ኤቦላ ተሐዋሲ መስፋፋትን ለመግታት የሚደረገዉ ጥረት በተጠናከረበት በዚህ ወቅት ላይቤሪያ ዉስጥ በጀርመን የሕክምና እርዳታ ድርጅት አክሽን ሜዲዮር የተገነባዉ የኤቦላ ታማሚዎች ማዕከል ግንባታ ተጠናቆ ሙሉ ሥራዉን ጀመረ።

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

በሊቢያ የሚታየዉ የፀጥታ ሁኔታ እጅግ አደገኛና አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ ስጋት ላይ ጥሎአል። ለዘመናት ሊቢያን በደቋሽ ክንዳቸዉ የገዙት የሊቢያዉ መሪ ሞአመር ጋዳፊ ከስልጣና ከተወገዱ ከሶስት ዓመት በኋላ ዛሬ የሚታየዉ የርስ በርስ ጦርነት ሀገሪቱን ወደ መንኮታኮት እያመራት መሆኑ ተመልክቶአል።

Image

የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ፖሊስ ጣቢያዎችን እንዲሰሩ ተጠየቁ Minilik Salsawi

የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች በየ አካባቢያቸው ለሚሰሩት አዳዲስ ፖሊስ ጣቢያዎች ገንዘብ እንዲያዋጡ መጠየቃቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ በየ አካባቢው የሚገኙት የፖሊስ ጣቢያዎች ነዋሪዎች ገንዘብ እንዲያዋጡ በየ ቤታቸው ደብዳቤና የገንዘብ መክፈያ ቅጽ እየሰጡ ሲሆን ነዋሪዎቹ ገንዘብ እንዲከፍሉ የተጠየቁበትን ቅጽ ሳይሞሉ መመለስ አይችሉም ተብሏል፡፡

ደብዳቤው ላይ ባለው የፖሊስ ጣቢያው ስልክ ቁጥር ደውለን ያነጋገርናቸውና ስማቸውን ለመግለጽ ፈቃደኛ ያልሆኑ አንድ የፖሊስ አባል ‹‹ህዝቡን ለምን ፖሊስ ጣቢያ እንዲሰራ ታስገድዳላችሁ?›› በሚል ላነሳነላቸው ጥያቄ ‹‹ህዝቡኮ ራሱ ነው ሴት ልጆቻችን በሰላም መግባት አልቻሉም እያለ ያለው፡፡ ፖሊስ የህዝብ እስከሆነ ድረስ ህዝብ ፖሊስ ጣቢያ ቢያሰራ ምን ችግር አለው? ህዝቡ አልከፍልም ካለ ሊቀር ይችላል፡፡ እናንተ ግን ይህን እንደጥያቄ የምታነሱት ስብሰባው ላይ ስላልነበራችሁ ነው፡፡›› ብለውናል፡፡

ከወራት በፊት ‹‹ማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ›› በሚል አደረጃጀት ህዝቡ በየቤቱና ከጎረቤት ጋር 1ለ5 በመደራጀት ከፖሊስ ጋር ግንኙነት እንዲኖረው የሚያዝ ህግ መውጣቱና ነዋሪዎቹንም ማደራጀት መጀመሩን ነገረ ኢትዮጵያ መዘገቧ ይታወቃል፡፡
Image

ደራሲ:- ኤርምያስ ለገሰ
ቅኝት:- መስፍን ማሞ ተሰማ

መንደርደሪያ
በድሮ ዘመን የኖሩ እንስሳት እንዲህ ዘመሩ።
የእንግሊዝ አራዊት፤
የአየርላንድ አራዊት፤
የየሀገሩ ሁሉ አራዊት፤
ተሳተፉ የደስታዬን ምንጩን፤
ስለመጪው ብሩህ ዘመን!
ይዘገያል ወይ ይፈጥናል፤
ያ! ቀን ግን ይመጣል፤
ጨቋኙ ሰው ይገረሰሳል! . . . ዘምረው ዝም አላሉም። ዘምረው አመፁ። አብዮት አፈነዱ፤ የእንስሳት አብዮት። በሚኖሩበት ሀገር – በእነሱ አጠራር፤ የእርሻ ጣቢያ – ለዘመናት በጭቆና ቀንበር ረግጦ ሲገዛቸውና ሲመዘብራቸው በኖረው የሰው ዘር ገዢያቸውና ግብረ አበሮቹ ላይ ሆ! ብለው ተነሱ። ቀንበር በቃን። ባርነት በቃን። ብዝበዛ በቃን። … ነፃነት እንጂ። 

ሙሉውን አስነብበኝ …

ዛሬ ህዳር 4/2007 ዓ.ም በፓርቲው ዋና ጽፈት ቤት መግለጫ የሰጠው የመኢአድ አዲሱ አመራር ከመኢአድ ጋር ተመሳሳይ ፕሮግራም ካላቸውና ከሌሎቹም የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር ከአሁን ቀደም አብሮ ለመስራት የተጀመረውን እንቅስቃሴ እንደሚያስቀጥል አስታውቋል፡፡

በ2003 ዓ.ም ከታህሳስ 15-17 ድረስ አይቤክ ሆቴል ጠቅላላ ጉባኤ ከተካሄደ በኋላ በፓርቲው አመራሮች መካከል ችግር እንደነበር የገለጸው አዲሱ አመራር ከዛ በኋላ አቶ አበባው መሃሪ ፕሬዝደንት የሆኑበት አካሄድ ትክክል እንዳልነበር፤ለአራት አመት ያህል በሁለቱ ቡድን መካከል የነበረው አለመግባባት በእርቅ እንደተቋጨና አቶ አበባው ኃላፊነታቸውን በፈቃዳቸው እንደለቀቁ የጻፉትን ደብዳቤ ዋቢ አድርጎ ገልጾአል፡፡ በመሆኑም የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች ያለ ምንም ገደብ ወደ መኢአድ ጽ/ቤት መምጣት ይችላሉ ሲል ጥሪውን አስተላልፏል፡፡

በአንጻሩ አዲሱ አመራር በህገ ወጥ መንገድ ነው ወደ ስልጣን የመጣው በሚል ቅር የተሰኙ የፓርቲው አመራሮችና አባላት ዛሬ ከሰዓት መግለጫ እንደሚሰጡ ተሰምቷል፡፡ ጉዳዩን ለማጣራት አቶ አበባው መሃሪ ጋር በተደጋጋሚ ብንደውልም የእጅ ስልካቸውን ሊያነሱ ባለመቻላቸው ሀሳባቸውን ማጠቃለል አልቻልንም፡፡

በሌላ በኩል አዲስ አመራር ማህተሙ አዲሱ አመራር ከመምጣቱ በፊት ፓርቲው ውስጥ በነበሩትና በአዲሱ አመራር ጋር ባልተስማሙ አካላት እንደተሰረቀ አስታውቋል፡፡ ‹‹ማህተሙ ከዚህ ቤት በነበሩ ሰዎች ተሰርቋል፡፡ ይህን ጉዳይ በወቅቱ ለፖሊስ አመልክተናል፡፡ በፓርቲው ማህተም እኛ የማናምንበትና ህገ ወጥ ነገር ቢሰራበት ተጠያቂ የሚሆኑት እነሱ ናቸው፡፡›› ሲሉ አዲሱ የፓርቲው ፕሬዝደንት አቶ ማሙሸት አማረ ገልጸዋል፡፡

– ለአስነዋሪ ተግባር ሽፋን የቃለ ህይወት ቤተክርስቲያን የሳምንት ቀለብ ልታቀርብ ነው::
– ለጉባዔ ተብሎ የጠፉት አገልግሎቶች ለጊዜው እንዲስተካከሉ መደረጉ በህዝቡ ዘንድ መነጋገሪያ ሆኗል
Minilik Salsawi

ከህዳር 6/2007 ዓ.ም እስከ ህዳር 10/2007 ዓ.ም በሶዶ ከተማ የሚደረገውን የደኢህዴን ድርጅታዊ ጉባዔ አስመልክቶ ሶዶ ከተማ ውስጥ የሚገኙ ጎዳና ተዳዳሪዎች በግዳጅ ወደ ካምፕ እንዲገቡ መደረጋቸውን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገለጹ፡፡

በመቶዎቹ የሚቆጠሩ ሴት፣ አዛውንትና ህጻናት ጎዳና ተዳዳሪዎች ሶዶ ውስጥ አራዳ ክፍለ ከተማ ተብሎ በሚጠራውና አዲስ እየተሰራ በሚገኘው ገለሜ የተባለ እስር ቤት ውስጥ በግዳጅ እንዲገቡ መደረጉን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገልጸዋል፡፡ ካምፕ ውስጥ የገቡትን የጎዳና ተዳዳሪዎችም የቃለ ህይወት ቤተ ክርስቲያን ለሳምንት ቀለብ እንደሚያቀርብላቸውና ጉባዔው ካለቀ በኋላ ወደነበሩበት እንደሚመለሱም ምንጮቻችን አክለው ገልጸዋል፡፡

‹‹ለጉባኤው ሲባል ዜጎችን በግዳጅ ወደ ካምፕ ማስገባቱ ደኢህዴን በከተማዋ ልማት እንደተመዘገበና ህዝቡን ከድህነት እንዳላቀቀ ለማስመሰል ያደረገው አስነዋሪ ተግባር ነው›› ያሉት የሰማያዊ ፓርቲ የወላይታ ዞን የአደረጃጀት ኃላፊ አቶ ታደመ ፈቃዱ ‹‹እስካሁን ሶዶ ከተማ ውስጥ መብራት ስለማይኖር በርካቶች ተዘርፈዋል፡፡ የተገደሉም አሉ፡፡ የከተማዋ ውበትም እምብዛም የተጠበቀ አልነበረም፡፡ አሁን ግን ከተማዋን ለማጽዳት እየተሯሯጡ ነው፡፡ መብራት ባልነበረበት ከተማ መንገዱ ሁሉ ባውዛ ሆኗል›› ሲሉ ስለሁኔታው አስረድተዋል፡፡

ለደኢህአዴን ጉባዔ ተብሎ የከተማዋ ውበት እንዲጠበቅና የጠፉት አገልግሎቶች ለጊዜው እንዲስተካከሉ መደረጉም በህዝቡ ዘንድ መነጋገሪያ ሆኗል ተብሏል፡፡ ስለ ጉዳዩ ያነጋገርናቸው አንድ የከተማዋ ነዋሪም ‹‹ህዝቡ በአገልግሎቶች መጥፋት ተማሯል፡፡ የከተማው ውበት ለሚኒስትሮቹ እንጅ ለእኛ አይደለም፡፡ እንዲህ ከሆነ ደኢህዴን በየ15 ቀኑ ጉባዔ ቢያደርግ ጥሩ ነበር›› ሲሉ ስለሁኔታው ገልጸውልናል፡፡

ለጉባዔው ሲባልም በጸጥታ ስም በተቃዋሚዎች ላይ ክትትል እየተጠናከረ ይገኛል ያሉት አቶ ታደመ ‹‹ከተማዋ በፖሊስ ተጥለቅልቃለች፡፡ ፖሊሶች በየ 10 ሜትሩ ቆመው ነው የሚታዩት፡፡›› ብለዋል፡፡

– የሁለቱንም አንጃዎች ዜና ዝርዝር ይመልከቱት :: – ድጋሚ እርቅ ያስፈልጋቸዋል; Minilik Salsawi
– ምርጫ በመጣ ቁጥር ስህተትን በመደጋገም የኢትዮጵያን ሕዝብ ትግል ማደናቀፍ ማብቃት አለበት::
– በህዝባችን ላይ እየተፈጸመ ያለው የፖለቲካ አሻጥር (ሳቦታጅ) ግልጽ መሆን አለበት::
– አዲሱ የመኢአድ አመራር ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር የተጀመረው ግንኙነት እንደሚያስቀጥል አስታወቀ
– አዲሱ የመኢአድ አመራር የፓርቲውን ማህተም ተሰርቄያለሁ ብሏል

በዚህም መሰረት በአቶ አበባው መሃሪ የሚመራው መኢአድ ስልጣኑን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ በኢሓዴግ ጥርስ ውስጥ በመግባቱ ከምርጫ ቦርድ እውቅና ከመነፈጉም በላይ ከአንድነት ጋር ሊያደርገው የነበረው ውህደት በምርጫ ቦርድ እንቅፋትነት ተንጠልጥሎ የቀረ ከመሆኑም በላይ የምርጫው ውህደት በሚፈጸምበት እለት አሁን መኢአድን በአመራርነት ላይ ነኝ የሚሉት አቶ ማሙሸት የኢትዮጵያን ቴሌቭዥንን እና የደህንነት ሃይሎችን አስከትለው በመምጣት አከባቢው ላይ ችግር ተፈጥሮ እንደነበር ይታእሳል::

ይህንን ተከትሎ አቶ ሃይሉ ሻውል በተገኙበት እርቅ ተፈጸመ ቢባልም ውጥረቱ ሰፍቷል የሚሉ የድርጅቱ አባላት እየተናገሩ ነው በዛሬው እለት ነገረ ኢትዮጵያ ለምንሊክ ሳልሳዊ በላከው ዜና መሰረት እና በአቶ አበባው የሚመራው የመኢአድ ጓድ የሰጠው መግለጫ እንደሚከተለው ሰፍሯል::

ዛሬ ህዳር 4/2007 ዓ.ም በፓርቲው ዋና ጽፈት ቤት መግለጫ የሰጠው የመኢአድ አዲሱ አመራር ከመኢአድ ጋር ተመሳሳይ ፕሮግራም ካላቸውና ከሌሎቹም የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር ከአሁን ቀደም አብሮ ለመስራት የተጀመረውን እንቅስቃሴ እንደሚያስቀጥል አስታውቋል፡፡

በ2003 ዓ.ም ከታህሳስ 15-17 ድረስ አይቤክ ሆቴል ጠቅላላ ጉባኤ ከተካሄደ በኋላ በፓርቲው አመራሮች መካከል ችግር እንደነበር የገለጸው አዲሱ አመራር ከዛ በኋላ አቶ አበባው መሃሪ ፕሬዝደንት የሆኑበት አካሄድ ትክክል እንዳልነበር፤ለአራት አመት ያህል በሁለቱ ቡድን መካከል የነበረው አለመግባባት በእርቅ እንደተቋጨና አቶ አበባው ኃላፊነታቸውን በፈቃዳቸው እንደለቀቁ የጻፉትን ደብዳቤ ዋቢ አድርጎ ገልጾአል፡፡ በመሆኑም የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች ያለ ምንም ገደብ ወደ መኢአድ ጽ/ቤት መምጣት ይችላሉ ሲል ጥሪውን አስተላልፏል፡፡

በአንጻሩ አዲሱ አመራር በህገ ወጥ መንገድ ነው ወደ ስልጣን የመጣው በሚል ቅር የተሰኙ የፓርቲው አመራሮችና አባላት ዛሬ ከሰዓት መግለጫ እንደሚሰጡ ተሰምቷል፡፡ ጉዳዩን ለማጣራት አቶ አበባው መሃሪ ጋር በተደጋጋሚ ብንደውልም የእጅ ስልካቸውን ሊያነሱ ባለመቻላቸው ሀሳባቸውን ማጠቃለል አልቻልንም፡፡

በሌላ በኩል አዲስ አመራር ማህተሙ አዲሱ አመራር ከመምጣቱ በፊት ፓርቲው ውስጥ በነበሩትና በአዲሱ አመራር ጋር ባልተስማሙ አካላት እንደተሰረቀ አስታውቋል፡፡ ‹‹ማህተሙ ከዚህ ቤት በነበሩ ሰዎች ተሰርቋል፡፡ ይህን ጉዳይ በወቅቱ ለፖሊስ አመልክተናል፡፡ በፓርቲው ማህተም እኛ የማናምንበትና ህገ ወጥ ነገር ቢሰራበት ተጠያቂ የሚሆኑት እነሱ ናቸው፡፡›› ሲሉ አዲሱ የፓርቲው ፕሬዝደንት አቶ ማሙሸት አማረ ገልጸዋል፡፡

ከዚህ በታች የመኢአድ ፕረዚዳንት አቶ አበባው መሃሪ ከስራ አስፈጻሚዎቹ ከአቶ ካሳሁን እና ከአቶ ሲራክ ጋር የሰጡትን መግለጫ በጥሞና ያንብቡ::
Image
Image
Image

“ስልጣኔን የለቀኩት በአንዳንድ ብልጣብልጦች እና የሴራና አድማ አካሄድ በሚችሉ ሰዎች ፓርቲው ስለተጠለፈ ነው::’ – አቶ አበባው መሓሪ የመኢአድ ፕሬዚዳንት

“ፓርቲው ወደፊት ለመራመድ የማይችልበት ወደፊትም የማይሻሻልበት ደረጃ ላይ ደርሷል::”አቶ አበባው
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)

የመኢአድ ፕረዚዳንት የነበሩት አቶ አበባው መሓሪ ስልጣናቸውን ሊለቁ የቻሉት በገጠማቸው አስገዳጅ የድርጅታዊ የውስጥ ጉዳይ መሆኑን ተናግረዋል እንደ አቶ አበባው ደብዳቤ በአብዛኛው የመኢአድ አባላት ከፍተኛ የድምጽ ድጋፍ ከተመረጥኩበት የፕሬዚዳንትነት ቦታ ላይ ድርጅቱ ወደፊት እንዳይራመድ የሚያደርጉ እና ከዚህ በፊት ተሳስረውና ተቆላልፈው በመጡ የውስጥ ችግሮች ለሃገራቸው መስራት አለመቻላቸውን በመጥቀስ ፓርቲው ወደፊት የማይራመድበት አጣብቂኝ ውስጥ መሆኑን ለጠቅላላው ጉባዬ ገልጸዋል::

የመኢአድ የውስጥ ችግር በመጪው የኢትዮጵያ ሕዝብ ትግል ላይ ውሃ የቸለሰ ነው ያሉት አቶ አበባው ኢትዮጵያውያን አቤት የሚልላቸው አካል እየጎደለ መሄዱን ጠቁመው በመኢአድ ውስጥ ያለው ችግር ከአቅም በላይ የሆነ ስለሆነ ፍርዱን እና መዝገቡን ለታሪክ በመተው ስልጣናቸውን እንደለቀቁት ከአቅም በላይም እንደሆነ አስረድተዋል::

ከአቅም በላይ ያሉትን ጉዳይ ሲገልጹ … ለየኢትዮጵያውያን ምሁራን ከትግሉ መሸሽ ምክንያቱ የትግሉ መስመር በአንዳንድ ብልጣ ብልጦች እና የሴራ እና የአድማ አካሄድን በሚችሉ ግለሰቦች ስለሚተለፍ መሆኑን መኢአድ ውስጥ ከተከሰተው ችግር እንደተገነዘቡ በደብዳቤያቸው ገልጸዋል::

የአቶ አበባው መሃሪ ፊርማ የሰፈረበትን ሙሉ ደብዳቤውን ከታች ያንብቡት :
Image

G20 በመባል የሚታወቁት የአለም ከበርቴ ሀገሮች መሪዎች በሳምንቱ ማብቂያ ከህዳር 6 እስከ 7 በ Brisbane ተገናኝተው በምጣኔ ሃብትና ልማት እድገት ላይ ለመነጋገር እየተዘጋጁ ባሉበት ወቅት፥ አፍሪካ ከዚህ ጉባኤ ተጠቃሚ ትሆናለች ወይ የሚሉ ጥያቄዎች ቀርበዋል።

ኀዳር ፬(አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ካለፈው አንድ ወር ጀምሮ በአካባቢው የሰፈሩ የፌደራል ፖሊስ አባላት በህዝቡ ላይ የሚወስዱት እርምጃ እየተባባሰ መጥቶ ረቡዕ ሌሊት ለሃሙስ አጥቢያ ፣ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ የፌደራል ፖሊሶች ወደ አንድ ወጣት መኖሪያ ቤት ሰብረው በመግባት እርሱንና እናቱን በአምስት አምስት ጥይኦች በአሰቃቂ ሁኔታ ገድለው ወደ ካምፓቸው አምርተዋል። የከተማው ህዝብ ተቃውሞውን ለማሰማት …

ኀዳር ፬(አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በቦሌ ለሚ በሚባለው አካባቢ የማሪያም ቤተክርስቲያን እንዲፈርስ መደረጉን የተቃወሙ ነዋሪዎች ከፖሊሶች በደረሰባቸው ጥቃት በርካታ ሰዎች የተጎዱ ቢሆንም፣ ፖሊስ ሃይሉን አሰባስቦ በመምጣት በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ወጣቶችን ይዞ አስሯል። አብዛኞቹ ወጣቶች በኮብል ስቶን ስራ ላይ ተሰማርተው የሚገኙ ሲሆን፣ ፖሊስ ወደ ድርጅቶቹ በመሄድ ወጣቶችን በጅምላ ማሰሩን የአይን እማኞች ገልጸዋል። ወንድሞቹ …

ኀዳር ፬(አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያውያን መብቶች የተባለው ድርጅት ለኢሳት በላከው መግለጫ የቶም ላንሶቶስ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች አያያዝ ዙሪያ ታዋቂ ሰዎች ሃሳባቸውን እንዲያካፍሉ ጋብዟል። ተናጋሪዎቹ በኢትዮጵያ ያለውን የሰብአዊ መብት አያያዝ በመገምገም የአሜሪካ መንግስት የዲፕሎማቲክና የገንዘብ ድጋፉን ተጠቅሞ በኢትዮጵያ የሚታየው የተበላሸ የሰብአዊ መብት አያያዝ እንዲሻሻል ግፊት ያደርጋል ተብሎ …

ኀዳር ፬(አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የፌዴራሉ ዐቃቤ ሕግ የዕንቁ መፅሔት አዘጋጅ በነበረው ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ ላይ የተሳሳተ መረጃን በመስጠት፣ ማነሳሳትና ግዙፍ በሆነ ማሰናዳት ወንጀል  የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 2ኛ ወንጀል አራዳ ምድብ ችሎት ህዳር 2 ቀን 2007 ዓ.ም ክስ የመሠረተበት ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ የተጠየቀውን የ20ሺህ ብር ዋስትና ማቅረብ ባለመቻሉ በቂሊንጦ በእስር ላይ …

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

ኢትዮ ቴሌኮም በአዲስ አበባ እና በክልሎች በሚሰጠው አገልግሎቱ ላይ የሚታየው ጉድለት ተጠቃሚዎችን ቅር አሰኘ። በተለይ ተገልጋዮች በሞባይል ስልክ እና በኢንተርኔት መቆራረጥ እጅግ መማረራቸውን ከመግለጽ ወደኋላ አላሉም።

በቀድሞዋ ምሥራቅ ጀርመን ይኖሩ የነበሩትና የዚያን ግዜዎቹ ኢትዮጵያዉያን የከፍተኛ ተቋም ተማሪዎች የሁለቱን ጀርመኖች ዉሕደት እንዴት አገኙት። የቀድሞቆቹ ተማሪዎች የዛሪዋን ጀርመንና ከዉሕደቱ በፊት የዛሬ 25 ዓመቱን የምሥራቅ ጀርመን የባህልና ኑሮ ልዩነት እንዲሁም ትስስር እንዲያጫዉቱን ጋብዘናል።

በቡርኪና ፋሶ የቀድሞው ፕሬዚደንት ብሌዝ ካምፓዎሬ በሕዝብ ኃይል የታከለበት ተቃውሞ ከሥልጣናቸው ወርደው ወደ ጎረቤት ኮት ዲቯር ሸሽተዋል። ሕዝቡ ካምፓዎሬ በህገ መንግሥቱ ላይ ማሻሻያ በማስደረግ የሥልጣን ዘመናቸውን ለማራዘም ያደረጉትን ጥረት በመቃወም ያካሄደው ዓመፅም አብቅቷል።

የናይጄሪያው ፕሬዚዳንት ጉድላክ ጆናታን በጎርጎሪዮሳዊው አዲስ ዓመት ለዳግም ዘመነ-ሥልጣን በመመረጥ እንደሚወዳደሩ መግለጣቸው በናይጄሪያውያን ዘንድ ከወዲሁ ቁጣ እና ደስታን የቀላቀለ ስሜት ፈጥሯል።

ከአምስት ቀናት የባሕር መናወጥ ቆይታ በኋላ ከጣሊያኗ ላምፔዱዛ ደሴት እስከ ሊቢያ ጠረፍ የባሕሩ ሞገድ ረግቷል። ካለፈው አንድ ሣምንት አንስቶ ደግሞ «ቪያኖ ዶ ካስቴሎ» የተሰኘችው የፖርቺጊዝ ባሕር ቃኚ መርከብ ከላምፔዱዛ 55 ኪሎ ሜትሮች ደቡባዊ ርቀት ላይ መቅዘፍ ጀምራለች።

በሙያ የአፈርና ቋጥኝ እንዲሁም የእሳተ- ገሞራ ተማራማሪ ነው– «ጂዎፊዚስት»፤ ጠፈርተኛ ፣ አሌክሳንደር ጌርስት! ካለፈው ዓመት ግንቦት 20 ቀን 2006 ዓ ም አንስቶ ግን፣ እስካለፈው እሁድ፣ ከምድር አናት ላይ ሆኖ ፣ ማለት 418ኪሎሜትር ከፍ ብሎ ነበረ ምርምሩን ሲያካሂድ የቆየው።

የጉልቾቹ ስም ብአዴን፣ኦህዴድ፣ደህዴን ሲባሉ የተሰሩትም ዴሞክራሴ ከተባለ ዘረመል(ሴል) ሆኖ ይህ ሴል ያለማችን ገራሚው የጉልቾች ሴል ተብሎ እንዲመዘገብ እራሱን ነፃ አውጭ ብሎ የሰየመው ህወሓት ባለም ቅርስነት እንዲመዘገብ አድርጉዋል፡፡

ይህ ሴል በውስጡ ሂዎት የሌለው አርቴፊሻል የህወሓት የላባራቶሪ መመራመሪያ ሲሆን እስካሁንም ወደር ያልተገኘለት ሂዎት አልባ ተንቀሳቃሽ ቁስ ግን የዎያኔ መጠቀሚያ ሆኖ ያገለግላል፡፡

አስገራሚው ነገር ህወሓት የሚባለው በድን የዴሞክራሴ ሴል ሰራሽ አካል የዴሞክራሴ ፅንሰ ሀሳብ የሌለው እራሱን ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ብሎ የሰየመ ሆኖ አላማውም የትግራይን ህዝብ እና ህዝብ ብቻ ነፃ ለማውጣት የተቋቋመ ጠባብና ዘረኛ የፖለቲካ አጀንዳ ያነገበ መሆኑ ነው፡፡

ሌላው ገራሚ የሚያደርገው ነገር እራሱን ህወሓትን ጨምሮ ሌሎች ኦህዴድ፣ደህዴን በድን የዲሞክራሴ ሴል ውስጣቸው እንዳለ ተደርገው የተሰሩት ቁሶች ህዝብ የሚል ሌላ የሚያምታታ ማጭበርበሪያ ታቤላ የተለጠፈባቸው ሲሆን ብአዴን የሚለው ጉልቻ ግን ከህዝብ ይልቅ ብሄር የሚል መታወቂያ ተሰጥቶታል ምክንያቱም ይህ ስም ለህወሓት የፖለቲካ መሳሪያ በቀጥታ ላገልግሎት እንዲጠቅም ተፈልጎ ነው፡፡
እዚህ ጋር መጤን የሚገባው ነገር ብሄር በሚለው ስም ብሄርብሄረሰቦች የሚለውን ሌላ የፖለቲካ ትርፋ ለማምጣትና የሰደቅ አላማውን የቀድሞ ልዕልናውን ለማሳጣትና የምሐለኛውን ሴጣናዊ ምናምንቴ በብሄር ብሄረሰብ ስም ለመለጠፍ ተፈልጎ የተሰራ አገር የማፍረስ ደባ ነው፡፡

አሁን ህወሓት በዚህ መልኩ ጉልቻዎቹን ከሰራ በሗላ ሁሉንም አንድ ለማድረግ የተጠቀመበት ዘዴ ጉልቾቹ ከተሰሩበት በድን የዴሞክራሴ ሴል በቀጥታ ሴሉን በመውሰድ ኢህአዴግ ብሎ በመሰየም ዋና ህዝብን ለማወናበድ ወደሚጠቀምበት አዛኝ ቅቤ አንጉዋች እንደሚባለዉ የጭቃ እሾኩን በኢትዮጵያ ህዝብ ውስጥ ተከለ፡፡

አሁን የሚቀረዉ ቁጭ ብሎ በነዚህ ከንቱ ያትራፊነት የሴራ መረብ በመጠቀም ምሁር ነን የሚሉትን ሁሉ በማታለልና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ይፈቀዳል፣መናገር ይቻላል፣መፅፍ ይቻላል እናም ሌሎች ኘሮፖጋንዳዎችን በመናገርና ህገመንግስት እያለው በሚጠራው ምናምንቴው ለይ የፃፈዉን በማየት ህብረተሰቡ እውነት መስሎት ተሸወደ ምሁሩም ተግባራዊ ለማድረግ ሞከረ ግን እንደማይቻል ሲያውቅ የታሰረውም ታስሮ ሞት የተፈረደበትም ተገደለና ጥቂት የማይባለው ወገኔ ሲሰደድ አብዛኛው ህብረተሰብ በሲቃይ መዓበል ውስጥ መፍተሄ አልባ የፅር ድምፅ እያሰማ በሐገሩ ባይተዋርና የበይ ተመልካች ሆኖ ተቀምጡዋል፡፡

ሶስቱ ጉልቾች የህወሓት የጀራ መጋገሪያ ምጣድ ለማስቀመጭያነት በቀጥታ የዋሉ ሲሆን አንዳንድ ግዜም ወጥ ለመስሪያ የሚጠቅም ድስት መጣጃዎች ሆነው እናያቸዋለን እዚህ ጋር ግን ሌላ ማስተዋል የሚጠበቅባችሁ ነገር የጉልቻዎቹ ትክክለኛ በድንነት የምትለዩት ምንም እሳት ቢነድባቸው ሚሊዮን እንጀራ ቢጋገርባቸው ቅንጣት የማይሰማቸው ስሜት አልባ እቃዎች መሆናቸዉ ነው፡፡

የሰወስቱ ጉልቾች አባላቶችና ደጋፊዎች ሆይ እባካችሁ ፈጣሪ ነፍስ ከዘራባችሁ ይህንን አንብቡትና የህወሓትን ስውር አደንዳ ከስር መሰረቱ ለመገርሰስ ሞክሩ ቢያንስ ለልጅ ልጆቻችሁ ታሪክ ነውና ንቁ፡፡ይሄንን ለማድረግም አይመሽባችሁም እስኪ ግማሾቻችሁ እንኩዋን በቃን ብላችሁ የዚህ አይነቱን የርግማን እንጀራ ከመብላት ተቆጠቡ ምክንያቱም አሁን የምትበሉት የህዝብ ስጋ ሲሆን የምጠጡትም የወገናችሁ እንባና ደም ነዉና ትውልድ ይዳን ትላንት የገደላችሁትና ያስገደላችሁት የግፍ ፅዋ ይብቃ እላችሗለሁ፡፡

ከላገሬ ኢትዮጵያ
03/03/2007
Image

ትንሽ የግል አስተያየት በሰማያዊ ላይ
==================== Girma Kassa
ኃዳር ሰባት ቀን በቤልሄር ሜዳ ሰማያዊ ፓርቲ ብዙም ስማቸው ከማይታወቅ ድርጅቶች ጋር በመሆን የአደባባይ ሕዝባዊ ስብሰባ ጠርቷል። የአደባባይ ስብሰባ ማለት ብዙ ከሰልፍ ተለይቶ የሚታይ አይደለም።
የሰማያዊ ፓርቲ ሰኔ ወር 2005 ከምርጫ ዘጠና ሰባት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሰልፍ በማድረግ ታሪክ የሰራ ድርጅት ነው። ወደ ሰባ ሺህ የሚሆን ሕዝብ በሰልፉ ተገኝቶ ነበር። ሰማያዊ ባደረገው ሥራ አንድነቶች ከእንቅልፋቸው ነቅተው የሚሊዮኖች ድምጽ በሚል ተስፋ ሰጪና አገር እቀፍ እንቅሳሴም ለማድረግ ችለዋል። ለዚህ የሰማያዊ ፓርቲ ትልቅ ምስጋና ይገባዋል።

ትንሽ ድጋፍ ሲያገኙና በየቦታው ስማቸው ሲጠራ፣ የሰማያዊ መሪዎች ሌሎች ድርጅቶችን ማሳነስ ጀመሩ። ሊቀመንበሩ ይልቃል «ምን የሚረባ ድርጅት አለ ብለህ ነው?” ብሎ እንደተናገው። በዚህ ምክንያት ከብዙ ድርጅቶች ጋር ሰማያዊ መጋጨት ጀመረ።

የአንድነት ፓርቲ ሚያዚያ 5 2006 በአዲስ አበባ ሰልፍ ለማድረግ ጠየቀ። ገዢው ፓርቲ እውቅና አልሰጥም አለ። ሚያዚያ 12 ተጠየቀ። ያኔም አልተቻለም ወደ ሚያዚያ 26 ሰልፉ ዞር። በዚህ መሃል ሰማያዊዎች በመሃል ገብተው፣ ሚያዚያ 12 ሰልፍ ለማድረግ ጠየቁ። ለአንድነት ተከልክሎ ለነርሱ እውቅና ተሰጣቸው (ያው አገዛዙ ማጋጨት ይወድ የለም) አብዛኞቻችን የሰማያዊ ድርጊት አልተመቸንም። ባይሆን ሰልፉ ከአንድነት ጋር ለምን አይደረግም ብለን ተሟገትን። በይልቃል የሚመራው የሰማያዊ አመራር ግን የአብራችሁ ቁም ጥሪያችንን አጣጣለው። ግትር ሆኑ።

በሰልፉ ቀን፣ የአዲስ አበባ ሕዝብ ለሰማያዊች መልእክቱን አስተላለፈ። ከዘጠኝ ወራት በፊት ወደ ሰባት ሺህ የወጣ ሕዝብ፣ ሰማያዊዎች ግማሽ ሚሊዮን ጠብቀው፣ ከአራት መቶ የማይበልጥ ህዝብ ብቻ ተገኘ። ሰማያዊ ትልቅ የፖለቲካ ክስረት አጋጠመው። በርካታ አባላቱም የአመራሩን ግትርነት መጠየቅ ጀመሩ። በአንድ አመት ዉስጥ የሰማያዉ ድጋፍ ወደ ታች አሽቆለቆለ።

በህዳር ሰባቱ ሕዝባዊ ሰብሰብ ወይም ሰልፍ፣ ከዚህ በፊት ግማሽ ሚሊዮን የሚደርስ ሕዝብ ይገኛል ብለው የነበሩት ሰማያዊዎች፣ «ወደ ሶስት ሺህ ይገኛል» አሉ። ሶስት ሺህ ሰው ብቻ የሚጠበቁ ከሆነ ለምን በአንድ አዳራሽ ስብሰባዉን እንደማያደርጉት አልገባኝም። ይመስለኛል በወረቀት ሶስት ሺህ ይበሉ እንጂ፣ በመቶ ሺህ የሚቆጠር ህዝብ ይገኛል የሚል ግምት ዉስጥ ዉስጡን ሊኖራቸው ይችላል።

የሰማያዊ ፓርቲ ሕዝባዊ ስብሰባዉን አዘጋጀሁ፣ የሚለው ከሌሎች ስምንት ድርጅቶች ጋር ነው። ከነዚህ ድርጅቶች ዉስጥ መኢአድን ስታስወጡት የሚቀሩት ሰባት ናቸው። (ለምን መኢአድ በአሁኑ ወቅት በዉስጥ ችግሮቹ የተጠመደ ስለሆነ)። ሰባቱ ድርጅቶች የኦሞ ህዝቦች፣ የከንባታ ሕዝቦች የመሳሰሉ፣ ጥቂት ግለሰቦችን ያካተቱ፣ የማይታወቁ ድርጅቶች ናቸው። እነዚህን ድርጅቶችን አሰባሰቦ ሰማያዊ ትልቅ ትብብር እንደተፈጠረ ለማስመሰል ተሞከረ እንጂ፣ በዋናነት ይሄንን ስብስበ የሚያንቀሳቅሰው የሰማያዊ ፓርቲ ነው።
ይህን ስጽፍ ከላይ ባየሁት ነው። ዉስጣዊ ድርጅታዊ ሥራ ተሰርቶ፣ በቂ ዝግጅት ተደርጎ ሊሆን ይችላል። በርግጥ ያኔ ብዙ ሳይታወቁ የመጀመሪያዉን ሰልፍ ባደረጉ ጊዜ የተገኘውን ያህል ወደ ሰባ ሺህ የሚቆጠር ህዝብ ከተገኘ፣ በርግጥ ትልቅ ነገር ነው። ለአገዛዙም ጠንካራ መልእክት ለማስተላለፍ ይቻላል።

ሆኖም አንድ ነገር በግልጽ መታወቅ አለበት። ሰልፍ መጥራትና በሰልፉ ዉጤት ማስመዝገብ የተለያዩ ነገሮች መሆናቸውን። ብዙ ተጠብቆ የመጣው ሰው ቁጥር ካነሰ የፖለቲክ ክስረትም ሊሆን ይችላል። ሰማያዊ ፓርቲ ከዚህ በፊት ሰባ ሺህ ሕዝብ ሰብስቦ፣ እንደገና በመቶ የሚቆጠር ሰው ብቻ ከመጣለት፣ ፓርቲው መንገዱን እና ስትራቴጂዉን መቀየር ይኖርበታል እላለሁ። ደርጅቱ እንደዚህ ወደ ታች እንዲያሽቆለቁል ያደረጉ ግትር የአመራር አባላቱን ተጠያቂ ማድረግና መቀየር ያስፈልጋል። እየተደረገ ያለው፣ ብዙዎችን ትልቅ ዋጋ የሚከፍሉበት አገርን ነጻ የማውጣት ትግል እንጂ የግለሰቦችን ወይንም ትናንሽ አማባገነኖችን ተክለ ሰዉነት መገንባት አይደለም።

ለማንኛውም ከእሁድ በኋላ ፣ የድርጅቱን ጥንካሬና የአስቀድሞ ዝግጅት አይተን በስፋት ትንተናዎች እናቀርባለን። የፌስ ቡክ ዘመቻው ግሩም እንደሆነ ታዝቢያለሁ። በሜዳ በየወረዳዉና በየቀበሌውስ ? የምናየው ይሆናል …

• ‹‹ይህ ሁሉ የሆነው የእምነቱን ተከታዮች በመናቅ ነው››

ትናንት ህዳር 3/2007 ዓ.ም ከቀኑ 5 ሰዓት ጀምሮ በቦሌ ክፍለ ከተማ የማሪያም ቤተ ክርስቲያን እንዳይፈርስ በመቃወማቸው የታፈኑት ዜጎች የት እንደደረሱ አልታወቀም ሲሉ በወቅቱ ጉዳዩን ሲከታተሉ የነበሩ የአካባቢው ነዋሪዎችና የእምነቱ ተከታዮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡

በወቅቱ 600 ያህል ዜጎች ተገኝተው ቤተ ክርስቲያኗ እንዳትፈርስ ሲቃወሙ እንደተመለከቱ የገለጹት የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች የቤተ ክርስቲያኗን መፍረስ የተቃወሙትን ጨምሮ ሌሎች በአካባቢው የተገኙ ዜጎችም በፖሊስ መታፈሳቸውን ገልጸዋል፡፡ ነዋሪዎቹ ‹‹ህዝቡ በሰንደቅ አላማ አምላክ አታፍርሱብን እያለ ቢለምንም እነሱ ግን ጥይት ወደላይ በመተኩስ ህዝቡን ከማሸበራቸውም በላይ ያገኙትን እየደበደቡ በ9 የድንጋይ መጫኛ መኪና አስገድደው በመጫን ወዳልታወቀ ቦታ ውስደዋቸዋል፡፡ አድማ በታኝ ፖሊስ ቄስ፣ አዛውንት፣ ህጻንና ሴት ሳይል ያገኘውም አፍሶ ወስዷል፡፡ የኮብል ስቶን ጠራቢዎች ሳይቀሩ በአካባቢው በመገኘታቸው ታፍሰው ታስረዋል፡፡ አሁን የት እንዳሉ አይታወቅም፡፡›› ሲሉ ገልጸዋል፡፡

ቤተ ክርስቲያኗ ከተሰራች ከሁለት አመት በላይ እንደሆነ የገለጹት አንድ የአካባቢው ነዋሪ ‹‹ቤተ ክርስቲያኗ ከተሰራችበት ጊዜ ጀምሮ እንድትፈርስ ጥያቄ እንደቀረበ ተገልጾልን አያውውም፡፡ አሁን ነው ደርሰው ያፈረሱት፡፡ የቤተ ክርስቲያኗን አገልጋዮች ጨምሮ በጣም ብዙ ሰው በዱላ ተደብድቧል፡፡ ይህ ሁሉ የሆነው የእምነቱን ተከታዮች በመናቅ ነው፡፡›› ሲሉ ቅሬታቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

የአካባቢው ነዋሪዎችና አማኞች ከቀኑ 5 ሰዓት ጀምሮ እስከ 9 ሰዓት ቤተ ክርስትያኗ እንዳትፈርስ እንደተቃወሙ፣ አድማ በታኝ ፖሊስ በአካባቢው ያገኘውን ሰው ካፈሰ በኋላ ቤተ ክርስቲያኗን በማፍረስ ቆርቆሮውን በመኪና ጭኖ እንደሄደ የአይን እማኞች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

በመተማ ገንዳ ውሃ በአርማጮህ እንዲሁም በጭልጋ ከህዝብ አመጽን ተከትሎ ከፍተኛ ተኩስ እየተሰማ መሆኑን የአከባቢው ምንጮች ጠቁመዋል::በተልይ በመተማ ገንዳ ውሃ ከፍተኛ ውጥረት ላይ ስትሆን ኦራሎች ወታደሮችን በማመላለስ ተግባር ላይ ተሰማርተዋል ሲሉ በአከባቢእ የሚገኙ የአማራ ንቅናቄ አባላት ተናግረዋል::የህዝቡ አመጽ ከፖሊሶች እና የአከባቢው ሚሊሻ በላይ በመሆኑ ተጨማሪ ወታደሮችን የጫኑ ኦራሎች ወደየከተሞቹ እያመሩ መሆኑን ታውቋል::የነጻነት ሃይሎች ነን የሚሉ ይህንን የህዝብ እንቅስቃሴ በመጠቀም ትግሉን ማስፋፋት እንደሚችሉ ተጠቁሟል::

ከባለፈው ወራት ጀምሮ መተማ ከተማ ሳሉግ በመባል የሚታወቁት የበረሃ ሰራተኞች መካከል በተነሳው አለመግባባት የሰው ህይወት መጥፋቱን ተከትሎ ግጭቱ በመባባሱ እስካሁን ከ10 በላይ ሰወች መገደላችውና በርካቶችም መቁሰላቸው የታወቀ ሲሆን፣ ችግሩን በማባባስም የወያኔ እጅ እንዳለበት ተረጋግጧል። ይህን የመሰለ ግጭት ከዚህ ቀደምም በተለይ በጎንደር፣ጎጃምና ወሎ ተወላጆች መካከል የሚደጋገም ሲሆን ወያኔ ነገሩን ሲያባብስ ቆይቶ ለአሁኑ ከባድ አደጋ አድርሶታል።

በአሁኑ ጊዜ ግጭቱ ሰፋ ባለ መልኩ እየቀጠለ ያለ እና በተለይም በምዕራብ አርማጭሆ ወረዳወች መዛመቱና ከጎንደር የሚያገናኙ መንገዶችም መዛጋታቸው ታውቁኣል። ጉዳዩ የሚመለከታችሁ አካላትም ሂደቱን በቅርብ እንድትከታተሉና ወጣቶቹ የእርስበርስ መጠፋፋቱን አቁመው ወያኔን ለማስወገድ በሚደረገው ትግል ተሰላፊ እንዲሆኑ ለሚደረገው ጥረት መስራት ያስፈልጋል።

ከሳምንታት በፊት በኮንትሮባንድ ነጋዴዎች ታጣቂዎች እና በፌዴራል ፖሊስ መካከል በተነሳ ግጭት አራት የፌዴራል ፖሊሶች መገደላቸው የሚታወስ ሲሆን በወቅቱ ተከስቶ የነበረው ግጭት ከፖለቲአክ አጀንዳና ከህዝባዊ ጥያቄ ውጪ የነበረ መሆኑን መረጃዎች ጠቁመዋል::

በአሁኑ ወቅት በአገራችን በከተሞችና በገጠሮች እየታዩ ያሉ ምልክቶችን በጥንቃቄ የመረመረ ማንኛውም ሰው የሚከተሉትን መታዘቡ አይቀርም።

በአንድ በኩል፣ ወያኔ የተወገደባት፣ ፍትህ የሰፈነባትና የበለፀገች ኢትዮጵያ እውን ሆና የማየት ተስፋችን እየለመለመ ነው። በዚህም ምክንያት ኢትዮጵያ ዉስጥ ለረጂም ዓመታት በሕዝብ ላይ ሰፍኖ የነበረው የፍርሀት ደመና እየገለጠ በመሆኑ ተዘግተው የቆዩ አንደበቶች መናገርና “ይኸ ሁሉ ግፍ ለምን?” ብለው መጠየቅ ጀምረዋል። ይህንን መነቃቃት በአስተሳሰብም፣ በተግባርም፣ በኪነጥበብም እያየነው ነው። የኢትዮጵያ ወጣቶች ለውጥ በአገራችን ሊመጣ እንደሚችል ከማመን አልፎ ራሳቸውን በለውጥ አምጭ ኃይልነት መመልከት ጀምረዋል። በርካታ ወጣቶች ወያኔን በትጥቅ ለመገዳደር የወሰኑ ወገኖቻችንን እየተቀላቀሉ በዚህም ምክንያት ጉልበታቸውን እያፈረጠሙ ነው። የለውጡ እርሾ ከሲቪሉ አልፎ በመከላከያ ሠራዊቱ እና በኢሕአዴግ ድርጅቶች ውስጥም እየተብሰለሰለ ነው። የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት፣ ህወሓት ኢትዮጵያን ለማጥፋት የሚጠቀምበት ኃይል መሆኑ እያበቃ በአንፃሩ የትግሉ አጋር የሚሆንባቸው ሁኔታዎች እየታዩ ነው። በሁሉም የሠራዊቱ ክፍሎች ጉምጉምታው ወደ ጩኸት እየተቀየረ በመሆኑ ሠራዊቱ በአለቆቹ ላይ የሚነሳበት ጊዜ እሩቅ አይደለም። በተለያዩ ምክንያቶች ህወሓትን ወይም ህወሓት የፈጠራቸውን ድርጅቶች የተጠጉ በአጠቃላይ ኢሕአዴግ በሚባለው ስብስብ ውስጥ የሚገኙ ወገኖቻችንም “ለመሆኑ ማንን ነው እያገለገልን ያለነው?” ብለው በመጠየቅ ላይ ናቸው። በዚህም ምክንያት ወያኔ ውስጡ እየተረበሸ ነው። ከኢትዮጵያም ውጭ በሚገኘው ኢትዮጵያዊ ዘንድ ያለው ቁጣና ዝግጁነት ከወትሮው እጅግ የላቀ ነው። በአጭሩ፣ በሁሉም አቅጣጫ፣ ደረጃ በደረጃ የሕዝባዊ እምቢተኝነት እንቅስቃሴዎች ተጀምረዋል።

በአንፃሩ ደግሞ፣ የጨለማ ንጉሥ የሆነው ወያኔ፣ የኢትዮጵያ ሕዝብን ወደ ፍርሀት ቆፈን ለመመለስ እስሩን ከመቸውም በላይ ያጧጧፈበት ጊዜ ነው። በትግራይ፣ በአማራ፣ በኦሮሚያ፣ በደቡብ፣ በአፋር በሶማሊ … በመላው ኢትዮጵያ ብሩህ ራዕይ የሰነቁ ወጣቶችና አዛውንት ታድነው እየታሰሩ ናቸው። የወያኔ እስር ቤቶች በአርቆ አስተዋይ ዜጎቻችን ተሞልተዋል። ወትሮም ከፍተኛ የነበረው ስደት ብሶበታል፤ ለእውነት በጽናት የቆሙ ጋዜጠኞች ወይ ታስረው፣ አልያም ተሰደው አልቀዋል። የወያኔ የግዴታ ስልጠና አገሩን እያመሰው ነው። የኢትዮጵያዊያን ኑሮ በእጦቶች የታጀበ ሆኗል። የነፃነት እጦት፣ የፍትህ እጦት፣ የመብራት እጦት፣ የስኳር እጦት፣ የዘይት እጦት፣ የታክሲ እጦት፣ የመኖሪያ ቤት እጦት፣ እጦት፣ …. እጦት።

እነዚህ ሁለት ተፃራሪ እውነታዎች ሁለት ተፃራሪ ኃይሎች ለወሳኝ ፍልሚያ ፊት ለፊት መፋጠጣቸዉን በግልጽ ያሳያሉ። ዛሬ አገራችን ኢትዮጵያ ውስጥ ነፃነትና ባርነት፣ ፍትህና ጭቆና፣ ደስታና ሀዘን፣ ተስፋና ተስፋ መቁረጥ፣ ብልጽግናና ድህነት፣ እውቀትና ድንቁርና፣ ብርሃንና ጨለማ፣ ለወሳኝ ግጥሚያ ተፋጠዋል። ይህ ፍጥጫ የኢትዮጵያን የወደፊት እጣ ፈንታን በመወሰን ረገድ አቢይ ሚና የሚኖረው ወሳኙ ግጥሚያ – ሕዝባዊ እምቢተኝነት – መጀመሩን አብሳሪ ነው። የነፃነት፣ የፍትህ፣ የተስፋ፣ የብልጽግና፣ የእውቀትና የብርሃን ወገኖች ነን የምንል ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ይህንን ፍልሚያ በድል መወጣት ግዴታችን ነው።

ወያኔ ታጋዮችን ቢያስር ትግሉን አያስርም። በእጦት ኑሮዓችን በማመሰቃቀል በድህነት ሊያንበረክከን ቢሻም፣ በፍጹም አንበረከክለትም። በተዘረፈ የድሆች ድካም ህንፃዎችን ቢገነቡም የራስ ባልሆነ ጌጥ አንኮራም። የወያኔ የሆነ የኛ አይደለም፤ የእነሱ መክበር የኛ መክበር አይደለም። ወያኔ እና የኢትዮጵያ ሕዝብ ገዢና ተገዢ፤ በዳይና ተበዳይ፣ ገፊና ተገፊ ናቸው።

ተበዳይና ተገፊ የሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ በዘረኞች፣ ሙሰኞችና ከፋፋዮች የህወሓት ባለሥልጣኖቻቸውና ሎሌዎቻቸው ላይ ይነሳሉ። የተጀመረው ሕዝባዊ እምቢተኝነት አመቺ በሆኑ መንገዶች ሁሉ ይጧጧፋል።

የወያኔ ትዕዛዛትን መሻር፤ በሥራ ላይ መለገም፤ ግብር አለመክፈል፤ አድማ መምታት፤ የወያኔ ካድሬዎችን ማግለልና ማዋረድ፤ የነፃነት ኃይሎችን መደገፍ፤ የፓሊስና የጦር ሠራዊት አባላትን ማቅረብ እና በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ እነሱም የትግሉ አካል እንዲሆኑ ማበረታታት፤ ህሊና ያላቸው የኢሕአዴግ አባላት የሕዝቡን ትግል እንዲያግዙ ማበረታታት … – እነዚህንና እነዚህን የመሳሰሉ በርካታ የትግል ስልቶች ከአሁን ጀምሮ በተከታታይ በሥራ ላይ መዋል ይኖርባቸዋል። የወያኔን የጭቆና ምሽግ ከውስጥ መሸርሸር፤ ከውጭ መደርመስ ይኖርበታል። የመሸርሸርና የመደርመስ ሥራዎች ተደጋግፈው እንዲሄዱ ማድረግ ይገባል። ጊዜው የእምቢተኝነት ነው።

ግንቦት 7: የፍትህ፣ የዲሞክራሲና የነፃነት ንቅናቄ የኢትዮጵያ ሕዝብ አጠገቡ ባሉት መሪዎቹ አስተባባሪነት በአንድነት እንዲነሳ ጥሪ ያቀርባል፤ በመላው ዓለም ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንም በኢትዮጵያ ውስጥ የሚደረገው ሁለገብ ትግል በጽናት እንዲደግፉ ያሳስባል። ይህንን ትግል በድል መወጣት ግዴታችን ነው፤ እንወጣዋለንም!

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

Hailu Gebreyohannes Gemoraw ደራሲ፣ ገጣሚና ባለቅኔ ኃይሉ ገብረዮሐንስ (ገሞራው) “… እንደ ኪሩብ ሁሉ – ክንፍ አካል ቢኖረኝ፣
መች እጠበስ ነበር – በዚህ ዓለም በቃኝ፣
ስላጣሁ ብቻ ነው – መሸሻ መድረሻ፣
በዚች በሽት ዓለም – የኖርኩ እንደውሻ …፣”
“… በሥጋዬ ብቻ ውጪ – ሀገር እስካለሁ፣
እወቁልኝ በርግጥ – አልኖርኩም ሞቻለሁ! …
ኃይሉ (ገሞራው)
Ethiopia Zare (ረቡዕ ኅዳር 3 ቀን 2007 ዓ.ም. November 12, 2014):- በኢትዮጵያ የሥነ-ጽሑፍ ታዋቂ የነበረው ደራሲ፣ ገጣሚና ባለቅኔ ኃይሉ ገብረዮሐንስ (ገሞራው) ባለፈው እሁድ ጥቅምት 30 ቀን 2007 ዓ.ም. (ኖቨምበር 9፣ 2014) በስደት በሚኖርባት ስዊድን ዋና ከተማ ስቶክሆልም በ79 ዓመቱ ከዚህ ዓለም ተለየ። ሥርዓተ ቀብሩ በስዊድን እንደሚፈፀም ታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ኢወጋን – በአዲስ አበባ ከተማ በተመረጡ ቦታዎች ላይ የቅስቀሳ መልእከቶችን ለህዝብ እይታ አብቅቷል። ‪#‎VIDEO https://www.youtube.com/watch?v=F2jq9pNgmzg የአትዮጵያ ወጣቶች የጋራ ንቅናቄ (ኢወጋን)አባላት በአዲስ አበባ ዋና ዋና የህዝብ መገናኛ ቦታዎች እና የአውቶብስ መጠበቂያ የገበያ ቦታዎች ላይ የወያኔን ስርአት የሚያወግዙ እና ስርአቱን ለማውረድ ህዝቡ በጋራ እንዲነሳ የሚያደርጉ ጥሪዎችን ያነገኡ መፈክሮችን በመለጠፍ እንዲሁም ለፖሊስ እና ጦር ሰራዊቱ የሚገባውን የአንድነት እና […]

ትናንት ማክሰኞ በመላው ዩናይትድ ስቴይትስ የአርበኞች ቀን Veteran’s Day ተከብሯል። የመጀመሪያው ዓለም ጦርነት ያበቃበት 100ኛ ዓመት ከዚህ በዓል ጋር ኩታ በመግጠሙ፤ ፈንጠዝያውና የማስታዎሻ ስነስርዓቱን በእጅጉ አድምቆታል። ትናንት ማምሻውን ታዋቂ አሜሪካዊያን ሙዚቀኞች በዋሽንግተን ዲሲ ታላቅ የሙዚቃ ዝግጅት አቅርበዋል። በዚህ ትእይንት የዩናይትድ ስቴይትስ ጦርን ያገለገሉ ወንዶችና ሴቶች ከነቤተሰቦቻቸው ተገኝተዋል። ዘገባው የArash Arabasadi – ሔኖክ ሰማእግዜር ያቀርበዋል።

ሱማልያ ውስጥ እንደገና የተፈጠረው የፖለቲካ ውጥረት የሃገሪቱን የወደፊት ጉዞ ሊገታ ወይም አሁን ከደረሰችበት የመረጋጋት ጎዳና ሊያፈናቅላት እንደሚችል ተሰግቷል።

ፊሌ ተብላ የተሰየመች ንብረትነቷ የአውሮፓ የጠፈር ኤጀንሲ የሆነ መንኩራኩር ሕዋ ውስጥ ከምትገኝ አንዲት ቀደም ብላ ከተላከች የአውሮፓ ኅብረት ማምጠቂያ መደብ ተወንጭፋ በልማድ “ጅራታም ኮከብ” እየተባሉ ከሚጠሩ የተፈጥሮ የሰማይ አካላት ወይም ኮሜቶች በአንዷ ላይ አረፈች፡፡

ዩናይትድ ስቴትስና ቻይና ወደ ከባቢ አየር የሚለቅቋቸውን በካይና ሙቀት አማቂ ጋዞችን መጠን ለመቀነስ ያስችላል የተባለ አዲስ ዕቅድ ይፋ አደረጉ፡፡

ባለፈዉ ዕሁድ በስደት በሚኖርበት ስዊድን ሐገር ያረፈዉ የኢትዮጵያዊው ባለቅኔ የኃይሉ ገብረዮሐንስ‬ (ገሞራው) የቀብር ሥነ-ሥርዓት ሰሞኑን እንደሚፈጸም ወዳጆቹ አስታወቁ።ኃይሉ በኢትዮጵያ ዘመናይ ሥነ-ፅሁፍ ሥመ ጥር ከነበሩ ደራሲዎች አንዱ ነበር።

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

ኀዳር ፫(ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በቦሌ ክፍለከተማ ወረዳ 11 በለሚ አካባቢ የምትገኘው ማሪያም ቤተከርስቲያን በህገወጥ መንገድ ተሰርታለች በሚል ፖሊሶች ለማፍረስ ሲሄዱ ህዝቡ ባሰማው ተቃውሞ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱ ታውቋል። ድርጊቱን የተቃወሙ ምእመናን “ቤተክርስቲያኑዋን ማፍረስ አትችሉም” ማለት ሲጀምሩ ፖሊሶች መደብደብ የጀመሩ ሲሆን፣ ህዝቡም በአጸፋው በፖሊሶችና በወረዳው አስተዳዳሪ ላይ ድንጋይ በመወርወር የተወሰኑ ፖሊሶችን አቁስሏል። የወረዳው …

ኀዳር ፫(ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ትምህርት ሚኒስቴር ” የከፍተኛ ትምህርት የኢህአዴግ የምርጫ ድል ልማት ሰራዊት ግንባታ አደረጃጃት ማንዋል፣ ለምርጫ 2007 የተሻሻለ” በሚል ርእስ ያዘጋጀውና ለኢህአዴግ ከፍተኛ ባለስልጣኖች የቀረበው ሰነድ እንደሚለው በአገሪቱ ያሉ ዩኒቨርስቲዎች ፕሬዚዳንቶች ውጤታቸው የሚሞላላቸው በምርጫው ለኢህአዴግ በሚያዘጋጁት የተማሪዎች የድጋፍ ሃይል መጠን ነው። ሰነዱ የትምህርት ልማት ሰራዊትን በዩኒቨርስቲዎች ለማስፋፋት የተደረገው ስራ …

ኀዳር ፫(ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአዲስአበባ ከተማ በርካታ አካባቢዎች የ24 ሰዓታት የውሃ አቅርቦት ማግኘት ካለመቻሉ ጋር ተያይዞ ነዋሪዎች ሥራቸውን በመተው ውሃ ለማግኘት ከሰፈር ሰፈር እንዲንከራተቱና ለተጨማሪ ወጪ እየተዳረጉ መሆኑን ዘጋቢያችን ተዘዋውሮ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት በአዲስአበባ በየትኛውም አካባቢ የመጠጥ ውሃ ችግር ተባብሶ መቀጠሉን የጠቆሙት  ነዋሪዎች አስተዳደሩ በየጊዜው ተስፋ ከመስጠት ባለፈ በተጨባች …

ኀዳር ፫(ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ግሎባል ፋይንሻል ኢንተግሪቲ ባወጣው ዘገባ በዚህ ሳምንት የቡድን 20 አገራት በአውስትራሊያ በሚያደርጉት ስብሰባ በህገወጥ መንገድ ገንዘብ በሚያዘዋውሩ ኩባንያዎች ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ጠይቋል። ተቀማጭነቱ አሜሪካ የሆነው ድርጅት በዋጣው ዘገባ፣ ኩባንያዎች ሽያጮቻቸውን፣ ታክሶቻቸውን፣ ትርፋቸውና ኪሳራቻውን ግልጽ እንዲያደርጉ መመሪያ ሊወጣላቸው ይገባል ብሎአል። ታዳጊ አገሮች በእነዚህ ኩባንያዎች የተነሳ በእየአመቱ 1 ትርሊዮን …

በሙያ የአፈርና ቋጥኝ እንዲሁም የእሳተ- ገሞራ ተማራማሪ ነው– «ጂዎፊዚስት»፤ ጠፈርተኛ ፣ አሌክሳንደር ጌርስት! ካለፈው ዓመት ግንቦት 20 ቀን 2006 ዓ ም አንስቶ ግን፣ እስካለፈው እሁድ፣ ከምድር አናት ላይ ሆኖ ፣ ማለት 418ኪሎሜትር ከፍ ብሎ ነበረ ምርምሩን ሲያካሂድ የቆየው።