በአውሮጳ ስደተኞችን የማዳን ተግባር

ከአምስት ቀናት የባሕር መናወጥ ቆይታ በኋላ ከጣሊያኗ ላምፔዱዛ ደሴት እስከ ሊቢያ ጠረፍ የባሕሩ ሞገድ ረግቷል። ካለፈው አንድ ሣምንት አንስቶ ደግሞ «ቪያኖ ዶ ካስቴሎ» የተሰኘችው የፖርቺጊዝ ባሕር ቃኚ መርከብ ከላምፔዱዛ 55 ኪሎ ሜትሮች ደቡባዊ ርቀት ላይ መቅዘፍ ጀምራለች።