Tag: ethiopian news in amharic
የቆሰለ አውሬ ለያዥ ለገራዥ አስቸጋሪ ነው፡፡ Minilik Salsawi
የሙግትና የአዕምሮ አክሮባት ከመሥራት ይልቅ፤ የህዝቡስ ሁኔታ እንዴት ነው? ማለት ዋና ጉዳይ ነው፡፡ በሀገራችን “ሲሾም ያልበላ ሲሻር ይቆጨዋል” የተባለው ተረት ዕድሜው እጅግ ረጅም ነው፡፡ የሥርዓቶቻችንን ያህል አርጅቷል፡፡ በተግባር ሲተረጐም ግን ገና ዛሬ የተወለደ ነው የሚመስለው፡፡ በየቢሮው፣ በየማህበሩ፣ በየፓርቲው የምናየው ሀቅ ነው፡፡ “አዲስ እረኛ ከብት አያስተኛ”፣ “እከክልኝ ልከክልህም” አብሮ ሲተረት የኖረ ነው፡፡ ማናቸውም ዕቅድና ስትራቴጂ ህዝብ […]
ምርጫ 2007 ለለዉጥ !!!!! – ግርማ ካሳ
በቅርቡ የሚከተለውን ጽፌ ነበር፡ “አገር ቤት ላሉ ተቃዋሚዎች ደግሞ የሚከተለዉን መልእክት አስተላልፋለሁ። የምርጫ ፓርቲ ናችሁ። ነገር ግን በባዶ እግራችሁ ብስክሌት ከያዘ ጋር እንወዳደራለን ብሎ መነሳት፣ ራሳችሁን ከማስገመት በተጨማሪም ለገዢው ፓርቲ የፖለቲካ ፍጆታ መጠቀሚያ ብቻ ነው የምትሆኑት። ምርጫ የምትሳተፉ ከሆነ፣ የምርጫ ዘመቻ ማድረግ አለባችሁ። ምርጫው ሰባት ወራት ነው የቀሩት። በሚቀጥለው አንድ ወራት ዉስጥ አገዛዙ ነገሮችን ካላስተካከለ […]
የቆሰለ አውሬ ለያዥ ለገራዥ አስቸጋሪ ነው፡፡
የሙግትና የአዕምሮ አክሮባት ከመሥራት ይልቅ፤ የህዝቡስ ሁኔታ እንዴት ነው? ማለት ዋና ጉዳይ ነው፡፡
Minilik Salsawi
በሀገራችን “ሲሾም ያልበላ ሲሻር ይቆጨዋል” የተባለው ተረት ዕድሜው እጅግ ረጅም ነው፡፡ የሥርዓቶቻችንን ያህል አርጅቷል፡፡ በተግባር ሲተረጐም ግን ገና ዛሬ የተወለደ ነው የሚመስለው፡፡ በየቢሮው፣ በየማህበሩ፣ በየፓርቲው የምናየው ሀቅ ነው፡፡ “አዲስ እረኛ ከብት አያስተኛ”፣ “እከክልኝ ልከክልህም” አብሮ ሲተረት የኖረ ነው፡፡ ማናቸውም ዕቅድና ስትራቴጂ ህዝብ ኑሮ ላይ ያነጣጠረ መሆን አለበት፡፡ ይሄ ማለት የእርስ በርስ ሙግትና የአዕምሮ አክሮባት ከመሥራት ይልቅ፤ የህዝቡስ ሁኔታ እንዴት ነው? ማለት ዋና ጉዳይ ነው፣ ማለት ነው፡፡
ሕዝቡ የኑሮ ውድነት ከበደኝ! የእቃ ዋጋ ንረት አስመረረኝ! ግፍ በዛብኝ! ሸምቶ መቃመስ አቃኝ የሚል ምሬት ሲያሰማ.. ሹመኞች አፍ ለማስያዝንና ለማሸማቀቅ ይሽቀዳደማሉ፡፡ የህዝብን የኑሮ ደረጃ ዝቅ ብሎ ወርዶ የሚያይ መሪ፣ አለቃ፣ ኃላፊ ማግኘት መታደል ነው፡፡ ያስቀናል፡፡ የዋጋ መናርና የታክስ ማሻቀብ አንድን ማህበረሰብ የጦርነትን ያህል ያጠፋዋል፡፡ ለዚህ ነው መሪዎች ሁሉ የህዝባቸውን ኑሮ በቅርብ ያስተውሉ የሚባለው፡፡ ህዝብ የሀገር ሙቀት መለኪያ ነው፡፡ ህዝብ የሚከፍለው ግብር ከሚያገኘው አገልግሎት ጋር ካልተመጣጠነ የቀዘቀዘች አገር ውስጥ ነው የሚኖረው፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው እውነት እና በገሃድ የሚታየው ህዝብ ደሞዙ ከሚኖረው ኑሮ ጋር ስለማይመጣጠን ኖረ አይባልም፡፡ ህዝብ ከዕለት ዕለት ህይወት እየከበደው በመሄዱ ከሳቁ ምሬቱ፣ ከደስታው ሐዘኑ እየበረታ ሥርዓቱን፣ አገዛዙን፣ ገዢዎቹን፣ አስተዳዳሪዎቹን እጅግ ጠልቷቸዋል፡፡ ሀገሩም የእሱ አትመስለውም፡፡ ህዝብ መሰረታዊ የፍጆታ ዕቃዎችን ለማግኘት ነግ-ሠርክ መሰለፉ ፤ አልፎ ተርፎም ከናካቴው ዕጥረት የሚከሰትበት ሁኔታ፣ ብሶቱ ወሰን የለውም በብሶት ተሞልቷል፡፡ ህዝብ በመኖሪያ ቤት ችግር እየተሰቃየ ሲሆን መሰረታዊ የኑሮ አስፈላጊ ነገር ጎሎበታል ፡፡
ከዚህ ሁሉ የሚከፋው ደግሞ ይህንን የሚገልፅበት መንገድ እንዳያገኝና በፍርሃት ተሸማቆ እንዲቀመጥ ተደርጓል፡፡ “አዲስ ያይጥ – ወጥመድ በሰራህ ቁጥር” አዲስ አይጥ የምትወለድ ከሆነ፣ ወይ ወጥመዷ ላይ ወይ አጥማጁ ላይ ችግር አለ ማለት ነው” ይባላል፡፡ በሙስና የተሞላ ልማት ዘርዛራ ወንፊት ነው፡፡ ዕብቁንም፤ እንክርዳዱንም፤ እያሳለፈ፤ እያዩ እህል አለን እንደሚሉት አይነት የዋህነት ይሆናል፡፡ የዚህ ሁሉ መጨረሻው ድህነት ነው፡፡ ድህነት ሲመጣ ቃላት ይበዛል። ስብሰባ፣ ንግግር፣ የማይተገበር ቃል – መግባት እንደህይወት ይወሰዳል፡፡ እንደኑሮ ይለመዳል፡፡ይህ በወያኔዎች በተግባር እያየነው ያለው ሃቅ ነው::
ሃገራችን እና ወገናችን በጨለማ ውስጥ እየዳከረ ባለበት በዚህ የወያኔ አገዛዝ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በመረባረብ የዜግነት ግዴታውን አውቆ ለህዝቦች መብት እና ነጻነት መታገል አለበን። ሃገሪቷ በዚህ አደጋ ውስጥ ባለችበት ሰአት ላይ ህዝብ አጣብቂኝ ውስጥ ገብቶ ለኑሮ ውድነት ለሞት ለስደት እየተዳረገ ኢትዮጵያዊነት እየተዋረደ ከመሆኑም ባሻገር ሃገሪቷን ወደ ፍርስራሽነት ለመቀየር የሚሮጡ ጥቂት ሆዳሞች ባሉበት ልንቀብራቸው ይገባል።
የሰንደቅ ዓላማ አዋጅ ቢሻሻልስ? በአያሌው አስረስ
የግብፅ መንግሥታት፣ ደካማ ኢትዮጵያን ለማየት ካላቸው ፍላጎት የተነሳ የኤርትራ ነፃነት ግንባሮችን መልምለው፣ አሠልጥነውና አስታጥቀው በኢትዮጵያ ላይ አዘመቱ፡፡ የኤርትራ ግንባሮች በበኩላቸው ጦርነቱ በሌሎች የኢትዮጵያ አካባቢዎች እንዲዳረስ ለማድረግ የተጠቀሙበት መንገድ የብሔረሰብ ንቅናቄዎችን መፍጠር እንዲሁም ሌሎች የእነሱን አርዓያ ተከትለው እንዲቋቋሙ ማገዝ ነው፡፡ የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል የተመሠረተውን የፌዴሬሽን ግንኙነት ማፍረሱ በቀጣናው ጦርነት እንዲቀሰቀስ ምክንያት ሆኗል፡፡ ዘውዳዊውም […]
የማህበረሰብ ውይይት በኢትዮጵያ ዘለቄታዊ ሰላምና ትብብር
በሰሜን አሜሪካና አውሮፓ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ከቅርብና ከሩቅ ተጠራርተው ቅዳሜለት በአርሊንግተን ቨርጂኒያ ስብሰባ አድርገው ነበር። ውይይታቸው በኢትዮጵያ ዘለቄታ ያለው ትብብር ለመገንባት የሚያስችሉ አዳዲስ ሃሳቦችና የጋር እሴቶችን በመመርመር ላይ ያተኮረ ነበር።
በሰሜን አሜሪካ የሚገኘው የጋራ እንቅስቃሴ ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የተባለ የሲቪክ ድርጅት ያሰናዳው ጉባዔ ከተለያዩ ብሄሮች፤ ጾታና የሃይማኖት አባላት፤ እራሳቸውን እንደግለሰብ ወክለው የተሳተፉበት ነበር።
ቅዳሜለት በዋሽንግተን ዲሲ አቅራቢያ በምትገኘው አርሊንግተን ቨርጂኒያ የተሰባሰቡ ኢትዮጵያዊያን፤ በሀገራቸው ተቋማዊ አስተዳድር ባልተጠናከረበት መልኩ፤ ማህበረሰቦች ሊጫወቱት የሚገባቸው ሚና፣ እንዲሁም እርስ በርስ የመተባበር ሃሳቦች ላይ ያተኮረ ነው።
የጋራ እንቅስቃሴ ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ በዋሽንግተን…
ፓርቲዎች ትብብሩን በመቀላቀል የተቃውሞ ጎራውን እንዲያጠናክሩ ጥሪ ቀረበ ገዥው ፓርቲ ራሱን ለለውጥ እንዲያዘጋጅ ተጠይቋል
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር : በትናንትናው ዕለት ህዳር 7/2007 ዓ.ም ሰብሰባ ጠርቶ በገዥው ፓርቲ ደህንነቶችና ፖሊስ የተበተነበት የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር የኢትዮጵያ ችግር ከአንድ ፓርቲ አቅም በላይ በመሆኑ በትብብሩ ምስረታ ወቅት የነበሩትንና ሌሎቹም ፓርቲዎች ትብብሩን በመቀላቀል የተቃውሞ ጎራውን እንዲያጠናክሩ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ጥሪ አቅርቧል፡፡
መግለጫው አክሎም አገር ውስጥም ሆነ ከአገር ውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የአገራቸውንና የዜግነት ክብራቸውን ለማስመለስ በቀጣይነት ለሚደረገው ሰላማዊ ትግል ጥሪ አወንታዊ ምላሽ በመስጠት በጋራ ‹‹በቃን›› ብለው እንዲነሱ ጥሪ አቅርቧል፡፡ በአንጻሩ የፖሊስ ኃይልና ሌሎች አስፈጻሚ አካላት በገዥው ፓርቲ ሴራ ተጠልፈው ከሰላማዊ ዜጎች ጋር እንዳይጋጩና ህገ መንግስቱንም እንዲያከብሩ እንዲሁም ገዥው ፓርቲም ካለበት ፍርሃትና ስጋት ወጥቶ ለለውጥ ዝግጁ እንዲሆን ትብብሩ አሳስቧል፡፡
በሌላ በኩል ‹‹በህዝብ ሀብት የሚተዳደሩት መገናኛ ብዙሃን ሙሉ በሙሉ በመንግስት ቁጥጥር ስር ውለው ገዥውን ፓርቲ ከማገልገል አልፈው በሰላማዊ ትግል የፖለቲካ ኃይሎች ላይ አፍራሽ ፕሮፖጋንዳ›› እንደሚነዙ ያስታወሰው ትብብሩ በአገር ውስጥም ሆነ ከአገር ውጭ የሚገኙ የመገናኛ ብዙሃን ስላደረጉት አወንታዊ አስተዋጽኦ አመስግኗል፡፡ በቀጣይም ለህዝብ በመወገን ከጎኑ እንዲቆሙ ጥሪ አቅርቧል፡፡
ስፖርት ፕሮግራም!
የእግርኳስ ኮከብ ተጫዋቾች የኢቦላን ቫይረስ ስርጭት ለመግታት የሚካሄደውን አለምአቀፍ ዘመቻ ተቀላቀሉ።
ከምሽቱ ሦስት ሰዓት የአማርኛ ዜና – ኖቬምበር 17, 2014
የፕሮግራም መግለጫ
ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡
ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡
የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡
ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና
ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና
ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ
ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት
ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)
ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና
ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡
ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡
የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡
ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የመጨረሻ ተስፋ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን ለአፍሪቃ ዋንጫ የመጨረሻ የማጣሪያ ጨዋታውን እጅግ የጠበበ ዕድል ይዞ ረቡዕ ያከናውናል። ቡድኑ በአዲስ የውጭ ሀገር አሠልጣኝ መመራት ከጀመረ ወዲህ ለማሸነፍ የቻለው አንድ ጨዋታ ብቻ ነው። ምክንያቱ ምንድን ነው? ጂብራልታርን 4 ለ0 ያሸነፈው የጀርመን ቡድን አሠልጣኝ በውጤቱ አልተደሰቱም።
ቡድን 20 ምጣኔ ሐብታዊ ወይስ ፖለቲካዊ?
አንዱ ቡድን በ15ለ 1 ተፃራሪ ሐይላት የተወጠረ፤ በ4መሐል ሰፋሪዎች የተትመከመከ መሆኑን መስካሪ ነዉ።ለዘንድሮዉ ጉባኤ የመነጋገሪያ ርዕስ፤ የአቋም መግለጫምከቡድኑ ይፋዊ አላማ ጋር የሚጣጠም ነዉ።ምጣኔ ሐብት።
በቤሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢቦላ ታይቶአል መባሉ እና ማስተባበያው
በማህበራዊ ድረ-ገጾች ላይ በኢትዮጵያ ሶስት የኢቦላ ተጠርጣሪ ህሙማን ተገኙ የሚል ደብዳቤ እየተሰራጨ ነው። የክልሉ ጤና ቢሮ ደብዳቤውን እንደማያውቀው የኢቦላ በሽታም በክልሉ አለመኖሩን አስታውቋል።
ቀድሞዋ ጀርመን መዲና የዛሪዋ ሳሊፊስቶች ማዕከል
ከጀርመን ወደ 450 ጀርመናዉያን ሳላፊስቶች ወደ ሶርያ መጓዛቸዉ ተመልክቶአል። ከነዚህ መካከል ደግሞ 10 በመቶዉ የሚሆኑት ራድዮ ጣብያችን ከሚገኝበት ከቦን ከተማ መምጣታቸዉ ነዉ የተነገረዉ። የቀድሞዋ የምዕራብ ጀርመን መዲና ቦን ለምን የፅንፈኞች ማዕከል ለመሆን በቃች?
መንግስት የ9ኙን ፓርቲዎች የአደባባይ ስብሰባ መከልከሉ ትግሉን እንደማያቆመው ፓርቲዎቹ ገለጹ
ኀዳር ፰(ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪነት 9 የፖለቲካ ድርጅቶች በጋራ የጠሩት የአደባባይ ስብሰባ በገዢው ፓርቲ የጸጥታ ሃይሎች እንዲበተን ከተደረገ በሁዋላ ድርጅቶቹ ባወጡት መግለጫ ” መንግሥት ከገባበት ከፍተኛ የፍርኃት ስሜት ለመውጣት ያስቀመጠው የሴራ መፍትሄ መስዋዕትነቱን ይጨምር እንደሆን እንጂ፣ ትግሉን አያቆመውም” ብለዋል። ፓርቲዎቹ ለአንድ ወር ባወጡት የስራ መርሃ ግብር መሰረት ከአራት ኪሎ እና …
የመንግስት ጋዜጠኞች የሙስና ጥያቄ እንዳማረራቸው ባለስልጣናት ለመንግስት ኮሚኒኬሺን ጉዳዩች አቤት አሉ፡
ኀዳር ፰(ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦሮምያ ፣ በደቡብ እና በአማራ ክልሎች በተካሄደ የመረጃ አመራር ስልጠና ላይ አሰተያየት የሰጡ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ጋዜጠኞች ‹‹ቡጨ›› በማለት የሚጠሩት ቡጨቃ ፤ቆረጣ ወይም ሃብትን መካፈል የሚባለው አሰራር እንዳማረራቸው ገልጸዋል። ባለስልጣኖቹ “መንግስት ከከፈላቸው አበል ውጭ በድጋሜ አበል ካልተከፈላቸው ፕሮግራሞቻችን በደንብ አይሸፈኑም፤ ምንም አይነት ሂሳብ ካላገኙ ወይም የምግብ ፤ የነዳጅ እና …
ቡርኪና ፋሶ ጊዜያዊ ፕሬዚዳንት ሾመች
ኀዳር ፰(ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የብሌስ ካምፓወሬ መንግስት በ2 ቀናት አመጽ ከተገለበጠ በሁዋላ ስልጣን ለሳምንታት ተረክቦ የነበረው የመከላከያ ሰራዊት ስልጣኑን ጊዜያዊ ፕሬዚዳንት እንዲሆኑ ለተመረጡት ለቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሚኬል ካፋንዶ እንደሚያስረክብ ታውቋል፤፡ሌ/ኮ አይሳክ ዚዳ ስልጣናቸውን በፍጥነት እንደሚያስረክቡ ቃል ገብተዋል። የ72 አመቱ ካፋንዶ ከሃይማኖት፣ ከጦር ሰራዊት፣ ከፖለቲካ፣ ከሲቪክ ማህበረሰቡና ከባህላዊ መሪዎች ተውጣጦ በተመሰረተው ጉባኤ …
ቤተክህነትም እንደ ቤተ መንግስትየልቡና ድርቅ መታታል በበላይነህ አባተ
ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
አራጣ (የጐንቻው)
ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
የአሜሪካ ድምጽ ፒተር ሃይንላይንን ከሃላፊነቱ አነሳ
(አዲስ ቮይስ) የአሜሪካን ድምጽ ዳይሬክተር ዴቪድ አንሶር የአፍሪካ ቀንድ የበላይ ሃላፊ የነበረው ፒተር ሃይንላይን ከሃላፊነቱ መነሳቱን አሳወቁ። ዳይሬክተሩ ባለፈው አርብ የክፍሉን ሰራተኞች በድንገት ሰብስብስበው እንዳስታወቁት ሃይንላይን ከሃላፊነቱ ተነስቶ በምትኩ የርሳቸው ከፍተኛ አማካሪ የሆኑት ዊሊያም ማርሽ በግዚያዊነት መሾማቸውን ገልጸዋል። በቅርቡ በአሱዛ ፓስፊክ ዩኒቨርሲቲ ለአቶ ሃይለማሪያም ደሳለኝ ተሰጥቶ የነበረ ክብር መሰረዙ ጋር በተያየዘ ከሄኖክ ሰማእግዜር ጋር በመተባበር […]
በኬንያ ስደተኞችን የማፈኑን ስራ የሚያስቀጥል የደህንነት ቡድን ናይሮቢ ገብቷል::
– በኬንያ ሰላም እያለች ራሷን የምታስተዋውቀው ገዳይ ሴት ተልእኮዋን አልተሳካላትም::
– በኬንያ የሚገኙ ስደተኞች በተጠንቀቅ እንዲቆሙ መረጃውን ያስተላልፉ::
Minilik Salsawi
በኬንያ የሚገኙ ስደተኞችን ለማፈን የሚረዳ የደህንነት ግብረሃይል ወደ ናይሮቢ መጓዙን ከኤምባሲው የደህንነት አታቼ ቅርብ የሆኑ ዲፕሎማቶች ያደረሱኝ መረጃ ይጠቁማል::አዲስ የተላከው ሃይል በናይሮቢ የከተመውን CID ብሎ ራሱን የሚጠራው የወያኔ የስለላ መዋቅር ጋር በመቀናጀት አስፈላጊ ናቸው የተባሉ ሰዎችን በማፈን ወደ ኢትዮጵያ በሰአታት ውስጥ ለመላክ የሚያስችለውን ስራዎች እንደሚሰራ ታውቋል::
የCID አባላት ታፍነው ይወሰዳሉ የተባሉትን አዋዋል ተከታትለው የጨረሱ ሲሆን እንዲሁም በቡድን የሚገናኙ ኢትዮጵያውያንን የሚገናኙበትን ጊዜ እና አከባቢ ጠብቀው ለማፈን ክትትል ላይ መሆናቸው ታውቋል:: ከኤምባሲው የደህንነት አታቼ ቢሮ የወጣው መረጃ እንደሚያመለክተው አዳዲስ ስደተኞች አንድ ላይ ሲሆኑ ለማፈስ ዝግጅት ጨርሰዋል ስልካቸውን እንዲቀይሩ እና ከሚያውኩት ሰው ውጪ ከማንም ጋር ናይሮቢ ውስጥ እንዳይደዋወሉ ሲል እየነጠሉ እንዳይወስዷቸው ሌሎቹ ያመልጡናል ብለው ስላሰቡ ለስራው የሚሆኑ ደህንነቶች ከኢትዮጵያ ገብተዋል ብሏል:: እንዲሁም አፈናው ስደተኞቹን በተዋወቁ አዛኝ መሳይ ቆነጃጅት ቀጠሮ ይፈጸማል የሚል ተጨማሪ መረጃ ተገኝቷል::
ይህ በእንዲህ እንዳለ በናይሮቢ ስደተኞችን እያጠመደች በተመረዘ ምግብ የምትገለው እና ራሷን ሰላ እያለች የምትጠራው ቆንጆ የተሰማራችበት ተልእኮ እንዳልተሳካ ታውቋል::በኢትዮጵያ ኤምባሲ ውስጥ እንደ ዲፕሎማት የተመዘገበቸው እና ለአምባሳደሩና ለደህንነት አታቼው ቅርብ እንደሆነች የምትታወቀው እንዲሁን ከCID አባላት ጋር በጋራ እንደምትሰራ የተደረሰባት ይህች ግለሰብ ከዚህ ቀደም በሚሊዮን ሹሩቤ ላይ የተጠቀመችውን ቃላቶች ልረዳህ እችላለሁ የፈለከው አደርግልሃለሁ ከማለት ጀምሮ ማግባት እና መውለድ ስለምፈልግ ከእንዳተ አይነት እውቀት ካለው ሰው ጋር …አንተን ለማኖርም ሆነ ለማዝናናት እችላለሁ ና ወደ ቤቴ ልውሰድህ …ወዘተ የሚል የማጃጃያ ዘዴ እና ውድ ግብዣዎችን በማድረግ አንድን ወጣት ለማጥመድ ያደረገችው ሙከራ ሳይሳካላት እንደቀረ የኤምባሲው ምንጮች ጠቁመዋል::ግለሰቧ ቋሚ ስልክ ቁጥር የሌላት ሲሆን በምትፈለግበት ሰአት የማትገኝ ድንገት ደውላ ለግብዣ የምታመቻች ናት::እንዲሁም በደወለችው ቁጥር ተመልሶ ቢደወል ስልኩ ዝግ መሆኑን ምንጮቹ አክለው ገልጸዋል::#ምንሊክሳልሳዊ
ከኃይሉ ሻውል ተጽዕኖ ያለወጣው መኢአድ ጠቅላላ ጉባዔውና አሳፋሪ ድራማ – በጌታቸው ባይፈርስ
የመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት /መአሕድ/ በ1984 ዓ.ም ተመስርቶ ገዢው ፖርቲ በኦሮሚያ፣ በጋምቤላና በደቡብ ክልሎች በሚኖሩ በአማራ ብሔረሰብ ላይ እየደረሰ ያለውን የግፍ ጭፍጨፋና የመብት ረገጣ ለመታገል፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶችንና የሕግ የበላይነትን እንዲሁም የዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታን ዕውን ለማድረግ ሰንቆ በተነሳው አላማ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ እንቅስቃሴ በማድረጉ የፖርቲው መስራችና እውቁ የሕክምና ምሁር ኘሮፌሰር አስራት ወልደየስ […]
“አንድነት የአዲሱ ትውልድ ፓርቲ ሆኗል” አቶ አስራት አብርሃም
አቶ አስራት አብርሃም በእስር ላይ የሚገኘው የአቶ ሃብታሙ አያሌው የስራ ኃላፊነት ተክቶ የአንድነት ፓርቲ ተጠባባቂ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ሆኖ በመስራት ላይ ይገኛል፡፡ ስለ ፓርቲው ወቅታዊ ሁኔታና የወደፊት አቅጣጫ በተመለከተ ከአቶ አስራት ጋር ተወያይተናል፡፡ ፍቱን፡-በዚህ ወቅት መንግሥት በያዘው አቋም እና ተቃዋሚዎች ባላቸው ደካማ አደረጃጀት እና ምላሽ ምክንያት ፓርቲዎቹ እንኳን የህዝቡን መብት ከጥቃት ሊከላከሉ ለራሣቸው መሆን አቅቷቸዋል፣ […]
የሰማያዊ መሪዎች ያስቡበት – ግርማ ካሳ
ዜጎች ሐሳባቸዉን በነጻነት የመገልጽ መብት፣ ዩኒቨርሳል መብት ነው። በተባበሩት መንግስት የሰብአዊ መብት ድንጋጌ ላይ በግልጽ ተቀምጧል። በአገራችን ሕግ መንግስትም ሐሳብን በነጻነት የመገልጽና ሰላማዊ ሰልፎች የማድረግ መብት ባልተሸራረፈ መልኩ ተጠቅሷል። ህዝባዊ ስብሰባም ሆነ ሰላማዊ ሰልፍ ሲደረግ፣ ከአዘጋጆች የሚጠበቀው ሰልፉ ወይም ስብሰባው እንደሚደረግ ማሳወቅ ብቻ ነበር። የሰማያዊ ፓርቲ ሕጉንና ደንቡን በመከተል መደረግ ያለበትን ሁሉ አድርጓል። ሆኖም አገዛዙ […]
ኦሮሞነት ዘረኝነት አይደለም — ግርማ ካሳ
በኦሮሞዉና በአማርኛ ተናገሪው መካከል ጥላቻ እንዲሰርጽ ተብሎ አንድ የተጻፈ መርዛማ መጽሐፍ አለ። የቡርቃ ዝምታ የሚባል መጽሃፍ። የዚህ መጽሀፍ ደራሱ አቶ ተስፋዬ ገበረ አብ ይባላሉ። የሕወሃት/ኢሓአዴግ ከፍተኛ ባለስልጣን የነበሩ ጊዜ የጻፉት መጽሀፍ ነው። በቅርቡ “በሞጋሳ ኦሮሞ ሆኛለሁ” ሲሉ አቶ ተስፋዬ ተናግረዋል። ምን ያህል የሞጋሳ ሚስጠር እንደገባቸው ግን አላውቅም። ከአራት መቶ አመታት በፊት፣ የኦሮሞ ጦረኞች አንድ አካባቢን […]
9ኙ ፓርቲዎች የጠሩት የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ በኃይል ተበተነ
ዛሬ ህዳር 7/2007 ዓ.ም 9ኙ ፓርቲዎች በትብብር የጠሩት የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ በፖሊስና በደህንነት ኃይሎች ተበትኗል፡፡ ፓርቲዎቹ ለሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል ያሳወቁ ሲሆን የፓርቲዎቹ አመራሮች ለፖሊስና ደህንነቶች ቢያሳዩም ‹‹የምናውቀው ነገር የለም፣ እኛ ታዘን ነው፡፡ ከፈለጋችሁ አለቆቻችን ሂዳችሁ አናግሩ፡፡›› በማለት ለስብሰባው የተዘጋጁትን ቁሳቁሶች ስብሰባው ሊደረግበት ከታሰበው ሜዳ እንዲነሱ አድርገዋል፡፡ የፓርቲዎቹ አመራሮችና በስብሰባው ለመሳተፍ ወደቦታው ያቀኑ አካላት […]
የሚሊየነሞች ድምጽ – በትግራይ እና በኦሮሚያ ክልሎች አንድነት መዋቅሩን እያጠናከረ ነው
በቅርቡ የአንድነት ፓርቲ በመቀሌ ከተማ ጽ/ቤቱን መክፈቱ ተዘግቧል። በተመሳስይ ሁኔታ በኦሮሚያ የምስራቅ ሸዋ ዞን ፣ በአዳማም በአዲስ መልኩ የዞኑ ጽ/ቤት ተከፍቷል። የምስራቅ ሸዋ ዞን በዉስጡ 11 ወረዳዎች ያሉት ሲሆን የዞኑ ወረዳዎችን በሙሉ ለለዉጥ፣ ለአንድነት ለማስቀሳቀስ ሥራ ተጀምሯል። የአዲስ አበባ ፓርቲ ብቻ ሆኖ ለዉጥ ማምጣት አይቻልም። በአገራችን ለዉጥ እንዲመጣ የለዉጥ ባለቤት የሆነውን መላው የኢትዮጵያን ሕዝብ ማደራጀትና […]
አንድነት ፓርቲ በሊበራሊዝም ርዕዮተ ዓለም ላይ ደማቅ ውይይት አካሄደ
በዛሬው ዕለት ህዳር 7 ቀን 2007 ዓ.ም. በፓርቲው የወጣቶች ጉዳይ ኃላፊ አቶ እንግዳ ወልደጻዲቅ አቅራቢነት በሊበራሊዝም ርዕዮተ ዓለም ላይ እጅግ ደማቅ የሆነ ውይይት ያደረገ ሲሆን በውይይቱ ላይ በርካታ ተሳታፊ ተገኝቶ ውይይቱን ተካፍሏል። በዚህ ውይይት ላይ የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ ተገኝተው ተጨማሪ ጠቃሚ የሆነ ሀሳቦች አካፍለዋል። ይህ ውይይት በወጣቶች ጉዳይና በህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴዎች የተዘጋጀ ሲሆን […]
አንድነት ፓርቲ የ2007 ምርጫ በተቀናጀ ሁኔታ ለመምራት የምርጫ ግብረ ኃይል አቋቋመ
የአንድነት ፓርቲ ብሄራዊ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በህዳር 6/2007 ዓ.ም. ባደረገው ስብሰባ የ2007 ምርጫ በተቀናጀ ሁኔታ ለመምራት እንዲቻል 10 አባላት ያሉት በከፍተኛ የፓርቲው አመራሮች የሚመራ የምርጫ ግብረ ኃይል አቋቁሟል። ይህ የምርጫ ግብረ ኃይል ፓርቲው በ2007 ምርጫ ውጤታማ ሆኖ እንዲወጣ አጠቃላይ የምርጫ ዘመቻውን በበላይነት የሚመራ ሲሆን፤ በተጨማረም በቅርቡ የሚጀመረው የሚሊዮኖች ድምፅ ለፍትሀዊና ነፃ ምርጫ ህዝባዊ ንቅናቄ ዘመቻ […]
ከምሽቱ ሦስት ሰዓት የአማርኛ ዜና – ኖቬምበር 16, 2014
የፕሮግራም መግለጫ
ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡
ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡
የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡
ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና
ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና
ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ
ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት
ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)
ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና
ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡
ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡
የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡
ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡
የኢትዮጵያ አብዮት አርባኛ ዓመትና ፖለቲካዋ
ከየካቲት 1966 ጀምሮ አንዳዶች የሚድኸዉ መፈንቅለ መንግሥት፤ ሌሎች አዝጋሚዉ አብዮት፤ ሌሎች ደግሞ ግብታዊዉ ለዉጥ የሚሉት አብዮት የወደፊት ሒደት በግልፅ የታየበት፤ደርግ «ያለ ምንም ደም» ከሚለዉ መሪ መፈክሩ በታቃሮኑ መቆሙ የተረጋገጠበት፤ የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ጉዞም በደም «በጨቀየ» ጎዳና መደናበር የጀመረበት ወቅት ነዉ።
ከኢንጂነር ኃይሉ ሻወል ተጽዕኖ ያልወጣው የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት /መኢአድ/ ጠቅላላ ጉባኤ እና አሳፋሪው ድራማ (MUST READ)
የመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት /መአሕድ/ በ1984 ዓ.ም ተመስርቶ ገዢው ፖርቲ በኦሮሚያ፣ በጋምቤላና በደቡብ ክልሎች በሚኖሩ በአማራ ብሔረሰብ ላይ እየደረሰ ያለውን የግፍ ጭፍጨፋና የመብት ረገጣ ለመታገል፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶችንና የሕግ የበላይነትን እንዲሁም የዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታን ዕውን ለማድረግ ሰንቆ በተነሳው አላማ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ እንቅስቃሴ በማድረጉ የፖርቲው መስራችና እውቁ የሕክምና ምሁር ኘሮፌሰር አስራት ወልደየስ ደ/ብርሃን ከተማ በጠሩት ሕዝባዊ ስብሰባ ላይ ባደረጉት ንግግር ወደ ውህኒ ወርደው በግፍ ሕይወታቸው ያለፈ ቢሆንም የፖርቲውን ተቀባይነትና እንቅ ቃሴ ገዥው ፖርቲ ኢህአዴግ የሚገደብበት አቅም አላገኘም ነበር፡፡
መአህድ ይዞት በተነሳው አገራዊ አላማ ከብሔር ድርጅትነት ራሱን በማሳደግ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት /መኢአድ/ የሚለውን ስያሜ በመያዝ በ1995 ዓ.ም ሕብረ ብሔራዊነቱን አውጆ እስከ 1996 ዓ.ም ባለው ጊዜ ከ1.2ሚ በላይ አባላት ያፈራና በርካታ ጽ/ቤቶችን በሀገሪቱ ክፍሎች በመክፈት ከፍተኛ የዕድገት ደረጃ ላይ የደረሰበት ጊዜ ነበር፡፡
መኢአድ በ1997 ዓ.ም ከሌሎች 3 /ሶስት/ ፖርቲዎች ጋር በመሆን ቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ /ቅንጅት/ ፖርቲን በመመስረት ለምርጫ 97 የመኢአድ መሰረቱን ተጠቅሞ ቅንጅት ባደረገው እንቅስቄሴ ለተገኘው የፖለቲካ ተሳትፎና የምርጫ ውጤት መኢአድ የአንበሳውን ድርሻ መያዙ የትናንቱ የታሪክ እውነታ እንደነበር ይታወሳል፡፡
የ97 ምርጫ ውጤትን ተከትሎ ገዥው ፖርቲ በወሰደው ኢዲሞክራሲያዊ የምርጫ ውጤት ቅልበሳ የተቆጣው የኢትዮጵያ ሕዝብ “ድምጻችን ይከበር” በማለት በየአደባባዩ ለወጣው ሰላማዊ ሰልፈኛ በታጣቂ ኃይሎች የተወሰደው ያልተመጣጠነ እርምጃ ብልጭ ብሎ የነበረውን የዲሞክራሲ ጭላንጭል ወደነበረበት ጨለማ በመቀልበስ የቅንጅት አመራሮችን ወደ ወህኒ ቤት በመወርወር ካሰረና ካስፈረደ በኋላ በተለመደ ድራማው ይቅርታ እንዲጠይቁ በማድረግ ከእስር እንዲለቀቁ የተደረጉት የቅንጅት አመራሮች በእስር ቤት እያሉ በተፈጠረ አለመግባባት ከወህኒ ቤት ከወጡ በኋላም በመቀጠሉ ጉዳዩን በጠረጴዛ ዙሪያ ለመፍታት አንድም ሙከራ ሳይደረግ ወደ አሜሪካና አውሮፖ በቡድን በመንቀሳቀስ ሁሉም የራሳቸውን ቡድን በማጠናከር አለመግባባቱን እንዲባባስ አድርገው በዚህ ምክንያት አብዛኛው የቅንጅት አመራር አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ /አንድነት/ የሚል ፖርቲ መስርተው ለመንቀሳቀስ የቻሉ ሲሆን ጥቂት የመአአድ አመራሮች ወደቀድሞው ፖርቲያቸው መኢአድ በመመለስ ከሰኔ 14-15 2000 ዓ.ም የፖርቲውን የመጀመሪያ ጠቅላላ ጉባኤ በማድረግ ኢንጅነሩን ኘሬዝዳንት በማድረግ የተናጠል ጉዞውን ሲጀምሩ የፖርቲውን የውድቀት ቁልቁለት “ሀ” ብለው የጀመሩ ሲሆን ለዚህ ውሣኔና አካሄድ ዋና ምክንያታቸው ደግሞ ምንም እንኳ ቅንጅት የሚለውን ስም ለማግኘት ለሌላ አካል የተሰጠ በመሆኑና ባያገኙትም ከቀስተ ደመና ፖርቲና ከአድሊ ፖርቲ ጋር አዲስ ፖርቲ መስርተው ለመቀጠል በአዲሱ ፖርቲ ውስጥ ቦታ አናገኝም ከሚለው ስጋታቸው በተጨማሪ በመኢአድ ፖርቲ ውስጥ በተለያዩ ደረጃ ተቀምጠው የሚያገኙት ጥቅማጥቅም ይቀርብናል የሚለው ትልቁ ምክንያታቸው እንደነበር በቀላሉ ለመረዳት ተችሏል፡፡
የመኢአድ አመራሮች በተናጠል የመስራትና የመጓዝ ልምዳቸው ከራስ ጥቅም ጋር የሚያያዝ ሲሆን ለ2002 ምርጫ ከመድረክ ጋር አብሮ ለመስራትም ሆነ የመድረኩ አባል ለመሆን አልመፈለግና የፖለቲካ ፖርቲዎችን የምርጫ ስነ ምግባር ለመፈረም ኢህአዲግ ከአጋሮቹ ጋር በመራው ውይይት ላይ የመኢአድ ተሳትፎና የፖርቲው ኘሬዝዳንት ኢንጅነር ኃይሉሻወል ከኢህአዲግ ሊቀመንበርና ጠቅላይ ሚኒስቴር አቶ መለስ ዜናዊ ጋር እጅ ለእጅ መጨባበጥ የፖርቲውን ትልቁን የውድቀት ርምጃ ያበሰሩ ሲሆን በአንዳንድ ግለሰብ አስተያየትም ኢንጅነሩ ካላቸው የንግድ ተቋምና ባለሀብትነት አኪያ “ልማታዊ ባለሀብት” አስብሎ ያስጠረጠራቸው እና በምርጫውም ላይ በገጠርም ሆነ በከተማ መኢአድ ላስመዘገበው ዝቅተኛ የድምፅ ቁጥር ዋንኛ ምክንያቱ ይሄው ሀቅ መሆኑ አጠያያቂ አልነበረም፡፡
የፖርቲው ጠቅላላ የውጤት መቀነስም ሆነ ኘሬዝዳንቱ በተወዳደሩበት የምርጫ ክልል እንኳ በግላቸው ያገኙት ዝቅተኛ የድምፅ መጠን የፖርቲውን እድገት እንደ ካሮት ወደታች መሔድ ከማሳየቱም በተጨማሪ የፖርቲው ኘሬዝዳንት ግንቦት 19/2002 ዓ.ም ከፖርቲ ኘሬዝዳንትነት ለቅቄያለሁ የሚለው የመልቀቂያ ደብዳቤ ማስገባት የዚሁ የምርጫ ውጤት ዝቅተኛነት መሆኑን ከመልቀቂያ ደብዳቤው ላይ ተገልጿል፡፡
ከዚህ በኋላ ፖርቲው ያለቅደመ ሁኔታ ከአንድነት ለፍትህ እና ለዲሞክራሲ እንዲሁም ከብርሃን ፖርቲ ጋር ለመዋሀድ የሶስትእዮሽ ድርድር በመፍጠር በአብዛኛው ውይይት የተስማሙ ቢሆንም ከታህሳስ 16-18 ለሚደረገው ጠቅላላ ጉባኤ ኘሬዝዳንቱ ወደ ፖርቲው በፍቃዳቸው በመመለስ ጉባኤውን አድርገን በጉባኤው እስከምናስወስን ድረስ የ3 /ሶስትዮሽ/ ድርድሩ ይቋረጥ የሚል ትዕዛዝ በመስጠታቸውና የሳቸውን ትዕዛዝ የሚቃወም አመራር ባለመኖሩ የውህደት ድርድሩ ተቋረጠ፡፡
ከታህሳስ 16-17/2003 በተደረገው የጠቅላላ ጉባኤ ላይም የፖርቲው ኘሬዝዳንት ስልጣን ይለቃሉ ተብሎ በመጠበቁ የኘሬዝዳንቱን ስልጣን የሚፈልጉ ሁለት ቡድኖች የራሳቸውን ቅስቀሳ /Lobbing/ በማጠናከራቸው ጉባኤው ጤናማ ሆኖ መቀጠል ባለመቻሉ የጉባኤው አባላት ኢንጅነር ኃይሉ ለ2/ሁለት/ ዓመት በኘሬዝዳንትነት እንዲቀጥሉ ሲያደርጋቸው እኔን በኘሬዝዳንትነት ከመረጣችሁ ተቀዳሚ ኘሬዝዳንት ሆኖ የሚያግዘኝ አቶ ያዕቆብ ልኬ በመሆኑ የእኔንም ጥቆማ አፅድቁልኝ በማለት ለጠቅላላ ጉባኤው ቅድመ ሁኔታ በማስቀመጣቸውና የኢንጅነሩን ቃል በጉባኤ ተቃውሞ ማቅረብ የተለመደ ባለመሆኑ ጉባኤተኛው አፀደቀላቸው፡፡
ይሁን እንጂ በተቃራኒው የኘሬዝዳንቱ ቦታ ይፈልጉ የነበሩ ቡድኖች የአቶ ያዕቆብ ልኬ ተቀዳሚ ኘሬዝዳንት ሆኖ መመረጥ ተቃውሞ ባያቀርቡም ውስጣቸው ደስተኛ አለመሆናቸው በግልጽ ይንፀባረቅ ነበር፡፡
ታህሳስ 20/2003 ዓ.ም የስራ አስፈፃሚውን የስራ ድርሻ ኘሬዝዳንቱ በራሳቸው ፍላጎት ደልድለው ሲያበቁ ቀደም ሲል በአቶ ማሙሸት አማረ ተይዞ የነበረው የፖርቲው ዋና ፀሐፊ ለአቶ ተስፋዬ ታሪኩ መሰጠቱን ተከትሎ በእነ አቶ ማሙሸት አማረ እና በኢንጅነር ኃይሉ ሻወል መካከል የነበረው የአባትና ልጅ እንዲሁም የአካባቢዋ ገመድ ትስስር ተበጥሶ ወደለየለት አጋች ታጋች ድራማ በመሸጋገሩ የፖርቲው ሌላው ዙር የውድቀት ምዕራፍ ተከፈተ፡፡
ሐምሌ 30/2003 ዓ.ም መኢአድ በእየሩሳሌም ሆቴል በጠራው የማዕከላዊ ምክር ቤት ስብሰባ ላይ የእነ አቶ ማሙሸት አማረ ቡድን ከፖርቲው እንዲባረሩ የተወሰነ ሲሆን ይህ ምክር ቤት ሌላ ታሪካዊ ውሣኔ ወሰነ፡፡ ይኸውም ከዚህ በፊት የነበረው የፖርቲው መተዳደሪያ ደንብ ለኘሬዝዳንቱ ሰፊ መብት ሰጥቶ የነበረ ሲሆን ከታህሳስ 14-15 በተጠራው የጠቅላላ ጉባኤ ወቅት ደንቡን እንዲሻሻል የማዕከላዊ ምክር ቤቱ በተሰጠው ስልጣን መሰረት የኘሬዝዳንቱን ስልጣን በመቀነስ ለፖርቲው ማዕከላዊ ምክር ቤትና ለስራ አስፈፃሚው ቀንሶ በመሰጠቱ በኘሬዝዳንቱ እና በአብላጫው 10 /አስሩ/ ስራ አስፈፃሚ መካከል ሌላ ዙር አለመግባባት ተፈጥሮ 10 /አስር/ ስራ አስፈፃሚ በማገድ ወደ ጽ/ቤት እንዳይገቡ በመደረጉ የአባላት መከፋፈል ፖርቲውን በውድቀት ቁልቁለት እያንደረደረው በመሔዱ እና የእነ አቶ ማሙሸት አማረ ቡድንም ሆነ የእነ አቶ አሰፋ ሀብተወልድ ቡድን በየራሳቸው የያዙት አባላትና ደጋፊ ኢንጅነሩ ጽ/ቤቱን ይዘው ከቀሩት አባላት በእጅጉ የገዘፈ በመሆኑ እና የመጨረሻ እልባት ለማግኘት የጠቅላላ ጉባኤ እንዲጠራ ለምርጫ ቦርድ ከሁለቱም ቡድኖች በቀረበው ጥያቄ መሠረት ፖርቲው የጠቅላላ ጉባኤውን በመጥራት ሁሉም ቡድኖች በተገኙበት ጉባኤው የሚሰጠውን ውሣኔ እንዲያሳውቅ ቦርዱ በሰጠው ትዕዛዝ መሠረት የፖርቲው ጠቅላላ ጉባኤ ሐምሌ 14 ቀን 2005 ዓ.ም የተጠራ ቢሆንም የእነ አቶ ማሙሸት አማረ ቡድንም ሆነ የእነ አቶ አሰፋ ሐብተወልድ/አብላጫው/ ስራ አስፈፃሚ በጉባኤ ተገኝቶ የታገደበትን እና የተከሰሰበትን ጉዳይ ለማስረዳት እና የመከላከል ሕገ መንግስታዊ መብቱ ሳይከበር ወደ ጉባኤው እንዳይገባ ተከልክሎ በጠቅላላ ጉባኤው እንድባረሩ ሲወሰን ጉባኤው የሁለቱም ቡድኖች ሐሳብ ለመስማት በጉባኤው ላይ እንድገኙ አለማድረጉ የመኢአድ ጠቅላላ ጉባኤ በኘሬዝዳንቱ ጫና ስር የወደቀ ለመሆኑ ሌላ ማስረጃ የሚያስፈልገው አይሆንም፡፡
በዚህ ጉባኤም የፖርቲው ኘሬዝዳንት ከኘሬዝዳንትነት ለቀው የፖርቲውን መተዳደሪያ ደንብ በማሻሻል የሌለ እና ያልተለመደ የፖርቲው የበላይ ጠበቂ የሚል አንቀጽ በመጨመር አቶ አበባው መሐሪ ኘሬዝዳንት በማድረግ ርሳቸው የበላይ ጠባቂ በመሆን ፖርቲውን ቤታቸው ሆነው ለመቆጣጠር ሪሞቱን አዘጋጁ፡፡
የዚህን ጠቅላላ ጉባኤ ውጤት እና አዲሱን የአመራር አመራረጥ ያልተቀበለው መሆኑን ቦርዱ ወዲያው ቢያሳውቅም ለአመት ያህል ይህ አመራር ፖርቲውን እያስተዳደረ ከቦርዱ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች የሚፃፃፋቸው ደብዳቤዎች እና የነበሩ የስራ ግንኙነቶች ሲታዩ ፖርቲው ሕጋዊ ሆኖ ቆይቷል ያሰኛል፡፡
ቀድሞ የተጀመረው የመኢአድ እና የአንድነት የውህደት ድርድር በእነ አቶ አበባው መሀሪ ስምምነት ላይ ሲደርስ እና ጠቅላላ ጉባኤ ለመጥራት ሲዘጋጁ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ የቆየ ገመዱን ለመምዘዝ ሲቻኮል እና የሁለቱን ፖርቲዎች የውህደት ሂደት ለማደናቀፈ የተደረገውን ሴራ ሲታይ የገዢው ፖርቲ ቀጭን ትዕዛዝ የለም ለማለት የሚያስደፍር አይደለም፡፡
ይህን ተከትሎ ውህደቱን በመቃወም “መኢአድ ተሸጠ” በማለት በእነ አቶ ማሙሸት አማረ የተሰጠው መግለጫ ሲታይና የመኢአድ ከጥቅምት 28-29 የጠቅላላ ጉባኤ መጠራትና ወደ ፖርቲው ጽ/ቤት ኢንጅነር ኃይሉሻወል ሲገቡ በእነ አቶ ማሙሸት አማረ ታጅበውና ተደግፈው ወደ መድረኩ ሲወጡ ላየ ፖለቲከኛ የትናንቱ የጋዜጣ መዝለፍለፍና እስከ ፍ/ቤት የደረሰ መካሰስ በምን አይነት ሽማግሌ እርቅ እንደወረደ ግልጽ ባይሆንም ቀድሞ መኢአድ ተሸጠ ብለው በጋዜጣ መግለጫ ያወጡትን የእነ ማሙሸትን ቡድን ያስማማ የጋራ ፍላጎት አጀንዳ ሆኖ ከመታየቱም ሌላ የ3/ሶስተኛ/ እጅ ስላለመናሩስ በምን እንዳንጠራጠር ያደርጋል፡፡ የፖለቲካ መሄጃና መምጫው የማይታወቅ በመሆኑ የመኢአድን ከአንድነት ጋር መዋሀድ ከማይፈልጉት ኃይሎች ውስጥ ኢንጅነር ኃይሉና እነ ማመሸት ብሎም ኢህአዲግ በመሆናቸው ሶስቱን አካሎች ያስተሳሰራቸውን ድራማ እና ታሪክ ወደፊት እስከሚያመጣው ድረስ ለጊዜው መተው የተሻለ ይሆንና የጥቅምት 28-29 ጠቅላላ ጉባኤ ሂደትና ውጤት ላይ ማተኮርን እመርጣለሁ፡፡
ጥቅምት 28/2007 የፖርቲው ማዕከላዊ ም/ቤት ስብሰባ ስለነበር የጉባኤው አባላት /የም/ቤቱ ምዕለተ ጉባኤ በመሟላቱ ስብሰባውን ኢንጅነሩ እንዲመሩት ተደርጐ፡፡ የእነ አቶ ማሙሸት ቡድንና የእነ አቶ አሰፋ ሀብተወለድ ቡድን ታግዶ የቆየበትን አሰራር ፖርቲው በሪፖርት ከገለፀ በኋላ ም/ቤቱ እንዲወያይበትና የውሣኔ ሀሣብ በማሳለፍ በቀጣዩ ቀን 29/02/07 ለጠቅላላ ጉባኤ እንዲቀርብ በተጀመረው ውይይት መሰረት የም/ቤቱ አካሄድ ኢንጅነሩ የጠበቁት ባለመሆኑ እና እነ አቶ ማሙሸትን ለማባረር የተዘጋጀ በመምሰሉ በዚህ ሁኔታ ውይይቱን ማስቀጠሉ ለቀጣይ ቀን ለጠቅላላ ጉባኤው የሚቀርብ የውሣኔ ሀሳብ ላይ ደስተኛ ያልሆኑት ኢንጅነሩ በለመዱት ተጽኖ ፈጣሪነት ከሰዓቱ መምሸት አኳያ እንደምክናያት ተጠቅመው ይሔ አጀንዳ ለነገ ከጠቅላላ ጉባኤው ጋር ውሣኔ ይሰጥበት በማለት አካሄዱን ቀይረው በይደር አሳለፋት፡፡
አዳሩን የገባው የጠቅላላ ጉባኤ አባላት እነ ማሙሸት እንደመለሱ እንዲወሰን ቅስቀሳ /Lobbing/ ሲደረግ ያደረ ሲሆን በ29/03/07 የጠቅላላ ጉባኤው ምለዕተ ጉባኤ የተሟላ በመሆኑ የእነ አቶ ማሙሸት አጀንዳ ሲከፈት የጉባኤው አባላት 3 /ሶስት/ ሀሣቦችን አቅርቦ ነበር፡፡ እነዚህም
1. እነ አቶ ማሙሸት ከዲሲኘሊን ውጭ የተንቀሳቀሱ ስለሆነ ከፖርቲ አባልነታቸው ይባረሩ፡፡
2. ፖርቲው ካለበት ችግርና እነሱም ለፖርቲው ከሰጡት አገልግሎት አንፃር በይቅርታ ታልፈው በአባልነት ይቀጥሉ፡፡
3. ወደ አመራርነት ሳይመጡ በአባልነት ለ2 /ሁለት/ ዓመት ይቆዩ የሚሉ ሲሆን በአብዛኛው በ3ኛው ውሣኔ ላይ በመስማማት ጉባኤተኛው በጭብጨባ ያፀደቁት ሲሆን ኢንጂነሩ ጉባኤውን በለመዱት አካሄድ ውሳኔውን የሻሩት በተለመደው ተጽኖ ፈጠርነታቸውን በመድገም ወደ ፖርቲው መመላለሳቸውን ምክንያት በማድረግ የማዕከላዊ ም/ቤት አባል እንደሆኑ በማድረግ የተለመደ ጫናቸውን በጉባኤው ላይ ሲያሳርፉ አንዳንድ የጉባኤው አባላትም ሰብስበውን እየረገጡ የሄዱ ቢሆንም አብዛኛው ጉባኤትኛ ከዚህ በላይ መከራከሩና ኢንጅነሩን ማሸነፍ ያልተለመደ በመሆኑ በሳቸው ተጽኖ ስር ጉባኤው ወደቀ፡፡
ጥቅምት 30/2007 የጠቅላላ ጉባኤው አባላት የተበተነና ቀጣዩ ኘሮግራም የማዕከላዊ ም/ቤት አባላት ስብሰባ የስራ አስፈፃሚውን የስራ ምደባ ማድረግ ስለነበር ኢንጂነሩ አቶ ማሙሸት አማረን ኘሬዝዳንት አድርገው ስልጣናቸውን አውርሰዋል፡፡
እነ ማሙሸትም በአካባቢያቸው ተወላጆች ታጅበው አመራሩን ይዘው እንዲቀጥሉ ሊያስማማቸው የሚችለው አካል ማን ሲሆን ይችላል የሚለውን ጥያቄ በሂደት የምንመለሰው ቢሆንም የጉባኤው ውሳኔ በኢንጅነሩ ተሽሮ ፖርቲው በእነ ማሙሸት አማረ እጅ መግባቱ በርካታ አባላቱንና አመራሩን ከማስቆጣት አልፎ በዚህ አመራር ስር ላለመቀጠል እና ሌሎች አማራጮችን ለመውለድ የተዘጋጀውን ኃይል ስናየው የፖርቲውን የመጨረሻ የውድቀት ምዕራፍ ያስተናጋደ ታሪካዊ ሂደት ሆኖ መኢአድን እስካሁን ከገጠመው የመከፋፈልና የአባላት ድርቀት የዚህ ጉባኤ ውጤት ያመጣው ጣጣ የሶስተኛውን አካል ተሳትፎ ያጐላ በመሆኑ እስካሁን ለፖርቲው የተከፈለውን ዋጋ የሸጠ የኢንጁነር ኃይሉ አሳዛኙ ድራማ ሆኖ በታሪክ ይመዘገባል፡፡
(በጌታቸው ባያፈርስ)
በ9ኙ ፓርቲዎች ተጠርቶ የነበረው የአደባባይ ስብሰባ ፖሊስ በኃይል በትኖታል! photos

ፖሊስ ህዝቡን ለመበተን እየጣረ ነው፡፡የስብሰባው አዘጋጆች አንሄድም ብለው ሜዳው ላይ ይገኛሉ፡፡
#Ethiopia #Blueparty #Election2007 #NegereEthiopia #MinilikSalsawi
9ኙ ፓርቲዎች የጠሩት የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ በኃይል ተበተበ
ዛሬ ህዳር 7/2007 ዓ.ም 9ኙ ፓርቲዎች በትብብር የጠሩት የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ በፖሊስና በደህንነት ኃይሎች ተበትኗል፡፡ ፓርቲዎቹ ለሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል ያሳወቁ ሲሆን የፓርቲዎቹ አመራሮች ለፖሊስና ደህንነቶች ቢያሳዩም ‹‹የምናውቀው ነገር የለም፣ እኛ ታዘን ነው፡፡ ከፈለጋችሁ አለቆቻችን ሂዳችሁ አናግሩ፡፡›› በማለት ለስብሰባው የተዘጋጁትን ቁሳቁሶች ስብሰባው ሊደረግበት ከታሰበው ሜዳ እንዲነሱ አድርገዋል፡፡
የፓርቲዎቹ አመራሮችና በስብሰባው ለመሳተፍ ወደቦታው ያቀኑ አካላት ለማሳመን ጥረት ቢያደርጉም ፖሊስ ግን ህዝቡን በኃይል በትኗል፡፡
ፖሊሶች የፓርቲውን አመራሮች በማስፈራራት ላይ ይገኛሉ #የቤለዬሩ_ሰልፍ Morning Update
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)
ስብሰባው እንዳይደረግ የሚከለክሉት ፖሊሶች ለምን ትከለክላላችሁ በሚል ለሚነሳው ጥያቄ እነሱ የሚሰጡት መልስ አናውቅም፣ ታዘን ነው የሚል ነው፡፡ የፓርቲዎቹ አመራሮች ስብሰባው እውቅያ ያገኘበትን ደብዳቤ ቢያሳዩዋቸውም እኛ ስለጉዳዩ አናውቅም ነው ያሉት፡፡
ፖሊስ ህዝቡን ለመበተን እየጣረ ነው፡፡ፖሊስ የአደባባይ ስብሰባ በኃይል ለማገድ እየወጣ ነው፡፡ ሞንታርቮና ጀኔሬተር የመሳሰሉትን ቁሳቁሶች በኃይል አንስተዋል፡፡ የስብሰባው አዘጋጆች አንሄድም ብለው ሜዳው ላይ ይገኛሉ፡፡ ለስብሰባው የመጣው ህዝብ ሁኔታውን ለመቅረጽ እንዳይሞክር እየጠደረገ ነው፡፡ በአንጻሩ ግን ደህንነቶች ህዝቡን እየቀረጹ ይገኛሉ፡፡
ከምሽቱ ሦስት ሰዓት የአማርኛ ዜና – ኖቬምበር 15, 2014
የፕሮግራም መግለጫ
ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡
ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡
የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡
ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና
ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና
ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ
ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት
ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)
ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና
ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡
ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡
የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡
ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡
የቡድን-20 የመሪዎች ጉባዔ ስምምነት
አውስትራሊያ – ብሪስባን በተካሄደው እና ኹለት ቀናት በፈጀው የቡድን-20 የመሪዎችጉባኤ ላይ ተሳታፊዎቹ መሪዎች የዓለም አቀፉን ምጣኔ ሀብት ለማሳደግ መወሰድ በሚገባቸው ርምጃዎች ላይ ተስማሙ። ፑቲን ጉባኤው ሳይጠናቀቅ እስከ ሩስያ ረዥም ጉዞ ነው የሚፈጀው በሚል ምክንያት ጉባኤውን ጥለው መሄዳቸውም ይፋ ሆኗል።
የቡድን-20 ሃገራት የመሪዎች ጉባኤና ፑቲን
በቡድን 20 አባል ሃገራት ጉባኤ የዩክሬይን ቀውስን አስመልክቶ በደረሰባቸው ብርቱ ወቀሳ የተነሳ የሩስያው ፕሬዚዳንት ጉባኤው ሳይጠናቀቅ አቋረጥው ሊወጡ እንደሚችሉ ዛቱ። በኢንዱስትሪ የበለፀጉት ሃገራት የሚያኪያሂዱት ጉባኤ የሚጠናቀቀው በኹለተኛ ቀኑ እሁድ ነው።
ዩጋንዳና የቀጣዩ ፕሬዚደንታዊ ምርጫ ዕጩ ጉዳይ
የዩጋንዳ «ናሽናል ሬዚዝተንስ ሙቭመንት» ፓርቲ ፕሬዚደንት ዮዌሪ ሙሴቬኒን እአአ ለ2016 ዓም ፕሬዚደንታዊ ምርጫ በዕጩነት ለማቅረብ የያዘው ዕቅድ ብርቱ ክርክር አስነስቷል።
የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ታሰሩ = ምግብ እንዳይገባላቸው ተከለከሉ
የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ታሰሩ
#Ethiopia #Blueparty #NegereEthiopia #MinilikSalsawi
– በቅስቀሳ ላይ የሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና አመራሮች እየታሰሩ ነው
– የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና አመራሮች ምግብ እንዳይገባላቸው ተከለከሉ
– ህዝብ በንቃት እንዲሳተፍ ጥሪ ቀርቧል
በተለያዩ የአዲስ አበባ ክፍሎች ለእሁዱ የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የታሰቱትን የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና አመራሮች ለመጠየቅ ወደ ፖሊስ ጣቢያ የሄዱት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ታሰሩ፡፡
በቅስቀሳ ወቅት የነበሩት የሰማያዊ አባላትና አመራሮች መያዛቸውን ተከትሎ የእሁዱን የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ ለስበስባና ሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቂያ ክፍል ያሳወቁበትን ህጋዊ ደብዳቤ በመያዝ የአባላቱና አመራሩ እስራት ህገ ወጥ መሆኑን ለማስረዳትና አባላቱን ለመጠየቅ ወደ አራዳ መምሪያ ፖሊስ ጣቢያ ያቀኑት የሰማያዊ ፓርቲ የፋይንስ ጉዳይ ኃላፊ አቶ ወሮታው ዋሴ እና የአደረጃጀት ጉዳይ ኃላፊው አቶ ብርሃኑ ተ/ያሬድ በፖሊስ ተይዘው ታስረዋል፡፡
የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር እሁድ ህዳር 7/2007 ዓ.ም ለሚያደርገው የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ ቅስቀሳ ላይ የነበሩ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና አመራሮች ታሰሩ፡፡የብሄራዊ ምክር ቤት አባል የሆነው አቶ ዮሴፍ ተሻገር እንዲሁም የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባል የሆነው ሲሳይ በዳኔ መገናኛ አካባቢ ቅስቀሳ ላይ በነበሩበት ወቅት ታስረዋል፡፡
በተመሳሳይ የምርጫ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባል አቶ ሳምሶን ግዛቸው እንዲሁም የአዲስ አበባ ዞን ምክትል ሰብሳቢና ህዝብ ግንኙነት አቶ ማቲያስ መኩሪያ በአራዳ ክፍለ ከተማ ቅስቀሳ ላይ በነበሩበት ወቅት በፖሊስ ተይዘው አራዳ ፖሊስ መምሪያ ታስረዋል፡፡በሌሎች የአዲስ አበባ ክፍሎች ቅስቀሳ ላይ የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና አመራሮች በፖሊስ ወከባ እየደረሰባቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ህዳር 7/2007 ዓ.ም ቤልየር ሜዳ ላይ የሚደረገው የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ ሰማያዊ ፓርቲ የሚያስተብብረው ሲሆን በአንድ ወር የሚደረጉትን ሌሎቹን መርሃ ግብሮች 9ኙ ፓርቲዎች በየተራ እንደሚያሰተብብሩ መስማማታቸው ይታወቃል፡፡
9ኙ ፓርቲዎች በትብብር ለሚያዘጋጁትና ሰማያዊ ፓርቲ ለሚያስተባብረው የህዳር 7/2007 ዓ.ም. የሚደረገው የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ ሲቀሰቅሱ እና ታሳሪዎቹን ለመጠየቅ ወደ ፖሊስ ጣቢያ በሄዱበት ወቅት የታሰሩት 6 የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ምግብ እንዳይገባላቸው ተከለከሉ፡፡
በሌላ በኩል ለነገው የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ በአብዛኛው የአዲስ አበባ ክፍሎች ስኬታማ ቅስቀሳ መደረጉን የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ገልጸዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ አገር ውስጥም ሆነ በውጭ የሚገኙ ለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያውያን፤ ህዝቡ በአደባባይ ስብሰባው እንዲሳተፍ በስልክ (በመደወልም ሆነ መልዕክት በመላክ)፣ በማህበራዊ ድህረገጽና ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ የበኩላቸውን እንዲያደርጉ፣ ለአንድ ወሩም መርሃ ግብርም ሆነ በሌላ የትግሉ አካል ሁለገብ ድጋፍና ተሳትፎ እንዲያደርጉ የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ጥሪ አድርጓል፡፡
በደ/ኦሞ: በሀ/ስብከቱ እና በማኅበረ ቅዱሳን መተባበር ከ16 ሺሕ በላይ ምእመናን ወደ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ሃይማኖት ተጨመሩ፤ ‹‹ለቤተ ክርስቲያን ታላቅ ደስታ ነው›› /ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ/
ከ1300 በላይ አዲስ አማንያን በቅዱስ ፓትርያርኩ እና በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ተጠመቁ በዓመቱ 17‚000 አዲስ አማኞችን ለማፍራት በመርሐ ግብር የተያዘው ዕቅድ አካል ነው ከተጠማቂዎቹ፣ ከባዕድ አምልኮ የተመለሱ አርብቶ አደሮች እንደሚገኙበት ተመልክቷል * * * በዲዛይን ሥራው የማኅበረ ቅዱሳን ሞያዊ አስተዋፅኦ ከተገለጸበት አዲሱ የጂንካ ደብረ ቀራንዮ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ቤት (ምረቃ) ጋራ ጥምቀተ ክርስትና የተፈጸመላቸውና …![]()
ኦሮሞነት ዘረኝነት አይደለም
ኦሮሞነት ዘረኝነት አይደለም — ግርማ ካሳ
======================
በኦሮሞዉና በአማርኛ ተናገሪው መካከል ጥላቻ እንዲሰርጽ ተብሎ አንድ የተጻፈ መርዛማ መጽሐፍ አለ። የቡርቃ ዝምታ የሚባል መጽሃፍ። የዚህ መጽሀፍ ደራሱ አቶ ተስፋዬ ገበረ አብ ይባላሉ። የሕወሃት/ኢሓአዴግ ከፍተኛ ባለስልጣን የነበሩ ጊዜ የጻፉት መጽሀፍ ነው። በቅርቡ “በሞጋሳ ኦሮሞ ሆኛለሁ” ሲሉ አቶ ተስፋዬ ተናግረዋል። ምን ያህል የሞጋሳ ሚስጠር እንደገባቸው ግን አላውቅም።
ከአራት መቶ አመታት በፊት፣ የኦሮሞ ጦረኞች አንድ አካባቢን በሚቆጣጠሩና በሚማርኩ ጊዜ፣ አንድ የሚያደርጉት ሥርዓት ነበር። የጎሳው ሽማግሌዎች ከተማዋ ሲገቡ ከዚያ ጊዜ ጀመሮ ያቺ ክከተማ ኦሮሞ ትሆናለች። በከተማዋም የሚኖረው ህዝብ፣ በሽማግሌዎቹ ፊት ያልፋል። በዘሩ ከሌላ ወገን ቢሆንም፣ በአለቃዉ ያለፈ ሰው ሁሉ ኦሮሞ ይሆናል። ይህ ስርአት ሞጋሳ ይባላል። ኦሮሞነት ከዘር ጋር ግንኙንት እንደሌለው የሚያስተምር የኦሮሞ ባህል !
ሞጋሳ የሚያሠባስብ ነው። አንድ የሚያደርግ ነው። በመሆኑም ኦሮሞነት አንድነት ነው። ኦሮሞነት ሌላውን እንደ እራስ አድርጎ ማቀፍ ነው። ኦሮሞነት ሌላውን ማሳነሳ፣ ሌላውን ማባረር፣ ሌላውን መጥላት አይደለም።
እርግጥ ነው አንዳንድ አክራሪ የኦሮሞ ብሄረተኞች፣ በኦሮሞነት ስም ሌሎችን የመጥላት ፖለቲካ ያራምዳሉ። ከሌሎች የመለየት፣ ሌሎችን የማግለል፣ የመከፋፈል፣ የጥላቻ ፖለቲካ ያራግባሉ። የኦሮሞ ባህል ግን ፣ የሞጋሳ ባህል ግን ፣ አንድ የሚያደርግ ባህል ነው። እነርሱ ከሚናገሩትና ከሚረጩት መርዝ ጋር ግንኙነት የለውም።
ሌላው በአማርኛም ሳይቀር የምንጠቀማት ቃል አለች። ጉዲፈቻ። ጉዲፈቻ ማለት የሌላውን ሰው ልጅ እንደ ራስ አድርጎ ማሳደግ ማለት ነው። ጉዲፋቻ የሚለውን ቃል በአማራኛ መጠቀማችን በራሱ የሚያሳየው፣ የሌላውን ልጅ እንደራስ አድርጎ የማቀፍ ባህል፣ በኦሮሞው ማህበረሰብ ዉስጥ ምንም ያህል ስር የሰደደ ባህል እንደሆነ ነው። የኦሮሞው ማህበረሰብ፣ ትግሬ ይሁኑ አማራ፣ ጉራጌ ይሁኑ ከፊቾ ፣ ከሌላ ዘር የሆኑትን እንደራሱ አድርጉ የሚያሳድግ ማህበረስብ ነው። ከሌላው ጋር የተዛመደ፣ የተዋለደ፣ የዘረኝነት ነገር የሌለበት ማሀብረሰብ ነው።
ላለፉት 23 አመታት ግን በሽታ ገባ። የኦሮሞ ማህበረሰብን ከሌላው ለማጣላት ብዙ ተሞከረ። የባለስልጣናቱ ካድሬዎች ሆን ብለው በኦሮሞው እና ኦሮሞ ባልሆነው ማህብረሰብ መካከል ልዩነቶች እንዲፈጠሩ ቀን እና ሌሊት መስራት ጀመሩ።
ለአማርኛው ተናጋሪዎች “ ኦሮሞዎቹ ዘረኞች ናቸው። አማርኛን ይጠላሉ። ይጨርሷቹሃል። ያርዱዋቹኋል” የሚል እድምታ ያለው መልእክት በጎን ያስተላልፋሉ። ለኦሮሞ ደግሞ ” እነርሱ ነፍጠኞች ናቸው። በቋንቋህ እንዳትናገር ሊያደርጉህ ነው። ሊያጠፉህ ነው። የድሮው የአማራ የበላይነትን ሊያመጡብህ ነው። አሃዳዊ ስርዓት ሊጭኑብህ ነው” ይሉታል። አማርኛ ተናጋሪዎች በአፋን ኦሮሞ ተናጋሪዎች ላይ ፣ አፋን ኦሮሞ ተናጋሪዎች ደግሞ በአማርኛ ተናጋሪዎች ላይ ጥርጥሬ እንዲያድርባቸውና እና እንዳይግባቡ እያደርጓቸው ነው። ኦሮሞዎች አማርኛ እንዳይማሩ፣ አማርኛ ተናጋሪዎች ደግሞ አማርኛ ብቻ እንዲናገሩ ተደርጎ፣ የአንድ አገር ልጆች ሆነን እንዳንግባባ ተደርገናል። መነጋገር ስላልቻልን፣ አንዳንች ስለአንዳንች የሚነጉን የአገዛዙ ካድሬውዎችና ዉጭ ያሉ አንዳንድ አክራሪዎች ናቸው። ነገሮችን እየጠመዘዙ ስለሚነግሩንም እርስ በርስ እየታመስን ነው።
መንቃት ይኖርብናል። እነዚህ የጥፋት ኃይሎች በኛ ላይ የሽረቡትን ወጥመድ ማፈራረስ አለብን። የኦሮሞ ባህል፣ የኦህደድ ካድሬዎች ወይንም ዉጭ ያሉ አንዳንድ ለኦሮሞ ተቆርቋሪ ነን የሚሉ ግን በጥላቻ የተሞሉ አክራሪዎች እንደሚነግሩን አይደለም። ኦሮሞነት ዘረኝነት አይደለም። ኦሮሞነት አንድነት ነው። ኦሮሞነት ሌሎች እንደ ራሱ አድርጎ መቆጠር ነው። ኦሮሞነት የሚለያይ ሳይሆን የሚያሰባስብ ነው። የኦሮሞነት ፖለቲካ የጉዲፈቻና የሞጋሳ ፖለቲካ ነው።
የኦሮሞ ማህበረሰብ ከምንም በላይ ፣ በበሃሉ የሚመቸውና የሚቀበለው የአንድነትን እና የፍቅርን ፖለቲክ ነው። “እገሌ ከዚህ ዘር ስለሆነ፣ ወይንም ይሄ ቋንቋ ስለሚናገር ከአገራችን ይዉጣ። ይሄ ምድር የኦሮሞ ብቻ ነው ….ወዘተረፈ” የሚባለው አክራሪዎችና ካድሬዎች የሚረጩት እንጂ, ከሕዝቡ የሚመጣ አይደለም። የኦሮሞ ማህበረሰብ በባህሉ ሌላውን የሚቀበል፣ እንደራሱ አድርጎ የሚያኖርና የሚያሳድግ ነው። ለዚህም ነው ከጊዜ ወደ ጊዜ የአንድነት ፓርቲ በኦሮሞ ማህበረሰብ ዘንድ ተቀባይነቱ እየጨመረ የመጣው።
አፋን ኦሮሞ የማናውቅ ካለን፣ እንማር። አማርኛ የማናውቅ ካለን፣ አማርኛ እንማር፡ ብዙ ቋንቋ ማውቅ በረክት ነው። ሌላ ቋንቋ መማር አያሳንሰንም። እንደ ወንድማማቾች፣ ለመግባባት፣ ለመነጋገር፣ አብረን አገራችንን ለማሳደግ ቋንቋ አለማወቃችን እንቃፋት ሊሆንብን አይገባም።
ሾልኮ የወጣው እና ከፍተኛ ሚስጥር የያዘው ደብዳቤ- ስለ ኢቦላ በሽተኞች በቤንሽንጉል ጉምዝ ክልልመንግስት ጤና ጥበቃ ቢሮ
#በኢቦላ ከተጠረጠሩ ወያኔ ፍቱን መድሃኒት አዘጋጅቶልዎታል ያውም በመጠርጠርዎ ብቻ አስቀድመው እና አሳምረው በጥንቃቄ ገድለው ይቀብሩዎታል ፡፡ መረጃውን ያንበቡ
ኢህአዴግ የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ አለመሳካቱን አመነ
ኀዳር ፭(አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዘንድሮ የሚጠናቀቀው የኢህአዴግ የአምስት ዓመት የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን የተለጠጠ ዕቅድ በግብርና ዘርፍ መዳከም ምክንያት ሳይሳካ መቅረቱን ኢህአዴግ ለመጀመሪያ ጊዜ በይፋ አመነ፡፡ ኢህአዴግ «አዲስ ራዕይ» በተሰኘው በርዕዮተ ዓለም ልሳኑ የመስከረም- ጥቅምት 2007 ዓ.ም ዕትም ላይ የአምስት ዓመት የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ የአራት ዓመታት አፈጻጸም አስመልክቶ ባሰፈረው ሐተታ እንደጠቆመው ለጥጦ የያዘውን ዕቅድ …
ከጉራፈርዳ የተፈናቀሉ አብዛኞቹ አርሶ አደሮች ወደ ቀያቸው ለመመለስ ፈቃደኛ አልሆኑም
ኀዳር ፭(አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በጋምቤላና በደቡብ ክልል አዋሳኝ በሆነው በጉራ ፈርዳ ወረዳ የተነሳውን ግጭት ተከትሎ ከፍተኛ የሰው ህይወትና ንብረት ከወደመ በሁዋላ የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣኖች ባለፉት ሁለት ቀናት የአካባቢውን አመራሮች በመሻርና በመሾም መረጋጋት እንደተፈጠረ በመግለጽ ተፈናቃይ አርሶደሮች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ ለማግባባት ቢሞክሩም፣ አብዛኞቹ አርሶአደሮች ግን ለህይወታችን ዋስትና የሚሰጠን ስለማይኖር ወደ አካባቢው ለመመለስ ፈቃደኞች …
በጅማ በአሰቃቂ ሁኔታ እናትና ልጅን የገደለው ወታደር በምን ሁኔታ ላይ እንዳለ አልታወቀም
ኀዳር ፭(አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ተሰድቤአለሁ በሚል ምክንያት አንድ አዛውንትን እስከ ልጃቸው በሌሊት የገደለው ወታደር ግድያውን ከፈጸመ በሁዋላ ወደ መካለከያ ካምፕ ቢያመራም ህግ ፊት ይቀርብ አይቀርብ የታወቀ ነገር የለም። ወጣት ዮናስ በ16 ጥይቶች ተባስስቶ መገደሉን ከቅርብ ሰዎች የተገኘው መረጃ የሚያመልክት ሲሆን ወ/ሮ መንበረም ከ10 ያላነሰ ቦታ ላይ ተደብድበው ተገድለዋል። የከተማው ህዝብ ወደ አደባባይ …