ዛሬ ማክሰኞ እንደአውሮፓውያን የዘመን ኣቆጣጠር ህዳር አስራ አንድ ቀን በየዓመቱ ሀገራቸውን በውትድርና ያገለገሉ እና መስዋዕትነት የከፈሉላት ወንዶችና ሴቶች የሚከበሩበት ዕለት ነው።

ታዲያ ዩናይትድ ስቴትስን በውትድርና ያገለገሉዋት አርበኞችዋ ዜጎችዋ ብቻ ኣይደሉም። .

በጦር ሃይሎች አገልግሎቱ ለመግባት የአሜሪካ ዜጋ ባይሆኑም ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ ግሪን ካርድ በሚባለው ማመልከት እንዲቻል ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ተፈቅዱዋል።

በዩናይትድ ስቴትስ የመከላከያ ሚኒስቴር መዝገብ መሰረት ጦር ሃይሎችዋ ውስጥ ግዳጅ ላይ ያሉ ከስድሳ ኣምስት ሺህ በላይ እና የውጭ ሃገር ተወላጆች አሉ።

የቪኦኤዋ Deborah Block በዋሽንግተን ኣካባቢ የሚኖሩ ኣንድ የሶማሊያ ኣንድ የፊሊፒንስ ተወላጅ ኣነጋግራ “ኣሜሪካ ጦር ሰራዊት ውስጥ ገብታችሁ ህይወታችሁን ለኣደጋ ማጋለጥን…

ደካማ የመንግስት አስተዳደር ለመለወጥ ምርጫ ያስፈልጋል፡፡ይሁን እንጂ ነጻነት በሌለበት ፍትሃዊ ምርጫ ማካሄድ አይቻልም፣ በምርጫ ሥም ጫፍ ላይ የደረሰው ሠላማዊ የነጻነት ትግል ጥያቄ መዳፈን የለበትም፡፡

======================

“ብልህነት የተሞላበት ታላቅ የትግል መርህ ማድረግና መስፋፋት፣ጥንቃቄ የተሞላበት ዕቅድ፣ጠንካራ ሥራና ሥነ-ሥርዓታዊ አበራታች ትግል ለድል የመብቃቱ ዕድል የሰፋ ነው፡፡” ይህ ፁሑፍ የተወሰደው ከአምባገነን አገዛዝ ወደ ዲሞክራሲ ከሚለው ከ ጄን ሻርፕ መፃሐፍ ነው፡፡ በዙህ አጋጣሚ ይህ መፃፍ እጅግ በጣም ጠቃሚ ነው፣በተለይ በአገር ውስጥ ለሚንቀሳቁ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ለሚያደርጉት አመፅ አልብ ትግል ብዙ አመላካች መረጃዎችን የሚሰጥ ነው፡፡ ዜጎች በሰላማዊ መንገድ የመሰብሰብና የመንግስትን የፖሊሲ ውሳኔዎች እና አሰራሮች የመቃወም መብታቸው የተጠበቀ ነው፣በሰላማዊ ሰልፍ፣በተቃውሞ የፊርማ ሰነድ ፣ለመንግስት ጥሪ ባለመተባበር፣በሥራ ማቆም አድማና በመሳሰሉት ዘዴዎች ተቃውሞ መግለፅ አለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው የዲሞክራሲ መብት ነው፡፡ በዓለም አቀፍ የተባበሩት መግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ጉባሄ ባፀደቀው መግለጫ ኢትዮጵያም በፈረመችው ስለ መሰብሰብ እና መደራጀት መብቶች የሚከተሉትን ብሏል ‹‹ የዜጎች የመሰብሰብ እና የመደራጀት መብቶች ተግባራዊ ሂደት ገደብ በማይጣልበት ሁኔታ መከበር ሲኖርበት ነገር ግን ገደብ ቢደረግ እንኳን ገደቡ የዓለም ዓቀፍ ህግና ሰብአዊ መብቶችን መሰረት ያደረገ እና የእነዚህን መብቶች ሁለንተናዊ ጥበቃ እዉን የሚያደርግ መሆን አለበት፤በተለይም ዜጎች የፖለቲካ እና የአይማኖት ለማስከበር የሚያደርጓቸው ተቃውሞዎች መደገፍ አለባቸው፡፡ ››የሚል ሲሆን ፡፡የኢፌዴሪ ህገ መንስት አንቀፅ 30 ንዑስ አንቀፅ 1 ማንኛውም ሰው ከሌሎች ጋር በመሆን መሣሪያ ሳይዞ በሰላም የመሰብሰብ ፣ሰላማዊ ሠልፍ የማድረግ ነፃነት እና አቤቱታ የማቅረብ መብት አለው፡፡ በማለት በህገመንግስቱ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ ሆኖም ግን ይህ መብት ምን ያህል በአገራችን ተፈፃሚ ነው ብሎ መጠየቅ እና ምላሹን ማወቅ ብዙ እርቀት መሄድን የማይጠይቅ አይደለም፡፡ ከዚህ ቀደም በተለያየ ወቅት እና ቦታ በሰማያዊ እና በአንድነት ፓርቲ የተደረጉ አመፅ አልባ የአደባባይ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች ምን ያህል ፈተኛ እንደነበሩ ለአብዛኞቻችን ግልፅ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ሂደቶ የገዥው መንግስት ፍላጎት ከማስጠበቅ አንፃር እንጂ በየትኛውም ሕግ ድጋፍ ሣይኖረው አብዛኛው የተቃውሞ እንቅስቃሴ ውጤት አልባ እንዲሆን ተደርጓል፡፡ይህ ማለት ግን የተደረጉ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች ሁሉ ውጤት አልነበራቸውም ማለት አይደለም፡፡ መንግሰት የሕግ ድጋፍ ሣይኖረው በራሱ ፍላጎትና ፍራቻ ብቻ የህዝቡን ቅሬታዎች ሁሉ ጫና በመፍጠር አፍኖን እንገኛለን፡፡ እንዲህ አይነቱን ሕገ-ወጥ መንግስታዊ ሥራ፣ አልቀበለም ማለት የማንኛውም ኢትዮጵያዊ ግዴታም ነው፡፡ይህን ደግሞ የማሳውቅ እና የማንቃት ኃላፊነት ስለ-አገሬ ጉዳይ ያገባኛል የሚል ሁሉ የሚመለከተው ሲሆን ፣በተለይ ፓርቲዎች የቀን-በቀን ሥራቸው መሆን አለበት፡፡ይሄንን ኃላፊነታቸውን በአግባቡ የተረዱ፣ ጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም ትብብር የመሰረቱት ዘጠኝ ፓርቲዎች “ ነፃነት ለፍትሃዊ ምርጫ” የሕዝባዊ ትግል ፕሮግራም የመጀመሪያ ዙር እንቅስቃሴ ይፋ አድርገዋል፡፡ በኢትዮጵያ የተቃወሞ እንቅስቃሴ በተቃዋሚ ፓርቲዎች ትብብር የተጠራ አመፅ አልባ የ24 ሰዓት የአዳር የአደባባይ የተቃውሞ ትይንት በታሪክ የመጀመሪያ ጊዜ ነው፡፡እንዲህ አይነቱ የሞራል የበላይነት እና ጥልቀት ያለው ሃሳብን የሚጠይቅ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ጥሪ ላስተላለፉት ፓርቲዎች በሙሉ አድናቆትን በሙሉ ልብ የሚያሰጥ ነው፡፡ በዚህ አጋጣሚ ሌሎች እውነተኛ የተቃዋሚ የፓርቲዎች በትብብሩ ያልታቀፉ፣ በተለይም በሂደቱ ከጅምሩ እስከ መጨረሻው ተሳትፋው በተለያየ ምክንያት የስምምነቱን ሰነድ ያልፈረሙ፣ የተቃውሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች ከጋራ ትግሉ ብትቀላቀሉ ውጤቱ የበለጠ ያማረ ይሆናል፡፡በመሆኑም ከሕግ አግባብ ውጪ በማን-አልብኝ እና ትምክተኝነት የተነጠቅነው “የአደባባይ ተቃውሞ” የምናስመልስበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው፡፡ ይዚህ ጽሑፍ አቅራቢ፣ ከዚህ ቀደም “ኢህአዴግ ለምርጫ አልተዘጋጅም” በሚል ርዕስ፡፡ “ኢሕአዴግ በጭራሽ እራሱን ነፃ ለሆነ የምርጫ ውድድር እያዘጋጀ አይደለም !የፖለቲካ ሊቃውንት እንደሚያስገነዝቡት እና ዓለም አቀፍ ነባሪዊ ሁኔታ የሚያመላክተው ለምርጫ መሰረታዊ ከሆኑት ውስጥ ፤በእኩል ደረጃ ባይወንም እንኳን በአንፃራዊነት የተወዳዳሪ ፓርቲዎች ነፃነት እና እኩል ተሣትፎ ሊኖር ይገባል፣ፓርቲዎችን ሊያወዳደሩ የሚችል ከማንኛውም ተጽእኖ ነፃ የሆነ ምርጫ ቦርድ እና ጉዳዩን ሙያዊ ስነምግባር መሠረት በማድረግ ለህዝብ መረጃ የሚያደርስ ነፃ ሚዲያ ያስፈልጋል፡፡እነዚህ መሰል ዋንኛ መስፈርቶች ባልተሟሉበት በአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ፣ በመጪው ግንቦት ወር ነፃ ምርጫ ማካሄድ የሚታሰብ አይደለም፡፡” ሲል ግንዛቤውን አቅርቧል፡፡ ፍትሃዊ ምርጫ የማይታሰብ በመሆኑ፣ የተዘጋውን በር ለማስከፈት ይቻል ዘንድ በ9 ፓርቲዎች ትብበር ትግሉን የ ‹‹ ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል የፕሮግራም መርህ የመጀመሪያውን ዙር እንቅስቃሴ በአዲስ አበባ ከተማ ለማድረግ የአንድ ወር ዕቅድ አዘጋጅቷል፡፡ በዕቅዳቸው መሠረት ዝግጅቱ የፕሮግራሙ የአፈጻጸም ስልት ፣የጊዜ ሰሌዳ፣ የቦታ ሽፋን፣የፋይናንስ ምንጭ፣ ዓላማዎች፣ትኩረት የሚደረግባቸው ጉዳዮችና መንግስታዊና የህዝብ ክፍሎች፣ዋና ዋና ተግባራት ፣በተጨማሪም በታሳቢነት በአፈጻጸም ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮች/ደንቃራዎችና ሥጋቶች እንዲሁም ለፕሮግራሙን ስኬት አጋዥ ሁኔታዎች እንዲካተቱ አድርገዋል፡፡ይህ ደግሞ ከላይ እንደተገለፀው የፓርቲዎቹ ጥንቃቄ የታከለበት ዕቅድ መንደፋቸው የሚያመላክት ነው ፡፡ዘጠኙ የትብብር ፓርቲዎች በህዳር ወር የሚያተኩሩባቸው የተቃወሞ ተግባራትን እንደሚከተለው ይፋ አድረገዋል፡- 1.በየቤተ እምነቱ ጸሎት ፕሮግራም እንዲደረግ ጥሪ ማድረግና አባላት እንደየእምነታቸው ተሳትፎ ማድረግ፤ 2. በምርጫ ዙሪያ የፓናል ውይይቶችን ማድረግ፤ 3. የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባዎችን ማድረግ፤ 4. ለመንግሥታዊ ተቋማት ደብዳቤ ማስገባት፤ 5. የተቃውሞ ድምጽ ማሰማት፤ 6. የህዝብ ተሳትፎ ማበረታታትና ድጋፍ ማሰባሰብ፤ ናቸው፡፡ የነዚህ እንቅስቃሴዎች ማጠቃለያ ሕዳር 27 ተጀምሮ ሕዳር 28 የሚያበቃ የ24 ሰዓት የአዳር “የአደባባይ ተቃወሞ” ነው፡፡ በዚህ ፁሑፍ መግቢያ ላይ እንደተገለፀው “ብልህነት የተሞላበት ታላቅ የትግል መርህ ማድረግና መስፋፋት፣ጥንቃቄ የተሞላበት ዕቅድ፣ጠንካራ ሥራና ሥነ-ሥርዓታዊ አበራታች ትግል ለድል የመብቃቱ ዕድል የሰፋ ነው፡፡” እንደተባለው ሁሉ በዘጠኙ የተቃወሚ ፓርቲዎች የተጠራው የሕዳር ወር የተቃውሞ እንቅስቃሴ በስልት የተሞላ ስለሆነ ሂደቱ እና ውጤቱ ታሪካዊ እንደሚሆን ተስፋ የሚጣልበት ነው፡፡ ገዥው ፓርቲ እንዲህ አይነት ገፍቶ የመጣ ሕዝባዊ ጥያቂ ዕድል በመስጠት ፣ለሚጠየቁ ሕጋዊና ሰላማዊ ጥያቄዎች አዎንታዊ ምላሽ መስጠት ይጠበቅበታል፡፡ይህ ደግሞ መንግሰት ደግ ስለሆነ የሚያደርገው ሣይሆን ግዴታውም ጭምር ስለሆነ ነው፡፡ሆኖም ግን ከዚህ በተቃራኒ በጦር መሣሪያ ኃይልና በደህንነት አቅም በመመካት የሕዝብን ጥያቄ ለማፈን በተለመደው መልኩ መሄድ ከባድ ቀውሶች እንዲፈጠሩ መመኘት ነው፡፡ ይሁን እንጂ እንዲህ አይነቱ አሉታዊ ነገር መንግስት እንዲፈጠር ቢፈለግ እንኳን፣ ሕዝብ ከፓርቲዎቹ በሚሰጠው መመሪያ ሥነ-ሥርዓታዊና ደፋር እርምጃ ፣ብልህነት የተሞላበት አካሄድ በመከትል ፤አደባባይ ይዞ የወጣውን ጥያቄ ምላሽ አሰጥቶ፣ ሁሉም ነገር በሠላም እንደሚያበቃ የለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ ፍላጎት ነው፡፡ በዚህም መሠረት የጉዳዩ ባለቤት የሆኑት የተቃዋሚ ፓርቲዎች ‹‹የፖለቲካ ምህዳሩ ጠቧል›› ከሚለው አልፎ ‹‹ ተዘግቷል›› ወደሚል ድምዳሜ መሸጋገራቸውን በተጨባጭ ማስረጃ አረጋግጠዋል፡፡እዚህ ደረጃ ላይ መድረሳችሁንም በጋዜጣዊ መግለጫቸው ለሕዝብ አሳውቀዋል፤ሕዝቡ ደግሞ ወትሮም ቢሆን በአገራችን እየተካሄዱ ባሉ ምርጫዎች ሙሉ በሙሉ እምነት የለውም፡፡ይህ ደግሞ “ሰኔ እና ሰኞ” እንደሚባለው ነው፡፡ አሁን ላይ የእምነት ነጻነት ጠያቂዎች፣ጋዜጠኞች፣ጦማሪያን፣የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችና አባላት፣ ከገዢው ፓርቲ የተለየ ሃሳብ ያላቸው ዜጎች በአፋኝ ህጎች፣ በፈጠራ ወንጀል ተከሰው አንድም በወህኒ ወይም በስደት ይገኛሉ፡፡በአገራችን የተረጋጋ የፖለቲካ ሥርዓት የለም፣የኑሮ ውድነት የአብዛኛ ኢትዮጵያዊ ትከሻ ያጎበጠ ነው፣ዜጎች በአገራችን ኢትዮጵያ ከቦታ ቦታ ተዘዋውሮ የመንቀሳቀስ እና ንብረት የማፍራት እንዲሁም የመኖር መብት እየተነፈገ ነው፣ሥራ-አጥነት፣ስደት ፣በአገር ላይ ተስፋ መቁረጥ እና ሌሎች መሰል ችግሮች በመንግሰት አስተዳደር ድክመቶች አማካኝነት የተከሰቱ ናቸው፡፡ ስለዚህም እንዲ አይነቱ ደካማ የመንግስት አስተዳደር ለመለወጥ ምርጫ ያስፈልጋል፡፡ይሁን እንጂ ነጻነት በሌለበት ፍትሃዊ ምርጫ ማካሄድ አይቻልም፣ በምርጫ ሥም ጫፍ ላይ የደረሰው ሠላማዊ የነጻነት ትግል ጥያቄ መዳፈን የለበትም፡፡ በመጨረሻም ለዚህ ጽሑፍ ማጠቃለይ እንዲሆን ሙሉ በሙሉ ከዘጠኙ የፓርቲዎች ትብብር ከሰጡት ጋዜጣዊ መግላጭ ሃሳብ በመዋስ ነው፣የዚህም ፁሑፍ አቅራቢ ከዚህ የተለይ እምነት የለውምና፡፡ “ ገዢው ፓርቲ በጉዳይ ፈጻሚው የምርጫ ቦርድ በኩል በተለመደው መንገድ በምርጫ ሥም ለመሥራት የተያያዘውን ቧልት ራቁቱን በማስቀረት ለ ነጻ፣ፍትሃዊ፣ ተኣማኒና አሳታፊ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ፣ የምርጫ ሜዳውን እንዲያስተካክል በሠላማዊ ትግል አዎንታዊ ተጽዕኖ ለማሳረፍ በእኛ በኩል አስፈላጊውን መስዋዕትነት ሁሉ ለመክፈልና እስከ መጨረሻው በጽናት መቆም ” በማለት ድምዳሜ ላይ ደርሰዋል ፡፡ይበል !!!

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር !
Image

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

በግብፅ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች (መያዶች) ምዝገባ ቀነ-ገደብ ሰኞ ኅዳር 1 ቀን፣ 2007 ዓም ተጠናቋል። የመያዶች አዲስ ሕግ መነሻ በቀድሞው የግብፅ ፕሬዚዳንት ሆስኒ ሞባረክ ወቅት እጅግ አፋኝ እንደነበረ የሚጠቀስለት ሕግ እንደሆነ ተነግሯል። በርካታ መያዶች የመወረስ አለያም የመዘጋት ዕጣ እንደተጋረጠባቸው በስጋት ተውጠው ገልጠዋል።

Image
ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ የብር 20,000(የሃያ ሺህ ብር) ዋስ ተጠይቆበት ወደ ማረፍያ ክፍል መግባቱ ታወቀ፡፡
ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር የጅማ ዩኒቨርሲቲ ባቀረበበት ክስ የፕሬስ ህጉን በሚፃረር መልኩ ለአራት ቀናት በማዕከላዊ ታስሮ የተለቀቀው ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ ክሱ እንደ አዲስ እንዲቀሰቀስበት ከተደረገ በኋላ ዛሬ በተለምዶ ገዳም ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ባለው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ሁለተኛ የወንጀል ችሎት ከእንቁ መፅሔት አምደኛ አምሳሉ ገ/ኪዳን ጋር እንዲቀርብ ተደርጓል፡፡
ችሎቱ በሰጠው ትዕዛዝም ጋዜጠኛ ኤሊያስ ገብሩ እና የእንቁ አምደኛ አምሳሉ ገ/ኪዳን እያንዳንዳቸው የብር 20,000(የሃያ ሺህ ብር) ዋስ እንዲያቀርቡ እስከዛውም ወደ ማረፊያ እንዲሄዱ አዟል፡፡ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ እና አምደኛ አምሳሉ ገ/ኪዳን በአሁኑ ሰዓት ችሎት መድኃኔዓለም አካባቢ በሚገኘው ወረዳ 8 ጣቢያ እንደሚገኝም ታውቋል፡፡

በቅርቡ ይፋ የሆነ ሠነድ እንዳመለከተዉ በአሁኑ ወቅት በዓለማችን 382 የስኳር ሕሙማን አሉ። በዚያ ላይም 316 ሚሊዮን ሕዝብ 2ኛዉ ደረጃ (ታይፕ 2 ) ለሚባለዉ የስኳር ሕመም የመጋለጥ እድሉ ሰፊ እንደሆነ መረጃዉ ይጠቁሟል።

ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት የዛምቢያ ፕሬዚደንት ማይክል ሳታ ሥርዓተ ቀብር ዛሬ በመዲናይቱ ሉሳካ ተፈፀመ። የፕሬዚደንት ሳታ ይፋ የቀብር ሥነ ሥርዓት ከ50,000 የሚበልጡ የሀገሪቱ ዜጎች እና በርካታ የአፍሪቃ ሀገራት መሪዎች በተገኙበት በአርበኞች ስቴድየም ውስጥ ነበር የተከናወነው።

የጀርመን ፌደራል መንግሥት የኤቦላ ጉዳይ ተጠሪ ቫልተር ሊንድነር የጀርመንን ተሳትፎ ሲያወድሱ ሌሎች የርዳታ ድርጅቶች የጀርመን ድጋፍ የተጓተተ ነው በማለት ይተቻሉ። በዛሬው የአውሮፓ እና ጀርመን ዝግጅት የምናነሳው ርዕስ ነው ።

ኢብቲህል አብደልላጢፍ በቀድሞው የቱኒዚያ አምባገነን ገዢ በዚን አል- አብዲን ቤን አሊ የቱኒዚያ ስርዓት ስር በደል የደረሰባቸውን ሰዎች ጉዳይ ይከታተላሉ። ወይዘርዋ ቀደም ሲል በአንድ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ውስጥ፣ አሁን ደግሞ በሀገሪቱ የሀቅ አጣሪ ኮሚሽን ውስጥ ያገለግላሉ።

የኢትዮጵያ አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) መንግሥት በፓርቲዉ አመራርና አባላት ላይ የሚሰነዝረዉን ማዋከብ ከምንጊዜዉም በላይ አጠናክሮ ቀጥሎአል ሲል ከሰሰ።

ኀዳር ፩(አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- “የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የኢህአዴግ የምርጫ ድል የልማት ሰራዊት ግንባታ አደረጃጀት ማንዋል ለምርጫ 2007″ በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ሰነድ በጥቅምት ወር በአዋሳ እንዲቀርብ ተብሎ የተዘጋጀ ቢሆንም፣  የሰነዱ ጥራት የወረደና በሰነዱ የተካተቱት ነጥቦች ከልማት ሰራዊቱ ኢህአዴግ ሙሉ በሙሉ መጠቀሙን  አያረጋግጥም በሚል  በኢህአዴግ ጽ/ቤት በመተቸቱ እንዲሻሻል ከተደረገ በሁዋላ እንደገና ህዳር 1 …

ኀዳር ፩(አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የአማራ ክልል የአስተዳደር እና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ደሴ አሰሜ እንደተናገሩት በምዕራብ ጎጃም ዞን ሜጫ ወረዳ ፤ ሰሜን እና ደቡብ አቸፈር ስራ አጥ ወጣቶች በከፍተኛ ሁኔታ ወደ ግንቦት ሰባት እና አርበኞች ግንባር እየተቀላቀሉ ነው። የወረዳው ወጣቶችን ያወያዩት ሃላፊው ወጣት አርሶ አደሩ ተምሮ ስራ ካላገኘ ፤ ወይ የሚያርሰው …

ኀዳር ፩(አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከሰሜኑ የአገሪቱ ክፍሎች የታፈኑ  የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ወደ ማዕከላዊ መዛወራቸውን ነገረ ኢትዮጵያ ዘግቧል፡፡ በሰሜን ጎንደር ዞን የሰማያዊ ፓርቲ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ አግባው ሰጠኝ ፣ የምእራብ አርማጭሆ  የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ  ሰብሳቢ አቶ አንጋው ተገኝ  ትናንት  ወደ ማዕከላዊ መወሰዳቸውን ጋዜጣው ዘግቧል። ሌሎች የተቃዋሚ አመራሮች ወደ ማእከላዊ ይወሰዱ አይወሰዱ …

ኀዳር ፩(አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ገልፍ ኒውስ ባወጣው ዘገባ 4 ወንዶች አንዲት ኢትዮጵያዊትን አአስገድደው መኪና ላይ ከጫኑዋት በሁዋላ በየተራ ደጋግመው በመድፈርና በመኪናቸው ገጭተው በመግደል በላዩ ላይ ድንጋይ በማስቀመጥ ለማምለጥ ሞክረዋል። ግለሰቦቹ ተይዘው ፍርድ ቤት ከቀረቡ በሁዋላ የጄራጂ ፍርድ ቤት በግለሰቦቹ ላይ የሞት ፍርድ ለማስተላለፍ በሂደት ላይ ነበር። ይሁን እንጅ ዳኛ አብዱላህ የሱፍ …

አባቶቻችን በቤተ ክርስቲያን ላይ ግለሰባዊ ዓምባገነንነትን አልፈቀዱም የቤተ ክርስቲያን አሠራርና አመራር ማኅበራዊና ጉባኤያዊ ነው፡፡ ግለሰባዊ አመራር÷ ክሕደትንና ኑፋቄን ለማስገባት፣ ለሌሎች አካላት ቁጥጥር እና ዘመን የፈቀደለት ኹሉ ልቡ የወደደውን በቤተ ክርስቲያን ላይ እንዲጭን ያመቻል፡፡ ቤተ ክርስቲያን እንደ መኪና መሪውን የያዘ መኪናውን ወደ ፈለገው ሊወስደው የሚችልባት ቦታ ብትኾን ኖሮ ዘመነ ሱስንዮስን መሻገር ባልቻለች ነበር፡፡ *             *             * …

( …. መርዝን በመርዝነት ስለመርዝ መመረዝ :
የመርዙን ለመርዙ በመርዙ ማስመረዝ …. )
(መርዝ ……. ::) #Ethiopia #EPRP #EthiopiaTeachers #MinilikSalsawi
iframe
የታላቁ ገጣሚ እና ባለቅኔ ሃይሉ ገብረዮሃንስ (ገሞራው) አጭር የሕይወት ታሪክ http://www.debteraw.com/gemoraw/ = ድምጽ ላጣው ሕብረተሰብ ድምጽ ሆኖ በማስተጋባቱ በሶስት መንግስታት ስቃይ ያየ ታላቅ ኢትዮጵያዊ ሃይሉ ገሞራው – ቨድዮውን ይመልከቱት

phpBB [video]

Image

ኢትዮጵያ በሰብዓዊ መብቶች ላይ የምትፈጽመውን ጥሰት ካላቆመች የአፍሪካ ህብረት መቀመጫውን ከአዲስ አበባ መቀየር አለበት ተባለ። በደቡብ አፍሪካ ዊትስ ዩኒቨርሲቲ በተካሄደ የአፍሪካ የምርመራ ጋዜጠኝነት ጉባኤ ላይ አንጎላዊው ጋዜጠኛ ራፋኤል ማርኩዌዝ ደ ሞራይዝ የኢትዮጵያ መንግስት ያሰራቸውን ጋዜጠኞች መፍታት አለበት ብሏል።
Image

ራፋኤል ማርኩዌዝ ደ ሞራይዝ አንጎላዊ ጋዜጠኛ ነው። በሙያው በሃገሩ አንጎላ በርካታ ክስ እና እስር እንደገጠመው ይነገራል። ባለፈው ወር በደቡብ አፍሪካ ዊትስ በተካሄደው የአፍሪካ የምርመራ ጋዜጠኝነት ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽን ጨምሮ በሰብዓዊ መብቶች ላይ ጥሰት በመፈጸም ከአፍሪካ ህብረት ህልም በተቃራኒ ቆማለች በማለት ተችቷል። ”የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ በቀዳሚነት የመላ አፍሪካውያንን ህልም ይወክላል። የሰው ልጅ ክብር እና የሰብዓዊ መብት ክብር ደግሞ የሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ህልም ነው። ኢትዮጵያ በዚህ ረገድ የሰዎችን ሰብዓዊ መብት በመጣስ በተቃራኒው መንገድ እየተጓዘች ነው። ይህ ደግሞ የአፍሪካውያንን ህልም አይወክልም። የኢትዮጵያ መንግስት ያሰራቸውን ጋዜጠኞች በመፍታት ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ ነጻነትን እንዲያከብር እና ዜጎች እና ጋዜጠኞች ህገ-መንግስታዊ መብታቸውን በተግባር እንዲያውሉ እንዲፈቅድ የአፍሪካ ህብረት ጫና ማድረግ ይኖርበታል። ”

ራፋኤል በጉባኤው የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎችን እስር እና ክስ እንዲሁም የቀድሞው ፍትህ ጋዜጣ አዘጋጅ ተመስገን ደሳለኝን የሶስት አመት ብያኔ በማሳያነት አንስቷል። አፍሪካውያን ጋዜጠኞችና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች በኢትዮጵያ ያለውን ሁኔታ በቸልታ አልፈዋል ሲልም ተችቷል። ኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብትን ማክበር ካልቻለች የአፍሪካ ህብረት ከአዲስ አበባ መነሳት ይኖርበታል ብሎ ያምናል።

”የተወሰኑ ጋዜጠኞችን አውቃለሁ። በ2005 ተኩስ ሲጀመር እና ተቃዋሚ ፖለቲከኞች ሲታሰሩ በአዲስ አበባ ነበርኩ። አሁን በሃገሪቱ ስላለው ሁኔታ በቂ ግንዛቤ አለኝ። ከኢትዮጵያውያን ምሁራን እና አሁን ባለው መንግስት የተለያየ ጫና የደረሰባቸውን ሰዎች አገኛለሁ። የአፍሪካ ህብረትን ለመወከል በመጀመሪያ ሰብዓዊ መብትን የሚያከብር ሃገር እንፈልጋለን። ኢትዮጵያ ይህንን ማድረግ ካልቻለች እንደ አፍሪካዊነታችን የአፍሪካ ህብረት መቀመጫውን ዜጎች ራሳቸውን የመግለጽ እና ሰብዓዊ መብት ወደ ተከበረበት ሃገር እንዲዛወር መጠየቅ ይኖርብናል። ምክንያቱም ግለሰቦች የሚከበሩባት መንግስታት የህዝብ አገልጋይ እንጂ ከህግ በላይ ያልሆኑባት አጋርነት የጠነከረባት አፍሪካን እንሻለን። ኢትዮጵያ ደግሞ በአሁኑ ወቅት ይህን እያደረገች አይደለም። ””

ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች ቡድን ባለፈው ሳምንት ባወጣው ዘገባ ባለፈው አመት ብቻ በኢትዮጵያ ስድስት የህትመት ውጤቶች ሲዘጉ ከ ሰላሳ በላይ ጋዜጠኞች መሰደዳቸውን ይፋ አድርጓል። በምህጻሩ ሲፒጄ ተብሎ በሚጠራው የጋዜጠኞች መብት ተከራካሪ ተቋም መሰረት ደግሞ ቢያንስ 17 ጋዜጠኞች በኢትዮጵያ በእስር ላይ ይገኛሉ። ራፋኤል ማርኩዌዝ በእስር ላይ ያሉ ጋዜጠኞች እንዲፈቱ አፍሪካውያን ሊተባበሩ ይገባል ሲል ይናገራል።

”አፍሪካውያን በሙሉ በተለይም ጋዜጠኞችና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች በትብብር ከሰራን የኢትዮጵያ መንግስት ቆም ብሎ ራሱን እንዲፈትሽ ማድረግ እንችላለን። አላማችን ኢትዮጵያን ማግለል አይደለም። አላማችን ኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን እንድታከብር ሃሳባቸውን በነጻነት የመግለጽ መብታቸውን በመጠቀማቸው የታሰሩትንም እንድትፈታ ነው።”

http://www.dw.de/%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1% … a-18051929

ፎቶ – ሐራ ተዋሕዶ

ቅዱስ ሲኖዶስ የቤተ ክርስቲያንን ሕግ በተመለከተ አሠረ ሐዋርያትን የተከተለ ሆኖ እንዲጸድቅ አድርጓል፡፡ አባቶቻችን በቤተ ክርስቲያን ላይ ግለሰባዊ አምባገነንነትን አልፈቀዱም፡፡ ጸሎተ ሃይማኖቱም ‹ነአምን በአሐቲ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንተ ላዕለ ኩሉ ጉባኤ ዘሐዋርያት›› በማት ቤተ ክርስቲያን ጉባኤ ዘሐዋርያት መሆንዋን ያመለክታል፡፡ በ50/51 ዓም በኢየሩሳሌም የተሰበሰበችው ሲኖዶስም ‹እኛና መንፈስ ቅዱስ› አለች እንጂ  ‹እኔ› የሚል ግለሰባዊ ድምጽ አልተሰማባትም፡፡
ኢትዮጵያውያን አበው የቅዱስ ሲኖዶስን ሥርዓት ብቻ ሳይሆን ሌሎችን የቤተ ክርስቲያን የአመራር ሥርዓቶች ከግለሰብ አምባገነንነት ለማውጣት መልካም የሆነ ሥርዓት ሠርተዋል፡፡ ቅዳሴው በአምስት ልዑካን እንዲሆን፣ አጥቢያው በሰበካ ጉባኤ እንዲመራ፣ ገዳማት በምርፋቅ (ጉባኤ አበው) ወይም በማኅበር እንዲመሩ፣ ጵጵስናን አንድ ጳጳስ (ፓትርያርክ እንኳን ቢሆን) ብቻውን እንዳይሰጥ፣ ቢያንስ ሦስት አበው ሊኖሩ እንደሚገባ፤ አንድ አባት ብቻውን ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን እንዳይለውጥ፤ አድርገው የሠሩበት አንዱ ምክንያት ግለሰባዊ አምባገነንነትን ለመቋቋም እንዲቻል ነው፡፡
ይህንን ማኅበራዊና ጉባኤያዊ የሆነ የቤተ ክርስቲያን አሠራርና አመራር ለማስወገድ በየዘመናቱ ጥረት ተደርጓል፡፡ የዚህም ምክያቱ ግልጽ ነው፡፡ ግለሰባዊ የሆነ አመራር ለሦስት ነገሮች የተጋለጠ ነውና፡፡ የመጀመሪያው ክህደትንና ኑፋቄን ለማስገባት ይመቻል፡፡ አንዱ ወሳኝ ሌላው ‹ኦሆ በሃሊ› ስለሚሆን እርሱ ትክክል ነው ያለው ትክክል፣ ስሕተት ነው ያለው ደግሞ ስሕተት ይሆናል፡፡ ቤተ ክርስቲያን ጉባኤያዊት በመሆንዋ አንዳንድ ግለሰቦች በየዘመናቱ ያመጡትን ክህደት በጉባኤ ተመልክታ በጉባኤ ለማውገዝ ጠቅሟታል፡፡ ደገኛ ትምርትና ድርሰት ሲገኝ ደግሞ እንዲሁ በጉባኤ ተመልክታ ለመቀበል ረድቷታል፡፡ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ መጽሐፈ ምሥጢርን ጽፎ በጨረሰ ጊዜ ጉባ ሊቃውንቱ ተመልክተው ‹አማንኬ ዮሐንስ አፈወርቅ ወቄርሎስ አፈ በረከት ተንሥኡ በመዋዕሊነ፡፤ ኢትዮጵያ ተመሰለት በቁስጥንጥንያ፤ ወተአረየታ ላዕለ እስክንድርያ – በእውነት ዮሐንስ አፈወርቅና አፈ በረከት የሆነው ቄርሎስ በዘመናችን ተነሥተዋ፡፡ ኢትዮጵያም ቁስጥንጥንያን መስላለች፤ ከእስክንድርያም ልቃ ከፍ ከፍ ብላለች›› ብለው ምስክርነታቸውን ሰጥተው ነበር፡፡

ሁለተኛው ደግሞ ለሌሎች አካላት ቁጥጥር ስለሚመች ነው፡፡ ጌታችን አስቀድሞ ኃይለኛውን ማሠር እንዳለው መሪውን የያዘ ቤተ ክርስቲያኒቱን አን ልቡ ለመዘወር ይመቸዋል፡፡

ይኼ ነገር በዘመነ ሱስንዮስ ጊዜ ታይቷል፡፡ ሮማውያን ግብጻዊውን ጳጳስ በሮማዊ ጳጳስ በመተካት ቤተ ክርስቲያኒቱን በሮማዊ ጳጳስ ለማስመራትና ለመቆጣጠር ፈልገው ነበር፡፡ ነገር ግን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጠባይ ማኅበራዊና ጉባኤያዊ በመሆኑ ጉባኤ ሊቃውንቱ ከግብጹ ጳጳስ ጋር ሆኖ ተቃወማቸው፡፡ ጳጳሱና ሊቃውንቱም እስከ ደም ማፍሰስ ድረስ መሥዋዕት ሆኑ፡፡ ጥቅምት 19 ቀን 1621 ዓም በምዕራብ ጎጃም በምትገኘው ደብረ መዊዕ የተሰበሰቡት የቤተ ክርስቲያን ማኅበርተኞች ለዚህ ማስረጃ ናቸው፡፡ በዚህ የደብረ መዊዕ ጉባኤ እስከ 7000 የሚደርሱ ምእመናን፣ ካህናት፣ መነኮሳትና ሊቃውንት ተሰባስበው ነበር፡፡ የጉባኤው መሪዎችም እነ አባ ተስፋ ኢየሱስ፣ አባ ዘጊዮርጊስ ዘዋሸራ፣ አባ እንጦንዮስ፣ አባ ግርማ ሥሉስ ዘውይት ነበሩ፡፡ የጉባኤው አፈ ጉባኤ ደግሞ አባ ግርማ ሥሉስ ነበሩ፡፡በዚህ ጉባኤ የተገኙት ሁሉ ንጉሡንና አዲሶቹን ሮማውያን የሃይማኖት መሪዎች ተቃውመው እንደ አንድ ልብ መክረው እንደ አንድ ቃል ተናግረው በተዋሕዶ ጸኑ፡፡ የንጉሥ ሱስንዮስም ጦር ጥቅምት 19 ቀን ከብቦ ፈጃቸው፡፡ 
እነዚህ ጽኑአን ጉባኤተኞች ነበሩ በኋላ ዐፄ ሱስንዮስ ሐሳባቸውን እንዲቀይሩና ‹ፋሲል ይንገሥ፣ ሃይማኖት ይመለስ› እንዲሉ ያደረጋቸው፡፡ ቤተ ክርስቲያን እንደ መኪና መሪውን የያዘ መኪናውን ወደ ፈለገው ሊወስደው የሚችልባት ቦታ ብትሆን ኖሮ ዘመነ ሱስንዮስን መሻገር ባልቻለች ነበር፡፡ 
ሦስተኛው ምክንያት ደግሞ ዘመን የፈቀደለት ሁሉ ልቡ የወደደውን በቤተ ክርስቲያን ላይ እንዳይጭን ነው፡፡ በተለያዩ ዘመናት የተነሡ መንግሥታት ለራሳቸው የሚመቻቸው መሪ በቤተ ክርስቲያን ላይ ለማስቀመጥ ሞክረው ነበር፡፡ የቤተ ከርስቲያን አሠራር፣ ሕግና ሥርዓት ግን በአንድ ሰው የሚዘወር ባለመሆኑ ገመዱን ከመበጣጠስ ያለፈ ጀነሬተሩን ማቋረጥ አልተቻላቸውም፡፡ የቤተ ክርስቲያን ውሳኔዎችም በጉባኤ እንጂ በአንድ ሰው ኅሊና ብቻ የሚወሰኑ ባለመሆናቸው አስተዳደራዊ ጥቅም ከማግኘትና በደል ከማድረስ ባለፈ አጥንቷን ለመስበር ዐቅም አላገኙም፡፡ 
ይህንን ታሪካዊና ቤተ ክርስቲያናዊ ሐሳብ ጠንቅቆ በመረዳት የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ቤተ ክርስቲያኒቱን ወደ ግለሰባዊ አምባገነንነት የሚወስደውን  መንገድ በማረም የቤተ ክርስቲያኒቱ ራስ ክርስቶስ፣ የቤተ ክርስቲያኒቱም የበላይ ወሳኝ አካል ቅዱስ ሲኖዶስ መሆኑን በሕገ ቤተ ክርስቲያን አጽንቶታል፡፡ 
የሀገራችን ሰው ሲተርት ‹የማያለቅስ ልጅ በእናቱ ጀርባ ይሞታል› ይላል፡፡ ይራበው አይራበው፣ ይታፈን አይታፈን፣ ይመመው አይመመው፣ ይመቸው አይመቸው አይታወቅምና፡፡ ምናልባትም ዝምታው እንደ ጨዋነት ታስቦለት ዘወር ብሎ የሚያየው ላይኖርም ይችላል፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት በቤተ ክርስቲያን ላይ፣ በቅዱስ ሲኖዶስ ላይና በሊቃነ ጳጳሳት መብት ላይ፣ ቤተ ክርስቲያንን ሊያገለግሉ በተነሡ ማኅበራትና ወጣቶች ላይ፣ በየገጠሩ በተሠማሩና የመከራ ገፈት በሚቀምሱ ካህናትና ምእመናን ላይ የሚደርሰውን በደልና ጫና እየሰሙና እያዩ ዝም ቢሉ በእናታቸው ጀርባ ላይ ሆነው መሞታቸው የማይቀር ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያኒቱን መብት ለማስከበር ደግሞ አስቀድሞ የቅዱስ ሲኖዶሱ መብት መከበር አለበት፡፡ ያልቆመ አንገት ራስን አይሸከምም እንዲሉ፡፡
የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት አንድ ሆነው የቅዱስ ሲኖዶሱን መብት እንዳስጠበቁትና ቤተ ክርስቲያኒቱንም ከግለሰብ አገዛዝ እንደታደጓት ሁሉ በአጠቃላይ የሰበካ ጉባኤውና በቅዱስ ሲኖዶሱ ጉባኤ የቀረቡትን በቤተ ክርስቲያን ላይ እየደረሱ ያሉ ችግሮችን አንድ ሆነው ለመፍታት በቀጣይ  መነሣት አለባቸው፡፡    

Image
“ኤፈርት-መር ካፒታሊዝም” ብዙዎችን እያደኸየ ጥቂት የወያኔ ጎጠኞ ገዢዎችን ግን በሃብት
እያንበሻበሸ በመገስገስ ላይ ነው። ለመሆኑ ኤፈርት ምንድነው? የማነው?
ኤፈርት /በትግርኛው ምህፃር “ትእምት” ወያኔ በረሃ እያለ ባንኮችን፣ የመንግሥት መኪናዎችን እና የግለሰቦችን ንብረት
በመዝረፍ ያቋቋመው ህገ-ወጥ የዘራፊዎች ድርጅት ነው፡፡ ወያኔ የሚኒሊክ ቤተመንግስትን ከተቆጣጠረ ወዲህም
ኤፈርት ራሱን በአስራ ሶስት ግዙፍ ኩባንያዎች አደራጅቶ በሁሉም አቅጣጫ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ በመቦጥቦጥ የወያኔ
ሹማምንትን ኪስ እንዲያደልብ አደራ የተጣለበት ተቋም ነው።
በዚህም መሠረት መሶበ የኮንስትራክሽን ግብዓት ማምረቻ፣ መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጂነሪንግ፣ አዲስ የመድሃኒት
ማምረቻ፣ ኢዛና የማዕድን ልማት፣ ጉና የንግድ ድርጅት፣ ሕይወት የግብርና ሜካናይዜሽን፣ ሳባ እብነ በረድ ማምረቻ፣
ሼባ የቆርቆሮ ፋብሪካ፣ ሱር ኮንስትራክሽን፣ አልሜዳ የጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ፣ ኤክስፕረስ የትራንዚት አገልግሎት፣
ኢትዮጵያን እንወቅ አስጎብኚ ድርጅት እና ትራንስ ኢትዮጵያ የጭነት ማመላለሻ አገልግሎት የተሰኙ ግዛዙፍ
ኩባንያዎችን አቋቁሞ እንደ ተባይ ድሆች ኢትዮጵያንን የሚመጥ “ካፒታሊዝም” ኢትዮጵያ ውስጥ ለማንሰራፋት
ተንቀሳቀሰ። ከጥቂት ዓመታት ሥራ በኋላ የቁጥጥር አድማሱን በማስፋት ብሩህ ተስፋ ፕላስቲክ ፋብሪካ፣ ማይጨው
ፓርቲክል ቦርድ ፋብሪካ፣ ዲማ የማር ማጣሪያ፣ አላጌ ደንና የደን ውጤቶች፣ ናሽናል ጂኦ-ቴክስታይል እና አበርደሌ
የእንስሳት ማድለቢያና ኢክስፖርት ድርጅት የተባሉ ስድስት ኩባንያዎች የያዘው ደጀና ኢንዳውመንት ተጨመረለት።
ይህ በአደባባይ የሚታወቀው ኤፈርት ነው። የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ በቅርበት የሚከታተሉ እንደሚያውቁት ሁሉ ኤፈርት
በኮንትሮባንድ ንግድ ጭምር የገባ “ወንበዴ ድርጅት” ነው። ኤፈርት ያሻውን ያህል ተበድሮ ያለመክፈል ልዩ ፈቃድ
ያለው ቅምጥል ድርጅት ነው፡፡ እስካሁን ከሶስት ቢሊዮን በላይ የባንክ እዳ እንደተሰረዘለት ይወራል፡፡ የህወሓት
ማዕከላዊ ኮሚቴ በተሰበሰ ቁጥር ከማይቀሩ አጀንዳች አንዱ ትዕምት (ኤፈርት) ነው። ለኤፈርት የቦርድ አባላትንም ሥራ
አስኪያጆችንም የሚሾምለት ህወሓት ነው። የአገሪቱ የፓርቲዎች ህግ ፓርቲዎች እንዳይነግዱ ይከለክላል። ህጉ ሕወሓት
ላይ አይሠራም። እርግጥ ኤፈርት ዘራፊ እንጂ ነጋዴ ስላልሆነ አዋጁ አይመለከተውም።
የኤፈርት ኢትዮጵያን የመዝረፍ ሕልም ትልቅ ነው። “በግል” ባንኮችም የአንበሳ ድርሻ አክሲዮን በመያዝ የፋይናንስ
ሴክተሩን ሊቆጣጠረው ደርሷል። በአገሪቱ ያሉ ያሉ ዋና ዋና የቢዝነስ ኮንትራቶችን የሚወስደው ኤፈርት ነው። ለሕዳሴ
ግድብ ግንባታም ዋና እቃ አቅራቢ ነው። የአገሪቱን 40 በመቶ የፒቪሲ (ፕላስቲክ ነክ ምርቶች) ገበያ ለመቆጣጠር
የሚያስችለውን ማምረቻ እየገነባ ነው። ኤፈርት የድሀውን ገንዘብ እየሰበሰ ለወያኔ ጄኔራሎችና ሹማምንት የሚያድል
አገርን ለማጥፋት የተቋቋመ ተቋም ነው። “የሙስና መርከብ” የኤፈርት የቤት ስሙ የሆነው ያለምክንያት አይደለም።

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም – በነጻነት ለሀገሬ)

 

.. 1984 የተከሰተው የኢትዮጵያ ታላቁ ረኃብ ሲታወስ (ክፍል 2)

ባለፈው ሳምንት ባቀረብኩት ትችቴ (እ.ኤ.አ በ1984 የተከሰተው የኢትዮጵያ ታላቁ ረኃብ ሲታወስ፡ ክፍል1)፣ ላለፉት በርካታ ዓመታት ረኃብን በማስመልከት ሳቀርባቸው በነበሩት ትችቶች የህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ እና አሁን በህይወት የሌለው መሪው መለስ ዜናዊ እ.ኤ.አ ከ1991 ጀምሮ በኢትዮጵያ ውስጥ ምንም ዓይነት ረኃብ የለም በማለት ሙልጭ አድርገው በመካድ ሲያደርጉት የነበረውን ተራ ቅጥፈት በማጋለጥ በተጨባጭ መረጃዎች ላይ በመመስረት ስሞግት የቆየሁባቸውን ዋና ዋና ጭብጦች በማካተት ክለሳ ማድረጌ ይታወሳል፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

‹‹ኢህአዴግ በጭቆና ውስጥ ጸጥ ብሎ የተቀመጠን ሕዝብ እየቆሰቆሰ ነው››

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ ከቃሊቲ እስር ቤት

(በኤሊያስ ገብሩ – ጋዜጠኛ)
ትናንት፣ በዕለተ ዓርብ እኔ እና የዕንቁ መጽሄት ማኔጂንግ ዳይሬክተር ከሆነው ፍቃዱ ማህተመወርቅ (ባሪያው) ጋር ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋንና ፖለቲከኛን አቶ አንዷለም አራጌን በቃሊቲ ተገኝተን ጠይቀናቸው ነበር፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

ከ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር የተላለፈ አገራዊ የጸሎት ጥሪ

በኢትዮጵያ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች ትብብር

አገራችን የክርስትናና እስልምና ኃይማኖቶችን በመቀበል ቀደምት በመሆኗ ብቻ ሳይሆን የኃይማኖቶቹ ተቋማት፣አባቶችና ምዕመናን በመከባበርና መቻቻል አብረው በሠላም በመኖር ለዓለም ህዝብ ተምሳሌት መሆናችን የምንኮራበት ነው፡፡ ለዚህም የቤተ እምነቶቹ አባቶች ለምዕመናኑ ያስተማሩት የሞራልና ሥነ-ምግባር እሴቶችና በአብሮነት ላይ የቆመ የአገር ፍቅር ስሜት፣ እነዚህንም እንዲጠብቋቸውና እንዲያከብሯቸው አርዓያ በመሆን ያደረጉት አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው፡፡

አገራችንና ህዝቧ በተፈጥሮ ሚዛን መዛባት በሚከሰትም ሆነ በአገዛዝ ሥርዓቶች ምክንያት በችግር ውስጥ በሚወድቁበት ጊዜ ሁሉ የእነዚህ ኃይማኖቶች ተቋማትና ምዕመናን መዓቱ እንዲርቅና ምህረቱ እንዲወርድ ፈጣሪያቸውን በጾምና በጸሎት በመለመን/ በመማጸን፣ በሃይማኖታዊ የሞራልና ሥነ ምግባር እሴቶቻቸው መሠረት በመተዛዘን ፣ በመረዳዳትና በመተጋገዝ የተገኘውን በመካፈል በአብሮነት ስሜት በርካታ ክፉ ጊዜያትን መሻገራቸው በታሪክ ተመዝግቦ ይገኛል፡፡

ዛሬ ላይ እነዚህ የሞራልና ሥነ-ምግባር እሴቶች እየተናዱ በመሄዳቸው ዜጎች ለማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ምስቅልቅል ተጋልጠዋል፣ የአገር ፍቅር ስሜት በጥያቄ ውስጥ ወድቋል፡፡ በዚህም በመቻቻል ፋንታ ግጭትና መፈናቀል በአራቱም አቅጣጫ ህዝብን ለሥቃይና ሥጋት ዳርጓል፣ የህግ ‹‹አምላክ›› ክብር እያጣ ፍትህ እየተዛባ ነው፣ ወህኒ ቤቶች በታሳሪዎች ተጨናንቀዋል፣ የምግብ ተረጂውና የጎዳና ላይ ተዳዳሪው ዜጋ ቁጥር ተበራክቷል፣… በአጠቃላይ የህዝባችን ኑሮና ህይወት፣ የአገራችን ሠላምና መረጋጋት ፈታኝና አሳሳቢ ደረጃ ላይ ናቸው፤ የዜጎች ተስፋ በመናመኑ የህይወት ዋጋ በሚጠይቅ ሁኔታ ውስጥ እየተሰደዱ በባዕድ አገር ለአደጋ እየተጋለጡ ነው፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ በአገራችን ያሉ የተፎካካሪ ፓርቲዎች/ገዢው ፓርቲና ተቃዋሚዎች/ ተጨባጩን ሁኔታ የሚመለከቱበትና የሚረዱበት መንገድ በሁለት ጫፍ ላይ በመወጠሩ የጋራ መፍትሄ ለማምጣት ያለው ዕድል በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ በመሆኑ ችግሮቹን እያባባሰ ይገኛል፡፡ ስለዚህ፡-
በአገራችን ውስጥ በተለያየ ምክንያት በሁለት ጠርዝ ላይ የቆሙ ኃይሎች ወደ ብሄራዊ መግባባትና ዕርቅ እንዲመጡ፣ በህዝብ ውስጥ የሚታየው የሞራልና ሥነምግባር ጉድለት እንዲቃናና የመቻቻልና መተሳሰብ ስሜት እንዲያንሰራራ፣ የዜጎች ሥቃይና ሥጋት ተወግዶ በተስፋ እንዲሞላ፣….፤

በአገራችን መረጋጋትና ዘላቂ ሠላም እንዲሰፍን፣ ቀጣይና ዘላቂ ልማት እውን እንዲሆን፣ አብሮነታችንና አንድነታችን እንዲጠናከር፣ የአገር ፍቅር ስሜት እንዲለመልምና ለሉዓላዊነታችን ያለን ቀናዒነት እንዲጠናከር፣….፤

በሰንበትና የጁምኣ ቀናት በጋራ እንዲሁም በየግል የዘወትር ጸሎት ፈጣሪ አምላክን በመለመን ለተያያዝነው አገራዊ ዓላማና የጋራ ጥረት ድጋፋችሁን እንድታደርጉ ለየቤተ እምነት ኃላፊዎች /ቤተ ክርስቲያናትና መስጂዶች/ እና ለምዕመናን በሙሉ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

ፈጣሪ አምላክ አገራችንንና ህዝቧን ከጥፋት ይታደግ ዘንድ በጸሎት እንትጋ!!

ኅዳር 01 ቀን በ2007 ዓ.ም፣ አዲስ አበባ

አቶ ማሙሸት አማረ :- አዲሱ የመኢአድ ፕሬዝዳንት ተስፋና ተግዳሮት ከዚህ ጉዳይ ጋር የተያያዘዉን መኢአድን የተመለከተ የአቶ ሸንቁጥ አየለን ጽሁፍ ያንብቡት :: ======================================= – “መኢአድን ለማዳን እንረባረብ::” የጠቅላላ ጉባዬ አባላቱ – ከድርጅቱ የተባረሩ የወያኔ ቅጥረኞች በእርቅ ስም ወደ ድርጅቱ ተመልሰዋል::(አባላት) – ጠቅላላ ጉባዬው የተካሄደው ፍጹም አምባገነንነት በሞላበት ሁኔታ ነው:: በኢትዮጵያ በአንጋፈነቱ የሚታወቀው እና በፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ […]

የኢትዮጵያ አትሌቶች በተለያዩ አለምአቀፍ የማራቶን ሩጫ ውድድሮች ድል ተቀዳጅተዋል። ፍቃዱ ግርማና ሙሉሀብት ጸጋ በቤይሩት፥ ሹሜ ሀይሉ በፈረንሳይ አሸንፈዋል። ጊዜአቸውም የፍቃዱ 2 – 12 – 26 እና 2- 29 – 15 ተመዝግቧል። በፈረንሳዩ የአልፕስ ማራቶን ደግሞ የወንዶቹን ሹሜ ሃይሉ በአንደኝነት አጠናቋል።

በሕገ ወጥ መንገድ የቴሌኮምዩኒኬሽን መሳሪዎችን በማስገባት የተጠረጠሩ ሰዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተዘገበ። ከተጠርጣሪዎቹ መካከል የውጭ አገር ዜጎች እንደሚገኙባቸው ተገልጿል።

ድርጊቱ አገሪቱን በብዙ ሚሊዮን ዶላር እንዳሳጣትም ዘገባዎቹ አመልክተዋል።

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

ጥቅምት ፴(ሠላሳ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ››በሚል መርህ ትብብር  የመሰረቱት 9 ተቃዋሚ ፓርቲዎች ቀደም ብለው ባሳወቁት የአንድ ወር መርሃ ግብር መሰረት የጀመሪያውን ጥሪ ለሃይማኖት ተቋማት አድርገዋል። ፓርቲዎቹ አገራችንና ህዝቧ በተፈጥሮ ሚዛን መዛባት በሚከሰትበትም ጊዜ ሆነ በአገዛዝ ሥርዓቶች ምክንያት በችግር ውስጥ በሚወድቁበት ጊዜ የኃይማኖት  ተቋማትና ምዕመናን ሚና ከፍተኛ እንደነበር አውስተው፣ ዛሬ ላይ እነዚህ …

ጥቅምት ፴(ሠላሳ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-‹በተለይ ባሳለፍነው አንድ ሳምንት ጊዜያት ውስጥ መቆራረጡ በወሳኝ ሰዓታት ጭምር ማለትም በምሽት እና በጠዋቱ ጊዜያት ተጠናክሮ መቀጠሉን የገለጹት ነዋሪዎች በዚህ ምክንያት ለከፍተኛ ኪሳራና ወጪ እየተዳረጉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ባለስልጣናት «የኃይል እጥረት የለም፣ እንዲያውም ተርፎን ለጎረቤት ሀገራት ኤክስፖርት እያደረግን ነው» በሚሉበት በዚህ ወቅት በተለይ የአፍሪካ ርዕሰ መዲና መሆንዋ በሚነገርላት አዲስአበባ …

ጥቅምት ፴(ሠላሳ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-‹በአማራ ክልል በተለያዩ ከተሞች የሚገኙ ነዋሪዎች ለኢሳት እንደገለጹት ከገቢያቸው ጋር በማይመጣጠን የግብር  እዳ እየተሰቃዩ  ነው። የገዢው ፓርቲ ባለስልጣኖች አድሎአዊ በሆነ መልኩ በሚጥሉት ግብር ነጋዴዎች ድርጅታቸውን እየዘጉ ነው። በእነብሴ ሳር ምድር   ወረዳ አሰፋ ሁነኛው፣ ኢሳየ ቸኮል፣ የንጉስ ዋለና  መሰሉ የሚባሉት ነጋዲዎች በጋራ ለቤት መስሪያ በባንክ ከስያዙት  ገንዘብ ላይ ያለፍላጎተቻው …

ጥቅምት ፴(ሠላሳ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ለደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫኪር ታማኝ የሆኑ የደህንነቶች ሰራተኞች ለኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የጦር መሳሪያ እና ሌሎች እቃዎችን ጭነው ሲጓዙ የነበሩ 4 መኪኖችን አስቁመዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቃል አቀባይ ስቴቨን ዱጃሪክ እንደገለጹት የደህንነት ሰራተኞች መሳሪያዎቹ ለአንድ ተቃዋሚ ሃይል ሊሰጥ ነው በሚል እንደያዙትና በሹፌሮቹ ላይ ጉዳት እንዳደረሱባቸው ገልጸዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት …

– “መኢአድን ለማዳን እንረባረብ::” የጠቅላላ ጉባዬ አባላቱ
– ከድርጅቱ የተባረሩ የወያኔ ቅጥረኞች በእርቅ ስም ወደ ድርጅቱ ተመልሰዋል::(አባላት)
– ጠቅላላ ጉባዬው የተካሄደው ፍጹም አምባገነንነት በሞላበት ሁኔታ ነው::

Minilik Salsawi

በኢትዮጵያ በአንጋፈነቱ የሚታወቀው እና በፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ የተመሰረተው መአሕድን የተካው በኢንጂነር ሃይሉ ሻውል ሲመራ ቆይቶ አቶ አበባው መሃሪ የተረከቡት የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ፓርቲ (መኢአድ)ከባድ የመፈረካከስ አደጋ ከፊቱ ተደቅኗል ሲሉ የድርጅቱ ምንጮች ለምንሊክ ሳልሳዊ በላኩት መረጃ ገልጸዋል::

መኢአድ ከአንድነት ፓርቲ ጋር የሚያደርገውን ውህደት ተከትሎ ገዢው ፓርቲ ከድርጅቱ የተባረሩትን እነ አቶ ማሙሸት እና ኮሎኔል ታምሩን አደራጅቶ ውህደቱን በመበጥበጥ በመኢአድ ቢሮ ውስጥ ከዚህ ቀደም በተደረገ ስብሰባ ላይ ደህንነቶችን እና ፖሊሶችን አስከትሎ በመምጣት ከፍተኛ የሆነ ብጥብጥ አንስተው የነበረ ቢሆንም ሳይሳካላቸው ቀርቷል::

ውህደቱ የጉሮሮ ላይ አጥንት የሆነበት የወያኔው መንግስት ምርጫ ቦርድን ተገን በማድረግ መኢአድን በማጉላላት ውህደቱ እንዳይፈጸም ከፍተኛ ደባ ከቅጥረኞቹ ከነማሙሸት ጋር በመሆን ሲፈጽም ቆይቶ በስተመጨረሻ ኢንጂነር ሃይሉን በማስገደድ የተባረሩ አባላትን አቶ አበባው መልሶ እንዲያስገባ ካላስገባ ስልጣኑን እንዲለቅ በሚል ጫና የበላይ ጠባቂነታቸውን ተገን በማድረግ የወያኔ ስራ አስፈጻሚዎች ወደ ድርጅቱ ሰርገው በመግባት ድርጅቱ አደጋ ውስጥ መሆኑን የድርጅቱ አባላት በምሬት ተናግረዋል::

ኢንጂነር ሃይሉ ሻውል ከዚህ ቀደም ከወያኔ ጋር ከድርጅቱ እውቅና ውጪ በራሳቸው ፍቃድ ከሟቹ መለስ ዜናዊ ጋር የምርጫ ደንብ የሚል ስምምነት ተፈራርመው ድርጅቱ እንዲዳከም እና ለወያኔዎች በሩን እንዲከፍት ያደረጉ ሰው ቢሆንም ቀደም ብለው ለትግሉ የከፈሉት አስታውጾ ታይቶ የድርጅቱ የበላይ ጠባቂ እና አማካሪ ቢደረጉም በድርጅቱ ማህተም የተባረሩ ቅጥረኞች ወደ ድርጅቱ እንዲመለሱ አድርገዋል ሲሉ አባሎቹ ተናግረዋል::ኢ/ር ሀይሉ ሻውል በፍጹም አምባገነንነት ጉባኤተኛውን አፍነው እርሳቸው በሚፈልጉት መልኩ በእርቅ ጭምብል አንዱን አስወጥተው አንዱን አስገቡ፡፡ ሲሉ የጠቅላላ ጉባዬ አባላቱ ተናግረዋል::

ከዚህ ጉዳይ ጋር የተያያዘዉን መኢአድን የተመለከተ የአቶ ሸንቁጥ አየለን ጽሁፍ ያንብቡት ::
viewtopic.php?f=2&t=89291

ጎርቫቾቭን ታቸር ከለንደን ሬገን ከዋሽግተን እየተቀባበሉ ሲያንቆለጳጵሷቸዉ፤ መራሔ መንግሥት ሔልሙት ኮል የቀዳሚዎቻቸዉንም፤ የራሳቸዉንም የሕዝባቸዉንም ሕልም ምኞት እዉን ለማድረግ ሞስኮዎችን እንደ ጥሩ ወዳጅ ቀረቧቸዉ።አግባባቡ አባበሉ።

ኢትዮጵያ በሰብዓዊ መብቶች ላይ የምትፈጽመውን ጥሰት ካላቆመች የአፍሪካ ህብረት መቀመጫውን ከአዲስ አበባ መቀየር አለበት ተባለ። በደቡብ አፍሪካ ዊትስ ዩኒቨርሲቲ በተካሄደ የአፍሪካ የምርመራ ጋዜጠኝነት ጉባኤ ላይ አንጎላዊው ጋዜጠኛ ራፋኤል ማርኩዌዝ ደ ሞራይዝ የኢትዮጵያ መንግስት ያሰራቸውን ጋዜጠኞች መፍታት አለበት ብሏል።

የአፍሪቃ ዋንጫ ማጣሪያ፣ እንዲሁም፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለዚሁ ማጣሪያ ውድድር የጀመረው ዝግጅት፣ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ያደረጉበት የቤሩት፣ ሊባኖስ እና የኒስ፣ ፈረንሳይ አትሌቲክስ ውድድር፣ የሳምንቱ

የአቶ ሸንቁጥ አየለን ጽሁፍ ያንብቡት ::
መግቢያ –
——-
“የቱ ይቀድማል?:- በዲክራሲያዊ መርህ ላይ የቆመ ሀገር ወይስ ዲሞክራሲን ሊሸከም የሚችል ባህል ላይ የቆመ ማህበረሰብ ?” በሚለዉ ጽሁፌ የፖለቲካ ፓርቲዎቻችን የዉይይትና የክርክር ባህል አለመዳበርን በማስመልከት የተወሰኑ ፓርቲዎችን እያነሳሁ ወቅሼአቸዉ ነበር:: ፓርቲዎች ዉስጥ በግለሰብ ወይም በቡድን ደረጃ የሀሳብ ክፍፍል ሲነሳ ፓርቲዎች በሀሳብ የመሸናነፍ ባህል እንዳላዳበሩ ምሳሌ አድርጌ ካቀረብኩት ፓርቲ አንዱ የመላዉ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ነበር:: እንዲህም ስል ፓርቲዉን በሀሳብ ሸንቆጥ አድርጌዉ ነበር:-

“መኢአድ ዉስጥ ችግር ከተፈጠረ አራት አመታት አለፉ:: በርካታ የእርቅ ጥረቶች እንደተደረጉ የኢትዮጵያ ሰዉ አስተዉሏል :: በልዬ ልዩ ሚዲያዎችም ላይ ተደምጧል:: ሆኖም በሃሳብ የተለያዩት ሰዎች አንድም ቀን ቁጭ ብለዉ ተደማምጠዉ በሀሳብ ተፋጭተዉ እና ልዩነታቸዉን አቻችለዉ መፍትሄ ላይ ሲደርሱ አልታዬም:: አንዱ ሌላዉን ይወነጅላል:: አንዱ አንዱን ሰርጎ ገብ ነዉ : ባንዳ ነዉ ሲል ስሙን ያጠፋል:: ደግሞ አንዱ እሱ ብቸኛ የድርጅቱ ተጠሪ ይሆንና ሌላዉን ለማግለል ዳዉላ ሙሉ ከዚያም ዘሎ ከቶንም ስፍር የበለጠ ሀሰትና ዉሸት ይደረድራል:: እናም መደማመጥና መነጋገር ብሎም በሀሳብ መፋጨትና ወደ መቻቻል መድረስ ቦታም አላገኙም:: አስቂኙ ነገር ታዲያ መኢአድ ዉስጥ ተከፋፍለዉ ያሉ ብድኖች ሳያፍሩ ስለ ብሄራዊ እርቅ ጉዳይ ሲናገሩ መስማት የተለመደ ነገር መሆኑ ነዉ:: እራሱን ከራሱ ጋር በሀሳብ ተከራክሮና ተወያይቶ ለማስታረቅ ያልቻለ ቡድን ስለብሄራዊ እርቅ ሲያወራ መስማት እጅግ አስቂኝ ነገር ነዉ::”

ይሄን ወቀሳ ያወረድኩበት በመኢአድ ላይ ብቻ አይደለም ነበር:: ሌሎችም የሀገራችን የፖለቲካ ፓርቲዎችንም አጣቅሸ ነበር:: ሆኖም ዛሬ ትኩረቴን መኢአድ ላይ አድርጌአለሁ:: ምክንያቱም ዛሬ መኢአድ ማንም ኢትዮጵያዊ ያላሰበዉን እና ያልጠበቀዉ የዲሞክራሲ ማማ ላይ ተፈንጥሮ ወጥቶ ተገኝቷልና::

ለራሱ ሀሳብና ህሊና ብቻ ተገዥ የሆነዉ ደፋሩ : እዉቁና ወጣቱ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ባንድ ወቅት የመኢአድ ሰዎች እርስ በርስ ንክሻ እና አለመግባባት ብቻ ሳይሆን በፕሮፌሰር አስራት የሙት አመት ላይ እንኳን ሲጣሉ ቢያስተዉል ” ዛሬ የፕሮፌሰር አስራት ሙት አመት ብቻ ሳይሆን የመኢአድም ሙት አመት ነዉ” ሲል መጻፉን አስታዉሳለሁ::

እኔም ሆንኩ ተመስገን ደሳለኝ በመኢአድ ላይ ትችቶችን ያወረድንበት ወደን ሳይሆን በሚጠበቅበት ስፍርና ቁመት ልክ ሆኖ አልገኝ ስላለን ነበር:: መኢአድ ከ2003 ዓም እስከ አሁኑ ጥቅምት 30/ 2007 ዓም ድረስ ለአራት አመታታ ያሳለፈዉ ዉጣ ዉረድ እና አባላቱም በአምስት ቡድን ተከፋፍለዉ ያደረጉት ሽኩቻ ጉድ የሚያስብል ብቻ ሳይሆን ወይ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የሚያሰኝ ነበር:: አንድ ፓርቲ አምስት ቡድን ተከፋፍሎ መልሶ ሊድን የሚችለዉ እንዴት ነዉ?

የመላዉ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ወደ ዲሞክራሲ የከፍታ ጉዞ ?
========================================

ለአራት አመታት በአምስት ቡድኖች ተከፋፍለዉ የማያቋርጥ አሉባልታ: ስድብ ወቀሳና ክስ ላይ ተጠምደዉ የነበሩ ሀይሎችን ወደ አንድ ማምጣትና በዉይይት ችግራቸዉን ፈትተዉ እርቅ ወርዶ አንድ የፖለቲካ ሀይል ሆነዉ እንዲቀጥሉ ማድረግ ይቻላል? ለአራት አመታት ያስተዋልነዉ ነገር አይቻልም የሚል ፍጹም አስተማማኝ ድምዳሜ ላይ መድረስ ነበር:: ለዚህም ነዉ ከንግዲህ የመኢአድ ነገር አከተመለት የተባለዉ ነበር::

የሆኖ ሆኖ በጠንካራ ሽማግሌዎች እረዳትነት እያንዳንዱን አምስት የተለያዬ ቡድን በማነጋገር : በተለያዬ ወቅት አመራር በመሆን የተመረጡትን ሀይሎች ሁሉ በማካተት እንዲሁም አንድንም ወገንን ያላገለለ : ከገጠር እስከ ከተማ ያለዉን አመራር በማካተት ጠቅላላ ጉባኤ በማድረግ አስገራሚ ዉጤት ላይ የደረሰ ፓርቲ ሆኖ ወጥቷል:: ዉጤቱን አስገራሚ ያደረገዉም የጠቅላላ ጉባዔዉ ሂደት እጅግ ጠንካራ: በበርካታ ሙግቶች : ክርክሮች : ፊት ለፊት በሚነሱ የተፋጠጥ አካሄዶች እዲሁም አንድም እዉነት ሳይቀር እዚችዉ እህዝብ ፊት ትፋት የሚል አካሄድ የታጀበ መሆኑ ነበር::

እያንዳንዱ ቅሬታ አለኝ የሚል ቡድን ከስድስት መቶ ተሰብሳቢ በላይ ባለበት እዉነት ስትሞግተዉ ወይ ያቀረቅራል ወይም እዉነትን ተርትሮ ለተሰብሳቢዉ ያስረዳል;: ተሰብሳቢዉ ያደምጣል: አፋጣጭ ጥያቄን ይጠይቃል ብሎም ደግሞ ብይንን ይበይናል:: መሸወድ አይቻልም:: ብዙሃን እዉነትን እሰዉ ፊት ላይ ያነባታል: ብዙሃን እዉነትን ከሰዉ ኪስ ዉስጥ በርብሮ ያወጣታል:: አሉባልታ ተናግሮ ማምለጥ አይቻልም:: ፊት ለፊት ላሉባልታዉ መልስ የሚሰጥ ወገን አለና:: ከሁሉም በላይ ደግሞ አይኑን እና ጆሮዉን አንቅቶ የሚያስተዉል ከስድስት መቶ በላይ ህዝብ አለና:: የትም መደበቅ አይቻልም:: የዲሞክራሲ ዉበቱ ህዝብ ፊት እራቁትን ስለሚያስቆም ነዉ::

እናም እያንዳንዱ ቡድን ከጥቅምት 28 እስከ ጥቅምት 30/2007 ዓም በተደረገዉ እልህ አስጨራሽ ግን ደግሞ የዲሞክራሲ የከፍታ ማማ ላይ የረገጠ ሊባል በሚችል የጠቅላላ ጉባዔ ሂደት ዉስጥ ያለዉ አማራጭ ወደ አንድ መምጣትና በጋራ ለዲሞክራሲ መታገል መሆኑን በደንብ የተማረበት: እያንዳንዱንም ለሌላው ወገን ያስተማረበት ወቅት ሆኖ አልፏል:: ለሶስት ቀናት በዘለቀዉ የስብሰባ ሂደት ዉስጥ እስከ ለሊቱ ስድስት ሰዓት ድረስ በማምሸት የተደረገዉ የዲሞክራሲ ከፍታ ላይ የደረሰ የሀሳብ ፍጭት: ክርክር: እና ዉይይት እጅግ ገንቢና ለወደፊት የኢትዮጵያ ፖለቲከኞች ጥሩ ልምድ ጥሎ ያለፈ አስተምህሮት ይመስላል:: እዚህች ጋ በተለያዩ ፓርቲዎች ስር የታቀፉ ፖለቲከኞቻችን ፈገግ ሲሉ ይታዩኛል:: እኛማ የዲሞክራሲዋን ቁልፍ ጨብጠናታል ሲሉ ፈገግ ማለታቸዉ አንዱ የዲሞክራሲ ድቀት መገለጫ መሆኑን እናጣቅስና እንለፈዉ::

ሀይሉ ሻዉል ከ28-30/3007 ዓም ባሉት መጨረሻ የፖለቲካ ቀኖቻቸዉ ዉስጥ የሰጡት አመራርም ብዙዎቹን አስገርሟል:: “ከንግዲህ እኔ ከማንም ጋር ጸብ የለኝም:: እያንዳንዳችሁም እርስ በርሳችሁ መታረቅና በመሃከላችሁ ያለዉን ጸብ ንዳችሁ አብራችሁ መስራት አለባችሁ::” ይሄን አቋማቸዉን የተፈታተኑ አንዳንድ ወገኖች ቢኖሩም የብዙሃኑም ተሰብሳቢ ዋና ምርጫ ዲሞክራሲያዊ ሂደትን ማዬት እንጅ ብጥብጥ ስላልነበረ ነገሮች ሁሉ በሰላማዊ መንገድ መጠናቀቅ ችለዋል:: በዉነቱ ሂደቱ እጅግ አስጨናቂ እንደነበረ ከ20 በላይ ተሰብሳቢዎችን አንድ ባንድ ቃለ መጠይቅ በማድረግ ተረድቻለሁ:: ብዙዎች እንዳሉትም በመጀመሪያ አካባቢ ሂደቱ ከመክበዱ የተነሳ አንድ አጀንዳ ላይ አንድ ቀን የመዋል አካሄድ እንደነበርም አብራርተዉልኛል::

አቶ ማሙሸት አማረ :- አዲሱ የመኢአድ ፕሬዝዳንት ተስፋና ተግዳሮት
=================================================
ማሙሸት አማረ የመኢአድ አዲስ ፕሬዝዳንት ሆኖ በከፍተኛ ድምጽ ተመርጧል:: ማሙሸት አማረ ገና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲት የአንደኛ አመት ተማሪ ሆኖ ዩኒቨርስቲ እንደ ገባ ወገን ሀገርህ አይደለም ተብሎ ካባቶቹ ሀገር ሲባረርና ገደል ሲገፈተር የምን ትምህርት ነዉ ሲል ከፕሮፈሴር አስራት ጋር የፖለቲካ የትግል አዉድማ በወጣት እድሜዉ የተቀላቀለ ሰዉ ነዉ:: አቶ ማሙሸት በፖለቲካ ሂወት ዉስጥ እየተመላለሰም በርካታ የትምህርት ዘርፎችን በማጥናት እራሱን ለአመራር ብቁ ያደረገ ሰዉ ነዉ :: በማርኬቲን ዲፕሎማ: በሊደርሽፕ/አመራር/ ዲፕሎማ እንዲሁም በማኔጅመንት ዲግሪዉን አጠናቋል:: በአሁኑ ሰዓት ደግሞ በፖለቲካ ሳይንስ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ትምህርቱን የቀጠለ ብርቱ የሰላማዊ ትግል መሪ ነዉ::

ለአስራ ሁለት አመታት የታሰረ ሰዉ ቢሆንም በኢትዮጵያ ፖለቲካ የማይማረር : በዲሞክራሲ ሂደት የሚያምን እና የሚያምንበትን ሀሳብ ፊት ለፊት የሚያራምድ ፖለቲከኛ ነዉ:: በቅርበት የሚያቁትም እንደሚገልጹት ለሚያምንበት ነገር ብቻ የሚኖር ሰዉ ሲሉ ይገልጹታል::

ማሙሸት በሀሳብ ልዩነት ያምናል:: በክርክር ያምናል:: ሰዉ አክባሪ እንደሆነ የሚነገርለት ማሙሸት ተናግሮ የማሳመን አቅሙን አብረዉት የሰሩ ሁሉ ይመሰክሩለታል:: ከ28-30/2007 ዓም በተደረገዉ ጠቅላላ ጉባዔ ላይም ይሄንኑ ተናግሮ የማሳመን ችሎታዉን እንዳስመሰከረ ብዙዎች ተስማምተዉለታል:: ሆኖም ማሙሸት አንድ ነገር አይሆንለትም:: ይሄዉም እዉሸትና መስሎ ማደር:: ይሄ ነገር ለፖለቲካ ሂወቱ ዋናዉ ተግዳሮትም አዎንታዊ ገጽታም ሆኖ ከፊቱ የተደነቀረ ይመስላል::

ለአራት አመታት ከማሙሸት አማረ ጋር በሀሳብ ተለያይተዉ የከረሙትና በማሙሸት ላይ ክፉኛ ቂም ይዘዉ የነበሩት ኢ/ር ሀይሉ ሻዉል ከማሙሸት ጋር ሲታረቁ ማሙሸት ለአቶ ሀይሉ በሽማግሌዎች ፊት ያቀረበላቸዉ አንዱ ጥያቄ “ለመሆኑ እኔ እርስዎን ሰድቤዎታለሁ?” የሚል ጥያቄ ነበር:: ሀይሉም ” እረ በፍጹም” ሲሉ መለሱ:: ማሙሸትም በማስከተል ” ታዲያ ሚዲያዉ ሁሉ ማሙሸት አማረ አቶ ሀይሉን ሰደባቸዉ እያለ ሲያናፍስ እርስዎ ዝምታን የመረጡት ለምን ነበር?” ሲል ጠየቀ:: ሀይሉም መለሱ “እኔ ለያንዳንዱ ሚዲያ ያሉባልታ ወሬ ምላሽ ልሰጥ የምችልበት እድሜ ላይ አይደለሁም” ሲሉ መለሱ::

“እኔና አንተ የተጣላንዉ አንተ ለእኔ አልታዘዝም ስላልክ ብቻ ነዉ” ሲሉ አስከትለዉ ሀይሉ ተናገሩ:: ማሙሸትም ለአቶ ሀይሉ ሲመልስ ” እኔ ለእርስዎም ሆነ ለማንም ህገወጥ በሆነ መንገድ የምታዘዝ ሰዉ አይደለሁም:: ከእርስዎም የተጣላንዉ እርስዎ የድርጅቱን ህገ ደንብ ጥሰዉ ያለስልጣንዎት የማይገቡ ዉሳኔዎችን ስለወሰኑ ነዉ::አሁንም ሆነ ወደፊት የድርጅትን ህገ ደንብ የሚጥስ መሪ አምባገነን መሪ ነዉ:: የተጣላንዉም እርስዎ ህግ ስለጣሱ ነዉ:: አሁን ያለዉን አምባ ገነን ስርዓት እየታገልን በተቃዋሚ ፓርቲዎች ዉስጥ ደግሞ የፓርቲ አምባ ገነንነትን አናበረታታም:: ማንኛዉንም አይነት አንባገነንነትን እንታገለዋለን እንጅ:: ” ሲል ቁርጥ ያለ መልስ መለሰ::

ማሙሸት በማስከተል እንዲህ አለ “አባቴ ገና ዩኒቨርስቲ አንደኛ አመት ተማሪ እያለሁ ጠርቶ “ወገን እያለቀ ዝም የምትሉት ምንድን ነዉ? ከፕሮፌሰር አስራት ጋር ተነስታችሁ ታገሉ:: ለእዉነት ሙት” ሲል ለእዉነት ብቻ እንድኖር መመሪያ ሰጥቶኛል:: እዉነትን ማንም ከጣሳት ከዚያ ሀይል ጋር በሀሳብ ሙግት መግጠሜ አይቀርም:: ከርስዎም ጋር የሆነዉ ይሄዉ ነዉ::” ሲል አስገራሚዉን ያባቱን ታሪክ ተናገረ:: ግን በዚህ ዘመን እንዲህ አይነት አባቶች አሉ እንዴ የሚያስብል ነገር ነዉ::

እናም ሀይሉ ሻዉል ጠቅላላ ጉባዔዉ በተደረገበት ቀን አንድ አስገራሚ ነገር ተናገሩ ” እናንተ ይሄን ማሙሸትን አታቁትም:: እሱ የሚለዉ እዉነት ብቻ ትዉጣ ነዉ:: እንደ ፖለቲከኛ የሚያድበሰብሰዉ ነገር የለም:: የሚፈልገዉ እዉነቷን ብቻ ነዉ:: በአንደበቱ ሁለት ወይም አንድ ነገር አይናገርም:: አንድ ነገር ብቻ ይናገራል:: እሱም እዉነት ብቻ::”

የጠቅላላ ጉባዔዉ ተሰብሳቢ በአቶ ሀይሉ ንግግር እየተገረመ እያለ ድርጅቱን ለተወሰነ ጊዜ በፕሬዝዳንትነት የመሩት አቶ አበባዉ ደግሞ (ከማሙሸት ጋር ጸብ የነበሩ ናቸዉ) ብድግ ብለዉ ” አቶ ማሙሸት ድርጅትን በመክዳት ወይም በገንዘብ ወይም በሌላ በምንም መጥፎ ባህሪ አይታማም :: የሱ ችግር ሀይለኝነት ብቻ ነዉ:: ተጋፋጭ ነዉ:: እልህኛ ነዉ” ሲሉ ስለ ማሙሸት አማረ ያላቸዉን አመለካከት አካፈሉ::

እንግዲህ እነዚህና ከሌሎችም በርካታ ምንጮች የሰበሰብኋቸዉ መረጃዎችን ስተነትናቸዉ ማሙሸት አማረ አሁን በተረከበዉ የፕሬዝዳንትነት ሀላፊነት ቦታ ላይ የሚያሳካቸዉ በርካታ አዎንታዊ ጉዳዮች እንደሚኖሩ መገመት ይቻላል:: እንዲሁም የሚገጥሙት ተግዳሮቶች ቀላል የሚሆኑ አይመስለኝም::

እነዚህ አሉታዊና አዎንታዊ ፈተናዎች ከኢትዮጵያ ባህላዊ ጽንፍ ዉስጥ መንጭተዉ የሚዎጡ ጭብጦች ናቸዉ:: በኢትዮጵያ እዉነት ወዳዱ ሰዉ ፍጹም እዉነት ወዳድ ነዉ:: ሸፍጠኛዉ ደግሞ ጽንፈኛ ሸፍጠኛ ነዉ:: ፕሮፌሰር ሰባስኪ የተባለ የጣሊያን ፕሮፌሰር የኢትዮጵያ ታሪክ በፋሽስት ኢጣሊያ ወረራ ወቅት በሚለዉ መጽሀፉ (እምሻዉ አለማዬሁ ወደ አማርኛ ተርጉሞታል ) አንድ አስገራሚ መረጃን አካፍሎናል:: ጣሊያኖች ስለ ሀበሻ ስነ ልቦና ጥናት አደረጉ:: በርግጥ ጥናቱ ወታደራዊ ጥናት ስለነበረ ያተኮረዉ የሀበሻን ሰዉ ስነልቦና ከወታደራዊ ጭብጥ አንጽር የመተንተን ስራ ላይ ነበር::

እናም የጥናቱ ዉጤት አስገራሚ ነበር:: አጭር የጥናቱ ድምዳሜም ሀበሻ ጀግና ከሆነ ፍጹም ጀግና ነዉ:: ከአፍሪካ ምድር የጀርመንን ጦር ጠራርገህ ለማስወጣት ከፈለግህ ጀግኖቹን የሀብሻ ወታደሮችን መልምል:: ሆኖም ደግሞ አበሻ ፈሪ ከሆነም ፍጹም ፈሪና አድር ባይ ነዉ:: ስለዚህ ምልመላችን ለመለዬት ከባድ ጥንቃቄ ያስፈልገዋል የሚል ነበር::

ልክ እንደ ጣሊያኖቹ ጥናት ሁሉ ኢትዮጵያ ባህል ዉስጥ እዉነተኛ ሰዎች ሁለት አይነት ጽንፈ ላይ የተንጠለጠለ ቦታ አላቸዉ:: አንድኛዉ ማማቸዉ የጀግናና የተወዳጅነት ማማ ሲሆን ሁለተኛዉ ማማ ደግሞ የተጠላ ማማ ነዉ:: ገትጋታ ተብለዉ የመጠላታቸዉ እድልም የዚያኑ ያህል ሰፊ ነዉ::

ለዚህ እንግዲህ ብቸኛዉ መፍትሄ ሁል አቀፍ የሆነ የጋራ አመራር እንዲኖር ማድረግ እንዲሁም የተለያዩ ሀሳቦች የሚያንጸባርቁ ቡድኖችን ማበረታታት ወሳኝ ነዉ:: ማሙሸት አማረ ትልቁ የቤት ስራዉ የሚሆነዉም ይሄዉ ነዉ:: እርግጥ ነዉ ባዋቀረዉ ካቤኔ ዉስጥ አካታች ስራን እንደሰራ ብዙዎች መስክረዉለታል:: በተለያዩ ጎራ ተከፋፍለዉ የነበሩትን ልዩ ልዩ አመራሮች ሁሉ ጥሩ አድርጎ በካቢኔዉ ዉስጥ ማካተቱም ለወደፊት ሰፊ የሀሳብ ምንጭ ያለዉ አመራርን በድርጅቱ ዉስጥ እንዲፈጠር ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር እንዳሰበ እንዲሁም ሁሉም አካላት በትክክል እንዲታቀፉ መፈለጉን አመላካች ነዉ:: የሆነ ሆኖ ግን ወደፊትም ሰፊ መሰረት ላይ የቆመ ሰፊ ማህበረሰብን የሚያካትት የአመራር ሀይል የመመስረት ጠንካራ ጥረት የሚጠበቅበት ይመስለኛል::

ከዚህ በተጨማሪም ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር በትብብር የመስራት እና የላቀ ሀገራዊ የዲሞክራሲ እሴት ላይ መስራት ሌላዉ ትልቁ የቤት ስራዉ የሚሆን ጉዳይ ይሆናል:: በተለይም የኢትዮጵያ ሰዉ እፊት ጀምሮ ፓርቲዎች ወይ ተባበሩ አለዚያ ተሰባበሩ የሚለዉ አቋሙ ወደፊት እየጠነከረ እንደሚመጣ ይጠበቃል:: እናም መኢአድ ለዚህ የህዝብ የልብ ትርታ የሚሰጠዉ ምላሽ የማሙሸት አማረ ያመራር ብቃትን ከሚፈትኑ ጥቂት ጉዳዮች ዉስጥ አንዱ የሚሆን ይመስላል::

ሌሎች ፓርቲዎች ከመኢአድ ተሞክሮ ምን ሊቀስሙ ይገባል?
==============================
መኢአድ ለአራት አመታት በተለያዩ ቡድኖች ተከፋፍሎ የዳከረዉን መዳከር ከቶ እንዳይደገም ደግሞም እንዳይታሰብ ብለዉ ሌሎች ፓርቲዎች ተሞክሮ ሊሆናቸዉ የሚችል አስተምህሮት መርምረዉ ማዉጣት ያለባቸዉ ይመስለኛል:: እኛ ሀገር የፖለቲካ ትንታኔ ማድረግ: ከአንድ ሂደት ምን ተማርን ብሎ መወያዬት : ሀሳብ ለሀሳስብ ለመለዋወጥ መነሳሰት ፈጽሞ ባህላችን አይደለም:: በተለያዩ ፓርቲዎች ጥላ ስር ታቅፈዉ ያሉ ሀይሎች በተለይም አሁን በተለያዩ ብድኖች ተከፋፍለዉ ያሉ ሀይሎች ቁጭ ብለዉ ትንታኔ መስሪያ ግዜአቸዉ ይመስለኛል::

ህጋዊ መፈንቅለ ስልጣን ተደረገ ብሎ አንዱ ወገን ሲጮ አንድኛዉ ወገን አትንጫጫ ብሎ አፍ ለማሲያዝ ከመሄድ የመኢአድ ተሞክሮ ምን ይመስላል ብሎ መጠዬቅና መወያዬት ብልህነት ይመስለኛል:: ጠንካራ ዉይይትና ክርክር ሁሉንም የሀሳብ ልዩነቶች ባይፈታቸዉም ዲሞክራሲያዊ ከፍታ ላይ መዉጣት ግን ያስችላል:: ዲሞክራሲ ከፍታ ላይ የወጣ ሀይል ደግሞ ሀሳቦችን ዲሞክራሲያዊ በሆነ አካሄድ ወደ ጋራ ስምምነት ያመጣቸዋል:: ከመኢአድ መማር የሚቻለዉ ይሄን ነዉ::

በዚህ አጋጣሚ እግዚአብሄር በሰጠን ጥቂት የጽሁፍ ጸጋ ሀሳባችንን የምናካፍል ሁሉ በኢትዮጵያ ያለዉ የፖለቲካ ባህላዊ እሴት ያብብ ዘንድ እያንዳንዱ ወገን ወደ ዲሞክራሲ ከፍታ ይራመድ ዘንድ የምንጽፈዉ ጽሁፍ : የምንሰነዝረዉ ሀሳብ ዋጋ ያገኝ ዘንድ ለሚመለከተዉ ሁሉ እናሳስባን:: ሆኖም ማንንም አንማጸንም::

Image

-በሰሞኑ የሰራዊቱ ግምገማ የወያኔው መከላከያ ሰራዊቱ እንደ ደርግ ሰራዊት ሊበተን ይችላል ተባለ::
-በአዲስ አበባ የለውጥ ሃይሎች በመተባበር የሕዝባዊ እንቢተኝነት ጥሪዎችን ለማድረግ ዝግጅት ላይ ናቸው::
-በአስመራ አርብ ቀን ሰው አልባ ተቃውሞ ከቤት ባለመውጣት ሓርነት አርቢ የተሰኘ ንቅናቄ ተጀምሯል::
Minilik Salsawi

ላለፉት 23 አመታት በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ሕዝቦች ላይ ከፍተኛ የቀውስ ማእበል ያስከተሉት ሕዝቦቻቸን ለስደት እና ለእስር እንዲሁም ለሞት የዳረጉት የገደሉት የሻእቢያ እና ወያኔ መንግስታት እስከዛሬ ድረስ ተደጋግፈው እዚህ የደረሱ ቢሆንም ከአሁን በኋላ ያላቸው ሃይል እየተሟጠጠ ህዝባዊ እምቢተኝነት እና አመጽ እየተፈጠረባቸው በውስጣቸውም እየተቦጠቦጡ በመፍረክረክ ላይ እንደሚገኙ ታውቋል::

የሻእቢያ እና ወያኔ ባለስልጣናት በመጭው ጊዜ ማድረግ የሚገባቸውን ጉዳይ እየተገናኙ እንደሚወያዩ እና በመደጋገፍ ቀሪውን ጊዜያት በስልጣን ለመቀጠል የሚያደርጉት ሙከራ የለውጥ ሃይሎች ህዝቡን በማስተማር እያከሸፉባቸው መሆኑ ተሰምቷል::በዚህም መሰረት በአስመራ ሐርነተ አርቢ ወይንም የአርብ ነጻነት የተባለ የለውጥ ንቅናቄ የተጀመረ ሲሆን ከኤርትራውያን ዲያስፖራዎች ጋር በተቀናጀ መልኩ በአጭር ጊዜ ዉስጥ ንቅናቄው ትልቅ ዉጤት አምጥቶ በአስመራ ከተማ ኢሳያስን የሚቃወም ወረቀት በብዛት ሲበተን የደህንነት አባላትና ፖሊሶችም ወረቀቶችን ሳይሰበስቡ ጥሪው ሕዝቡ ዘንድ እንዲደርስ መተባበራቸው ታውቋል። እንዲሁም በአዲስ አበባ የሚገኙ ዋና ዋና ተቃዋሚ ፓርቲዎች ትንንሽ ፓርቲዎችን በትብብር በማቀፍ እንዲሁም በተናጠል በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የሃገሪቱ ከተሞች ታላላቅ ሰልፎችን እና ተቃውሞዎችን በማድረግ ህዝባዊ እምቢተኝነት እንዲፈጠር ዝግጅት እያደረጉ ሲሆን የኢትዮጵያውያን የዲያስፖራ የለውጥ ግብረሃይልም ከባዱን ሚና በመጫወት ትግሉ እንዲፋፋም አስታውጾ እያበረከተ ነው::

ይህ በእንዲህ እንዳለ ይህን ሰሞን በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ እየተደረገ ባለ ግምገማ ላይ የመከላከያ ሰራዊቱ የአሸባሪ ሃይሎችን መቆጣጠር ካልቻለ እጣው እንደ ደርግ ሰራዊት መበተን ነው ሲሉ የግምገማው መሪዎች መናገራቸው ታውቋል:: በምድር ጦር መምሪያ ስር ባሉ የሰራዊት ክፍሎች በተደረገ ግምገማ በሁሉም አደራሾች ይህ አይነት የመበታተን አደጋ እንዳለ በይፋ ተገልጿል::የአሸባሪ ሃይሎች የተባሉት በሃገሪቱ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና የዲያስፖራ ጽንፈኞች እንደሆኑ የተገለጸ ሲሆን የዲያስፖራ ጽንፈኞች በሃገር ቤት የሚገኙሃይሎችን በመርዳት አመጽ ሊቀሰቅሱ ሕገመንግስቱን ሊያፈርሱ ምናምን የሚል ዛቻ እና ሃይል የተቀላቀለበት መመሪያ ሲሰጥ የነበረ ሲሆን ከፍተኛ የጦር መኮንኖች የብሄራቸው ስም እየተጠራ እና እየተለየ ሲተቹ እና ሲገመገሙ እንደነበር ታውቋል::

የደቡብ ሱዳን ተፋላሚ ኃይላት ከድርጊታቸው ካልተቆጠቡ የምሥራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ-መንግስታት ባለሥልጣን በምህጻሩ ኢጋድ እንደሚቀጣቸው በድጋሚ አስጠነቀቀ። አስፈላጊ ከሆነም ኢጋድ ደቡብ ሱዳን ውስጥ ጣልቃ ሊገባ እንደሚችል ዝቷል። የደቡብ ሱዳን አማፂያን በበኩላቸው የደቡብ ሱዳን መንግስት ስምምነቱን ጥሶ ውጊያ ከፍቶብናል ሲሉ ከሰዋል።