የልማት ርዳታዎችና መጠነኛዉ ዉጤት

የጀርመን የኤኮኖሚና የልማት ትብብር ሚኒስቴር ሀገሪቱ ለልማት የምታዉለዉን የርዳታ በጀት ማሳደጉን አስታወቀ። ምክር ቤት ከትናንት በስተያ በልማት በጀቱ ላይ ክርክር አካሂዷል። የተቃዉሞ ፖለቲከኞች ሀገሪቱ ከዓመታት በፊት ለአዳጊ ሃገራት የልማት ርዳታ የበለጸጉት በየዓመቱ እንዲያዋጡ ከተስማሙበት መጠን ለመድረስ ጀርመን ይቀራታል ሲሉ ተችተዋል።