በኬንያ ያሉ ሶማልያውያን ስደተኞችን ለመመለስ መታሰቡ

የኬንያ እና የሶማልያ መንግሥታት በኬንያ ከለላ ያገኙ ከ500,000 የሚበልጡ የሶማልያ ስደተኞችን ወደ ትውልድ ሀገራቸው ለመመለስ ከተመድ የስደተኞች ጉዳይ ተመልካች መሥሪያ ቤት፣ በምሕፃሩ «ዩ ኤን ኤች ሲ አር» ጋ አንድ ስምምነት መፈራረማቸው ይታወሳል።