ዛሬ ረፋድ ላይ … በሳውዲ ዋና ከተማ ዛሬ ከረፋዱ ጀምረው እስከ እኩለቀን በሪያድ መንፉሃ ወደ ሃገራችን ስደዱን በሚል መንፉሃ ባንክ አልራጅህ አካባቢ በርካታ ኢትዮጵያውያን መንግስት የወሰደውን እርምጃ ተቃውመው ወጡ! ቤተሰቦቻቸውን እና ሻንጣቸውን ይዘው አውራ መንገድ የወጡት ኢትዮጵያውያን ህጋዊ መኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው ግማሾቹ ወደ ሪያድ ኢንባሲና ኮሚኒቱ መስሪያ ቤት በእግራቸው ያመሩ ሲሆን መንፉሃ አካባቢ የቀሩት ከፖሊስ […]

(ፋክት መጽሔት፤ ቅጽ ፪ ቁጥር ፲፱ ጥቅምት ፳፻፮ ዓ.ም.) ተመስገን ደሳለኝ … ኢሠፓ መራሹ መንግሥት በኢሕአዴግ ከተተካ ጥቂት ወራት ቢያልፈውም፣ የተራዘመው የእርስ በርስ ጦርነት ያልደረሰባቸው በደቡብ ኢትዮጵያ የሚገኙ አንዳንድ ከተሞችን ገና በቅጡ አልተቆጣጠራቸውም፤ በአናቱም በኢሠፓ መንግሥት ሽንፈት ሳቢያ እንዲበተን ከተገደደው የአገሪቱ መደበኛ ወታደር አብዛኛው ከእነትጥቁ የትውልድ መንደሩንና ቤተሰቡን መቀላቀሉ በአገሪቱ ላይ ከባድ ፍርሃት አንብሯል፡፡ በሰላም …

እ.አ.አ በ፲፱፻፵፯ ዓ.ም. በአሥመራ ከተማ ተወልደው የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአሥመራ፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በጅማ ተከታትለዋል፡፡ የመጀመርያ ዲግሪያቸውን ከአሥመራ ዩኒቨርሲቲ በሕግ አግኝተዋል፡፡ ከ፲፱፻፸፪ – ፲፱፻፸፬ ዓ.ም በአሥመራ ዩኒቨርሲቲ ያስተማሩት ፕሮፌሰር ተከሥተ በሎንዶን ዩኒቨርሲቲ ከ‹‹ስኩል ኦቭ ኦሪየንታል ኤንድ አፍሪካን ስተዲስ›› ሁለተኛ ዲግሪ ያገኙ ሲኾን የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ከስዊድን ኡፕሳላ ዩኒቨርስቲ በታሪክ ትምህርት ሠርተዋል፡፡ ፕሮፌሰሩ ዛሬ ታትሞ ከወጣው አዲስ …

ምዕራብ አፍሪቃዊቱ ሀገር ማሊ እአአ የፊታችን ህዳር 24 አዲስ ምክር ቤት ትመርጣለች። የምርጫው ዘመቻ በሳምንቱ መጀመሪያ የተጀመረ ሲሆን፣ ለ147 የብሔራዊ ምክር ቤት መንበሮች 1141 ዕጩዎች በተወዳዳሪነት ቀርበዋል።

ጥቅምት ፳፱(ሃያ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኢትዮጵያ የብሄራዊ መረጃና ደህንነት ዋና ሃለፊ በአቶ ጌታቸው አሰፋ እና በጠቅላይ ሚኒስትሩ የብራዊ ደህንነት አማካሪ በአቶ ጸጋየ በርሄ ቁጥጥር የተመራና በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌና በግንቦት7 ህዝባዊ ሀይል መሪዎች ላይ የተቀነባበረው የግድያ ሙከራ ከሸፈ። ከግንቦት7 ህዝባዊ ሀይል ለኢሳት የደረሰው መረጃ እንዳመለከተው ለግድያ የተላከው ሙሉቀን መስፍን የተባለው ግለሰብ በትናንትናው እለት በቁጥጥር …

ጥቅምት ፳፱(ሃያ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ምክር ቤቱ ነገ በሚያደርገው ስብሰባ ለመንግስት ስልጣን አስጊ ሆኗል ባለው የሽብርተኝነት አደጋ ላይ እንደሚመክር ለማወቅ ተችሎአል። ምክር ቤቱ ከፍተኛ ስጋት ደቅነዋል ባላቸው ግንቦት7 እና የኤርትራ መንግስት ላይ ተነጋግሮ የመፍትሄ እርምጃ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል። ምክር ቤቱ በሳውዲ አረቢያ በካምፕ ውስጥ ስላሉ ኢትዮጵያም ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል። የውጭ ጉዳይ መስሪያ …

ጥቅምት ፳፱(ሃያ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮምሽን በመካሄድ ላይ ባለው 6ኛው የአፍሪካ ሚዲያ አመራሮች ፎረም ላይ ኢህአዴግ የሚያቀነቅነው  የልማታዊ ጋዜጠኝነት ጽንሰ-ሀሳብ በአፍሪካ ጋዜጠኞች ተተችቶአል። ኢትዮጵያዊያን ጋዜጠኞች ችግሮቻቸውን ፊትለፊት አውጥተው መናገር ባለመቻላቸውም ወቀሳ ደርሶባቸዋል። ጠ/ሚኒስትር ኃ/ማርያም ደሳለኝ በዚሁ ጉባዔ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር የፕሬስ ነጻነት በኢትዮጽያ መረጋገጡን በማውሳት ፕሬሱ ግን በውስጡ …

ጥቅምት ፳፱(ሃያ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰሞኑን በሶማሊ ክልል ዋና ከተማ ጅጅጋ የሚታየው ሁኔታ እስከ ዛሬ ከታዩት ሁሉ የተለየ ነው ይላሉ ነዋሪዎች። ከሌሎች አካባቢዎች በመሄድ ወደ ከተማው መግባት ወይም ከከተማው በመውጣት ወደ ሌሎች አካባቢዎች መሄድ  የተከለከለ ነው ይላሉ። የመከላከያ ሰራዊት አባላት በከተማው በብዛት በመገኘት ቤት ለቤት የሚያካሂዱት ፍተሻ ለነዋሪዎች ጭንቀትን ፈጥሮባቸዋል። በክልሉ ፕሬዚዳንት ትእዛዝ …

ጥቅምት ፳፱(ሃያ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በየካ ክፍለ ከተማ በቀድሞ አጠራሩ ከፍተኛ 12 ቀበሌ 18 ለህዝብ አገልግሎት በሚል የተሰራው ጤና ጣቢያ ካለፉት 6 ወራት ጀምሮ የእስረኞች ማጎሪያ ፖሊስ ጣቢያ እንዲሆን መደረጉን ነዋሪዎች ገልጸዋል። የአካባቢው ነዋሪ በቂ የህክምና ቦታ አጥቶ በሚቸገርበት ጊዜ ፣ መንግስት ጤና ጣቢያውን ፖሊስ ጣቢያ ማድረጉ በእጅጉ እንዳሳዘናቸው ነዋሪዎች ለኢሳት ገልጸዋል። በጉዳዩ …

የሳውዲ አረቢያ መንግስት ህገወጥ ነዋሪዎችን በዚህ ሳምንት ተከታትሎ መያዝ ከጀመረ ወዲህ ታዳጊ ወጣት ኢትዮጵያውያን የሚማሩበት የጂዳው ትምህርት ቤት ሥራ መሰናከሉ በርካታ ወላጆችን ስጋት ላይ ጥሏል።

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ) ከጥቅምት 27 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ትቅምት 29 ቀን 2006 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስድስተኛው የአፍሪካ ሚዲያ መሪዎች ፎረም እየተካሄደ ነው፡፡ ፓርቲያችንም ይህንን ጉባዔ በአንክሮ እየተከታተለው ሲሆን በርካታ የአፍሪካ ሚዲያ ባለሙያዎች የፕሬስ ነፃነት ባልተረጋገጠበት፣ የግል ጋዜጦችና መፅሄቶች ተልካሻ ሰበብ እየተፈለገ በሚዘጉበት፣ ጋዜጠኞች ሀገር […]

ጥቅምት ፳፰(ሃያ ስምንት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ክልል በቁጫ ወረዳ የሚማሩ ተማሪዎች ከማንነት እና መብት መከበር ጋር በተያያዘ ያነሱትን ተቃውሞ ተከትሎ በርካታ የአንደኛ እና መለስተኛ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች ትምህርት ማቆማቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል። ተማሪዎቹ በቋንቋችን እንማር፣ በአካባቢያችን የሚታየው የመብት ረገጣ ይቁም የሚሉ ጥያቄዎችን ማንሳታቸውን የሚናገሩት ነዋሪዎች፣ የፌደራል ፖሊስ አካባቢውን ከተቆጣጠረው በሁዋላ ቁጥራቸው ከ25 …

ጥቅምት ፳፰(ሃያ ስምንት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከመሬት፣  ከኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ጋር በተያያዘ በመላ አገሪቱ ለቀረቡ 990 ሺ 627 አቤቱታዎች  መንግስት መልስ ለመስጠት እንደተሳነው መረጃዎች አመልክተዋል። የመልካም አስተዳደር ኮማንድ ፖስት ሴክሬታርያት ፅ/ቤት የ2005 የ6 ወራት የመልካም አስተዳደር ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እንደሚያሳየው ከመሬት፣  ከኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ጋር በተያያዘ በመላ አገሪቱ ለቀረቡ 990 ሺ 627 አቤቱታዎች …

ጥቅምት ፳፰(ሃያ ስምንት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሰሜን ወሎ ዞን በእያንዳንዱ ቀበሌ  10 ሰዎች እየተመለመሉ አሸባሪዎችን ነቅተው እንዲጠብቁ ስልጠና እየተሰጣቸው መሆኑን አርሶ አደሮች ተናግረዋል። በስልጠናው የተነሳ አዝመራችንን እንኳ በወቅቱ ለመሰብሰብ አልቻልንም የሚሉት አርሶደአሮች፣ በአካባቢያቸው ጸረ ሰላም ሀይሎች ሲንቀሳቀሱ ከተመለከቱ ወይም ጸጉረ ልውጦችን ከተመለከቱ ለመንግስት አካላት ሪፖርት እንዲያደርጉ ተነግሮአቸዋል። ለሁለት ሳምንት በሚቆየው በዚህ ስልጠና አርሶአደሮቹ …

ጥቅምት ፳፰(ሃያ ስምንት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በጉራጌ ዞን የእንድብር ከተማ  ነዋሪዎች እንደተናገሩት በከተማቸው ካለፉት 5 ቀናት ጀምሮ መብራት በመጥፋቱ እናቶች እህል አስፈጭተው ልጆቻቸውን መመገብ የማይችሉበት ደረጃ ላይ ደርሰዋል። አቅሙ ያላቸው 30 ኪሎ ሜትሮችን ተጉዘው ወልቂጤ ከተማ በመሄድ እህል ለማስፈጨት መቻላቸውን የሚናገሩት ነዋሪዎች፣ አቅሙ የሌላቸው ግለሰቦች ግን ይህን ማድረግ ባለመቻላቸው ለከፍተኛ ችግር ተዳርገዋል ብለዋል። …

ጥቅምት ፳፰(ሃያ ስምንት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የስዊዝ ሳይንቲስቶችን የምርመራ ውጤት በመጥቀስ አልጀዚራ  እንደዘገበው፤ በያሲር አራፋት ሰውነት ውስጥ ከመጠን ያለፈ ፖሎኒየም የተሰኘ የራዲዮ አክቲቭ ንጥረ ነገር ክምችት ተገኝቷል። ይሁንና እንደ አውሮፓ አቆጣጠር በ2004 ለሞት የተዳረጉት ያሲር አራፋት በፖሎኒየም የተመረዙት መቼ እንደሆነ የሳይንቲስቶቹ ጥናት አያመለክትም። የምርመራ ጥናቱ ውጤት በያሲር አራፋት አስከሬን ውስጥ ከትክክለኛው መጠን   የ …

የስደተኛው ማስታወሻ በተስፋዬ ገብረአብ Yesedetegnaw Mestawesha by Tesfaye Gebreabበይምርሐነ ክርስቶስ ጣራ ላይ የሚገኘው የዳዊት ኮከብዳንኤል ክብረት

ባለፈው ሳምንት ተስፋዬ ገብረ አብ አቡነ ተክለኃይማኖትን በተመለከተ ያነሣቸውን ነጥቦች ማየት ጀምረን ‘የሦስቱን ተክለ ሃይማኖቶች’ ጉዳይ ለዛሬ አቆይተነው ነበር። እንቀጥል።

1) የሰባተኛው መክዘ ተክለኃይማኖት
ተስፋዬ የጠቀሳቸው የሰባተኛው መክዘ ተክለኃይማኖት የሉም። እስካሁንም እንደርሱ ፈጠራቸውን የሚናገሩ እንጂ ማስረጃ ያመጡ አልተገኙም።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ኢትዮጵያ ውስጥ የሽብር ጥቃቶች ሊደርሱ ይችላሉ በሚል የጸጥታ ኃይሎች በተጠንቀቅ እንዲቆሙ በታዘዙበት በኣሁኑ ወቅት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በኣንድ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ላይ በፈነዳ ቦምብ አራት ሰዎች መሞታቸው ተዘገበ።

የጀርመን ባለሃብቶች በልዩ ልዩ ቀውሶች ና በሙስና ስሟ በሚነሳው በአፍሪቃ በአመዛኙ መዋዕለ ንዋያቸውን ለማፍሰስ አይደፍሩም ። ይኽው ጉዳይ ከትናንት በስተያ ቦን ውስጥ በተካሄደው አፍሪቃ ውስጥ የሚሰሩ የጀርመን ባለሃብቶች የምጣኔ ሃብት ማህበር ጉባኤ ላይ ትኩረት ተስጥቶት ነበር ።

አንዳድ የመብት ተሟጋቾች ከሰወስት መቶ ሐምሳ በላይ ኤርትራዉያን ስደተኞች ወደ አዉሮጳ ለመሻገር ሲሞክሩ ላፑዱዛ አጠገብ በደረሰዉ የጀልባ አደጋ ሰምጠዉ ለመሞታቸዉ የአዉሮጳ ሕብረትን የስደተኞች መርሕ ተጠያቂ ያደርጋሉ

ክፍል 1 ሰሞነኛ አዲሱን አመት ተቀብለን ሁለት ወራት ሳንሻገር ጥቅምት 11 ቀን የኢትዮ ምህዳር ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው ወርቁ እና ሥራ አሥኪያጁ ጋዜጠኛ ሚሊዮን ደግነው ክስ ተመስርቶባቸው ፍርድ ቤት ቀረቡ፤ በዳግም ቀጠሮ ዕረቡ ጥቅምት 20 ቀን በሐዋሳ ከተማ ጋዜጠኞቹ ለፍርድ ቤት ቀጠሮ ሄደው በስልት የተቀናበረ በሚመስል ሆኔታ ለመኪና አደጋ ተዳርገው ጋዜጠኛ ኤፍሬም የከፋ አደጋ […]

በእኛ አገር መንግስትና ፓርቲን መነጠል አይቻልም፡፡ህገ መንግስቱ ሳይቀር በብዙ አንቀጾቹ የገዢው ፓርቲ ፕሮግራም ግልባጭ መሆኑ ትስስሩን ላቅ ያደርገዋል፡፡ስለዚህ መንግስት ሲለወጥ ባንዲራ፣ህገ መንግስት፣ብሄራዊ መዝሙር እንቀይራለን፡፡የመንግስት ስርዓት መዘርጋት አለመቻላችን ያመጣብን ጣጣ ልንለው እንችላለን፡፡
ህዝቡ በፓርቲው እምነቱን አጣ ማለት መንግስትንም አያምነውም ተብሎ ሊወሰድ ይችላል፡፡ኢህአዴግ በኢትዮጵያ የመንገስታት ታሪክ አመኔታ በማጣት ረገድ ግምባር ቀደሙ ይመስለኛል፡፡እምነት የጠፋበት አጋጣሚም ከኢህአዴግ የትጥቅ ትግል ቆይታ ጋር የተቆራኘ ነው፡፡ደርግ የያኔዎቹን አማጺያን ወንበዴ፣አገር አስገንጣይ በማለት ይፈርጃቸው ነበር፡፡ከተሜው የደርግን ፕሮፓጋንዳ ሲጋት በመቆየቱ ተጋዳላዮቹ ወደ ከተማ ሲገቡ የተቀበላቸው በፍርሃት ድባብ ታስሮ ነበር፡፡
ትግራይን ነጻ ለማውጣት በረሃ የገቡት የትግራይ ልጆች የህዝቡን አመኔታ ለማግኘት የሐውዜንን ድብደባ ለደርግ የተሳሳተ መረጃ በመስጠት የቪዲዮ ካሜራ በማዘጋጀት የተዋጣለት ፊልም መቅረጻቸውና ለጊዜውም ቢሆን በዚህ ምክንያት የትግራይ ህዝብን ድጋፍ ለማግኘት ቢበቁም እያደር ግን የሐውዜን ምስጢር አፈትልኮ መውጣቱ ተአማኒነታቸው ላይ አሉታዊ ተጽእኖ ፈጥሯል፡፡በግሌ እምነት የሰጧቸው ዋና ዋና ተግባሮቻቸው የሚከተሉት ናቸው
—- በትግራይ መንግስት የወረሳቸውን ቤቶች በመመለስ ለሌሎቹም ይህንን እንደሚያደርጉ ቃል ቢገቡም ቃላቸውን መጠበቅ አለመቻላቸው
—- የአልባንያን ሶሻሊዝም ተጋዳላዮቹን ይግት የነበረው ኢህአዴግ አዲስ አበባን ለመቆጣጠር ከጫፍ በደረሰበት ወቅት የምዕራባዊያንን ድጋፍ ለማግኘት ራሱን ነጭ ካፒታሊስት በማድረግ መጥራት መጀመሩ ርዕዮት አልባ አድርጎታል፡፡ይህም በሚከተለው የፖለቲካ ፍልስፍና አቋመ ቢስ ስላደረገው የገዛ ታጋዮቹን እምነት አሳጥቶታል፡፡
—–በበደኖ፣በአርባጉጉና በአሰቦት በተፈጸሙ አንድ ብሄር ላይ ያነጣጠሩ ጭፍጨፋዎች ኦህዴድና/ኦነግ ሃላፊነት በመውሰድ መጠየቅ ይገባቸው የነበረ ቢሆንም ኢህአዴግ የኦህዴድን እጅ እንደ ጲላጦስ በማጠብ የደሙን ዋጋ ኦነግ ላይ መጣሉ በኦሮሚያ አማኝ አሳጥቶታል፡፡
—– የመምህራን ማህበር ፕሬዘዳንት የነበሩትን መምህር ዶክተር ታዬ ወ/ሰማያትን የ17 ዓመት እስራት ሲያከናንብ በዜና ያስደመጠው ‹‹ታጣቂ ቡድን እያደራጁ ነው››ብሎ የነበረ ቢሆንም በፍርድ ቤት ይህንን ማስመስከር አልቻለም፡፡
—–እነ ርዕዮት አለሙ በታሰረበት ቅጽበት ምሽቱን በኢቴቪ የተደመጠው ዜና ‹‹በመንግስት መሰረተ ልማቶች ላይ አደጋ ለማድረስ ሲያሴሩ ተገኝተዋል፡፡››ተብሏል፡፡ፍርድ ቤት ጋዜጠኞቹ በቀረቡበት ወቅት ግን በኢቴቪ የቀረበው በክሳቸው ውስጥ አልተካተተም፡፡ይህም አመኔታን የሚያሳጣ ድርጊት ሆኖበታል፡፡
—-የ1997 ምርጫን ነጻና ፍትሃዊ አደርጋለሁ በማለት ቃል የገባው ኢህአዴግ ለ200 ሰዎች ዕልቂት መንስኤ የሆነን ኮሮጆ ግልበጣ ፈጽሟል፡፡
—-የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ቢሮን ለአመታት ተቆጣጥረውት የነበሩት አቶ ስዮም መስፍን የኢትዮ ኤርትራ የድንበር ኮሚሽን ፍርድን ለኢትዮጵያ ህዝብ ባስደመጡበት ወቅት ‹‹እንኳን ደስ አለን ብዙ ሺህ የህይወት ዋጋ የከፈልንባት ባድመ ለእኛ ተፈረደች››በማለት ህዝቡ ደስታውን በሰላማዊ ሰልፍ እንዲገልጽ ቢያደርጉም እውነታው ግን ባድመ ለኤርትራ መወሰኗ ነበር፡፡
—- በተለያዮ ቦታዎች ስለተፈጸሙ የቦንብ ፍንዳታዎች መንግስት ተቃዋሚዎችን ተጠያቂ ቢያደርግበትም ዊኪሊክስ በቅርቡ በለቀቀው መረጃ መንግስት ሆን ብሎ እንዲህ አይነት ድራማዎችን እነደሚሰራ አጋልጧል፡፡እስከ እናንተ ለምን መንግስትን እንደማታምኑ ምክንያታችሁን አካፍሉን፡፡

ምንጭ :- START – UNIVERSITY OF MARYLAND – የአሸባሪዎች አጥኚ ቡድን

የአሸባሪ ድርጅቶች መዝገብ
በሃገሩ ቋንቛ መጠሪያው .. አልተገለጸም

የድርጅቱ ስም …..የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር (TPLF)

የሚንቀሳቀስበት አከባቢ … ኢትዮጵያ

የተቋቋመበት ጊዜ ….. አልተገለጸም

የአባላቶቹ ቁጥር/ጥንካሬው … አይታወቅም

መለያው ….. ኮሚኒስት/ሶሻሊስት/ብሄርተኛ/ተገንጣይ

የገንዘብ ምንጩ …. አይታወቅም

የተነሳበት የፖለቲካ ፍልስፍና
ራሱን የትግራይ ንቅናቄ ወይንም ወያኔ በማለት በ1970ዎቹ መጀመሪያ በመንግስቱ ሃይለማርያም አገዛዝ ላይ የተጀመረ ተቃውሞ
በ1975 አከባቢ የትግራይ ነጻ አውጪ በማለት ተመስርቶ በኤርትራ ነጻ አውጪ ስር እየተዳደረ ውጊያ የከፈተ ድርጅት ነው::አላማቸው የአልቤንያን ሞዴል የተከተለ የኮሚኒስት ስርኣት በማስፈን የታለመ…የትግራይን ህዝብ ከደርግ አገዛዝ ነጻ ለማውጣት የተነሳ ነበር::በሜይ 1989 የደርግን ሰራዊት በማሸነፍ ሙሉ ትግራይን መቆጣጠር ችሎ ነበር::በተለያየ ጊዜ ከሻእቢያ ጋር እና በተናጠል በተለያዩ አከባቢዎች የአሸባሪነት ድርጊት ፈጽሟል::
ዝርዝር መረጃውን ከዚህ ድህረገጽ ያገኙታል:- http://www.start.umd.edu/start/data_col … sp?id=4287

በእኛ አገር መንግስትና ፓርቲን መነጠል አይቻልም፡፡ህገ መንግስቱ ሳይቀር በብዙ አንቀጾቹ የገዢው ፓርቲ ፕሮግራም ግልባጭ መሆኑ ትስስሩን ላቅ ያደርገዋል፡፡ ስለዚህ መንግስት ሲለወጥ ባንዲራ፣ህገ መንግስት፣ብሄራዊ መዝሙር እንቀይራለን፡፡የመንግስት ስርዓት መዘርጋት አለመቻላችን ያመጣብን ጣጣ ልንለው እንችላለን፡፡ ህዝቡ በፓርቲው እምነቱን አጣ ማለት መንግስትንም አያምነውም ተብሎ ሊወሰድ ይችላል፡፡ኢህአዴግ በኢትዮጵያ የመንገስታት ታሪክ አመኔታ በማጣት ረገድ ግምባር ቀደሙ ይመስለኛል፡፡እምነት የጠፋበት አጋጣሚም ከኢህአዴግ የትጥቅ […]

ይድረስ ያልኩት በቀጥታ ባይደርሶትም መስማትዎ እንደማይቀር እገምታለሁ፡፡ ሰላም የምሎት ሰላምታ የእግዚአብሄር በመሆኑ ነው፡፡ እንጂ ጫንቃችን ላይ ተጎብራችሁ የዜግነት ክብንርን አውርዳችሁ የዜግነት ክብር የምታዘምሩ በሆናችሁ፣ በብሄር ፣በጎሳ ከፋፍላችሁ…ሰብዓዊ መብታችንን ገፋችሁ..ኑሮን መቋቋም እንዳንችል አድርጋችሁ ለስደት ስለዳረጋችሁን ሰላምስ ማለት አይገባም ነበር፡፡ ለስምም ሆነ አልሆነ በአሁኑ ሰዓት ለሀገሪቷ ጠ/ሚኒስትር በመሆንዎ ነው ይድረስ ያልኩት ለእርሶ ይሁን እንጂ ለሚመለከታቸው ባለስልጣኖች ሁሉ […]

ለሸገር ልጆች፦፦፦
የድሮ አራዶች እነ ድንጋይ ኳሱ
ቦርቸሌን ከርቸሌን በደንብ ያዳረሱ።
ለወሬ ነጋሪ ካሉ የተረፉ፧
ምን አለ ቢያወጉን፧ምን አለ ቢጽፉ፧
ያዲሳባ ልጆች አብሮ አደጎቼ፣
በናፍቆት ባዘኑ እያነቡ አይኖቼ።
ድንገት ሣናስበው እንደተለያየን፣
በሞያሌ ሾልከን በቦሌ እንገባለን፣
አይቀርም አንድ ቀን፦እናወራዋለን፣
በአመቺው ዘዴ እንተርከዋለን፣
ዕድሜና ጤናውን አምላክ ካልነፈገን።፧
ሁል ግዜ ድሪሜ፣
የዘወትር ህልሜ፣
እንዳይነፍገን ዕድሜ።
እስከምንገናኝ በአካል በዐይነ ስጋ፣
ፌስ ቡክ ያገናኘን እርሱም እስኪዘጋ።
*ድንገት ለተለያየነው አብሮ አደጎቼና ወዳጆቼ ሁሉ መታሠቢያ ተፃፈ።
ተዱ ዘአራዳ ከዩጋንዳ

እለተ ሰኞ – ጥቅምት ሊሸኝ ህዳር ሊገባ የቀሩት ጥቂት ቀናት ብቻ ናቸው። በሳውዲ አረቢያ በህጋዊ መንገድ ገብተው ከአሰሪዎቻቸው ጋር ባለመግባባትና ፈርጀ ብዙ በሆነ ምክንያት መኖሪያ ፍቃድ የተበላሸባቸው ማደስ እንዲችሉ ፣ ከአሰሪዎቻቸው ጠፍተው ያለ ህጋዊ ሰነድ በግል ሲሰሩ ለነበሩ ፣ ከአምስት አመታት በፊት በህጋዊ መንገድ በሃጅ በኡምራ ገብተው ወደ ሃገራቸው ሳይመለሱ በህገ ወጥ መንገድ ያለ መኖሪያ […]

በለገጣፉ ፖሊስ ከቢሮው ቅዳሜ ዕለት የተወሰደው ጋዜጠኛ ሚልዮን ደግነውና ሰኞ ማለዳ የስራ አጋሩን የተቀላቀለው ጋዜጠኛ ጌታቸው ወርቁ በእስር ከቆዮ በኋላ ትናንት አመሻሽ እያንዳንዳቸው 600 ብር ዋስ በማስያዝ መለቀቃቸው ታውቋል፡፡ ጋዜጠኞቹ ለእስር የተዳረጉት በኢትዮ ምህዳር ጋዜጣ በለገጣፉ የተፈጸመን የመሬት ሙስና የሚያትት ዜና እና ዘገባ በመስራታቸው መሆኑም ታውቋል፡፡ፖሊስ ቅዳሜ የያዘውን ሚልዮንን በማረፊያ ቤት በማቆየት ቃሉን የተቀበለው ሰኞ […]

ጥቅምት ፳፯(ሃያ ሰባት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከማንነት ጋር በተያያዘ አንዴ ሲሞቅ ሌላ ጊዜ ሲቀዘቅዝ የነበረው የቁጫ ተቃውሞ በዛሬው እለት በሰላም በር ከተማ ተጠናክሮ መካሄዱን ከአካባቢው ያገኘነው መረጃ ያመልክታል። ዛሬ ተቃውሞውን ያካሄዱት ተማሪዎች ሲሆኑ ፣ ተማሪዎችም ላቀረብነው ጥያቄ መልስ የማይሰጠን ከሆነ ትምህርት አንማርም ብለዋል። ተቃውሞውን አስተባብረዋል የተባሉ መምህራንም በአስቸኳይ ስብሰባ ተጠርተው ተቃውሞን የመሩትን እንዲያጋልጡ …

ጥቅምት ፳፯(ሃያ ሰባት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የጸረ ሽብር ግብረሀይል  ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ባስተላላፈው መልእክት አልሸባብና በኤርትራ የሚደገፉ ሀይሎች በመላው አገሪቱ ጥቃት ለመፈጸም እየተዘጋጁ መሆኑን አስተማማኝ መረጃ ደርሶኛል ብሎአል። ዜጎች እራሳቸውን ለመከላከል አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸውም ገልጿል። ሰሞኑን በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ፍተሻዎች ሲደረጉ የሰነበቱ ሲሆን፣ የትናንቱ ማስጠንቀቂያም ይህን ተከትሎ የተሰጠ ነው። መንግስት በኤርትራ የሚደገፉ የሽብር …

ጥቅምት ፳፯(ሃያ ሰባት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የሚኒስትሮች ምክር ቤትን ደንብ ቁጥር 250/2003 ሽሮ እንደገና ለማቋቋም የተዘጋጀ ፤ ተጠሪነቱ ለጠ/ሚኒስትሩ የሆነ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲን ለማቋቋሚያ የወጣው አዋጅ ሀሙስ ይጸድቃል።በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ተዘጋጅቶ በካቢኔ ፀድቆ ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የቀረበው ረቂቅ አዋጅ ኮምፒዩተርን መሰረት ያደረጉ የትራንሰፖርት እና የኢንዱስትሪ የቁጥጥር ስርዓቶች ደህንነት ኮምፒዩተርን መሰረት …

ጥቅምት ፳፯(ሃያ ሰባት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰንደቅ እንደዘገበው በ2004 በጀት ዓመት ባልተሟላ ሰነድ ከ3 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ባላይ ወጪ በማድረጉ በፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት ጠንካራ ትችት የቀረበበት የመከላከያ ሚኒስቴር የሒሳብ መዛግብቱን ዋናው ኦዲተርን ጨምሮ ለማንኛውም አካል ሚስጢር ማድረግ የሚያስችለውን ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቷል። አዲሱ የመከላከያ ሠራዊት ረቂቅ አዋጅ ሰነድ በአንቀጽ 72 ንዑስ አንቀጽ …

ጥቅምት ፳፯(ሃያ ሰባት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከወጣት እስከ አዋቂ ያለው ከግማሽ በላይ የሚሆነው ኢትዮጵያ በልጅነቱ  በቂ ምግብ ሳያገኝ ተጎድቶ እንደሚያድግ የተመለከተው በኢትዮጵያ ይፋ በሆነው the cost of hunger in Ethiopia ጥናት ውስጥ ነው። 67 ከመቶ የሚሆነውና ከ15 አስከ 64 የእድሜ ክልል ውስጥ ያለው ኢትዮጵያዊ ጠንካራ ሰራተኛ ቢመስልም በልጅነቱ ያጣው የተመጣጠነ ምግብ አቀንጭሮትና አቀጭጮት …

ጥቅምት ፳፯(ሃያ ሰባት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሾፈሮቹ ለኢሳት እንደገለጹት ከኢትዮጵያ ወደ ጅቡቲ የሚሄዱና   ከጅቡቲ ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ እቃዎችን የጫኑ ተሽከርካሪዎች ተፈትሸው ለማለፍ ረጅም ጊዜ እንደሚወስዱባቸው ተናግረዋል። ከ10 እስከ 15 ኪሎ ሜትር የሚደርስ የመኪኖች ሰልፍ መኖሩን የሚናገሩት ሾፌሮች፣ በጸሀይ ላይ በሚያደርጉት ጥበቃ በርካታ ሾፌሮች እየተጎዱ መሆኑንም ይገልጻሉ። ፍተሻው የተጀመረው ዛሬ አራት አመት ገደማ ቢሆንም፣ …

ከፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም ከነጻነት ለሀገሬ

በዚህ ዓመት በኢትዮጵያ ሙስናን አስመልክቶ ይሀ ለሰባተኛ ጊዜ ያቀረብኩት ትችት በማዕድኑ ዘርፍ ላይ ያተኮረ ነው፡፡ በሙስና ላይ ያቀረብኳቸውን ሌሎችን ትችቶች “Al Mariam’s Commentaries” የሚለውን ድረ ገጽ በማየት ግንዛቤ መውሰድ ይቻላል፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

በኤሌክትሪክ መጥፋት ምክንያት የአገልግሎት ሰጭ ድርጅቶች ሥራ በተደጋጋሚ እንደሚስተጓጓልና በዕለት ተዕለት ኑሮም በኤሌክትሪክ ማብሰያዎች መጠቀም አስቸጋሪ እየሆነ መምጣቱን ዶቼቬለ የጠየቃቸው አስተያየት ሰጭዎች ተናግረዋል ።

ዉጭ የሚኖሩ የሶማሊያ ተወላጆች ወደሀገራቸዉ ከፍተኛዉን የዉጭ ምንዛሪ እንደሚልኩ ይነገርላቸዋል። ሰሞኑን ግን ታዋቂዉ የብሪታንያ ባንክ ባርክሌ ከሶማሊያ ጋ መስራት አልፈልግም በማለቱ የሶማሊያዉያን ገንዘብ መለዋወጫ ባንኮች ችግር ገጥሟቸዋል።

የኤሌክትሪክ መጥፋት ምክንያት የአገልግሎት ሰጭ ድርጅቶች ሥራ በተደጋጋሚ እንደሚስተጓጓልና በዕለት ተዕለት ኑሮም በኤሌክትሪክ ማብሰያዎች መጠቀም አስቸጋሪ እየሆነ መምጣቱን ዶቼቬለ የጠየቃቸው አስተያየት ሰጭዎች ተናግረዋል ።

የሳውዲ መንግሥት ለ ሁለተኛ ጊዜ የሰጠው የምህረት አዋጅ ቀነ ገደብ ካበቃበት ካለፈው እሁድ አንስቶ በተካሄደ የፖሊስ ክትትል ሁለት ኢትዮጵያውያን መገደላቸውን ሳውዲ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን አስታወቁ ። እነዚሁ ነዋሪዎች እንዳሉት ባለፉት ሶስት ቀናት ከሞቱት ሌላ በርካታ ኢትዮጵያውያን ታፍሰዋል ።

የዴሞክራቲክ ኮንጎ ሬፓብሊክ መንግሥት እና አማፅያኑ «ኤም 23» ቡድን በምሥራቃዊ የሀገሪቱ አካባቢ የሚያካሂዱትን ውጊያ ለማብቃት በካምፓላ ዩጋንዳ ከብዙ ወራት ወዲህ የጀመሩት ድርድር ካለውጤት በተበተነበት ባሁኑ ጊዜ የኮንጎ ጦር በአማፅያኑ ላይ ሙሉ ድል ተቀዳጅቶዋል።

ባለፈዉ ሰሞን የኢትዮጵያ ኤሌትሪክ ኃይል ኮርፕሬሽን ከአንድ የዉጭ ኩባንያ ጋር ከከርሰ ምድር እንፋሎት ኃይል ለማመንጨት እና ከእንፋሎት የሚገኝን የኤሌትሪክ ኃይል ጥቅም ላይ ለማዋል ተስማምቷል። የመሬት ዉስጥ የእንፋሎት ኃይል ምንጭ ምንድን ነዉ?

ዳንኤልክብረት
ተስፋየ ገብረ አብ ‹የስደተኛው ማስተዋሻ› የተሰኘ መጽሐፍ ማውጣቱንና ባነበው መልካም እንደሆነ ገልጦ አንድ ወዳጄ ‹ስስ ቅጅውን› ከ ገረ አሜሪካ ላከልኝ፡፡ ከዚህ በፊት ሌሎች መጻሕፍቱን አንብቤያቸዋለሁ፤ በአጻጻፍ ችሎታው የምደሰተውን ያህል እንደ አበሻ መድኃኒት ነገሩን ሁሉ እርሱ ብቻ የሚያውቀው ምስጢር ስለሚያደርገው፤ በአንዳንድ ጉዳዮችም ሆን ብሎም ሊያናጋቸው የሚፈልግ ኢትዮጵያዊ እሴቶች ያሉ ስለሚመስለኝ፤ ተስፋዬ ለምን እንደዚህ ይጽፋል? እያልኩ የምጠይቃቸው ነገሮች ነበሩ፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

Normal
0

false
false
false

MicrosoftInternetExplorer4

/* Style Definitions */
table.MsoNormalTable
{mso-style-name:”Table Normal”;
mso-tstyle-rowband-size:0;
mso-tstyle-colband-size:0;
mso-style-noshow:yes;
mso-style-parent:””;
mso-padding-alt:0cm 5.4pt 0cm 5.4pt;
mso-para-margin:0cm;
mso-para-margin-bottom:.0001pt;
mso-pagination:widow-orphan;
font-size:10.0pt;
font-family:”Times New Roman”;
mso-fareast-font-family:”Times New Roman”;
mso-ansi-language:#0400;
mso-fareast-language:#0400;
mso-bidi-language:#0400;}

(ፕ/መስፍንወልደ ማርያም)

 

ወያኔና የነፖሊቲካ አጋሮቹ የሚያደርጉትን ለእነሱ የሚመች አከፋፈል ትተን አበሻን ለሁለት እንክፈለው፤ ሆድ ያለውና ሆድ የሌለው፤ ወይም የሚበላና የማይበላ፤ ዛሬ የምናገረው ሆድ ስላለው ወይም ስለሚበላው አበሻ ነው፤ አታውቁት እንደሆነ ተዋወቁት፤ በአጠቃላይ ስንመለከተው ግን የአበሻ ፍቅርም ሆነ ጠብ ለሆድ ነው፤ አበሻን የሚያጣላው፣ የሚያነታርከው፣ የሚያቧጭቀው የሆድ ነገር ነው፤ ለመብላት ነው፤ አንዳንዴም ሎሌውን ለማብላት ነው፤ ግብር ለማግባት ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …