የኢትዮጵያዉያን ስደተኞች ጩኸት

በሌሎች ሐገሮች የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን ስደተኞች እየተበደልን ነዉ ይሉ ይዘዋል።ስደተኞቹ እንደሚሉት የየሐገሩ ባለሥልጣናት ያስሯቸዋል፥ ያንገላቷቸዋል፥ ያስፈራሯቸዋል፥ ቀለል ሲል ደግሞ ጉቦ ይጠይቋቸዋል።በየሥፍራዉ ለሚገኙ የኢትዮጵያ ኤምባሲዎችና ለዓለም አቀፍ የርዳታ ድርጅቶች በየጊዜዉ አቤት ቢሉም እስካሁን የረዳቸዉ የለም