ፑንትላንድን የመታዉ ማዕበል
የሶማሊያዋ ራስ ገዝ ግዛት ፑንትላንድን በሳምንቱ መጨረሻ በመታዉ ኃይለኛ ማዕበል የሞቱት ሰዎች ቁጥር 300 መቶ ሊደርስ ይችላል ሲል መንግስት ስጋቱን እየገለጸ ነዉ። መንግስት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የደነገገ ሲሆን በማዕበሉ ለተጎዱ አካባቢዎችም ዓለም ዓቀፍ ርዳታ ጠይቋል።
የሶማሊያዋ ራስ ገዝ ግዛት ፑንትላንድን በሳምንቱ መጨረሻ በመታዉ ኃይለኛ ማዕበል የሞቱት ሰዎች ቁጥር 300 መቶ ሊደርስ ይችላል ሲል መንግስት ስጋቱን እየገለጸ ነዉ። መንግስት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የደነገገ ሲሆን በማዕበሉ ለተጎዱ አካባቢዎችም ዓለም ዓቀፍ ርዳታ ጠይቋል።
ከአፍሪቃ ማላዊ ና ኢትዮጵያ ን እንዲሁም ከደቡብ እስያ ማሌዥያና ፊሊፒንስን በመሳሰሉ ሃገራት የወሊድ መቆጣጠሪያ አገልግሎት ከቀድሞው በተሻለ ደረጃ ላይ ይገኛል ።
SHARE:Urgent call to all Ethiopian & Friends of Ethiopian in Addis Ababa to protest unlawfully killings and inhuman treatment of Ethiopian immigrants by police and security force of Saudi Arabia. Over 20 people were killed and number of our sister …
እንደ ኢህአዴግ ፈሪ ፓርቲ ከወደየት አለ? ጌታቸው ሺፈራው
beዚህ ጽሁፍ መግለጽ የምፈለግው የኢህአዴግን መጠነሰፊ ፍርሃት ያሳያሉ ያልኳቸውንጥቂት ምሳሌዎች ነው፡፡ እስካሁን እንደ ኢህአዴግ ፈሪ ፓርቲ አጋጥሞኝ ስለማያውቅም እንደ ኢህአዴግ ፈሪ ድርጅት ከወደየት አለ? ብሎ መጠየቁ አግባብ መስሎ ታይቶኛል፡፡ ፈሪው ድርጅት ‹‹የለም ከእኛ በላይ ፈሪ ድርጅቶች እዚህ እዚህ…አገር ይገኛሉ›› የማለት መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ እንዲያውም እስካሁን የነበረበትን ከፍርሃት የመነጨ ድብቅነት በጥቂቱም ቢሆን እንደቀነሰ እንረዳለታለን፡፡ በድፍኑ ‹‹አይ እኛ ፈርተን አናውቅም!›› ቢል ግን ያው የተለመደ ስለሆነ የሚያምነው አያገኝም፡፡ ደግሞስ እየፈሩ ‹‹አልፈራንም›› ማለት ምን ማለት ነው? ‹‹አልፈራንምንስ ምን አመጣው? ኢህአዴግ የሚፈራውን ከመዘርዘር ይልቅ ራሱ የማይፈራቸው ነገሮች ካሉ ቢነግረን የተሻለ ነበር፡፡ እኔ ግን ከሚፈሯቸው ነገሮች መካከል በጣም ጥቂቶቹን ብቻ በመጥቀስ የፍርሃቱን መጠን ለማሰየት እሞክራለሁ፡፡ ህገ መንግስቱን ለብሄር ብሄረሰቦች መብት መከታ ነው የሚባለው የወቅቱ ህገ መንግስት የአቶ መለስና ለንጮ ለታ የፖለቲካ ማህተም ያረፈበት እንደሆነ ይነገርለታል፡፡ ይህ ህገ መንግስት እንደ አንቀጽ 39ን ያሉትን ጨምሮ ስለ የመሬት ፖሊሲ፣ አንድነትና ሌሎች ጉዳዮች ያለው ህጸጽ እንዳለ ሆኖ ከነ ድክመቱም ቢሆን ቢተገበር አሁን ካለንበት ብልሹ ፖለቲካ የተሻለ ስርዓት ሊመሰርት እንደሚችል ይታመንበታል፡፡ በተለይ ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ፣ የአመለካከትና ሌሎች ዴሞክራሲያዊና ሰብአዊ መብቶችን ከዳር ዳር ከማጨቅ ውጭ ተግባራዊ ሲሆኑ አይታዩም፡፡

ከተግባራዊነቱ ይልቅ ለይስሙላህነቱ እንዲውል ተደርጓል፡፡ ይህም የሆነው ህገ መንግስቱ ላይ የሰፈሩት አብዛኛዎቹ መርሆች ተግባራዊ ቢሆኑ የገዥውን ፓርቲ ስልጣን የሚያሳጡ መስለው ስለሚሰሙት ነው፡፡ እናም ኢህአዴግ ‹‹ባለ ራዕዩ›› መሪ በበላይነት መርጠው ያጸደቁትን ህገ መንግስቱንም ቢሆን ለመተግበር ይፈራዋል፡፡ ስለሆነም በተቻለ መጠን ህገ መንግስቱ ላይ ያሉት መርሆች ተግባራዊ የማይሆኑበትን አጋጣሚ ሁሉ ይጠቀማል፡፡ ለዚህ አተገባበሩ የዳኝነት ሰርዓቱን ጨምሮ በጉዳዩ ተያያዥነት ያላቸውን አካላት የገዥውን ፖሊሲ የሚያቀነቅኑ እንዲሆኑ ጥሯል፡፡ ይህ ግን በቂ አልነበረም፡፡ በተለይ በ1997 በኋላ ኢህአዴግ እንደ አንዳች ነገር የሚፈራቸው ወሳኝ የህገ መንግስቱ መርሆች በጸረ ህገ መንግስት አዋጆች ታጥረው ተቀምጠዋል፡፡ የጸረ ሽብር፣ የሶቪክ ማህበራት፣ የፓርቲዎች የስነ ምግባር፣ የሚዲያ…..አዋጆች ህዝብን ብቻ ሳይሆን ህገ መንግስቱን አሽገው ለህዝብ እንዳይቆም ያደረጉ አዋጆች ናቸው፡፡ ተወዳዳሪ ፓርቲን ኢህአዴግ መድብለ ፓርቲን መርህን እቀበላለሁ እያለ የጠንካራ ፓርቲዎችን መኖር ግን በእጅጉ ይፈራል፡፡ ለዚህም ሲባል ከፓርቲዎች ጋር አብሮ ከመስራት ይልቅ ተገንጣዮችን በመፈልፈል የኢትዮጵያን ፓርቲዎች ከ80 በላይ አድርሷቸዋል፡፡ በእርግጥ ይህ የጠንካራ ፓርቲ ‹‹ፎብያ›› የጀመረው ህገ መንግስቱ ላይ ‹‹የበድብለ ፓርቲ›› በስምም ቢሆን ከተፈቀደ በኋላ አይደለም፡፡ ህወሓት በዱር እያለም ፓርቲዎችን ከዚህም በላይ ይፈራቸው እንደነበር ታሪኩ ያስረዳል፡፡ መጀመሪያ አካባቢ ኢህአፓ ከህወሓት ጎን ለጎን አብሮ ይንቀሳቀስ ነበር፡፡ ይሁንና የኢህአፓ ህብረ ብሄርነት ህወሓት የቆመለትን የመገንጠል ፖሊሲ አደጋ ላይ በመጣሉ ህወሓት ‹‹ከትግራይ መሬት ውጡልን ይህ የትግራይ ህዝብ መሬት ነው›› ብሎ አባረረው፡፡ የትግራይ አርነት ግንባርን (TLF)ንም የትግራይ ህዝብ ከአንድ በላይ ፖለቲካ ፓርቲ መሸከም አይችልም ብሎ አጥፍቶታል፡፡ እንዲያውም የትግራይ አርነት ግንባር አባላት ከህወሓት ጋር ለመደራደር ከተስማሙ በኋላ በተኙበት በህወሓት መጨፍጨፋቸውንና ይህን ዘግናኝ የጭፍጨፋ ሂደት አንዳንድ የህወሓት አባላት ለህዝብ ይፋ አድርገዋል፡፡ እንደራደር ብሎ የመጡትን ፖለቲከኞች መጨፍጨፍ መቼም ጀግንነት፣ ድፍረት ሊሆን አይችል፡፡ ኢህአዴግም እየተጠቀመበት የሚገኘው ይህን የህወሓትን የፍርሃት ልምድ ነው፡፡ ገና ስልጣን እንደያዘ ጠንካራ ከሚባሉት ኦነግ፣ ኦብነግና ሌሎች የብሄር ድርጅቶችን ጋር ከጥርጣሬም አልፎ አለመግባባት ውስጥ ገባ፡፡ በምትካቸው ደግሞ እንደ ኦህዴድ፣ ሶዴፓ ያሉ ደካማ ፓርቲዎችን ተገን ማድረግ ጀመረ፡፡ ለጠንካራ ፓርቲዎች በርካታ ደካማ ተገን ፓርቲዎችን የሚፈጥረው ኢህአዴግ ከመቼውም በላይ ስለፈራ 80 ያህል ደካማ ፓርቲዎች አገሪቱን ተፍልፍለዋል፡፡ ኢህአዴግ ተቃዋሚዎቹን ብቻ ሳይሆን አብረውት እየሰሩ የሚገኙትንም ቢሆን ‹‹በአጋር ፓርቲነት›› ስም ብቻ ፖለቲካውን ከእርቀት እንዲመለከቱ እያደረገ ነው፡፡ በአገሪቱ የረባ የፖለቲካ ተሳትፎ የሌላቸውን እነዚህ ፓርቲዎች ያፈነግጡብኛልበማለትም የህወሓት/ኢህአዴግን አማካሪዎች በተቆጣጠሪነት ከማስቀመጥ ጀምሮ መረዎቻቸውን በተለያየ መንገድ ማግለል የተለመደ የፖለቲካው እቃ እቃ ጨዋታ ሆኗል፡፡ የሶማሊ፣ ጋንቤላና ቤንሻንጉልን ህዝቦች ስም ‹‹አጋር›› የሆኑት እነዚህ ፓርቲዎች መሪዎቻቸው ከአዲስ አበባ በተላከ ትዕዛዝ በተደጋጋሚ ገለል የሚደረጉት ያፈነግጡብኛል ብሎ ስለሚፈራቸው ነው፡፡ የአገር አንድነትን ኢህአዴግ የአንድነት ፍርሃት የሚጀምረው እስካሁንም ድረስ የትግራይን ህዝብ ነጻ ለማውጣት የቆምኩ ነኝ የሚለውን ስሙን ለመቀየር ከሚፈራው ህወሓት ነው፡፡ የህወሓት የተገንጣይ ስምም ቢሆን እስካሁን የማይቀየረው አንድነት ይቅርና ፌደራሊዝሙም ላይ ፍራቻ ሳላለው ይመስላል፡፡ ከዚህ ውጭ የትኛውም አንድነትን የሚወክል ወይንም የሚያንጸባርቅ ነገር ለህወሓት/ኢሀአዴግ ያስበረግገዋል፡፡ ልክ እንደ ህወሓት/ ኢህአዴግ ሁሉ የኢትዮጵያ አንድነትን የሚጠላው ሻዕቢያ መጀመሪያ የተረባረበው የአንድነት ዋነኛው መገለጫ የሆነው ሰንደቅ አላማው ላይ ነበር፡፡ ሻዕቢያ ባልታጣ መቋጠሪያ የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ ዋነኛው የዱቄት መቋጠሪያው አድርጎ ተጠቅሞበታል፡፡ በለስ (ቁልቋል) ሳይቀር የሚሸመጥጡት በኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ እንደነበር ይነገራል፡፡ ህወሓት በተለይ መጀመሪያ አካባቢ ትጥቅም ሆነ ስንቅ (ዱቄት) ይቀበል የነበረው ከሻዕቢያ ነውና ከሻዕቢያ የተለየ ተግባር ሊፈጽም እንደማይችል መገመት ቀላል ነው፡፡ አቶ መለስ ስልጣን ከያዙ በኋላ ስንደቅ አላማውን ጨርቅ ያሉት ከሻዕቢያ በወረሱት የአንድነት ፍርሃት መሆኑን እንረዳለን፡፡ ሁለቱም ድርጅቶች ይህ በደል የፈጸሙት ከሰንደቅ አላማው በስተጀርባ ያለውን አንድነት በእጅጉ ስለሚፈሩት ነው፡፡ ኢህአዴግ ለዚህ የረዥም ጊዜ ፍርሃት መሃል ላይ ያስቀመጠው ኮከብም ፍርሃቱን ሊያስወግድለት አይቻለም፡፡ አቶ መለስ ከመሞታቸው ከወራት ቀደም ብለው ሰንደቅ አላማውን የዘቀዘቁት አሁን ባለው ቅርጹም ቢሆን ስለሚፈሩት ይመስለኛል፡፡ ዛሬም ቢሆን ኢህአዴግ ራሱ መጥኖ በጠራው ጉዳይ ካልሆነ በስተቀርሰ ህዝብ በስፋት ባለኮከቡን ሰንደቅ አላማ በክብር ሲያነሳም ብርክ ይይዘዋል፡፡ አማራጭ ሚዲያን ኢትዮጵያ በሚዲያ ወደኋላ ከቀሩት አገራት መካከል የመጀመሪያዋ ናት፡፡ ለ90 ሚሊዮን ህዝብ ያለን አንድ ፕሮፖጋንዳ የሚሰራጭበት ቴሊቪዝን ጣቢያ ብቻ ነው፡፡ በአንጻሩ 6 ሚሊዮን ህዝብ ያላት ላኦስ፣ ሁለት ሚሊዮን ህዝብ ያላት ጃማይካ፣ አንድ ሚሊዮን ህዝብ ያላት ትሪንዳድና ቴቪጎ እያንዳንዳቸው የግልን ጨምሮ ባለ ሰባት ጣቢያዎች ናቸው፡፡ 400 ሺህ ህዝብ ያላት ማልታ 8፣ 36 ሺህ ህዝብ ያላት ሞናኮ 5 ጣቢያዎች ለህዝባቸው አማራጭ መረጃ ያስተላልፋሉ፡፡ ከኢትዮጵያ ጋር የሚነጻጸር ህዝብ ያላቸው አገራት ደግሞ በርካታ ጣቢያዎች ባለቤቶች ሆነዋል፡፡ ለአብነት ያህል ከኢትዮጵያ ጋር በአባይ በኩል የምትተሳሰረው ግብጽ 98 ያህል ጣቢያዎች ባለቤት ነች፡፡ ከኢትዮጵያ ህዝብ ከግማሽ ያነሰ ህዝብ ያላት ጎረቤት ኬንያ እንዲሁም 34 ሚሊዮን ህዝብ ያላት ዩጋንዳ እያንዳንዳቸው 8 ጣቢያ ያላቸው ሲሆን አብዛኛዎቹ የግል ሚዲያዎች ናቸው፡፡ ኢትዮጵያ ሚዲያ ይህን ያህል ከአገሪቱ ታሪክም ይሁን ህዝብ ጋር የሚቃረን የሆነው ኢህአዴግ በእጅጉ ስለሚፈራው ነው፡፡ ሚዲያ ህዝብን ያነቃል፣ ሙስናንና ሚስጥርን ያጋልጣል፣ አንድነትን ያጠናክራል፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ሲቪክ ማህበራት አማራጭ ሀሰብ ህዝብ ዘንድ እንዲደርስ ያደርጋል፡፡ ይህ የነቃ ማህበረሰብ የሚፈጥረው ሚዲያ ደግሞ ለአንድ ፓርቲና ግለሰብ የበላይነት ጸር ነው፡፡ ለህዝብ ልዓላዊነት እንጅ ለ‹‹አውራ ፓርቲ›› አያመችም፡፡ ስለሆነም ኢህአዴግን ከምንም በላይ ያስፈራዋል፡፡ ለዚህም ነው 90 ሚሊዮን ህዝብ አሰልች ፕሮፖጋንዳ በሚነዙ የመንግስት (ፓርቲ ሚዲያዎች) ብቻ የተወሰነው፡፡ በፍርሃቱ ምክንያትም የህትመት ሚዲያው አሳሩን ሊበላ የግድ ሆኖበታል፡፡ ህገ መንግስቱም ሆነ አዋጁ አማራጭ (የግል) ሚዲያን አይከለክልም፡፡ እንዲያውም በአዋጁ የብሮድካስት ሚዲያም በግል እንደሚፈቀድ ሁሉ አስቀምጧል፡፡ ይህ በሆነበት ግን አንድም የግል ቴሊቪዥን ጣቢያ የለንም፡፡ ሚዲያ ህዝብን እንደሚያነቃ የሚያውቀውና ይህንን የሚፈራው ኢህአዴግ ኢሳትን ጨምሮ በርካታ ሚዲያዎችን ለመዝጋት አገሪቱን ከፍተኛ ገንዘብ በማባከን ላይ ነው፡፡ በአንድ ወቅት አልጀዚራም ጭምር የታገደበት አጋጣሚ ተፈጥሯል፡፡ አማራጭ ሀሳብ የሚተላለፍበትን ሚዲያ እንዲህ የሚጠላው ‹‹አብዮታዊ›› ፓርቲ ፌስ ቡክን እንኳ ንቆ አልተወውም፡፡ በርካታ ፌስ ቡክ ላይ የሚጽፉ አካላት ጽሁፋቸው አገር ውስጥ እንዳነበብ ይደረጋል፡፡ እስክንድር ከታሰረባቸው ምክንያቶች ቀዳሚው ፌስ ቡክ ላይ በሚጽፋቸው ትንታኔዎቹ ነው፡፡ አሁን ደግሞ ልክ የቻይና እና የኢራን አምባገነን ፓርቲዎች በአንድ ወቅት እንዳደረጉት ፌስ ቡክን ሊዘጋ እንደሚችል እየተነገረ ነው፡፡ ሰላማዊ ሰልፍና የአደባባይ ሰልፍ በኢህአዴግ ዘንድ የሚፈራ ብቻ ሳይሆን የሚጠላም ተግባር ለመሆን ደርሷል፡፡ ታይቶ ከጠፋው የ1997 ምርጫ በኋላ ለአለፉት 8 አመታት ከድጋፍ ሰልፍ ውጭ የህዝብ ሮሮ የሚሰማባቸው ሰላማዊ ሰልፎች በግልጽም ሆነ በተዘዋዋሪ ታግደው ቆይተዋል፡፡ ባለፉት ስድስትና ሰባት ወራት የሰላማዊ ሰልፍ መብት እንደገና ተመልሶ የነበር ቢሆንም አሁን ግን እንደገና ታግዷል፡፡ ኢህአዴግ ሰላማዊ ሰልፍን ብቻ ሳይሆን አደባባዮችንና ጎዳናዎችን ኢትዮጵያዊ ታህሪር እንዳይሆኑ አብዛቶ ፈርቷል፡፡ ለአብነት ያህል 97ት ላይ ክፉኛ የደነገጠበት መስቀል አደባባይ ለድጋፍ ሰልፍ እንጅ ለሰላማዊ ሰልፍ ክልክል ሆኗል፡፡ ከዚህ አለፍ ሲልም ኢትዮጵያውያን ኳስ እንዳያዩበት ሁሉ እየተደረገ ነው፡፡ የናይጀሪያንና የኢትዮጵያን ጨዋታ መስቀል አደባባይ ላይ ለመመልከት ሰንደቅ አላማ ለብሰው የጎረፉ ኢትዮጵያውያን ደጋፊዎች ተደብድበው ተመልሰዋል፡፡ ሀይማኖት፣ ግለሰባዊነት፣ ነጻ ተቋም… ብቻ ኢህአዴግ የማያስፈራውን ነገር ቢናገር ይሻል ነበር፡፡ በእርግጥ አቶ ሀይለማሪያም ደሳለኝ ‹‹አንፈራም!ፓርቲው እንደማይፈራ ታሪኩ ይናገራል፡፡›› ብለውናል፡፡ እዚህ ላይ አቶ ሃይለማሪያም እንደተለመደው ተሳስተው ይመስለኛል፡፡ ምክንያቱም እሳቸው አይፈራም ብለው ለመከራከር የፈለጉት አርሳቸው ያልነበሩበትን የኢህአዴግን የጠብመንጃ ታሪክ ነው፡፡ መሳሪያ ያነሳ ሁሉ ግን ደፋርም ጀግናም አይደለም፡፡ እንዲያውም ፈሪ ዱላው፣ ጠብ መንጃው፣ መሳሪያው፣ መሰሪነቱም ከልክ በላይ በርካታዎች ናቸው፡፡ ከእነ ተረቱም ቢሆን የፈሪ ዱላ ይባላል እኮ፡፡ ፈሪ ይህን ያህል ጉዳት ሊያደርስበት የማይችለውን አካል ሁሉ ያለ አቅሙ ይደበድባል፡፡ በራሱ አይተማመንምና እንደገና እንዳያስፈራራው ያወድመዋል፡፡ አይደለም አንዳች የሚንቀሳቀስን አካል ይቅርና ጥላውን እንኳ አያምንም፡፡ የመዋጋት፤ የማሰር፣ የመፈረጅ ታሪክ ከዚሁ ከፈሪነት ባህሪው የመነጩ ናቸው፡፡ በአንጻሩ ደፋር ለመርህ ይታገላል፡፡ ለአቆመው ህግና ስርዓት ራሱንም የሚሰዋ ታማኝ ነው፡፡ ያቆመውን ስርዓት፣ አብሮት የሚኖረውን አካልና ራሱን ያምናል፡፡ በህዝብና በአገሩ ስለሚያምን፣ በራሱ ስለሚተማመን ህዝብን በፍቅር ያቀርባል፣ ተቀናቃኙን በፍቅር ይስባል እንጅ በግድ ወደኔ ካልመጣህ ብሎ ለማጥፋት ከሆነ አንዳች ነገር ፈርቷል ማለት ነው፡፡ ያኔ ፈርቷል፣ ተፍረክርኳል፣……ይባላል፡፡ ልክ እንደ ኢህአዴግ!
ወገናችንን በጥይት ሲደፉት በራሱ ላይ አረንጓዴ፣ ቢጫና ቀይ ባንድራችንን ጠምጥመውበታል[1]። ጭካኔ በተሞለበት መንገድ የተገደለው ይህ ኢትዮጵያዊ አስከሬኑም በሰላም አላረፈም። በአካሉ ላይ ያረፈውን ጨርቅ በሴንጢ እየቆራረጡ በሰብአዊ ፍጡር ላይ ሊደረግ የማይገባውን ሁሉ አደረጉበት። ድርጊቱ ናዚዎች በኦሽዌትስ ይፈጽሙት የነበረውን አሰቃቂ ግፍ ያስታውሰናል። በ21ኛው ዘመን እንዲህ አይነቱ ክስተት ይደገማል ብሎ የሚያስብ የለም። እነሆ ሳውዲ አረቢያ በኢትዮጵያውያን ላይ እየፈጸመችው […]
ህዳር ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ካለፉት 5 ቀናት ጀምሮ በሳውዲ አረብያ በተለያዩ የማጎሪያ ጣቢያዎች ታስረው በሚገኙ ኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሰ ያለው ግፍ እንደቀጠለ ሲሆን፣ በዛሬው እለት 2 ሰዎች መሞታቸው ታውቋል። ኢትዮጵያውያኑ እንደሚናገሩት ሰዎቹ የተገደሉት ባልና ሚስቶችን ለመለያየት በተደረገ ሙከራ ላይ በተፈጠረ ግርግር ነው። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም ከሳዑዲው አቻቸው ልዑል ሳውድ አል …
ህዳር ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አልሸባብ የተባለው አሸባሪ ቡድን እና በኤርትራ መንግስት እገዛ የሚንቀሳቀሱ የሽብር ቡድኖች በኢትዮጽያ ውስጥ የተለያዩ ስፍራዎች የሽብር ጥቃት ለመፈፀም እየተዘጋጁ መሆናቸውን የሚያሳይ አስተማማኝ መረጃ ያለው መሆኑን የብሄራዊ ደህንነትና መረጃ አገልግሎትና የፌደራል ፖሊስ የፀረ ሽብር ግብረ ሃይል ጥቅምት 27 ቀን 2006 ዓ.ም ካስታወቁ በኃላ በአዲስአበባ በመንግስት በግል ተቋማት ከወትሮው የተለየ ፍተሻ …
(ተመስገንደሳለኝ)
…ኢሠፓ መራሹ መንግስት በኢህአዴግ ከተተካ ጥቂት ወራት ቢያልፈውም፣ የተራዘመው የእርስ በእርስ ጦርነት ያልደረሰባቸው በደቡብ ኢትዮጵያ የሚገኙ አንዳንድ ከተሞችን ገና በቅጡ አልተቆጣጠራቸውም፤ በአናቱም በኢሠፓ መንግስት ሽንፈት ሳቢያ እንዲበተን ከተገደደው የ ገሪቱ መደበኛ ወታደር፣ አብዛኛው ከእነ ትጥቁ የትውልድ መንደሩንና ቤተሰቡን መቀላቀሉ በ ገሪቱ ላይ ከባድ ፍርሃት አንብሯል፤ በሰላም ወጥቶ ለመመለስ እርግጠኛ መሆን የማይቻልበት ከበባዊ አየርም አስፍኗል፡፡ በበርካታ ቦታዎች ተጠንተውና ታቅደው የሚፈፀሙ ወን ሎችም፣ ከአምስት እስከ አስራ አምስት በሚደርሱ ወታደሮች የተደራጁ ልዩ ልዩ ህገ-ወጥ ቡድኖች በየማዕዘኑ እያቆጠቆጡ መሆኑን አመላክቷል፡፡
ነብዩ ሲራክ
የማለዳ ወግ
በሪያድ መንፉሃ በተከሰተው ሁከት ግራም ነፈሰ ቀኝ ተጎጅዎች እኛ ነን! እንኳንስ ሰው ተደብድቦ ፣ ሞቶባቸው፣ እንኳንስ መኪና ተሰብሮባቸው እንዲያውም እንዲው ናቸው። ከማለዳ እስከ ሌሊት የዘለቀውን ሁከት መቆጣጠር ይቻል ዘንድ ገና ሲ መር አቅጣጫውን አይተው የመንግስት ተወካዮችን የመከሩ በርካታ ነበሩ።
News, Ask the Doctor, Agriculture and Business
ታላቅ ሀገራዊ የተቃውሞ ጥሪ!
ከወገኖቻችን ጐን በመቆም ብሄራዊ ክብራችንን እናስመልሳለን
ሰሞኑን የሳውዲ አረቢያ መንግሥት በኢትዮጵያዊያን ላይ እየፈፀመ ያለውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት በመቃወም ሰማያዊ ፓርቲ ታላቅ የተቃውሞ ጥሪ አስተላልፏል፡፡
በመሆኑም በዜጎቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን ኢሰብዓዊ ድርጊት ለማስቆምና የዜጐችን ህይወት ለመታደግ እንዲሁም ዜጐቻችን በአፋጣኝ ወደ ሀገራቸው የሚመለሱበትን ሁኔታ መንግሥት እንዲያመቻች እና በተጨማሪም በዜጐቻችን ላይ ለደረሰው የአካል መጉደል፣ እንግልት፣ ድብደባ፣ አስገድዶ መድፈርና የህይወት መጥፋት ኃላፊነቱን የሚወስዱ አካላት ተጠያቂ እንዲሆኑ፤ ለተጐዱ ወገኖቻችንና ቤተሰቦቻቸውም አስፈላጊው ካሳ እንዲደረግላቸው ፓርቲያችን አበክሮ እያሳሰበ፤ የብሄራዊ ክብርና የወገኖች ስቃይ የሚያሳስባቸው አካላት በሙሉ በዚህ ታላቅ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ላይ እንዲሳተፉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
የተቃውሞ እንቅስቃሴ አፈፃፀም፡-
1. በዜጐቻችን ላይ የአካል መጉደል፣ እንግልት፣ ድብደባ፣ አስገድዶ መድፈርና የህይወት መጥፋት ያደረሰው የሳውዲ አረቢያ መንግሥት ኢምባሲ በሚገኝበት ቦታ አርብ ከረፋዱ 5፡30 ሰዓት ጀምሮ የሚደረግ የተቃውሞ ሰልፍ፣
2. ከአርብ ጠዋት ጀምሮ እስከ እሁድ ማታ ድረስ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሀዘን ልብስ (ጥቁር ልብስ) በመልበስ በግፍ ለሞቱና ለተንገላቱ ወገኖቻችን ሀዘናችንን መግለፅ፣
3. የእምነት ተቋማት አርብ በመስጊድ በጁምአ ሥነ ሥርዓት ላይ እና ቅዳሜና እሁድ በአብያተ ክርስቲያናት የፀሎት ሥነ ሥርዓቶች ላይ ወገኖቻችንን በፀሎት እንዲታሰቡ፣
4. ቅዳሜ በሚደረገው የኢትዮጵያና የናይጄሪያ የእግር ኳስ ጨዋታ ላይ ተጫዋቾቻችን ጥቁር ሪቫን በክንዶቻቸው ላይ አጥልቀው እንዲጫወቱ፣ እንዲሁም መላው ደጋፊ ጥቁር ጨርቆችን በመያዝ ወይም ልብስ በመልበስ ሀዘኑንና ቁጭቱን እንዲገልፅ፣
በፓርቲው የተወሰነ በመሆኑ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች፣ ሲቪክ ተቋማት፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች፣ ፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ዓለም አቅፍ ማኅበረሰቡ በአጠቃላይ መላው ኢትዮጵያዊና የኢትዮጵያ ወዳጆች በጠራነው የተቃውሞ ሰልፍና እንቅስቃሴዎች ላይ በመገኘት ከግፉአን ወገኖቻችን ጐን መቆሙን እንዲያረጋግጥ በአፅንኦት እንጠይቃለን፡፡
የወገኖቻችን ሰቆቃ እስኪያበቃ በፅናት እንታገላለን!!!
ከዛሬ 75 ዓመት በፊት ጀርመን ውስጥ በአይሁዶች ላይ የተፈፀመው ግፍ ሰሞኑን እዚህ ጀርመን በልዩ ልዩ ዝግጅቶች እየታሰበ ነው ።
በጎርጎሮሳውያኑ ህዳር 9 ለህዳር 10 አጥቢያ 1938 ዓም በመላ ጀርመን የሚገኙ የይሁዲዎች ሙክራቦች ፣ ሱቆችና መኖሪያ ቤቶች በናዚዎች ትዕዛዝ እንዲወድሙ ተደርጓል ። ይሁዲዎችም ግፍ ተፈጽሞባቸዋል ።
አሁንም እዚያዉ ሳዑዲ አረቢያ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን በተለያየ ችግር እየተሰቃዩ መሆናቸዉን እያስታወቁም ነዉ።በስልክ ያነጋገርናቸዉ ኢትዮጵያዉያን እንደሚሉት ወደ ሐገራቸዉ ለመግባት ቢፈልጉም ከሳዑዲ አረቢያ ፀጥታ አስከባሪዎች የሚደርስባቸዉን ድብደባና በደል ፍራቻ በየቤታቸዉ ለመሸሸግ ተገድደዋል።
ከሁለት ዓመታት በፊት በተሠራ ጥናት መሠረት ኢትዮጵያ ዉስጥ በመዉለድ የእድሜ ክልል ከሚገኙ ሴቶች 27 በመቶዉ የወሊድ መቆጣጠሪያ ስልቶችን ይጠቀማሉ። የሀገሪቱ የስነህዝብ ፖሊሲ አንዲት እናት በአማካኝ አራት ልጆች ብትወልድ የሚል ግብ ነዉ ያለዉ።
ኢትዮጵያና ኤርትራ የሚዋሰኑበት ከ 1000 ኬሎ ሜትር የድንበር ክልል ያላቸዉ ሲሆን፤ በአሁኑ ወቅት በርካታ ኤርትራዉያን ሀገራቸዉን እየጣሉ ይሰደዳሉ። በሰሜን ምዕራብ ትግራይ አቅጣጫ ብቻ በቀን ከ 50 በላይ ኤርትራዉያን ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ እየገቡ እንደሆነም ተነግሮአል።
የዕለቱ ዜና
ክንፉ አሰፋ
ወገናችንን በጥይት ሲደፉት በራሱ ላይ አረንጓዴ፣ ቢጫና ቀይ ባንድራችንን ጠምጥመውበታል። ጭካኔ በተሞለበት መንገድ የተገደለው ይህ ኢትዮጵያዊ አስከሬኑም በሰላም አላረፈም። በአካሉ ላይ ያረፈውን ጨርቅ በሴንጢ እየቆራረጡ በሰብአዊ ፍጡር ላይ ሊደረግ የማይገባውን ሁሉ አደረጉበት። ድርጊቱ ናዚዎች በኦሽዌትስ ይፈጽሙት የነበረውን አሰቃቂ ግፍ ያስታውሰናል። በ21ኛው ዘመን እንዲህ አይነቱ ክስተት ይደገማል ብሎ የሚያስብ የለም። እነሆ ሳውዲ አረቢያ በኢትዮጵያውያን ላይ እየፈጸመችው ነው። በስውር ሳይሆን በግልጽ። እንደ ኦሽዊትስ በታጠረ የማጎርያ ካምፕ ሳይሆን በአደባባይ።
እንቅስቃሴውን የጀመሩት ስዊድናዊ ጠበቃ ከኢትዮጵያውና ጋር ውይይት አደረጉ
Ethiopia Zare (ማክሰኞ ኅዳር 3 ቀን 2006 ዓ.ም. Nov. 12, 2013)፦ ባለፈው ቅዳሜ ጥቅምት 23 ቀን 2006 ዓ.ም. (ኖቬምበር 2 ቀን 2013) የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ መድረክ በስዊድን የወያኔን መንግሥት በዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት ለማቅረብ የተጀመረውን ክስ መነሻ በማድረግ የክሱን ሂደት ከሚመሩት ከስዊድናዊው ጠበቃ ከስቴላ ያርዴ እና ከሌሎች እንግዶች ጋር በርካታ ኢትዮጵያውያን በተገኙበት ወይይት አደረገ።

ጥቁር ሽብር ወያኔ ቁምጣ የለበሰ ደርግ ነው ! እመኑኝ በየትኛውም የታሪክ ገጠመኝ የሳወዲ መንግስት የዚህ አይነት ድፍረት ያውም በአደባባይ በዜጎቻችን ላይ አሳይቶ አያውቅም ፡፡ ነገሮችን ተመልሰን ከተመለከትን ይህ ግፍና በደል የእኛው ባለስልጣናት ሳውዲወችን አደፋፍረው ያስፈፀሙት ጉዳይ ነው፡፡
ይህም ሁለት ፖለቲካዊ ምክንያቶች አሉት ፡፡ የመጀመሪያው ፡- የወያኔ ባለስልጣናት በሳውዲ የሚኖሩ ኢትዮጲያዊያንን ቦንድ እንዲገዙ በሰበሰቡበት ወቅት ተደጋጋሚ ተቃውሞ ደርሶባቸው እንደነበር የሚታወቅ ነው ፡፡ ይህም ድምፃችን ይሰማ ባሉ ሙስሊሞች ላይ በሃገር ውስጥ የሚደርሰው በደል ይቁም ለጥያቂያቸውም አጥጋቢ መልስ ይሰጥ በሚል ምክንያት ነበር ፡፡ ቂመኛው መንግስታችን ይህን እንደበደል በመቁጠር በእጅ አዙር ዜጎቻችንን እያስጋዘ ይገኛል ፡፡ ለዚህ በደሉ ሽፋን እንዲሆነው በቅርቡ በተለያዩ ሚዲያወቹ አረብ አገራት ላይ ያተኮሩ ወሬወችን ሲነዛ ቆይቷል ፡፡ የሳዲ መንግስት በሰጠው የጊዤ ገደብ የሚያስፈልጋቸውን መረጃ ሊጠይቁ ወደ ‹‹ኢትዮጲያ ኤምባሲ ›› የሄዱ ሚስኪን ለፍቶ አደሮች ቦንድ ግዙ እየተባሉ ሲመላለሱ የጊዜ ገደቡ አልቆላቸዋል ፡፡ ሁለተኛው ምክንያቱ ፡- አገር ውስጥ ያለው ‹‹የድምፃችን ይሰማ ›› እንቅስቃሴ አረብ አገራት ባሉ ኢትዮጲያዊያን የገንዘብ ድጋፍ ያገኛል በሚል ፍርሃት ነው ፡፡ፍርሃት ብቻ ሳይሆን በግልፅም በወቲቪ (የ ወያኔ ቴሌቪዥን ) በተደጋጋሚ ተናግሮታል ፡፡ በመሆኑም ይህን የራሱን ስጋት ለማስታገስና መመለስ ያልቻለውን የማይችለውንም የመብት ጥያቄ ለማፈን የገቢ ምንጭ ናቸው ያላቸውን በአረብ አገር የሚኖሩ ኢትዮጲያዊያንን ሰላም ደህንነትና ሂወት ጭምር በእጅ አዙር እየነጠቀ ነው ፡፡ (እዚህ ላይ ሳውዲወች የቴውድሮስ አድሃኖም ስምምነት አለበት ማለታቸውን እንዳንዘነጋ) አሁን ከወደኪዌት እንደምንሰማው ደግሞ ከስራቸው በገፍ የተፈናቀሉ ኢትዮጲያዊያን ሰልፍ እንወጣለን አልያም ስራ ይሰጠን እያሉ ነው ፡፡ እኒህ ኢትዮጲያዊያን ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ከስራቸው የተፈናቀሉ ናቸው ፡፡
ወያኔ እና የወያኔ ጭፍን ደጋፊወች ማወቅ ያለባችሁ ጉዳይ ድህነት ትግልን ያባብሳል እንጅ አያዳፍንም ‹‹አፈር እየቃምን ድንጋይ እየቆረጠምን ደርግን ጣልነው ›› እንደምትሉት ይህም ህዝብ ሆነ ብላችሁ የምትጭኑበትን ድህነትና እንግልት ተቋቁሞ ድል ማድረጉ የማይቀር ነው ፡፡ ታውቁታላችሁ እናውቀዋለን ! ወያኔ ማለት ቁምጣ ለብሶ የመጣ ደርግ ነው ፡፡ ደርግ ቀይ ሽብር ብሎ ህዝብ ፈጀ ፤ ወያኔ በተዳፈነና የህዝብን መብት ፣ ነፃነትና ሂወት ጭምር በጋረደ ጨለማ አገዛዙ ጥቁር ሽብሩን አወጀ፡፡ እነሆ አገራችን በጥቁር ሽብር ውስጥ ወድቃለች ንጋትን ናፍቆ የተሰደደ ህዝብ በገፍ እየተሰቃየ ነው ፡፡ https://www.facebook.com/photo.php?v=286230021510610
Information for Ethiopia blog
የቀጣፊዎቹ ልሣን የሆነው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ትናንት ማታ በመስኮቱ ሦስት ሆዳም የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች ማህበር አመራሮች አቅርቦ ነበር።ሦስቱ ሆድ አደሮች በበረከትና በሺቀጥል ከማል ተጠፍጥፈው የተሠሩ የጋዜጠኞች ማህበር መሆናቸው ነው።
ኢነጋማ አባላቱና አመራሩ ተጠራርገው ከሐገር ከተባረሩበት የጥቅምቱ መሬት አንቀጥቅጥ ሕዝባዊ ማዕበል በአግአዚ ጭፍጨፋ ከከሸፈ ወዲህ የነበረከት ስሪቶቹ በቀቀኖች አይናቸውን በጨው አጥበው ዕአንድም ጋዜጠኛ በሙያው ምክንያት አልታሠረም።የምዕራቡ ሚዲያ የኢትዮጵያን ሚዲያ ገፅታ አለአግባብ እየኮነነ ነው።የኢትዮጵያ ሚዲያ ነፃ ነው ዕዕሲሉ ለፈጣሪዎቻቸው ታማኝነታቸውን አረጋግጠዋል።
ጋዜጠኛ ባንዳ ሆኖ ህሊናውን ሲያመክን ማየት እንዴት ያሣዝናል፧
በእስክንድር፣በርዕዬትና በውብሸት ኮራሁ።በአብርሐም፣በወንደሠንና በመሠረት አታላይ አፈርኩ።ሦሥቱም አታላዮች መሆናቸው ነው።ያታለሉት ግን ራሣቸውን ነው።ህሊናቸውን ነው።
የሐገራችን ሚዲያ መቃብር ከወረደ ስምንተኛ ዓመቱን በምንዘክርበት በአሁኑ ወቅት ጋዜጠኞችን አሸባሪ እያለች ዘብጥያ የምትወረውር ሐገር ውስጥ የአፍሪካ ሚዲያ መሪዎች መድረክ በመባል የሚታወቀው አኅጉር አቀፍ የሚዲያ ባለድርሻዎች የውይይት መድረክ ስድስተኛ ጉባዔውን ሲያከናውን በመለስ ዜናዊ ሚስጥራዊ መመርያና የተፈቀደ በጀት አማረ አረጋዊ ባለ ቀይ ጃኖው የሪፖርተር ጋዜጣ አሣታሚና የ ኤም ሲ ሲ ባለቤት እንዳለውዕየአፍሪካ ሚዲያ መሠረታዊ ችግሮች ሁለት ነጥቦችን አንስቷል፡፡ በዋናነት የጠቀሱት የሚዲያ ተቋማቱ አቅም ማነስና የሚዲያ ነፃነት ችግሮች መሆናቸውን፣ ሌላኛው ደግሞ የውጭ አገሮች አድልኦና ፍላጐት ነው ፡፡ በኢትዮጵያ የሚዲያ ነፃነት ችግር ቢኖርም ከሳዑዲ ዓረቢያ ጋር ሲነፃፀር የተሻለ ቢሆንም፣ ነገር ግን በሰፊው እየተዘገበ ያለው ስለኢትዮጵያ ብቻ ነው ዕአማረ አረጋዊ ዕበኢትዮጵያ የሚዲያ ነፃነት ችግር ቢኖርምዕሲሉ መናገራቸው የግሉ ፕሬስ የነፃነት ችግር እንዳለበት ከመሸም ቢሆን ያመኑ ይመስላል።
በቀጣይ ልጅ ደመቀ መኮንን አሉት እንደተባለው ጋዜጠኞቹ በሙያቸው ምክንያት አለመታሰራቸውን ገልጸዋል፡፡
ዕጋዜጠኞቹ በተግባር በሽብር እንቅስቃሴ ውስጥ ተገኝተዋል ለዚህም ተገቢውን ሕጋዊ ሥርዓት የተከተለ ዕርምጃ ተወስዶባቸዋል፤ዕዕ
ዕኢትዮጵያ ካለችበት ቀጣና አንፃር የሽብር እንቅስቃሴ ዋነኛ ሥጋቷ ነው፡፡ በመሆኑም መንግሥት የህልውና ጉዳይ አድርጐ ይመለከተዋል፤ዕ ብለዋል፡፡ ከዚህ ውጪ በጋዜጣዊ የሙያ ተግባሩ የተከሰሰ አንድ ግለሰብ ብቻ ነው በማለት አስረድተዋል፡፡
ዕበጋዜጣዊ የሙያ ተግባሩ የተከሰሰ አንድ ግለሰብ ብቻ ነው።ዕያሉት ጋዜጠኛ ስሙ ማን ይሆን፧በረከት ለምን ይህን ተናገሩ ብሎ እንደማይቆጣዎ ተስፋ እናድርግ፧ተላላኪው ቢሆኑም ቅሉ።
የኬንያው ምክትል ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ፣በወርቃማ ቃላት ይህን ብለዋል። ዕሙያዊ ተግባራቸውን በመወጣታቸው ጋዜጠኞችን ማሰርና መቅጣት ኋላ ቀር የሆነ አስተሳሰብ ነው፤ዕ ሲሉ ገልጸውታል፡፡
የሚዲያ ነፃነት በኬንያ መሠረቱ እንዲስፋፋ መንግሥታቸው የሚያምን መሆኑን የሚናገሩት ምክትል ፕሬዚዳንቱ፣ ይህንን የሚያደርጉት ለሚዲያ ተቋማቱ ሲባል ብቻ ሳይሆን ኬንያውያን ሥልጣን ላይ ያስቀመጧቸው መሪዎች እንዴት እያስተዳደሯቸው እንደሆነ የማወቅ መብት ስላላቸውና ስለሚገባቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አንዳንድ የጉባዔው ተሳታፊዎች የአኅጉሪቱ የፖለቲካ አመራሮች ወይም መንግሥታት የሥልጣን ቆይታቸውን ለማራዘም የአኅጉሪቱ የሚዲያ ነፃነትን በሚያወጧቸው የተለያዩ አፋኝ ሕጐች ገድበዋል፡፡ የሚዲያ ባለሙያዎችም በእነዚህ ሕጐች ሰለባ ሆነዋል በማለት ጋዜጠኞች ተከራክረዋል፡፡ በርካቶችም ሙያዊ ተግባራቸውን በመወጣታቸው ሕይወታቸውን እስከማጣት ደርሰዋል በማለት በውይይቱ የተሳተፉ ጋዜጠኞችና የመስኩ ባለሙያዎች የአኅጉሪቱን የፖለቲካ አመራሮች ወቅሰዋል፡፡ ተሳታፊዎቹ የሚዲያ ባለሙያዎች ባገኟቸው አጋጣሚዎች ሁሉ በሙያቸው ምክንያት በርካታ የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች እስር ቤት እንደሚገኙ በማሳያነት ይጠቅሳሉ፡፡
ይህን የመሠለ መድረክ መዝጊያ ላይ ነው የነበረከት በቀቀኖች ዕበኢትዮጵያ አንድም ጋዜጠኛ በሙያው ምክንያት አልታሠረም።የምዕራቡ ሚዲያ የሐገራችንን ሚዲያ ገፅታ አለአግባብ እየኮነነ ነው።የኢትዮጵያ ሚዲያ ነፃ ነው።ዕየሚሉን።
ህሊና ከሌላቸው ሆዳምና አድርባይ ጋዜጠኞች ይሠውረን።
ፔን ዘ ኢትዮጵያ
ግሩም ተ/ኃይማኖት
ይድረስ ያልኩት በቀጥታ ባይደርሶትም መስማትዎ እንደማይቀር እገምታለሁ። ሰላም የምሎት ሰላምታ የእግዚአብሔር በመሆኑ ነው። እንጂ ጫንቃችን ላይ ተጎብራችሁ የዜግነት ክብንርን አውርዳችሁ የዜግነት ክብር የምታዘምሩ በሆናችሁ፣ በብሔር፣ በጎሳ ከፋፍላችሁ … ሰብዓዊ መብታችንን ገፋችሁ … ኑሮን መቋቋም እንዳንችል አድርጋችሁ ለስደት ስለዳረጋችሁን ሰላምስ ማለት አይገባም ነበር።
News, Sports, African Topics and Health
ሃኢያን የተሰኘው ከባድ አዉሎነፋስ የፊሊፒንስን ምሥራቃዊ የባህር ዳርቻን ከመታ ዛሬ አራተኛ ቀን ተቆጠረ። የፈራረሱ ቤቶች መተላለፊያ መንገዶችን ዘግተዋል። የስልክ እና የመብራት መስመሮች ተቋርጠዋል።
በዛሬው የስፖርት ዝግጅት ለብራዚል 20ኛው የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ግጥሚያ ማጣሪያ የኢትዮጵያ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን የፊታችን እሁድ ከናይጀሪያ ጋ የሚጠብቀው የመጨረሻ ጨዋታ፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፣ እንዲሁም፣ የአዉሮጳ እግር ኳስ ክበቦች ባለፈው የሳምንት መጨረሻ ያደረጉዋቸው ግጥሚያዎች እና የሜዳ ቴኒስ ተካተዋል።
ሳዉዲ አረብያ የመኖርያ ፈቃድ የሌላቸዉን እና በሕገ-ወጥ መንገድ የሚኖሩ የዉጭ ሀገር ዜጎችን እያሳደደች ማሰር ከጀመረች ሳምንትን አስቆጥራለች። የኢትዮጵያ መንግስት በሳዉዲ የሚገኙ ዜጎቹን ወደ ሀገሩ ለመመለስ ማቀዱ ከተሰማ በኋላ ዛሬ፤
የአፍሪቃ ሚዲያ መሪዎች ጉባኤ ካለፈው ረቡዕ እስከ ዓርብ ድረስ በአዲስ አበባ ተካሂዷል። በዚህ ጉባኤ ላይ ከተካፈሉ ድርጅቶች መካከል ለጋዜጠኞች መብት የሚሟገተዉ ዓለም ዓቀፉ ድርጅት «ሲ ፒ ጄይ» ይገኝበታል።
ባለፈዉ ሐምሌ-ሐሰን ሩሐኒ ለፕሬዝዳትነት ሲመረጡ ፕሬዝዳንት ኦባማ ከአራት ዓመት በፊት ለዓለም ሠላም ከገቡት ብዙ ቃል-ኢምንቱን እንኳ ገቢር አላደረጉም።ከሰጡት አያሌ ተስፋ-አብዛኛዉ ከተስፋ አላለፈም።ያም ሆኖ ኦባማ ሲሆን እራሳቸዉን ካልሆነም ቢል ክሊንተንን እንጂ ጆርጆ ቡሽን እንዳልሆኑ አስመስክረዋል።
የዓለም ዜና
ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ(አንድት) የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ በአባቶቻችን ደም ታፍራና ተከብራ የኖረችው ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት በገዢው ፓርቲ ቸልታ፣ የፖሊሲ ችግርና የሀገር ፍቅር ማጣት የተነሳ ዜጎቿ በውርደት እንዲኖሩ ተፈርዶባቸዋል፡፡ ዛሬም መገለጫችን ስደት፣ ጦርነት፣ በዜግነታችን ክብር ማጣትና ሞት ከሆነ ሰነባብቷል፡፡ ሀገራዊ ውርደትና ሞት ከተበላሸ ሥርዓት የሚወለድ፣ ካልተስተካከለ የኢኮኖሚ ፖሊሲ የሚፈጠር ነው፡፡ ፓርቲያችን የተሻለ ኢኮኖሚ ፍለጋ፣ የተሻለ ማህበራዊ ፍትህ […]
እንደ ሰው አንድ የሚያደርገን ባሕርይ፣ እንደ ኢትዮጵያዊነትም ሁላችንንም የሚመለከተንና የፖለቲካም ሆነ የሃይማኖት ልዩነት የማይነጣጥለው በደል በሳዑዲ አረብያ ግዛት እየተፈጸመ ነው። የጥቃት ዒላማዎቹ ኢትዮጵያውያን ናቸው። የጥቃቱ ልክ የለሽነትና አሰቃቂነት ደግሞ ይበልጥ የጎላው በሴት እህቶቻችን ላይ ነው። ይህ ዛሬ በሳዑዲ አረብያ የሚደረገው ጥቃትን ማስቆምና ቁጣችን መቆምያ እንደማይኖረው ማሳየት ለነርሱ ብቻ ሳይሆን ለራሳችን ደህንነትም ጭምር የምናደርገው ነው። ምክንያቱም ነገ ተመሳሳይ ጥቃትና በደል በመላው አለም ይስፋፋል። በአፍሪካ ሀገሮች የተበተኑ ኢትዮጵያን ከሶማሌና ኤርትራ ከሚሰደዱት በተለየ ይዘረፋሉ፣ ይደፈራሉ ይዋረዳሉ። እንደ አገር ልጅ አብረው እንዳይቆሙ በዘር በሀይማኖትና በፖለቲካ አቋም ምክንየት የተበተኑ ናቸው። ለሰላሳና አርባ አመት አምባገነኖች ያደረጉት ጭፈጨፋና በደል ፍርሃትን ሰማይ ጥግ አውጥቶታል። እናም ኢትዮጵያዊ በየተበተነበት ሁሉ ተኛ ሲሉት የሚተኛ አውልቅ ሲሉት እርቃኑን የሚቆም ፈሪ እንዲሆን ተደርጓል። ሲቸግረው የሚጮኸውን ያህል ሲመቸው ለወገን የሚደርሰው ጥቂቱ ነው። ይህ ሊቀጥል አይገባም!
ቀደም ባለው ጊዜ አንድ ኢትዮጵያዊ ጥቃት ቢደርስበት ባገኘው መሳርያ ዘነጣጥሎም ቢሆን ይገድል ስለነበር ማንም አይደፍረውም ነበር። በዘመነ ኮሎኒያሊዝም ኢትዮጵያውያን በሄዱበት ሁሉ አንገት የማይደፉና ክብራቸውን የማያስነኩ ነበሩ። ዛሬ ጠቁመው የሚያስይዙ፣ ወገናቸውን የሚያሻሽጡና የሚሰልሉት ሁሉ ኢትዮጵያውያን ናቸው። የዚህ ጽሁፍ መነሻም ሆነ መድረሻው የድሮውን አሁን እየሆነ ካለው ጋር ማወዳደር አይደለም። ለዚህ የሚሆን የቅንጦት ጊዜም የለንም። ዓላማው አሁን እየደረሰብን ያለውን በደል በቁርጠኛነት አንታገለው ነው። ይህ ኢትዮጵያውያንን በሙሉ ከዳር እስከዳር ማስነሳት ካልቻለና ቁጣቸውንም ለመላው አለም ማሳየት ካልቻለ እውነትም አገራችን እያበቃላት ነው ማለት ይቻላል።
የዱር አውሬ እንኳን ከዚህ የተሻለ ክብር አለው። እነዚህ አጅግ ሁዋላ ቀር የሆኑ አረመኔዎች ከእንስሳ እንኳን አንሰው አንዲት በፍርሃት ነብሷን የሳተችን ሴት አስር ሆነው የሚደፍሩትን እያየን የተደፈሩት ህጋዊ ናቸው ህገወጥ የሚል የሕግ አንቀጽ መረጣ ውስጥ ልንገባስ እንዴት ይቻለናል? በመላው አለም ያለ የሳዑዲ ኤምባሲ ፊት ለፊት ሰልፍ ሊደረግና የሳዑዲ ወሮበሎች በወጣት ሴቶች ላይ እያደረሱ ያለው ግፍ በመረጃም ተደገፎ በበራሪ ወረቀትም ተዘጋጅቶ ለአለም ሕዝብ ሊበተን ይገባዋል። ተፈጥሮ ዘይትን ስትቸራቸው አእምሮ ግን እንደነፈገቻቸው ከዚህ በላይ መረጃስ ከየት ይመጣል?
እንደ ትውስታ ከወሰድነው በኬንያ ያሉ ስደተኞች ላይ በደል ይደርስ በነበረበት ወቅት ያ በጨካኝነቱ የሚታወቀው መንግሥሰቱ ሀይለማርያም አንኳን “ኢትዮጵያውያኑ የተሰደዱት የምናራምደውን ፖለቲካ እንጂ ሀገራቸውን ጠልተው አይደለም…” በሚል ኬንያን ማስጠንቀቁን መስማቴ ትዝ ይለኛል። በየወሩ 40 ሺህ ሴቶችን እንልካለን እያለ እንደ እንቁላል በየአረብ ቤቱ ሲያከፋፍል የነበረው መንግስት ዛሬ ዜጎቹ እንዳይሆን መጫወቻ ሲሆኑ ዝም ብሎ መመልከቱ እጅግ የሚያሳዝን ነው። ኢትዮጵያውያኑ ምናልባትም ኤምባሲውን ራሱን መቆጣጠር የሚገባቸው እስኪመስል ያስቆጣል።
በኢትዮጵያዊነት ላይ የተነጣጠረን ክፋት እንደ ሀገርና እንደ ሕዝብ ካላስቆምነው በሳዑዲ የተጀመረው መረን የጥላቻ ሰደድ ሊቀጣጥል የሚችልና የየሀገሩ የፖለቲካ ኪሳራ ማስተንፈሻ የሚሆነው አገር አጥቶ የተሰደደው ኢትዮጵያዊው ላይ ሁሉ ይሆናል። ይህንን በአስቸኳይ ለመቃወም ያሉ የትግል መንገዶች ሁሉ ክፍት ሊሆኑ ይገባል። እኔ አዘጋጀሁ እኔ ጠራሁ የሚል ደካማ የፖለቲካ ትርፍ ፍለጋ መንቀሳቀስ ሳይሆን ለሰብዓዊ ክብርና የመከራ ማጥ ውስጥ ሆነው የወገን ያለህ ለሚሉት እህት ወንድሞቻችን የድረሱልን ጥሪ ምላሽ እንስጥ። በጣም የሚያሳዝነው አብዛኞቹ ለስራ የሚሄዱት ወጣቶች የትምህርት ደረጃቸው አነስተኛ የሆነና በድህነት ውስጥ ያሉ ቤተሰቦቻቸውን ለመርዳት የሆነው ይሁን ብለው ከቤታቸው የወጡ ናቸው። አንዳንዶቹም ግሩም እድል አንደሚገጥማቸው በደላላዎች እየተነገራቸው ከቤት ወጥተው የቀሩ ናቸው። ለኒህ አጋር መሆን ለሀገር እንኳን ደንታ ባይኖረን ለነብስ የሚበጅ ስራ ነው። የኢትዮጵያ ኮሙኒቲዎች፣ በኢትዮጵያ ስም የተቋቋሙ የሀይማኖት ማዕከላት፣ ሲቪክ የፖለቲካ ድርጅቶች በሙሉ ለዚህ ዓላማ ቢቻል አደራጆች ካልተቻለም ዋንኛ ተሳታፊዎች ሊሆኑ ይገባል። ይህ በደል እጅ ለእጅ ሊያስተሳስረንና አንድ ላይ እንድንቆም ሊያደርገን የሚችል የጋራ ጉዳይ ነው። ዛሬ ነገ ሳንል በተደራጀና አለም አቀፍ ትኩረት ሊኖረው በሚያስችል አቅሙ እንነሳ ለወገንም አንድረስ።የመከራ ቀናችንን ለማሳጠር እንደ ሕዝብም ከአንገታችን ቀና እንድንል በያለንበት እንትጋ!
የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ሊቀመንበር ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ እየታካሄደ በሚገኘው የአዲስ አበባ ዞን ምክር ቤት 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ በመገኘት በሀገራችን ኢትዮጵያ ባለው የፖለቲካ፤ የዲሞክራሲ እና የፍትህ እጦት እንዲሁም ሁሉንም ኢትዮጵውያንን የሚያሣትፍ የኢኮኖሚ እድገት ባለመኖሩ ምክንያት ብዙ ዜጎች ወደ ደቡብ አፍሪካ ሃገራትና ወደ አረብ ሀገራት በእግር ሳይቀር ለመሰደድ ከመገደዳቸው በተጨማሪ በጉዞ ወቅት በአውሬ መበላት በበሽታ […]
ሰሞኑን የኢሕአዴግ መንግሥት ይፈራል አይፈራም የሚል ጉዳይ ከፓርላማ ተነስቶ ወደ መገናኛ ብዙኃንም ደርሷል። ጉዳዩ የተነሳው የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ አዲሱ ፕሬዚዳንታችን በፓርላማ ያደረጉትን ንግግር አስመልክቶ ባቀረቧቸው የማማሻሻያ ሐሳቦችና ጠቅላይ ሚኒስትራችን በሰጡት ምላሽ ዙሪያ ነው። ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዝ ሪፖርተር ጋዜጣ ጥቅምት 13 ቀን 2006 ዓም በአወጣው ዕትሙ ‹‹’ፈሪ’ መንግሥት?›› በሚል ርዕስ ጋዜጠኛ የማነ ናግሽ ጥሩ […]
የኢሕአዴግ መንግሥት አሳምሮ ይፈራል!
===========
በኃይሉ አርአያ (ዶ/ር) – የአንድነት ብሔራዊ ምክር ቤት አባል
ሰሞኑን የኢሕአዴግ መንግሥት ይፈራል አይፈራም የሚል ጉዳይ ከፓርላማ ተነስቶ ወደ መገናኛ ብዙኃንም ደርሷል። ጉዳዩ የተነሳው የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ አዲሱ ፕሬዚዳንታችን በፓርላማ ያደረጉትን ንግግር አስመልክቶ
ባቀረቧቸው የማማሻሻያ ሐሳቦችና ጠቅላይ ሚኒስትራችን በሰጡት ምላሽ ዙሪያ ነው። ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዝ ሪፖርተር ጋዜጣ ጥቅምት 13 ቀን 2006 ዓም በአወጣው ዕትሙ ‹‹’ፈሪ’ መንግሥት?›› በሚል ርዕስ ጋዜጠኛ የማነ ናግሽ ጥሩ ትንተና አቅርቧል። የፍርኃት ነገር ከተነሳ ጋዜጠኛው ያነሳውን ለማዳበር በእኔም በኩል የምለው አለኝ። የኢሕአዴግ መንግሥት አሳምሮ ይፈራል። የኢሕአዴግ መንግሥት አሳምሮ ይፈራል ስል ግን በደፈናው አይደለም። በርካታ የማይፈራቸው ነገሮች አሉ። ለምሳሌ ጦርነትን አይፈራም። በተለይ ሕወሓት/ኢሕአዴግ ጥርሱን ነቅሎ ያደገበት ጉዳይ ነው። ሕግ መጣስን አይፈራም። ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶችን መጣስን አይፈራም። መዋሸትን አይፈራም።
የኢሕአዴግ መንግሥት ይፈራል ስል በተለይ የማተኩረው በአንድ ጉዳይ ላይ ነው። እውነት ላይ። የኢሕአዴግ መንግሥት እውነትን ይፈራል። እውነትን ስለሚፈራ እሱ ራሱ በሚፈልገው መንገድ እንዲታወቅ ከሚፈልገው ውጪ ሕዝቡ እውነቱን እንዲያውቅ አይፈልግም። ይህ ደግሞ የአምባገነን አውራ ፓርቲዎች መንግሥታት አንዱና ዋናው የደባቂነትና የሸማቂነት መገለጫ ባህሪ ነው። የኢሕአዴግ መንግሥት እውነትን ለመፍራቱ በርካታ ማስረጃዎችን መጥቀስ ይቻላል። ለጊዜው ግን አራቱን ብቻ በምሳሌነት እንደሚከተለው ልጥቀስ።
1. ከቅርቡ የሶማሊያ ጦርነት ጋር በተያያዘ የእውነት መረጃን ከሕዝብ መደበቁ
እንደሚታወቀው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ጎረቤት ሶማሊያ ውስጥ ገብቶ ከአክራሪና ከሽብር ኃይሎች ጋር ተዋግቷል። እኔ እስከሚገባኝ ድረስ አሁንም እየተዋጋ ነው። ከማን ጋር ነው የተዋጋውም ሆነ የሚዋጋው? ለምንድን ነው የተዋጋው/የሚዋጋው? ጣልቃ ገብነቱ ሕጋዊ ነው አይደለም? ወደሚሉት ውስብስብ ጥያቄዎች አልገባም። እኔ የምገባው ወደ እውነት መረጃ አስፈላጊነት ነው። ጦርነት ነውና ወታደሮች ሞተዋል፣ ቆስለዋል። ገንዘብ ወጪ ሆኗል። የሞቱት የሕዝብ ልጆች ናቸው። ወጪ የሆነው የሕዝብ ገንዘብ ነው። ጦርነቱ የተካሄደው በውጭ ዕርዳታ ገንዘብ ነው እንዳልል፣ ነፍሳቸውን ይማርና የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትራችን አቶ መለስ ዜናዊ ጦርነቱን በተመለከተ ፓርላማ ፊት በመቅረብ የአውራ ጣታቸውንና የሌባ ጣታቸውን ጫፎች አነካክተው ዜሮን በማሳየት ‹‹ሳንቲም ዕርዳታ አላገኘንም›› ማለታቸውን አስታውሳለሁ።
የሞቱት የሕዝብ ልጆች ናቸውና የኢትዮጵያ ሕዝብ ስንት ልጆቹ እንደሞቱ እውነቱን ለማወቅ ይፈልጋል። እውነቱን የማወቅ መብትም አለው። የወጣው የሕዝብ ገንዘብ ነውና ሕዝቡ ያወጣውን ለማወቅ ይፈልጋል። እውነቱን የማወቅ መብትም አለው። እኔ እስከማውቀው ድረስ በተለይ በእነዚህ ሁለት ጉዳዮች ላይ የኢሕአዴግ መንግሥት የጉዳዩ ባለቤት ለሆነው ሕዝብ በይፋ የሰጠው መረጃ የለም። ምናልባት ለአሜሪካ፣ ለአፍሪካ ኅብረትና ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ‹‹እኔ እንደ መንግሥት እየከፈልኩ ያለሁትን መስዋዕትነት ዕወቁልኝ›› በሚልና የባለውለተኛ ወሮታ ለማግኘት በሚስጥር አሳውቆ ሊሆን ይችላል። ይህ መደረጉ አይከፋም። መጀመሪያ መስማት ያለበት ግን ባለጉዳዩ ሕዝብ ነው። ለምንድን ነው ባለፈው እውነታውን ለሕዝብ ያላሳወቀውና አሁንም ቢሆን የማያሳውቀው? እውነትን ስለሚፈራ ነው። መደበቅና መሸመቅ ዓይነተኛ ባህሪው ስለሆነ ነው። ለሕዝብ የማወቅ መብት አክብሮት ስለሌለው ነው።
ጦርነቱን በበጎ ጎኑ አይተነው፣ ሠራዊታችን ሶማሊያ የገባው ሉዓላዊነታችንን ላለማስደፈር፣ ድንበራችንን ለማስከበር፣ የአገራችንንና የአካባቢያችንን ሰላም ለመጠበቅና ከዚያም ባለፈ የዓለማችንን ሰላም ለማስከበር ለሚደረገው ዓለም አቀፍ ጥረት የበኩላችንን አስተዋጽኦ ለማድረግ ነው እንበል። ታዲያ እንደዚህ ላለ ‹‹የተቀደሰ›› ዓላማ የተከፈለን መስዋዕትነት የኢትዮጵያ ሕዝብ ቀርቶ ዓለም እንዲያውቀው ይደረጋል እንጂ ይደበቃል?
ይህን አጭር ጽሑፍ ለማዘጋጀት ሳስብ እስቲ አሜሪካ በቪየትናም ጦርነት የሞቱባትን ወታደሮች ለሕዝብ በይፋ አሳውቃ እንደሆነ ልይ ብዬ ኢንተርኔት ውስጥ ገባሁ። “Us Soldiers Killed in Vietnam” በሚል ‹‹ጉግል›› ሳደርግ ያገኘሁት መረጃ ብዛትና ዝርዝር የሚገርም ነው። በአጭሩ ግን 58,220 ወታደሮች እንደሞቱ፣ የሟቾቹ ቁጥርም በዘር፣ በፆታ፣ በሃይማኖት፣ በመጡበት ‹‹ስቴት››፣ በሠራዊት ምድባቸው (አየር ኃይል፣ ምድር ጦር፣ መርከበኛ፣ ወዘተ.)፣ በአሟሟታቸው ሁኔታ (በውጊያ፣ በድንገተኛ አደጋ፣ በሕመም፣ እርስ በርስ መገዳደል፣ ወዘተ.)፣ በጦርነቱ መጀመሪያ የሞተ ወታደር ስም፣ ጦርነቱ ሊፈጸም ሲል በመጨረሻ የሞተ ወታደር ስም፣ ወዘተ፣ ተዘርዝሮ ተቀምጧል። በተመሳሳይ ሁኔታ የኢራቅንና የአፍጋኒስታንንም አየሁ። መረጃው ከሞላ ጎደል በታመሳሳይ ሁኔታ ተቀምጧል። ወጪ የሆነው የገንዘብ መጠን ሁሉ ተቀምጧል። ከዚያ በኋላ እስቲ መንግሥታችንም ምናልባት ሳናውቀው መረጃ አስቀምጦ እንደሆን ብዬ ለማየት ሞከርኩ። የውጭ ጋዜጦችና ሌሎች የዜና ምንጮች በዜና መልክ ካስቀመጧቸው ጥቂት ተባራሪ መረጃዎች በስተቀር ምንም ነገር የለም።
ለምንድን ነው የአሜሪካ መንግሥት ከላይ የተጠቀሱትን ጦርነቶች በተመለከተ ዝርዝር መረጃ ለሕዝቡና ለተቀረው ዓለም ሲሰጥ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት በሶማሊያ ያካሄደውን ጦርነት በተመለከተ መረጃ ትንፍሽ ያላለው? ይህን ጥያቄ በአግባቡ ለመመለስ ብዙ ማለት ይቻላል። በአጭሩ ግን የአሜሪካ መንግሥት መረጃ የሰጠው እውነትን ስለማይፈራ ነው። በራሱ ስለሚተማመንና ሕዝቡንም ስለሚያምን ነው። የሕዝቡን መረጃ የማግኘት መብት ስለሚያከብር ነው። የኢሕአዴግ መንግሥት መረጃ ያልሰጠው በእኔ እምነት እውነትን ስለሚፈራ፣ በራሱ ስለማይተማመንና ሕዝቡንም ስለማያምንና መረጃ የማግኘት መብቱንም ስለማያከብር ነው።
በዲሞክራሲ የዳበሩ መንግሥታት ምንጊዜም እውነትን አይፈሩም፣ አይደብቁም፣ አይሸምቁም ማለቴ አይደለም። አልፎ አልፎ እውነትን ይፈራሉ፣ ይደብቃሉ፣ ይሸምቃሉ። ሆኖም እውነትን መፍራት፣ መደበቅና መሸመቅ እንደ አምባገነን መንግሥታት ዓይነተኛና መገለጫ ባህሪያቸው አይደለም። ከሁሉም በላይ ደግሞ በእነዚህ አገሮች ውስጥ ጠንካራ ተፎካካሪ ፓርቲዎች፣ ነፃና ጠንካራ ፕሬስ፣ ነፃና ጠንካራ ሲቪክ ማኅበራትና ንቃተ ህሊናው የዳበረና ለመብቱ ቀናዒ የሆነ ሕዝብ ስላሉ እውነትን የሚፈራ፣ የሚደብቅና የሚሸምቅ መንግሥት ይዋል ይደር እንጂ ይጋለጣል። የአሜሪካው የዋተርጌትና የቢል ክሊንተን-ሞኒካ ለዊንስኪ ቅሌት እንዲሁም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በጁሊያን አሳንጅና በኤድዋርድ ስኖውደን እንዲሁም በሌሎች ንቁና ተቆርቋሪ ዜጎች አማካይነት እየጎላ የመጣው የመረጃ ፍልፈላና ፍትለካ የዚህ አንድ ማስረጃ ነው። በዚህም ምክንያት ዲሞክራሲያዊ መንግሥታት እውነትን ከመፍራት፣ ከመሸመቅና ከመደበቅ ድርጊት በተቻላቸው መጠን ይቆጠባሉ። በአምባገነን ሥርዓት ግን የመንግሥት ፕሬስ አድር ባይ በመሆኑ፣ ነፃው ፕሬስ፣ ተቃዋሚዎችና ሲቪክ ማኅበራት ደካሞች በመሆናቸው፣ ሕዝቡም የታፈነና በፍርኃት ድባብ ውስጥ የሚኖር በመሆኑ መረጃ የመፈልፈልና እንዲያፈተልክ የማድረግ አቅም ያንሳቸዋል። ስለዚህ መንግሥት በእነዚህ ኃይሎች ድክመት ምክንያት በማናለብኝነት እንደፈለገው ይሆናል፣ እንደፈለገው ያደርጋል።
2. የመንግሥት መገናኛ ብዙኃንን በሞኖፖል መያዙ
የኢሕአዴግ መንግሥት እውነትን የሚፈራ ለመሆኑ ሌላው ዋና ማስረጃ በሕዝብ ገንዘብ የሚሠሩ መገናኛ ብዙኃንን (ጋዜጣ፣ ሬዲዮ፣ ቴሌቪዥን) በሞኖፖል መያዙ ነው። በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 29 ንዑስ አንቀጽ 4 ላይ ‹‹ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎች፣ ሐሳቦችና አመለካከቶች በነፃ መንሸራሸራቸውን ለማረጋገጥ ሲባል ፕሬስ በተቋምነቱ የአሠራር ነፃነትና የተለያዩ አስተያየቶች የማስተናገድ ችሎታ እንዲኖረው የሕግ ጥበቃ ይደረግለታል፤›› ይላል። በተጨማሪ በዚሁ አንቀጽ በንዑስ አንቀጽ 5 ‹‹በመንግሥት ገንዘብ የሚካሄድ ወይም በመንግሥት ቁጥጥር ሥር ያለ መገናኛ ብዙኃን የተለያዩ አመለካከቶችን ለማስተናገድ በሚያስችል ሁኔታ እንዲመራ ይደረጋል፤›› ይላል። የኢሕአዴግ መንግሥት እውነትን ከመፍራቱ የተነሳ በእነዚህ ንዑሳን አንቀጾች ውስጥ የተካተቱ መሠረታዊ መብቶች ፍርክስክሳቸውን አውጥቶታል። ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎች፣ ሐሳቦችና አመለካከቶች በነፃ መንሸራሸራቸውን ይፈራል። እውነትን ይፈራል። ለዲሞክራሲ ሥርዓት መልካም አሠራር ሲባል የተለያዩና ጥርስ ያላቸው አስተያተቶች ማስተናገድን ይፈራል። ከመፍራቱ የተነሳ የመንግሥት መገናኛ ብዙኃንን ዘግቶ ይዟል።
አልፎ አልፎ የተለያዩ አስተሳሰቦችን ያቀረበ ለማስመሰል በቤት ልጆች እዚያው ተፈጭተው፣ እዚያው ተቦክተው፣ እዚያው ተጋግግረው የሚቀርቡ ፕሮግራሞችን ያይራል (Air) ያደርጋል። በምርጫ ሰሞንም ነፃነት ያለ ለማስመሰል የሚዲያ በሩን ለስሙ ገርበብ አድርጎ በመክፈት የተለያዩ ሐሳቦች ይቀርባሉ ለማስባል ይሞክራል። በዚህም ቢሆን የቀረቡ ሐሳቦችን በቅድሚያ ቀርፆ የሚፈራቸውን ሐሳቦች ቆርጦ (ሳንሱር አድርጎ) ነው የሚያቀርበው። በጋዜጣና በሬዲዮ የሚቀርቡ ሐሳቦችን ደግሞ ‹‹ይህን ካላስወጣችሁ››፣ ‹‹ይህን ካላስተካከላችሁ›› እያለ በቅድሚያ ሳንሱር የማያላውስ እንቅፋት ይፈጥራል። እንደ እውነተኛ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት አካሄድ ከሆነ፣ እንዲሁም በጎረቤትና በሩቅ አገሮችም እንደሚታየው ከሆነ ብዙ የግልና ነፃ የቴሌቪዥንና የሬዲዮ ጣቢያዎች እንዲሁም ጋዜጦች መኖር ነበረባቸው። የመንግሥት የሚባል ቴሌቪዥንም ሆነ ሬዲዮ መኖር አልነበረበትም። ትላልቅ የሚባሉ፣ በዲሞክራሲ የዳበሩና በራሳቸው የሚተማመኑ አገሮች የቴሌቪዥንም ሆነ የሬዲዮ ጣቢያዎች የሏቸውም። (ያሏቸው የሉም ማለት ግን አይደለም)። የእኛ መንግሥት ግን ሲጀመርም እውነተኛ ዲሞክራሲ የሚባል ነገር ስላልተዋሀደው፣ እንዲሁም በግል ቴሌቪዥና በግል ሬዲዮ ጣቢያዎች ሊንሸራሸሩ የሚችሉ እውነታዎችን ስለሚፈራና እውነትን በእውነት ለመጋጠም ችሎታውም፣ ድፍረቱም ስለሌው እነዚህ ተቋማት እንዳይኖሩ ከልክሏል። ተረጋግተው፣ በነፃነታቸው ተማምነው የሚሠሩ ነፃ ጋዜጦችም የሉም ማለት ይቻላል። ስለዚህ ሥራዬ ብሎ የመረጠው መንገድ የመንግሥት የመገናኛ ብዙኃንን የሕዝብን የተለያየ መረጃ የማግኘት መብትን በሚፃረር ሁኔታ በሞኖፖል በመያዝ እሱ የመረጠውን እውነታ ብቻ፣ እሱ በመረጠው ጊዜና መንገድ ለሕዝብ ማንቆርቆር ነው። የዚህ ዓይነት መንገድ የፍርኃት አካሄድ ነው።
ጽጌረዳና ዲሞክራሲ አንድ ናቸው። ጽጌረዳ አበባዋ ውብ ነው። ከውብ አበባዋ ጋር ግን እሾህ አላት። እሾሁ የተፈጠረው ለክፉ ነገር አይደለም። የአበባዋን ውበት ከጉዳት የሚጠብቅ የተፈጥሮ መከላከያ ነው። እሾሁም የውበቷ አካል ነው። ስለዚህ ጽጌረዳን ስንወድ የተፈጥሮዋ አካል ከሆነው ከእሾህዋ ጋር ነው። ዲሞክራሲም ‹‹እሾህ›› አለው። የዲሞክራሲ ‹‹እሾህ›› ነፃነቱ፣ ሙያዊ ብቃቱና ትጋቱ ካለው ፕሬስ፣ ብቃቱና ቁርጠኝነቱ ካላቸው ተቃዋሚ ፓርቲዎች፣ ነፃነቱና ጥንካሬው ካላቸው ሲቪክ ማኅበራት፣ ንቃቱ ካላቸው ዜጎች የሚሰነዘሩ ገንቢና ሂሳዊ እውነታዎች ናቸው። የኢሕአዴግ መንግሥት ከእነዚህ አቅጣጫዎች የሚመጣውን እሾህ ስለሚፈራ እውነተኛ ዲሞክራሲን በሩቁ ብሏል።
3. ኢትዮ ተሌኮምን በሞኖፖል መያዝ
ቴሌኮሙዩኒኬሽን በዘመናዊ መልኩ ቴክኖሎጂ የወለደው የእውነት መረጃ መንሸራሸሪያ ጎዳና ነው። በሌላው ዓለም እንደ ፀጋና እንደ ልማት መሣሪያ ሲወሰድ በአምባገነን ሥርዓቶች ግን እንደ አደገኛ መሣሪያ ይወሰዳል። በዚህ ምክንያትም በአገራችንም ይህን ‹‹አደገኛ›› መሣሪያ ለመቆጣጠር ሲባል መንግሥት በሞኖፖል ይዞታል። መንግሥት እንደሚለው ኢትዮ ቴሌኮምን በሞኖፖል የያዘው ለልማት የሚውል ከፍተኛ የገንዘብ ምንጭ (‹‹የምትታለብ ላም››) ስለሆነ ብቻ አይደለም። የመረጃ መንሸራሸሪያ ጎዳናና የእውነት ምንጭ ስለሆነ ነው። እንዲያውም የኢሕአዴግ መንግሥት ኢትዮ ቴሌኮምን በሞኖፖል ለመያዙ ዋናው ምክንያት የከፍተኛ ገንዘብ ምንጭ ከመሆኑ ይልቅ የመረጃ መንሸራሸሪያ፣ የሕዝብ መገናኛና የእውነት ምንጭ የመሆኑ ፍራቻ ነው ብዬ አምናለሁ። የኢሕአዴግ ምንግሥት መረጃ ኃይል የመሆኑን እውነታ ጠንቅቆ ያውቃል። ይህንን እውነታ ይፈራል።
4. በአሳሪና አስፈሪ ሕጎች ራሱን ማጠሩ
የኢሕአዴግ መንግሥት ዙሪያውን በአስፈሪና አሳሪ ሕጎች በማጠር የእውነት ፍርኃቱን ለመቀነስ ይሞክራል። የእውነት መምጫ መንገዱ ብዙ ነው። ለምሳሌ በነፃ ፕሬስ አማካይነት ይመጣል። በጠንካራ ሲቪክ ማኅበራት አማካይነት ይመጣል። የጠያቂነትና የለምን ባይነት መንፈስ ባላቸው ዜጎች አማካይነት ይመጣል። እውነትን የሚፈራው የኢሕአዴግ መንግሥት አንዱ ዋነኛ ሥራው ሆኖ የተገኘው የእውነት መንገዶችን የሚዘጉ አስፈሪና አሳሪ አዋጆችን ማውጣት ነው። ነፃው ፕሬስ የእውነት መምጫ መንገድ እንዳይሆን በአሳሪና አስፈሪ የፕሬስ አዋጅ ታጥሯል። ሲቪክ ማኅበራት የእውነት መምጫ መንገዶች እንዳይሆኑ በሲቪክ ማኅበራት አዋጅ ታስረው እንዲሽመደመዱ ተደርገዋል። የጠያቂነትና የለምን ባይነት መንፈስ ያላቸው ዜጎች የእውነት መንገድን እንዳያሳዩ በሽብር ሽፋን በፀረ ሽብርተኝነት አዋጅ እንዲሸማቀቁ ተደርገዋል። ከዚያም ባለፈ ወደ ወህኒ እንዲወርዱ የተደረጉም አሉ።
ኢትዮጵያ የሽብርተኝነት ሥጋት የለባትም ማለት አይደለም። የፀረ ሽብርተኝነት ሕግ ስታወጣም የመጀመሪያ አገር አይደለችም። ሌሎች አገሮችም አውጥተዋል፣ በተለይ በዲሞክራሲ የዳበሩ አገሮች። ትልቁ ጥያቄ ‹‹የወጣው ፀረ ሽብር አዋጅ በማን እጅ ነው? በምን ዓይነት መንግሥት እጅ ነው?›› የሚለው ነው። በዲሞክራሲ በዳበሩ አገሮችና በእኛ አገር ያለው ሁኔታ የሰማይና የምድር ያህል ይራራቃል። በዲሞክራሲ የዳበሩ መንግሥታት ራሳቸው የዜጎቻቸው መብቶች እንዳይነኩ በከፍተኛ ደረጃ የሚጨነቁ፣ የሚጠበቡና የሚጠነቀቁ ናቸው። አርባ ዓመት ለመግዛት ዕቅድ በማውጣት ቸክለው የተቀመጡና ሥልጣናቸውን ለመከላከል ከፀሐይ በታች ባለ በማንኛውም ዓይነት ስልት ከመጠቀም ወደ ኋላ የማይሉ አይደሉም። የፍትሕ ተቋሞቻቸው ነፃ ናቸው፣ የአስፈጻሚ አካላት ትእዛዝ ፈጻሚዎች አይደሉም። ፖሊሶቻቸውና የደኅንነት ሰዎቻቸው በከፍተኛ ደረጃ የሠለጠኑ፣ የዜጎችን ሰብዓዊ መብቶች የሚያከብሩ፣ ዓለም አቀፍ ሰብዓዊ ሕግን በሚገባ የሚያውቁና የሚያከብሩ ናቸው። ስንዝር ሥልጣን ሲሰጣቸው ክንድ የሚወስዱ አይደሉም። ፀረ ሽብር አዋጆቻቸውም በአመዛኙ የሚያተኩሩት ከውጭ በሚመጡ አደጋዎች ላይ ነው። በእኛ አገር በአሁኑ ጊዜ የአዋጁ ዋና ሰለባ የሆኑት በአመዛኙ የአገሪቱ ዜጎች ናቸው። ስለዚህ የኢሕአዴግ መንግሥት በፀረ ሸብር ሽፋን አዋጁን ተቃዋሚዎችንና የጠያቂነትና የለምን ባይነት መንፈስ ያላቸውን ዜጎች ለማጥቃትና በአጠቃላይ ሕዝቡን ለማሸማቀቅና ለማሸበር በመሣሪያነት ይጠቀምበታል የሚል ከፍተኛ ሥጋት አለ።
የኢሕአዴግ መንግሥት አፈ ቀላጤዎች ‹‹የፀረ ሸብር ሕጉን የሚፈሩት ሕገወጦች ብቻ ናቸው›› ይሉናል። አዎ፣ እውነት ነፃ በምታወጣበት አገር አባባሉ ያስኬዳል። በእኛ አገር ግን እውነት ነፃ ታወጣለች ብሎ መተማመን አይቻልም። በዚህ ምክንያት ንፁኃን ዜጎችም ፀረ ሽብር ሕጉን ይፈራሉ፣ ሽብርተኞች ሆነው ግን አይደለም። ዜጎች ሽብርተኝነትን ያወግዛሉ። የሚፈሩት የኢሕአዴግ መንግሥት አዋጁን እንደሚፈልገውና እንደሚያመቸው በመለጠጥ ያለ ኃጥያታችን ሊወነጅለንና ሊጎዳን ይችላል ከሚል ሥጋት በመነሳት ነው። ሥጋታቸው ደግሞ ያለመሠረት አይደለም። እንግዲህ የኢሕአዴግ መንግሥት ከነፃው ፕሬስ፣ ከነፃና ጠንካራ ሲቪክ ማኅበራት እንዲሁም የጠያቂነትና የለምን ባይነት ባህሪ ካላቸው ዜጎች የሚመጣ እውነትን ለመከላከል በተደራራቢ አዋጆች ዙሪያውን አጥሯል። ይህ ደግሞ እውነትን ለመፍራቱ ግልጽ ማሳያ ነው። ለመሆኑ የኢሕአዴግ መንግሥት እውነትን መፍራትና መበርገግ የጀመረው ከመቼ ጀምሮ ነው? መፍራት የጀመረው እውነትን ፊት ለፊት ያየ ዕለት ነው። ያ ዕለት ደግሞ ሚያዝያ 30 ቀን 1997 ዓ.ም. ነበር። በዚያን ዕለት ያየውን እውነት በሳምንቱ ግንቦት 7 ቀን 1997 ደግሞ አየው። ይህ ዕለት ደግሞ በምርጫ ቦርድ ውሳኔ ሳይሆን በሕዝብ ድምፅ መሸነፉን የተረዳበትና ይበልጥ የበረገገበት ዕለት ነበር። የአቶ መለስ ዜናዊ የግንቦት 7 ምሽት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅም የዚህ መበርገግ ዓይነተኛ ምልክት ነበር። ከእነዚህ የእውነት ቀናት ጀምሮ እስካሁን ድረስ የኢሕአዴግ መንግሥት እንደበረገገ አለ። የእነዚያን ቀናት የሽንፈት እውነታ ዳግም ላለማየት የማይፈነቅለው ድንጋይ፣ የማይወስደው ዕርምጃ፣ የማያወጣው ግልጽም ሆነ ስውር መመርያ፣ የማይቀይሰው ስትራቴጂ፣ የማይደነቅረው መሰናክል፣ የማያወጣው ወጪ፣ የማይጥሰው እሴት የለም። በምርጫ የመሸነፍ እውነታን ሲያስበው ስለሚያስበረግገው፣ ለ2007 ምርጫ ዝግጅት የጀመረው በ2002 ምርጫ ማግሥት ነው። የ2002 ምርጫ ዝግጅት የጀመረው በ1997 ምርጫ ማግሥት ነው። (ይህ አካሄድ በእንድ ጎኑ ሲታይ የሚደነቅ ነው። ምርጫ ወራት ብቻ ሲቀረው የሚንደፋደፉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ከዚህ ብዙ ትምህርት ሊቀስሙ ይችላሉ፣ እስካሁን አላደረጉትም እንጂ)።
ለማጠቃለል የኢሕአዴግ መንግሥት አሳምሮ ይፈራል። አልፈራም ካለ አለመፍራቱን በድርጊቶቹ ያሳይ። በሶማሊያ ጦርነት የኢትዮጵያ ሕዝብ የከፈለውን መስዋዕትነት በተመለከተ ትክክለኛና ይፋዊ መረጃ በመስጠት የሕዝብ መረጃ የማግኘት መብቱን ያክብር። የመንግሥት መገናኛ ብዙኃንን ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች (እውነተኛ ተቃዋሚዎችን ጨምሮ) ለሚመጡ ሐሳቦች መንሸራሸር በአምስት ዓመት አንድ ጊዜ ሳይሆን ዓመቱን በሙሉ ክፍት ያድርግ። በተጨማሪ የመገናኛ ብዙኃን ዘርፉንና ኢትዮ ቴሌኮምንም ለግሉ የንግድ ዘርፍ ክፍት ያድርግ። አሳሪና አስፈሪ ሕጎችን በመሰረዝ ወይም በማሻሻል እንደ ምሽግና እንደ ማጥቂያ መሣሪያ መጠቀምን ያቁም። የኢሕአዴግ መንግሥት በእነዚህ ጉዳዮች ላይ ተጨባጭ ለውጥ ካላመጣ አሥር ጊዜ በቃል ‹‹አልፈራም!›› ቢልም እውነትን ለመፍራቱ በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ ተጽፈው የሚታዩ ጉልህና ተጨባጭ ማስረጃዎች ሆነው ይቀጥላሉ።

Getachew Shiferaw VIA Minilik Salsawi
ከጓደኞቼ ጋር በጠየቅነው ወቅት እንድናስተላልፍ አደራ ብሎናል፡፡ ድምጻችን ይሰማዎች ሆይ! እስክንድር አድንቋችኋል፡፡ ከሁለትና ሶስቱ ውጭ ቢሮ ውስጥ ተቀምጠው የሚውሉት ከ70 በላይ ፓርቲዎች ጉዳያችን አይደለም ቢሉትም እስክንድር ግን ቃሊት ሆኖ እያንዳንዱን እንቅስቃሴያችሁን ይከታተላል፡፡
መልዕክቱንም እንዲህ አስተላልፏል፡፡ ‹‹ድምጻችን ይሰማ ብለው የተነሱት ወጣቶቻችን ለፖለቲካው እንቅስቃሴም ትልቅ ተምሳሌት ናቸው፡፡ ሌላው ማህበረሰብም ሊደግፋቸው ይገባል፡፡ ወጣቶቹ ኢትዮጵያ ውስጥም አምባገነንን ሊያስጨንቅ የሚችል ሰላማዊ እንቅስቃሴ እንደሚቻል በቀላሉ አስመስክረዋል፡፡ መብቱን በቀላሉ አሳልፎ የማሰጥ ወጣት እንዳለው አሳይተዋል፡፡ እስኪ አስቡት ይህ የወጣት እንቅስቃሴ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ቢሆን ምን ታዕምር ሊፈጥር እንደሚችል? እውነቴን ነው የምላችሁ ፓርቲዎችን ጨምሮ በፖለቲካው ዘርፍ እንቀሳቀሳለሁ የሚል አካል ድምጻችን ይሰማን ሞዴል ማድረግ ይኖርበታል››፡፡
እስክንድር እውነት አለው፡፡ እኔ በበኩሌ የማይዋዥቅ እንቅስቃሴ ያየሁት ድምጻችን ይሰማን ነው፡፡ ለሌላኛው የፖለቲካ እንቅስቃሴም ቢሆን ቀላል የማይባል ድምቀት ሰጥቶታል፡፡ በፖለቲካው ዘርፍ ብቻ ያተኮረው እንቅስቃሴን በተለይ በፌስ ቡክ በቅርብ አመታት ጠንከር እያለ ቢሆንም አጀንዳ ቀረጻው፣ አደረጃጀቱና እንቅስቃሴው አዝጋሚ ነው፡፡ ሰላማዊ ሰልፍ ሲኖር፣ ባለሰልጣናት ሲመረጡ፣ ሲሻሩ፣ ሙስና ተከሰተ፣ መሬት ተሸጠ ሲባል ዜና ማስተላለፍ፣ ወቅታዊ ጉዳይን ማስተላለፍ ላይ የተጠመደ ነው፡፡ በእርግጥ ይህም አንድ በጎ ጅምር ነው፡፡
ሆኖም ትኩስ ጉዳይ ካላገኘ እንደገና ይቀዘቅዛል፡፡ አንዱን አጀንዳ ጥሎ ሌላ ከማንሳት ያለፈ ዳር የማድረስ ችግር ይታይበታል፡፡ ቀደም ብሎ የያዘው ጉዳይ (እስራት፣ የዜጎች መፈናቀል፣ ሙስና……) ዳር ሳይደርስ ሌላ አዲስ ወሬ ከመጣ ዋና አስመስሎት የነበረውን አጀንዳ በትኖ አዲሱን ይቀበላል፡፡ ያው ዋና አጀንዳው አልነበረውም ማለት ነው፡፡ አሊያም አጀንዳ ለመያዝ አቅም አልነበረውም፡፡ በዚህ ረገድ ድምጻችን ይሰማ የተለየ ነው፡፡ ኳስም ይኑር ሩጫ፣ ሙስናም ይሁር ሹምሽር በድምጻችን ይሰማ ሰፈር የሙስሊሙ ጉዳይ፣ የኮሚቴዎቼ ዜና አይደበዝዝም፡፡ በፖለቲካው ጉዳይ ግን በወረት አጀንዳዎች ዳር ሳይደርሱ ሌላኛውን ማንሳት የተለመደ ነው፡፡ አዲስ ዜና ያጠቃናል፡፡ በአሁኑ ወቅት ለጭቆና ራሱን መስዕዋት ያደረገውን የኔሰው ገብሬን እያስታወስነው አይደለም፡፡ ውብሸት ታዬን እኛ እረስተነው ያስተወሱት ፈረንጆቹ ናቸው፡፡ ከክልል የሚባረሩት ኢትዮጵያውያን የአንድ ሰሞን ጉዳይ ነው፡፡ ታሰረ፣ ተፈታ፣ ተገደለ፣ ሙስና…….ዜና ሆነው ያልፋሉ፡፡ ከሳምንት በኋላ በሳውዲ የሚሰቃዩትን ዜጎቻችንን ጉዳይ ረስተን ሌላ ጉዳይ እናነሳለን፡፡ ከዋናው ጉዳያችን ልቅ የኢህአዴግ ካድሬዎች የሚያነሷቸው ማስቀየሻዎች ላይ በርካታ ጊዜያችን እንገድላለን፡፡ እንደገና ሌላ ዜና ይመጣል፡፡
እኔ እንደሚመስለኝ ዋናው ችግራችን የተበታተንን በመሆናችን ነው፡፡ ፌስ ቡኩንም ሆነ ሌላውን እንቅስቃሴ በተደራጀ መለኩ፣ በሙያ፣ በስነ ምግባር የሚመራው አልተገኘም፡፡ ዲያስፖራውና አንዳንድ ፓርቲዎች አካባቢ የሚገኙ በጣት የሚቆጠሩ ግለሰቦች (በግል) ብቻ እንቅስቃሴ የትም ሊያደርሰው አይችልም፡፡ ማህበራዊ ድህረ ገጹ፣ ፖለቲካ እንቅስቃሴው የመሪ ያለህ እያለ ነው፡፡
በ1960ና 70ዎቹ ትውልድ በብጫቂ ወረቀት፣ በመልዕክተኛ፣ አልፎ አልፎም በቤት ስልክ ተገናኝተው ለራሳቸው ሳይሆን ለሰፊው ህዝብ ታግለዋል፡፡ በዛን ወቅት ፌስ ቡክ ቢኖር በየ ካፌና ጠባብ ቤቶች ተሰብስቦ የራሱን አገራዊ ፖሊሲ መቅረጽ የቻለው ያ ትውልዱ ምን ያህል ሊጠቀምበት ይችል እንደነበር መገመት አያዳግትም፡፡
ይህ ግን የአሁኑ ትውልድ በአጠቃላይ ችግር እንዳለበት የሚያሳይ አይደለም፡፡ ጥቂቶችም ቢሆኑ የአሁኑ ትውልድ በሙሉ የባከነ እንዳልሆነ እያሳዩን ነው፡፡ ድምጻችን ይሰማን በዚህ በፈዘዝነው መካከል ሆኖ መደራጀት፣ መጠየቅ፣ አጀንዳና ማንሳትና ዳር ማድረስ፣ አምባገነንን ማስጨነቅ ችሏል፡፡ ስለሆነም ድምጻችን ይሰማን መመልከቱ አዋጭ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ድምጻችን ይሰማ ሆይ! የኢትዮጵያውያን ድምጽ ጮህ ብሎ ይሰማ ዘንድ እናንተም አርዕያነታችሁን ተወጡ፡፡
የድሮው ትውልድ ፍልስጤም ድረስ ተጉዞ ሰልጥኗል፡፡ የሌሎች አገር ዜጎች እንኳን ስል አብዮት ብለው ኢትዮጵያ ድረስ መጥተው አሰልጥነዋል፡፡ አሁን ፌስ ቡክ የሚባል አውላላ ሜዳ ትልቅ ማሰልጠኛ ጣቢያ ሆኗል፡፡ እናም የዳሌ ምስል እየተከተለ ‹‹like›› የሚያደርገውን ወጣት፣ አንዱን ዜና ይዞ ሌላኛውን የሚያነሳውን፣ በአገር ጉዳይ አያገባኝም ብሎ ራሱን የሚሸነግለውን ስለ ትግል ስልት፣ ስል መደራጀት፣ ስለ አጀንዳ ቀረጻ ስልጠና ብትሰጡት፣ ‹‹ዱብ ዱብ›› እንዲል ብታደርጉት ምን ይመስላችኋል? —
እንደ ሰው አንድ የሚያደርገን ባሕርይ፣ እንደ ኢትዮጵያዊነትም ሁላችንንም የሚመለከተንና የፖለቲካም ሆነ የሃይማኖት ልዩነት የማይነጣጥለው በደል በሳዑዲ አረብያ ግዛት እየተፈጸመ ነው። የጥቃት ዒላማዎቹ ኢትዮጵያውያን ናቸው። የጥቃቱ ልክ የለሽነትና አሰቃቂነት ደግሞ ይበልጥ የጎላው በሴት እህቶቻችን ላይ ነው። ይህ ዛሬ በሳዑዲ አረብያ የሚደረገው ጥቃትን ማስቆምና ቁጣችን መቆምያ እንደማይኖረው ማሳየት ለነርሱ ብቻ ሳይሆን ለራሳችን ደህንነትም ጭምር የምናደርገው ነው። ምክንያቱም […]
በግንቦት 7 አና በአርበኞች መካከል ያለው ልዩነት እየጎላ መጥቷል:: ጀነራል ፍፁም አርበኞች ወደ ገንቦት 7 እንዲቀላቀል ግዳጅ ቢሰጥም ከአረበኞት ተቀባይነት አላገኘም:: በትናቸው(አንዳርጋቸው) ጥጌ በወያኔ የግድያ ሙከራ ተፈፅሞብኝ ነበር የሚለው ከሃቅ የራቀ አውነቱን ለመሸፈን የተደረገ ፕሮፓጋንዳ ነው:: ዋናው ቁምነገሩ አርበኞች በጉራጌና “በጋላ” (አንዳርጋቸው) አንመራም እያሉ ነው:: አርበኞች በብዛት ከጎንደር የመጡ ሲሆን ከመቶ አይበዙም:: ግንቦት 7 በአሁኑ ሰዓት ምላስ እንጂ ምንም ጡንቻ የለውም:: የአንዳርጋቸው ጥጌ የአስመራ ጉዞ ስኬታማ አልነበረም:: በአስመራ ያሉት የተለያዩ የኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች በጎሪጥ ነው የሚተያዩት:: አይተማመኑም::
News, Radio Magazine or Mestawot
የዕለቱ ዜና
ኢትዮጵያ የተለያዩ የኃይል ምንጮችን ለኤሌክትሪክ አቅርቦት ለመጠቀም ጥረት ከተጀመረች ዓመታት አልፏታል።
መጽሐፍ ወሬ ነጋሪ ደራሲ መሐመድ ይማም ግምገማ በልጅግ ዓሊ በሚያዚያ ወር የሰሜን አሜሪካ ክረምት ገና ሙሉ በሙሉ ሳይለቅ በፊላደልፊያ ከተማ ውስጥ በማይታወቅ ሰው ኢትዮጵያዊቷ ጀግና ተገደለች። በምሳ ሰዓት አካባቢ ወደ ቤት የተመለሰችው እህቷ ጠዋት በሰላም የተለየቻትን በደም አበላ ውስጥ ተዘፍቃ አገኘቻት። ፖሊስም ጠራች። የፍላደልፊያ ፖሊስ ይህንን የተቀነባበረ ግድያ የፈጸመውን ወንጀለኛ መያዝ ስላቃተው እንቆቅልሹ ያልተፈታ በሚል […]
ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
በሪያድ መንፉሃ በተከሰተው ሁከት ግራም ነፈሰ ቀኝ ተጎጅዎች እኛ ነን ! እንኳንስ ሰው ተደብድቦ ፣ ሞቶባቸው ፣ እንኳንስ መኪና ተሰብሮባቸው እንዲያውም እንዲው ናቸው ። ከማለዳ እስከ ሌሊት የዘለቀውን ሁከት መቆጣጠር ይቻል ዘንድ ገና ሲጀመር አቅጣጫውን አይተው የመንግስት ተወካዮችን የመከሩ በርካታ ነበሩ። የሰማ አካል ግን የለም ! ስልክ ተደውሎ የማይነሳበት ፣ አልፎ አልፎ መስመሩ ሲነሳ ሃላፊዎችን […]