አቡጊዳ – ባህር ዳር በቅስቀሳ ደምቃለች
አንድነት እና መኢአድ በባህር ዳር ቅስቀሳቸውን ቀጥለዋል። ሕገ መንግስቱን በመጻረር ፣ ዜጎች ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብታቸውን በመገፋት የብአዴን ካድሬዎች የተለያዩ ምክንያቶ እያቀረቡ የሰልፉ አስተባባሪዎች የማገት፣ የማስፈራራት ሥራ እየሰሩ እንደነበረ የደረሰን ዜና ይጠቁማል።

አንድነት እና መኢአድ በባህር ዳር ቅስቀሳቸውን ቀጥለዋል። ሕገ መንግስቱን በመጻረር ፣ ዜጎች ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብታቸውን በመገፋት የብአዴን ካድሬዎች የተለያዩ ምክንያቶ እያቀረቡ የሰልፉ አስተባባሪዎች የማገት፣ የማስፈራራት ሥራ እየሰሩ እንደነበረ የደረሰን ዜና ይጠቁማል።
ባጃጆች (ትናንሽ ታክሲዎች)፣ በፈቃዳቸው ከጀርባቸው የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪን ያነገቡ ፖስተሮችን ተሸክመው ባህር ዳርን እየዞሩ ይገኛሉ፡፡ የከተማይቱ ግድግዳዎች የስልክ እንጨቶች ‹‹ብአዴን/ኢህአዴግ ህዝብን የመምራት ሞራልም ብቃቱም የላቸውም››በሚሉ መፈክሮች እየተጥለቀለቁ ነው፡፡ በድምጽ ማጉያም መፈክሮች ፣ ቅስቀሳውቾ እየተሰሙ ነው።

