በመፍቀሬ-ሩሲያ አማፅያን ታግተው የቆዩ የአውሮጳ የፀጥታ እና የትብብር ድርጅት በእንግሊዘኛ ምኅፃሩ «ኦኤስሲኢ» ታዛቢዎች ትናንት ምሽት ጀርመን መዲና በርሊን ገቡ። እንደ አማፅያኑ፤ ታጋቾቹ ነጻ የተለቀቁት ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ነዉ።

አንድነት በኦሮሚያ ክልልና በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በሚማሩ የኦሮሞ ተማሪዎች ላይ የመንግስት ሐይሎች በወሰዱት እርምጃ ቁጥሩ በውል ያልታወቀ የሰው ህይወት በመቀጠፉና ብዙዎችም ለአካል ጉዳት በመዳረጋቸው የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን በመግለጽ ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ ለማበጀት መወያየት የግድ መሆኑን አስምሮበታል፡፡ በተማሪዎችና በተለይም በአምቦ ከተማ ህዝብ ላይ የተፈጸመው የመብት ጥሰት ምን ያህል መሆኑን ለማወቅ በቀጣዩ ሳምንት አንድነት የራሱን ልዑክ ወደ […]

መፍቀሬ-ሩሲያ አማፅያን የታገቱ የአውሮጳ የፀጥታ እና የትብብር ድርጅት ታዛቢዎች ዛሬ ተለቀቁ። እንደ አማፅያኑ፤ ታጋቾቹ ነጻ የተለቀቁት ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ነዉ።

በካዛንቺስ አካባቢ የቅስቀሳ ስራ ይሰሩ የነበሩ አባላት የሚሰሩትን ለመዘገብ ከቀስቃሽ ቡድኑ ጋር የነበረው የፍኖተ ነጻነት ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ነብዩ ሐይሉ በታሰረበት የስድስተኛ ፖሊስ ጣብያ ከተያዘበትና በፍርድ ቤት ከቀረበበት ክስ ጋር በማይገናኝ ጉዳይ ሲቪል በለበሱ ደህንነቶች ምርመራ እንደተደረገበት ምንጮቻችን ጠቆሙ፡፡ የአዲስ አበባ መስተዳድር እውቅና ለሰጠው ሰላማዊ ሰልፍ የቅስቀሳ ስራ ለመስራት ወደ አራት ኪሎና ካዛንቺስ አቅንተው የነበሩት […]

አንድነት ሰላማዊ ሰልፉን በማስመልከት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠ የዕሪታ ቀን በሚል መሪ ቃል አንድነት ነገ ለሚያከናውነው ሰላማዊ ሰልፍ በጽህፈት ቤቱ ጋዜጣዊ መግለጫ በመስጠት የአዲስ አበባ ህዝብ በነቂስ በመውጣት በሰልፉ እሪታውን እንዲያሰማ ጠይቋል፡፡የመግለጫውን ሙሉ ቃል ያንብቡ፡፡ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ) እሁድ የሚካሄደው የተቃውሞ ሠልፍ ላይ የአዲስ አበባና አካባቢዋ ኗሪዎች […]

የመሬት ጥያቄ ብዙ መስዋዕት የተከፈለበት ቢሆንም አሁን በባሰ ሁኔታ ወያኔ ከሁሉም ዜጋ ነጥቆ በግሉ አድርጎታል። ማንም ኢትዮጵያዊ የሃገሩ፣ የመሬቱ ባለቤት አይደለም። ከዚህ የባሰ ዜጎችን የማዋረድ ተግባር የለም። አባቶቻችን መሬታቸውን ለባዕድ አንሰጥም በማለት ህይወታቸውን ከፍለው አቆይተውናል። ዛሬ እኛ የራሳችን መሬት ባለቤት እንዳንሆን ሁላችንንም መሬት አልባ ያደረገን ስርዓት ዜጎችን አፈናቅሎ ካድሬዎቹን በመሬት ችብቸባ አሰማርቷል። ለባዕዳን ከመሸጥ አልፎ […]

ጤና ይስጥልኝ! ኢትዮጵያዉያን ወገኖቼ፤ ሰላም ለእናንተ ይሁን! ተክሌ በቀለ እባላለሁ፡፡ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚደንት ነኝ፡፡ የአንድነት የፖለቲካ አላማ ብዝሃነቷ የተጠበቀ፣ የግለሰብና የቡድን መብቶች የተከበሩባት፣ የበለጸገች፤ የአለምን ስልጣኔ እና እድገት የተቀላቀለች ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን መገንባት ነዉ፡፡ ለዚህ አላማ መሳካትም የምንከተለዉ ስልት ፍፁም ሰላማዊና ህጋዊነትን የተላባሰ አካሄድ ነዉ፡፡ በእዉቀት እና ጥበብ ላይ የተመሰረተ አማራጭ […]

One of this year plans was to awake the public at large into participating in politics without a fear. Of all the methods we engaged in demonstration was one of it. On April 27, 2014, we decided to have the protest. Our enquiries are very clear: TPLF/EPRDF is incapable of ruling so it has to leave power and religious interference by the ruling party has to stop, forcing citizens to leave their neighborhood because of their ethnic group is a crime and that has to stop and forcing citizen to leave and demolishing their houses without any compensation because of ‘development’ is unlawful and negligent. Those are the issues we mainly raised in the protest.
When the day and place first decided, we wrote a letter for Addis Ababa City administration office to let them know about it. Within few hours they sent us a letter that suggests a change of date for a vague reason which is stated as “because there will be international meetings in the city” which is as well far from the truth. Then we had to send another letter to inform them that their reply was unacceptable for it lacks clarity and that conflict with the 1987’s proclamation of public gatherings. While three of the demonstration organizing committee delegates went to give the letter, the officer at desk snubbed and left them at the office with the letter. “He,” they said, “was scared and unconfident to receive the letter. Finally they counted witnesses and left the letter and returned back.
A day, two days . . . passed. According to the 87’s proclamation “unless you’re given an excuse to change because of a vivid reason in 12 working hours it will be considered as officially accepted and known. Therefore in regards to that we started to act; prepared all the flyers to promote the protest, give orientations to members and etc. Monday was the first time we started our promotion. There were 10 teams in all sub cities. Later in late afternoon two teams who went out to Kasanchiz and Gulele got caught by the police and were detained. In the morning they appeared to the court house. Six of them at Arada court house and the other 7 at Mexico court house. The first six were presented and without any dialogue nor argument they were sent back to prison to be brought back in 7 days as requested by the police; those who were presented at Mexico court house were bailed out 1000 birr each.

The next day a letter came from the city office. It issued a filling of a form about the demonstration. Then the organizers thought it was right and went. Yet during the process the officer told them to change the place from Janmeda to other place. They couldn’t accept the change and left the office. It took almost two days to settle the argument about the place. At last the organizing committee and the executive members decided to change the place to Signal Meda(woreda 8 meda) because of a road to Janmeda under construction. Though on Thursday about 14 members counting 2 executives were arrested while distributing flyers and promoting the demo’.
On Friday again police arrested some of our members who went out promoting the demo’. Six members and two cars with all the electronics that were about to be used were detained. When this happened three executive members: the chairman Eng. Yilkal Getnet, Ato Sileshi Feyisa(Vice Chairperson and Demo’ Organizing Committee Assistant Convener) and Ato Brhanu T/Yared(Public Relations Head and Demo’ Organizing Committee Convener) went to discuss the matter with the officials yet as soon as they got out of the office three of them were detained and had to walk to Yeka police station guarded with many polices. The scene looked like some sort of terrorists got caught.
Late at night that evening Eng. Yilkal Getnet was forced to leave the prison separately from the other two comrades. However Yilkal refused to go out and had to go through a long argument with the officials at the station. He insisted not to leave because there was no reason to why he should separately return home while they were caught and had been working together. Nevertheless it was “meaningless and was not productive” so he came back around 09:00pm in the evening.

Consequently supporters, members and leaders of Semayawi(Blue) Party determinedly insisted on keep going and make sure that the demonstration would go as planned even though more than 30 members including 4 executives remained in prison. It was believed at the time that the ruling party was trying to break us down. The regime wanted us to call off the demonstration. In fact not only the regime but also some political personalities didn’t expected Semayawi would execute the event while many of its members and leaders were still in prison.
Conversely on Sunday morning we went out. It was very colorful and loud. All the participants were whistling, blowing ‘turumba’(trumpet), shouting out loud and experience the free breath of fear free environment. The protest went like that until it got to Adwa Square. At the square the police prohibited the crowed from going to the route Semayawi decided to go through. There happened the extraordinary during the confrontation with the police. Unlikely many of the partakers in the protest stood firm and demanded a way through to Balderas which the police debarred. None went back – many joined the push-forward at some point the police could not handle the pushing forward so they were about to start beating then at that point someone at the front told the crowd to kneel down. It was done and the police was confused and couldn’t do a thing. Then when it was calm the confrontation started all over again. While the struggle to pass through the way was going on some assigned representatives of the party were dealing with the police officers. They explained and showed them the form. After a while the route was open and Eng. Yilkal, who were in the middle of the confrontation himself, wave his hand to move forward and all screamed of joy and moved on for all courageously stood for their rights and earned it.
The demonstration was so peaceful and boldly stated all the problems in the country and underlined the incapability of the ruling party to lead this big nation and it need to leave power. Many protesters had been voice of the millions. It was such a symbolic protest that gives lesson to all and motivates many to be brave enough to stand for their rights and to fight for it peacefully yet assertively.
When this report is written about 26 were still arrested and demanding justice because they have been asked a bail about 5000br and an identity card of a person who works for government organizations for 6 prisoners each; 1600br and an ID for 14 prisoners each, and 1000br and an ID for 6 prisoners each in total 58,400br asked for bailing them out. The arrested claimed and argued that they haven’t done anything against the law and they should be freed without any bail or anything like that.
With all the drama, in general, Semayawi (Blue) party executed its second demonstration successfully in regards to its objectives which are mentioned over. It cost the party a lot yet gained even more. Many of us needed to spend a week or two in prison, some are still in jail to motivate and awake the people and make their voice be heard. Many invested out of their pocket yet be happy for all sees hope in the progress.

The change is sure to come and we are ready to carry the load and the burden.

Ethiopia rises and all will be fine!
Semayawi(Blue) Party!

ሚያዚያ 26 ቀን በአዲስ አበባ ለሚደረገዉ ሰላማዊ ሰልፍ ቅስቀሳው ዛሬም በደመቀ ሁኔታ መካሄዱን ከስፍራዉ የደረሰን ዜና ያመለክታል። ትላንት የተደረጉ የመኪና ቅስቀሳዎች ወቅት መኪናዎችን እየተከታተሉ፣ በርካታ ሰዎች በመሰብሰባቸው፣ ቅስቀሳዎቹ በራሳቸው እንደ ሰልፍ የነበሩበት ሁኔታ የነበረ ሲሆን፣ ይህ በሕዝቡ ዘንድ ያለው መነሳሳት ያላስደሰታቸው ገዢዎች፣ ሕግ መንግስቱን በመናድ ፣ በመኪና መቀስቀስ አትችሉም በሚል፣ ትላንት ማምሻዉን መኪናዎችን ወደ ማገትና […]

አንድነት በደራሼ ወረዳ በጊዶሌ ከተማ ለሚያደርገው ሰላማዊ ሰልፍ እውቅና አማግኘቱን ለማረጋገጥ ችለናል።፡ የፊታችን እሁድ ሚያዚያ 29 ቀን ለሚረርገው ህዝባዊ የተቃውሞ ሰልፍ የክልሉ አስተዳደር እውቅና መስጠቱን ተከትሎ በሰላማዊ ሰልፉ የወረዳውና የአካባቢው ነዋሪ እየደረሰበት የሚገኘውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት፣የመልካም አስተዳደር እጦትና የካድሬዎች ጭቆናን በይፋ የሚቃወምበት እንደሚሆን ፓርቲው አስታውቋል፡፡ በ2002 የደራሼ ወረዳ ሕዝብ በራሱ አነሳሽነት ሰልፍ ወጥቶ የነበረ ሲሆን፣ […]

ጤና ይስጥልኝ ! ግዛቸው ሽፈራው እባላለሁ። የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሊቀመንበር ነኝ። አንድነት በኢትዮጵያ ሕጋዊ ፍቃድ አግኘቶ፣ በአገሪቷ ባሉ ክልሎች ሁሉ ሰላማዊ በሆነ መንገድ የሚንቀሳቀሰ ድርጅት ነው። አንድነት ከማንም ኢትዮጵያዊና ድርጅት ጋር ፀብ የለዉም። የአንድነት ፖለቲካ የኢትዮጵያዊነት፣ የፍቅርና የመቻቻል ፖለቲካ ነው። አላማችን ፣ የበለፀገች፣ ልጆቿ፣ በዘር ፣ በሃይማኖት፣ በጾታ ልዩነት ሳይደርገባቸው እኩል የሆኑባት፣ አንድነቷና […]

የሶማሊያ የወደፊት ዕጣ ፈንታ ምናልባት በአመዛኙ የሚንጠላጠለው ምናልባት በብሔራዊ ጦሯ ላይ ሳይሆን አይቀርም እየተባለ ነው፡፡

ይሁን እንጂ አንድነት ያለውና የተደራጀ ኃይል የመፍጠር ነገር ለመንግሥቱ ግዙፍ ፈተና፣ ለሃገሪቱ ሰላምም አስጊ መሰናክል ሊሆን እንደሚችልም የሚጠቁሙ አሉ፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

 

ይህ ዓመት ለአሜሪካ ጃዝ ሙዚቃ ትልቅ ዓመት ነው፡፡

ይህንን ቀን በታላቅ ጉጉት ሲጠብቁ የኖሩ ብዙ ናቸው፡፡

የብሉ ኖት ቀረፃ መለያ ከተፈጠረ እነሆ ሰባ አምስት ዓመት ሆነው፡፡

በትንግርታዊው ብሉ ኖት የልደት ዓመት ላይ የተጠናቀረውን የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ኦሮሚያ መስተዳደር በተለያዩ ዩንቨርስቲዎች ፤ የኦሮሞ ብሔር አባላት የሆኑ ተማሪዎች ፣ የኢትዮጵያ መዲና አዲስ አበባ ፣ ከኦሮሚያ ክልል ቦታ በመጨመር የምትሰፋበትን አካሄድ በሰላማዊ ተቃውሞ ሲገልፁ፤ ከፖሊስ ጋ በተፈጠረዉ ግጭት ቢያንስ 11 መገደላቸውን መንግስትን ጠቅሶ አሶሲየትድ ፕረስ ከአዲስ አበባ ዘግቧል።

የአፍሪቃ ግብርና ሚኒስትሮች ጉባኤ በአፍሪቃ አዳራሽ በመካሄድ ላይ ይገኛል። በተመድ ለአፍሪቃ ልማት በተለያዩ ዘርፎች እንቅስቃሴዎች መደረጋቸዉን ተከትሎ የዘንድሮዉ የጎርጎሪዮሳዊ ዓመት ደግሞ የግብርናዉ ዘርፍ ትኩረት እንዲያገኝ ተወስኗል።

በደቡብ ክልል ደራሼ ወረዳ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የፊታችን እሁድ ለሚያደርገው ህዝባዊ የተቃውሞ ሰልፍ የክልሉ አስተዳደር እውቅና ሰጥቷል፡፡ በሰላማዊ ሰልፉ የወረዳውና የአካባቢው ነዋሪ እየደረሰበት የሚገኘውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት፣የመልካም አስተዳደር እጦትና የካድሬዎች ጭቆናን በይፋ የሚቃወምበት እንደሚሆን ፓርቲው አስታውቋል፡፡

ዛሬ ሀገራችን ኢትዮጵያ ካለችበት የኢህአዲግ ስርአት ለመላቀቅ እና ከገባችበት ፖለቲካዊ ማህበራዊ እና ኢኮኖሜያዊ ውድቀት ወጥታ ህዝቡም ከወያኔ ስርዓት ተላቋ ወደ ተሻለ እና ወደ ተረጋጋ ሕይወት ለመድረስ ሁሉም ዜጋ የበኩሉን ድርሻ መወጣት እና በሁሉም አቅጣጫ እና በሚችለው መንገድ መታገል ይጠበቅበታል:: ዛሬ ላይ ወያኔ ኢህአዲግ የእምነታችንን ነጻነት እያሳጣን የዜጎቻችን ሰብዓዊ መብት እየረገጠ እና የዜግነት ክብራችንን እና ነፃነታችንን […]

እነደሁልጊዜው ሁሉ ህገ መንግስታዊ መብቶቻችን መጠየቅ እንቀጥላለን በማሰርና በመደብደብና በመግደል የአገር ችግር አይፈታም
ክቡራን የዞን ዘጠኝ ነዋሪያን
ሳምንቱ በአራማጅነት ቆይታችን ከነበሩን ጊዜያት መካከል በጣም ከባድ ሆኖ አለፈ። የዞን ዘጠኝ አባላትና ወዳጅ ጋዜጠኛ ጓደኞቻችን ከታሰሩ 7 ቀናትን አሳለፋ፡፡ በሳምንቱ ውስጥ ቤተሰብና የህግ ባለሞያ ሳያገኛቸው እሁድ ቀን ፍርድ ቤት መቅረባቸውን ከመስማት ውጪ አያያዛቸውንም ሆነ ያሉበትን የጤንነት ሁኔታ ለማወቅ አልተቻለም፡፡ እስካሁንም ቤተሰብም ሆነ የህግ ባለሞያ እነዲያያቸው አልተፈቀደም፡፡ ይህ በግልጽ ህገ መንግስቱን የሚጥስ የምርመራ ሂደት በማእከላዊ ሲካሄድ አዲስ አይደለም፡፡ ከዚህ በፌት የነበሩ የፓለቲካ እስረኞችም በተመሳሳይ ሁኔታ የመታየት መብታቸው ከማእከላዊ ጀምሮ ተነፍጎ አሁንም ቤተብሰብም ሆነ ወዳጅ እነዳይጎበኛቸው የተደረጉ እንዳሉ ይታወቃል ፡። ዞን 9 ከመጀመሪያ ዘመቻዎች አንስቶም ህገመንገስቱ አንዲከበረ ስንጠይቅ መቆየታችን ይታወቃል፡። ይህ መሆኑ ሳያንስ የመሰብሰብና ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብታቸውን ሲጠቀሙ የነበሩ (ሶስተኛው የዞን ዘጠኝ ዘመቻ) የኦሮሞ ተወላጅ ተማሪዎች እስር የአካል ጉዳትና ሞት እየደረሰባቸው ይገኛል፡፡ይህ በመላው አገሪትዋ እየታየ ያለውን ተቃውሞ መንግስት ምላሽ እየሰጠ ያለበት መንገድ አሳሳቢ አስፈሪና አሳፋሪ ከመሆኑም በላይ ሳምንቱንም በሰብአዊ መብቶች ረገድ በጣም የከፋ ያደርገዋል፡፡
መንግስት የዞንዘጠኝ አባላትንና ጋዜጠኞቸን ሰርተዋል ብሎ ያቀረበው ወንጀል በማህበረሰብ ሚዲያ በመጠቀም ህዝብን ለብጥብጥ ማነሳሳት ነው ሲል የመንግስት ቃል አቀባይ በበኩላቸው በጻፉት ሳይሆን በወንጀል በመሰማራታቸው ነው የታሰሩት ብለዋል፡፡ ወንጀሉ ፓሊስ እንዳቀረበው ደግሞ በማህበረሰብ ሚዲያ ብጥብጥን የማንሳት ተግባር ከአገር ውጨ ከሚገኝ ራሱን ከሰብአዊ መብት ብሎ ከሚጠራ ተቋም ጋር ተባብረው ብጥብጥ ማስነሳት ነው ብሎታል ፡፡ ክሱ በአጭሩ ሁለት ነገሮችን ይይዛል፡፡ አንደኛው በማህበረሰብ ሚዲያ ብጥብጥ ማስነሳት ሲሆን ሁለተኛው በሃሳብና በገንዘብ ከውጪ ድርጅቶች ጋር መተባበር ነው ፡፡
ማህበረሰብ ሚዲያ ብጥብጥ?
በማህበረሰብ ሚዲያ ብጥብጥ ማንሳት የሚል ክስ ለማቅረብ በማህበረሰብ ሚዲያ ብጥብጥ የሚያስበሱ መልእክቶቸን ማስተላለፍ ያስፈልጋል፡፡ በዚህ ረገድ ማንኛውም የዞን 9 ነዋሪያን እነደሚመሰክሩት ህገ መንግስታዊ መብቶች እነዲከበሩ ከመጠየቅና መንግስትን የሚተቹ ጽሁፎችን ከማቅረብ ባለፈ አንድም የዞኑ ስራ ለብጥብጥ እና ለሁከት ምክንያት ለመሆን የሚበቃም አይደለም፡፡ ይህንነ ለመረዳት የዞኑን ዘመቻዋች እና ጽሁፎች ማየት ብቻውን የክሱን አስቂኝነት ለማስረዳት ይበቃል፡፡ እስከዛሬ በጻፍናቸው የመንገስት ትችቶች ካልሆነ በስተቀር ባነሳሳናቸው ብጥብጦች አንታወቅም ፡፡ ለዚያም ነው በጽሁፋቸው አይደለም የታሰሩት የሚለውን የመንግሰት ማስተባበያ አስቂኝ የሚያደርገው ፡። በጽሁፍ ካልሆነ በምንድነው የዞን 9 አባላትን እንድ ላይ እንደቡድነ ሰብስቦ መክሰስ የሚቻለው??
ከውጨ ድርጅት ጋር መተባበር 
ዞን 9 ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ ላለፉት ሁለት አመታት በነበረው ቆይታ የተለያዩ አጋርነቶችነ ከተለያዩ አካላት ጋር ፈጥሮአል፡። በዚህም በተለያየ ጊዜ እነደግለሰብም አንደቡድን ተወካይ በመሆን አባላቱ አገሪትዋ ውስጥ ያለውን የሰብአዊ መብጥ ጥሰት አያያዝ አስመልክቶ ለተለያዩ ቦታዎች ንግግር አድርገዋል፡፡ ኢንተርኔት ለነጻነትና ለዴሞክራሲ የሚያደርጋቸውን አስተዋእጾም አስመልክቶ በቡድንም በነጠላም በተለያዩ ቦታቸዎች ላይ በመገኘት ልምዳቸውን አካፍለዋል፡፡ ይህ መንግስት ሲፈልግ የሚፈቅድላቸው ሲፈልግ ወንጀል የሚያስመስለው ተግባር ሳይሆን የሁሉም ኢትዮጲያዊ ህገ መንግስታዊ መብት ነው፡፡ ዜጎች በመጓዛቸው ስራቸውን እና ልምዳቸውን በማካፈላቸው እነዲሁም ራሳቸውን ብቁ በማድረግ የሚሰሩትን የሰብአዊ መብት እነቅስቃሴ ለሌሎች መናገራቸውን ወንጀል ለማስመሰል የሚደረገውን ጥረት አሁንም ቢሆን እንደዞን 9 አጥብቀን እናወግዛለን፡፡ ከዚህ በፌትም እነደተናገርነው በህግ እስካልተከለከለ ድረስ ህጋዊ እንቅስቃሴዎቸን መንግስት ስላልወደዳቸውና ህገ ወጥ ስላስመሰላቸው የምናቆምበት ምንም ምክንያት የለም፡፡ ሁሉም የዞን ዘጠኝ አባላትና ወዳጆች በፓርላማ በህገ ወጥነት ከተፈረጁ ተቋማት ጋር ምንም አይነት ግንኙነት አልነበራቸውም የላቸውምም፡። ለዞን ዘጠኝ ስራም ምንም አይነት የፋይናንስ ድጋፍ አግኝተን አናውቅም፡፡ (በመሰረቱ የፋይናንስ ድጋፍ የማያስፈልገው የበጎ ፍቃደኝነት ስራ ነው የምንሰራው ) ከዚያ ውጪ ግን በፓርላማ ህገ ወጥ እስካልተባሉ ወይም ከልካይ ህግ እስካልመጣ ድረስ ከተለያዩ በተባበሩት መንግስታት እውቅና ካላቸው የመብት ተሟጋች ተቋማት ጋር ያለንን ግንኙነት ወንጀል ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት አንቀበለውም፡።
አንዳንድ አስቂኝ የመንግስት ወዳጆች በህቡህ ተደራጅተው የሚል ክስም ሲለጥፉብን ሰምተናል፡፡ ህቡህ ማለት ምን ማለት እነደሆነ ትርጉሙን እንዲያጣሩ ከመጠየቅ ባለፈ ምንም የምንጨምረው ነገር የለንም ፡፡ ባለፉት ሁላት አመታት ቆይታችን ፎቶአችን የሚታይ ሙሉ ህጋዊ ስማችን የሚታወቅ አገር ውስጥ የምንኖር ኢንተርኔት ላይ የተናገርነውን በግንባር የምንደግም ህጋዊ ዜጎች ነን፡። ከዞን ዘጠኝ እሴቶች መካከልም አንዱ ለተናገሩትም ሆነ ለሚያስተላልፉት መልእክት ሙሉ ሃላፌነትን መውሰድም ጭምር ነው ፡፡ በመሰረቱ ኢንተርኔት ላይ ቡድን መመስረት በየትኛውም ህግ የማይከለከል ህጋዊ ተግባር መሆኑን ለመንግስትና የመንግሰት እርምጃ ለደገፉ ለማስታወስ አንወዳለን፡፡
ባለፉት ቀናት ስንናገር እንደነበረው መንግሰት የዞን ዘጠኝ አባላትና ወዳጆችን እነዲፈቱ መጠየቁን አሁን ደግሞ በኦሮሞ ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍ በመቃወም በጋራ ድምጻችንን ማሰማታችንን እንቀጥላለን፡፡ ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን እየተደበደቡና እየሞቱ የዞን9 አባላትን እስር ብቻ ለይተን ዘመቻ ማድረጉን ሃላፌነት የሚሰማው ሆኖ አላገኘነውም፡፡ በመሆኑም ሁለቱ ጉዳዪች ላይ አተኩረን የሚመለከተው አካል ሃላፌነቱን እነዲወጣ ግፌት ለማድረግ እንሞክራለን፡። ዞን ዘጠኝ እንቅስቃሴን በማሰር ለመገደብ ቢሞክርም ብዙ የዞኑ ነዋሪያን ጋር በመተባበር ከምርጫ ጋር የተያያዙ ስራዎችን የመስራት እቅዳችነን አጠናክረን እንቀጥልበታለን፡።
ከነገ ሚያዝያ 25 ጀምሮ የዞን 9 ጦማርያንን እና ወዳጅ ጋዜጠኞችን መፈታት እነዲሁም በኦሮሞ ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት የምን ቃወምበት መጠነ ሰፌ ዘመቻ እንጀምራለን፡፡ እስካሁን በተናጠል ላሳያችሁን ህብረት በከፍተኛ ሁኔታ እያመሰገንን በጋራ የአገራችንን “ዞን ዘጠኝተነት” በመቃወም ህብረታቸንን እናሳይ ፡።
የዘመቻውን ዝርዝር በሚቀጥሉት ፓስቶች የምናሳውቅ ይሆናል፡፡

በዝዋይ የሚገኙ የፖለቲካና የህሊና እስረኞች የተለያዩ ጥያቄዎችን በማንሳት ጥያቄያቸው እንዲመለስ ጫና ለመፍጠር የምግብ ማቆም አድማ ጀመሩ፡፡ አድማው ለ3 ቀን እንደሚቆይ ታውቋል፡፡ ጥያቄያቸውም፡- 1ኛ የፖለቲካው ሥነ -ምህዳር እንዲሰፋና የፓርቲዎች በነፃነት የመንቀሳቀስና የመደራጀት መብት ሳይሸራረፍ እንዲከበር፣ 2ኛ አፋኝ የሆኑት የመያዶች ህግ፣ የፀረ-ሽብር ህግ፣ የፕሬስ ህግ እንዲሻሩና ነፃ የሙያ ማህበራት ላይ የሚደረገው አፈና እንዲቀም፣ 3ኛ በግሉ ሚዲያ ላይ […]

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) እሁድ ሚያዝያ 26 ቀን 2006 ዓ.ም ለሚያደርገው ሰላማዊ ሰልፍ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ድርጅት አላስተናግድም ማለቱን የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው ገለጹ፡፡ የህ/ግ ኃላፊው እንደገለጹት ከሆነ ማንኛውንም ህጋዊ አካል ወይንም ዜጋ በእኩልነት ማስተናገድ የሚገባው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ምንም አይነት ህጋዊ ምክንያት ሳያቀርብ አናስተናግድም ማለቱ አንድ የሕዝብ አገልጋይ ነኝ ከሚል ተቋም […]

ዛሬ ማለዳ ሜክሲኮ በሚገኘው የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የቀረቡት የአንድነት ፓርቲ የአዲስ አበባ ሊቀመንበር፣የብሄራዊ ምክር ቤት አባሉ ዘላለም ደበበና ጋዜጠኛ ነብዩ ኃይሉ በፖሊስ የአስራ አራት ቀን የምርመራ ጊዜ ተጠይቆባቸው ፍርድ ቤቱ የአስራ አንድ ቀን ጊዜ ቀጠሮ ለፖሊስ በመፍቀድ በእስር ቤት እንዲቆዩ ተወስኖባቸዋል፡፡ ፖሊስ በአንድነት አባላት ላይ ባቀረበው ክስ ‹‹ለቅስቀሳ ባልተፈቀደ ቦታ ሲቀሰቅሱ አግኝቻቸዋለሁ፣የተፈቀደላቸው ለሰላማዊ ሰልፍ […]

ከዚህ በፊት በዚሁ ጦማርና በልዩ ልዩ ሚዲያዎችም በተነገረው መሠረት ለሀገራቸውና ለሕዝባቸው መልካም ሠርተዋል የተባሉ ከ100 በላይ ኢትዮጵያውያን ተጠቁመዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ እጅግ የተሻሉትን ለመምረጥ የመጨረሻው ሂደት እየተከናወነ ነው፡፡

መርሐ ግብሩ የሚካሄደው ቅዳሜ ግንቦት 23 ቀን ከቀኑ በ 8 ሰዓት አዲስ አበባ ካዛንቺስ አካባቢ በሚገኘው እሊሌ ሆቴል ሲሆን፣ ተሸላሚዎች፣ ተጋባዥ እንግዶች፣ ጋዜጠኞችና ሌሎችም በተገኙበት ይከናወናል፡፡ ሽልማቱ የሚከናወነው በሰባት ዘርፎች ነው፡፡

  1. የሀገራዊ ዕርቅና ሰላም ዘርፍ

  2. የበጎ አድራጎት(ሰብአዊነት) ዘርፍ

  3. የኪነ ጥበብ/ ሥነ ጥበብ ዘርፍ

  4. ግብርናና ኢንዱስትሪ ዘርፍ

  5. መንግሥታዊ ኃላፊነትን በብቃት የመወጣት ዘርፍ

  6. ቅርስ ጥበቃ፣ ባሕልና ቱሪዝም ዘርፍ

  7. ሳይንስና ቴክኖሎጂ/ ጥናትና ምርምር ዘርፍ

በእነዚህ ዘርፎች የተመረጡ ተሸላሚዎች በመጨረሻ መራጮች ድምጽ ከተሰጠባቸው በኋላ ይታወቃሉ፡፡ የሽልማቱ ዋና ዓላማ ገንዘብ አይደለም፡፡ በጎ ሰዎችን በማበረታታት፣ ለበጎ ሰዎችም ዕውቅና በመስጠት ለሀገር ሰው ማትረፍ እንጂ፡፡ ኢትዮጵያዊና የኢትዮጵያ ወዳጆች የሆኑ ጀግኖችን ማሳወቅ ሥራቸውም ለትውልድ አርአያ እንዲሆን ማድረግ እንጂ፡፡ የመመሰጋገንንና የመበረታታትን ባሕልም ማበልጸግ እንጂ፡፡

በዕለቱ መገኘት ለሚፈልጉ በቅርቡ የመግቢያ ካርዱ የሚገኝበትን መንገድ እንጠቁማለን፡፡

የዩክሬይን መንግሥት ወታደሮች ስሎቫንስክን ፣ መነጠል ይፈልጋሉ ከሚባሉት መፍቀሬ- ሩሲያ ኃይሎች እጅ አስለቅቆ ለመቆጣጠር ወታደራዊ የማጥቃት ዘመቻ መክፈታቸውን ጊዜያዊው የሀገር አስተዳደር ሚንስትር አርሰን አባኮቭ ገለጡ።

(ኢ.ኤም.ኤፍ) – በኦሮሚያ ከፍተኛ ተቋማት ውስጥ የተጀመረው ረብሻ ወደ ከተሞች እየተዘመተ መሆኑን ዛሬ ምሽት ያገኘነው መረጃ አሳውቋል። የአምቦ ዩኒቨርስቲ ረብሻ ወደ ከተማው ተዛምቶ ሰባት ሰዎች ተገድለዋል። በመዳ ወላቡም ከዩኒቨርስቲው አልፎ በከተማው በተነሳ ረብሻ ሶስት ሰዎች ሞተዋል። ዛሬ ቀን ላይ ደግሞ በሃረማያ ዩኒቨርስቲ ኳስ ጨዋታ ይመለከቱ የነበሩ ከመቶ በላይ ተማሪዎች ላይ ቦንብ ተጥሎባቸው፤ ሰባ ያህሉ ላይ […]

በአዲሱ የአዲስ ማስተር ፕላን በአዲስ አበባ ዙርያ ያሉ የኦሮምያ ክልል ገጠር መሬቶች የአዲስ አበባ ከተማ አካል ያደርጋቸዋል። ይሄን ጉዳይ በኦሮሞ ህዝብ ባጠቃላይ በኦሮሞ ተማሪዎች ደግሞ በተለይ ዓመፅ አስነስቷል። ማስተር ፕላኑ የገጠር ቦታዎች ማካተቱ በራሱ ችግር አይደለም። እንዳዉም ፕላኑ ኦሮምያ አልፎ መቐለም ቢያጠቃልል ደስ ባለኝ ነበር። ከተማ ቢያድግ መልካም ነው። ከተማ ሲያድግም በዙርያው ይሰፋል። ይህ ባህርያዊ […]

ጎንደር ከተማ ውስጥ ቀበሌ 18 ልዩ ቦታ አርምጭሆ ሰፈር፣ ገንፎ ቁጭና ህዳሴ የተባሉ ሰፈሮች የከተማው አስተዳደር ‹‹ህገ ወጥ ሰፈራ ነው፡፡›› በሚል ቤቶችን ለማፍረስ መዘጋጀቱን ተከትሎ አፍራሾቹ ከህዝብ ጋር በፈጠሩት ግጭት ከ6 በላይ ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች መቁሰላቸውንና መታሰራቸውን ከቦታው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ ግጭቱ ከሶስት ሰዓት እስከ አራት ሰዓት ተኩል ድረስ ቀጥሎ የነበር ሲሆን ምንጫችን ደውሎ በሚነግረን […]

ከታሰሩ የዞን ዘጠኝ አባላት መካከል አንዱ የሆነው ናትናኤል ፈለቀ በቅርበት እንደሚያወቅት የገለጹት የአሜሪካዉ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጆን ኬሪ፣ አቶ ኃይለ ማሪያም ደሳለኝም ጨምሮ ላገኟቸው ባለስልጣናት ፣ ጋዜጠኞችን ማሰርና የዜጎንች ነጻነትን መገደድ ለኢትዮጵያ እንደማይጠቅም አሳሰበዋል። ከኢትዮጵያ ጋር አሜሪካ የቅርብ ግንኙነት እንዳላት የገልጹ ኬሪ፣ የዴሞክራሲና የሰባአዊመ ጉዳይ በጣም እንደሚያሳስባቸው ገለጸዋል። « እየተናገሩት ያለው እንዲሁ ለመናገር ያህል የተናገሩት፣ […]

በአዲስ አበባ ዙሪያ ያሉ ከተሞችን በዋና ከተማይቱ ማስተር ፕላን ውስጥ አካትቶ ለማልማት በሚል የተያዘውን ዕቅድ ከተቃወሙ የኦሮሚያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ጋር በተነሣ ግጭት በሰው ይወትና ንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን የመንግሥት ኮመዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት አስታወቀ፡፡

አዲሱን የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን በመቃወም፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሚገኙ የኦሮሞ ተማሪዎች፣ ተቃዉሞ እንዳሰሰሙ ገዳ.ኮም ድህረ ገጽ ዘገበ። ተማሪዎቹ የተለያዩ መፈክሮችን ያሰሙ የነበረ ሲሆን ፣ቁጥራቸው ከአምሳ እስለ መቶ እንደሚጠጋ በቪዲዮም የሚታየው ምስል ያመለክታል። ተማሪዎቹ ያሰሟቸው የነበረ መፈክሮች በእንግሊዘኛ እና በአፋን ኦሮሞ ብቻ የነበረ ሲሆን ከመፍክሮቹም ዉስጥ የሚከተሉት ጥቂቶቹ ነበሩ፡ Our rights should be respected ! […]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ብሉ ናይል በተባለው ተቋም አማካይነት በአባይ ላይ የተሰሩ ምርምሮችን በማሰባሰብ ተማራማሪዎችና ፖሊሲ አውጭዎችና መረጃውን የሚፈልጉ የተለያዩ አካላት እንዲያገኙት ለማስቀመጥ ተሞክሯል ።

ፈረንሳይ ከቀረቡላት ማመልከቻዎች የተቀበለችው ቁጥር ዝቅተኛ መሆኑ አስተችቷታል ። ከዚህ ሌላ ፈረንሳይ ተገን ጠያቂዎችን የምትይዝበት መንገድም ኢትዮጵያውያን ተገን ጠያቂዎችን አማሯል።