የኢራን ኑክሌር ድርድር

ባለፈዉ ሐምሌ-ሐሰን ሩሐኒ ለፕሬዝዳትነት ሲመረጡ ፕሬዝዳንት ኦባማ ከአራት ዓመት በፊት ለዓለም ሠላም ከገቡት ብዙ ቃል-ኢምንቱን እንኳ ገቢር አላደረጉም።ከሰጡት አያሌ ተስፋ-አብዛኛዉ ከተስፋ አላለፈም።ያም ሆኖ ኦባማ ሲሆን እራሳቸዉን ካልሆነም ቢል ክሊንተንን እንጂ ጆርጆ ቡሽን እንዳልሆኑ አስመስክረዋል።