የብአዴን ውጪ ነብስ ግቢ ነብስ….

የአማራውን ህዝብ ለሃጫም ልጋጋም ….. በማለት በመርዛም ሕወሓታዊ ምላሱ መርዝ ብሎ የተሳደበው የብኣደኑ የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ እና የክልሉ ምክትል ርእሰ መስተዳደር የባህር ዳር የተቃዋሚዎችን ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ጥሪ ተከትሎ አማራውን አልሰደብኩም የሚል ንግግር ማድረግ መጀመሩ በድርጅቱ ውስጥ የገባውን ድንጋጠ ያመለክታል።

አቶ አለምነው መኮንን የጭንቁ ቀን ሲመጣ “አማራውን አልሰደብኩም” ብሎ በክልሉ መገናኛ ብዙሃን መለፍለፍ መጀመሩን እየሰማን ነው፤ ሰውየው የአንድነትና የመኢአድ የተቃውሞ ሰልፍ 2 ቀናት ብቻ ሲቀሩት ለማስተባበል መሞከሩ የብአዴንን ውጪ ነብስ ግቢ ነብስ ያሳያል ።