ማምሻውን በደረሰን መረጃ

SHARE:

ማምሻውን በደረሰን መረጃ
ሳውዲ አረቢያ በሚገኙ ዜጎቻችን ላይ የደረሰውን በድል እና ስቃይ ለመቃወም አዲስ አበባ በተጠራው ሠላማዊ ሠልፍ የኢትዮጵያ መንግስት ፖሊሶች አሰቃቂ ድብደባና እሰር መፈፀማቸው ቀደም ተብሎ መገለፁ የሚታወቅ ነው፡፡ አሁን በደረሰን መረጃ ቁጥራቸው ወደ 100 የሚጠጉ እስረኞች የተለቀቁ ሲሆን ፤ከነዚህም መካከል ጋዜጠኞች እንደሚገኙበት ለማወቅ የተቻለ ሲሆን የተቀሩት ማለትም፡-
1ኛ. ኢ/ር ይልቃል ጌትነት የፓርቲው ሊቀ/መ
2ኛ. አቶ ስለሺ ፈይሳ የፓርቲው ም/ት ሊቀ/መ
3ኛ. አቶ ወረታው ዋሴ የፓርቲው የፋይናስ ጉዳይ አላፊ
4ኛ. አቶ ጌታነህ ባልቻ የፓርቲው የአደረጃጀት ጉዳይ አላፊ
5ኛ. አቶ ብርሃኑ ተ/ያሬድ የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት አላፊ
6ኛ. አቶ ዮናታን ተስፋዬ የፓርቲው የወጣቶች ጉዳይ አላፊ
7ኛ. አቶ አብታሙ ደመቀ የብሔራዊ ም/ቤት አባል
8ኛ. አቶ ዮናስ ከድር የብሔራዊ ም/ቤት አባል
9ኛ. ዮሴፍ ተሻገር የብሔራዊ ም/ቤት አባል
10ኛ. ወጣት አቤል ኤፍሬም አባል
11ኛ. ሰለሞን ወዳጄ አባል
12ኛ. ፋሲካ ቦንገር አባል
13ኛ. መርከብ ሀይሌ አባል
14ኛ እመቤት ግርማ አባል
15ኛ. አስራት አብርሃም ደራሲና ጻአፊ (በግል)
16ኛ. ዳዊት ፀጋዬ ደራሲና ጻአፊ (በግል)
17ኛ. እየሩስ ተስፋ አባል
18ኛ. ንግስት ወንድኢፍራው አባል
ከላይ በስም ዝርዝ የተገለፁ እስካሁን መስቀል ፍላወርና ፒያሳ ማዘጋጃ አካባቢ በሚገኙ ፖሊስ ጣቢያዎች በፖሊስ ቁጥጥር ስር የሚገኙ ሲሆን ከፍተኛ ደብደባ እየተፈፀመባቸው እንደሆነ ለማወቅ ተችሎአል፡፡ እንዲ አይነቱን ድርጊት ፓርቲው ያስቆጣው መሆኑን እየገለፀ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የሚገኙ በአስቸኳይ እንዲለቀቁ እንጠይቃለን፡፡