የኢትዮጵያ መንግሥት የተራቀቁ የስለላ ሶፍትዌሮችን እየለቀቀባቸው የኮምፕዩተሮቻቸውን ይዘት እንደሚሠርቅ እና የግል ግንኙነቶቻቸውንም እንደሚከታተል በውጭ የሚኖሩ በርካታ ኢትዮጵያዊያን ስሞታዎችን እያሰሙ መሆናቸው እየተነገረ ነው፡፡

አንድ የዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ ነዋሪ በዩናይትድ ስቴትስ ፌደራል ፍርድ ቤት በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ክሥ መመሥረታቸው፤ ሌላ አንድ ሰው ደግሞ ለእንግሊዝ ፖሊስ አቤቱታ ማስገባታቸው ታውቋል፡፡

ከትናንት በስተያ ማክሰኞ ዋሽንግተን ዲ.ሲ. ውስጥ በሚገኝ አንድ ፌደራል ችሎት የተከፈተ ዶሴ ከዚህ የስለላ አድራጎት ጀርባ ያለችው ኢትዮጵያ እንደሆነች ጠቁሞ ከሣሹ የአሥር ሺህ ዶላር የጉዳት ካሣ እንዲከፈለው ጠይቋል፡፡

እንግሊዝ ዋና ከተማ ለንደን ላይ በቀረበ ሌላ ክሥ እዚያ በስደት የሚኖሩትና የግንቦት ሰባት ሥራ…

Share:

እሁድ የካቲት 16 ከጥዋቱ ሶስት ሰዓት ላይ በሳምራት ሆቴል ከራስ ሆቴል ፊት ለፊት – ከዚራ
ሰማያዊ ፓርቲ እሁድ በወቅታዊ ጉዳዮች እና በፓርቲው ዓላማና ፕሮግራሞች ላይ ህዝባዊ ውይይት ያካሄዳል

አዘጋጅ የድሬደዋ ዞን ሰማያዊ ፓርቲ ማስተባበሪያ መዋቅር!

«በባህር ዳር ከተማ፣ ለተጠራው ሰላማዊ ሰልፍ፣ ሁሉም ድጋፉን ይስጥ» ሲል የበርካታ አንጋፍ ደርጅቶች እና ሲቪክ ማህበራት ስብስብ የሆነው ሸንጎ ለመኢአድ እና አንድነት አጋርነቱን ፣ የካቲት 10 ቀን ባወጣዉ መግለጫ ገለጸ። «የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ፣ ከመኢአድ ጋር በመሆን በባህር ዳር ከተማ የካቲት 16 ቀን፣ ለጠራው ሰላማዊ ሰልፍ፣ ያለውን ድጋፍ ይገልጻል» ሲል […]

አንድነት እና መኢአድ የተሳዳቢው ባለስልጣን አቶ አለምነው መኮንን እንጀራ እናት የሆነችውን ብአዴንን ለመቃውም እሁድ በባህር ዳር ሰልፍ መጥራታቸው እንደተስማ፤ እኒያ የአማራ ህዝብ ምንትስ ነው… ቅብርጥስ ነው… ብለው በሞቅታ ውስጥ ያለ ሰው እንኳ የማይሞክረውን የስድብ ውርጂብኝ “በመረጣቸው” ህዝብ ላይ ያወረዱት ሰውዬ፤ ዛሬ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ቀርበው። “ድምፁ የእኔ ነው ስድቡ ግን የእኔ አይደለም… ይህ የተደረገው በኮምፒውተር ቆርጦ […]

ኢሕአዴግ ሕዝብን የሰደቡና ያዋረዱ የብአዴን አመራር አባል አቶ አለምነህ መኮንንን ተጠያቂ በማድረግና ከሃላፊነታቸው ከማንሳት ይቅል፣ ከጎናቸው መቆሙን አረጋገጠ። መኢአድ እና አንድነት ፣ በአማራዉ ክልል የሚኖረው ሕዝብ ላይ ከአንድ መሪ የማይጠበቅ አሳዛኝ፣ ንቀት አዘል አስተያየት የሰጡት አቶ አልምነዉ መኮንን ከሃላፊነታቸው እንዲነሱና ለፍርድ እንዲቀርቡ መጠየቁ ይታወቃል። ኢሕአዴግ ፓርቲዎቹ ያቀረቡትን ጥያቄ አናንቆ፣ ምንም ምልሽ ባለመስጠቱ፣ አንድነት እና መኢአድ […]

የካቲት ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአማራ ክልል የክልሉ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የብአዴን ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አለምነው መኮንን በአማራ ህዝብ ላይ የሰነዘሩትን ዘለፋ ተከትሎ የተነሳውን ተቃውሞ ለማብረድ የብአዴን የወጣቶች ሊግ ለአባለቱ  የስልጠና እና የግምግማ ስራ በባህር ዳር ፤ ደሴ እና ጎንደር እያከናወነ ነው። የካቲት 16  አንድነትና መኢአድ በጋራ የጠሩትን ሰልፍ ተከትሎ በባህር …

የካቲት ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢትዮጵያን አየር መንገድ ንብረት የሆነውን ቦይንግ 767 አውሮፕላን  በመጥለፍ ጄኔቫ ያሳረፈው ሃይለመድህን አበራ፣ ከጸባዩ በተጨማሪ ብቃት ያለው አብራሪ መሆኑን ግለሰቡን የሚያውቁ ሰዎች ለኢሳት ተናግረዋል። ከስልጠና ጀምሮ የሚያውቁት ጓደኞቹ እንደተናገሩት ሃይለመድህን ለሰዎች ህይወት የሚጨነቅና ጥንቃቄ የሚያደርግ፣ አውሮፕላኑን ከጠለፈ በሁዋላ ተሳፋሪዎች ሳይቸገሩ እንዲያርፍ ማድረጉ የፓይለቱን ብቃት ያሳያል ብለዋል። …

ካምፓላ ተለጣፊ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ሊቋቋም ነው።
የወያኔ ቆንስላ በዩጋንዳ ቅዳሜ ህወአት ውብድናና የጀመረበትን ሠላሣ ዘጠነኛ ዓመት ሲያከብር ተለጣፊ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ በአምሣሉ ለመፍጠር በፓስፖርት የሚኖሩን ኢትዮጵያዊያን ተጋዳላይ ፍሬወይኒ ዮሐንስ በስልክ እየጠሩ ሲሆን ስደተኛ ነን ባዮቹን ደግሞ አቶ አምሣሉ እንዲገኙ እያባበለ መክረሙን ከውስጥ አዋቂዎች የተገኘው መረጃ ጠቆመ።
ወያኔ ከትግራይ መቀሌ ውጪ መከበር የማይገባውን ቀን ካምፓላ ላይ ማክበሩ የሐገሪቱን ካዝና
እንደፈለገ እንደሚጫወትበትና እስከዛሬ በታሪክ ውንብድና የጀመረበትን ቀን በማክበር ሐፍረት የማይሠማው
ህወአት ብቻ መሆኑን ሐገር ወዳዶች ይናገራሉ።
ስደተኞች ወያኔ ኤንባሲ የሚሄዱበት ምንም አይነት ምክንያት እንደሌላቸው አውቀው ከፈንጂ ወረዳ እንዲርቁ መንገር እንደሚገባና እግራቸውን ለማይሠበስቡ ስደተኞች ግን ለዩጋንዳ መንግስትና ለዩኤንኤችሲአር በማጋለጥ እውነተኛ ስደተኞች ደህንነታቸውን ማረጋገጥ እንደሚገባቸው በስልክ ያነጋገርናቸው ወገኖች ከስፍራው ገልፀውልናል።

የካቲት ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አባላቱ ቅሬታቸውን የሰነዘሩት በ2ኛው የመከላከያ ሰራዊት በአል ላይ ነው። በቀን አንድ ዳቦ እና ሁለት ጭልፋ ወጥ ለእራትም በተመሳሳይ ሁኔታ የሚቀርብላቸው የመከላከያ ስራዊት አባላት፣  የቀን የምግብ ፍጆታ በጀታቸው ከህግ ታራሚዎች ያነሰ ነው። ወታደሮቹ  በቀን ስምንት ብር ከሃምሳ ሳንቲም በሆነ የምግብ በጅትየሚተዳደሩ ሲሆን፣ የሚቀርብላቸውን ዳቦ እንኳን  ለመብላት እንደሚቼገሩ …

የካቲት ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዘጋርድያን እንደዘገበው የ18 አመቷ ወጣትና ነፍሰጡሩዋ ኢትዮጵያዊት በዝሙት ተግባር በመከሰሷ በድንጋይ ተወግራ ልትገደል እንደምትችል የምስራቅ አፍሪካ የሴቶች ስትራቴጂክ ኔትወርክ ወይም ሲሃ የተባለውን ድርጅት በመጥቀስ ዘግቧል። የ9 ወር ነፍሰ ጡሩዋ ወጣት በእስር ቤት ውስጥ ያለምንም ምንጣፍ በባዶ ኮንክሪት ላይ እንደምትተኛ ጋዜጣው ዘግቧል። ኢሳት ከወር በፊት ዜናውን ይፋ …

የካቲት ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአማጺው መሪ ሪክ ማቻር እና በ ፕሬዚዳንት ሳል ቫኬር ያለው ልዮነት እየስፋ መሆኑን ቅርበት ያላቸው ምንጮች በመግለጽ ላይ ይገኛሉ:: ከትላንት በስትያ በነዳጅ የበለጸገችው የአፐር ናይል ስቴት ዋና ከተማ ማላካል  ከባድ ጦርነት ተካሂዷል። ወደ ማላካል የሚደረጉ  የአየር በረራዎችች መሰረዛቸውንና አካባቢው በከባድ ጦርነት ውስጥ መሆኑን ማረጋገጥ ተችሎል:: ማላካል የተባለው ቦታ …

በደቤብ ኢትዮጵያ ዳውሮ ዞን የዲሳ እና ዙሪያው አካባቢ ኗሪዎች የወረዳ መስተዳድር እንዲመሰረትላቸው እየጠየቁ ነው።
የመንግስት ባለስልጣናት ግን አካባቢው ለወረዳ መስተዳድር መሰረታዊ መመዘኛዎችን ኣያሟላም እያሉ ነው። በዚሁ ምክኒያት ተቃውሞ ያሰሙ

የጀርመኑ ዓለም አቀፍ የፊልም መድረክ “በርሊናለ” ዘንድሮ ለ 64ኛ ግዜ የተካሄደ ሲሆን በዓለም ዙሪያ በተለያዩ አገሮች የተሠሩ ከ5000 በላይ ፊልሞች ቀርበዉ በመድረኩ ከ 400 በላይ ፊልሞች ታይተዉበታል። ለአስር ቀናት የዘለቀዉ የጀርመኑ ዓለም አቀፍ ፊልም ፊስቲቫል በኢትዮጵያዉያን የተሠራ ፊልምን፤ አቀርቦ ሸልሞአል።

የአውሮፓውሕብረት፣በዝብምባብዌላይጥሎትየነበረውንማዕቀብበአብዛኛውእንዲነሣአድርጓል።ከፕሬዚዳንት
ሮበርት ሙጋቤና ባልተቤታቸውበስተቀር ፰ የመንግሥትአባላትየሆኑፖለቲከኞችወደአውሮፓውሕብረትአባልሃገራት
መግባትይፈቀድላቸዋልተብሏል።የአውሮፓው ሕብረት በዝምባባዌ ላይ ማዕቀብ

አቶ አልምነው መኮንን በ«አማራዉ» ላይ በተናገሩት የንቀት አባባሎች ምክንያት፣ ባለስልጣኑ ከሃላፊነታቸው እንዲነሱና ለፍርድ እንዲቀርቡ፣ አንድነት እና መኢአድ በመጠየቅ የክልሉ መስተዳደር በሚገኝበት በባህር ዳር ከተማ እሁድ የካቲት 16 ቀን ሰላማዊ ሰልፍ መጠራቱ ይታወቃል። በባህር ዳር ቅስቀሳው እየተፋፋመ ባለበት ወቅት፣ አቶ አልምነዉ መኮንን ማስተባበያ በኢቲቪ እየተላለፈ መሆኑ የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት ፌስቡክ የሚሊየነሞች ድምጽ ለነጻነት ፌስ ቡክ ፔጅ […]

አንድነት እና መኢአድ በባህር ዳር ቅስቀሳቸውን ቀጥለዋል። ሕገ መንግስቱን በመጻረር ፣ ዜጎች ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብታቸውን በመገፋት የብአዴን ካድሬዎች የተለያዩ ምክንያቶ እያቀረቡ የሰልፉ አስተባባሪዎች የማገት፣ የማስፈራራት ሥራ እየሰሩ እንደነበረ የደረሰን ዜና ይጠቁማል። አንድነት እና መኢአድ በባህር ዳር ቅስቀሳቸውን ቀጥለዋል። ሕገ መንግስቱን በመጻረር ፣ ዜጎች ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብታቸውን በመገፋት የብአዴን ካድሬዎች የተለያዩ ምክንያቶ እያቀረቡ የሰልፉ […]

የአማራውን ህዝብ ለሃጫም ልጋጋም ….. በማለት በመርዛም ሕወሓታዊ ምላሱ መርዝ ብሎ የተሳደበው የብኣደኑ የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ እና የክልሉ ምክትል ርእሰ መስተዳደር የባህር ዳር የተቃዋሚዎችን ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ጥሪ ተከትሎ አማራውን አልሰደብኩም የሚል ንግግር ማድረግ መጀመሩ በድርጅቱ ውስጥ የገባውን ድንጋጠ ያመለክታል።

አቶ አለምነው መኮንን የጭንቁ ቀን ሲመጣ “አማራውን አልሰደብኩም” ብሎ በክልሉ መገናኛ ብዙሃን መለፍለፍ መጀመሩን እየሰማን ነው፤ ሰውየው የአንድነትና የመኢአድ የተቃውሞ ሰልፍ 2 ቀናት ብቻ ሲቀሩት ለማስተባበል መሞከሩ የብአዴንን ውጪ ነብስ ግቢ ነብስ ያሳያል ።

የአንድን አገር ህዝብ የማይለወጠው የጋራ ማንነቱ ዜግነቱ ነው፡፡ ብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች የግለሰቦች ጥርቅም እስከሆኑ ድረስ ኦነግ፣ ኦብነግ፣ ግንቦት ሰባት፣ ጽንፈኛ፣ አሸባሪ፣ ኪራይ ሰብሳቢ፣ ተላላኪ፣ ኒዮ ሌንራል፣…….የሚባሉት መለጠፊያዎች እየተሰጧቸው አሳራቸውን የሚበሉት ‹‹ብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች›› ናቸው፡፡

ምንም ያህል ልዩነት ቢኖረው የአንድን አገር ህዝብ የማይለወጠው የጋራ ማንነቱ ዜግነቱ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን ከሌሎች ህዝቦች ይልቅ የሚያመሳስሉን፣ የምንጋራቸው በርካታ እሴቶች አሉን፡፡ ከምንም በላይ ደግሞ ኢትዮጵያውይነታችን (ዜግነታች) የጋራችን ነው፡፡ ብሄር፣ ብሄረሰብ፣ ህዝብ ተብሎ በጅምላ ዜግነት ሊሰጠው አይችልም፡፡ አንድ ሰው ኢትዮጵያዊ ለመሆን መደራጀት አይጠበቅበትም፡፡

በሚሊዮን የሚቆጠሩ ግለሰብ ኦሮምኛ ተናጋሪዎችን ‹‹ኦሮሞ››፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩትን ግለሰብ አማርኛ ተናጋሪዎች ‹‹አማራ››፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ግለሰብ ሶማልኛ ተናጋሪዎን ‹‹ሶማሊ››…….እያሉ ነው ኢትዮጵያውያንን ‹‹ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች›› በሚል አዲስ ማምነት የሚደረድሩን፡፡ ብሄር፣ ብሄረሰብ፣ ህዝብ የሚባለው ከግለሰቦች እንጅ ከምንም የመጣ አይደለም፡፡ የብሄር ብሄረሰቦች መብት መከበር ካለበት መጀመሪያ መቅደም የሚገባው የስሪታቸው የግለሰቡ መብት ነው፡፡

ኦሮሞ፣ አማራ፣ትግሬ….› እየተባሉ የተቦደኑት ህዝቦች አንድ አይነት አይደሉም፡፡ እንዲያውም ኦሮምኛ ተናጋሪው ‹‹ኦሮሞ›› ከሚባለው ውጭ ከአማርኛ ተናጋሪው ጋር የሚጋራው በርካታ ማንነቶች ይኖሩታል፡፡ አማርኛ ተናጋሪው ‹‹አማራ›› ከተባለው ይልቅ ከኦሮምኛ ተናጋሪው ጋር የሚያመሳስሉት በርካታ ማንነቶች ይኖሩታል፡፡ ለአብነት ያህል ትግርኛ፣ አማርኛ፣ ኦሮምኛ፣ ሶማሊኛ፣ ….ተናጋሪው ህዝብ ከቋንቋውም በላይ አንዱ የሌላውን ድንበር ተሸግሮ ከሌላኛው ቋንቋ ተናጋሪ ጋር በእምነት፣ በፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ሌሎች ገመዶች ይገናኛል፡፡ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የአንድ ብሄር ሰዎች አይደሉም፡፡ የሙስሊሙ እንቅስቃሴ እንዲህ እስካሁን በጥንካሬ የዘለቀው በድንበር ተሸጋሪው ማንነቱ እንጅ በጠባብ ‹‹የብሄር›› ማንነት ታጥሮ አይደለም፡፡ ኦርቶዶክሶቹ፣ ፕሮቴስታንቶቹ፣ ካቶሊኮቹ በ‹‹ብሄር›› የታጠሩ አይደሉም፡፡

የአንድ ‹‹ኦሮሞ፣ አማራ፣ ትግሬ…›› የእምነት፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ…መብቱ በግለሰብ ደረጃ ካልተጠበቀለት በስተቀር የ‹‹ኦሮሞ፣ አማራ፣ ትግሬ…›› መብት ሊጠበቅ አይችልም፡፡ ችግሩ የ‹‹ብሄርና›› ሌሎች ማንነቶችን የሚጠቀሙ የፖለቲካ ቡድኖች ከግለሰብ ማንነት ይልቅ ጥቅል ማንነትን የሚያስቀድሙት ለራሳቸው ጥቅም ሲሉ መሆኑ ነው፡፡ በ‹‹ኦሮሞ፣ አማራ፣ ትግሬ፣ሶማሊ…….›› ስም በጅምላ ከመነገድ ያለፈ ስለ እያንዳንዱ ህዝብ አያስጨንቀቃቸውም፡፡ 30 ወይንም 40 ሚሊዮን የአንድ ‹‹ብሄር›› ህዝብ በአንድ ጉዳይ ሊከፋ አይችልም፡፡ ቢያንስ ከገዥዎች ጋር ሆኖ የሚጠቀም አይጠፋም፡፡

ከፊሉን በእምነቱ፣ ከፊሉን በኢኮኖሚው፣ ከፊሉን እናከብርልሃለን በሚሉት ቋንቋው፣ ከፊሉን በነጻነቱ…. እያሉ ግን ሁሉንም ይጨቁኑታል፡፡ ሁሉንም ይጎዱታል፡፡ መስፈርቱ በብሄር ሳይሆን በግለሰብ ቢሆን ግን የሚድበሰበስ ነገር አይኖርም፡፡ ሁሉም የግለሰብ መብቶች እስከተከበሩ ድረስ የአገሪቱ ህዝብ መብት ይከበራል፡፡ የግለሰብ መብት ካልተከበረ ግን የማንም መብት ሊከበር አይችልም፡፡ ብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች የግለሰቦች ጥርቅም እስከሆኑ ድረስ ኦነግ፣ ኦብነግ፣ ግንቦት ሰባት፣ ጽንፈኛ፣ አሸባሪ፣ ኪራይ ሰብሳቢ፣ ተላላኪ፣ ኒዮ ሌንራል፣…….የሚባሉት መለጠፊያዎች እየተሰጧቸው አሳራቸውን የሚበሉት ‹‹ብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች›› ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድን አስተድደራዊ ብልሹነት እና የዘረኝነት አድልዎን ያማከለ የኢትዮጵያን እና የአማራን ጉዳይ ያካተተ አንገብጋቢ አጀንዳዎች ይዞ እንዲሁም በግሉ ከጀርባው አልወርድ ያሉትን የወያነ ቅማሎች ደህንነቱን የሚያበረውን አውሮፕላን በመጥለፍ አሊያም በማገት በሰላም ጀነቭ ያሳረፈው ረዳት አብራሪ ሃይለመድህን የተመለከቱ ዘገባዎች መውጣታቸውን እንደቀጠሉ ነው።

በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን ዘንድ ድጋፍ የተቸውረው ይህንን የጠለፋ /እገታ ጉዳይ በተመለከተ የወያነው መንግስት ለውጥ የሚያደርግበት እና ለፖሊሲዎቹ አፋጣኝ አትኩሮት ሊሰጥ ይገባዋል ከሚሉ የስር አቱ ደጋፊዎች ጀምሮ እስከ የሃገሪቷን የሰብ ኣዊ መብት ጥሰቶች እያነሱ የፖለቲካው ምህዳር ጥበቱን በዘረኝነት ልይ የተመረኮዘን የኢኮኖሚ ብዝበዛውን እና የኢትዮጵያን ህዝብ ወደ ጎን ያገለለውን ስር ኣት ማስረጃ እያጣቀሱ በመተቸት ጠላፊውን የደገፉ እንዲሁም በተሰቡን ጨምሮ ጀግና እስከማለት የደረሱበት ሁነታ ተከስቷል።

እስካሁን ድረስ ጠላፊውን በተመለከተ ምንም አይነት ዝርዝር ጉዳዮችን ያልተናገረው የስዊዘርላንድ ፖሊስ አይሮፕላኑ በተጠለፈበት ሰኞ የወጡ ዘገባዎች እንደሚይመለክቱት ረዳት አብራሪው የደህንነት ስጋቶች እንዳሉበት እና በሃገሪቱን ያለው ስር ኣት የሚከተላቸው የዘረኝነት አስተዳደር እና የሃይማኖት ጣልቃ ገብነት እንዲሁም የአየር መንገዱ የአስተዳደር ብልሹነት የፈጠሩት እንደሆነ ሳይታለም የተፈታ ጉዳይ ነው።

የወያነ ስር ኣት የቅርብ ሰዎች የረዳት አብራሪውን ስም እና የበተሰቡን ስም ጥላሸት ከመቀባት ጀምሮ ጉድዩን ወደ ዘረኝነት የወሰዱትም ጠባቦች ሲኖሩ ወደ ወያነ ጠጋ ብለው ለመኖር የፈለጉም ሃይለመድህንን አብጠልጥለዋል ሆኖም አንዳቸውም አልተሳካላቸውም።….

ጉዳዩን በቅርብ እየተከትተለ ያለው የኢሳት ተለቭዥን በተሰቦቹን ወዳጆቹን ጓደኞቹን እና የአየር መንገድ ሰዎቹን በማነጋገር ሰፊ ጊዘውን ሰቷል። ያነጋገራቸው የበተሰቡ አባላት ሃይለመድህንን በመደገፍ የሃገር ጉዳይ የሚያንገበግበው ጀግና ሲሉት ወዳጆች እና ጓደኞቹ የሃይለመድህንን መልካምነት በይፋ መስክረዋል። እንዲሁም የአየር መንገዱ ሰራተኞች የሃይለመድህንን ታታሪነት እና ጸባየ ሸጋነት አረጋግጠዋል።

እንዲሁም ቢቢኤን ራዲኦ ኢትዮጵያውያን በአውሮፓ ጠበቃ እንዳቆሙረት በፕሮግራሙ ላይ ዘግቧል። የጠለፋውን ሁነታ ተከትሎ በኢትዮጵያ አየር መንገድ በበረራ ደህንነት ስራ ውስጥ ለረጅም ጊዜ ያገለገለውና በክትትልና ደህንነት ስጋት ከአመት በፊት ድርጅቱን ለቆ በስዊዘርላንድ ጥገኝነት የጠየቀው ሚካኤል መላኩ ከኢሳት ጋር ባደረገው ሰፊ ቃለምልልስ፣ በድርጅቱ ውስጥ ያለውን ዘረኝነትና የአስተዳደር መበላሸት አጋልጧል።

ወጣቱ ፓይለት የተለያዩ አውሮፕላኖችን አብርሮ ልምድ ካካበተ በሁዋላ 767 የተባለውን አውሮፕላን በረዳት ፓይለትነት ለማብረር መቻሉን የገለጸው ሚካኤል፣ በዚህ ደረጃውም ከፍተኛ የሆነ ክፍያ የሚከፈለው በመሆኑ የገንዘብና የምቾት ችግር እንደማያጋጥመው ገልጿል። አብራሪው የ3 ሺ ሰራተኞችን ዋይታ ይዞ መምጣቱን የሚናገረው ሚካኤል፣ የኢትዮጵያ ህዝብ ከጎኑ ሊቆምለት ይገባል ብሎአል

የካፒቴን ሃይለመድህን የጠላፋ ምክንያት አወዛጋቢ ሆኖ በቀጠለበት ሁኔታ ፣ ካፒቴኑ ከአጎቱ ከዶ/ር እምሩ ስዩም ሞት ጋር በተያያዘ እየተረበሸ መምጣቱን አቶ አሳምነው መላኩ የተባሉ የካፒቴን ሃይለመድህንን አጎት በመጥቀስ በአሶሺየትድ ፕሬስና በክርስቲያን ሞኒተሪንግ ተዘግቧል። አዲስ አበባ የኑቨርስቲ በድረገጹ ባሰፈረው መረጃም የዶ/ር እምሩ አሟሟት መንስኤ እንግዳ እንደሆነ ጠቅሷል። ኢሳት በበኩሉ ከዘመዶቹ ባገኘው መረጃ መሰረት ዶ/ር እምሩ በሰዎች መገደላቸውን አንዳንድ የቤተሰብ አባሎች እንደሚያምኑና አጎቱን ማን ገደላቸው የሚለው ጥያቄ አለመመለሱን ዘግቧል።

ይሁን እንጅ የዶ/ር ስዩም ባለቤት ነኝ ያሉ ወ/ሮ አንጓች ቢተው ባለቤታቸው የሞቱት ታህሳስ ወር ላይ ጧት ፍላሚንጎ አካባቢ ተሳፍረው ቤተመንግስት አካባቢ ሲደርሱ ከጠዋቱ 2፡30 ላይ መሞታቸውን፣ የሞታቸውም ምክንያት በልብ ህመም ምክንያት መሆኑን በመግለጽ ሰው ገደለው ተብሎ የቀረበው ዘገባ ስህተት መሆኑን አስረግጠው ተናግረዋል። ወ/ሮ አንጓች ካፒቴን ሃይለመድህን በአጎቱ ምክንያት እንደተረበሸ ተደርጎ በሚሰጠውን አስተያየት ዙሪያም ምንም የሚያዉቁት ነገር እንደሌለ፣ ከካፒቴኑ ጋር በአመት በአል ወቅት ካልሆነ ብዙም እንደማይገናኙ ተናግረዋል።

ካፒቴን ሃይለመድህን ከአጎቱ ሞት ጋር በተያያዘ ይረበሽ ነበር በማለት መግለጫ የሰጡትን ሌላውን አጎት አቶ አሳምነውን ለማግኘትና ማብራሪያ ለመጠየቅ የተደረገው ሙከራ አልተሰካም። በጉዳዩ ዙሪያ አስተያየቱን የጠየቅነው ዘጋቢያችን፣ ዶ/ር ስዩም በልብ ህመም መሞታቸውን ካፒቴን ሃይለመድህን የሚያውቅ ከሆነ፣ የሚጨነቅበት ምክንያት አይኖርም፣ ከአጎቱ ሞት ጋር በተያያዘ የሚሰጠው አስተያየትም ትክክል ላይሆን ይችላል ብሎአል።

ጠላፊው አውሮፕላኑን ወደ ጄኔቭ ከመውሰዱ በፊት ሮም ላይ ማረፉን የገለጸቸውን ዜና በተመለከተ አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች አውሮፕላኑ ሮም ላይ እንዳላረፈ በመግለጽ አስተያየታቸውን የገለጹ ሲሆን፣ ኢሳት በድጋሜ ተሳፋሪዋን ባነጋገረበት ወቅት፣ በአቋሟ በመጽናት አውሮፕላኑ ሮም ላይ አርፎ ወደ ሚላን ሲያቀና መጠለፉን፣ የበረራ ትኬቱዋን ለኢሳት በመላክ ትክክለኛ መረጃ መስጠቱዋን በድጋሜ ተናግራለች።

ጉዳዩ እንዴት ሊሆን ይችላል ስንል ጥያቄ ያቀረብንለት ሚካኤል መላኩ አውሮፕላኑ ሮም ላይ አርፎአል በሚል የተላለፈው ዘገባ ትክክለኛ ነው ብሎ እንደሚያምን የአየር መንገዱን አሰራር በመግለጽ አስረድቷል
የመንግስት የኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት ሃላፊ የሆኑት አቶ ሬድዋን ሁሴን አውሮፕላኑ ካርቱም ላይ ማረፉን ፣ ቀጥሎ ደግሞ ካርቱም ላይ ማረፍ የነበረበት ቢሆንም ተጠልፎ ማረፍ ሳይችል ቀረ ብለው የገለጹት የአየር መንገዱን አሰራር ሳይዉቁ የተናገሩት አሳፋሪ ንግግር ነው ብለዋል። በአየር መንገድ የበረራ ታሪክ አውሮፕላኑ በቀጥታ ከአዲስ አበባ ወደ ሮም እንደሚያርፍ በመግለጽ ካርቱም ላይ ማረፍ ነበረበት የሚለውም ትክክል አይደለም ብሎአል።

አለማቀፍ የመገናኛ ብዙሃን ፓይለቱ አውሮፕላኑን ይዞ ጄኔቫ ላይ በመሽከርከር ለማስፈራራት ሙከራ አድርጎ ነበር በማለት ዘገባዎችን አቅርበዋል። ይሁን እንጅ እንደ ሚካኤል ገለጻ ማንኛውም አውሮፕላን ከማረፉ በፊት ነዳጅ ማቃጠል ስለነበረበት ፓይለቱ ይህን ማድረጉን እንዲሁም ለ10 ደቂቃ ጉዞ ብቻ የሚበቃ ነዳጅ ነበረው ተብሎ በመገናኛ ብዙሃን የቀረበውም ትክክል ያልሆነና በአየር መንገዱ ህግ መሰረት ለ2 ሰአት በረራ የሚያበቃ መጠባበቂያ ነዳጅ እንደሚይዝ ገልጿል። — at Minilik Salsawi.

Share:

በክፍል.1 ላይ ቃል በገባሁት መሰረት ዛሬ የካቲት 12 ሰማዕታት ሐውልት ስር ሆኜ «ስለነዚያ» ወጣቶችና በዙሪያቸው ስለነበሩ የአርበኝነት ተጋድሎው አጋሮች በጥቂቱ አወሳልሃለሁ፡፡ አዎ፣ ዛሬ ስለ የካቲት 12 ቀን፣ በዋነኛነትም ስለ አብርሃ ደቦጭና ሞገስ አስግዶም እንዲሁም ሌሎች ከጉዳዩ ጋር የተገናኙ የታሪኩ ዋና ዋና ተዋናዮችና ነጥቦችን እያነሳን እንጥላለን፡፡

የካቲት 12/1929 ዓ.ም የአዲስ አበባ ህዝብ የግፍ እልቂት በተነሳ ቁጥር ሞገስ አስግዶም እና ጓደኛው አብርሃ ደቦጭ አብረው ይነሳሉ፡፡ ሁለቱም ወጣቶች የኤርትራ ተወላጆች ናቸው፡፡ ሁለቱም ከኤርትራ ወደ አዲስ አበባ በጣሊያኖች አማካኝነት እንዲመጡ ከተደረጉ በሗላ ሞገስ በዳግማዊ ምኒልክ ት/ቤት፣ እንዲሁም አብርሃ በተፈሪ መኮንን ት/ቤት ገብተው መማር ቀጠሉ፡፡ እዚህ ላይ መረሳት የሌለበት ነጥብ ወጣቶቹ ወደ አዲስ አበባ የመምጣታቸው ምስጢር ለፋሽስት ጣሊያን አስተርጓሚና ሰላይ ሆነው እንዲያገለግሉ ታስቦ እንደነበር ነው (ፈረንሳይኛ፣ ጣሊያንኛ፣ እንግሊዝኛና በመጠኑ ጀርመንኛ እንዲሁም የሀገሬውን ቋንቋ ይናገሩ እንደነበር ተጠቅሷል)፡፡

በሌላ ወገን ደግሞ የወጣቶቹን ወደ አዲስ አበባ መምጣት በወቅቱ በፋሽስት አስተዳደር ስር በነበረችው ኤርትራ ያለውን ጭቆና ገፊ ምክንያታቸው እንደነበር የሚጠቅሱ አሉ፡፡ በተለይም ወጣት ሞገስ ኢትዮጵያን አብዝቶ ይወድና በኢትዮጵያዊነቱ የሚኮራ ነበር፡፡ ስለሆነም ወደ አዲስ አበባ ለመምጣት የዘወትር ፍላጎቱ ሆኖ ቆይቷል፤ «ሞገስ ጣሊያንን ሳያስፈቅድ የቅኝ ግዛት ድንበር አቋርጦ ወደ ኢትዮጵያ ገባ» እንዲል፡፡ ኸረ እንዲህም ተመስክሮለታል፤ «His heart and mind was for Ethiopia.»፤ ከዚህ ነጥብ መረዳት እንደሚቻለው ኢትዮጵያ በህልሙም በእውኑም ሞገስ ውስጥ ነበረች፡፡

ሞገስና አብርሃ ትምህርታቸውን እንዳጠናቀቁ ሞገስ በመሬት ይዞታ መስሪያ ቤት ጸሐፊ ሆኖ ሲቀጠር አብርሃ በበኩሉ በጣሊያን ሌጋሲዮን ተቀጥሮ መስራት ቀጠሉ፡፡ በጊዜው በጣሊያን ፖለቲካ ውስጥ ከሞገስ ይልቅ አብርሃ ብዙ ስራዎች ሲሰራ ነበር፤ ሞገስ ባብዛኛው የአብርሃ ረዳት ነበር ማለት ይቻላል፡፡ የካቲት 12/ 1929 ዓ.ም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ (ያኔ ገነተ ልዑል ቤተ መንግስት) በግራዚያኒ ላይ አብርሃና ሞገስ ቦምብ ጥለው አቆሰሉት ከመባሉ በፊት በጣሊያን ላይ አኩርፈው ተቀምጠዋል ከተባሉ መኳንንት ጋር ወጣቶቹ ምስጢራዊ ግንኙነት ሲያደርጉ ቆይተዋል፡፡

በነገራችን ላይ የካቲት 12 ግራዚያኒንና ሌሎች የፋሽስት ወታደራዊ ባለስልጣናትን ለመግደል በተሸረበው ሴራ ዋና ተዋናዮቹ ሞገስና አብርሃ ብቻ አልነበሩም፡፡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት በእለቱ ለተፈጸመው ጸረ ፋሽስት ድርጊት ከጽንስሱ ጀምሮ ስድስት ኢትዮጵያዊያን ስማቸው ይነሳል፡፡ እነዚህም ቀደም ብለን የጠቀስናቸው ሞገስና አብርሃ፣ በመምህርነት ሞያ ይሰራ የነበረው ስብሃት ጥሩነህ፣ ስምዖን አደፍርስ፣ ቤጅሮንድ ለጥይበሉ ገብሬና ባሻህውረድ ሃብተወልድ ነገሩን አውጥተው አውርደው ጥቃቱ እንዲፈጸም ታትረዋል፡፡ (ስምዖን አደፍርስ እነ አብርሃን ከጥቃቱ በሗላ በታክሲ በመሸኘት እንዲሸሹ ያስቻላቸው እሱ መሆኑን ስላሴ ካቴደራል በሚገኘው የመቃብር ስፍራው ላይ የሰፈረው ጽሑፍ ይናገራል፡፡)
የሚገርመውና የሚደንቀው ግን ስደት ላይ የነበሩት ንጉሰ ነገስት ቀዳማዊ ሃይለስላሴ በሴራው ላይ እጃቸው ነበረበት መባሉ ነው፡፡

ስደተኛው ንጉስ በየካቲት 12ቱ ሴራ እቅድ እጃቸው እንደነበረበት የሚጠቅሱት ወገኖች የሚያነሱት ነጥብ ንጉሱ ከቤጅሮንድ ለጥይበሉ እና ባሻህውረድ ጋር ምስጢራዊ ግንኙነት ማድረጋቸውን ነው፡፡ ዝርዝር እቅዱንና አፈጻጸሙን ሁሉ ያውቁ ነበር ባይባልም እነ ቤጅሮንድ ለጥይበሉ ከእነ አብርሃ ጎን እንዲቆሙ ግን ድጋፋቸውን አሳይተው እንደነበር ታውቋል፡፡

ማይጨው ላይ ዘምተው ድል መሆናቸው የማይቀር መሆኑን የተገነዘቡት ንጉሰ ነገስቱ ሸሽተው ወደ አውሮፓ ቢሰደዱም ትግላቸው ግን አልተገታም ነበር፤ በተለይ በዲፕሎማሲው መስክ፡፡ ከዚህ ባለፈ ግን ንጉሱ እንግሊዝ ሎንደን ሆነው አርበኞችን በመደገፍና ምስጢራዊ ግንኙነት በማድረግ ወራሪው ፋሽስት የኢትዮጵያ ቆይታው በአጭር እንዲቀጭ ሚናቸው የላቀ ነበር፡፡
አሁንም የሰማዕታት ሐውልቱ ስር ነን፡፡ ድጋሜ ላስታውስህ፤…ሞገስና አብርሃ ቦምብ በጣሉበት አዲስ አበባ ብቻ 30,000 ህዝብ የፈጀ ጅምላ ጭፍጨፋ ተካሂዷል፡፡ ቀጥሎም አብርሃና ሞገስ ሸሽተው በሄዱበት ደብረሊባኖስ ገዳም በተመሳሳይ ግንቦት 12 ቀን ብዙ ህዝብ ተጨፍጭፏል፡፡ በሗላም ሰሜን ሸዋ ወደነበሩት የተባበሩት አርበኞች ግንባር ይዞታ በሄዱ ጊዜ አንዳንዶቹ በሰላም ሲቀበሏቸው አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ምን እንደሚሰራ በቂ መረጃ እንደነበራቸው የሚታወቀው እነ ሻለቃ መስፍን ስለሺ እና ባላምባራስ አበበ አረጋይ ግን ወጣቶቹን እንዲታሰሩ አደረጓቸው፡፡
እነሞገስ ከእስር እንደተፈቱ ሀገር ጥለን ወደ ጠረፍ እንሄዳለን ብለው ምክንያት ከመስጠታቸው በቀር በትክክል ወደየት እንደሄዱ አይታወቅም የሚሉ አሉ፡፡ ሌሎች ደግሞ ከእስር እንደተለቀቁ ወደ ዳር ሀገር በመሸሽ ላይ እያሉ ቋራ ላይ እንደተገደሉ ይናገራሉ፡፡

የግራዚያኒ የጭፍጨፋ ትዕዛዝ መነሻ «እነ አብርሃ ቦምብ ወርውረውብኝ ሲሄዱ ህዝብ ወንጀለኞችን በዝምታ ከመመልከቱም በላይ ትብብሩን አሳይቷል» የሚል ነበር፡፡ በጊዜው ግራዚያኒ ወጣቶቹ የሚገኙበትን ለጠቆመ እስከ 10,000 ማሪያ ትሬዛ ብር ለመስጠትም ቃል ገብቶ ነበር ይባላል፡፡ ይህም ሆኖ ግን ሰላማዊውን ህዝብ በጥይት፣ በአዷማ፣ በገጀራ፣ በአካፋ፣ በመጥረቢያ… በአውሬያዊ ጭካኔ ከማንኮት አልተመለሰም፡፡
ወራሪው ጣሊያን የፈጀውን ህዝብ ስንመለከት አስከፊነቱ በቁጥር ብቻ የሚገለጽ አልነበረም፡፡ ኢትዮጵያ ባለ በሌለ አቅሟ ውጭ ሀገር ድረስ ልካ ያስተማረቻቸው ውድ ልጆቿ በፋሽስታዊ ጭፍጨፋ ጠፍተዋል፡፡ እንዲያውም በወቅቱ አንድ የተማረ ትውልድ «ሙሉ ለሙሉ» ወድሟል ይባላል፡፡ ይህም ሀገሪቱን ምን ያህል ዋጋ እንዳስከፈላት መገመት ትችላለህ፡፡

የፋሽስት ግፍ ሌላም ታሪክ እንድናስታውስ ያደርገናል፡፡ አዎ፣ ከዚህ የጭፍጨፋ ታሪክ አንድ አመት ቀደም ብሎም ጣሊያን አቡነ ጴጥሮስን በግፍ መግደሉ ይታወሳል፡፡ በሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም በማዘጋጃ ቤት አጠገብ በጥይት ተደብድበው እንዲሞቱ የተፈረደባቸው አቡነ ጴጥሮስ የኢትዮጵያን ህዝብ ለአርበኝነት ያነሳሱና ለፋሽስት መገዛትን ያወግዙ የነበሩ ጀግና አባት ነበሩ፡፡ በዚህ ድርጊታቸው ምክንያትም አቡኑ ለይስሙላ በተሰየመ የፋሽስቶች ችሎት ቀርበው የመሐል ዳኛ በነበረው ጣሊያናዊ ዳኛ እንዲህ የሚል ጥያቄ ቀርቦላቸው ነበር፡፡

«ካህናቱም ሆነ የቤተ ክህነት ባለስልጣኖች፣ ሊቀ ጳጳሱ አቡነ ቄርሎስም ጭምር የጣሊያንን መንግስት አሸናፊነት አምነውና አሜን ብለው ሲቀበሉ እርስዎ ለምን አመጹ? ለምንስ ብቻዎን አፈንጋጭ ሆኑ?»
አቡነ ጴጥሮስ እንዲህ ሲሉ መለሱ፤ «አቡነ ቄርሎስ ግብፃዊ ናቸው፤ ስለ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊያን የሚገዳቸው ነገር የለም፡፡ እኔ ግን ኢትዮጵያዊ ነኝ፤ ሃላፊነትም ያለብኝ የቤተ ክርስቲያን አባት ነኝ፡፡ ስለዚህ ስለሀገሬና ስለቤተ ክርስቲያኔ እቆረቆራለሁ፡፡ ከዚህ በቀር ለእናንተ ችሎት የማቀርበው ነገር የለኝም፤ ለፈጣሪዬ ብቻ የምናገረውን እናገራለሁ፡፡ እኔን ለመግደል እንደወሰናችሁ አውቃለሁ፤ ስለዚህ በእኔ ላይ የፈለጋችሁትን አድርጉ፡፡ ተከታዮቼን ግን አትንኩ» በማለት ተናገሩ፡፡ (በነገራችን ላይ ግብፃዊው አቡነ ቄርሎስ በየካቲት 12ቱ ጥቃት ወቅት ከግራዚያኒ ጎን ነበሩ፤ በዚህም በቦምብ ፍንዳታው ቆስለው እንደነበር መረጃዎች ያሳያሉ፡፡)

አቡነ ጴጥሮስ እንዳሉትም ሆነ፤ ፋሽስት ቀድሞውኑ አቡኑን ለመግደል ወስኖ ስለነበር የአዲስ አበባ ህዝብ መቀጣጫ እንዲሆነው ግድያው ሲፈጸምባቸው እንዲመለከት በማድረግ አረመኒያዊ እርምጃውን ወሰደባቸው፡፡ አቡኑም ከመሞታቸው በፊት የኢትዮጵያ ህዝብና መሬት ለፋሽስት ጣሊያን እንዳይገዙ አወገዙ፡፡ አቡነ ጴጥሮስ የፍቼ ቀዬ ያፈራቸው ድንቅ አርበኛና የቤተ ክርስቲያን አባት ነበሩ፡፡
ከዚህ ጋር በተገናኘ ሌላ ነገር እናስታውስ፤ ስመጥሯ ሴት አርበኛ ሸዋረገድ ገድሌ የካቲት 12 ቀን 1929 ዓ.ም ከደረሰው አደጋ ጋር በተያያዘ በጣሊያን ሰዎች ተይዘው ወደ አዚናር ተወስደው ታስረው ነበር፡፡
ይህ ሁሉ ዋጋ የተከፈለበትን የነጻነት ትግል እና መስዋዕትነት ለመመስከር የቆመው ሐውልት ስር ሆኜ ታሪካቸውን ሳወሳ ለአሁኑ ማንነቴ የዋሉልኝን ውለታ እውቅና በመስጠት ነው፡፡ አቤት፣ ነጻነት ዋጋዋ ብዛቱ! አቤት፣ ኢትዮጵያዊነት እና የአልገዛም ባይነት ስሜት የተቆራኙበት ሲባጎ ጥንካሬ! በል ለእነዚህ ሰማዕታት የከበረ ምስጋና እናቅርብ….የወደቁላትን ሀገር መልካሙን ብቻ ልናደርግላትና ነጻነቷን ልንጠብቅ ቃል እንግባላቸው፤ ስለ ኢትዮጵያ የተሰዋችሁ ሁሉ ክብር ለእናንተ ይሁን!

(የቀዳማዊ ሃይለስላሴን ህይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ፣ የፋንታሁን እንግዳ ታሪካዊ መዝገበ ሰብ፣ የኢያን ቻምቤል «Ethiopia 1937: The Plot to Kill Graziani» እና የአምስቱ የመከራ አመታት አጭር ታሪክ የተሰኙ መጽሐፍትን መረጃ ተውሸባቸዋለሁ፤)

የአብዛኞቹ የአብነት መምህራን የጤና ችግር ከዐይን እክል ጋራ የተያያዘ ነው ‹‹የተለያዩ የጤና ምርመራዎች ከተደረገላቸው 170 መምህራን ከ70 በላይ የሚኾኑት የካታራክት እና ትራኮማ ተጠቂ ናቸው፤ ዋነኛ መንሥኤው ኬሚካል ተቀላቅሎበት የሚመረት የጧፍ ጢስ ነው፤ ክብካቤና ክትትል ካልተደረገላቸው ለዐይነ ስውርነት ያደርሳቸዋል፡፡›› /የማኅበረ ቅዱሳን ሞያ አገልግሎት የሕክምና ቡድን/ (ሰንደቅ፤ የካቲት ፲፪ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም.) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን …

የጀርመን የትምህርትና የምርምር ሚንስቴር ፣ እ ጎ አ ከ እንደ ጎርጎሪዮሳዊው ዘመን አቆጣጠር ከ 2000 ዓ ም አንስቶ፣ ዐበይት የሳይንስ አርእስት እየመረጠ፤ ሕብረተሰቡ በያመቱ በአንድ ርእሰ ጉዳይ ላይ እንዲወያይ ፤ እንዲከራከር፤ በቀጥታ በተግባር

የካቲት ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የካፒቴን ሃይለመድህን አበራ የጠለፋ ምክንያት  በአየር መንገዱ ውስጥ የሚታየውን የአስተዳደር መበላሸት ለአለም ለማሳየት ነው  ይችላል የሚለው ምክንያት አሳማኝ ነው ሲሉ አንድ የቀድሞው የድርጅቱ ሰራተኛ ገለጹ በኢትዮጵያ አየር መንገድ  በበረራ ደህንነት ስራ ውስጥ ለረጅም ጊዜ ያገለገለውና በክትትልና ደህንነት ስጋት ከአመት በፊት ድርጅቱን ለቆ በስዊዘርላንድ ጥገኝነት የጠየቀው ሚካኤል …

የካቲት ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢትዮጵያውያን በጣሊያን ወራሪ ሃይል በግፍ የተጨፈጨፉበት ቀን በመላው አለም በሚገኙ ኢትዮጵያውያን እየተዘከረ ነው። በአዲስ አበባ ስድስት ኪሎ በሚገኘው የሰምአታት ሃውልት ጀግኖች አባት አርበኞች በተገኙበት በአሉ ተከብሯል። የካቲት 12፣ 1929 ዓም አብርሃ ደቦጭና ሞገስ አስገዶም የተባሉ ኢትዮጵያውያን ግራዚያኒን ለመግደል የጣሉትን ቦንብ ተከትሎ፣ የጣሊያን ወራሪ ሰራዊት በወሰደው እርምጃ  …

የካቲት ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአዕምሮ ቸግር ፤ ዘገምተኝነት ፤ ሱስ ፤ ራስን መጣል ፤ የስነ ልቦና ችግር ፤ድብርት ፤ ከሰው መገለል፤ተስፋ መቁረጥ ፤ እራስን ማጥፋት ፤ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ችግሮች፤ አሰገድዶ መደፈር ችግር የጣላባቸው ጠባሳ በህይወታቸው ላይ ከባድ ተጽኖ ሁኖ ይሰተዋልባቸዋል ሲል የሰራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ያስጠናው ጥናት አመልክቷል፡፡ ከአርባ …

ከማክሰኞ፥ የካቲት 11 ቀን 2006 ዓም አንስቶ የተባባሰዉ የዩክሬን የፀጥታ ሁኔታ ወደእርስ በርስ ጦርነት እንዳያመራ እየተሰጋ ነዉ። የሀገሪቱ የፀጥታ ኃይሎች የመንግስት በጎዳና ላይ በሚካሄደዉ ግጭት መሃል ተቃዋሚዎች ወደ1,500 ጠብመንጃ መዉሰዳቸዉን አመልክተዋል።

ከ 20 ዓመት በፊት ሩዋንዳ ውስጥ ሙቩምባ በተባለች ሰሜን ምሥራቃዊ ከተማ ከንቲባ የነበሩት ኦንስፎር ሩዋቡኮምብ የተባሉት የ 54 ዓመት ጎልማሳ ፣ ያኔ በአንድ ቤተ-ክርስቲያን የተጠለሉ ሩዋንዳውያን እንዲጨፈጨፉ በማድረጋቸው ፣ ፍራንክፈርት ጀርመን ውስጥ

ኢትዮጵያ እጅግ ደሀ ከሚባሉት ጥቂት የዓለማችን ኣገሮች መካከል ብትመደብም በሌላ ጎኗ ደግሞ በተፈጥሮ ኃብት የበለጸጉ ከሚባሉት አካባቢዎች መካከልም ያንኑ ያህል ትጠቀሳለች። ለዓብነት ያህልም ለግብርና ምቹ በሆነ ሰፊ መሬት የታደለችው ኢትዮጵያ በቡና ምርትም ቀዳሚ ከሚባሉት መካከል ስትሆን በእንስሳት ሀብቷም እንዲሁ ከዓለም 10ኛ ናት።

ኢትዮጵያ ዉስጥ የመሬትና ዉሃ ቅርምት ማኅበረሰቡን እየጎዳ እንደሚገኝ ዓለም ዓቀፉ የመብት ተሟጋች ሂዉማን ራይትስ ዎች አመለከተ። ድርጅቱ ይህን አመልክቶ ባወጣዉ ዘገባ በዚህ ምክንያትም ኢትዮጵያና ኬንያ ዉስጥ 500,000 አርብቶ አደሮች ለችግር መጋለጣቸዉን ገልጿል።

የዚህ ዕትም እንግዳችን ታዋቂው አርቲስትና አክቲቪስት ታማኝ በየነ ነው። ረዥም ጊዜያት በኪነ-ጥበብ ሙያ ላይ የቆየው ታማኝ፣ የደርግ መውደቅን ተከትሎ ኢሕአዴግ የአራት ኪሎውን ቤተ-መንግስት ከተቆጣጠረበት ዕለት (ግንቦት 20/1983 ዓ.ም) ጀምሮ በድፍረት የስርዓቱን አምባገነንነት፣ ከፋፋይነት፣ በብሔራዊ ጥቅም ላይ ያለውን ቸልተኝነት… ጠቅሶ ተችቷል። ይህንንም ተከትሎ በደረሰበት ከባድ ጫና፣ እስርና ግርፋት ሀገሩን ለቆ ለመውጣት ተገድዷል። በስደት በሚኖርባት አሜሪካም ያለውን የተከፋፈለ የተቃውሞ ፖለቲካ አስተባብሮ ከመምራቱም በላይ በየጊዜው የህሊና እስረኞች እንዲፈቱ የሚጠይቁና መሰል ሀገራዊ ጉዳዮችን በተመለከተ የሚዘጋጁ የተቃውሞ ሰልፎችን አስተባብሮ መርቷል። በዚህም በመላው ዓለም በሚገኙ በርካታ ኢትዮጵያውያን ከበሬታን አትርፏል። አክትቪስት ታማኝ በየነ፣ ከተመስገን ደሳለኝ ጋር ያደረገው ቃለ-መጠይቅ እንደሚከተለው ተዘጋጅቷል።

iframe

Image

የደህንነት ስጋት ፤የአስተዳደር ብልሹነት እና የዘረኝነት መድልዎን የሚቃወም የአይሮፕላን ጠለፋ

ታዋቂነታችን በድርቅ በድህነት ብሎም በጭፍጨፋ ደሞ በሰብኣዊ መብት ጥሰት

ምንሊክ ሳልሳዊ :- በሃገሪቱ የተንሰራፋውን የደህንነት ስጋት በመልካም አስተዳደር እና በዘረኝነት ላይ የተመሰረተ አድልዎ ተከትሎ የተደረገው የአይሮፕላን ጠለፋ ህዝቦች በገዛ አገራቸው በደህንነት ላይ ምን ያህል ስጋት እንዳጠላበት እና በመኖር ህልውናቸው ላይ ኢትዮጵያውያን የስርአቱ ፖሊሲዎች እያሸማቀቋቸው እንደሚገኙ አለም ካለፈው ጊዘ በተሻለ እውነታውን ፍንትው አድርጎ እየመሰከረ ነው።

የሕወሓት መራሹ ጁንታ ወደ ስልጣን በጠበንጃ ሃይል ከመጣ ጀምሮ በአለም አቀፍ ደረጃ የተደነገጉ የሰብኣዊ መብት ህጎችን ካለምንም ማርቅርቅ እና ድካም ከሌሎች በመገልበጥ በወረቀት ላይ ከማስፈሩም በተጨማሪ ጥናቶች እንደሚጠቁሙት በአለም ላይ የሰው አገር ህግን እና አለማቀፍ ድንጋጌን ከሃገራችን ሁኔታ ጋር ሳይገናዘቡ በስፋት በደመነፍስ ለፍጆታ የተጻፈበት ሃገር ኢትዮጵያ ብቻ ሲሆን በየትኛውም አለም ሃገራት ያልተከሰተ የአለም አቀፍ ህጎችን ግልባጭ በከፊል በህገመንግስት እንዲሁም የገዢ ፓርቲን የፖለቲካ ፕሮግራም በከፊል ደባልቆ በጋር እንደ አውራ ህግ የወጣባት ሃገር ብትኖር ኢትዮጵያ ብቻ ናት::ኢትዮጵያ በታሪኳ ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ የመብቶች ሕጋዊነት በተጨበጨበለት ሁኔታ እና ይህ በማይባል ደረጃ የተደነገጉባት አገር ነች፡፡ እንግዲህ ይህ ሆኖ እያለ ነው በአገሪቱ የመብቶች ጥሰት ጉዳይ ከአገሪቱ ብሔራዊ አነታራኪ ፖለቲካዊ አጀንዳነት አልፎ ዓለም አቀፍ አጀንዳ ሆኖ ተገኝቷል፡፡

ጥላቻ በፈጠረው ፍርሃት ብቻ የሃገሪቱን ህጎች ዜጎች ለመጥለፍ እያዋሉት ነው::
የቀድሞ መንግስትን ሽንፈት ተከትሎ በኢትዮጵያ የሰብኣዊ መብት ጥሰቶች የፍፃሜ ምዕራፍ ይሆናል ተብሎ ተስፋ ተደርጎ ነበር፡፡ ነገር ግን ጭራሽ ብሶበት ቁጭ አለ፡፡ የሕወሓት ወንበሩን መቆጣጠር ተንተርሶ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያሉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በተለይም ሒዩማን ራይት ዎችና አምነስቲ ኢንተርናሽናል የወያኔን ጁንታ በሰብዓዊ መብት ጥሰት በማብጠልጠል ነበር የተቀበሉት፡፡ ባለፉት ሃያ ሁለት ዓመታት የሰብኣዊ መብት ጥያቄዎች አቤቱታ ማሰማታቸውን አላቆሙም፡፡ ጋዜጠኞችን የሃሳብ ነጻነት ከሚገድብ ጥቃት በመከላከል ላይ የተሰማሩ የመብት አስከባሪ ድርጅቶችም ወያኔ በሚፈጥረው ከባድ የሰብኣዊ መብት ጥሰት በየጊዜው መክሰስ ሥራቸው ሆኗል::የአሜሪካው ስቴት ዲፓርትመንት በየጊዜው በሚያወጣው ዓመታዊ መግለጫው ወያኔን በሰብዓዊ መብት ጥሰትና የፖለቲካ መብቶችን ማፈን ይከሰዋል፡፡ ባሁን ወቅትየእነኚህን አካላት መግለጫዎች የታወቁ ዓለም አቀፍ መገናኛ ድርጅቶች በመቀባበል ኢትዮጵያ የዜጎቿን መብቶች በመጣስና በማፈን ወደር የሌላት አገር እንደሆነች ዓለም እንዲረዳው እያደረጉ ናቸው፡፡

ኢትዮጵያ በአስከፊ ድርቅና ረሃብ ለመታወቅ እንደበቃችው ሁሉ ወያኔ የዜጎችን መብቶች በመጣስና በማፈን እንዲሁም በሰብዓዊነት ላይ በሚፈጽመው ወንጀል በዓለም ላይ ታዋቂነትን እያተረፈ ነው፡፡ ይህ ብቻ አይደለም;ወያኔ የፖለቲካ ተቀናቃኞችን መብቶች ለመጣስ ስለሚጠቀምባቸው ዘደዎች የሚቀርቡ ማስረጃዎች እና ማብራሪዎች እጅግ ዘግናኝ ናቸው፡፡የወያኔ መሪዎች የፖለቲካ ተቀናቃኖችን ለማዳከም ሲሉ ንፁኃንን ወንጀለኛ የሚያደርግ ዘዴዎችን ሥራ ላይ እንደሚያውሉ በተለያዩ ይፋዊ ሪፖርቶች ላይ ሁሉ ከነማስረጃው እየተነገረ ይገኛል::

የህ የሰብኣዊ መብጥ ጥሰት እየተባባሰ የሚሄድበት ምክንያት ወይኔ በአብዛኛው ካድሬዎች ዘንድ በስፋት ሰርጾ እንዲገባ ያደረገው የተቃዋሚዎች ጥላቻ እና እንዲሁም የተቃዋሚው ቡድን የትግል አቅጣጫው በተመሳሳይ መልኩ በጥላቻ ላይ የተመረኮዘ መሆኑ ነው::ተቃዋሚዎች የታጠቁ ሃይላት ባለመሆናቸው የመርሃቸው እንቅስቃሴ የተገደበ እና ለፖለቲካ እና ለሚዲያ ፍጆታ የዋለ ተዳፍኖ የሚገኝ ሲሆን የወያኔው ግን በታጠቁ የጸጥታ ሃይሎች እና በፖለቲካ ማጭበርበሮች ላይ ስለተመረኮዘ ካድሬዎቹ በተሰጣቸው የጥላቻ ተግዳሮት እና ወያኔያዊ ስልቶች የፈጠሩትን ጥቅማጥቅሞች ጠብቀው ለማቆየት ሲባል ጥላቻ በፈጠረው ፍርሃት ብቻ የሃገሪቱን ህጎች ዜጎች ለመጥለፍ እያዋሉት ነው::

ይህ ፍርሃት እና ጥላቻ በወያኔ ከትልቅ እስከ ትንሽ ካድሬዎች አናት ውስጥ ስር ለስር በመስደድ የፈጠረው ነገር ቢኖር ማንኛውም ዜጋ ተቃውሞ ካሰማ በወንጀለኛነት በመፈረጅ በማሳደድ በማጥፋት እረፍት ለማግኘት እና ጥቅማቸውን ለማስጠበቅ ሲራወጡ የህዝብን የበላይነት አፈር ከተውታል::ማእከላዊ የወያኔ ጁንታ በዲሞክራሲ ባለመወቀጣቸው የህጎችን የበላይነት ማረጋገጥ ካለመቻሉም በተጨማሪ በህዝብ እና በዲሞክራሲ ላይ በደሎችን የሚያደርሱ ባለስልጣናት የሚጠየቁት በሃገሪቱ የበላይ ህጎች ሳይሆን በወያኔያዊ የፓርቲ መመሪያዎች በመሆኑ በጥቅም መተሳሰር በፈጠርው ዝግ መንገድ የሰብኣዊ መብት ጥሰቶች እየተብራከቱም ከመሆኑ አልፎ የእለት ተእለት ተግባራት አካል ሆነዋል:: የአይሮፕላን ጠለፋዉም ከላይ ከገለጽኩት ጉዳዮች ጋር ቁርኝት ያለውና በሃገሪቱ እየተተገበረ ያለውን የቡድን አምባገነንነት በማጋለጥ ረገድ ትልቁን ሚና ተጫውቷል።

የፓትርያርኩ ልዩ ጽ/ቤት በጓሮ በር ለሚገቡ ሙሰኞችና ጎጠኞች ሽፋን መስጠቱን ቀጥሎበታል፡፡ ልዩ ጽ/ቤቱ እንደቀድሞው ጊዜ ኹሉ ዛሬም በማይመለከተው ጉዳይ ጣልቃ እየገባ የሕገ ቤተ ክርስቲያን ጥሰት እየፈጸመ ይገኛል፡፡ ሙሰኞችና ጎጠኞች የበላይነት ይዘው በተቆጣጠሩት ጽ/ቤት የቅ/ሲኖዶሱን ውሳኔ እየተላለፈ በሚፈጽመው ኢ-ፍትሐዊ ተግባር የመንበረ ፓትርያርኩን ተቀባይነትና አገልጋዩና ምእመኑ በመልካም አስተዳደር መስፈን ላይ ያለው እምነት እንዲሸረሸር መንሥኤ እየኾነ ይገኛል፡፡ ከላይ …

የካቲት 16 በሚደረገዉ የባህር ዳር ሰልፍ፣ መኢአድ እና አንድነት በጋራ የጠሩት ነዉ። ድርጅቶች እንዲህ ሲተባበሩ ያስደስታል። የተናጥል የብቻ ጉዞ የትም አይደርስምና። ይህ ሰልፍ ምንም እንኳን የብሃአዴን አንድ አመራር አባል ለፍርድ እንዲቀርቡ የሚጠይቅ ቢሆንም፣ ጉዳዩ ከአንድ ግለሰብ ያለፈ መሆኑን መረዳት አለብን። ባለስልጣኑ ጸያፍና ነውረኛ አስተያየት ሰጡ የሚል ክስ ሲቀርበባቸው ፣ ገዚው ፓርቲ ፣ ግድ የለም፣ አሁኑኑ […]