የኢትዮጵያ መንግሥት በኦሮሞ ተወላጆች ላይ የእስራት፣ የስቃይ፣ የግድያ እና የግፍ ተግባር ይፈፅማል ሲል ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት አምኒስቲ ኢንተርናሽናል ይፋ ባደረገዉ ሪፖርት ገለፀ። ድርጅቱ ይፋ ባደረገዉ ሪፖርት በሽዎች የሚቆጠሩ ኦሮሞዎች የእስር የስቃይና የግድያ ሰለባ ሆነዋል።

የሶርያዉ ደም አፋሳሽ የርስ በርስ ጦርነት አራት ዓመት ሆነዉ። በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሶርያዉያን ጦርነቱን በመሸሽ ሀገር ቀያቸዉ ጥለዉ ተሰደዋል። ፖለቲከኞችና የርዳታ ድርጅቶች የዓለም ዓቀፍን ድጋፍ እየጠየቁ ነዉ። ዛሬ የ 40 ሀገራት መንግሥታትና ዓለማቀፍ ድርጅቶች የሶርያን ስደተኞች በተመለከተ ጉባኤ አድርገዋል።

የአፍሪቃ ቀንድ ሀገራት ሰላም እና ፀጥታን ለማጠናከር እንዲሰሩ በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት ጉብኝት ያደረጉት የተመድ ዋና ጸሐፊ ፓን ኪ ሙን እና የዓለም ባንክ ፕሬዚደንት ጂም ዮንግ ጂም፣ እንዲሁም፣ በኢትዮጵያ የአውሮጳ ህብረት ተጠሪ ማርኮ ካማሮ ጠየቁ።

ከጥቂት ወራት በፊት ሰንዓ የመን ውስጥ ተይዘው ለኢትዮጵያ ተላልፈው የተሰጡት የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነትና የዴሞክራሲ ፓርቲ ዋና ፀሃፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ጉዳይ በተመለከተ የብሪታንያ ጠቅላይ ሚንስትር ዴቪድ ካምረን ለኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ከጥቂት ጊዜ በፊት ደብዳቤ እንደላኩ ተገልጾዋል።

ያደረውን የሕገ ቤተ ክርስቲያን አጀንዳ በፈቃዳቸው ትተው ሌላ ርእሰ ጉዳይ አንሥተዋል የተቃወሟቸውን አባቶች በአሳፋሪ ንግግሮች በመዝለፍ ለማሸማቀቅ ሙከራ አድርገዋል የሕገ ቤተ ክርስቲያኑ አጀንዳ ቀጣይነት በድምፅ ሊወሰንበት እንደሚችል ተመልክቷል እንደ ሕጉ ስብሰባውን በአግባቡ ካልመሩ ምልአተ ጉባኤው ሌላ ሰብሳቢ መርጦ ይቀጥላል *                *               * ‹‹ተጠሪነትዎ ለቅዱስ ሲኖዶስ ነው፤ በቤተ ክርስቲያን ሕግ ቢመሩ፣ ቅዱስ ሲኖዶሱን ቢያከብሩ ይሻልዎታል፤ ሕግ …

ባሳለፍናቸው አመታቶች የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሃገር አቀፍ በብሄር አቀፍ እና ቤተሰብ አቀፍነት ተመስርተው ከስመዋል። ሲንደባለሉ ለአሁኑም ወቅታዊ ጡዘት የደረሱም እያዛጉ እና እያፋሸኩ በፖለቲካ አንጎበር እየተናጡ በገሺው አምባገነን ፓርቲ እየተደቆሱ ላለመሞት በወንዳታነት እየተፈራገጡ ይገኛል። የተቃዋሚ ሃይሎች እና የለውጥ ፈላጊ ሃይሎች አንድነት የሚያስፈልግበት ወቅታዊ እና ወሳኝ ትግል ላይ መድረሳችን ለሕዝብ ያለንን አክብሮት ለማሳየት እና ግባችንን በመምታት ለህዝባዊ […]

በአቤ ቶኪቻው

ወዳጃችን ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፤ ከተከሰሰባቸው ክሶች በአንደኛው ሶስት አመት ጽኑ እስራት ተፈረደበት።

በሌሎቹ ክሶች ምን እንደሚፈረድበት ቀጥሎ የምናየው ቢሆንም ተሜ እና ሌሎች ወንጀለኛ ያልሆኑ ሰዎችን… (ይሄን ግዜ አንዳድ አብዝተው የዋህ የሆኑ ሰዎች እና አብዝተው የኢህአዴግ ዝምድናን የተጋመዱ ግለሰቦች ፍርድ ቤት ወንጀለኛ ያላቸውን ሰዎች ከወንጀል ነጻ ናቸው ማለት ተገቢ ነውን… እያሉ ሊሞግቱን ጣታቸውን ሲያሞጠሙጡ ይታየኛል…

ሙሉውን አስነብበኝ …

ነቢዩ ሲራክ

ወንድሜ ሆይ ማምሻውን ” … አሁን የማወራው ስለ ብትቱው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ሳይሆን ስለ ሆደ ባሻዋ እና ርህሩዋ እናታችን ነው! ” በማለት ስለ እናትህ ጭንቀት የጻፍከውን ሳነበው ፣ ስለ እናትህ ልቤ በሃዘን ተጎዳ ፣ ስለ ጀግኖች ሳይሆን ስለ ጀግና እናቶች መከራ አነባሁ ፣ እንደ ሰው በእልህ ሰውነቴ ጋለ ፣ ተናደድኩ …በቁጭት ግን አልቆዘምኩም …!

ሙሉውን አስነብበኝ …

ነቢዩ ሲራክ

ወንድሜ ሆይ ማምሻውን ”… አሁን የማወራው ስለ ብትቱው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ሳይሆን ስለ ሆደ ባሻዋ እና ርህሩዋ እናታችን ነው!” በማለት ስለ እናትህ ጭንቀት የጻፍከውን ሳነበው፣ ስለ እናትህ ልቤ በሃዘን ተጎዳ፣ ስለ ጀግኖች ሳይሆን ስለ ጀግና እናቶች መከራ አነባሁ፣ እንደ ሰው በእልህ ሰውነቴ ጋለ፣ ተናደድኩ … በቁጭት ግን አልቆዘምኩም …!

ሙሉውን አስነብበኝ …

ስለ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

በዓለማየሁ ገላጋይ 

የጉብኝት ጉዞው በማለት ተጀምሯል፤ ያለንበት መኪና ወደ አዲስ አበባ ደቡብ አፍንጫውን ቀስሯል፤ በመካከላችን ጸጥታ ረብቧል… ዕጣ ፈንታህ በዘመን እጅ ነው ዘመን ሲፈቅድ የዘመንህ ‹‹ ጉዱ ካሳ›› ትሆናለህ፤ ስውር እስር ቤት ትገባለህ፤ እንደ እብድ ትታያለህ፤ በመገለል ዘብጥያ ባመደመጥ ዋርድያ ስር ትሆናለህ፡፡ እውነትህ እንደቅራቅንቦ ይቆጠራል ይናቃል…
… ወይም ….

ሙሉውን አስነብበኝ …

ክስ ሳይመሰረትበት ለአራት ወራት በማእከላዊ እስር ቤት የሚገኘው የአንድነት የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ ወጣት ሃብታሙ አያሌው፣ ከፍተኛ ኢሰብአዊ ግፍ እየተፈጸመበት እንደሆነ ታወቀ። ሃብታሙ አያሌው ለአንድ ሳምንት ወደ መጸዳጃ ቤት እንድዳይሄድ በመከልከሉ በፌስትታል ይጠቀም እንደነበረ፣ ለሶስት ሳምንታትም ቁጥር ስምንት በምትባል የጨለማ ቤት ዉስጥ ለብቻው እንዲቀመጥ መደረጉንም አረጋግጠናል። “ወደ ፖለቲካው የማትመለስ ከሆነ ትወጣለህ። አለበለዚያ እዚሁ ነው የምትሞተው” […]

ፓትርያርኩ የማኅበራት ገንዘብ ወደ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ገቢ ኾኖ በማእከል ካልተመራ በሚል ከማኅበራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ጋራ የሚቃረን ግትር አቋም ይዘው ውለዋል፡፡ አቋማቸው ተቀባይነት ካላገኘ ስብሰባውን ለመምራት እንደሚቸገሩ በመግለጽ ምልአተ ጉባኤን ለማስገደድ ያደረጉት ሙከራ በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳቱ ጽኑ አቋም ሳቢያ አልተሳካላቸውም፡፡ ጉዳዩ ‹‹ከአዲስ አበባ የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች ጋራ ብዙ የሠራኹበትና የደከምኩበት ነው፤ በቀላሉ የምተወው አይደለም›› …

ጥቅምት ፲፮(አስራ ሥድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የመስተዳድሩ ኃላፊዎች በፖለቲካ ስልጠና እና በግምገማ መወጠራቸው ውሳኔ በወቅቱና በአግባቡ የሚሰጥ አካል በመጥፋቱ ነዋሪዎች አገልግሎት ለማግኘት ተቸግረዋል። በእያንዳንዱ የሴክተር መስሪያ ቤት ውስጥ የሚገኙጥ ኃላፊዎች የሉም ያለው ዘጋቢያችን፣ ውሳኔዎችን የሚሰጥ በመጥፋቱ የውጪም ሆነ የውስጥ አግልገሎት ቆሟል። ኦህዴድ በአዲስ አበባ ያሉትን ከፍተኛ የአመራር አካላት ወደ አዳማ በመጥራት ለ14 ቀናት …

ጥቅምት ፲፮(አስራ ሥድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በጋምቤላና በደቡብ ክልል አዋሳኝ ቦታዎች በሚኖሩ በመዠንገርና በመንግስት ታጣቂ ሃይሎች መካከል የተፈጠረውን ግጭት ተከትሎ፣ ቁጥራቸው 50 የሚጠጋ የፌደራል ፖሊስ፣ የመከላከያና የአካባቢው ሚሊሺያዎች ከተገደሉ በሁዋላ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የመከላከያ ሰራዊት አሁንም በአካባቢው እንቅስቃሴ እያደረገ ነው። ወኪላችን እንደሚለው ጦርነት ይነሳል በሚል ካለፈው ሳምንት አጋማሽ ጀምሮ ከፍተኛ ስጋት የነበረ ሲሆን፣ …

ጥቅምት ፲፮(አስራ ሥድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ የነበረው እውቁ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ህዝብን ለአመጽ በማነሳሳት፣ ግዙፍ ባልሆነ ማሰናዳትና የመንግስትን ስም በማጥፋት ወንጀል ተከሶ ሲከራከር ከቆየ በሁዋላ፣ የፌደራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት 9ኛ ወንጀል ችሎት በ3 አመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል። ጋዜጣውን ሲያሳትም የነበረው ማስተዋል የህትመትና ማስታወቂያ ስራ ድርጅት ደግሞ በ10 ሺ …

ጥቅምት ፲፮(አስራ ሥድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፌደራል ፖሊስ አባላት አሸባሪዎች ገብተዋል በማለት የሚያደርጉት ተደጋጋሚ ፍተሻ እንዳስመረራቸው ነዋሪዎች ለኢሳት ገልጸዋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሚታየው የተጠናከረ ፍተሻ ሰኞ እለት ተጠናክሮ መቀጠሉን የተናገሩት በቦሌ አካባቢ ነዋሪ የሆኑ ግለሰቦች፣ አሸባሪዎች ገብተዋልና አጋልጡ በሚል መኪኖች ሲፈተሹ መዋላቸውን፣ መንገደኞች እየቆሙ መፈተሻቸውን እንዲሁም የቤት ለቤት አሰሳ መደረጉን ለሰአታት ታግተው የቆዩ …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ኩባ ዓለም አቀፍ ቀውስ ሲያጋጥም እንዴት ባፋጣኝ ለርዳታ መረባረብ እንደሚቻል ፣ ወረት የማካበት ሥርዓት ያለውን ምዕራቡን ዓለም በማስተማር ላይ ናት። ከመስከረም ወር ማለቂያ ገደማ አንስቶ እስካሁን ከ 250 በላይ የህክምና ዶክተሮችንና ነርሶችን ወደ ምዕራብ አፍሪቃ ልካለች።

የአውሮጳ ህብረት፣ የዓለም ባንክ እና ሌሎች ያካባባ የልማት ባንኮች ለአፍሪቃ ቀንድ ሀገራት ስምንት ቢልዮን ዶላር ርዳታ ለመስጠት ቃል ገቡ። ይህ ዜና ይፋ የሆነው የተመድ ዋና ጸሐፊ ፓን ኪ ሙን ከዓለም ባንክ ፕሬዚደንት ጂም ዮንግ ኪም ጋር ዛሬ ኢትዮጵያን በጎበኙበት ጊዜ ነው።

ምልአተ ጉባኤው በመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤው የጋራ መግለጫና የውሳኔ ሐሳብ ላይ መክሮ አጽድቋል፤ በሥራ ላይ እንዲውልም መመሪያ ሰጥቷል፡፡ ከአጠቃላይ ጉባኤው አጀንዳ ውጭ በማኅበረ ቅዱሳን ላይ ለማስወሰን ታቅዶ በፓትርያርኩ ግፊትና በአማሳኞች ውትወታ የተከፈተው መድረክ÷ ስብሰባው ‹‹ባለቤት የለውም ወይ?›› ያሰኘና የአጠቃላይ ጉባኤው ክብረ ሞገስ በርእሰ መንበሩ አመራርና የቀጥተኛ ተሳትፎ መብት በሌላቸው አማሳኞች ሥርዐት አልባነት የተጣሰበት …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ዓርብ ዕለት የተከበረውን የአቡነ አረጋዊ በዓል ለማክበር አውስትራልያ አደላይድ ነበርኩ፡፡ እዚያ ከተማ የሚገኝ አንድ የድሮ ወዳጄ በፌስ ቡክ አገኘኝና አደላይድ መሆኔን ነገርኩት፡፡ ‹‹የት እንገናኝ›› ሲለኝ ‹‹ነገ (ቅዳሜ) የአቡነ አረጋዊን በዓል ለማክበር ስለምሄድ እዚያ እንገናኝ›› አልኩት፡፡ ‹‹አንተም እርሱን በዓል ታከብራለህ?›› አለኝ፡፡ በዓይነ ኅሊናየ ራሱን እየነቀነቀ ታየኝ፡፡ ‹‹እንዴት?›› አልኩት፡፡ ‹‹የእነ እንትና ታቦት አይደል እንዴ›› አለኝ የሆነ የኢትዮጵያ አካባቢ ጠርቶ፡፡ ‹‹ማን እንደዚያ አለ?›› ስል ጠየቅኩት፡፡ ‹‹ምን፣ የታወቀኮ ነው›› አለኝ፡፡ እየገረመኝ ተለያየን፡፡

በማግሥቱ በዓሉ ላይ ተገኘሁ፡፡ በዓሉን እኩለ ቀን ላይ ጨርሼ ስወጣ ሌላ የጥንት ዘመዴን አገኘሁት፡፡ ያ ትናንት ማታው ጓደኛዬ እዚህ ከተማ እንዳለ የማላውቅ መስሎት ይኼኛው ነገረኝ፡፡ እኔም ሰው ላለማጋጨት ብዬ ያለኝን ሳልዘረዝር እንዴው በደፈናው ደውዬለት መምጣት አልችልም እንዳለኝ ነገርኩት፡፡ ይኼኛውም እኔ እንዳልነግረው የደበቅኩትን እርሱ ገልብጦ ነገረኝ ‹‹የኛ ታቦት ሲሆንኮ እነ እንትና አይመጡም›› አለኝ ፈገግ እያለ፡፡ ‹‹ማን ነው የእናንተ ታቦት ያደረገው›› አልኩ በአግራሞት›› ‹‹ያው አቡነ አረጋዊ የኛ ሀገር ሰው አይደሉ›› አለኝ የሠፈሩ ሰው ያህል ርግጠኛ ሆኖ፡፡ ወይ ግሩም፣ ይኼ በሽታ ለካ ማናችንንም ሳይለይ በደንብ ይዞናል አልኩ በልቤ፡፡

ጋሽ ግርማ ከበደ ‹‹ሰው የሚጠላውን ኃጢአት ደጋግሞ ይሠራዋል›› ይል ነበር፡፡ ብዙዎቻችን የሌላውን ሰው ዘረኛነት ለመግለጥ የምንጠቀምበት መንገድ ራሱ ዘረኛ ነው፡፡ አሁን እየተጓዝንበት ያለው አቅጣጫ በመካከላችን ምንም ዓይነት የጋራ ነገር እንዳይኖረን የሚያደርግ ነው፡፡ የጋራ ሆነው የቆዩትን ነገሮች እንኳን አሁን አሁን ወደ ራስ መውሰድ፣ አለበለዚያም ደግሞ የሌላው ብቻ አድርጎ ከራስ ክልል ማስወጣት ጀምረናል፡፡ ምንም እንኳን የኔታ እሸቱ ‹‹የጎጥ ጀግና የለም፤ ጀግና ከሆነ የሁላችንም ነው፤ ያለበለዚያ ደግሞ ጀግና አይደለም›› ቢሉም፡፡ አንዳንድ ጊዜ ምንኖርባትንና የቆምንባትን ኢትዮጵያ ያወቅናት አልመሰለኝም፡፡ ከሰሜን የጀመረ መስቀል ደቡብ፣ ከደቡብ የጀመረ ቆጮ ሰሜን በዘለቀባት ሀገር፤ የኮንሶ የእርከን ሥራ የትግሬ ገበሬ ገንዘብ፣ የትግራይ አምባሻ የደቡብ የቅንጦት ምግብ በሆነባት ሀገር፣ የኦሮሞ ጉዲፊቻ የሁሉም ባህል በሆነባት ምድር፣ ይኼ የእነ እገሌ ብቻ ነው፣ እኛን አይመለከትም ብሎ ለመናገር እንደመድፈር ያለ የአላዋቂ ድፍረት የለም፡፡

ማንኛውም ነገር መነሻ ይኖረዋል፡፡ ዓባይ ከግሼ ዓባይ እንደሚመነጨው፡፡ ነገር ግን መነሻው መድረሻው አይደለም፡፡ ዓባይ ከግሼ ዓባይ ስለመነጨ የጎጃም ቀርቶ የኢትዮጵያ ብቻ ሊሆን አልቻለም፡፡ አዋሳኙ ሁሉ የእኔም ነው ብሎ ሲመክርበት ይኖራል፡፡ በመካከለኛው ምሥራቅ የተጀመሩትን ኦሪትን፣ ክርስትናንና እስልምናን የኛ አድርገን እየኖርንባቸው አይደል እንዴ ? ከአውሮፓ የወረስነውን ኮትና ሱሪ ቂቅ ብለንበት እየተዳርንበት አይደለም እንዴ? በፖርቹጋሎች በኩል ከሜክሲኮ የደረሰን በርበሬ ይኼው የአበሻ መለያ ሆኖ የለም እንዴ፤ የአውስትራልያ ባሕር ዛፍ ኢትዮጵያዊ ሆኖ የለም እንዴ፤ እንዴት ነው ጎበዝ፡፡ ጤፍ ለምግብነት ዋለ የሚባለው ከክርስቶስ ልደት በፊት 5000 ዓመት ቀደም ብሎ በሰሜን ደጋማ ቦታዎች ነው፡፡ ዛሬ ግን ይኼው ድፍን ሐበሻ ባሕሉ አድርጎት፤ ዘልቆም ድፍን ዓለም ሊበላው እየተሻማ ይገኛል፡፡ የሰሜን ነው ብሎ ማን ተወው፡፡

መልካም ነገር ከአንድ ቦታ ይነሣል፡፡ ከዚያም ሌላውም ከባሕሉና እምነቱ ጋር እያዛመደ ይዋረሰዋል፤ ወይም ገንዘብ ያደርገዋል፡፡ ከዚያም የእርሱም ጭምር ይሆናል፡፡ በተለይ በታሪካችን ውስጥ ከአንዱ የተነሣ ነገር ሰፍቶና መልቶ የሌላውም ገንዘብ የሆነበት አጋጣሚ ብዙ ነው፡፡ እንዲያውም በሚያስደንቅ መልኩ ከመነሻው ጠፍቶ ከመድረሻው የተገኘ ብዙ ነገር አለ፡፡

ከላይ መነሻዬ ከሆነው የአቡነ አረጋዊ ነገር ልጀምር፡፡ አቡነ አረጋዊ ሀገራቸው ኢትዮጵያ አይደለም፡፡ ሮማዊ ናቸው፡፡ በ5ኛው መክዘ ከተሰዓቱ ቅዱሳን አንዱ ሆነው ወደ ኢትዮጵያ መጡ፡፡ አቡነ አረጋዊ መጨረሻቸውን በደብረ ዳሞ፣ ትግራይ ቢያደርጉትም በወሎ፣ በጎንደር፣ በጎጃም፣ በሸዋና በደቡብ ታሪክ ውስጥ ግን አሉ፡፡ ደቡብ ጎንደር ውስጥ ጥንታዊው ገዳማቸውና የዝማሬ መዋሥዕት ማስመስከሪያው ዙር አባ አረጋዊ አለ፡፡ ጣና ቂርቆስ፣ አዲስ አበባ አጠገብ የሚገኘው የረር፣ እንዲያውም ከዚያ ተሻግሮ ጋሞጎፋ የምትገኘው ብርብር ማርያም ታሪካቸውን ከእርሳቸው ጋር ያገናኛሉ፡፡ የመጨረሻውና ታላቁ ገዳማቸው ደብረ ዳሞ ስለሆነ የኛ አይደሉም ብለው አያውቁም፡፡ የጎንደር ሊቃውንት በ17ኛውና በ18ኛው መክዘ ለዓመት የሚቆመውን ዚቅ ሲያዘጋጁ ቦታ ከሰጧቸው ቅዱሳን አንዱ አቡነ አረጋዊ ናቸው፡፡ የአቡነ አረጋዊ ቤተ ክርስቲያን የሀገሪቱ ድንበር ጠባቂ ሆኖ ሞያሌ ላይ ይገኛል፡፡ ለሁለቱ ኢትዮጵያውያን የምንኩስና መሠረቶች ለአቡነ ተክለ ሃይማኖትና አቡነ ኢየሱስ ሞአ ምንኩስናን የሰጠው ደብረ ዳሞ ነው፡፡ ዋርካው ሲሰፋ እዩት፡፡

እንግዲህ እኒህን ከሁሉም በላይ ሆነው፣ የሁሉም የሆኑትን አባት ነው አንዳች ጎጥ ውስጥ ልንከታቸው መከራ የምናየው፡፡ ልክ አንዳንዶቹ አቡነ ተክለ ሃይማኖትን ከሸዋ ብሎም ከአማራ ጋር ለማያያዝ እንደሚሞክሩት፡፡ እንዲያውም በሚገርም ሁኔታ ገድላቸው የአያቶቻቸውን ጥንተ መሠረት ከትግራይ፣ በኋላም ከዋድላ ጋር ነው የሚያያይዘው፡፡ በኋላም ሥርዓተ ምንኩስናን የፈጸሙት በአምሐራና በሐይቅ እስጢፋኖስ(ወሎ)፣ በስተ መጨረሻም በደብረ ዳሞ(ትግራይ) ነው፡፡ በውስጣቸውም የትግራይ ገዳማትን የመጎብኘት ልዩ ፍላጎት ስለነበራቸው ለብዙ ዓመታት በዚያው በትግራይ እየተዘዋወሩ አገልግለዋል፣ ተሳልመዋልም፡፡ ታላቁንና የሰሜን ኢትዮጵያ የምንኩስና መሠረት ከሆኑት አንዱ የሆኑትን አቡነ መድኃኒነ እግዚእንም አመንኩሰዋል፡፡ እንዲያውም እዚያው ትግራይ ውስጥ ቀንጦራር በተባለ ቦታ(በደቡብ ምሥራቅ ትግራይ?) ለመቅረትና ገዳም ለመመሥረት ፈልገው ነበር፡፡

አያሌ የኤርትራና የትግራይ ገዳማት የምንኩስና ሐረጋቸውን ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት የሚጀምሩትም በዚህ ምክንያት ነው፡፡ እንደ አጭር ማሳያ የዋልድባውን አቡነ ሳሙኤልና የቆየጻውን አቡነ ሳሙኤል መጥራቱ ብቻ ይበቃል፡፡ በጣና ገዳማት የሚገኙት የግድግዳ ላይ ሥዕሎች ሁለቱን አባቶች – አቡነ ተክለ ሃይማኖትንና አቡነ ኤዎስጣቴዎስን ጎን ለጎን ነው የሚሥሏቸው፡፡

ከሰሜን ተነሥቶ ደቡብ መምጣት፣ ከደቡብ ተነሥቶም ሰሜን መሄድ እንዲህ እንዳሁኑ ከባድ አልነበረም፡፡ እነ አቡነ ፊልጶስና አቡነ አኖሬዎስ ነገሥታቱ ሲያሳድዷቸው የተጠለሉት በትግራይ ገዳማት ነበር፡፡ የተጋዙትም ወደ ዝዋይና አርሲ ነበር፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የሠራዔው አቡነ ኤዎስጣቴዎስ እስከ ሸዋ ምድር ድረስ ደርሰው አስተምረዋል፡፡ የአኩስም ጽዮን ካህናት ከዮዲት መዓት ለማምለጥ ወደ ዝዋይ ነበር የመጡት፡፡ ያለ ሀገራችሁ፣ ያለ ክልላችሁ ያላቸው አልነበረም፡፡ በ14ኛው መክዘ በነበረው የሰንበት ክርክር ጊዜ የሞረቱ ዜና ማርቆስ ገዳም መነኮሳት በቦታ ከሚቀርባቸው ደብረ ሊባኖስ ገዳም ይልቅ የኤርትራ ገዳማት የያዙትን አቋም ደግፈው ነበር፡፡ የሙገርን ቅዱሳን ያስተማረው ሐራንኪስ የአኩስም ተወላጅ ሲሆን የቡልጋን ቅዱሳን ያስተማረው ሕይወት ብን በጽዮን ደግሞ የተማረውና የማስተማሪያ መጽሐፉን ያገኘው ከትግራይ ገዳማት ነው፡፡ እንዲያውም ለብዙ ዓመታት በትግራይ ገዳማት ቆይቶ ተምሮ ሲመለስ የተወለደባትን ዞረሬን ባያት ጊዜ ‹‹እንደ ሀገሬ እንደ አኩስም መሰለችኝ›› ነበር ያላት፡፡

በኤርትራ ታላቅ ቦታ ያላቸው አቡነ አብራንዮስ የጎጃም ሁለት እጁ እነሴ ተወላጅ ሲሆኑ፣ በምሥራቅ ጎጃምና በደቡብ ጎንደር ታላቅ ቦታ ያላቸው አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ደግሞ የኤርትራ ተወላጅ ናቸው፡፡ የምሥራቅ ጎጃም ገበሬ በኤዎስጣቴዎስ ከማለ መላሽ የለውም፡፡ የሙገሩ አቡነ አኖሬዎስ በሸዋ የነበረው ገዳማቸው ሲጠፋ በላስታና በደቡብ ወሎ ግን  ገዳማቸው አሁንም በክብር አለ፡፡ እንዲያውም ልብሳቸው፣ መስቀላቸው፣ የጸሎት መጽሐፋቸው የሚገኘው ላስታ፣ ዋናው ገድላቸው የሚገኘው ተንቤን ነው፡፡ ቅዱስ ያሬድ አኩስም ቢወለድም ድጓው የሚገኘው ደቡብ ጎንደር ቤተልሔም፣ ዝማሬ መዋሥዕቱ የሚገኘው ደቡብ ጎንደር ዙር አምባ ነው፡፡ አሁን በያሬድ ዜማ ሲዘም ማን አኩስምነቱ ትዝ ይለዋል፡፡ የላስታው ላሊበላ በላስታ ካለው ደብር በላይ በምዕራብ ጎጃም ያለው ይልጣል፡፡ በዚያ ከአምስት በላይ በስሙ የሚጠሩ አድባራት አለው፡፡ በጉራጌ ትልቁን ሐዋርያነት የሠሩት የሰሜን ሸዋው አቡነ ዜና ማርቆስ ናቸው፡፡ በጎንደር ደግሞ ትልቁን ሥራ የሠሩት የጉራጌ ሊቃውንት ናቸው፡፡

በግራኝ አሕመድ ዘመን ከሆነው ጥፋት በኋላ ጎንደርን ሊያቀና የተነሣው ዐፄ ሠርፀ ድንግል ትልቅ ችግር የሆነበት ለጎንደር አድባራት የሚሆኑ ሊቃውንትን ማግኘት ነበር፡፡ በኋላ ግን እነዚህ ሊቃውንት ከጉራጌ ምሑር ኢየሱስ ገዳም ተገኙ፡፡ እነዚህ ‹‹አርባዕቱ ሊቃውንተ ምሑር›› በመባል የሚታወቁት አባ መሰንቆ ድንግል ዘቤተ ልሔም፣ አባ ለባዌ ክርስቶስ ዘዙር አምባ፣ አባ ብእሴ እግዚአብሔር እና መምህር ተክለ ወልድ ዘለገደባ ማርያም ናቸው፡፡ በላይ ጋይንት ደብረ ማርያም የሚገኘው ሃይማኖተ አበው ‹‹ዐርባዕቲሆሙ ኅቡረ፣ ቃላቲሆሙ ሥሙረ – አራቱም አንድ ነበሩ፣ ቃላቸውም የሠመረ ነበረ›› ይላቸዋል፡፡ እነዚህ ሊቃውንት ነበሩ እየተማከሩ ጎንደርን እንደገና አቅንተው የሊቃውንት መፍለቂያ ያደረጓት፡፡ በጎንደር ከተማ የዘር ነገር የማይነሳው ለዚያ ይሆን?

ከጎንደር ሳንወጣ ዛሬ አደባባይ ኢየሱስ የሚባለው ቤተ ክርስቲያን ታቦት ጥንት የነበረው ከምባታ ነበር፡፡ (በገድለ ተክለ ሃይማኖት አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወደ አካባቢው ባደረጉት ጉዞ መጀመሪያ የተከሉት ታቦተ ኢየሱስን መሆኑ ይናገራል፤ ምናልባት እርሱ ሊሆን ይችላል) በግራኝ ጊዜ በተፈጠረው ስደት ካህናቱ ተሰደዱ፡፡ ታቦቱንም በአንድ ቦታ ሠረወሩት፡፡ የመከራው ጊዜ ሲያልፍ ደብሩን እንደገና ቢደብሩትም ታቦቱን ግን ማግኘት አልቻሉም፡፡ በዐፄ ሠርፀ ድንግል ዘመን አባ ንዋይ የተባሉ አባት ወደ ከምባታ ወርደው ታቦቱ ያለበትን ቦታ ለ47 ዓመት ሲፈልጉ ቆይተው በ1570 ዓም አካባቢ አገኙት፡፡ ወደ ንጉሡም ይዘውት መጡ፡፡ ዐፄ ሠርፀ ድንግልም ያመፀውን ባሕረ ነጋሽ ይስሐቅንና ቱርኮችን ለመውጋት በዝግጅት ላይ ስለነበሩ በ1572 ዓም ደንቢያ ላይ እያሉ ከአባ ንዋይ ጋር ተገናኙ፡፡ በዚህ ጊዜ የባሕረ ነጋሽ የትዕቢት መልእክት ከሁለት ጥይት ጋር መጥቶላቸው ነበርና አንዱን በታቦተ ኢየሱስ፣ ሌላውን በግምጃ ቤት ማርያም ላይ አድርገው እንዲጸልዩበት አዘዙ፡፡

ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ታቦተ ኢየሱስ ከንጉሡ አልተለየም፡፡ በ1572 ረዳዒ የተባለውን የቤተ እሥራኤል መሪ፣ በ1579 ጎሼን ለመውጋት ሲዘምቱ አብሮ ነበረ፡፡ በኋላ በዐፄ ፋሲል ዘመን አደባባይ ኢየሱስን ሠርተው ታቦቱን በዚያ አኖሩት፡፡ ይኼው ከከምባታ መጥቶ ጎንደር ላይ ተተክሎ ይኖራል፡፡ ልክ ወሎ መካነ ሥላሴ የነበረውና በግራኝ ተቃጥሎ ፍራሹ የሚታየው የመካነ ሥላሴ ታቦት አሁን አራት ኪሎ ሥላሴ ካቴድራል እንደሚገኝው ማለት ነው፡፡ የቁልቢ ገብርኤል ታሪክ ከአኩስምና ከቡልጋ ጋር እንደተያያዘው፡፡

መርጡለ ማርያምን ቤተ ክርስቲያንን ከግራኝ ዘመን ትንሽ ቀደም ብሎ ባመረ ሁኔታ እንደገና አሠርተዋት የነበሩት እቴጌ ዕሌኒ የሐድያ ተወላጅ ነበሩ፡፡ ሕዝቡ በደግነታቸው ስለሚወዳቸው በሞቱ ጊዜ ከሩቅ ሀገር ሳይቀር እየሄደ መርጡለ ማርያም ከመቃብራቸው ላይ ያለቅስ ነበር ይላል አልቫሬዝ፡፡

እንዴው ባጠቃላይ እንደ ዘሐ ዘጊ ወዲህና ወዲያ እንዲህና እንዲያ በተዋረሰውና በተወራረሰው ሕዝብ መካከል ‹‹የዚያ ብቻ›› ወይም ‹‹የእኔ ብቻ›› የሚል ነገር ማምጣት ካለ ማምጣቱ ይልቅ የሚከብድ ይመስለኛል፡፡ እንኳን ደጉ ነገር ክፉው ነገራችን እንኳን ተዋርሶ ተዋርሶ የሁላችን ሆኗል፡፡ ምንም እንኳን የራሳችን ቋንቋ፣ ባሕልና ማንነት ቢኖረንም፣ የበለጠ የሚያዋጣን የኛንም ሸጠን፣ የሌላውንም ገዝተን የተዋርሶና የተገናዝቦ ማንነት ብንፈጥር ነው፡፡ ከአጥሩ ይልቅ ድልድዩ ያተርፈናል፡፡ ሀገር እንደ ገና ዳቦ ስትያያዝ እንጂ እንደ ቡሄ ዳቦ ስትነጣጠል ዘላቂ አትሆንም፡፡

አደላይድ፣ አውስትራልያ

“ይምርጡን ሳናዳላ፤ ሳንገል፤ ሳናስር፤ሳንዋሽና ሳንሰርቅ ፍፁም በሆነ አገራዊ ፍቅር አክብረንህ እናስተዳድራለን ”። የምርጫ መሪ ቃል ብትሆን ያልኳት። ጎሽ እንዲህ ነው መቅደም። አገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ዘጠኝ ድርጅቶች በጋራ ለመታገል መስማማታቻውን ስሰማ ሀሴት ነው ያደረኩት። መጀመርያ ዜናውን ስሰማ ጥሩ ነው አልኩ። አንድነትና መድረክ ስይካተቱ የሚፈለገውን ውጤት አያመጣም በሚል አላካበድኩትም ነበር። ደስታዬን ሙሉ ያደረገው ከሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር በኢሳት […]

እለተ አርብ ጥቅምት 14 ቀን 2007 ይላል የቀን መቁጠሪያው ። በጠዋቱ ተነስቸ መብተክተክ ይዣለሁ ፣ መነሻየ ከሳምንት በፊት በሃገረ ሊባኖስ መዲና ቤሩት ስሟን ለደህነንነት ስል የማልገልጻት ኢትዮጵያዊቷ የቤት ሰራተኛ በግድያ ወንጀል ተጠርጥራ ባለችበት ሁኔታ በነፍሰ ገዳይነት ውንጀላ መክሻሸፍ አስመልክቶ አዳዲስ መረጃን ለወዳጆቸ ለእናንተ ለማቀበል ነው ። ብዙም ሳልቆይ ቤሩት የመረጃ ምንጭ ወዳጆቸ ስልክ ደወልኩ … […]

ልማቱ የሀብት ምንጭን በማስፋት አቅምን የመገንባት የድርጅቱ ስትራተጅያዊ ዕቅድ አካል ነው ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት እስከ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ያለው ይዞታችን ይለማል 13 ሕንፃዎች፣ ባለ4 ኮከብ የእንግዳ ማረፊያ፣ የስብሰባ አዳራሽና ሙዝየም ሥራዎችን ያካትታል የግንባታ 3ቢልዮን ብር ወጪ 85% በኩባንያው፣ 15% በአስተዳደርና ልማት ድርጅቱ ይሸፈናል የከተማውን የቤት እጥረት ከማቃለልና የአካባቢውን ገጽታ ከመቀየር አገራዊ ጠቀሜታው ባሻገር …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ዛምቢያ ከብሪታንያ ቅኝ አገዛዝ ከተላቀቀች ትናንት፡ እአአ ጥቅምት ሀያ አራት፡ 2014 ዓም ሀምሳ ዓመት ሆናት። የነፃነቱ ዓወዳመት ትናንት በመላ ዛምቢያ በይፋ የተከበረ ሲሆን፡ የሀገሪቱ ዜጎች ዕለቱን በዚህ በያዝነው የጥቅምት ወር በተለያዩ ዝግጅቶች በማክበር ላይ ይገኛሉ።

ቅዱስ ሲኖዶስ በዛሬ፣ ጥቅምት ፲፭ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም. አራተኛ ቀን ውሎው የድሬዳዋና ምዕራብ ሐረርጌ ሊቀ ጳጳስ የኾኑት ብፁዕ አቡነ ዕንባቆም፣ በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ገዳማት ሊቀ ጳጳስ ኾነው እንዲሠሩ የምደባ ውሳኔ አሳልፏል፡፡ ምልአተ ጉባኤው ውሳኔውን ያሳለፈው፣ ከግንቦት ፳፻፭ ዓ.ም. ጀምሮ የኢየሩሳሌም ሊቀ ጳጳስ ኾነው በነበሩት ብፁዕ አቡነ ዳንኤልና በማኅበሩ መካከል በተፈጠረው አለመግባባት ዙሪያ ከመከረ በኋላ ነው፡፡ ቅዱስ …

በጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ

‹መለስ በህይወት ቢኖር ራሱ የሚቃወማቸው ይመስለኛል››
‹‹አቶ ኃይለማርያም፣ የራሱን አመለካከት አሳድራለሁ ያለ ቀን፤ ወደ እነአንዱአለም ጎራ ይቀላቀላል፤ መለስ ቢኖርም ባይኖርም!!!››
አቶ ሀብታሙ አያሌው /የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ/

አሁን በእስር ላይ ማዕከላዊ ሆኖ እና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በእግር ህመም እየተሰቃየ የሚገኘው የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ፤ አቶ ሀብታሙ አያሌው ከመታሰሩ 10 ቀናት ቀደም ብሎ ለ‹‹ቀዳሚ ገጽ›› ጋዜጣ እኔ እና ባልደረባዬ አናንያ ሶሪ በ‹‹መለስ ራዕይ›› ዙሪያ ሰፋ ያለ ቃለ ምልልስ አድርገንለት ነበር፡፡ ቃለ-ምልልሱም በጋዜጣው ላይ ተስተናግዷል፡፡ ቃለ-ምልልሱን ማንበብ ላልቻላችሁ ወገኖቼ ታነቡት ዘንድ የተወሰነውን እንዲህ አቅርቤዋለሁ፡-

ሙሉውን አስነብበኝ …

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም

ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ

እራሱን ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ/ወያኔ እያለ በሚጠራው እና ትግሉን በሰለጠነ መልኩበጠረጴዛውይይት እናየሀሳብ የበላይነት ሳይሆን ከጫካ በመግባት ብረትን የኃያልነት ዋስትናበማድረግ በንጹሀንዜጎች ደም ላይ ተረማምዶየጫካ ባህሪውን ከነግሳንግሱ እንዳለ ተሸክሞከህዝቦች ፈቃድ ውጭ በኃይልበህዝቦች ጫንቃ ላይ ተፈናጥጦ በሚገኘውየሽፍታ ቡድን የበላይነትየሚመራው በኢትዮጵያ ያለው ገዥአካል በአፍሪካ ወደር የማይገኝለት አምባገነን እናአረመኒያዊስብስብ እንደሆነ በተደጋጋሚ ስገልጽቆይቻለሁ። ዴሞክራሲ በህዝብ ለህዝብ የተቋቋመ ህዝባዊአስተዳደርከሆነ የወሮበላ አገዛዝ መንግስትደግሞ በዘራፊዎች እና በወሮበላዎች ለዘራፊዎች እናለወሮበላዎች የተቋቋመ የማፊያቡድን ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ፕ/ር መስፍን ወልደማሪያም

በግዞትም ቤት አደባባይ ታስሮ ሳለ የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደኤርምያስ መጣ፡– ሂድ ለኢትዮጵያዊውም ለአቤሜሌክ እንዲህ በለው፤ — የእሥራኤል አምላክ የሠራዊት ጌታ ፣ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤- እነሆ ለበጎነት ሳይሆን ለክፋት ቃሌን በዚህች ከተማ ላይ አመጣለሁ፤ በዚያም ቀን በፊትህ ይፈጸማል፤ በዚያ ቀን አድንሃለሁ፤ ይላል እግዚአብሔር፤ በምትፈራቸው ሰዎች እጅ አልሰጥህም፤ ፈጽሜ አድንሃለሁ፤ ነፍስህም እንደምርኮ ትሆንልሃለች እንጂ በሰይፍ አትወድቅም፤ በበእኔ ታምነሃልና ይላል እግዚአብሔር፡፡ ትንቢተ ኤርምያስ 39/15-18

ኑዛዜ ኤርምያስን አነበብሁ፤ጉድ ነው! አንድ የማውቀውን ነገር አረጋግጥሁ፤ ብዙ የማላውቃቸው ነገሮችን አወቅሁ፤ የማውቀው ነገር ሂሳብ የተማረ ሰው ምን ጊዜም ጭፍን ሎሌ መሆን የማይችል መሆኑን ነው፤ሂሳብ የተማረውን ሰው ለጭፍን ሎሌነት የሚቀጥረው ሰው ግን አንጎሉ የፈረጠ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ጋዜጠኛ ኤሊያስ ገብሩ 

‹ተመስገን፣ ጥሩ ታጋይ እና ሰው ሆኖ ከእስር ይወጣል››
‹‹ተመስገን፣ የህዝብ ልጅ ነው፤ ነገም ከነገወዲያም የህዝብ ልጆች ይፈጠራሉ››

እስክንድር ነጋ ‹‹ስለተመስገን ደሳለኝ ሃሳቤን አስተላልፍልኝ›› ካለኝ የተወሰደ

ከትናንት በስትያ፣ ሰኞ ዕለት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እና የአንድነት ፓርቲ ጸሐፊ የሆነውን አቶ አንዷለም አራጌን በ2007 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ ላገኛቸው ችዬ ነበር – ለአቤል አለማየሁ ጋር። ባለፈው ሳምንት የ‹‹ባንዲራ ቀን›› በተከበረበት ዕለት ቃሊቲ ከወዳጄ እዩኤል ፍስሐ ጋር ሄጅ እነስክንድርን መጠየቅ ሳንችል ተመልሰን ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ጥቅምት ፲፫(አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአዲስ አበባ ለ3ኛ ጊዜ በተዘጋጀው የፖለቲካ ስልጠና መድረክ ከወረዳ ጽ/ቤት እስከ ማዕከል ቢሮዎች የሚገኙ ሰራተኞች እና የፌደራል መ/ቤት ሰራተኞች ከማክሰኞ ጥቅምት 3 ቀን እስከ ቅዳሜ ጥቅምት 14/2007 ዓ.ም ለተከታታይ 11 ቀን የፖለቲካ ስልጠና የተሰጠ ሲሆን፣  በዚህ መድረክ እስካሁን ከታዩት በላይ በሰልጣኖችና በኢህአዴግ አመራሮች መካከል ፍጥጫ ታይቷል። ጠንካራ …

ጥቅምት ፲፫(አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢትዮጵያ በፈረንጆች አቆጣጠር ከ2008 እስከ 2013 በነበረው ጊዜ ከፖሊዮ ነጻ አገር ተብላ የተወደሰች ቢሆንም፣ ካለፉት 2 አመታት ጀምሮ በሽታው እንደገና መታየቱን ዩኒሴፍ አስታውቋል። ባለፈው አመት 10 የፖሊዮ ተጠቂዎች መታየታቸውን የገለጸው ዩኒሴፍ፣ የበሽታው እንደገና መከሰት ለአገሪቱ ፣ ለቤተሰቦችና ለህጻናቱ እጅግ አደገኛ ክስተት ነው ብሎአል። ኢትዮጵያ በሽታውን ለመከላከል ተጨማሪ …

ጥቅምት ፲፫(አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢትዮጵያውያኑ በህገወጥ መንገድ መግባታቸውን የገለጸው የኬንያ ፖሊስ፣  54ቱ ኢትዮጵያውያን በአንድ ቤት ውስጥ ታጭቀው ተገኝተዋል ብሎአል። ሰዎቹን ወደ ኬንያ ያመታው ግለሰብ መጥፋቱንም ፖሊስ ገልጿል። ኢትዮጵያውያንን ወደ ደቡብ አፍሪካ ማሻገር ትልቁ የገቢ ምንጭ እየሆነ መምጣቱን ፖሊስ ገልጿል። ወደ ደቡብ አፍሪካ እንጓዛለን በማለት ሙከራ ያደረጉ ኢትዮጵያውያን፣ በ ዝምባብዌ፣ ታንዛኒያ፣ ኬንያና …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች