ሺሻይ አዘናው፣ የቀድሞ የአረና አሁን ደግሞ አንድነት ፓርቲ አባል፣ መቀሌ በሚገኝ ፍርድ ቤት ቀርቦ “ሽብርተኛ ነህ” በሚል ክስል ተመስርትበታል። በሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ ማስተርሱን ይማር የነበረው ሺሻይ፣ በትግራይ ድምጻቸዉን ከሚያሰሙ ደፋርና አንጋፋ ወጣት ፖለቲከኞች መካከል አንዱ ነበር። ኢትዮሜዲያ የሚከተለዉን ዘግቧል፡ http://www.ethiomedia.com/15store/4251.html

ነሐሴ ወር 2006 ዓ.ም መኢአድ እና አንድነት ዉህደት ይፈጽማሉ ተብሎ ተጠብቆ እንደነበረና የሕወሃት ምርጫ ቦርድ ለመኢአድ አመራር እውቅና አልሰጥም በሚል ዉህደቱን ማጨናገፉ ይታወቃል። ከሁለት አመታት በላይ በአቶ አበባው መሐሪ ከሚመራው መኢአድ ጋር ደብዳቤዎች ሲጻጻፍ የነበረው ምርጫ ቦርድ ፣ አንድም ጊዜ በአመራሩ ላይ ጥያቄ አንስቶ ሳያውቅ፣ ዉህደት ሊደረግ ሲል፣ ሸንካላ ምክንያት በመፍጠር ሆን ብሎ ዉህደቱን ማጨናገፉ፣ ምርጫ ቦርዱ በሕወሃት አመራር ታዞ ያደረገዉ እና ምንም አይነት ገለልተኝነት እንደሌለው ያሳየበት እንደሆነ ብዙዎች ያናግራሉ።

የምርጫ ቦርድን ሕገ ወጥ ጥይቄ ለማሟላት መኢአድ ቅዳሜ ጥቅምት 29 እና እሁድ ጥቅምት 30 ጠቅላላ ጉባኤ ጠርቶ የነበረ ሲሆን፣ ጠቅላላ ጉባኤው ባለመስማማት እንደተጠናቀቀ ለማወቅ ችለናል።

አርብ ጥቅምት 28 ቀን፣ የመኢአድ ላእላይ ምክር ቤት ተሰብስቦ የመኢአድ አመራር የነበሩና በተለያዩ ችግር የተገለሉ ፣ አቶ ማሙሸት አማረን ያካተተ ፣ 14 ሰዎችን ጉዳይ፣ ጠቅላላ ጉባኤው በነገታው ዉሳኔ እንዲያሳልፍ ስምምነት የተደረሰ ሲሆን፣ ምንም እንኳን ከአንድንት ጋር ሊደረግ የነበረዉን ዉህደቱ ምርጫ ቦርድ ቢያጨናግፈውም፣ የምርጫ ዘመቻውን ከአንድነት ጋር በተቀናጀ መልኩ ለማድረግ በጠቅላላ ጉባኤው ዉሳኔ ለማስወሰን ታስቦም እንደነበረ ለማወቅ ችለናል።

ቅዳሜ ጥቅምት 29 ቀን ጠቅላላ ጉባኤው በአቶ ሃይሉ ሻዉል መሪነት የተከፈተ ሲሆን፣ ከ335 በላይ የጠቅላላ ጉባኤ አባላት ተገኝተዉም ነበር። እነ አቶ ማሙሸት በርካታ ሰዎች በስብሰባው እንዲገኙ ማድረጋቸዉንም ለማረጋገጥ ችለናል።

በስብሰባው ወቅት በአቶ ኃይሉ ሻዉልና በአቶ አበባው መሐሪ መካከል ጠንካራ ልዩነቶችና አለመስማማቶች የነበሩ ሲሆን ስብሰባው በጥሩ ሁኔታ እንዳልተጠናቀቀም ለማውቅ ችለናል። አቶ አበባው፣ ከሁለቱ በስተቀር የሥራ አስፈጻሚ አባላት በሙሉ ለደህንነታቸው ፈርተናል በሚል ስብሰባዉ ጥለው እንደወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ። ከስብሰባው ከወጡት መካከል የመኢአድ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊው አቶ ተስፋሁን አለምነህም ይገኙበታል።

ስብሰባው እሁድ ጥቅምት 30 በቀሩት በአብዛኛው እነ አቶ ማሙሸት የሰበሰቧቸው ተወካዮች ባሉበት አቶ ማሙሸት አማረን የመኢአድ ፕሬዘዳንት አድርገው መርጠዋል።

ጠቅላላ ጉባኤው ቅዳሜ ጥቅምት 29 ቀን የተደረገ እለት የምርጫ ቦርድ ተወካይ እንዳልነበረም የደረሰን ዘገባ ሲያመለክት፣ የምርጫ ቦርድ ተወካይ በሌለበት፣ አብዛኛው የጠቅላላ ጉባኤ ተወካዮች አልተገኙም በተባለበት የተደረገ ምርጫ ምን ያህል ሕጋዊ ሊሆን እንደሚችል ግልጽ የሆነ ነገር እንደሌለ ከመኢአድ አባላት የሚደርሱ ዘገባዎች ይገልጻሉ።

ከአራት አመታት በላይ ያልታዩት ኢንጂነር ኃይሉ ሻዉል፣ በዚህ መልኩ ስብሰባው በሰላም እንዲጠናቀቅ አለማድረጋቸው እንዳልተደሰቱ የሚገልጹት አንድ ያነጋገርናቸው የመኢአድ አባል ለመኢአድ አሁን ያለበት ደረጃ በዋናነት ተጠያቂው አቶ ኃይሉ ሻወል እንደሆኑ ይናገራሉ።
በመኢአድ እና በአንድነት መካከል ሊደረግ ታስቦ የነበረ አብሮ የመስራት ዉሳኔ በነበረው አለመስማምምት አልመሳካቱ ጥሩ እንዳልነበረ የተናገሩት እኝሁ የመኢ፤አድ አባል፣ “አብዛኛው የመኢአድ አባል ከአንድነቶች ጋር እየታሰረ፣ እየተደበደበ፣ እየተገደለ ነው። በተግባር የመኢአድ እና የአንድነት አባላት አንድ ናቸው” ሲሉ በአመራሮች ዘንድ አለመስማማቶች ቢፈጠሩም በሜዳ በየዞኑና በየወረዳው ያለው የመኢአድ ታግይ እንኳን እርስ በርሱ እንደ አንድነቶ ካሉ ሌሎች የትግል አጋሮቹ ጋር አንድ ሆነ እየሰራ እንደሆነም ይገልጻሉ።
በጉዳዩ ላይ ያነጋገርናቸው ከበርካታ ተወካዮች ጋር ስብሰባዉን ለቀው የወጡት አንድ የመኢአድ ከፍተኛ አመራርር አባል፣ በማንም ድርጅት አለመስማማቶች እንደሚፈጠሩ ገልጸው፣ ብሶት ለመናገር ወደ ኢቲቪ እንደማይሮጡ ገልጸዋል።

በአቶ አማረ ማሙሽት የሚመራው መኢአድ ጽ/ቤቱን ተቆጣጥሮ አዲስ ካቢኔም እንዳዋቀረ ለማወቅ ችለናል። በዚሁ መሰረት አዲስ ካቢኔ የሚከተሉት አባላትን አካቷል፡

1: አቶ ማሙሸት አማረ (ፕሬዝዳንት)
2: ዶ/ር ታዲዎስ ቦጋለ (ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት)
3: አቶ እንድርያስ ኤሮ (ምክትል ፕሬዝዳንት)
4: አቶ ተስፋየ መላኩ (ዋና ፅሃፊ)
5: አቶ ሰማሀኝ አብርሃም (የድርጂት ጉዳይ)
6: ኮኔሌር ትርሶት ጉልላት(የህዝብ ግንኙነት)
ገ: ወ/ሮ አለማየሁ ሞገድ (የሴቶች ጉዳይ)
8: አቶ አብርሀም ጌጡ (የውጭ ጉዳይ)
9: አቶ ሀብተማርያም ያንተ(ፋይናንስና አስተዳድር)
10: አቶ ታጠቅ አሰፋ (የወጣቶች ጉዳይ)
11:አቶ ሀይለየሱስ ሚናስ (የምርጫ ጉዳይ)
13:አቶ ተስፋሁን አለምነህ (ትምህርትና ስልጠና አላፊ)
14 : መ/አ አየለ አለ(የህግና ዲስፕሊን አላፊ)
15: አቶ ወርቁ ከበደ (የምሃል ቀጠና ሃላፊ)
16: አቶ አዳነ ጥላሁን(የሰሜን ቀጠና ሃላፊ)
17: አቶ ብሩ ደሲሳ( የምራብ ቀጠና ሃላፊ)
18: አቶ ገለቱ ደጀርሳ (የደቡብ ቀጠና ሃላፊ)
19: አቶ ተፈራ መንግስቴ (የምስራቅ ቀጠና ሃላፊ)\

ጄ/ል አበባው ታደሰ ወደ ውጭ ለመውጣት ሲሉ ከቦሌ አየር ማረፊያ በደህንነቶች እንዳይወጡ መደረጋቸውን ታማኝ ምንጮች ጠቁመዋል። ከመከላከያ የጦር አዛዥነታቸው በጄ/ል ሳሞራ የኑስ እንዲነሱ የተደረጉት ጄ/ል አበባው ከአገር እንዳይወጡ የተደረገበት ምክንያት ግልፅ እንዳልሆነ ምንጮቹ አያይዘው ገልፀዋል። በመከላከያ ሰራዊቱ ውስጥ የተለያዩ ጥያቄዎች እንዳሉ በመግለፅ ለኢታማጆር ሹሙ ጄ/ል ሳሞራ ከረር ያለ ሪፖርት ያቀረቡት ጄ/ል ሰዓረ፣ ጄ/ል ሞላና ጄ/ል […]

በሰሞኑ የሰራዊቱ ግምገማ የወያኔው መከላከያ ሰራዊቱ እንደ ደርግ ሰራዊት ሊበተን ይችላል ተባለ:: -በአዲስ አበባ የለውጥ ሃይሎች በመተባበር የሕዝባዊ እንቢተኝነት ጥሪዎችን ለማድረግ ዝግጅት ላይ ናቸው:: -በአስመራ አርብ ቀን ሰው አልባ ተቃውሞ ከቤት ባለመውጣት ሓርነት አርቢ የተሰኘ ንቅናቄ ተጀምሯል:: ላለፉት 23 አመታት በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ሕዝቦች ላይ ከፍተኛ የቀውስ ማእበል ያስከተሉት ሕዝቦቻቸን ለስደት እና ለእስር እንዲሁም ለሞት […]

ፍኖት ታትማ ወጥታለች ኢቲቪ (ወይም አዲሱ ስማችውው ኢቢሢ)፣ የኢትዮጵያ ሬድዮ፣ አዲስ ዘመን ጋዜጣ በመንግስት ገንዘብ የሚተዳደሩ የመገናኛ ብዙሃን ናቸው። የሕገ መንግስቱ አንቀጽ 29 ንኡስ አንቀጽ 5 “በመንግስት ገንዘብ የሚካሄድ ወይም በመንግስት ቁጥጥር ሥር ያለ መገናኛ ብዙኃን የተለያዩ አስተያየቶችን ለማስተናግገድ በሚያስችለው ሁኔታ እንዲመራ ይደረጋል።” እንደሚለው የተለያዩ አስትያየቶችን ፣ በአገሪቷም ያሉ በሕግ የተመዘገቡ ሲቪክና የፖለቲካ ድርጅቶችን ከኢሕአዴግ […]

ነሐሴ ወር 2006 ዓ.ም መኢአድ እና አንድነት ዉህደት ይፈጽማሉ ተብሎ ተጠብቆ እንደነበረና የሕወሃት ምርጫ ቦርድ ለመኢአድ አመራር እውቅና አልሰጥም በሚል ዉህደቱን ማጨናገፉ ይታወቃል። ከሁለት አመታት በላይ በአቶ አበባው መሐሪ ከሚመራው መኢአድ ጋር ደብዳቤዎች ሲጻጻፍ የነበረው ምርጫ ቦርድ ፣ አንድም ጊዜ በአመራሩ ላይ ጥያቄ አንስቶ ሳያውቅ፣ ዉህደት ሊደረግ ሲል፣ ሸንካላ ምክንያት በመፍጠር ሆን ብሎ ዉህደቱን ማጨናገፉ፣ […]

ኢትዮጵያና ጀርመን ዘመናት የተሻገረ የሁለትዮሽ ግንኙነት በመካከላቸዉ የመሠረቱ ሃገራት መሆናቸዉ በመረጃዎች የተመዘገበ ነዉ። ሁለቱ ሃገራት ይፋዊ የዲፕሎማሲ ዉል ከተፈራረሙም 105 ዓመታት ተቆጥረዋል።


 ከታሳሪ ዞን9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች
 
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ሕገ መንግስታችንን ያክብሩ!
ሠላም ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር!? እንዴት ነዎት? ያስታውሱ ከሆነ የዛሬ ሁለት ዓመት አካባቢ ከፊሉ የዚህ ማስታወሻ ፀሃፊዎች ‘ግልፅ ደብዳቤ ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ’ በሚል ርዕስ:
“ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር እባክዎትን የተለያዩ የመንግስት አካላት የሕገ መንግስታችንን ድንጋጌዎች እየጣሱ ነውና እርስዎም በሕገ መንግስቱ አንቀፅ 74/13/ መሠረት ሕገ መንስቱን የማስከበርና የማክበር ግዴታ ስላለብዎት ሕገ መንግስቱን ያክብሩ” በማለት አንዲት አጭር ደብዳቤ ፅፈንልዎት ነበር፡፡
ድንገት በተለያዩ ምክንያቶች የጻፍንልዎትን ደብዳቤ ካላነበቡት ወይም ማስታወስ ካልቻሉ ዛሬ ይሄን ማስታወሻ ስለምንፅፍልዎት ግለሰቦች አንድ ሌላ ማስታወሻ እንስጥዎ፡ ከ6ወራት በፊት /በሚያዚያ 2006 ዓ.ም/ ሶስት  ጋዜጠኞችንና ስድስት ጦማሪያንን ‘ሕገ መንግስቱንና ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ በመሞከር ወንጀል ጠርጥሬያችኋለሁ’ በማለት መንግስትዎ ልማታዊ ርምጃ (አብዮታዊ ርምጃ እንደሚባለው) ወስዶ ነበር፡፡
እኛም የዚህ ማስታወሻ ፀሃፊዎች የዚህ ‘ልማታዊ ርምጃ’ ሰለባ የሆንን ግለሰቦች ነን፡፡ በርግጥ ከሁለት ዓመታት በፊት ‘ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ሕገ መንግስቱን’ ያስከብሩልን በማለት ጥያቄ ያቀረብንልዎት ግለሰቦች ‘ከ6ወራት በፊት ሕገ መንግስቱን ለመናድ  ሞክራችኋል’ በማለት መንግስትዎ ሲያስረን ሕገ መንግስቱ እንዲከበር ጠይቀን ሕገ መንግስቱን ለመናድ በመሞከር ወንጀል ተጠርጥረን ስንታሰር እስሩ በጣም ግራ አጋብቶን ነበር፡፡ በዚህ ያልቆመው መንግስትዎ ክሱን ‘ሕብረተሰቡንና ሀገሪቱን ለማሸበር አቅዳችኋል ሞክራችኋል አሲራችኋል…’ በማለት ወደ ‘ሽብርተኝነት’ ያሳደገው ሲሆን እርስዎም ከዚህ ጋር በተያያዘ ሃሳብዎትን ሲሰጡ ስለተመለከትንዎ ትንሽ ቅሬታ ይዘን መጣን፡፡
በቅድሚያ አሁን ያለንበትን ሁኔታ በትንሹ ብናስረዳዎት ቅሬታችንን ለመረዳት ያስችልዎታልና አንዳንድ ጉዳዮችን እንንገርዎት፡፡
ይሄን ማስታወሻ በምንፅፍልዎት ወቅት ከታሰርን ከ 200 ቀናት የተቆጠሩ ሲሆን፣ነገር ግን ጉዳያችን ገና በቅድመ ክስ (Pre Trial) የክርክር ሂደት ላይ ይገኛል፡፡ ይሄ የሆነበት ዋነኛ ምክንያትም መንግስትዎ እንኳን ለእኛ ለተከሳሾች ለከሳሽ አካልም ግልፅ ያልሆነ ክስ በማቅረቡ ነው፡፡ ይሄንንም ስንል ልትፈፅሙት ነበር የተባለው ‘የሽብርተኝነት ድርጊት’ ሳይጠቀስ ‘በቃ የሽብርተኝነት ድርጊት ልትፈፅሙ ነበር’ በማለት በጨበጣ ስለመጣብን ነው፡፡
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር እንግዲህ የብዙ ድብደባ፣ ዛቻ እና ስድብ ሰለባዎች ከሆንን በኋላም የቀረበው ይሄ  ክስ ነው ከ6 ወራት በኋላም ተከሳሾች ከሳሾቻችንም ሳንረዳው በየቀጠሮው እየታሸ ነው የሚገኘው፡፡ ‘የተፋጠነ ፍትህ’ ሕገ መንግስትዊ መብት ነውና የተፋጠነ ፍትህ ይሰጠን፣ እርስዎም ይሄን ሕገ መንግስታዊ መብት ያክብሩ እያልንዎት አይደለም ‘ሕገ መንግስቱ ተከብሮ እያለ ሕገ መንግስቱ ይከበር በማለቴ ጥፋተኛ ነኝ’ በማለት ‘ጥፋት የሚያሳምን’ ( አንዱ የዚህ ደብዳቤ ጸሃፌ ጦማሪ ጥፋት ብሎ አንዲፈርም የተገደደው ህገ መንግስቱ ተከብሮ እያለ ህገመንግስቱ ይከበር ማለቴ ጥፋት ነው ብሎ መሆኑ መንግስትዎን መልክ ግልጽ አድርጎ ያሳያል) መንግስት አለዎትና ይህ ጥያቄ አንደሚበዛብዎት እናውቃለን፡፡
ይልቁንም ቀላልና ግልፅ ቅሬታን ነው ይዘን የመጣነው፡፡ ይሄውም የኢፌድሪ ሕገ መንግስት በአንቀፅ 20/3/ ላይ
‘የተከሠሡ ሰዎች[…]  በፍርድ ሂደት ባሉበት ጊዜ በተከሰሱበት ወንጀል እንደ ጥፋተኛ ያለመቆጠር […]መብት አላቸው::’
በማለት የደነገገ ሲሆን፣ ይሄንን ሕገ መንግስታዊ መብትም ማንኛውም የመንግስት አካል እንዲሁም ግለሰብ የማክበር ግዴታ አለበት፡፡
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር እርስዎና መንግስትዎም በተደጋጋሚ ‘ሕገ መንግስቱ ሳይሸራረፍ እናስከብራለን’ ይላሉና ይሄን ሕገ መንግስታዊ ድንጋጌ የምታውቁት ይመስለናል፡፡ ነገር ግን ከታሰርን ወዲህ ስለእኛ የእስር ጉዳይ በተጠየቁባቸው ጊዜያት ይሄን ሕገ መንግስታዊ ድንጋጌ በመጣስ ‘ፍርድዎትን’ በተደጋጋሚ ሲሰጡ ታዝበናል፡፡ እናስረዳዎ፡- ሐምሌ 12/2006 ዓ.ም በሰጡት ጋዜጣሚ መግለጫ ላይ ስለእኛ እስር ጉዳይ ለቀረበልዎት ጥያቄ ሲመልሱ፡-
‘ከአስመራ እስከ ሞቃዲሾ የተዘረጋው የሽብር ሰንሰለት ውስጥ አንዴ ከገቡ በኋላ ብሎገር ነኝ፣ ጋዜጠኛ ነኝ ማለት ዋጋ የለውም’
በማለት ብዙ ነገሮችን ተናገሩ፡፡ ይሔውልዎት ስህተትዎ፡-
  1.   የክሳችን ዋነኛ ጭብጥ በሃገር ውስጥ ‘የሽብርተኛ ድርጅት በማቋቋም ‘የሽብርተኝነት’ ተግባራትን ለመፈጸም አሲረዋል፡ አቅደዋል… የሚል እንጂ፣ እርስዎም እንደሚሉት ‘ሰንሰለት’ ምናምን አይደለም፣ 
  2.      እሺ አሸባሪዎችም ይበሉን፣ ነገር ግን ሕገ መንግስቱ እንደሚደነግገው በፍርድ ቤት ‘ጥፋተኝነታችን’ እስሚረጋገጥ ቢጠብቁስ ምናለበት? ይህ የሚያመለክተው እርስዎም እነደማእከላዊ መርማሪዎች ነፃ ሆኖ የመገመት (presumption of innocence) መብታችንን እያከበሩልን እንዳይደለ ነው፡፡
ይሄ ነገር የሆነው በድንገት ሊሆን ይችላል ብለን ዝም ብንልም እርስዎ ግን በድጋሚ ጥቅምት 6/2007 ዓ.ም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርበው ከምክር ቤቱ አባል ለቀረበልዎ ጥያቄ ሲመልሱ፡-
“የብሎገር ጭምብል አጥልቆና በጋዜጠኝነት ሙያ ውስጥ ተሸሽጎ ከተከሳሽነት ማምለጥ አይቻልም፡፡ ሽብርተኝነትን መዋጋታችን ይቀጥላል…” እያሉ እርስዎ ያሉትን የብሎገር ጭምብል አውልቀውና ተሸሸጉበት ያሉትን የጋዜጠኝነት ሙያ መሸሸጊያ አፍርሰው ባንዴ ‘የአሸባሪነት’ ካባ ደረቡልን፡፡
ክቡር ጥቅላይ ሚኒስቴር፣ እያልን ያለነው የአንድ ሰው ‘አሸባሪነት/ወንጀለኝነት’ የሚረጋገጠው በፍርድ ቤት እንደሆነ ሕገ መንግስቱ ደንግጎ እያለ፣ እርስዎ ግን ነፃ ሆኖ የመገመት መብታችን ወደ ጎን ብለው እንደ ከሳሽም እንደ ፈራጅም በመሆን ‘አሸባሪዎች’… እያሉን ይገኛሉ ነው፡፡
ምናልባት ‘ስራ አስፈጻሚው ከሳሽ ነውና እኔም የስራ አስፈጻሚው አካል መሪ ስለሆንኩ የፈለኩትን አስተያየት የመስጠት መብት አለኝ’ ብለው ከሆነ፣ ሕገ መንግስቱን የማክበር ጉዳይ ‘ርስዎን ጨምሮ ሁሉም ዜጎች ላይ የተጣለ ግዴታ ነው፡፡ እርስዎ ‘L’e’tat, c’est moi’ ይሉት አይነት የራስ ግምት ውስጥዎ ከሌለ በስተቀር እንዲህ በግልፅ እየጠየቅንዎት ‘ሕገ መንግስትቱን  አላከብርም’ በማለት ገና ዋነኛ ክርክሩ እንኳን ያልተጀመረ ክስን (ዋነኛ ክርክር ካለው) መሠረት በማድረግ ከዚህ በኋላ እኛን ‘አሸባሪዎች’ አይሉንም ብለን ተስፋ እናደርጋለን፡፡ ይህን ተመሳሳይ ምላሽ “በእርግጠኝነት አሸባሪ ናቸው” በሚል ቃና ለቢቢሲ ለኢንቢሲ ለመሳሰሉት አለም አቀፍ ሚዲያ  ተቋማትም መስጠትዎን ሰምተናል፡፡
ሌላው ልናስታውስዎ የምንፈልገው ጉዳይ እንደኛ አይነት የተራገበ( በሰፊው በታወቀ የአደባባይ) የፍርድ ጉዳይ ([un] popular case) ላይ የመንግስት አካላት አስተያየት (say) ያለውን ተፅእኖ እንዲያስቡት ነው፡፡ እርስዎ በምክር ቤት ቀርበው የአሸባሪነት ፍርድ ከበየኑብን (አሁን እያደረጉት እንዳሉት) ፍርድ ቤትም ሆነ ሌሎች የመንግስትዎ አካላት ምን ሊያስቡ እንደሚችሉ አስተውለውታልን?!
ይሄን ሁሉ ስንልዎ እንዲያው ሕጉን ያክብሩልን ለማለት ያክል ነው እንጅ፣ ከሽብርተኝነት ጋር የሚያገናኘን ቅንጣት ያክል እውነት /A segment of fact/ እንደሌለና የሰው ልጆች መልካምና ደስተኛ ሕይወት እንዲኖራቸው ከመመኘትና ለአገራችን ያገባናል ከማለት ያለፈ ሕይወትም ፍላጎትም እንደሌለን እኛም እናውቀዋለን እርስዎና መንግስትዎም ያውቁታል፡፡ ነገር ግን ካለፉት ስድስት ወራት አንስቶ ጨዋታውን በግድ ካልተጫወታችሁ ተብለናልና እየተጫወትን ነው፡፡ የአሁኑ ጥያቄያችን ግን በጣም ቀላል ነው፣ ጨዋታው ገና በደንብ እንኳን ሳይጀመር ውጤቱን እይወስኑት ነው፡፡
እርስዎ ወደ ጠቅላይ ሚኒስትርነት የስልጣን ደረጃ በወጡ ሰሞን አብዛኞች የዚህ ማስታወሻ ፀሃፊዎች መጠነኛ ለውጥና ማሻሻዎች ያደርጋሉ የሚል ተስፋ ሰንቀን “The First 100 Days” ወዘተ እያልን ብዙ ጠብቀንዎት ነበር፡፡ ከሁለት ዓመት በሚበልጥ ግዜ እንደተመለከትንዎ ግን ተስፋችን ፍሬ ሊያፈራልን አልቻለም፡፡ አሁንም አዲስ ተስፋ ሰንቀን ግን ፡- “ክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር እባክዎትን ሕገ መንግስቱን ያክብሩ! የእኛንም መብት ያክብሩልን” እንላለን፡፡
‘’የብሎገር ካልሲ አድርጎ፣ የጋዜጠኝነት ጫማ ተጫምቶ የሽብረተኝነት ሰንሰለት ውስጥ ከገቡ በኋላ ሕገ መንግስቱን ያክብሩልኝ ማለት ዋጋ የለውም!’’ በማለት ተስፋችን ዋጋ እንደማያሳጡት ተስፋ አለን፡፡
ከአክብሮት ጋር
  ጦማርያን                    ጋዜጠኞች
 ዘላለም ክብረት                  ኤዶም ካሳዬ 
 ናትናኤል ፈለቀ                  ተስፋለው ወ/የስ
 በፍቃዱ ሃይሉ                   አስማማው ኃ/ጊዮርጊስ
 አጥናፍ ብርሃኔ                       
 አቤል ዋበላ
 ማህሌት ፋንታሁን
 

የዞን ፱ ጦማርያንና የጋዜጠኞችን የ200 ቀናት እስር አስመልክቶ በማኅሌት ሰለሞን የተዘጋጀ

                                     
                       


                                     
                       

Image
Eritrean refugees in North Ethiopia

በአውሮፓና በአሜሪካ፣ በአፍሪካና መካከለኛው ምሥራቅ፣ በሩቅ ምስራቅና በአውስትራልያ ሳይቀር እያደር
ኤርትራና ስደት ተወራራሽ ቃላት (synonymous) እየሆኑ መጥተዋል። እገሌ/ እገሊት እኮ ኤርትራዊ
ነው/ነች ሲባል ስደተኛ ነው/ነች እንዴ? – ብሎ መጠየቅ የተለመደ አነጋገር ሆኗል። እዚህ አገር ስደተኞች
በዝተዋል ሲባል ሱማሌና ኤርትራውያን በዝተዋል የሚል – ድምዳሜ ላይ ይደረሳል። ኢትዮጵያውኖችም
በዝተዋል ሊባል ትንሽ ቀርቷል።
በቅርብ ዘመናት የነበሩት የኢትዮጵያ ነገስታት ከአውሮጵውያኖች ዘመናዊ መሳርያና ጥቅማጥቅሞችን
ይፈልጉ ነበርና ከባህረ ነጋሹ መሬት (ቦገስ፣ሠሃጢን) ቆንጠር እያደረጉ ለባእዳኑ ኃይላት እንደ መወዳጃነት
ይሰጡ ነበር። የስዊዝ ቦይ ሲከፈት ታድያ የቀይ ባህር ቀጠናነቱ እየጎላ በመሄዱ የአውሮጳ ቅኝ ገዝዎችን
ቀልብ እየሳበ መጣ። በመሆኑም እንግሊዝ ግብጽን – ነጭ አባይን ራሷ መቆጣጠር ፈልጋ ለጥቁር አባይ
ቃፊር በመፈለጓ ይህንኑ ኃላፊነት ኢጣልያ ላይ ወረወረች። ኢጣልያ ይህንኑ ተልዕኮ ተግባራዊ ለማድረግ
ስትቅበዘበዝ የአድዋው ጦርነት ተከስቶ የውርደት ሸማ ተከናነበች። ይሁንና ግን በወቅቱ በነበረው
አስቸጋሪ ነባራዊ ሁኔታ ኢጣልያ ከመረብ ወድያ ያለውን የኢትዮጵያ መሬት በቁጥጥሯ ሥር አደረገች።
በመሆኑም ባህረ ነጋሽን – ኤርትራ የሚል መጠርያ ሰጥተዋት ከእናት ሀገርዋ ነጠሏት።
ኤርትራውያን ከስድሣ ዓመታት በላይ በእጣልያ አገዛዝ በነበሩበት ወቅት የኢጣልያን ስልጣኔ እጅግ
ቀስመዋል። በእጃቸው ከመብላት ይልቅ ሹካና ማንኪያን መጠቀምን ለምደዋል። የቤት ቁሳቁሶችን
አጠቃቀምና በንጽህና አያያዝን ያውቁበታል። አለባበሳቸው ይማርካል። አነጋገራቸውና ዘበናይነታቸው ደስ
ያሰኛል። ጓደኝነታቸው በወረት አይደለም፣ በችግርም ይሁን በደስታ ጊዜ ከወደዱት አይለዩም።
ኤርትራውያን በክልልላቸው ጉዳይ ላይ ድብቅ ቢሆኑም እንኳን በተለያዩ ቁምነገሮች ላይ ለወዳጆቻቸው
ግልጽ ናቸው። ብዙውን ጊዜ ከሸጋዋ ኤርትራዊ ቆንጆ ጋር የተፈጸመ ትዳር እንደ አበባ የፈካ ነው።
ከትዳር አክባሪዋ ኤርትራዊ ጋር የሚመሰረት ጋብቻ ጽናትን ይወልዳል።
ኤርትራውያን ወንድምና እህቶቻችን “ኤርትራን” እንደማትታየዋ “ሠማያዊዋ ሀገራቸው” ሲያመልኳት
ሌሎቹን የአለም አሕጉራት ደግሞ እንደ “ምድራዊ ሀገራቸው” ይቆጥራሉ። ብዙዎች ኤርትራን በሩቅ ሆነው
እንደ መካና መዲና ያከብሯታል፣ ይጨፍሩላታል፣ የጀግኖች ሀገር እያሉ ያወድሷታል እንጂ ጎጇቸውን
ከእሷ ዘንድ መቀለሱን አይመርጡም። በእድሚአቸው የገፉት እንኳን ሳይቀሩ ሀገራቸውን ትተው በውጭ
ሀገር መኖር አይከብዳቸውም። መሰደዱ አላንገሸገሻቸውም። ይህን አስመልክቶ አቶ መለስ
“ኤርትራውያን እግር እንጂ ሀገር የላቸው” – አሉ እየተባለ ይቀለዳል።
ኤርትራውያን አስመራን ንጹሂቷ ትንሿ ሮማ ይሏታል። ሥዕሏ እንደ መላዓከ ሚካኤል ሥዕል ከቢታቸው
ግድግዳ ተለጥፋለች። ነግደው ያተረፉባትን – ተምረው የከበሩባትን አዲስ አበባ ግን ቆሻሻ ይበዛባታል ሲሉ
ያንቋሽሿታል። አፋቤትን፣ ምጽዋን፣ ከረንን፣ ደቀመሀሪን ያንቆላጵሷቸዋል – ረብጣ ነዋይ የዛቁባቸውን
ድሬዳዋን፣ ናዝሬትን፣ አዋሳንና ጅማን አያስታውሷቸውም።
የኤርትራና ስደት መወደጃጀት እክልላቸው መኖር ካለመፈለግ ምክንያት የመነጨ ይመስላል። ስደት
ይቀናቸዋል – ያሳምራቸዋልም። ስለ መሪያቸው አቶ ኢሳይያስ አንዳች ክፉ ነገር ለመናገር የማይፈልጉት
እነዚሁ ኤርትራውያን ይልቁንም በሳቸው ፈላጭ ቆራጭ ባላባታዊ አገዛዝ ምክንያት የመሰደዱ በር ዳግም
ክፍት ስለሆነላቸው በውስጣቸው ያከብሯቸዋል። አቶ ኢሳያስም ቢሆን በበረኸኝነት እልሃቸው ፈረንጆቹን
መናቃቸውና ፊት መንሳታቸው በሌላ በኩል ለኤርትራውያኑ የምዕራቡ ሀገር የመግቢያ ቪዛ መገኛ ስልት
ሆነ።
የኤርትራ የነጻነት ትግል – “ሕዝቡን ነጻ የማውጣት ትግል” – ወይንስ – “መሬቱን ነጻ አውጥቶ ለአቶ
ኢሳይያስ መሸለም”? – የሚለው ጥያቄ አዲስ የማህበራዊ ሳይንስ ንድፈ ሃሳብን ፈንጥቋል። ብዙ ሰዎች
ምትክ የሌላት ሕይወታቸውን ሰውተውላቸው፣ በመድፍና በታንክ እየተታኮሱላቸው የትልቅ ጋሻ መሬት
ብቸኛ ባለቤት እንዲሆኑ በማድረግ – ባለርስቱ ፕሬሲደንት ኢሳያስ በጣት ከሚቆጠሩት የዓለም ሰዎች
አንዱ ናቸው። ግናስ ሕዝቡ አካባቢውን እንደ ኒውክለር ራድየሽን ብክለት እየፈራ የሚፈረጥጠው ለምን
ይሆን? ይህም ጥያቄ አዲስ የማህበራዊ ሳይንስ ምርምርን መፈንጠቁ አልቀረም።
በቅርቡ ሃያ አንድ ዓመት የነጻነታቸውን በዓል ያከበሩት ኤርትራውያን ታሪክ በቅጡ የመዘገበው የግማሽ
ምዕት ዓመት የጦርነትና የስደት ታሪክ አላቸው። ከሃያ አንድ ዓመት በፊት የተጎናጸፉት ነጻነት በየሀገሩ
በስደት የወጡትን ዜጎች ሊመልስ አልቻለም። ይህ ከናቅፋ የተተኮሰው የፋኖ መራዒው የነጻነት ጥይት –
“የመንፈሱን ነጻነት” – ማምጣት አልቻለም። ይልቁንም ከነጻነቱ ማግስት ጀምሮ የሚሰደደውን ሕዝብ
ብዛት ባለፈው ሰላሳ ዓመት ከተሰደደው በመብለጥ ኤርትራውያን ከሶማሌያ ቀጥሎ ምዕራቡን ዓለም
ኢትዮጵያን ጨምሮ እንዲያጨናንቁ አድርጓል። ከባለእርስቱ አቶ ኢሳይያስ ጋር የውስኪ ብርጭቆ
የሚያነሱት የግል አውሮፕላን ነጂዎቻቸው ሳይቀሩ በቅርቡ አውሮፕላኑን ሰርቀው ወደ ሳውዲ
መኮብላላቸው ራሱ አቶ ኢሳይያስ ወዳጅ አልባ መሆናቸውን ያስመሰክራል።
ኤርትራውያኖችን የስደቱ ሰለባ ያደረገው የብሔር ብሔረሰቦችን ጥያቄ አስመልክቶ ንድፈሀሳባዊ ግንዛቤን
ለማግኘት የማርክስንና ኤንግልስን ሥራዎች በጥሞናና ስነምግባራዊ በሆነ መንገድ መረዳትን ይጠይቃል።
በተጨማሪም የራሽያ የጥቅምቱ አብዮት ክስተትንና ተያይዞ የመጣውን የብሔር ጥያቄ ጽንሶችን በጽሞና
መመርመርም ከውዥንብር ያድናል። በእርግጥ የብሔር ብሔረሰብ ጥያቄ አቀንቃኞች ማርክስና ኤንግልስክ
ብቻ ሳይሆኑ ቦልሸቪኮች፣ ሮዛ ሉክሰምበርግና ካርል ካውትስኪም ተጠቃሾች ናቸው።
ማርክስ እ/ኤ/አ በ 1848 ዓ/ም ወደ ተሻለ ማህበራዊ ብልጽግና ደረጃ የሚያሸጋግሩት የምርት ኃይሎች
እድገት (productive forces) ወሳኝ እንደሆኑ አትቶ ይኸው ሂደት በተለያዩ የብሔር ጥያቄዎች ላይ
እንኳን ቢሆን ተጽዕኖ እንደሚያሳርፍ ገልጿል። በመሆኑም በሰራተኛው መደብ (working class) ትግል
ውስጥ የብሔር ጥያቄ የሞተ ነው ሲል ማርክስ ጨምሮ አብራርቷል። የሰራተኛው ትግል መደቦችንና
(classes) ብሔሮችን (nationalities) ስለሚያጠፋ የብሔሮች ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄ ቦታ
አያገኝም ብሎ ነበር። የማርክስ ዋነኛ መፈክር የዓለም ሠራተኞች ሁሉ ተባበሩ ነበር። (workers of all
countries unite)
ማርክስና ኤንግልስክ ከ እ/ኤ/አ 1850 በፊት ስለ ብሔር ጥያቄ በቂ ንድፈሃሳቦችን ያልቀረጹ ቢሆንም ቅሉ
እ/ኤ/አ – በ 1863 በተከሰተው የፖላንድ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን ብሔራዊ ጥያቄ ላይ
አስተሳሰባቸውን በመለወጥ አየርላንድ ከእንግሊዝ ተገንጥላ ራሷን ማስተዳደር ትችላለች የሚል ጠበቅ
ያላለ፣ ብዥታዊ መደምደምያ ላይ ሊደርሱ ቻሉ። ሌኒንም በተመሳሳይ በሠራተኛው መደብ ልዕልና ላይ
በማተኮር የአርመንያኑ ሶሻል ደሞክራሲ የመገንጠልን ጥያቄ በሠራተኛው መደብ ነጻ መውጣት ይፈታል
ቢልም ቅሉ ሀሳቡን በመለወጥ የተጨቆነ ብሒረ እስከ መገንጠል ሊያደርስ የሚችል መብት አለው ሲል
ድንብርብር ያለ ጽሁፍ ሞነጫጭሯል። በሌላ በኩል ደግሞ ስታሊን – ሌኒንን መሠረት በማድረግ አንድ
ሕዝብ ተመሳሳይ ቋንቋ ከተናገር፣ ባንድ አካባቢ ሳይነጣጠሉ የሚኖሩ ከሆኑ፣ አካባቢአቸው ድንበር
ሊበጅለት የሚችል ከሆነ፣ ሕዝቡ በቂ የምጣኔ ኃብት ክምችት ካለው፣ ተመሳሳይ ስነልቦናዊ አመለካከት
እንዲሁም ተመሳሳይ ባህላዊ ትስስር ካለው ብሔር ሊባል የሚያስችለውን መስፈርት ስለሚያሟላ
የመገንጠል ጥያቄ ሊያቀርብ ይችላል የሚል መደምደምያ ሰጠ። ሆኖም ግን ስታሊን ከነዚህ ስድስቱ
መስፈሮቶች አንድ እንኳን ለተጓደለ ብሔር ስለማይባል መገንጠል እንደማይቻል አስጠንቅቋል።
ይህ ከላይ የተመለከትነው የፈረንጆቹ አኳኋን፣ ፖለቲካ፣ ፍልስፍና፣ ርዕዮተ ዓለም፣ ብዥታ፣ አመለካከትና
ነባራዊ ሁኔታን ያላገናዘበ ትምህርት ወደ ኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ ውስጥ ዘልቆ በመግባት –
“የብሔረሰቦች ስታሊናዊ ራስን በራስ ማስተዳደር እስከመገንጠል” – በሚል አጉል ሀሳብ ተቀሽሮ ቀረበ።
ሻዕቢያ ከዚህ ንድፈሃሳብ በመነሳት – “አረብ ነኝ” – የሚለውን ጀብሃ ካስወገደ በኋዋላ በመገንጠሉ ጥያቄ
ጸንቶ ሲያበቃ ኦነግን በራሱ አምሳያ በመፍጠር መከረኛይቱን ኢትዮጵያ በእርስ በእርስ ጦርነት አናውጦ
ሲያበቃ ተገነጠለ።
ሻዕቢያ አስቀድሞም ቢሆን ኤርትራን ለመገንጠል ያመቸው ዘንድ በንጉሡ ዘመን የተሰነዘሩትን
የኢትዮጵያን ጭቁን ሕዝብ ጥያቄዎች በራሳቸው ስውር ዓላማ ሥር ሸሽገው ላይ ላዩን ኢትዮጵያዊ
ተቆርቋሪዎች መስለው በደጋፊዎቻቸው በመታገዝ በጥንቃቄ ሲንቀሳቀሱ ቆይተዋል። ከቀዝቃዛው ጦርነት
ማክተም በኋላ የማርክሲዝም ሌኒኒዝም ሃሳቦች በሚካኤል ጎርባቾቭ ፔሪስትሮይካና ግላስኖስት ተሀድሶ
አዲስ መልክ ቢይዝም ቅሉ ሻዕቢያ፣ ሕወሀትና ኦነግ በመገንጠሉ ርዕዮት ላይ ጽናታቸውን አሳዩ።
ሻዕቢያ በገሀድ፣ ሕወሀት በዘዴ ኦነግ በተቀጽላነት። እንዴት?
የኃይለሥላሴ ንጉሳዊ መንግስት በድንገት መገርሰሱ “ለማርኪሲዝም ሌኒኒዝም” ርዕዮተ ዓለም መስፋፋት
ጥርጊያ መንገድ እንዳዘጋጀ ሁሉ፣ የደርግ በራሱ የውስጡ ቅራኔ ምክንያት መፈረካከሱ ደግሞ
ለብሔረሰቦቹ “የራስን በራስ መወሰን እስከመገንጠል” ዓላማ ተግባራዊነት እጅግ ምቹ ሆነ። ድንገት
ሳይታሰብ የሚኒልክ ቤተ መንግስቱን የተቆጣጠሩት በሕወሀቱ ውስጥ የነበሩት ታጋዮች – “የታላቋ ትግራይ”
– ምስረታን መርሀ ግብር ለጊዜው ወደ ጎን ቢተዉም ቅሉ በወቅቱ ለተከሰተው ድንገተኛና አስቸጋሪ ነባራዊ
ሁኔታ ተጋለጡ። ኢሕአዲጎቹ አባቱ ሻዕቢያን ተከትሎ ኦሮምያን ለማስገንጠል ያሰፈሰፈውን ኦነግ
ለማዘናጋት እንዲሁም አዲስ አበባ ድረስ አብሯቸው የመጣውን የጦር አጋራቸውን ሻዕቢያ ላለማስቀየም
መላ በመዘየድ የብሔረሰቦች ራስን በራስ ማስተዳደር እስከመገንጠል የሚለውን የማርክሲዝም ሌኒኒዝም
ጽንሰሃሳብ አንቀጽ 39 በህገመንግስቱ ውስጥ ለማካተት ተገደዱ። ቀስ በቀስ ግን ኢሕአዲግ የኦነግን
ሠራዊት ከቦ ከማረከና መሪዎቹን ከምክር ቤቱ ሲያስወግድ ” አንቀጽ 39″ ለይስሙላ የተቀመጠች አንቀጽ
መሆኗ ገሀድ ወጣ። የሕወሃቶቹ ትግራይዋዎቹ፣ ከተወሰኑ ዓመታት ቆይታ በኋላ፣ ኤርትራውያን ቀድሞ
ያካበቱት ሃብት ንብረታቸው ተቀምቶ ባዷቸውን እንዲባረሩ ሲያደርጉ መገንጠል ፋይዳ ቢስ የእልኸኞች
ፖለቲካ መሆኑን በማሳየት ከመቶ ሃምሳ ዓመት በፊት ማርክስና ኤንግልስን ውዥንብር ውስጥ ከቶ
የነበረውን የብሄረሰቦች እስከመገንጠል ጥያቄን ውጤት አልባነትን በተግባር በማሳየት ለሲሪላንካ ታሚል
ተገንጣዮች አዲስ ትምሕርት አስገኙ። ኢሕአዲግ በሌላ በኩል ደግሞ የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻ አውጭ
ግንባርን (ኦብነግ) በመፋለም ላይ ሲገኝ የመገንጠሉ ጥያቄ ከስታሊን ጋር አብሮ ለመቀበሩ ገለጻ ለማድረግ
ናይሮቢ ውስጥ ስብሰባ ጠርተዋቸዋል።
በመሆኑም ከስታሊናዊው – “የብሔር ራስን በራስ ማስተዳደር እስከመንገንጠል” – ጽንስ የተወለደችዋ
ኤርትራ ውርዴ ስትሆን አንቀጽ 39 የእንግዴው ልጅ ነው። በዚህም በዚያም ሰበብ ግን ገናናዋና ጥንታዊዋ
ኢትዮጵያ ወደብ አልባ ሀገር እንድትሆን ክፉ ደባ ተሸረበባት።
የመገንጠሉ ሰለባ የሆነው የኤርትራ ሀገር ሕዝብ እንደ ግለሰብ እጅግ መልካሞች ናቸው። ከሚወዷት
እናት ሀገራቸው የነጠላቸው ዘመናዊው የፈረንጆቹ ፖለቲካ ነው። ይኸው የትዕቢትና የማናህሎኝነት
ማኦኢስት ፖለቲካዊ አስተሳሰብ በተማሪዎች ንቅናቄ ዘመን ከነበሩት ተማሪዎችና የዛሬው መሪዎች
አዕምሮ ውስጥ ፈጽሞ እስካልተነቀለ ድረስ ሕዝቡ በራሱ ፈቃድ መኖር አይችልም። ፖለቲካ በማስተዋል
ካልታገዘ መከራን ይወልዳል። ፖለቲካ በጥበብ፣ በትዕግስት፣ በሥነምግባርና በጨዋነት ካልተመራ ሕዝብን
ያሸብራል። ከንቱ እልህና ጀብደኝነት ደሀውን ያሰቃያል። በምስኪኑ ሕዝብ ስቃይ የሚደሰቱ ደግሞ የኋላ
ኋላ የመከራውን ጽዋ ይጨልጡታል። የእቴጌ ጣይቱ ፍርሀት እውን ሆኖ ኢትዮጵያ ራሷ ዘመናዊ
ትምህርት ያስጨበጠቻቸው ልጆችዋ ተረከዛቸውን አነሱባት። በእርግጥ እግዚአብሔር ታሪክ ሠሪ ነው።
ኢትዮጵያን እየጠበቀ ዘመን ከዘመን አሻግሯታል። እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ፈጽሞ አይተዋትም።
የሻዕቢያው ባለሥልጣናትና በርከት ያሉ ኤርትራውያን ደጋፊዎቻቸው ኤርትራ ከእናት ሀገርዋ ኢትዮጵያ
መሬት ጋር ዳግም እንድትዋሀድ አይፈልጉም። ኤርትራን የጀግንነት ምሳሌአቸው፣ የስልጣኔ ምንጫቸውና
የቀይ ባህር በራቸው አድርገው ይቆጥሯታል። ማንም እንዲነካባቸው አይፈልጉም። የሕወሀቶቹ
ኤርትራውያኖቹም ቢሆን ባለርስቱ ፕሬዚደንት ኢሳይያስን ማስቀየም አይፈልጉም። ከዚህ ቀደም ሥልጣን
ላይ በነበሩት የሕወሀቱ ትግራዋዮች የተፈጸመውን ኤርትራን የኢትዮጵያ ኤኮኖምያዊ ድጋፍ ያሳጣውን
ርምጃ ለመካስ በሚቻለው ይሞክራሉ። ላንዳንዶቹ ንግዳቸውንና ቤታቸውን እየመለሱላቸው ነው።
አንዳንዶቹም የተጀጋጀውን ቅጽ እየሞሉ ኢትዮጵያው ውስጥ ኢንቨስት እንዲያደርጉ ፈቅደውላቸዋል።
“ጠርጥር ከገንፎም አይጠፋ ስንጥር” – ያሉ ደግሞ ነገ ምን እንደሚፈጠር ስለማይታወቅ መጠንቀቁ
ይበጃል በሚል አርፈው እተሰደዱበት ሀገር ሆነው አድፍጠዋል።
የሻዕቢያውም ሆነ የሕወሀቱ ቀን የሰጣቸው ኤርትራውያኖች በክፉም በደጉም ጊዜ አብረውት የኖሩትን
የየዋሁን ኢትዮጵያ ሕዝብ ስነልቦናዊ አመለካከት ጠንቅቀው ስለሚያውቁ ማናከሱን፣ ማከፋፈሉንና
ማጠላለፉን እንደ በቀል ዱላ ይጠቀሙበታል። የግፍ ሥራዎችንም የሥልጣን ዘመናቸው ማራዘምያ
ምትሀት አድርገው ሊጠቀሙበት ይሞክራሉ። “የቤት ሥራ” – የሚሏቸውን እነዚህኑ የርኩስ መንፈስ
ሕዋሳት በየፖለቲካ ማህበሮች፣ ትምህርት ቤቶች፤ ሕዝባዊ ስብስቦችና በየመዝናኛ ቦታዎቹ ሳይቀር እንደ
አንደ አንደ መተት እያሰሩ የዋሁን ኢትዮጵያዊ ያደነዝዛሉ። ታድያ ይህን እያወቁ አንዳንድ ተቃዋሚዎች
ከሻዕቢያ ጋር የመሞዳሞዳቸው ጥፋት – “የፖለቲካ ቂልነት” ወይም “የፖለቲካ ንዝህላልነት” – ተብሎ ብቻ
ሊታለፍ የሚችል አይደለም። ማን ይሙት ማን ሻዕቢያ የወያኔን መውደቅ ይሻል? ወያኔም ቢሆን ልብን
በፕሮፖጋንዳ እያደረቀ እግዚአብሄር በቃ እስከሚለው ቀን ድረስ ያሾፋል እንጂ ከኤርትራ ጫፍ እንኳንስ
ጦር ሣር እንደማይመዘዝ ያውቃል።
እግዚአብሄር በቃ ሲል ኤርትራውያን ወንድምና እህቶቻችን በበጎና በንጹህ ፍላጎት ወደ እናት ሀገራቸው
ጉያ ይመጣሉ። ተንኮል – ተንኮልን መውለዱን ያቆማል። መሠሪነት፣ ሸርና ደባ ወደ ጥልቁ ይወረወራሉ።
ጊዜው ይቅረብም ይራቅም እግዚአብሔር ይህንንም መስራት አይሳነውም።
ኢትዮጵያ ስትበደል እግዚአብሔር ዝም አይልም። ሰላምና ብልጽግና – ፍቅርና አንድነት ለመላው ሕዝብ
ይሁን።
ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሄር ትዘረጋለች። አሜን
ከሀበሻ አበበ (ኖርዌ)

እ ጎ አ ከነሐሴ ወር 1961 ዓ ም አንስቶ በርሊንን ከ ሁለት በመክፈል 28 ዓመታት የዘለቀው 15 ኪሎሜትር ርዝማኔ የነበረው የግንብ አጥር የፈረሰበት 25ኛ ዓመት ዛሬ በደመቀ ሥነ ሥርዓት ሲከበር ውሏል። ከበርሊን ውጭ ፤ በአጠቃላይ 155 ኪሎሜትር

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

ኢትዮጵያና ጀርመን ዘመናት የተሻገረ የሁለትዮሽ ግንኙነት በመካከላቸዉ የመሠረቱ ሃገራት መሆናቸዉ በመረጃዎች የተመዘገበ ነዉ። ሁለቱ ሃገራት ይፋዊ የዲፕሎማሲ ዉል ከተፈራረሙም 105 ዓመታት ተቆጥተዋል።

”ፕሮፌሰር መስፍንን ለቀቅ” ለሚለው ለአቶ አንተነህ መርዕድ ጽሁፍ መልስ፣ ቁ. 1 ዛሬ ኦክቶበር 8/2014 ምሳ ሰዓት ላይ አንድ ጓደኛዬ ደውሎ ”ፕሮፌሰር መስፍንን ለቀቅ” የሚለውን ጽሁፍ አንብቤው እንደሆን ጠየቀኝ። ይህ ሰው በፕሮፌሰር መስፍን ማንነት ላይ ይቅርታ ጠይቄው ስለነበር ”ቢጤህ የጻፈውን እየው” ለማልት ማሾፉ ነበር። ለፕሮፌሰር መስፍን ከወጣትነት በተለይም የትግራይ ብሄረተኞች ስልጣን ላይ ሊመጡ አጥቢያ ጀምሮ በየአደባባዩ […]

በገዥው ኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ክንፍ የደ.ህ.ዴ.ን ፖለቲካ ፖርቲ አባላት ወዳጆቸ ባደረጉልኝ ግብዣ መሰረት በደ.ህ.ዴ.ንን 22ኛ ዓመት ክብረ በዓል ላይ ተገኝቸ ነበር ። እንደ ዛሬው የደ.ህ.ዴ.ን በዓል ፍሪዳ ተጥሎ የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ድርጅቶች የልደት በዓላቸውን ሲያከብሩ እግር ጥሎኝ ስገኝ በምባረርበት የጅዳ ቆንስል ግቢ በሚገኘው የኮሚኒቲ አዳራሽ ተገኝቸም ኬክ እስኪቆረስና ሙዚቃው እስኪጀመር ያለውን ፕሮግራም ተከታትያለሁ። በልደት ፕሮግራሙ በቀረበው የድርጅቱ የትግልጉዞ “የስምጥ […]

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

ጀርመንን ለኹለት ከፍሎ የቆየው ግንብ የተገረሰሰበትና ኹለቱ ጀርመኖች ውህደት የፈጠሩበት 25ኛ ዓመት በርሊን ውስጥ እየተከበረ ነዉ። በ15 ኪሎ ሜትሮች ርዝመት ወደ 7000 የሚጠጉ ክብ አንፖሎች ብርሃን እየፈነጠቁ እንደወሰን ቆሞ የነበረዉን ግንብ ማመላከታቸዉ ለበርሊን ነዋሪዎችና ከመላው ዓለም ለተሰበሰቡ ጎብኝዎች መስህብ መሆናቸዉ ተነግሮአል።

Image

-በውሳኔው የማይስማማ ከሆነ በሱና በቤተሰቡ በወዳጆቹ ስም የተመዘገበው ሃብት እንዲጣራ ተብሏል::
-ሳያገግሙ ስብሰባ እንዲመራ እና ሚዲያ ላይ እንዲቀርብ ታዟል::
Minilik Salsawi

የብአዲን/ኢሕአዲግ ከፍተኛ ባለስልጣን የሆኑት አቶ በረከት ስምኦን ያቀረቡት የስልጣን መልቀቂያ ለጊዜው በሚል ውድቅ መደረጉን ሆኖም በቅርቡ መልስ ይሰጥበታል ሲሉ የሕወሓት ባለስልጣናት መመለሳቸውን የውስጥ አዋቂ ምንጮች ለምንሊክ ሳልሳዊ ተናግረዋል::

አብዛኛውን ጊዜ ራሳቸውን ከቤት በማስቀመጥ እና በማዝናናት ያሳልፋሉ የተባሉት አቶ በረከት ስምኦን በልባቸው ላይ በተገጠመላቸው አርቴፊሻል መሳሪያ በጤንነታቸው ላይ ከባድ እክል እንደፈጠረባቸው እና ከወራት በፊት ሳኡድ አረቢያ ታክመው ቢመጡም ሊሻላቸው እንዳልቻለ እንዲሁም ባለፈው ሳምንት በድጋሚ ቢሄዱም ሆስፒታሉ ተስፋ እንዳስቆረጣቸው ሲታወቅ ከሕክምና መልስ ወደ ቢሯቸው የገቡት በጣት የሚቆጠር ቀናት እንደሆነ ታውቋል::

ይህን ሰሞን ስብሰባ መምራት አለብህ በሚዲያ መታየት አለብህ የሚል ግዳጅ ከሕወሓት ባለስልጣናት ወርዶላቸው የተደናበሩት አቶ በረከት ማገገም እንኳን ሳይችሉ በስራ መደራረብ እንዲሞቱ እየተደረገ ነው ሲሉ ከቤተሰባቸው አንዱ የሆኑት ሲናገሩ ተሰምቷል::አቶ በረከት በከፍተኛ ህመም ውስጥ እንዳሉ ሲታወቅ የሕወሓት ባለስልጣኖች የአዜብን ቡድን እንደመቱት ወዲያው በረከትንም ከጠቅላይ ሚኒስቴር ቢሮ አሽቀንጥረው ካሳንቺስ አዲስ ቢሮ እንደሰጡት ሲታወቅ መገፋቱ እያንገበገበው በሽታውን እንዳባባሰበት ታውቋል::

ከጀርመን ዉኅደት በኋላ በምሥራቅ የሀገሪቱ ክፍል የተጀመረዉ ግንባታ ተጠናቆአል። በአዲሶቹ የጀርመን ግዛቶት በአብዛኛዉ ክፍል እጅግ ከፍተኛ ልማት ታይቶበታል። ቢሆንም ይህ ልማት ፍሬያማነቱ እስካሁን አመርቂ እንዳልሆነ ነዉ የሚገለጸዉ። ፍሬ ለማግኘት ገና ብዙ ግዜን ይጠይቃል፤ ያን ለመጠበቅ ደግሞ ግዜ የለም።

ጥቅምት ፳፯ (ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በየስብሰባዎቹ የተሳተፉ ምንጮች ለዘጋቢያችን እንደተናገሩት በየመድረኩ የጋዜጠኞች መታሰር፣ የሃይማኖት እኩልነትና ነጻነት አለመከበር፣ የመልካም አስተዳደር ችግሮች መባባስ፣የሙስናና ብልሹ አሠራር መንሰራፋት፣ የህወሃት የበላይነት መኖር፣ የድህነት መንሰራፋትና የዋጋ ግሽበት አለመቀረፍ፣ በተቃዋሚ ፓርቲዎች ላይ ወከባና እስር መጠናከር በተደጋሚሚ የሚነሱና ኢህአዴግ በቂ ምላሽ ሊሰጥባቸው ያልቻለባቸው አበይት ጉዳዮች መሆናቸው ታውቆአል፡፡ ጥያቄዎቹ በተለይ …

ጥቅምት ፳፯ (ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የድረገጹ አዘጋጆች ለኢሳት በላኩት መግለጫ እንደጠቀሱት ድረገጹ በኢትዮጵያ ውስጥ ወንጀሎችን ያቀዱ፣ ለወንጀሎቹ ውሳኔ የሰጡ፣ ወሳኔዎችን ያስፈጸሙ፣ የመሩና ያቀነባበሩትን በሰሜን አሜሪካ፣ በአውሮፓ እንዲሁም በየትኛውም የምእራብ ሀገሮች እንደ የሀገሮቹ የህግ አግባብ መሰረት ክስ ለመመሥረት የሚያስችሉ ልዩ ልዩ መረጃዎችንና ምስክሮችን ማሰባሰብ እና ማጠናቀር አላማ አድርጓል። ወንጀል በፈጸሙት ላይ በቂ …

አፍሪቃ በጋዜጦች የተሰኘው ፕሮግራማችን ስለ አፍሪቃ ከተጻፉት የተወሰኑትን ጨምቆ ያቀርባል። አንድ ስደስተኛውን የኢትዮጵያ መሬት የማልማት እቅድ ወጣ፣ ብሪትናያ ለኢትዮጵያ ፖሊስ ከምትሰጠው እርዳታ ቀነሰች የሚሉት ይገኙባቸዋ።

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

ፍኖተ ነፃነት

በዛሬው ዕለት ወደ ቂሊንጦ የተዛወሩትን የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ወደ ስፍራው በማምራት አቶ ሀብታሙ አያሌውን፣ አቶ ዳንኤል ሺበሺንና ሌሎችን የፖለቲካ እስረኞችን ማነጋገራቸውን ለፍኖተ ነፃነት ገለፁ፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

የምስራች! ነገ ጠዋት ቅዳሜ ጥቅምት 29 2007 በጉጉት የምትጠብቋት ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣችን በገበያ ላይ ትውላለች፤ እንግዲህ ዝም ያልኩ መስሎዎታል ሲታሰብ ነው እንጂ ዝም ማለት የታል! እንደተባለው፤ አሁንም እስሩ ሲበረታ ዝም ምል መስሎታል መታገል ነው እንጂ እጅ መስጠት የታል! እያላችሁ አንብቧት።

አክራሪ ሙስሊም አማፂ ቡድኖችን የሚቀላቀሉት በብዛት ወንድ ወጣቶች ሲሆኑ ፤ ከቅርብ ጊዜ አንስቶ የሴቶቹም ቁጥር እየጨመረ መጥቷል። ወጣቶች ለምን የሳላፊቾች ቡድንን እንደሚቀላቀሉ እና ያላቸውን ሚና በዛሬው የወጣቶች ዓለም እንቃኛለን።

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት(መኢአድ) የቀድሞ ዋና ጸሃፊ እና አባላት በጸጥታ ሃይሎች ተወስደው ያሉበት አለመታወቁን ፓርቲው አስታወቀ።የአቶ ተስፋዬ ታሪኩ በጸጥታ ሃይሎች ሲወሰዱ በቦታው ነበርኩ የሚሉት ባለቤታቸው ቤታቸው ሲፈተሽ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ አለመያዛቸውን ተናግረዋል።

አምባገነኑ የኢህአዴግ ስርዓት ፖለቲካዊ እስርን እንዳንድ ተቀዋሚዎች የማዳከሚያ ስልት በመውስድ ህግ ወጥ በሆነ ሁኔታ አባሎቻችን በማሳርና በማዋከብ ላይ ይገኛል። አንድነት ከምስርታው ጀምሮ አመራሮቹና አባላቱ የተለያየ ሽፋን በመጠቀም ለእስርና ለእንግልት ተዳርጓል፤ አሁንም እየታሰሩና እየተዋከቡ ይገኛሉ፤ በቅርብ ደግሞ ለየት ባለ ሁኔታ አጠቃላይ ፓርቲው በሚያዳክም መልኩ በሁሉም የሀገሪቱ አከባቢዎች የሚገኙ የአንድነት አባላት እያሳደደ በማሰር ላይ እንደሚገኝ ከየአከባቢው የሚደርሱን […]

ፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም- በነጻነት ለሀገሬ)

እውነታው ከልብወለድ በላይ እንግዳ ነገር ነው!

እ.ኤ.አ ሴፕቴምበር 7/2014 “ድፍረት፡ የፊልም ጠለፋ በኢትዮጵያ ” በሚል ርዕስ ባወጣሁት ትችት ድፍረት በሚለው ፊልም ላይ የኢትዮጵያ መሪ ተዋንያን ሆና በሰራችው የውርጃ ድርጊት ላይ የነበረኝን ቁጣ ገልጨ ነበር፡፡ በአበራሽ በቀለ እውነተኛ ታሪክ ላይ ተመስርቶ የተሰራው ያ ፊልም በአሁኑ ጊዜ ጠለፋ እየተባለ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ለአቅመ አዳም ባልደረሱ ልጃገረዶች ላይ የሚፈጸመውን እውነተኛ ኢሰብአዊ እና ኋላቀር ልምድ በማጋላጥ እየተሰራ ያለውን የትወና ታሪክ ይተርክልናል፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

ነቢዩ ሲራክ

በገዥው ኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ክንፍ የደ.ህ.ዴ.ን ፖለቲካ ፖርቲ አባላት ወዳጆቸ ባደረጉልኝ ግብዣ መሰረት በደ.ህ.ዴ.ንን 22ኛ ዓመት ክብረ በዓል ላይ ተገኝቸ ነበር ።  እንደ ዛሬው የደ.ህ.ዴ.ን በዓል ፍሪዳ ተጥሎ የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ድርጅቶች የልደት በዓላቸውን ሲያከብሩ እግር ጥሎኝ ስገኝ በምባረርበት የጅዳ ቆንስል ግቢ በሚገኘው የኮሚኒቲ አዳራሽ ተገኝቸም ኬክ እስኪቆረስና ሙዚቃው እስኪጀመር ያለውን ፕሮግራም ተከታትያለሁ። በልደት ፕሮግራሙ በቀረበው የድርጅቱ የትግልጉዞ “የስምጥ ሸለቆው ታጋዮች ” የሚል ስያሜ የተሰጠውን የደቡብ የነጻነት ታጋዮች ከህወሃት ጋር ተቀዳጅተው በቅድመ ደርግ ያደረጉትን ትግል ለመጀመሪያ ጊዜ ነበር  የሰማሁት።

ሙሉውን አስነብበኝ …

የሺዋስ አሰፋ የሰማያዊ ፓርቲ አመራር አባል ነው። ሰማያዊ ከመቋቋሙ በፊት ነው የማውቀው። ሰማያዊ እንደተመሰረተ የሰማሁት ከርሱ ነው። የድርጅቱን ድህረ ገጽ ልኮልኝ ከጅምሩ ስለሰማያዊ ፓርቲ አላማ ይነግረኝ ነበር። የሰማያዊ ፓርቲም ደጋፊ ነበርኩ። ሰማያዊ የመጀመሪያዉን ሰልፍ ሲጠራ በዉጭ ያለን አንድነትን የምንደግፍ ድጋፋችንን ለሰማያዊም እንድንሰጥ መጠየቄን አውቃለሁ። የአንድነት ፓርቲ የአዲስ አበባ መዋቅርም በወቅቱ ሰማያዊ በጠራው ሰልፍ መተባበራቸውም አስደስቶኝ […]

ህወሀት የትግራይ ክልልን የግል ሜዳው በማድረግ ስለሚቆጥር ክልሉ ከፓርቲው የተለየ ባንዲራ እንዳይኖረው እስከማድረግ መድረሱ የሚታወቅ ነው፡፡ ከትግራይ ክልል ውጪ ህወሀት አልጋ ሆኖ የማያውቅ ቢሆንም የህትመት ውጤቶች በትግራይ ብርቅ ሆነው ህዝቡ ከህወሀት ውጪ እንዳይሰማ፣ ፕሮፌሰር መስፍን ባንድ ወቅት እንዳሉት፣ ከአንድ ፋብሪካ እንደ ወጣ ምርት፣ አንድ አይነት አስተሳሰብ እንዲይዝ ህወሀት የቻለችውን አድርጋለች፡፡ በትግራይ ክልል ከህወሀት የተለየ አጀንዳ […]

የምሥራቅ አፍሪቃ አፍሪቃ ሃገራት ፤ የኢትዮጵያ ኬንያና ዩጋንዳ መሪዎች፤ 11 ወራት በእርስ በርስ ጦርነት ላይ የሚገኙትን የደቡብ ሱዳን ተቃናቃኝ መሪዎች ለመሸምገል ዛሬም አዲስ አበባ ውስጥ ጉባዔ አካሂደዋል።

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

ጥቅምት ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአባይ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት እቅድ እንደሚያሳየው ግድቡ ሲጠናቀቅ 1600 ኪሎሜትር ስኩየር  መሬት የሚሸፍን ውሃ የሚተኛበት ሲሆን፣ የዚህ መሬት አካል 90 በመቶው በደን የተሸፈነነ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ አንጻራዊ በሆነ መልኩ የተሻለ የደን ሽፋን አለው የሚባለው ግድቡ የሚሰራበት የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቢሆንም፣ ከ200 ኪሎ ሜትር ያላነሰ ስፋት ያለው …

ጥቅምት ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰሞኑን ተጠናክሮ የቀጠለው የገዢው ፓርቲ አፈና መንግስት ራሱ ያስታጠቃቸውን ታጣቂዎች ትጥቅ እስከማስፈታት መድረሱን ምንጮች ገለጹ በትግራይና በአማራ ክልሎች ባለፉት ሶስት ቀናት ሲካሄድ የነበረው አፈና ቀጥሎ ጥቅምት 26 ቀን 2007 ኣም የሰላም ታጋይ እየጠባለ የሚታወቅ ወጣት ሽሻይ አዘናው በመቀሌ ከተማ በትግራይ ክልል የፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ገ/ህይወት ካህሳይ …

ጥቅምት ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰሞኑን በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ በኢትዮጵያ እና በአረብ ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት እንዲሁም መንግስት ወደ አረብ አገራት በሚላኩ ዜጎች ጉዳይ ሊፈጽመው ያሰበው ስምምነት ምን ደረጃ ላይ  እንደደረሰ ግምገማ ተካሂዶ ነበር። መንግስት ተጓዝ ሰራተኞችን በሚመለከተ ያወጣው ህግ በአረብ መንግስታት እውቅና የተነፈገው ሲሆን፣ የአረብ አገራት ባለስልጣናት ኢትዮጵያውያን …

ጥቅምት ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በዩኒቨርስቲው ውስጥ በሚታየው ተደጋጋሚ የሃይል መቆራረጥና የውሃ እጥረት ተማሪዎች ትምህርታቸውን በአግባቡ ለመከታተል አልቻሉም። ከውሃ እጥረት ጋር በተያያዘ ከጽዳት ጋር ለተያያዙ በሽታዎች ሊደራጉ እንደሚችሉ ተማሪዎች ፍርሃታቸውን ገልጸዋል።

«ባርያዉ» በሚል መጠርያዉ የሚታወቀዉ ወጣት ሰመረ ካሳ በመድረክ በሚያቀርባቸዉ አዝናኝና አስተማሪ ቀልዶቹ ተወዳጅነቱ ታዋቂነቱ እየጎላ መጥቶአል። በዕለቱ ዝግጅታችን ባርያዉን ከነቀልዱ ይዘን «ሂስ የማኅበረሰብ አረም መንቀያ መሳርያ ነዉ» ያሉንን ምሑራን ጋብዘን የሂስን ምንነት ለማየት ቀርበናል።

ከ 50 የሚበልጡ የደቡብ ሱዳን ዜጎች፤ የሰብዓዊ ተቋማትና ፤ ዓለማቀፍ የሰብዓዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት እንዲሁም የደቡብ ሱዳን ጎረቤት ሃገራት የተመድ የፀጥታ ምክር ቤት በደቡብ ሱዳን ላይ አስቸኳይ የጦር መሳርያ ማዕቀብ እንዲያደርግ ጥሪ አቀረቡ።

የአፍሪቃ ሕብረት ኮሚሽን ፕሬዚዳንት እንኮሳዛና ድልሚኒ ዙማ ፤ ኢቦላ የተከሠተባቸውን የምዕራብ አፍሪቃ ሃገራት ፤ ሴራሊዮንና ላይቤሪያን ተዘዋውረው ጎብኝተው ከተመለሱ በኋላ ፤ ለርዳታ ለመሠማራት ቃል የገቡትን

የቀድሞው የየመን ፕሬዚዳንት አሊ አብደላ ሳሌህ፣ ዩናይትድ ስቴትስ ገር ለቀህ ውጣ አልችኝ ሲሉ ምሬት -አዘል ቃል ቢሰነዝሩም ዩናይትድ ስቴትስ ፣ ሳሌህ ያሉትን አለማድረጓን ገልጻለች። ባለፈው ሳምንት ዩናይትድ ስቴትስ፤