ካምፓላ ተለጣፊ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ሊቋቋም ነው።
የወያኔ ቆንስላ በዩጋንዳ ቅዳሜ ህወአት ውብድናና የጀመረበትን ሠላሣ ዘጠነኛ ዓመት ሲያከብር ተለጣፊ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ በአምሣሉ ለመፍጠር በፓስፖርት የሚኖሩን ኢትዮጵያዊያን ተጋዳላይ ፍሬወይኒ ዮሐንስ በስልክ እየጠሩ ሲሆን ስደተኛ ነን ባዮቹን ደግሞ አቶ አምሣሉ እንዲገኙ እያባበለ መክረሙን ከውስጥ አዋቂዎች የተገኘው መረጃ ጠቆመ።
ወያኔ ከትግራይ መቀሌ ውጪ መከበር የማይገባውን ቀን ካምፓላ ላይ ማክበሩ የሐገሪቱን ካዝና
እንደፈለገ እንደሚጫወትበትና እስከዛሬ በታሪክ ውንብድና የጀመረበትን ቀን በማክበር ሐፍረት የማይሠማው
ህወአት ብቻ መሆኑን ሐገር ወዳዶች ይናገራሉ።
ስደተኞች ወያኔ ኤንባሲ የሚሄዱበት ምንም አይነት ምክንያት እንደሌላቸው አውቀው ከፈንጂ ወረዳ እንዲርቁ መንገር እንደሚገባና እግራቸውን ለማይሠበስቡ ስደተኞች ግን ለዩጋንዳ መንግስትና ለዩኤንኤችሲአር በማጋለጥ እውነተኛ ስደተኞች ደህንነታቸውን ማረጋገጥ እንደሚገባቸው በስልክ ያነጋገርናቸው ወገኖች ከስፍራው ገልፀውልናል።