የቁጫ ሕዝብ ጥያቄና የሰሞኑ እሥራቶች

በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ክልል በቁጫ ወረዳ፥ ከ 20 በላይ ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል። ከ 100 በላይ ተማሪዎች፥ መምህራንና አርሶ አደሮች መታሠራቸውም ይነገራል።

ከወረዳው ባለሥልጣናት ጉዳዩን ለማጣራት ባባለፉት ሁለት ቀናት ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም።

መለስካቻው አምሃ ተከታዩን ከአዲስ አበባ ልኳል።