ያልፈጸምነው ነገር እንዳይኖር፣ ልናስበው ሲገባን ያላሰብነው ነገር እንዳይኖር ነው መፍራት፡፡ እንጂ ሊመጣ ያለውን ነገር አይደለም መፍራት፡፡ ክርስቲያን ሞትን አይፈራም አሟሟቱን እንጂ፡፡   

ሰውዬው በሩን በጠንካራ ብረት ዘግቶ ሲጠብቅ ያየው ጎረቤት ‹‹ምነው እንዲህ ታጠብቀዋለህ፤ አላህን አታምንም እንዴ ብሎ ቢጠይቀው ‹‹አላህንም አምናለሁ፣ በሬንም አጠብቃለሁ›› እንዳለው በእግዚአብሔር ያለንን እምነት ማጽናት በራችንንም ማጥበቅ ያስፈልገናል፡፡ የአመራር አቅማችን እንዴት ነው? መደበኛ አገልጋዮቻችንና አባሎቻችን እንዴት ናቸው? በአመራራችን ደስተኞች ናቸው? ማዕከሎቻችን እንዴት ናቸው? ከሊቃነ ጳጳሳትና ከአህጉረ ስብከት ጋር ያላቸው ግንኙነት መልካም ነው? ግቢ ጉባኤያቱ እንዴት ናቸው? ሚዲያዎቻችንስ በቀድሞው ጥንካሬና ብስለት ላይ ናቸው? ሌሎችንም በሮች ማጠባበቁ የሚበጅ ይመስለኛል፡፡

ከዚያ ወዲያ ግን፣ የምንችለውን ሁሉ ካደረግን በኋላ ግን፣ የዐቅማችንን ሁሉ ከፈጸምን በኋላ ግን ‹‹እግዚአብሔር ምን አለ? የሚለው እንጂ እነ እገሌ ምን አሉ›› የሚለው ሊያሳስበን እንጂ ሊያስጨንቀን አይገባም፡፡ ቂጣ ከሆነ ይጠፋል፣ ሺልም ከሆነ ይገፋል፡፡

እንደ ክርስትና ትምህርት ከሆነ ህልውና ከግዘፋዊ ኑባሬ ጋር አይደለም የሚያያዘው፡፡ በእግዚአብሔር ዘንድ ከሚገኝ ሕይወት እንጂ፡፡ ግዘፋዊ ኑባሬ ማለት እታየ እየተደሳሰሰ፣ አካላዊ ቦታ ይዞ መኖርን ነው፡፡ እያሉ የሌሉ እንዳሉት ሁሉ እንደሌሉ የተቆጠሩ ደግሞ አሉ፡፡ ሰማዕታት በግዘፋዊ ኑባሬ አሁን በዚህ ዓለም የሉም፡፡ ነገር ግን ዘለዓለማዊ ህላዌ አላቸው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ግዘፋዊ ኑባሬ እያላቸው እየበሉና እየጠጡ፣ እየሠሩና እየተንቀሳቀሱ እንደሌሉ የተቆጠሩም አሉ፡፡ የጠፋው ልጅ ወደ አባቱ ሲመጣ ‹ሞቶ ነበር›› የተባለው በዚህ ምክንያት ነው፡፡

እኛም ህልውናችንን መመዘን ከግዘፋዊ ኑባሬ ጋር ሳይሆን ከእግዚአብሔር ጋር ከመኖር አንጻር ነው፡፡ መጨነቅ ያለብንም ያለ ዘለዓለማዊ ህልውና እንዳንቀር እንጂ ግዘፋዊ ኑባሬያችንን እንዳናጣ አይደለም፡፡ ዘለዓለማዊ ህልውና ከእምነታችን፣ ከሠራናቸው ሥራዎችና ካተረፍነው መክሊት የሚመነጭ ነው፡፡

ክርስትና የመሞት እንጂ የመግደል ሃይማኖት አይደለም፡፡በክርስትና በመሞት እንጂ በመግደል አክሊል አይገኝም፡፡ ስንክሳራችንን የሞሉት ቅዱሳን በዓላውያን ተገድለው አክሊል ሰማያዊ ያገኙ ናቸው፡፡ ይህንን ያልተረዱ ሰዎች የሚያወጧቸው ስሞች ሊገርሙን አይገባም፡፡

ባይሆን የጎዱን መስሏቸው ታሪካዊና ሀገራዊ ስሕተት ለሚሠሩት ልናዝንላቸው ይገባል፡፡ አሁን ለሚሠሩት ስሕተት ግማሽ ምዕተ ዓመት እንኳን ሳይሞላ እንደሚፀፀቱበት ልንነግራቸው ይገባል፡፡ አሁን ‹‹ስቅሎ ስቅሎ›› የሚሉት የቤተ ክህነቱን ሰዎችም ይህንን ያስታውሱ፡፡ አይሁድ ጌታን ለሮማውያን አሳልፈው ከሰጡ ከ35 ዓመታት በኋላ ጌታን አሳልፈው የሰጧቸው ሮማውያን በጥጦስ አማካኝነት በእነርሱም ላይ ዘምተው እነርሱንም ከተማቸውንም አጥፍተዋቸዋል፡፡

እነርሱም፣ እነዚያም፣ እኛም ወደ ውጭ እያየን ችግሮቻችንን ከውጭ ከመፈለግ ይልቅ ወደ ውስጦቻችን እንመልከት፡፡ ውስጣችንን በደንብ ካየነው በውስጡ በኩል ውጩ በደንብ ያታየናል፡፡ በውጩ በኩል ግን ውስጡን ማየት አይቻልም፡፡ ቁም ነገሩ ‹ምን አሉን›› አይደለም፤ ምንድን ነን? ነው፡፡  እንዳንሆን እንጂ እንዳይሉን መከላከል አንችልምና፡፡ 

በተመስገንደሳለኝ (አዲስ አበባ)

– ከ253, 336 ከ42 ሳንቲም ዩሮ በላይ ኪሳራ ደርሷል ተብሏል

– የአእምሮ ችግር እንዳሌለበትም ተረጋግጧል

ፍትሕ ሚኒስቴር በረዳት አብራሪ ኃይለመድን አበራ ላይ የካቲት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ሌሊት የበረራ ቁጥር ET 702 የሆንን ቦይንግ አውሮፕላንን ከእነ 202 ተሳፋሪዎቹ ወደ ሮም በሚበርበት ወቅት ጠልፎ ሲውዘርላንድ አሳርፏል በማለት በከፍተኛው ፍርድ ቤት 3ኛ ወንጀል ችሎት ክስ መመስረቱን የፍትሕ ሚኒስቴር ምንጮቼ አረጋግጠውልኛል፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ጊኒ ቢሳው ውስጥ ለብዙ ጊዜ ሲተላለፍ የቆየው ፕሬዚደንታዊ ምርጫ እሁድ ሚያዝያ 5 ቀን፥ 2006 ዓም ይካሄዳል። የሀገሪቱ ሕዝብ እአአ በ2012 ዓመ መፈንቅለ መንግሥት ከተካሄደ ወዲህ አንድ ሕጋዊ መንግሥት እንዲመሠረት ሲጠብቅ ነው የቆየው።

ሰበር ዜና
የተነጠቁ መብቶቻችንን እናስመልሳለን!!!
የተነጠቁ መብቶቻችንን እናስመልሳለን በሚል መሪ ቃል ሰማያዊ ፓርቲ ሚያዚያ 19 እሁድ ታላቅ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ከጠዋቱ 4 ሰአት እስከ 8 ሰኣት ድረስ በጃንሜዳ ያደርጋል፡፡

ነጻነት ዋጋ ያስከፍላል። አገር ቤት ያሉ ወገኖቻችn እጅግ በጣም ከባድና ፈታኝ በሆነ ሁኔታ ለሰላም፣ ለዴሞክራሲ፣ ለሕግ የበላይነት ፣ ለነጻነትና ለኢትዮጵያ አንድነት፣ እልህ አስጨራሽ ትግል እያደረጉ ነው። «ሽብርተኞች ናቸው» በሚል በቃሊት ፣ በቂሊንጦ፣ ዝዋይ በመሳሰሉ ዘግናኝ እሥር ቤቶች እየማቀቁ ያሉ ፣ የሰላምና የዴሞክራሲ አርበኞች የሆኑ፣ ብርቅዬ የኢትዮዮጵያ ልጆችን መመልከቱ ይበቃል። አንዱዋለም አራጌ፣ ናትናኤል መኮንን፣ በቀለ ገርባ፣ […]

የሰማያዊ ፓርቲ ሚያዚያ 19 ቀን በአዲስ አበባ ሰልፍ እንደሚያደርግ አሳወቀ። ሰልፉ የሚደረግበት ቀን የዳግማይ ትንሳኤ ቀን ሲሆን፣ ለሰልፉ እውቅና ከአስተዳደሩ፣ ይገኝ አይገኝ ገና የታወቀ ነገር የለም። የአዲስ አበባ አስተዳደር ከአንድ አመት በፊት፣ የሰማያዊ ፓርቲ ከአራት ኪሎ እስከ ጥቅር አንበሳ ጋር እስካለዉ ሃዉልት ድረስ፣ ሰልፍ እንዲያደርግ እውቅና መስጠቱ፣ ይታወቃል። ለሰማያዊ ተፈቅዶ በነበረበት ቦታ፣ መጋቢት 28 ቀን […]

በስልጣን ላይ ያለው የኢህአዴግ መንግስት ሀገሪቱን ተቆጣጥሮ ስልጣን ከያዘ 23ዓመት አስቆጠረ። ይህን ያህል አመት በስልጣን ቆይቶ ህዝቡን በሰላም መምራት አልቻለም። ኢህአዴግ የኢትዮጵያን ህዝብ ነፃ አውጥቻለሁ፣ ሀገሪቱንም እያሳደኩ ነው..ቢልም ህዝቡ ግን፥ ኑሮ ተወደደ፣ ሀገራችን ተከፋፈለች፣ ዲሞክራሲ የለም፣ ሰብአዊ የመብት ረገጣ እየተፈጸመ ነው በማለት ማማረሩን ቀጥሎዋል። ከብዙ ኢትዮጵያውያኖች ጋር በተለያዩ ሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ የማይታረቅ ቅራኔ ውስጥ ገብቶዋል። […]

በታዋቂዉ የሰብአዊ መብት ተከራካሪ አቶ ኦባንግ ሜቶ የሚመራዉ የሶሊዳሪቲ ንቅናቄ፣ የሚሊዮኖች ድምድ ለመሬታ ባለቤትነት እና ለፍትህ እንቅስቅሴን እንደሚደገፍና የእንቅስቃሴዉም አካል እንደሚሆን ባወጣዉ መግለጫ ገለጸ። ሶሊዳሪቲ «እኛም ከሚሊዮኖች አንዱ ነን» በሚል ባወጣዉ መግለጫ፣ ኢትዮጵያውያን ሁሉ እንቅስቃሴዉን እንዲቀላቀሉና የድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስቧል። በግለሰብ ደረጃ ተራ ሰዎች ብንሆንም፣ ከተባበረንና ሚሊዮኖች ከሆነን ፣ ሊቋቋመን የሚችል ምንም ኃይል እንደሌለ የገለጸው የሶሊዳሪቲ […]

‘ዜጎች ነንና ፍትሓዊ ልማት ያስፈልገናል’ ሲንል አሰሩን። ‘ደማችን ገብረናልና ሰለማዊ ሰልፍ የመውጣት መብታችን ይከበርልን’ ስንል ደበደቡን። ‘ብዙ መስዋእት ከፍለናልና ነፃነታችንን አትንፈጉን’ ስንል ትጥቃችንን አስፈቱን። መብታችንን ለማስከበር ስንሞክር ገደሉን። ግን ይህን ሁሉ ወላጆቻችን፣ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን የከፈሉት መስዋእት ዓላማው ምን ነበር? ደርግን ደምስሶ ሌላ ደርግ መመስረት? ይሄማ ሊሆን አይችልም። ደርግ’ኮ ደርግ ያሰኘው ተግባሩ ነው። ደርግን የምንጠላው ደርግ […]

በሽብር ወንጀል ተከስሰው በክርክር ላይ የሚገኙት የሙስሊሙ ማኅበረሰብ ጥያቄዎች መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላትና ሌሎችም ተከሣሾች ለፍርድ ቤት ሲሰጡ የቆዩትን ቃል ዛሬ አጠቃልለዋል።

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የጀርመን የኤኮኖሚና የልማት ትብብር ሚኒስቴር ሀገሪቱ ለልማት የምታዉለዉን የርዳታ በጀት ማሳደጉን አስታወቀ። ምክር ቤት ከትናንት በስተያ በልማት በጀቱ ላይ ክርክር አካሂዷል። የተቃዉሞ ፖለቲከኞች ሀገሪቱ ከዓመታት በፊት ለአዳጊ ሃገራት የልማት ርዳታ የበለጸጉት በየዓመቱ እንዲያዋጡ ከተስማሙበት መጠን ለመድረስ ጀርመን ይቀራታል ሲሉ ተችተዋል።

ማንኛውንም መንገድ ተደቅመው ዳግም ወደ ሳውዲ አረቢያ የሚሰደዱ ወጣት ኢትዮጵያንኖች ባለፈው ህዳር ወር የሳውዲ ዓረቢያ መንግሥት በሀገሪቱ የሚገኙ ህገ ወጥ የሚለውን ስደተኞች እያሰረ ከሀገር ሲያባርር፤

ተክለሚካኤል አበበ (ቶሮንቶ)

የማርቆስ ብዙነህ ደብዳቤ፤

1-       “በርካታ ትምህርት ቤቶች፤ ዩኒቨርስቲና የመንግስት ተቋማት በሚገኙበት አካባቢ ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ የማይቻል በመሆኑ፤ የተጠየቀው የሰላማዊ ሰልፍ እውቅና ጥያቄ ተቀባይነት ያላገኘ መሆኑን እንገልጻለን” ይላል፤ በአዲስ አበባ መስተዳድር የሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቅ ክፍል ሀላፊ፤ በአቶ ማርቆስ ብዙነህ ማንደፍሮ፤ መጋቢት 23 ቀን 2006/2014 የተፈረመው ደብዳቤ፡፡ አንድነት፤ ሰልፉን ለማድረግ ያቀረባቸው መስመሮች 3 ሲሆኑ፤ ሶስቱም መስመሮች ከቀበናው የአንድነት ጽ/ቤት ይነሳሉ፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

ከሁለት ሣምንታት በኋላ አዲስ አበባ ላይ የሚያካሂዱት የእግር ጉዞ ዓላማ በተመሣሣይ ፆታ ግንኙነትና በሌሎችም “መጤ” ባሏቸው ልማዶች ወይም የባሕል ዘርፎች ላይ ግንዛቤ መፍጠር መሆኑን አዘጋጆቹ ማኅበራት አስታውቀዋል፡፡

ሁለቱ ማኅበራት ዛሬ በሰጡት መግለጫ የተመሣሣይ ፆታ ግንኙነት “ሊወገዝ የሚገባ ነው” ብለዋል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

መጋቢት 28 ቀን ይደረጋል ተብሎ የተጠበቀዉ የአንድነት የእሪታ ቀን ሰልፉ ፣ «ሰልፍ እንዲደረግ በታሰበበት ቀን፣ ሌሎች ዝግጅቶች ስላሉ በቂ ጥበቃ ልናሰማራ አንችልም» በሚል እውቅና ባለመስጠቱ ለሚያዚያ 5 ቀን መተላለፉ ይታወቃል። የሚያዚያ አምስቱን ሰልፍ በተመለከተ ምላሽ የሰጠው የአዲስ አበባ አስተዳደር፣ በሚያዚያ 5 ቀን ፣ ሩጫ ስለሚኖር ሰልፉ ለቅዳሜ ሚያዚይ 4 ቀን እንዲደረግ የሚጠይቅ ደብዳቤ ለአንድነት ፓርቲ […]

የአንደኛዉ የዓለም ጦርነት ከመጀመሩ በፊት አባታቸዉ የቀድሞዉ የጀርመን የቅኝ ግዛት አፍሪቃ ሃገር ከካሜሩን ወደ ጀርመን ሲገቡ፤ በደስታ ነበር አቀባበል የተደረገላቸዉ። ቆየት ብሎ ግን አፍሪቃዊዉ በቆዳ ቀለም ላይ የተመሰረተ ጥላቻን አዩ፤ እየቆዩም የቅኝ ግዛት ፊልሞችን በተመለከተ በሚሰሩ ፊልሞች ላይ አጫጭር ተዉኔቶችን እንዲተዉኑ ተደርገዋል።

ዩጋንዳ በዓለም አቀፉ የጦር ወንጀል ተመልካች ፍርድ ቤት በእስር የሚፈለጉትን የዓማፂው ቡድን «ሎርድ ሬዚስተንስ አሚ፣ » በምሕፃሩ « ኤል አር ኤ» መሪ ጆሴፍ ኮኒን ለመያዝ በጀመረችው እንቅስቃሴ ላይ ዩኤስ አሜሪካ ተባብራ ትሰራለች። በዚሁ ትብብሯ ቀደም ሲል 100 ወታደሮች የላከችው የዩኤስ አሜሪካ ፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ ባለፈው

የጀርመን ሩዋንዳ ትብብር በመግባባትና በጋራ ፍላጎት ላይ የተመረኮዘ እንደሆነ የሩዋንዳ ባለስልጣን አመለከቱ። የሩዋንዳ የትምህርት ሚኒስትር ዴታ ማቲያስ ሃርባሙንጉ ሀገራቸዉ በአሁኑ ወቅትም በትምህርት ዘርፍ ከጀርመን የዳበረ ልምድ እየተጠቀመች ነዉ ይላሉ።

በዓባይ ዳር በሚገኝ መንደር የምትኖር አንዲት ወፍ ነበረች፡፡ በዚያ ወንዝ ለሚዋኙም ሆነ ለሚሻገሩ ደምፅዋን አሠማምራ ትዘምር ነበረች፡፡ ደግሞ ላባዎቿ በኅብር ቀለማት የተሞሉ ነበሩ፡፡ እርሷ ላይ የሌሉ የአዕዋፍ ቀለማት አልነበሩም፡፡ ዝማሬና ዜማዋ ከቶ አይቀየሩም፡፡ በዚህም የተነሣ ዝማዋን ለምደውት አብረዋት የሚያዜሙ ብዙዎች ነበሩ፡፡ በዙሪያዋ ያሉ አዕዋፍ፣ ከወንዙ ለመጠጣት የሚመጡ አራዊት፣ በወንዙ ውስጥ የሚገኙ ዐሣት አብረዋት ያቀነቅናሉ፡፡ እንኳንና በነፍስ የሚኖሩ ሰዎችና በደመ ነፍስ የሚንቀሳቀሱ እንስሳት ቀርተው ዕጽዋት እንኳን እንደ ቅኔ ማኅሌት እንደ ገባ ደብተራ አብረዋት ያሸበሽባሉ፡፡ የእርሷ ዝማሬ ምንም የማይመስላቸው በወንዙ ዳር የተጎለቱት ድንጋዮች ብቻ ናቸው፡፡

እንዲህ እያለች ስትኖር ለዐቅመ ዕንቁላል ደረሰች፡፡ ጎጆ ልትቀልስም አሰበች፡፡ እንጨትና ሣር ሰብስባ ቤቷን የአንድ ጎጆ ባጥ ሥር መቀለስ ጀመረች፡፡ እንጨትና ሣር ደልድላ ጭድ በመካከሉ ልታስቀምጥ ስትል የሠፈሩ ልጆች መጡና በድንጋይና በእንጨት ፍርስርሱን አወጡባት፡፡ እርሷ ለመሥራት አንድ ወር የፈጀባትን እነርሱ ለማፍረስ አፍታም አልወሰደባቸው፡፡ ልጆቹ ጎጆዋን አፍርሰው የጀግንነት ስሜት ተሰምቷቸው እየሳቁና እየተደሰቱ ሄዱ፡፡ እርሷ ግን መከራዋን ታቅፋ ቀረች፡፡ መገንባት እንደ ማፍረስ መች ቀላል ነውና፡፡

መቼም ያለ ጎጆ አይኖር፤ ያለ ጎጆም ዕንቁላል አይጣል፡፡ ያለ ጎጆም ጫጩት አይፈለፈል፡፡ አማራጭ አልነበራትምና ዛፍ ላይ ሣርና እንጨቱን መሰብሰብ ቀጠለች፡፡ ልጆቹ ዐውቀው እንዳያፈርሱባትም በቅጠል ሸፈንፈን አደረገችው፡፡ ዕንቁላሉ መደላድል እንዲያገኝም ጭድ በመካከሉ ረበረበችበት፡፡ ነፋስ ወዝውዞ እንዳይጥለው በልጥ ከግንዱ ጋር ጠለፈችው፡፡ የፀሐይ ብርሃን እንዲያገኝም በስተ ምሥራቅ በኩል በር ሠራችለት፡፡ ከሥራዋ እፎይ ብላ ዕንቁላሏን ልትጥል ስትደላደል ግን እንደ አውሎ ነፋስ የሚያስገመግም ድምፅ ከወደ ዛፉ አካባቢ ሰማች፡፡ ድምፁም ወደ እርሷ ጎጆ እየቀረበ መጣ፡፡

ጎጆዋ ተነቃነቀ፡፡ የመሬት መንቀጥቀጥ የመጣ መሰለ፡፡ ቱር ብላ ወጣችና ዙሪያዋን እያንዣበበች ተመለካከተች፡፡ የሰማይ ስባሪ የሚያህል አሞራ እርሷ ጎጆ የሠራችበት ዛፍ፣ ያውም ጎጆው ከተንጠለጠለበት ግንድ ላይ ክንፉን እያማታ ቆሟል፡፡ አንዳች የሚበላ አጥንት በምንቃሩ ወሽቆ ከሥጋው ጋር ይታገላል፡፡ እርሱ ከሥጋው ጋር በታገለ ቁጥር የእርሷ ጎጆ ይነቃነቃል፡፡ ክንፉን ግራና ቀኝ ባማታው ቁጥር ኃይለኛ ነውጥ ይፈጥራል፡፡ ነውጡ በተፈጠረ ቁጥርም የእርሷ ጎጆ ይፈርሳል፡፡ አሞራው ጎጆዋን በግማሽ አፍርሶት ሄደ፡፡ እርሷም በዚያ አሳዛኝ ዝማሬዋ ታስተዛዝል ጀመር፡፡

እያስተዛዘለች እያለ አሞራው አሁንም እንደገና ከእርሱ ቁመት የማይተናነስ ሙዳ ሥጋ ይዞ መጣ፡፡ ለክፋቱ ደግሞ እዚያው ግንድ ላይ ቆሞ ቀሪውን የወፍ ጎጆ ይነቀንቀው ጀመር፡፡ አሞራው አራተኛ ጉርሻ ላይ ሲደርስ ጎጆው ሙሉ በሙሉ ፈረሰ፡፡ የወፏም ዝማሬ ወደ እንጉርጉሮ ተለወጠ፡፡የት ትሂድ? የትስ መሄጃ አላት? ወፍ ባትሆን ተመኘች፡፡ ግን ወፍ ናት፡፡ አሞራው ለመብላት ሲል ጎጆዋን ያፈርሳል፡፡ እርሷ ግን ጎጆዋን እሠራ ብላ የአንዲት ፍሬ ፍርካሽ እንኳን ለመቅመስ ዕድል አልነበራትም፡፡

አዝና አዝና ስትጨርስ የግድ ነውና ጎጆዋን ለመሥራት እንደገና ፈለገች፤ እንደገና አሰበች፡፡ እንደገናም ሣርና እንጨት፣ ቅጠልና ጭድ ፍለጋ መንከራተት ጀመረች፡፡ የነበረው እንዳልነበረ ሆኗልና እንደገና ሀ ብላ ወጠነች፡፡ አሁን ዜማዋ ከፊል እንጎርጉሮ፣ ከፊል ምሬት፣ ከፊል ደግሞ ተስፋ ሆኗል፡፡ ተስፋ ያልቆረጠችው ተስፋ ያለው ነገር አግኝታ አይደለም፡፡ ተስፋ ከመቁረጥ የሚሻል ሆኖ እንጂ፡፡

አሁን ከሰውም ከእንስሳትም ርቃ ዓባይ ዳር በሚገኝ የደንገል ዛፍ ላይ ጎጆዋን መሥራት ጀመረች፡፡ ምናልባት በዓለም ከመኖር ብሕትውናው ይሻል ይሆን ብላ፡፡ ‹‹ወይከውን ከመ ዕጽ እንተ ትክልት ኀበ ሙሐዘ ማይ – በወንዝ ዳር እንደተተከለች ተክል ይሆናል፤ እንተ ትሁብ ፍሬሃ በበጊዜሃ – ፍሬዋን በየጊዜው እንደምትሰጥ፤ ወቆጽላኒ ኢይነግፍ – ፍሬዋም እንደማይደርቅ›› የሚለውን አስባ፡፡

እንደ ገና ድካም እንደገና ልፋት፡፡ ጎጆዋን ልትቀልስ፣ ዕንቁላሏን ልትጥል፤ ጫጩት ልትፈለፍል፡፡ ከመጀመሪያው ቤት ሁለተኛው፣ ከሁለተኛውም ሦስተኛው ከበዳት፡፡ እንጨቱ እየተማገደ፣ ሣሩ እየተመደመደ፣ ጭዱም እየተወሰደ አልቋል፡፡ ለምለሙ ጊዜ አልፎ የበጋው ደረቅ ወቅት መጥቷል፡፡ በቅርብ ይገኝ የነበረው ነገር ሁሉ ርቋል፡፡ ግን ምን ይደረጋል፡፡  

ክንፏን እስከሚያማት ድረስ ባክና በሰበሰበችው እንጨት፣ ሣርና ጭድ ጎጆዋን ለሦስተኛ ጊዜ ቀለሰች፡፡ አንድ ሦስት ቀን የቀደመው መዓት ይመጣል ብላ ብትጠብቅ ምን የለም፡፡ እንዲህ ከሰውም ከእንስሳም መራቁ ይሻላል ብላ በምርጫዋ ተደሰተች፡፡ አንድ አንድ እያለችም ዕንቁላሏን መጣል ጀመረች፡፡ ችግሩ ግን ያን ጊዜ መጣ፡፡ እርሷ ዕንቁላሏን ጥላ ምግብ ፍለጋ ሄዳ ስትመለስ ዕንቁላሏን አታገኘውም፡፡ ሁለት ሦስት ቀን ወድቆ ይሆናል ብላ አሰበች፤ ጥፋቱም የእርሷ እንደሆነ አመነች፡፡ እንዳይወድቅ ለማድረግም ጎጆዋን እንደገና አጠባበቀች፡፡ በአራተኛው ቀን ግን አሁንም ዕንቁላሏን አላገኘችውም፡፡ ፈለገችው፡፡ እንዳች ስባሪ በአካባቢው አላገኘችም፡፡ በአምስተኛው ቀን ዕንቁላሏን ጥላ ከጎጆዋ ወጣችና እልፍ ብላ በሌላ ዛፍ ላይ ተቀምጣ የሚሆነውን ማየት ጀመረች፡፡

እነሆ ጉዱ፡፡

እርሷ ወጣ ከማለቷ አንድ ዕባብ በግንዱ ላይ እየተሳበ መጣ፡፡ ዕባቡ የመጣው ከወንዙ ዳር ነው፡፡ አስጠሊታ ራሱን ወደ ጎጆዋ አዝልቆ ዕንቁላሏን ሰለቀጠው፡፡ ነፍስ አልነበራትም እንጂ ድንጋጤው ነፍሷን ያወጣው ነበር፡፡ አሁን የከፋ አደጋ መጣ፡፡ ቤቷ አይደለም የፈረሰው፤ ዕንቁላሏ ነው የሚበላው፡፡ ምትኳ፣ ዘሯ፣ ተስፋዋ፣ ሀልወቷ፣ ኑባሬዋ ነው የሚበላው፡፡ ዕንቁላል እንዳትጥል አልተከለከለችም፤ የምትጥለው ግን ለሌላ ሆነ፡፡ እርሷ አንድ ቀን ዕንቁላል መጣል ታቆማለች፡፡ ያን ጊዜ ህ ዕንቁላል የለመደ ዕባብ እርሷን መብላት ይጀምራል፡፡ ከሁሉም ተገላገልኩ ብላ የመጣችበት ቦታ ከሁሉም የባሰ ሆነ፡፡

በረረረች፣ ከነፈች፣ ወጣች፣ ወረደች፣ ከነፋሱም ጋር ሄደች፣ ከነፋሱም በተቃራኒም ነጎደች፡፡ መሬት ወረደች፣ ወንዝ ውስጥ ገባች፡፡ በመጨረሻ ደከማት፡፡ ሲደክማት አንድ ዛፍ ላይ ቆማ እንዲህ እያለች ታንጎራጉር ጀመር፡፡

ኦ እለሎ፣ ኦ እለሎ

ኦ እለሎ፣ ኦ እለሎ

ወዴት ሄጄ ልኑር

ወዴት ሄጄ ልሥራ፤

ባጡ ሥር ስሠራ

ልጆቹ መከራ፣

ዛፉ ላይ ስሠራ

አሞራው መከራ፣

ወንዙ ዳር ስሠራ

ዕባቡ መከራ፡፡

ወዴት ሄጄ ልኑር፣

የት ሄጄ የት ልሥራ፤

የት ውዬ የት ልደር፤

 © ይህ ጽሑፍ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት የወጣ ነው

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሁለተኛውን የሕዝብ ንቅናቄ መጀመሩ የሚታወስ ነው። ፓርቲው ከዚህ ቀደመ “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” በሚል መሪ ቃል የሕዝባዊ ንቅናቄ መድረኮች አዘጋጅቷል። አሁን ደግሞ “የሚሊዮኖች ድምፅ ለመሬት ባለቤትነት” በሚል መሪ ቃል ፕሮግራሙን ይፋ አድርጓል። ባለፈው እሁድ መጋቢት 28 ቀን 2006 ዓ.ም በደሴ ከተማ ፕሮግራሙን በሰላማዊ ሰልፍ አከናውኗል። በደሴ ስለተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍና “የሚሊዮኖች ድምፅ […]

የማርቆስ ብዙነህ ደብዳቤ፤ 1- “በርካታ ትምህርት ቤቶች፤ ዩኒቨርስቲና የመንግስት ተቋማት በሚገኙበት አካባቢ ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ የማይቻል በመሆኑ፤ የተጠየቀው የሰላማዊ ሰልፍ እውቅና ጥያቄ ተቀባይነት ያላገኘ መሆኑን እንገልጻለን” ይላል፤ በአዲስ አበባ መስተዳድር የሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቅ ክፍል ሀላፊ፤ በአቶ ማርቆስ ብዙነህ ማንደፍሮ፤ መጋቢት 23 ቀን 2006/2014 የተፈረመው ደብዳቤ፡፡ አንድነት፤ ሰልፉን ለማድረግ ያቀረባቸው መስመሮች 3 ሲሆኑ፤ ሶስቱም መስመሮች […]

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ለመጋቢት 28 ቀን 2006 ዓ.ም ሊያደርገው ለነበረው ሰላማዊ ሰልፍ የመስተዳድሩ የሰላማዊ ሰልፍና ማሳወቂያ ክፍል ዘግይቶ በጻፈው ደብዳቤ የሰልፉ ቀን በሌላ ፕሮግራም መያዙን በመጥቀስ የቀን ለውጥ እንዲደረግ መጠየቁ አይዘነጋም፡፡ ፓርቲው የቀረበውን አስተያየት በመቀበል ሰልፉ ለሚያዚያ 5 ቀን 2006 ዓ.ም እንዲደረግ መወሰኑን በመግለጽ ለመስተዳድሩ አሳውቋል፡፡ሆኖም መስተዳድሩ ዕለቱ በታላቁ ሩጫ መያዙን በመጥቀስ ለፖሊስ ጥበቃ […]

የሚሊዮኖች ድምጽ ንቅናቄ በአገሪቷ ዉስጥ ባሉ አሥራ አራት ከተሞች፣ ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች እንደሚያደርግ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። እንቅስቃሴ በደሴ ሰላማዊ በማድረግ የተጀመረ ሲሆን፣ በሌሎች ከተሞች ከአንድነት ጽ/ቤቶች ወደ አደባባይ በሚሄድ ትይንተ ሕዝቦች በማድረግ ይቀጥላል። በደሴ ከተማ የተደረገዉን እንቅስቃሴ በደንቬር የሚገኙ ኢትዮጵያዉያን ስፖንሰር ያደረጉት ሲሆን፣ በአዲስ አበባ የሚደረገዉን የመጀመሪያው እንቅስቅሴን ላስ ቬጋሶች፣ ሃዋሳ አትላንታዎች፣ ድሬደዋን የደብተራ ፓልቶክ ክፍል፣ […]

«ከምዕራብ ሸዋ ተፈናቅለው በፌዴሬሽኑ አፈ ጉባዔ አግባቢነት የተመለሱት ዜጎች መሬታቸውን በሃይል ተነጠቁ» ሲል ፍኖት ዘገበ። “ከሰላሳ የማያንሱ የምዕራብ ሸዋ ዞን አምቦ ዳኖ ወረዳ ባጅላ ዳሌ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ነዋሪዎች «ወደ ክልላችሁ ተመለሱ » ተብለው መሬታቸውን ለመነጠቅ መቃረባቸውን ለማመልከት አዲስ አበባ በመምጣት የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ካሳ ተ/ብርሃንን ካናገሩ በኋላ አፈ ጉባኤው ‹‹ወደ ቀዬአችሁ […]

ኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢና በአካባቢዋ በሚገኙ ስደተኞች ላይ በመንግሥቱ እየተፈፀመ ነው የሚሉት አፈሣና እሥራት በእጅጉ እያሣሰባቸው መሆኑን ስደተኞቹ እየገለፁ ነው፡፡

የኬንያ መንግሥት በሃገሪቱ ውስጥ እየደረሱ ያሉት ፍንዳታዎች ለፀጥታዬ አደጋና ሥጋት ደቅነዋል በሚል ስደተኞች ወደዚያ ሲገቡ ወደየተመደቡባቸው ሠፈሮቻቸው እንዲመለሱ በቅርቡ ማስታወቂያ አውጥቶ እንደነበረ ይታወሣል፡፡

ከዚያ ማስታወቂያ ወዲህ ባለፉት ከአምስት እስከ ሰባት በሚሆኑ ቀናት ብዙ ስደተኞች እየታፈሱና እየተንገላቱ መሆኑ ይሰማል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

የደቡብ ሱዳን ገዥ ፓርቲ – የሱዳን ሕዝብ አርነት ንቅናቄ – ኤስፒኤልኤም ውስጣዊ ችግር ከተፈታ የሃገሪቱ ችግርም ሊፈታ ይችላል ሲሉ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትርና የኢህአዴግ ሊቀመንበር ኃይለማርያም ደሣለኝ ተናግረዋል፡፡

ፓርቲው ራሱን ለሚገመግምበትና ለሚያይበት ቀጣይ ስብሰባ መንገድ የሚጠርግ ውይይት አዲስ አበባ ላይ ተከፍቷል፡፡

ውይይቱን የሚያስተባብሩትና የሚመሩት የኢትየጵያው ገዥ ፓርቲ ኢህአዴግና የደቡብ አፍሪካው ገዥ ፓርቲ የአፍሪካ ብሔራዊ ምክር ቤት – ኤኤንሲ ሲሆኑ በኢትየጵያ በኩል የጠቅላይ ሚኒስትሩ ልዩ አማካሪ አቶ በረከት ስምዖን በዚሁ ኃላፊነት ተሰይመዋል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የእስክንድር ፍሬውን ዘገባ ያዳምጡ፡፡

 

ባለፉት አርባ ዓመታት አፍሪካ በካፒታል ሽሽት ምክንያት ከ103 ትሪሊዮን ዶላር በላይ ማጣቷ ተገለፀ፡፡

አፍሪካ ይህንን ገንዘብ ማስቀረት ችላ ቢሆን ኖሮ የሚሌኒየሙን የልማት ግቦች ከማሳካት የበለጠ ብልፅግና ይኖራት ነበር ተብሏል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የመለስካቸው አምፅን ዘገባ ያዳምጡ